ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ ክርስቶስ <<በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ>> ብለን እንድንጸልይ እንጂ ያስተማረን << #እመቤታችን ሆይ>> ብለን እንድንጸልይ አላስተማረንም። የተሰጠንም #መንፈስ #አባ #አባ ብለን የምንጮህበት #መንፈስ #ብቻ ነው እንጂ #እማ #እማ ብለን የምንጮህበት አይደለም [ሮሜ 8፥15]። <<ስምህ ይቀደስ>> እንድንል እንጂ << #ሰላምታ #ይገባሻል>> እንድንል <<በደላችንን ይቅር በለን>> እንጂ << #ይቅርታን #ለምኚልን ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን ዘንድ>> እንድንል አላስተማረንም። የሁለቱም #ጸሎቶች #አድራሻና #ፍሬ ነገራቸው #የሰማይና #የምድር #ርቀት ያክል ልዩነት ያላቸውና #የሚጣረሱ ናቸው።

▶️ ከክርስቶስ #ትምህርት ጋር ሌሎችንም <<የጸሎት መጻህፍት>> የተባሉትን ብናስተያያቸው
እንደ <<አንቀጸ ብርሃን መጽሀፍ>> << #ስምሽ #የተመሰገነ ነው>> እንድንል ሳይሆን <<ስምህ ይቀደስ>> እንድንል፤ እንደ <<ተአምረ ማርያም መጽሀፍ>> << #ድንግል ሆይ #ፈጥነሽ እንድትመጪ>> [43፥26] እንድንል ሳይሆን <<መንግስት ትምጣ>> ብለን የክርስቶስን #መንግስትህ መምጣት #በናፍቆት እንድንጠባበቅ፤ <<ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን>> በማለት የእርሱ #ሰማያዊ #ፍቃድ ብቻ በምድራችን እንዲሆን እንጂ እንደ ተአምረ ማርያም ጸሀፊ << #ፈቃድሽ #ይሁንልን ይደረግልን>> እንድንል አላስተማረንም [100 ፤ 29-32]። <<የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን>> በማለት #የዕለት #ኑሮአችንንም እንዲያቀናልን እንድንጸልይ እንጂ። እንደ <<መልክዓ ማርያም መጽሀፍ>> << #መጻህፍትሽ #የማዳን #እንጀራንና የተፈተነ #መድሀኒት መጠጥን ስለሚሰጡ #ሰላምታ ይገባል[ለእራኃትኪ]>> እንድንል አላስተማረንም። <<ኃጢአታችንን ይቅር በለን>> እንድንል እንጂ እንደ <<መልክዓ ማርያም>> ደራሲ << #ኃጢአታችንን #ይቅር #በይን[ለመዛርዕኪ]>> እንድንል አላስተማረንም። <<ከክፉ አድነን>> በማለት #ከክፉ እንዲያድነን ወደ #እግዚአብሔር እንድንጸልይ እንጂ << #ከአዳኝ #አውሬ #አድኝኝ>> [የዘውትር ጸሎት ሰላምለኪ] እንድንል አላስተማረንም። <<ኃይል ክብርም ምስጋናም ለዘላለም ድረስ ላንተ ይሁን>> እንድንል እንጂ እንደ <<ተአምረ ማርያምና እንደ ቅዳሴ ማርያም>> <<ድንግል ሆይ #ክብርና #ምስጋና #ለዘላለም ይገባሻል>> እንድንል አላስተማረንም። ስለሆነም ይህን #ከክርስቶስ #ትምህርት ጋር የሚጣረስ ትልቅ #ኑፋቄ ወደ #ቤተክርስቲያን ማስገባትና ማስተማር ታላቅ #በደልና #ኃጢአት ነው።

▶️ አንዳንድ #ሰዎች ደግሞ ይህን #ኑፋቄ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ለማስመሰል #ከሉቃስ ወንጌል 1፤ 28- ጀምሮ ያለውን ክፍል ይጠቅሳሉ።

በክፍሉ እንደሚነበበው ግን #መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል #ከእግዚአብሄር ዘንድ ተልኮ ወደ #ድንግል #ማርያም በመጣ ጊዜ በሚያስደንቅ #ሰላምታ ከተገናኘ ቡኃላ የተላከበትን ጉዳይ <<እግዚአብሔር #ከአንቺ ጋር ነው>> በማለት ስለሚወለደው ቅዱስ #የእግዚአብሄር #ልጅና #ስልጣን ላይ አተኩሮና #ሰፊ ጊዜ ወስዶ ሲያበስራት ልክ እንደ ማንኛውም ሰው ወደ #አንድ #ቤት ወይም #ከጓደኛው ጋር ሲገናኝ #አይነቱ ይለያል እንጂ #ሰላምታ መለዋወጥ በየትኛውም #ሀገር ያለና የተለመደ #ባህላዊ #ስርአት ስለሆነና በተለይም #በመንፈሳዊ ሰዎች ዘንድ ሲገናኙ #ሰላምታ መለዋወጥ #ልማድ ከመሆኑም ጭምር እንዲሁም #መጽሀፍ ቅዱሳዊ በመሆኑ [ማቴ 10፤ 12-13]። መለአኩ #ቅዱስ #ገብርኤልም ያደረገው ይኸንን ነው #ጸሎት እያቀረበ አለመሆኑን ማንም #ሰው አንብቦ #መረዳት የሚችለው ነገር ነው። #ማርያምም ለቀረበላት ሰላምታ <<ይህ #እንዴት ያለ #ሰላምታ ነው>> ብላ አሰበች እንጂ እንደ #ጸሎት #ተቀባይ ወይ እንደ #ጸሎት #ሰሚ ሆና አልቀረበችም [ሉቃ 1፥29]። ነገር ግን አንዳንዶች ይህን ክፍል በመጥቀስ #ማርያምን <<በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ #ሰላም #እልሻለው>> እንዲባል #አስተምረዋል ጽፈው አልፈዋልም ዛሬም #የሚያስተምሩ አልጠፉም።
▶️ በቅዱስ ገብርኤል #ሰላምታ #ሰላም እልሻለሁ የሚለውን #ቃል ራሱ ብናየው #የተሳሳተ #አባባልና #ያልተለመደ #ንግግር ነው። በሌላ አገላለጽ #ዩሐንስ #ለጋይዮስ #ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው #ሰላምታ [3ኛ ዩሀ 1፥15] #ጋይዮስ ሆይ #በዩሐንስ ሰላምታ #ሰላም እልሃለው እንደማለት ነው። ነገሩን #ግልጽ ለማድረግ አቶ #አበበ አቶ #ከበደ ቤት ገብቶ <<አቶ #ከበደ በአቶ #አበበ #ሰላምታ #ሰላም #እልሀለው>> ብሎ #ሰላምታ እንደመስጠት ያክል ነው። ይህም በማንኛውም #ህብረተሰብና #ክፍለዘመን ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው #ከጤናማው #የሰላምታ ሥነ-ሥርዓት የወጣ #አባባል ነው።

▶️ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል #ከእግዚአብሔር ዘንድ #መልዕክት አድርስ ተብሎ ወደ #ድንግል ማርያም በመምጣት ያደረገውን #ሰላምታ ተንተርሶ #አጼ #ዘረዓ #ያዕቆብ <<ይወድስዋ መላእክት - {መላዕክት ማርያምን ያመሰግኗታል}>> የሚል #ድርሰት ሲያዘጋጅ #የቦረናው #አባ #ጊዮርጊስ #ዘጋስጫ ደግሞ <<ተፈሥሒ ኦ ሙኃዘፍስሐ፤ የተድላና የደስታ መፍሰሻ ሆይ ደስ ይበልሽ መላእክት ብለዋታል[1]>> ብሏል። ነገር ግን ወደ #ማርያም ተልከው የመጡት #መላእክት ሳይሆኑ አንድ #መለአክ ነው። እርሱም ቅዱስ #ገብርኤል ሲሆን ንግግሩም #ከእግዚአብሄር ዘንድ እንደተላከ ማሳወቅና #ክርስቶስን ያለ #ወንድ #ዘር #በድንግልና እንደምትወልድ የሚገልጽ እንጂ የተለየ #ምስጋና ለመስጠትና #የተድላና #የደስታ #መፍሰሻ እንደነበረች ያሳሰበበት #ክፍል አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን #መልአኩ እርሱ ከመምጣቱ በፊት #ማርያምን #የሚያመሰግንበትም የተለየ #የሰራችው አንዳች ነገር የለም። ያም ሆኖ አንዳንዶች እንደሚያደርጉት #መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤልም ሆነ #ድንግል #ማርያም በነበራቸው የአጭር ጊዜ የመረዳዳት #ውይይትን እንደመደበኛ #የግል #ጸሎታቸው አድርገው #መጽሀፍ አዘጋጅተው የሚደግሙ አሉ። ነገር ግን እነርሱ ራሳቸው መልአኩ #ገብርኤልም ሆነ #ድንግል #ማርያም #ውይይት አደረጉ እንጂ #አንዱ #ለአንዱ ያቀረቡት #ጸሎት የለም። ንግግራቸውም #የዘውትር #ጸሎት እንዲሆንላቸው ያሳሰቡት ነገርም የለም።

▶️ ጌታ #ኢየሱስ ክርስቶስ የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደ #ሰማይ ሲያርግ #ድንግል #ማርያም ባለችበት #በማርቆስ #እናት ቤት ሐዋሪያት #በአንድነት #በጸሎት ሲተጉ አጠገባቸው ያለችውን #ማርያምን <<በገብርኤል #ሰላምታ ሰላም እንልሻለን #በነፍስሽም #በስጋሽም ድንግል ነሽ ከተወደደው #ልጅሽ #ይቅርታ #ለምኚልን #ኃጢአታችንን ያስተሰረይልን ዘንድ>> አሏሏትም፤ #የጸሎት #ማዕከላቸውም አልነበረችም። እርሷም እነርሱም በአንድነት << #የሁሉንም #ልብ የምታውቅ #ጌታ ሆይ>> እያሉ #ጌታን እያከበሩ ወደ #ጌታ ሲጸልዩ ነበር። በድንገት #መንፈስ ቅዱስም ለእሷም ለእነሱም #እኩል ያለልዩነት ወረደባቸው። [ሐዋ 1፤ 12-14፣ ሐዋ 2፤ 1-4]።

በተለይ ደግሞ << #ይቅርታን #ለምኚልን>> የሚለው #ቃል ጠቅላላውን #የክርስቶስን #ይቅርታ #ለሰው ልጆች እንዴት እንደተሰጠ አለማወቅና #የክርስቶስን #የደኅንነት #መስዋዕት #ከንቱ የሚያደርግ ነው። በመሆኑም ይህን #ጸሎት ማቅረብ #የጸሎትን #ትርጉም አለማወቅ ብቻ ሳይሆን በግልጽ #የክርስቶስ #ተቃዋሚ መሆን ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_____________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ "መጽሐፈ ሰዓታት" ገጽ 29።