#ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን በዐድዋ
____________________________
...የመጨረሻውና አስደማሚው ኩነት...
#ዳግማዊ_አፄ ምኒልክ ታቦተ ጊዮርጊስ በድንኳን ይዘው አድዋ ላይ ሰፍረው በነበረ ጊዜ ባንዳ የነበረ ሰው በኢትዮጵያ የጦር ሰፈር መሰላቸት እንዳለና ስንቅ እያለቀ መሆኑን ለኢጣሊያኖት እየሄደ ያወራ ነበር። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ይህን ወሬ በሰሙ ጊዜ በድንኳኑ ውስጥ የቅዱስ የጊዮርጊስ ታቦት የሚገለግለውን ካህን ጠርተው እንደ አባቶቼ ተዋግቼ እንድሞት እባክህን ጦርነቱን አስጀምረው ብለህ ንገርልኝ ሲሉ ይልኩታል።እርሱም እንደታዘዘው ያደርጋል።
ጦርነቱ ሲጀመር የኢትዮጲያ ወታደሮች በኢጣልያን ጦር ይጠቁ ጀመር ለዚህም ትልቁ ምክንያት ጀግንነታቸው ነበር ጣሊያኖች ምሽግ ይዘው ሲተኩሱ ጀግኖች አባቶቻችን ግን ምሽግ ውስጥ ተደብቆ መተኮስን እና ማጥቃትን እንደ ነውር በመቁጠር ደረታቸውን እየገለበጡ ፊት ለፊት ይዋጉ ስለነበር ነው ።በእውነቱ ይህ.ግሩም ድንቅ የሆነ ጀግንነት ነው!...
#እቴጌ_ጣይቱም ኢጣሊያ ይጠጣው የነበረውን የውኃ ጉድጓድ አስያዙት በዚህም ጣልያን ትንሽ ተዳከመ ሆኖም ሐበሻ መጠቃቱን አልቀረም ነበር ። ይህን የሐበሻን መጠቃት የተመለከተው የልዳው ሰማዕት ከእመቤታችን ጋር የገባውን ቃል ይፈጽም ዘንድ በነጭ አባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ መጥቶ ኢጣልያኖችን ፈጃቸው ድሉም የኢትዮጵያ ሆነ። ይህንንም በምርኮ የተያዙ የኢጣሊያ ጭፍሮች በአድናቆት ሆነው መስክረዋል።
በዚህም የድል ወቅት በጎጃም ዲማ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በፍሬም የተሰቀለ ትልቅ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ነበር:: ጠዋት የገዳሙ እማሆይ አቃቢ ግብረ ማህረዕ ለመፈጸም ይህን ሥዕል ሊሳለሙ ሲገቡ ሥዕሉን ከቦታው ያጡታል በኃላ ወደ ማታ ይህው ሥዕል እየበረረ መጥቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባ ያዩታል እማሆይም አቃቢም አባቴ ጊዮርጊስ የት ውለህ መምጣትህ ነው ? ቢሉት ጌታሽን " ምኒልክን ስረዳው ውዬ መምጣቴ ነው" ብሎ በስብአዊ ልሣን አናገራቸው።
#እማ_ሆይም ከሥዕሉ በጦርነቱ የኢትዮያን አሸናፊነት ተረድተው በዕልልታ አቀለጡት:: አፄ ምኒልክም ከድሉ ሲመለሱ ከደስታቸው የተነሳ በአዲስ አበባ ለሰማዕቱ ውለታ ይሆን ዘንድ ፒያሳ የሚገኘውን የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ሰሩለት::
ዋቢ:- ልሳነ ተዋህዶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ጥር ፪ ሺህ ፫ ዓ.ም ያሳተመው መጽሔት
................ይቆየን ...........
#የእግዚአብሔር_ቸርነት_የድንግል_ማርያም_አማላጅነት_የሰማዕቱ_የቅዱስ_ጊዮርጊስ_ጥበቃና_ረድኤት አይለየን!
" ዐውደ ምሕረት የእናንተ "
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/112544300256976/posts/277932900384781/?app=fbl
____________________________
...የመጨረሻውና አስደማሚው ኩነት...
#ዳግማዊ_አፄ ምኒልክ ታቦተ ጊዮርጊስ በድንኳን ይዘው አድዋ ላይ ሰፍረው በነበረ ጊዜ ባንዳ የነበረ ሰው በኢትዮጵያ የጦር ሰፈር መሰላቸት እንዳለና ስንቅ እያለቀ መሆኑን ለኢጣሊያኖት እየሄደ ያወራ ነበር። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ይህን ወሬ በሰሙ ጊዜ በድንኳኑ ውስጥ የቅዱስ የጊዮርጊስ ታቦት የሚገለግለውን ካህን ጠርተው እንደ አባቶቼ ተዋግቼ እንድሞት እባክህን ጦርነቱን አስጀምረው ብለህ ንገርልኝ ሲሉ ይልኩታል።እርሱም እንደታዘዘው ያደርጋል።
ጦርነቱ ሲጀመር የኢትዮጲያ ወታደሮች በኢጣልያን ጦር ይጠቁ ጀመር ለዚህም ትልቁ ምክንያት ጀግንነታቸው ነበር ጣሊያኖች ምሽግ ይዘው ሲተኩሱ ጀግኖች አባቶቻችን ግን ምሽግ ውስጥ ተደብቆ መተኮስን እና ማጥቃትን እንደ ነውር በመቁጠር ደረታቸውን እየገለበጡ ፊት ለፊት ይዋጉ ስለነበር ነው ።በእውነቱ ይህ.ግሩም ድንቅ የሆነ ጀግንነት ነው!...
#እቴጌ_ጣይቱም ኢጣሊያ ይጠጣው የነበረውን የውኃ ጉድጓድ አስያዙት በዚህም ጣልያን ትንሽ ተዳከመ ሆኖም ሐበሻ መጠቃቱን አልቀረም ነበር ። ይህን የሐበሻን መጠቃት የተመለከተው የልዳው ሰማዕት ከእመቤታችን ጋር የገባውን ቃል ይፈጽም ዘንድ በነጭ አባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ መጥቶ ኢጣልያኖችን ፈጃቸው ድሉም የኢትዮጵያ ሆነ። ይህንንም በምርኮ የተያዙ የኢጣሊያ ጭፍሮች በአድናቆት ሆነው መስክረዋል።
በዚህም የድል ወቅት በጎጃም ዲማ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በፍሬም የተሰቀለ ትልቅ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ነበር:: ጠዋት የገዳሙ እማሆይ አቃቢ ግብረ ማህረዕ ለመፈጸም ይህን ሥዕል ሊሳለሙ ሲገቡ ሥዕሉን ከቦታው ያጡታል በኃላ ወደ ማታ ይህው ሥዕል እየበረረ መጥቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባ ያዩታል እማሆይም አቃቢም አባቴ ጊዮርጊስ የት ውለህ መምጣትህ ነው ? ቢሉት ጌታሽን " ምኒልክን ስረዳው ውዬ መምጣቴ ነው" ብሎ በስብአዊ ልሣን አናገራቸው።
#እማ_ሆይም ከሥዕሉ በጦርነቱ የኢትዮያን አሸናፊነት ተረድተው በዕልልታ አቀለጡት:: አፄ ምኒልክም ከድሉ ሲመለሱ ከደስታቸው የተነሳ በአዲስ አበባ ለሰማዕቱ ውለታ ይሆን ዘንድ ፒያሳ የሚገኘውን የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ሰሩለት::
ዋቢ:- ልሳነ ተዋህዶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ጥር ፪ ሺህ ፫ ዓ.ም ያሳተመው መጽሔት
................ይቆየን ...........
#የእግዚአብሔር_ቸርነት_የድንግል_ማርያም_አማላጅነት_የሰማዕቱ_የቅዱስ_ጊዮርጊስ_ጥበቃና_ረድኤት አይለየን!
" ዐውደ ምሕረት የእናንተ "
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/112544300256976/posts/277932900384781/?app=fbl
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.