#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
የዚያን ቀን በሰላም ወደ ቤቴ የተመለስኩት ፈጣሪ ጠባቂ መላእክቱን ልኮ ጋርዶኝ መሆን አለበት፡፡ እንጅማ ያንን ተራራ የሚያህል ዱሩዬ እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ አድርጌ አበሻቅጨው እንኳን በሰላም መመለሴ በሕይዎት መመለሴም ተዓምር ነበር፤ ግን ሆነ፡፡
ልክ የማደንዘዣ መርፌ እንደወጉት ሰው እኮ ነው ፍዝዝ ብሎ ሲመለከተኝ የነበረው፡፡እንኳን እኔ፡ በዚያ ጋን ጋን በሚሸት ትንፋሹ እፍ ቢለኝ ሱሉልታ የምገኝ ላንጌሳ ቀርቶ፣መሣሪያ ለታጠቀ ፖሊስም የማይመለስ ጉድ ነው፡፡ የዛሬ ዓመት የፍርድ ቤት መጥሪያ
ሊሰጠው የሄደውን ፖሊስ እይደለም እንዴ ጆሮ ግንዱን በጥፊ እንድዶት፣ ከነመሣሪያው ካፈር የቀላቀለው?! ቆቡ አንድ ቦታ፣ የክላሽንኮቩ የጥይት መጋዘን ሌላ ቦታ ተበታትኖ፣ ለቃቅመው ነበር በቃሬዛ የወሰዱት፡፡ ማዕረጉ ሳይቀር ከትከሻው ላይ ተነቅሎ በርሮ ቱቦ
ውስጥ ነው የተገኘው፡፡ ምን እሱ ብቻ፤ጋሽ አለበልንስ ቢሆን እንዲህ ሁለት የፊት ጥርሱን በቡጢ አርግፍ፣ አፉን የጋራዥ በር አስመስሎ የቀረው ማን ነው? …ይኼው ወጠምሻ ዱርዩ ነው !!
የጋሽ አለበልን ጥርስ ለማውለቅ (ማውለቅማ ወግ ነው፤ አረገፈው እንጂ ምን እንዳነሳሳው ሲጠየቅ “በቀን አሥር ጊዜ ሰላም እያለ አስመርሮኝ ነው አለ አሉ: እስቲ ለግዜር ሰላምታ ቡጢ መመለስ ምን የሚሉት እብደት ነው? …ጋሽ አለበል፣ ሚስኪን የሦስት ልጆች አባት ነው፡፡ ጎረቤቱ ሁሉ “ሰላምታ ይብቃ ይከተት በጋሽ አለበል!” የሚልለት ሰላምተኛ … ታዲያ አንድ ቀን ለምሳ ወደቤቱ እየገባ፣ ይኼን ወመኔ መሃል
መንገድ ላይ ቁሞ ያገኘዋል። ባርኔጣውን ከራሱ ላይ አንስቶ ፣በአክብሮት ጎንበስ
በማላት፣ “ሰላም ዋልክ ብሎ አለፈ፤ ሰው መስሎት፡ አለፍ ከማለቱ ዱርየው እንደ
አንዳች ነገር ተወርውሮ፣ ከኋላው ኮሌታውን ጨምድዶ ከያዘ በኋላ፣ በዚያ የግንድ ጐማጅ በሚያከል እጁ በቡጢ ከመሬት ደባለቀው፡፡ ሚስኪኑ አለበል ጥቅልል ብሎ ወደቀና እንደ ትል እጥፍ ዘርጋ እያለ አፈር ላይ ተንፈራገጠ፡፡ በኋላ ነው ጥርሱም መርገፉን ያወቀው፡፡ ደግሞ አያፍሩም ሰው አግኝተው ሙተው ይኼን ዱርየ ስሙን ኢዮብ አሉት፡፡ ስም አይገዛ! “ስምን መላእክት ያወጡታል” ቢባልም ቅሉ፣ የአንዳንዱ ሰው ስም ሲወጣ፤ መላእከት በአካባቢው ዝር እንደማይሉ የገባኝ በዚህ ሰው ነው ፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ ኢዮብ ጌታን ተቀብያለሁ፤ ከአሁን በኋላ ወንጌል ሰባኪ ነኝ!" አለና መጽሐፍ ቅዱስ ይዞ እዚያቹ ሁልጊዜ የሚቀመጥባት ድንጋይ ላይ ተቀምጦ፣ አላፊ አግዳሚውን እያስቆመ፣ስብከት አይሉት ማስፈራሪያ ጀመረ፡፡(ሰው ነፍሱ ሲቀየር እንዴት
ወንበሩ አይቀየርምስ) ትተውት እይሄዱ ነገር ኢዮብ ሆነባቸው፡፡ ከሰማዩ እሳት በፊት የኢዮብ ቡጢ ትዝ እያላቸው ደግሞም ጋሽ አለበልን ያየ፣ ኢዮብን ከኋላው አድርጎ እንዴት በሰላም ይራመዳል ብለው ቁመው ይሰሙት ጀመረ፡፡ መቼስ ክርስቶስ ከተሰቀለ
ወዲህ፣ ወንጌልን እንዲህ አድርጎ የሰበከ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም! ድንገት አንዱ መንገደኛ ፊት መንገዱን ዘግቶ፣ እንደ ጅብራ ይገተርና የደፈረሰ ዓይኑን አፍጥጦ ኢየሱስ ጌታ ነው!" ሲል ማነው ወንዱ የሚቃወም?! ጋሽ ሐምዛ እንኳን ሳይቀሩ ለጁሙዓ ሶላት ወደ መስጅድ እየተጣደፉ ሲሄዱ መንገድ ላይ አስቆማቸውና…
“ጋሽ ሐምዛ!” አላቸው፡፡
ለብይካ !"
“ኢየሱስ ጌታ ነው!” ሲላቸው፣
እንግዲህ ከአንተ ጋር ስነዛነዝ ሶላት ከሚያመልጠኝ፣ ይሁና ኢዮብ ብለው ወደ
መስጅዳቸው!! ወዲያው አንድ ወር እንኳን ሳይቆይ፣ ይኼ ወጠምሻ ፓስተር ደብድቦ
ታስረ፡፡ “ለምን ፓስተር ደበደብከ?” ሲባል “ከፉ መንፈስ አለብህ ብሎኝ ነው!” አለ፡፡
ከእስር ሲፈታ መጽሓፍ ቅዱሱን ጣጥሎ ወደ መጠጥ ቤቱ ተመለሰ፡፡እንዳገረሽ ዱርየንት አደገኛ ነገር የለም፤ባሰበት! ዓምደ ሚካኤል የሚባለው የሰንበት ትምርት ቤት ኃላፊ ሳይቀር፣ “ከዚህስ ያንኑ የመናፍቅ ስብከት ቢሰብከን ይሻል ነበር!” እሰኪል ድረስ፡፡ ይሄው ሲጠግብና ሲሰከር አላፊ አግዳሚውን እየደበደበ፣ እጁ ላይ ሳንቲም ሲያጣ እየነጠቀ፤ቦዝኖ ተመችቶት ይኖራል፡፡ ይኼን ጉድ ነው እንግዲህ እንዳይሞት እንዳይሽር
አድርጌ በስድብ እጥረግርጌው በሰላም ወደቤቴ የተመለስኩት፡፡ ያውም እቤቱ ሂጄ እፈልግሃለሁ ና ውጣ " ብዬ፡፡ ምን አገናኛቸው?” የሚል አይጠፉ መቸስ ጎደሎ ቀን ነዋ።
ኢዮብ የባለቤቴ ታላቅ ወንድም ነው የመጀመሪያ ልጃችንን የወለድን ጊዜ እንደወጉ ቁርጥ አባቱን ከሚለው አራስ ጠያቂው ይልቅ “ኢዮቤ አጎት ሆነ!"ባዩ ይበዛ ነበር፡፡
ሰው የመናገር ነፃነትን የሚነፍገው አምባገነን መንግሥት ብቻ ይመስለዋል፤ በየመንደሩ ስንት ጥቃቅን አፋኝ አለ! አንድ ቀን ታዲያ ይኼ አፄ በጉልበቱ የማይታለፍ መስመር አለፈ- እንኳን እንድ የመንደር ዱርየ፣ ሞት ራሱ መጥቶ እፊቴ ቢቆም፣ የማልደራደርበትን ጉዳይ ደፈረ አበድኩ እግሮቼ እንደ እግር ሳይሆን እንደ ክንፍ አብርረው ወደቤቱ ወሰዱኝ፣ ያውም ከሥራ እንደወጣሁ ሙሉ ልብሴን ከነከረቫቴ ግጥም አድርጌ ለብሼ፡፡
ሰው አገሩ ሲነካበት አሮጌ ጠመንጃ አንስቶ ከሰማይ ከምድር ከገዘፈ ጠላት ጋር የሚፋመው፣ ከጀግንነት ይልቅ በፍቅር ተገፍቶ መሆኑን ያወቅሁት በዚያች ቀን ነው፡፡
ኢዮብን እየተንጠራራሁ እንባረኩበት…ማነኝ ነው የምትለው!? አልኩት …መንደር
ለመንደር እየዞርክ ማንንም ስላስፈራራህ የምፈራህ መሰለህ ወይ? አልኩት… ወይ እኔ፣ ወይ እንተ እንሞታለን እንጂ ፍርሃት የሚባል ነገር የለም አልኩት፡፡ ኢዮብ ቢጨንቀው ቡጢውንም፣ ጡጫውንም ረስቶ…የተወው ሃይማኖተኝነት አስታውሰና፣ “ኧረ ጌታ ይገፅስህ አለኝ :።በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜም አንድ እርምጃ ወደኋላ አፈገፈገ፡፡
እኔም ቀሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጠብና ድብድብ እንድ ርምጃ ወደፊት ተራመድኩ፡፡ከዚህ ሁሉ ጩህቴ በኋላ ግን የምለውም የምናገረውም አልቆብኝ፣ በእልህ እየተንቀጠቀጥኩ ማለት የቻልኩት “ምን አደረገቻችሁ ብቻ ነበር፡፡
ከሁለት ዓመት በፊት መደረግ የማይገባውን ነገር አደረግሁ፡፡ ጉዳዩን የሰማ ሰው ሁሉ “ተሳስተሃል? ይለኛል፡፡ መሳሳቴን ገና ድሮ ነው ያወቅሁት፡፡ ምክር ፈልጌ ስሄድ፣ ፍርድ አሸክመውኝ እመለሳለሁ፡፡ ከመምከር ይልቅ መፍረድ ቀላል ሳይሆን አይቀርም፡፡አገር ምድሩ እኔ ላይ ለመፍረድ የተሠየመ ችሎት እስኪመስል፣ እስትንፋስ ያለው ሁሉ
እኔ ላይ ፈረደ፡፡ እግዜር የፈጠረው ሳር ቅጠል ሁሉ ጠበቃና ዳኛ ሆነ፡፡ ነገሩ የጀመረው ከቤቴ ነው፣ ሚስቴ ሔራን ገና ከጅምሩ እኔ ላይ ፈረደች፡፡ “ምን ታድርግ፤እውነት አላት ብዬ ዝም አልኩ፡፡ቤተሰቦቼ እኔ ላይ ፈረዱ፡፡ያው መቼስ ለልጅ የሚወረወር ድንጋይ፣የወላጅን ልብ መውገሩ አይቀርምና፣ የወላጅ ፍቅራቸው ነው ያበሳጫቸው ብዬ ቻልኩ፡፡ እንዲያውም አባቴ ቁጣው ገንፍሎ እንዲህ አለኝ
ስማ ይኼን ነገር ወዲያ እልባት አበጅተህ ካላረፍከ፣ እደጄ እንዳትረግጥ፤ አባቴ
ብለህም እንዳትጠራኝ፣አልበዛም እንዴ? ከዛሬ ነገ ልጅነትህ ሲያልፍ ልብ ትገዛለህ
ብለን ዝም አልን፡፡ አንተ ጭራሽ እሰይ! የተባልክ ይመስል አድሮ ቃሪያ፣ ከርሞ ጥጃ ትሆናለህ፣ በዘራችን የሌለ መልከስከስ ከየት አመጣኸው!? ሌላው ይቅር፣ በሥራህ ቦታ ያለህበት ደረጃ ቀላል ነው እንዴ? እንዴት ለራስህ አክብሮት አይኖርህም!? በቃ ውስጤ
በአባቴ ተቀየመ … ከወላጆቼ ቤት ቀረሁ ፡
ጓደኞቼ እኔ ላይ ፈረዱ:: ሲጀመር ተው!" ብለው ሲመክሩኝ አልሰማኋቸውምና፣ ፍርድና ግፃፄያቸውን የሚገፋ ወኔ አልነበረኝም:: እንዲያውም የቅርብ የምላቸው ጓደኞቼ ቀስ እያሉ ከእኔ ራቁ፡፡ የሚስቴ ስሞታ ሰልችቷቸው መሆን
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
የዚያን ቀን በሰላም ወደ ቤቴ የተመለስኩት ፈጣሪ ጠባቂ መላእክቱን ልኮ ጋርዶኝ መሆን አለበት፡፡ እንጅማ ያንን ተራራ የሚያህል ዱሩዬ እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ አድርጌ አበሻቅጨው እንኳን በሰላም መመለሴ በሕይዎት መመለሴም ተዓምር ነበር፤ ግን ሆነ፡፡
ልክ የማደንዘዣ መርፌ እንደወጉት ሰው እኮ ነው ፍዝዝ ብሎ ሲመለከተኝ የነበረው፡፡እንኳን እኔ፡ በዚያ ጋን ጋን በሚሸት ትንፋሹ እፍ ቢለኝ ሱሉልታ የምገኝ ላንጌሳ ቀርቶ፣መሣሪያ ለታጠቀ ፖሊስም የማይመለስ ጉድ ነው፡፡ የዛሬ ዓመት የፍርድ ቤት መጥሪያ
ሊሰጠው የሄደውን ፖሊስ እይደለም እንዴ ጆሮ ግንዱን በጥፊ እንድዶት፣ ከነመሣሪያው ካፈር የቀላቀለው?! ቆቡ አንድ ቦታ፣ የክላሽንኮቩ የጥይት መጋዘን ሌላ ቦታ ተበታትኖ፣ ለቃቅመው ነበር በቃሬዛ የወሰዱት፡፡ ማዕረጉ ሳይቀር ከትከሻው ላይ ተነቅሎ በርሮ ቱቦ
ውስጥ ነው የተገኘው፡፡ ምን እሱ ብቻ፤ጋሽ አለበልንስ ቢሆን እንዲህ ሁለት የፊት ጥርሱን በቡጢ አርግፍ፣ አፉን የጋራዥ በር አስመስሎ የቀረው ማን ነው? …ይኼው ወጠምሻ ዱርዩ ነው !!
የጋሽ አለበልን ጥርስ ለማውለቅ (ማውለቅማ ወግ ነው፤ አረገፈው እንጂ ምን እንዳነሳሳው ሲጠየቅ “በቀን አሥር ጊዜ ሰላም እያለ አስመርሮኝ ነው አለ አሉ: እስቲ ለግዜር ሰላምታ ቡጢ መመለስ ምን የሚሉት እብደት ነው? …ጋሽ አለበል፣ ሚስኪን የሦስት ልጆች አባት ነው፡፡ ጎረቤቱ ሁሉ “ሰላምታ ይብቃ ይከተት በጋሽ አለበል!” የሚልለት ሰላምተኛ … ታዲያ አንድ ቀን ለምሳ ወደቤቱ እየገባ፣ ይኼን ወመኔ መሃል
መንገድ ላይ ቁሞ ያገኘዋል። ባርኔጣውን ከራሱ ላይ አንስቶ ፣በአክብሮት ጎንበስ
በማላት፣ “ሰላም ዋልክ ብሎ አለፈ፤ ሰው መስሎት፡ አለፍ ከማለቱ ዱርየው እንደ
አንዳች ነገር ተወርውሮ፣ ከኋላው ኮሌታውን ጨምድዶ ከያዘ በኋላ፣ በዚያ የግንድ ጐማጅ በሚያከል እጁ በቡጢ ከመሬት ደባለቀው፡፡ ሚስኪኑ አለበል ጥቅልል ብሎ ወደቀና እንደ ትል እጥፍ ዘርጋ እያለ አፈር ላይ ተንፈራገጠ፡፡ በኋላ ነው ጥርሱም መርገፉን ያወቀው፡፡ ደግሞ አያፍሩም ሰው አግኝተው ሙተው ይኼን ዱርየ ስሙን ኢዮብ አሉት፡፡ ስም አይገዛ! “ስምን መላእክት ያወጡታል” ቢባልም ቅሉ፣ የአንዳንዱ ሰው ስም ሲወጣ፤ መላእከት በአካባቢው ዝር እንደማይሉ የገባኝ በዚህ ሰው ነው ፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ ኢዮብ ጌታን ተቀብያለሁ፤ ከአሁን በኋላ ወንጌል ሰባኪ ነኝ!" አለና መጽሐፍ ቅዱስ ይዞ እዚያቹ ሁልጊዜ የሚቀመጥባት ድንጋይ ላይ ተቀምጦ፣ አላፊ አግዳሚውን እያስቆመ፣ስብከት አይሉት ማስፈራሪያ ጀመረ፡፡(ሰው ነፍሱ ሲቀየር እንዴት
ወንበሩ አይቀየርምስ) ትተውት እይሄዱ ነገር ኢዮብ ሆነባቸው፡፡ ከሰማዩ እሳት በፊት የኢዮብ ቡጢ ትዝ እያላቸው ደግሞም ጋሽ አለበልን ያየ፣ ኢዮብን ከኋላው አድርጎ እንዴት በሰላም ይራመዳል ብለው ቁመው ይሰሙት ጀመረ፡፡ መቼስ ክርስቶስ ከተሰቀለ
ወዲህ፣ ወንጌልን እንዲህ አድርጎ የሰበከ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም! ድንገት አንዱ መንገደኛ ፊት መንገዱን ዘግቶ፣ እንደ ጅብራ ይገተርና የደፈረሰ ዓይኑን አፍጥጦ ኢየሱስ ጌታ ነው!" ሲል ማነው ወንዱ የሚቃወም?! ጋሽ ሐምዛ እንኳን ሳይቀሩ ለጁሙዓ ሶላት ወደ መስጅድ እየተጣደፉ ሲሄዱ መንገድ ላይ አስቆማቸውና…
“ጋሽ ሐምዛ!” አላቸው፡፡
ለብይካ !"
“ኢየሱስ ጌታ ነው!” ሲላቸው፣
እንግዲህ ከአንተ ጋር ስነዛነዝ ሶላት ከሚያመልጠኝ፣ ይሁና ኢዮብ ብለው ወደ
መስጅዳቸው!! ወዲያው አንድ ወር እንኳን ሳይቆይ፣ ይኼ ወጠምሻ ፓስተር ደብድቦ
ታስረ፡፡ “ለምን ፓስተር ደበደብከ?” ሲባል “ከፉ መንፈስ አለብህ ብሎኝ ነው!” አለ፡፡
ከእስር ሲፈታ መጽሓፍ ቅዱሱን ጣጥሎ ወደ መጠጥ ቤቱ ተመለሰ፡፡እንዳገረሽ ዱርየንት አደገኛ ነገር የለም፤ባሰበት! ዓምደ ሚካኤል የሚባለው የሰንበት ትምርት ቤት ኃላፊ ሳይቀር፣ “ከዚህስ ያንኑ የመናፍቅ ስብከት ቢሰብከን ይሻል ነበር!” እሰኪል ድረስ፡፡ ይሄው ሲጠግብና ሲሰከር አላፊ አግዳሚውን እየደበደበ፣ እጁ ላይ ሳንቲም ሲያጣ እየነጠቀ፤ቦዝኖ ተመችቶት ይኖራል፡፡ ይኼን ጉድ ነው እንግዲህ እንዳይሞት እንዳይሽር
አድርጌ በስድብ እጥረግርጌው በሰላም ወደቤቴ የተመለስኩት፡፡ ያውም እቤቱ ሂጄ እፈልግሃለሁ ና ውጣ " ብዬ፡፡ ምን አገናኛቸው?” የሚል አይጠፉ መቸስ ጎደሎ ቀን ነዋ።
ኢዮብ የባለቤቴ ታላቅ ወንድም ነው የመጀመሪያ ልጃችንን የወለድን ጊዜ እንደወጉ ቁርጥ አባቱን ከሚለው አራስ ጠያቂው ይልቅ “ኢዮቤ አጎት ሆነ!"ባዩ ይበዛ ነበር፡፡
ሰው የመናገር ነፃነትን የሚነፍገው አምባገነን መንግሥት ብቻ ይመስለዋል፤ በየመንደሩ ስንት ጥቃቅን አፋኝ አለ! አንድ ቀን ታዲያ ይኼ አፄ በጉልበቱ የማይታለፍ መስመር አለፈ- እንኳን እንድ የመንደር ዱርየ፣ ሞት ራሱ መጥቶ እፊቴ ቢቆም፣ የማልደራደርበትን ጉዳይ ደፈረ አበድኩ እግሮቼ እንደ እግር ሳይሆን እንደ ክንፍ አብርረው ወደቤቱ ወሰዱኝ፣ ያውም ከሥራ እንደወጣሁ ሙሉ ልብሴን ከነከረቫቴ ግጥም አድርጌ ለብሼ፡፡
ሰው አገሩ ሲነካበት አሮጌ ጠመንጃ አንስቶ ከሰማይ ከምድር ከገዘፈ ጠላት ጋር የሚፋመው፣ ከጀግንነት ይልቅ በፍቅር ተገፍቶ መሆኑን ያወቅሁት በዚያች ቀን ነው፡፡
ኢዮብን እየተንጠራራሁ እንባረኩበት…ማነኝ ነው የምትለው!? አልኩት …መንደር
ለመንደር እየዞርክ ማንንም ስላስፈራራህ የምፈራህ መሰለህ ወይ? አልኩት… ወይ እኔ፣ ወይ እንተ እንሞታለን እንጂ ፍርሃት የሚባል ነገር የለም አልኩት፡፡ ኢዮብ ቢጨንቀው ቡጢውንም፣ ጡጫውንም ረስቶ…የተወው ሃይማኖተኝነት አስታውሰና፣ “ኧረ ጌታ ይገፅስህ አለኝ :።በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜም አንድ እርምጃ ወደኋላ አፈገፈገ፡፡
እኔም ቀሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጠብና ድብድብ እንድ ርምጃ ወደፊት ተራመድኩ፡፡ከዚህ ሁሉ ጩህቴ በኋላ ግን የምለውም የምናገረውም አልቆብኝ፣ በእልህ እየተንቀጠቀጥኩ ማለት የቻልኩት “ምን አደረገቻችሁ ብቻ ነበር፡፡
ከሁለት ዓመት በፊት መደረግ የማይገባውን ነገር አደረግሁ፡፡ ጉዳዩን የሰማ ሰው ሁሉ “ተሳስተሃል? ይለኛል፡፡ መሳሳቴን ገና ድሮ ነው ያወቅሁት፡፡ ምክር ፈልጌ ስሄድ፣ ፍርድ አሸክመውኝ እመለሳለሁ፡፡ ከመምከር ይልቅ መፍረድ ቀላል ሳይሆን አይቀርም፡፡አገር ምድሩ እኔ ላይ ለመፍረድ የተሠየመ ችሎት እስኪመስል፣ እስትንፋስ ያለው ሁሉ
እኔ ላይ ፈረደ፡፡ እግዜር የፈጠረው ሳር ቅጠል ሁሉ ጠበቃና ዳኛ ሆነ፡፡ ነገሩ የጀመረው ከቤቴ ነው፣ ሚስቴ ሔራን ገና ከጅምሩ እኔ ላይ ፈረደች፡፡ “ምን ታድርግ፤እውነት አላት ብዬ ዝም አልኩ፡፡ቤተሰቦቼ እኔ ላይ ፈረዱ፡፡ያው መቼስ ለልጅ የሚወረወር ድንጋይ፣የወላጅን ልብ መውገሩ አይቀርምና፣ የወላጅ ፍቅራቸው ነው ያበሳጫቸው ብዬ ቻልኩ፡፡ እንዲያውም አባቴ ቁጣው ገንፍሎ እንዲህ አለኝ
ስማ ይኼን ነገር ወዲያ እልባት አበጅተህ ካላረፍከ፣ እደጄ እንዳትረግጥ፤ አባቴ
ብለህም እንዳትጠራኝ፣አልበዛም እንዴ? ከዛሬ ነገ ልጅነትህ ሲያልፍ ልብ ትገዛለህ
ብለን ዝም አልን፡፡ አንተ ጭራሽ እሰይ! የተባልክ ይመስል አድሮ ቃሪያ፣ ከርሞ ጥጃ ትሆናለህ፣ በዘራችን የሌለ መልከስከስ ከየት አመጣኸው!? ሌላው ይቅር፣ በሥራህ ቦታ ያለህበት ደረጃ ቀላል ነው እንዴ? እንዴት ለራስህ አክብሮት አይኖርህም!? በቃ ውስጤ
በአባቴ ተቀየመ … ከወላጆቼ ቤት ቀረሁ ፡
ጓደኞቼ እኔ ላይ ፈረዱ:: ሲጀመር ተው!" ብለው ሲመክሩኝ አልሰማኋቸውምና፣ ፍርድና ግፃፄያቸውን የሚገፋ ወኔ አልነበረኝም:: እንዲያውም የቅርብ የምላቸው ጓደኞቼ ቀስ እያሉ ከእኔ ራቁ፡፡ የሚስቴ ስሞታ ሰልችቷቸው መሆን
👍3
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ፍቅር አለችኝ። ስጠራኝ እንዲህ ነው።
“ወይዬ" አልኩ፡፡ ያው የተለመደውን ተጠንቅቀህ ንዳ፡እና እንዳታመሽ” ምክር ነበር የጠበቅሁት፡፡
እስከ መቼ ነው ይችን ልጅ የምንረዳው? ምንድነው መጨረሻው? አትማርም፣
አትሠራም እሺ ይሁን መርዳት ካለብህ እርዳት፣ ለምን የሚያስፈልጋትን ነገር
አትልክላትም? በአካል መገናኘቱ ለምን አስፈለገ?” አለችኝ፡፡ ሐኑንን ከዛ በፊት “ይቺ ልጅ!” ብላ ጠርታት አታውቅም ነበር፡፡ ልለብስ ያዘጋጀሁትን ኮት እንዳንጠለጠልኩ በግርምት ዙሬ ተመለከትኳት፡፡ ፊቷ አይቼው የማላውቀው ምሬት ተጥለቅልቆ፣
ዓይኖቿን ከእኔ ላይ ዘወር አደረገች።
እንዴ! …ከምርሽ ነው?” ብየ ጠቅኋት ተገርሜ፡፡
ከምርሽ ነው ማለት ምን ማለት ነው? የግድ አፍ አውጥቼ መናገር ነበረብኝ?
“እንደ ሌሎች ሚስቶች መጨቃጨቅ ነበረብኝ”
እንደዚያ ማለቴ ሳይሆን " እና እንዴት ማለትህ ነው?…ምን ማለት ነው ከምርሽ ነው ወይ' ማለት ?…ልክ ተአምር ነገር እንደተናገርኩ፣ የምትገረመው ለምንድነው? ከዚህ በኋላ ባታገኛት ደስ ይለኛል፣በቃ! ሁሉም ነገር ልክ አለው፡፡ ሥራ መሥራት ካለባት ትስራ ! ማግባት ካለባትም አንዱን ታግባ!" ንግግሯ ምሬት የተቀላቀለስት፣ ከጥያቄ ይልቅ ወደ ትእዛዝ ያዘነበለ ነበር፡፡ ያነሳሁትን ኮት ሶፋው መደገፊያ ላይ ጣል አድርጌ፤ ከተቀመጠችበት ሶፋ ፊት ለፊ ያለ
ክብ የመስተዋት ጠረጴዛ ጫፍ ላይ፤ ፊት ለፊቷ ተቀመጥኩ፡፡ ጉልበታችን ሲነካካ፣
እግሯን ወደኋላ ሰብሰብ አደረገች! በውስጤ፣ “በእርግዝናና በወሊድ ወቅት የሴቶች ሆርሞን መጠነኛ የባሕሪ ለውጥ እንደሚያስከትል” ያነበብኩትን እያሰብኩ ላረጋጋት ሐሳብ ሳሰባስብ፣ ልክ ያሰብኩትን ቀድማ ያወቀችዉ ይመስል(አውቀችው እንጂ)
“ምን እንደምታስብ ይገባኛል፤ሆርሞን ምናምን ብለህ ልታጽናናኝ እንዳትሞከረ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ እዚያው ስለ ወንድነትህ ሆርሞንህ እስብ:: በየትኛውም ሎጅክ ቢሆን እያደረከው ያለው ነገር ልክ አይደለም፡፡በቃ! ቤተሰብ ቀልድ አይደለም! ትዳር ነው ይኼን!” ግራ ገባኝ ፤ሐኑን በራሷ በባለቤቴ ጥሪ፣ በሰርጋችን ዕለት አብራን ነበረች ቤታችን ውስጥ ዝግጅት ሲኖር፡ ባለቤቴ እየጠራቻት ስትመጣና በደስታውም በሐዘኑም አብራን ስታሳልፍ ቆይታለች፡፡በእርግጥ ሐኑን ከባለቤቴ ጋር ባትገናኝ ደስ ይለኝ ነበር:ምክንያቱም ለሳር ቅጠሉ ትሁትና የሚመች ፀባይ ያላት ባለቤቴ ሔራን፣ ሐኑን ላይ ሲሆን ትንሽ የሚጫን ባሕሪ አላት። ለእኔ ብቻ የሚገባ ሲበዛ ውስብስብ የሆነ ባህሪ ነው፡፡ ግን አንዴ
ከተዋወቁ በኋላ ባለቤቴ ራሷ እየደወለች፣ በአካልም እያገኘቻት፡ ልክ እንደጓደኛ
ስለተቀራረቡ ምንም ማድረግ አልቻልኩም ፡፡ብናገርም ሌላ ጥርጣሬ መፍጠር ነው ብየ
ዝም አልኩ፡፡ ቢሆም ግን፣ የባለቤቴና የሐኑን ጓደኝነት መቼም ቢሆን ተውጦልኝ
አያውቅም እሳትና ጭድ፡፡
ቆይ! እስከዛሬ እምነሽበት የተቀበልሽውን ነገር ዛሬ…”
አምነሽበት? ምኑን ነው
የማምንበት? እንዴት ነው የምታስበው? በዚህ በሠለጠነ ክፍለ ዘመን ባሌ
እንደድሮ ሰው በትዳሩ ላይ ቅምጥ ማስቀመጡን ነው የማምንበት? ይኼን ነው የማምንበት? በቃ ከዚህ በኋላ ይኼ ነገር መቀጠል የለበትም፡፡ የባንክ አካውንት ከፍተህም ቢሆን የምትፈልገውን ብር አስገባላት፡፡ እያወጣች ትጠቀም፣ጤነኛ ናት፤
እየሄድክ ሰማንያ አታርሳትም:: እንደውም እንደሴቶቹ ሂዳ ትስራ አረብ አገር
የሚልኩ ሰዎኝ ጋር ላገናኛት እችላለሁ! ከዚህ በኋላ በምንም መንገድ ከእሷ ጋር
እንድትገናኝ ከልፈልግም :: ሁሉም ነገር ልክ አለው በቃ”
ጩህቷ እና ቃል አባይነቷ ግልፍ አደረገኝ እናም ሶሬ አልችልም!" አልኳት፡፡
ምን ማለት ነው አልችልም? ይሄኮ ጥያቄ ወይም አስተያየት አይደለም፡ ሕጋዊ ባለቤትህ። ነኝ! ሳንጋባ በፊት ስለነበረው ነገር እይመለከተኝም፣ ከተጋባን በኋላ ግን አያገባሽም እያልክ ብቻህን መወሰን ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው የበፊት ፍቅረኛህን አዲስ አበባ ድረስ አምጥተህ ቤት ተከራይተህ ማኖርህን እሽ ይሁን ብዬ ተቀበልኩ፣ በየወሩ ገንዘብ ተቆራጭ ማድረግህንም ይሁን ብዬ ፈቀድኩ፤ ይሄን ሁሉ የተቀበልኩት መብትህ ስለነበረ
እይደለም. ከራስሀ እንዲመጣ ስለፈለኩ እንጅ! ጭራሽ በየጊዜው እቤቷ እየሄድክ
መዋልና ማምሸትሆን አቁም ስላልኩህ፣ እፍህን ሞልተህ አልችልም ትለኛለህ እንዴ? እኔን ብትንቅ እንኳን፣ ለልጅህ ስትል ትዳርህን አታከብርም!? ብላ፣ ቤቱ እስኪናወጥ ጮኸት፡፡ ገና የሁለት ወር ልጅ ምነው ተወልዶ ሰበብ ላደረኩት ብላ በጉጉት የጠበቀችው ነው የሚመስለው፡፡ “ልጅህ” ስትል፣ አቅፋ ጡት የምታጠባውን ልጅ ስለናጠችው፣ መጥባቱን አቁሞ ጭርር ብሎ አለቀሰ: ለማጥባት ሳይሆን አፉን ለማዘጋት
በሚመስል ሁኔታ የጡቷን ጫፍ አፉ ውስጥ በእልህ ወተፈችበት ሲያለቅስ ወደውስጥ የሳበውን አየር እንኳን ሳያወጣው አጉረምርሞ ዝም አለ፡፡ አፍና የገደለችው ነበር የመሰለኝ፡፡ ማመን አልቻልኩም፡፡ ይኼን የተናገረችው ባለቤቴ ሔራን ናት ብዬ መቀበል ተሳነኝ።
ዝም ብዬ አየኋት! ዙሪያዋን የተዝረከረከውን ማቀፊያ ልብስ፣ጡጦ እና ምናምን ሁሉ በቁጣ በታትናው ልጃችንን አቅፋ እያለቀሰች ወደ መኝታ ቤት ገባችና የቤቱ መሠረት እስኪነቃነቅ ቀሩን በእግሯ ወደኋላዋ ወርውራ ዘጋችው፡፡ጓ...ሳሎን መሃል ተገትሬ
ቤቱን ቃኘሁት፡ችግር ችግር ሸተተኝ፡፡ አደጋ አደጋ፡፡ ቤታችን ከግድግዳ ሳይሆን ከአራት ቋሚ ችግሮች የተሠራ የመብረቅ ጣሪያ ከላይ የተደፋበት መሰለኝ፡፡ የዘራሁት ኃጢያት ማቆጥቆጥ እንደጀመረ ገባኝ፡፡ ለመሆኑ ሐኑን ብር በባንክ ብልክላትና ሁለተኛ አልመጣም ብላት (አልላትም እንጂ ) ምን ይሰማት ይሆን? ሐኑን…. ሐኑን ሐኑን ሐኑን …የቀጠፍኳት አበባ መዓዛዎ አስክሮኝ ውበቷ አስክሮኝ ጨብጫት ኖሬ ወደቀልቤ
ስመለስ እና የጨበጥኩበትን መዳፌን ስዘረጋ፣ እፍኝ ሙሉ እሾህ ተሰከስኮባት፣ ያውም የሚያንገበግብ እና የሚመረቅዝ ቁስል ፈጥሮ አገኘሁት፡፡ አላርፍ ያለ መዳፍ ፡፡
ከስድስት ዓመት በፊት የምሠራበት ባንክ ወደ ድሬደዋ መድቦ ሲልከኝ፡ግማሽ ልቤ አዲስ በተሰጠኝ እድገት እና ደመወዝ ሲደሰት፣ ግማሽ ልቤ ደግሞ ከአዲስ አበባ በመራቄ ደብቶት ነበር፡፡ ባየሁት ቁጥር የዓለም መጨረሻ የደረሰ የሚመስለኝ ችኩል ሥራ አሰኪያጅ ወደ ቢሮው ጠራኝና እንዲህ ሲል መርዶ ይሁን የምሥራች ግራ ያጋባኝን ዱብ ዕዳ አፈረጠው፡፡
እ..ያው እንደሚታወቀው፣ አዲስ አበባና ወደዚህ ወደ ሰሜኑ ያሉ ቅርንጫፎቻትን
ሥራችንን ካሰብነው በላይ እያስኬዱልን ነው፡፡ ይሁንና፣ ድሬዳዋ የከፈትነው ቅርንጫፍ በየዓመቱ ችግር ብቻ ነው የሚያተርፈው፤ ሰውየውም ከሠራተኞቹ ጋር መግባባት አልቻለም፣ እና ማኔጅመንቱ ትላንት በነበረው ስብሰባ፣ ጉዳዩ ላይ በስፋት ተነጋግሮበት አንድ ውሳኔ አሳልፏል” ካለ በኋላ የስልኩን እጀታ አንስቶ ወደ እኔ እየተመለከተ፣
“ምን ይምጣልህ?” አለኝ :
“ምንም እልፈልግም” አልኩ በአክብሮት፡፡ እኔ እንደሆንኩ ለወሬው ነበር የቸኮልኩት
ኃላፊየ ግን ያልኩትን ወደጎን ትቶ፣ “ሁለት ቡና አምጡልን!” ብሎ አዘዘና ወደጉዳዩ ገባ፡፡በረዥሙ ስለሁኔታው ሲያብራራ ቆይቶ
እና እንደነገርኩህ ማኔጅመንቱ ድሬደዋ ላለው ቅርንጫፍ ቢሮ መፍትሔ ብሎ ያሰለው፤እዛ ያለውን ሰው በማንሳት፣ ጠንካራና ኮሚትድ የሆነ ሥራ አስኪያጅ መመደብ ነው::ለቦታው የሚመጥን ሰው ስናነሳና ስንጥል ቆይተን ….በመጨረሻ…”
ቡና እንድታመጣ የታዘዘችው ልጅ ድንገት በሩን ከፍታ ገባችና ቡናውን በየፊታችን
አቅርባልን ወጣች፡፡ ምንም አልፈልግም ያልኩት ሰውዬ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ፍቅር አለችኝ። ስጠራኝ እንዲህ ነው።
“ወይዬ" አልኩ፡፡ ያው የተለመደውን ተጠንቅቀህ ንዳ፡እና እንዳታመሽ” ምክር ነበር የጠበቅሁት፡፡
እስከ መቼ ነው ይችን ልጅ የምንረዳው? ምንድነው መጨረሻው? አትማርም፣
አትሠራም እሺ ይሁን መርዳት ካለብህ እርዳት፣ ለምን የሚያስፈልጋትን ነገር
አትልክላትም? በአካል መገናኘቱ ለምን አስፈለገ?” አለችኝ፡፡ ሐኑንን ከዛ በፊት “ይቺ ልጅ!” ብላ ጠርታት አታውቅም ነበር፡፡ ልለብስ ያዘጋጀሁትን ኮት እንዳንጠለጠልኩ በግርምት ዙሬ ተመለከትኳት፡፡ ፊቷ አይቼው የማላውቀው ምሬት ተጥለቅልቆ፣
ዓይኖቿን ከእኔ ላይ ዘወር አደረገች።
እንዴ! …ከምርሽ ነው?” ብየ ጠቅኋት ተገርሜ፡፡
ከምርሽ ነው ማለት ምን ማለት ነው? የግድ አፍ አውጥቼ መናገር ነበረብኝ?
“እንደ ሌሎች ሚስቶች መጨቃጨቅ ነበረብኝ”
እንደዚያ ማለቴ ሳይሆን " እና እንዴት ማለትህ ነው?…ምን ማለት ነው ከምርሽ ነው ወይ' ማለት ?…ልክ ተአምር ነገር እንደተናገርኩ፣ የምትገረመው ለምንድነው? ከዚህ በኋላ ባታገኛት ደስ ይለኛል፣በቃ! ሁሉም ነገር ልክ አለው፡፡ ሥራ መሥራት ካለባት ትስራ ! ማግባት ካለባትም አንዱን ታግባ!" ንግግሯ ምሬት የተቀላቀለስት፣ ከጥያቄ ይልቅ ወደ ትእዛዝ ያዘነበለ ነበር፡፡ ያነሳሁትን ኮት ሶፋው መደገፊያ ላይ ጣል አድርጌ፤ ከተቀመጠችበት ሶፋ ፊት ለፊ ያለ
ክብ የመስተዋት ጠረጴዛ ጫፍ ላይ፤ ፊት ለፊቷ ተቀመጥኩ፡፡ ጉልበታችን ሲነካካ፣
እግሯን ወደኋላ ሰብሰብ አደረገች! በውስጤ፣ “በእርግዝናና በወሊድ ወቅት የሴቶች ሆርሞን መጠነኛ የባሕሪ ለውጥ እንደሚያስከትል” ያነበብኩትን እያሰብኩ ላረጋጋት ሐሳብ ሳሰባስብ፣ ልክ ያሰብኩትን ቀድማ ያወቀችዉ ይመስል(አውቀችው እንጂ)
“ምን እንደምታስብ ይገባኛል፤ሆርሞን ምናምን ብለህ ልታጽናናኝ እንዳትሞከረ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ እዚያው ስለ ወንድነትህ ሆርሞንህ እስብ:: በየትኛውም ሎጅክ ቢሆን እያደረከው ያለው ነገር ልክ አይደለም፡፡በቃ! ቤተሰብ ቀልድ አይደለም! ትዳር ነው ይኼን!” ግራ ገባኝ ፤ሐኑን በራሷ በባለቤቴ ጥሪ፣ በሰርጋችን ዕለት አብራን ነበረች ቤታችን ውስጥ ዝግጅት ሲኖር፡ ባለቤቴ እየጠራቻት ስትመጣና በደስታውም በሐዘኑም አብራን ስታሳልፍ ቆይታለች፡፡በእርግጥ ሐኑን ከባለቤቴ ጋር ባትገናኝ ደስ ይለኝ ነበር:ምክንያቱም ለሳር ቅጠሉ ትሁትና የሚመች ፀባይ ያላት ባለቤቴ ሔራን፣ ሐኑን ላይ ሲሆን ትንሽ የሚጫን ባሕሪ አላት። ለእኔ ብቻ የሚገባ ሲበዛ ውስብስብ የሆነ ባህሪ ነው፡፡ ግን አንዴ
ከተዋወቁ በኋላ ባለቤቴ ራሷ እየደወለች፣ በአካልም እያገኘቻት፡ ልክ እንደጓደኛ
ስለተቀራረቡ ምንም ማድረግ አልቻልኩም ፡፡ብናገርም ሌላ ጥርጣሬ መፍጠር ነው ብየ
ዝም አልኩ፡፡ ቢሆም ግን፣ የባለቤቴና የሐኑን ጓደኝነት መቼም ቢሆን ተውጦልኝ
አያውቅም እሳትና ጭድ፡፡
ቆይ! እስከዛሬ እምነሽበት የተቀበልሽውን ነገር ዛሬ…”
አምነሽበት? ምኑን ነው
የማምንበት? እንዴት ነው የምታስበው? በዚህ በሠለጠነ ክፍለ ዘመን ባሌ
እንደድሮ ሰው በትዳሩ ላይ ቅምጥ ማስቀመጡን ነው የማምንበት? ይኼን ነው የማምንበት? በቃ ከዚህ በኋላ ይኼ ነገር መቀጠል የለበትም፡፡ የባንክ አካውንት ከፍተህም ቢሆን የምትፈልገውን ብር አስገባላት፡፡ እያወጣች ትጠቀም፣ጤነኛ ናት፤
እየሄድክ ሰማንያ አታርሳትም:: እንደውም እንደሴቶቹ ሂዳ ትስራ አረብ አገር
የሚልኩ ሰዎኝ ጋር ላገናኛት እችላለሁ! ከዚህ በኋላ በምንም መንገድ ከእሷ ጋር
እንድትገናኝ ከልፈልግም :: ሁሉም ነገር ልክ አለው በቃ”
ጩህቷ እና ቃል አባይነቷ ግልፍ አደረገኝ እናም ሶሬ አልችልም!" አልኳት፡፡
ምን ማለት ነው አልችልም? ይሄኮ ጥያቄ ወይም አስተያየት አይደለም፡ ሕጋዊ ባለቤትህ። ነኝ! ሳንጋባ በፊት ስለነበረው ነገር እይመለከተኝም፣ ከተጋባን በኋላ ግን አያገባሽም እያልክ ብቻህን መወሰን ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው የበፊት ፍቅረኛህን አዲስ አበባ ድረስ አምጥተህ ቤት ተከራይተህ ማኖርህን እሽ ይሁን ብዬ ተቀበልኩ፣ በየወሩ ገንዘብ ተቆራጭ ማድረግህንም ይሁን ብዬ ፈቀድኩ፤ ይሄን ሁሉ የተቀበልኩት መብትህ ስለነበረ
እይደለም. ከራስሀ እንዲመጣ ስለፈለኩ እንጅ! ጭራሽ በየጊዜው እቤቷ እየሄድክ
መዋልና ማምሸትሆን አቁም ስላልኩህ፣ እፍህን ሞልተህ አልችልም ትለኛለህ እንዴ? እኔን ብትንቅ እንኳን፣ ለልጅህ ስትል ትዳርህን አታከብርም!? ብላ፣ ቤቱ እስኪናወጥ ጮኸት፡፡ ገና የሁለት ወር ልጅ ምነው ተወልዶ ሰበብ ላደረኩት ብላ በጉጉት የጠበቀችው ነው የሚመስለው፡፡ “ልጅህ” ስትል፣ አቅፋ ጡት የምታጠባውን ልጅ ስለናጠችው፣ መጥባቱን አቁሞ ጭርር ብሎ አለቀሰ: ለማጥባት ሳይሆን አፉን ለማዘጋት
በሚመስል ሁኔታ የጡቷን ጫፍ አፉ ውስጥ በእልህ ወተፈችበት ሲያለቅስ ወደውስጥ የሳበውን አየር እንኳን ሳያወጣው አጉረምርሞ ዝም አለ፡፡ አፍና የገደለችው ነበር የመሰለኝ፡፡ ማመን አልቻልኩም፡፡ ይኼን የተናገረችው ባለቤቴ ሔራን ናት ብዬ መቀበል ተሳነኝ።
ዝም ብዬ አየኋት! ዙሪያዋን የተዝረከረከውን ማቀፊያ ልብስ፣ጡጦ እና ምናምን ሁሉ በቁጣ በታትናው ልጃችንን አቅፋ እያለቀሰች ወደ መኝታ ቤት ገባችና የቤቱ መሠረት እስኪነቃነቅ ቀሩን በእግሯ ወደኋላዋ ወርውራ ዘጋችው፡፡ጓ...ሳሎን መሃል ተገትሬ
ቤቱን ቃኘሁት፡ችግር ችግር ሸተተኝ፡፡ አደጋ አደጋ፡፡ ቤታችን ከግድግዳ ሳይሆን ከአራት ቋሚ ችግሮች የተሠራ የመብረቅ ጣሪያ ከላይ የተደፋበት መሰለኝ፡፡ የዘራሁት ኃጢያት ማቆጥቆጥ እንደጀመረ ገባኝ፡፡ ለመሆኑ ሐኑን ብር በባንክ ብልክላትና ሁለተኛ አልመጣም ብላት (አልላትም እንጂ ) ምን ይሰማት ይሆን? ሐኑን…. ሐኑን ሐኑን ሐኑን …የቀጠፍኳት አበባ መዓዛዎ አስክሮኝ ውበቷ አስክሮኝ ጨብጫት ኖሬ ወደቀልቤ
ስመለስ እና የጨበጥኩበትን መዳፌን ስዘረጋ፣ እፍኝ ሙሉ እሾህ ተሰከስኮባት፣ ያውም የሚያንገበግብ እና የሚመረቅዝ ቁስል ፈጥሮ አገኘሁት፡፡ አላርፍ ያለ መዳፍ ፡፡
ከስድስት ዓመት በፊት የምሠራበት ባንክ ወደ ድሬደዋ መድቦ ሲልከኝ፡ግማሽ ልቤ አዲስ በተሰጠኝ እድገት እና ደመወዝ ሲደሰት፣ ግማሽ ልቤ ደግሞ ከአዲስ አበባ በመራቄ ደብቶት ነበር፡፡ ባየሁት ቁጥር የዓለም መጨረሻ የደረሰ የሚመስለኝ ችኩል ሥራ አሰኪያጅ ወደ ቢሮው ጠራኝና እንዲህ ሲል መርዶ ይሁን የምሥራች ግራ ያጋባኝን ዱብ ዕዳ አፈረጠው፡፡
እ..ያው እንደሚታወቀው፣ አዲስ አበባና ወደዚህ ወደ ሰሜኑ ያሉ ቅርንጫፎቻትን
ሥራችንን ካሰብነው በላይ እያስኬዱልን ነው፡፡ ይሁንና፣ ድሬዳዋ የከፈትነው ቅርንጫፍ በየዓመቱ ችግር ብቻ ነው የሚያተርፈው፤ ሰውየውም ከሠራተኞቹ ጋር መግባባት አልቻለም፣ እና ማኔጅመንቱ ትላንት በነበረው ስብሰባ፣ ጉዳዩ ላይ በስፋት ተነጋግሮበት አንድ ውሳኔ አሳልፏል” ካለ በኋላ የስልኩን እጀታ አንስቶ ወደ እኔ እየተመለከተ፣
“ምን ይምጣልህ?” አለኝ :
“ምንም እልፈልግም” አልኩ በአክብሮት፡፡ እኔ እንደሆንኩ ለወሬው ነበር የቸኮልኩት
ኃላፊየ ግን ያልኩትን ወደጎን ትቶ፣ “ሁለት ቡና አምጡልን!” ብሎ አዘዘና ወደጉዳዩ ገባ፡፡በረዥሙ ስለሁኔታው ሲያብራራ ቆይቶ
እና እንደነገርኩህ ማኔጅመንቱ ድሬደዋ ላለው ቅርንጫፍ ቢሮ መፍትሔ ብሎ ያሰለው፤እዛ ያለውን ሰው በማንሳት፣ ጠንካራና ኮሚትድ የሆነ ሥራ አስኪያጅ መመደብ ነው::ለቦታው የሚመጥን ሰው ስናነሳና ስንጥል ቆይተን ….በመጨረሻ…”
ቡና እንድታመጣ የታዘዘችው ልጅ ድንገት በሩን ከፍታ ገባችና ቡናውን በየፊታችን
አቅርባልን ወጣች፡፡ ምንም አልፈልግም ያልኩት ሰውዬ
❤1👍1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ድሬዳዋ ግሪክ ሰፈር የሚባል ሰፊ የሀብታም ግቢ ውስጥ፣ የራሱ ገላ መታጠቢያ ከፍልና፣ መጸዳጃ ቤት ያለው ባለ ሁለት ክፍል ቤት ከነዕቃው ተዘጋጅቶልኝ ነበር፡፡ ቤቱ የአንድ ባለሀብት ቤት ሲሆን፡ የምሠራበት ባንክ የተከራየው ሕንፃ ጭምር የሰውዬው ነበር፡፡ እንዲሁ ስጠረጥር ባለሀብቱ ቤታቸውን ያከራዩት፣የኪራይ ብር አስጨንቋቸው
ሳይሆን፤ሕንፃቸውን ተከራይቶ በየዓመቱ ጠቀም ያለ ብር የሚከፍላቸውን ባንክ ሥራ አስኪያጅ፣ ቤተኛ ለማድረግ ይመስለኛል፡፡ “ባለቤቱ ይኼ ናቸው” ቢሉኝ ገረመኝ፡፡
ሽርጥ ያገለደሙ ተራ ሰንደል ጫማ ያጠለቁ፣ ከጉያቸው ሥር ምንጊዜም በላስቲክ የተጠቀለለ ጫት የማይጠፉ፣ ጺማቸው በርስሬ መስሎ የቀላ ሽማግሌ፤ የዚያ ሁሉ ሀብት ባለቤት አልመስል ብለውኝ ነበር፡፡ ሰውዬው ለምንም ነገር ግድ የላቸውም፡፡ ሁልጊዜ ከሰዓት በኋላ ጫታቸውን ይዘው በረንዳቸው ላይ ይፈርሹና፤ ጓደኞቻቸው ከመጡ
ከጓደኞቻቸው ጋር፣ ከሌሉም ብቻቸውን ቁጭ ብለው፣የምታምር ልጃቸው አንዴ ቡና አንዴ ሻይ እያቀረበችላቸው፣ ሱዳንኛ ዘፈን ከፍተው ጫታቸውን እየቃሙ ይውላሉ፡፡ያንን በሚያክል ግቢ ውስጥ፣ ከአንዲት ቆንጆ ሴት ልጃቸው ጋር ብቻቸውን ነው የሚኖሩት፡፡ መጀመሪያ አካባቢ አብሪያቸው ጫት እንድቅም በተደጋጋሚ ይጋብዙኝ ነበር፡፡
ልጅ …ጫት አትቅምም ?” ይሉኛል፡፡
“ኤልቅምም አባባ!” “ምነው? በሰላም!?”
ሳቄ ይቀድመኛል፡፡በኋላ እንደማልቅም ገብቷቸው፣ማጨናነቁን ትተው፣እቤት ከዋልኩ ኮካ-ኮላና ለውዝ ይልካልኛል፡፡ ቡናና ሻይ ሲፈላ ደግሞ ልጃቸውን፣ “ሐኑን ነይ ለዚህ ልጅ ውሰጅለት” ይሏታል፡፡
ልጃቸው ሐኑን ከፀጉሯ ላይ እየተንሸራተተ የሚያስቸግራትን መሸፈኛ አሥር ጊዜ
ወደፊት፣ወደግንባሯ ሳብ እያደረገች፣ ቡና አልያም ሻይ በሚያምር ሰርቪስ ትሪ ይዛልኝ ትመጣለች፡፡ ቢነኳት የምትፈርጥ የምትመስል ቆንጆ ልጅ ነች፡፡ ገና በር ላይ በአክብሮት ጫማዋን አውልቃ ስትገባ፣ ውብ እግሮቿ ላይ ዓይኔ እያረፈ ኧረ ጫማሽን አታውልቂ እላታለሁ፡፡ ምንግዜም ግን ሳታወልቅ አትገባም፡፡ በእርግጥ በዕድሜ ከእኔ ታንሳለች::
በስምን ወይም በዘጠኝ ዓመት ሳልበልጣት አልቀርም፡፡ ቢሆንም ለመጀመሪያ ጊዜ ካየኋት ቀን ጀምሮ ባየኋት ቁጥር፣ ለመቀራረብ የሚገፋኝን ፍላጎቴን መቋቋም አልቻልኩም፡ ቀስ በቀስ ማውራት ስንጀምር፣ የበለጠ ቀረብኳት፡፡ ብዙ አታወራም ፈገግ ብላ ትልልቅ ዓይኖቿን እያንከባለለች ዝም ትላለች፡፡ ምንም ቃል ሳይወጣት ብዙ
ያወራን የሚመስለኝ ነገር ነበር፡፡
ሐኑን፣ ከሌላ ሴት የወለዷት የሰውዬው ዘጠነኛ ልጅ ናት፡፡ ስምንት የወለደችላቸውን ሚሰታቸውን አስቀምጠው፣ያውም እቤታቸው ሠራተኛ ሆና ከተቀጠረች ሴት ነበር ሐኑንን የወለዱት፡፡ ይኼ ነገር በልጆቻቸውም ሆነ በሚስታቸው በቀላሉ የሚታለፍ ነገር
አልሆነም፡፡ ትዳራቸውን ሊበትነው ደረሰ፡፡ በመጨረሻ ሠራተኛዋን ከነልጇ ቤት
ተከራይተው በድብቅ እስቀመጡ፡፡ ወሬው ግን የሚደበቅ አልሆነም፡፡ ባልና ሚስት
ከዝያ በኋላ በሰበብ አስባቡ መጋጨት ሆነ ሥራቸው :: በተለይ ሚስት ከልጆቻቸው ጋር አብረው ሰውዬውን መቆሚያ መቀመጫ አሳጧቸው፡፡ሰውየው ደግሞ ንዝንዝ አይወዱም፡፡ ለአንድ ሰዓት ሰላም በልዋጩ ያላቸውን ሀብት ቢከፍሉ የማይቆጫቸው
ዓይነት ሰው ናቸው፡፡
በስልክ እንኳን እያውሩ ትንሽ ንዝንዝ ቢጤ ከሆነባቸው “አቦ! ልቃምበት እንግዲህ አትነጅሱኝ ብለው ጥርቅም ያደርጉና ስልካቸውን ወዳያ ይወረውሩታል፡፡ሐኑን አንስታ
እለመሰበሩን ካረጋገጠች በኋላ እቤት ታስቀምጥላቸዋለች፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ሚስታቸውን ቁጭ አደረጉና፣ እንግዲህ አጠፋሁ፤ የተተፋ ምራቅ መልሶ አይዋጥም፣ አንቺም ጧት ማታ እያነሳሽ በሰበቡ ከምትነዘንዥኝ፣ ከልጆቼም ጋር ከፉ ደግ ከምነጋገር የወደድሽውን ንብረት ያዥና ከልጆችሽ ጋር ኑሪ፣ በቃ ፈትቼሻለሁ ብለው ቤቱን ለሚስታቸውና ለልጆቻቸው ትተው ወጡ፡፡ ከቤት ሲወጡ የያዙት ነገር ቢኖር፥ የጀመሯት በላስቲክ የተጠቀለለች ጫት ብቻ ነበር፡፡በሽማግሌ ወደ ቤታቸው
እንዲመለሱ ቢለመኑ ቢደረጉ እምቢ አሉ፡፡ብዙም አልቆዩም ሐኑን እናት ጋ ጠቅልለው ገቡ ፡፡ የልጆቻቸው እናት ይሄን ሲስሙ፣ ድሮም ጤና አልነበራቸዉም ውሎና አዳራቸው ሆስፒታል ሆነ፡፡በመጨረሻም እንዲቹ እንደተብሰለሰሉ አረፉ፡፡ ልጆቻቸው የእናታቸው
ገዳይ የሐኑን እናት እንደሆነች ነው የሚያምኑት፡፡ ጦሱ ምንም ለማታውቀው ሐኑንም ተርፎ ልክ የሌለው ኃይለኛ ጥላቻ ነበር ያለባቸው፤ለዓይናቸው ሊያዩዋት
አይፈልጉም፡፡ቃል በቃል የገረድ ልጅ እናታችንን ያስገደለች ይሏታል፡፡
የእርሷም እናት እኔ እዚያ ቤት ከመግባቴ ከአምስት ዓመት በፊት ነበር የሞተችው፡፡
ለዚያም ይሆናል ሁሉጊዜም በቆንጆ ፊቷ ላይ እንደ ስስ ደመና የሐዘን ስሜት
የማያንዣብብ የሚመስለኝ፡፡አስረኛ ክፍል ላይ የትምህርት ነገር በቃኝ ብላ፣ ቤት ውስጥ ነበር የምትውለው፡፡ አባቷም ከቤት እንድትወጣ አይፈልጉም ፡፡ አላህ እንዲህ ያለልክ አሳምሮ ኸልቆብኝ በገባች በወጣች ቁጥር ይሄ ባለጌ ወንድ ሁሉ እየተከተለ አስቸገራት፡ አቦ ከዚህ ሁሉ ብትተወውስ ብየ፣ ይኼው እቤት ነው ውሎዋ_አላህ ደጉን ኢማን ያለውን ሰው እስኪወፍቃት” ምከንያታቸው ይኼ ብቻ አልነበረም፡፡ የራሳቸው ልጆች
አንድ ነገር ያደርጓታል ብለው ይፈራሉ፡፡ እኔም በኋላ ሳውቃቸው ልጆቹ አያደርጉም የሚባሉ ዓይነት አልነበሩም፡፡
ሐኑን ጋር ቀስ በቀስ ተላመድን፡፡ እንዲያውም ቡና ከማመላለስ ባለፈ፣ አንዳንዴ ኣባቷ ሳይኖሩ እኔ ቤት ትመጣና ስንጫወት ቆይተን ትሄዳለች፡፡ ረጋ ያለ አነጋገሯ አንዳች ጊዜን የማቆም ኃይል ያለው ይመስለኛል፡፡ በተፈጥሮዬ ተኝቼ እንኳን ሐሳቤ የማያርፍ እዚያና እዚህ የምዛብር ሰው ነኝ፡፡ ፊልም እንኳን ከፍቼ አንድ ቀን መጨረሻውን አይቼ አላውቅም የሚያንቀዠቅዥኝ ነገር አለ፡፡ ሐኑን ጋር ስሆን ግን አንዳች የመረጋጋት ስሜት ይሰፍንብኛል፡፡ ጥልቅ ዕረፍት ውስጥ ነፍሴ ትዋኛለች ፡፡ይኼንንም ፍቅር ነው
ብየ ነበር::
እሷም ብትሆን እንደወደደችኝ ገብቶኝ ነበር፡፡ በእፍረቷ፣ አንዳንዴ ደግሞ እያመለጣት በምትናገራቸው ቃላት፡፡ ስንቆይ፣ አንዱን የቤቴን ቁልፍ ወስዳ፣ በሌለሁበት ቤቴን አዘጋጅታልኝ ትሄዳለች፡፡ ሁልጊዜ አልጋየ የሚያሰክር ሽቶ ተረጭበት ሳገኘው፣ ነፍሴ ሐሤት ታደርጋለት በድሬዳዋ ቆይታዬ ሐሳቤ ሁሉ ሁለት ነገሮች አይዘልም ሐኑንና ስራዬን፡ክፉኛ እየወደድኳት ነበር፡፡ ከሥራ ስወጣ ወደ ገነት የምሄድ እስኪመስለኝ ድረስ
ልቤ በደስታ ትዘላለች፡፡ ቁልቁለት ላይ እንደሚሮጥ ሰው፣ ራሴን ልቆጣጠርና ልቆም ስታገል፣ ግን ግፊቱ ሲያንደረድረኝ ይሰማኛል ፡፡
አንድ ቀን ልነግራት ወሰንኩ፡፡ ግን በብዙ ሐሳቦች ዙሪያውን ተወጣጥሬ ቃል መተንፈስ አቃተኝ፡፡ በሁለት ምክንያቶች እንደምወዳት ለመናገር ፈራሁ። አባቷ እንደ ልጃቸው ስለቀረቡኝ፣ ድንገት ይኼ ጉዳይ ጆሯቸው ቢገባና፣ አዲስ አበባ ላሉት አለቆች
“የላካችሁት ጎረምሳ ልጄን እያማገጠ ነው? ብለው ቢናገሩ፣ የሚለው ሐሳብ
አስጨነቀኝ፡፡ ለብዙ ነገር ግዴለሽ ናቸው የሚባሉ ሰዎች፣ በማይወላውል ለሰላሳ ማንነት እንደተራራ ረጋ ብለው ቢቀመጡም፤ ድንገት እንደ እሳተገሞራ በውስጣቸው ያለው እሳት ወጥቶ፣ አካባቢያቸውን የሚያቃጥልበት ሽንቁርም አይጠፋቸውም::እኒህም ሰው
ለሀብታቸውም ሆነ በዙሪያቸው ላለ ነገር ግዴለሽ ይመስላሉ ማለት፤ ለልጃቸው ግዴለሽ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ዓይናቸው ናት ሐኑን፡፡ዋጋ የከፈሉባት፡፡ ብትመነዘር የስምንት ልጅ ዋጋ ያላት፡፡
ሌላው ጭንቀቴ ሐኑን ራሷ ነበረች፡፡ ገና ለፍቅር ሳስባት
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ድሬዳዋ ግሪክ ሰፈር የሚባል ሰፊ የሀብታም ግቢ ውስጥ፣ የራሱ ገላ መታጠቢያ ከፍልና፣ መጸዳጃ ቤት ያለው ባለ ሁለት ክፍል ቤት ከነዕቃው ተዘጋጅቶልኝ ነበር፡፡ ቤቱ የአንድ ባለሀብት ቤት ሲሆን፡ የምሠራበት ባንክ የተከራየው ሕንፃ ጭምር የሰውዬው ነበር፡፡ እንዲሁ ስጠረጥር ባለሀብቱ ቤታቸውን ያከራዩት፣የኪራይ ብር አስጨንቋቸው
ሳይሆን፤ሕንፃቸውን ተከራይቶ በየዓመቱ ጠቀም ያለ ብር የሚከፍላቸውን ባንክ ሥራ አስኪያጅ፣ ቤተኛ ለማድረግ ይመስለኛል፡፡ “ባለቤቱ ይኼ ናቸው” ቢሉኝ ገረመኝ፡፡
ሽርጥ ያገለደሙ ተራ ሰንደል ጫማ ያጠለቁ፣ ከጉያቸው ሥር ምንጊዜም በላስቲክ የተጠቀለለ ጫት የማይጠፉ፣ ጺማቸው በርስሬ መስሎ የቀላ ሽማግሌ፤ የዚያ ሁሉ ሀብት ባለቤት አልመስል ብለውኝ ነበር፡፡ ሰውዬው ለምንም ነገር ግድ የላቸውም፡፡ ሁልጊዜ ከሰዓት በኋላ ጫታቸውን ይዘው በረንዳቸው ላይ ይፈርሹና፤ ጓደኞቻቸው ከመጡ
ከጓደኞቻቸው ጋር፣ ከሌሉም ብቻቸውን ቁጭ ብለው፣የምታምር ልጃቸው አንዴ ቡና አንዴ ሻይ እያቀረበችላቸው፣ ሱዳንኛ ዘፈን ከፍተው ጫታቸውን እየቃሙ ይውላሉ፡፡ያንን በሚያክል ግቢ ውስጥ፣ ከአንዲት ቆንጆ ሴት ልጃቸው ጋር ብቻቸውን ነው የሚኖሩት፡፡ መጀመሪያ አካባቢ አብሪያቸው ጫት እንድቅም በተደጋጋሚ ይጋብዙኝ ነበር፡፡
ልጅ …ጫት አትቅምም ?” ይሉኛል፡፡
“ኤልቅምም አባባ!” “ምነው? በሰላም!?”
ሳቄ ይቀድመኛል፡፡በኋላ እንደማልቅም ገብቷቸው፣ማጨናነቁን ትተው፣እቤት ከዋልኩ ኮካ-ኮላና ለውዝ ይልካልኛል፡፡ ቡናና ሻይ ሲፈላ ደግሞ ልጃቸውን፣ “ሐኑን ነይ ለዚህ ልጅ ውሰጅለት” ይሏታል፡፡
ልጃቸው ሐኑን ከፀጉሯ ላይ እየተንሸራተተ የሚያስቸግራትን መሸፈኛ አሥር ጊዜ
ወደፊት፣ወደግንባሯ ሳብ እያደረገች፣ ቡና አልያም ሻይ በሚያምር ሰርቪስ ትሪ ይዛልኝ ትመጣለች፡፡ ቢነኳት የምትፈርጥ የምትመስል ቆንጆ ልጅ ነች፡፡ ገና በር ላይ በአክብሮት ጫማዋን አውልቃ ስትገባ፣ ውብ እግሮቿ ላይ ዓይኔ እያረፈ ኧረ ጫማሽን አታውልቂ እላታለሁ፡፡ ምንግዜም ግን ሳታወልቅ አትገባም፡፡ በእርግጥ በዕድሜ ከእኔ ታንሳለች::
በስምን ወይም በዘጠኝ ዓመት ሳልበልጣት አልቀርም፡፡ ቢሆንም ለመጀመሪያ ጊዜ ካየኋት ቀን ጀምሮ ባየኋት ቁጥር፣ ለመቀራረብ የሚገፋኝን ፍላጎቴን መቋቋም አልቻልኩም፡ ቀስ በቀስ ማውራት ስንጀምር፣ የበለጠ ቀረብኳት፡፡ ብዙ አታወራም ፈገግ ብላ ትልልቅ ዓይኖቿን እያንከባለለች ዝም ትላለች፡፡ ምንም ቃል ሳይወጣት ብዙ
ያወራን የሚመስለኝ ነገር ነበር፡፡
ሐኑን፣ ከሌላ ሴት የወለዷት የሰውዬው ዘጠነኛ ልጅ ናት፡፡ ስምንት የወለደችላቸውን ሚሰታቸውን አስቀምጠው፣ያውም እቤታቸው ሠራተኛ ሆና ከተቀጠረች ሴት ነበር ሐኑንን የወለዱት፡፡ ይኼ ነገር በልጆቻቸውም ሆነ በሚስታቸው በቀላሉ የሚታለፍ ነገር
አልሆነም፡፡ ትዳራቸውን ሊበትነው ደረሰ፡፡ በመጨረሻ ሠራተኛዋን ከነልጇ ቤት
ተከራይተው በድብቅ እስቀመጡ፡፡ ወሬው ግን የሚደበቅ አልሆነም፡፡ ባልና ሚስት
ከዝያ በኋላ በሰበብ አስባቡ መጋጨት ሆነ ሥራቸው :: በተለይ ሚስት ከልጆቻቸው ጋር አብረው ሰውዬውን መቆሚያ መቀመጫ አሳጧቸው፡፡ሰውየው ደግሞ ንዝንዝ አይወዱም፡፡ ለአንድ ሰዓት ሰላም በልዋጩ ያላቸውን ሀብት ቢከፍሉ የማይቆጫቸው
ዓይነት ሰው ናቸው፡፡
በስልክ እንኳን እያውሩ ትንሽ ንዝንዝ ቢጤ ከሆነባቸው “አቦ! ልቃምበት እንግዲህ አትነጅሱኝ ብለው ጥርቅም ያደርጉና ስልካቸውን ወዳያ ይወረውሩታል፡፡ሐኑን አንስታ
እለመሰበሩን ካረጋገጠች በኋላ እቤት ታስቀምጥላቸዋለች፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ሚስታቸውን ቁጭ አደረጉና፣ እንግዲህ አጠፋሁ፤ የተተፋ ምራቅ መልሶ አይዋጥም፣ አንቺም ጧት ማታ እያነሳሽ በሰበቡ ከምትነዘንዥኝ፣ ከልጆቼም ጋር ከፉ ደግ ከምነጋገር የወደድሽውን ንብረት ያዥና ከልጆችሽ ጋር ኑሪ፣ በቃ ፈትቼሻለሁ ብለው ቤቱን ለሚስታቸውና ለልጆቻቸው ትተው ወጡ፡፡ ከቤት ሲወጡ የያዙት ነገር ቢኖር፥ የጀመሯት በላስቲክ የተጠቀለለች ጫት ብቻ ነበር፡፡በሽማግሌ ወደ ቤታቸው
እንዲመለሱ ቢለመኑ ቢደረጉ እምቢ አሉ፡፡ብዙም አልቆዩም ሐኑን እናት ጋ ጠቅልለው ገቡ ፡፡ የልጆቻቸው እናት ይሄን ሲስሙ፣ ድሮም ጤና አልነበራቸዉም ውሎና አዳራቸው ሆስፒታል ሆነ፡፡በመጨረሻም እንዲቹ እንደተብሰለሰሉ አረፉ፡፡ ልጆቻቸው የእናታቸው
ገዳይ የሐኑን እናት እንደሆነች ነው የሚያምኑት፡፡ ጦሱ ምንም ለማታውቀው ሐኑንም ተርፎ ልክ የሌለው ኃይለኛ ጥላቻ ነበር ያለባቸው፤ለዓይናቸው ሊያዩዋት
አይፈልጉም፡፡ቃል በቃል የገረድ ልጅ እናታችንን ያስገደለች ይሏታል፡፡
የእርሷም እናት እኔ እዚያ ቤት ከመግባቴ ከአምስት ዓመት በፊት ነበር የሞተችው፡፡
ለዚያም ይሆናል ሁሉጊዜም በቆንጆ ፊቷ ላይ እንደ ስስ ደመና የሐዘን ስሜት
የማያንዣብብ የሚመስለኝ፡፡አስረኛ ክፍል ላይ የትምህርት ነገር በቃኝ ብላ፣ ቤት ውስጥ ነበር የምትውለው፡፡ አባቷም ከቤት እንድትወጣ አይፈልጉም ፡፡ አላህ እንዲህ ያለልክ አሳምሮ ኸልቆብኝ በገባች በወጣች ቁጥር ይሄ ባለጌ ወንድ ሁሉ እየተከተለ አስቸገራት፡ አቦ ከዚህ ሁሉ ብትተወውስ ብየ፣ ይኼው እቤት ነው ውሎዋ_አላህ ደጉን ኢማን ያለውን ሰው እስኪወፍቃት” ምከንያታቸው ይኼ ብቻ አልነበረም፡፡ የራሳቸው ልጆች
አንድ ነገር ያደርጓታል ብለው ይፈራሉ፡፡ እኔም በኋላ ሳውቃቸው ልጆቹ አያደርጉም የሚባሉ ዓይነት አልነበሩም፡፡
ሐኑን ጋር ቀስ በቀስ ተላመድን፡፡ እንዲያውም ቡና ከማመላለስ ባለፈ፣ አንዳንዴ ኣባቷ ሳይኖሩ እኔ ቤት ትመጣና ስንጫወት ቆይተን ትሄዳለች፡፡ ረጋ ያለ አነጋገሯ አንዳች ጊዜን የማቆም ኃይል ያለው ይመስለኛል፡፡ በተፈጥሮዬ ተኝቼ እንኳን ሐሳቤ የማያርፍ እዚያና እዚህ የምዛብር ሰው ነኝ፡፡ ፊልም እንኳን ከፍቼ አንድ ቀን መጨረሻውን አይቼ አላውቅም የሚያንቀዠቅዥኝ ነገር አለ፡፡ ሐኑን ጋር ስሆን ግን አንዳች የመረጋጋት ስሜት ይሰፍንብኛል፡፡ ጥልቅ ዕረፍት ውስጥ ነፍሴ ትዋኛለች ፡፡ይኼንንም ፍቅር ነው
ብየ ነበር::
እሷም ብትሆን እንደወደደችኝ ገብቶኝ ነበር፡፡ በእፍረቷ፣ አንዳንዴ ደግሞ እያመለጣት በምትናገራቸው ቃላት፡፡ ስንቆይ፣ አንዱን የቤቴን ቁልፍ ወስዳ፣ በሌለሁበት ቤቴን አዘጋጅታልኝ ትሄዳለች፡፡ ሁልጊዜ አልጋየ የሚያሰክር ሽቶ ተረጭበት ሳገኘው፣ ነፍሴ ሐሤት ታደርጋለት በድሬዳዋ ቆይታዬ ሐሳቤ ሁሉ ሁለት ነገሮች አይዘልም ሐኑንና ስራዬን፡ክፉኛ እየወደድኳት ነበር፡፡ ከሥራ ስወጣ ወደ ገነት የምሄድ እስኪመስለኝ ድረስ
ልቤ በደስታ ትዘላለች፡፡ ቁልቁለት ላይ እንደሚሮጥ ሰው፣ ራሴን ልቆጣጠርና ልቆም ስታገል፣ ግን ግፊቱ ሲያንደረድረኝ ይሰማኛል ፡፡
አንድ ቀን ልነግራት ወሰንኩ፡፡ ግን በብዙ ሐሳቦች ዙሪያውን ተወጣጥሬ ቃል መተንፈስ አቃተኝ፡፡ በሁለት ምክንያቶች እንደምወዳት ለመናገር ፈራሁ። አባቷ እንደ ልጃቸው ስለቀረቡኝ፣ ድንገት ይኼ ጉዳይ ጆሯቸው ቢገባና፣ አዲስ አበባ ላሉት አለቆች
“የላካችሁት ጎረምሳ ልጄን እያማገጠ ነው? ብለው ቢናገሩ፣ የሚለው ሐሳብ
አስጨነቀኝ፡፡ ለብዙ ነገር ግዴለሽ ናቸው የሚባሉ ሰዎች፣ በማይወላውል ለሰላሳ ማንነት እንደተራራ ረጋ ብለው ቢቀመጡም፤ ድንገት እንደ እሳተገሞራ በውስጣቸው ያለው እሳት ወጥቶ፣ አካባቢያቸውን የሚያቃጥልበት ሽንቁርም አይጠፋቸውም::እኒህም ሰው
ለሀብታቸውም ሆነ በዙሪያቸው ላለ ነገር ግዴለሽ ይመስላሉ ማለት፤ ለልጃቸው ግዴለሽ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ዓይናቸው ናት ሐኑን፡፡ዋጋ የከፈሉባት፡፡ ብትመነዘር የስምንት ልጅ ዋጋ ያላት፡፡
ሌላው ጭንቀቴ ሐኑን ራሷ ነበረች፡፡ ገና ለፍቅር ሳስባት
👍2❤1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ክንብንቧ ጫፍ ላይ የተንጠለጠሉ ክሮችን እያፍተለተለች ቆየች ጣቶቿን አያቸዋለሁ።ጫፎቻቸው እንደቲማቲም የቀሉ፣ ስትዘቀዝቃቸው የሚንጠባጠቡ የደም ጤዛዎች ይመሳስላሉ ውብ ጣቶች አስቀይሚያት ይሆን ብዬ ስለፈራሁ፤ ቀረብ አልኳትና በሁለት እጆቼ ጉንጮቿን ይዤ ቀና አደረኳት፡፡ እንባዋ በንጹህ ቀይ ቆዳዋ ላይ ኮለል ብሎ ፈሰሰ።ቃል አልተነፈሰችም አልተነፈሰችም፡፡ በለስላሳ እጇ ጉንጫ ላይ ያረፈ እጄን ያዘችኝ፡፡ትኩስና ለስላሳ መዳፏ ልክ እንደ ከንፈር የልቧን ሐሳብ የሚያወራ ይመስል ነበር፡፡ጥብቅ አድርጋ ያዘችኝ፤ እናም አንድ ነገር ብቻ ተናገረች
እውነትህን ነው? እኔን ታገባኛለህ?”
እዎ”
መልሳ አቀረቀረች፡፡ እጇ ግን እጄን እንደያዘ ነበር፡፡ይኼ ቃሌ እስካሁንም እንደ እሳት ጅራፍ ራሴን ይገርፈኛል፡፡ወንዳዊ ማንነቴ በደመነፍስ የፈጠረው ክፉ ማጭበርበር ነበር። ልምዱ ኑሮኝ አልነበረም፡፡ እንዲያው እንዲህና እንዲያ ልበላት ብዬ ቃል ቀምሬም አልነበረም፡፡ከየት እንደመጣ ባላውቀውም እእምሮዬ አጠቃላይ ሁኔታወችን በፍጥነት ደምሮና ቀንሶ ሐኑን ምን እንደምትፈልግ ገብቶት ነበር: አፍቅራ እዚህ መኖር አልነበረም
ፍላጎቷ፡፡ ከዚህ በጠቆረ ትዝታ ከጠቆረ ግቢ ብን ብላ መውጣት ነበር መሻቷ ልክ በውሃ በተከበበ ደሴት ላይ ተከባ መውጫ ላጣች ነፍስ፣ራሴን ከዚህ መውጫ ጀልባ ነኝ ብዬ አቀረብኩላት፤ ማቄን ጨርቄን ሳትል ጀልባዋ ላይ ወጣች!!
እጇ ትንሽ የተንቀጠቀጠ መሰለኝ ወይስ የእኔ ነው!? ከዚህ ቀን በኋላ ሐኑን እኔ
በፍቅር ከነፍን፡፡ ግን ፍቅር ነው ወይ እላለሁ፣ ራሴን አላምነውም፡፡ የአባቷ እግር ከቤት ከወጣ የሐኑን እግር እኔ በር ላይ ነው፡፡ ፍቅር እንደ እሳተ ገሞራ ነው- የተረጋጋውን ምድር፣በሰላም ለዘመናት ተኮፍሶ የኖረን የአለት ተራራ ሽቅብ ፈነቃቅሎት ሲወጣ፣ ብናኝና ጭሱ አካባቢውን ይሸፍነዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ገሞራ የፈነዳበት ምድር ወደነበረበት
ተፈጥሮው አይመለስም:: እዚያ ግቢ የዚያን ጊዜ የሆነው እንደዚያ ነበር፡፡ የፍቅር ገሞራው ሲፈነዳ፣ ብናኙ የሐኑንን ፊት ሸፈነው፡፡ረጋ ያለችው ልጅ፣ የምትይዝ
የምትጨብጠውን አጣች፡፡ ብናኙ ፈገግታ ሆኖ ፊቷን ሸፈነው…ብናኙ የመሻት ነበልባሉን ወደቤቴ ልኮ አለት ብቸኝነቴን አቀለጠው፡፡ የሐዘን ደመና ከውብ ፊቷ ላይ ተገፎ እንደጥዋት ፀሐይ ውብ ፈገግታ ሲረጭ ግቢውን እሳት ሞላው፣ደግሞ ግቢውን ውሃ ሞላው ግቢው በረሃ ሆነ ደግሞም ግቢዉ የኤደን ገነት ሆነ፣ በአንድ ጊዜ ሁሉም ነገር ሆነ፡፡ በዚህ ፍንዳታ ውስጥ ተረጋግተው ጫታቸውን የሚቅሙት አባቷ
ልጅ ትንሽ አትሞክርም? ይሉኛል ጫታቸውን እያሳዩኝ፡፡ “በዚህ ላይ ጫት
ተጨምሮበት” እላለሁ በውስጤ፡፡ አለመታመንኮ ነው ሰው ግቢ ገብቶ የሰው ሴት ልጅ - ያውም ያመኑት የአንድን ትልቅ ተቋም ሥራ አስኪያጅ ነው፣ ራሱን የገዛ ሰው ነው ያሉትን ሰው … ግን ደግሞ ቦታና ጊዜ፣ ሥራና ደረጃ፣ ፍቅር ፊት ምን ጉልበት አላቸው? ዋናው ጥያቄ ይኼ እብደት ፍቅር ነው ወይ ነው? ራሴን አላምነውም!
ሐኑን ጋር ዓይኖቻችን ተንሰፍስፈው ይፈላለጋሉ፡፡ ግድቡን እንደጣሰ ጎርፍ ራሷን መቆጣጠር አቅቷት ነበር፡፡ አንዳንዴ አባቷ እቤት እያሉ ጭምር ድንገት እቤቴ
ትመጣለች ፡፡
ኧረ አባባ እላለሁ በጭንቀት ድምፄን ቀንሸ፡፡
እየሰገደ ነው ትለኛለች፡፡ ከዛ እቅፌ ውስጥ ናት፡፡
ኧረ አባባ እላለሁ፣
ውጭ ስልክ እያወራ ነው ትላለች፡፡ ይሉኝ ነካክቼ እንደ አልኮል ያስከራትን ፍቅር
በምን ላረጋጋው? ዓይኗንም ልቧንም የሠወረው ፍቅር፣ሁለታችንንም አባቷ ዓይን ላይ ሊጥለን እያዳፋ የሚነዳ ደራሽ ጎርፍ ሆነብኝ፡፡ ፈጣን ነበር_ሁሉም ነገር በጣም ፈጣን እየተጨነቅሁ እሰማታለሁ፡፡ እያሰብኩ በደመነፍስ እጓዛለሁ፡፡ አንዳንዴ ሌሊት ትደውልልኛለች፡፡ ፍቅር ከጊዜ ሥርዓት ያፈነገጠ ስሜት መሆኑ የገባኝ ያን ጊዜ ነበር፡፡ ብዙ ከዛ በፊት ያልገባኝ ነገር የገባኝ ያኔ ነበር፤ ብዙ ከዛ በፊት ገብቶኛል ያልኩት ነገር የጠፋብኝም ያኔ ነበር፡፡ የመኝታ ቤቷ መስኮት እና የሳሎኔ መስኮት ትይዩ ስለሆነ መጋረጃችንን ሰብስበን ዝም ብለን እንተያያለን እስር ቤት ያሉ ነፍሶች ነበር የምንመስለው፡፡
እነዚያ ሌሊቶች መቼም የሚረሱኝ አይደሉም አንድ ምሽት ደረቅና ሞቃታማዋ ድሬዳዋ፣በድንገተኛ ዶፍ ዝናብ ተጥለቀለቀች፡፡ የድሬደዋ ሰማይ ግፏን አፍና እንደኖረች ሴት፣ ድንገት ነው አስፈሪ ዶፉን እንደ እንባ የሚዘረግፈው፡፡ ዝናቡ ከሰማይ ብቻ ሳይሆን፤ከምድርም ይፈልቅ ይመስል፣ ከምኔው ምድሩ በጎርፍ እንደሚጥለቀለቅ ይገርመኛል፡፡ የዚያን ቀን ዝናቡ ሌሊቱን ሙሉ አላቋረጠም፡፡ በየመኻሉ ሰማዩን ሰንጥቆ
አካባቢውን በብርሃን የሚያጥለቀልቅ የመብረቅ ብልጭታ የመስኮቴን መጋረጃ እያለፈ ቤቴን በብርሃን ይሞለዋል፡፡ በተደጋጋሚ ወገግ ይላል፡፡ ምን እንደገፋኝ እንጃ ፣ተነስቼ የመስኮት መጋረጃዬን ሰበሰብኩት፡፡ ሐኑን ልከ የተቀጣጠርን ይመስል መጋረጃዋን ስብስባ ውብ ጉርድ ፎቶ ግራፍ መስላ መስኮቱ ጋ ቆማ ነበር …በእያንዳንዱ ብልጭታ፣ የሐኑንን ውብ ፊት አእምሮየ እንደፎቶ እያተመ ያስቀምጣል፡፡ በግራ ትከሻዋ በኩል
አልፎ ጡቷ ላይ የሚርመሰመሰዉ ጸጉሯ ግማሽ ፊቷን የከበበ ጥቁር ፍሬም መሰሏል፡፡ እስከ ዛሬ ሐኑንን ሳስብ፣ ያ መልኳ ነው ቀድሞ የሚታወሰኝ፡፡ እንደ ቲማቲም የቀሉ ከንፈሮች ከመቅላቱ ብዛት በወርቃማ ቆዳ የተለበጠ የሚመስል ደረት…ሥዕል፡፡
በየመስኮት መስታዎቶቻችን ላይ የሚንኳለለው የዝናብ ውሃ፣ ነጋችንን አውቆ እርሙን የማያወጣ የዘመን እንባ ይመስል ነበር፡፡ ጡቶቿ ቢጫ የሚበዛበትን ባለብዙ አበባ ሥዕል፣ ስስ የሌሊት ልብሷን ወጥረው፣ ከተደገፈችዉ መስተዋት ጋር ጫፋቸው ተነካክቷል፡፡ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ አፍንጫዋ በመስተዋቱ እየተደፈጠጠ ያስቀኛል፡፡
እኔን በፈገግታ እያየች መስተዋቱን ስትስመው፣ቀያይ ውብ ከንፈሮቿ መስተዋቱ ላይ በክቡ ተለጥፈው፣ ትንፋሽዋ መስተዋቱ ላይ ጭጋግ ይፈጥራል፡፡ በትንፋሽዋ ጉም
በተሸፈነው መስተዋት ላይ፣በጣቷ የልብ ቅርጽ ትሥልበታለች ፡፡ትንፋሽዋ መስተዋቱ ላይ በሚፈጥረው ላቦት ምስሏ መደብዘዝ ሲጀምር፣ መስተዋቱን በመዳፏ ትወለውለዋለች፡፡ በዚህ ጊዜ የደበዘዘዉ ምስሏ ቦግ ብሎ ይወጣል፡፡ በቃ እንተያያለን፣ ያለድምፅ ዝም ብለን
መተያየት…በምልከት ልተኛ ነው ስላት በእጇ ትንሽ እንድቆይ ትለምነኛለች፡፡ያ ሌሊት በተደጋጋሚ ሕልሜ ይመጣል፡፡
መስተዋት ተደግፌ አድሬ፣ ሊነጋጋ ሲል ድብን ያለ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ጧት የቤቴ በር ሲከፈት እንኳን አልሰማሁም፡፡ በጧት እንደ እሳት የሚፋጅ ላሰላሳ ገላዋ፣ የሞቀ አልጋዬ ውስጥ ገብቶ ስትለጠፍብኝ ነበር የነቃሁት፡፡ በእንቅልፍ በሰከረ አእምሮዬ ላይ በሽቶ ባበደ ጠረኗ የታጀበ ሰውነቷ ሲያቅፈኝ፡ ነገሩ ሕልም ይሁን እውነት በወጉ እንኳን ሳይገባኝ፣ የሐኑን የሚንቀጠቀጡ ትኩስና ለስላሳ ከንፈሮት፣ ከንፈሬ ላይ አርፈው ነበር፡፡
ሰውነቴ ከእእምሮዩ ቀድሞ ነቃ፤ ረዥም በሰመመን የተሞሉ ደቂቃዎች ይሁኑ ሰዓታት ከሥሬ ሆና በለስላሳ ቀይ ፊቷ ቆዳ ላይ እንባዋ ኮለል ብሎ ወደ ጆሮዋ ሲወርድና በሕመም ስትቃትት፡ ሥጋዊ ወንድነቴ ከሚሰማው አብሮነት ይልቅ፡ አንዳች የነፍሴ ክፍል ላይ ነፍሷ ለዘላለም ሲነቀስ ይሰማኝ ነበር፡፡ አእምሮዬ በአንድ ጊዜ ሁለት ተቃራኒ ሐሳቦችን እያሰበ ነበር፡፡ እየተሳሳትኩ ነው” እና “ልክ ነኝ” የሚሉ ሐሳቦች፡፡ እንደዚያ ነበር የማስበው፡፡ አእምሮየ ምንም ያስብ ምን፡ ገና ከጅምሩ ሰውነቴ ለአእምሮዬ መታዘዙን ትቶት ነበር፡፡ ብዙ ሰው የሆንኩ እስኪመስለኝ ድረስ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ክንብንቧ ጫፍ ላይ የተንጠለጠሉ ክሮችን እያፍተለተለች ቆየች ጣቶቿን አያቸዋለሁ።ጫፎቻቸው እንደቲማቲም የቀሉ፣ ስትዘቀዝቃቸው የሚንጠባጠቡ የደም ጤዛዎች ይመሳስላሉ ውብ ጣቶች አስቀይሚያት ይሆን ብዬ ስለፈራሁ፤ ቀረብ አልኳትና በሁለት እጆቼ ጉንጮቿን ይዤ ቀና አደረኳት፡፡ እንባዋ በንጹህ ቀይ ቆዳዋ ላይ ኮለል ብሎ ፈሰሰ።ቃል አልተነፈሰችም አልተነፈሰችም፡፡ በለስላሳ እጇ ጉንጫ ላይ ያረፈ እጄን ያዘችኝ፡፡ትኩስና ለስላሳ መዳፏ ልክ እንደ ከንፈር የልቧን ሐሳብ የሚያወራ ይመስል ነበር፡፡ጥብቅ አድርጋ ያዘችኝ፤ እናም አንድ ነገር ብቻ ተናገረች
እውነትህን ነው? እኔን ታገባኛለህ?”
እዎ”
መልሳ አቀረቀረች፡፡ እጇ ግን እጄን እንደያዘ ነበር፡፡ይኼ ቃሌ እስካሁንም እንደ እሳት ጅራፍ ራሴን ይገርፈኛል፡፡ወንዳዊ ማንነቴ በደመነፍስ የፈጠረው ክፉ ማጭበርበር ነበር። ልምዱ ኑሮኝ አልነበረም፡፡ እንዲያው እንዲህና እንዲያ ልበላት ብዬ ቃል ቀምሬም አልነበረም፡፡ከየት እንደመጣ ባላውቀውም እእምሮዬ አጠቃላይ ሁኔታወችን በፍጥነት ደምሮና ቀንሶ ሐኑን ምን እንደምትፈልግ ገብቶት ነበር: አፍቅራ እዚህ መኖር አልነበረም
ፍላጎቷ፡፡ ከዚህ በጠቆረ ትዝታ ከጠቆረ ግቢ ብን ብላ መውጣት ነበር መሻቷ ልክ በውሃ በተከበበ ደሴት ላይ ተከባ መውጫ ላጣች ነፍስ፣ራሴን ከዚህ መውጫ ጀልባ ነኝ ብዬ አቀረብኩላት፤ ማቄን ጨርቄን ሳትል ጀልባዋ ላይ ወጣች!!
እጇ ትንሽ የተንቀጠቀጠ መሰለኝ ወይስ የእኔ ነው!? ከዚህ ቀን በኋላ ሐኑን እኔ
በፍቅር ከነፍን፡፡ ግን ፍቅር ነው ወይ እላለሁ፣ ራሴን አላምነውም፡፡ የአባቷ እግር ከቤት ከወጣ የሐኑን እግር እኔ በር ላይ ነው፡፡ ፍቅር እንደ እሳተ ገሞራ ነው- የተረጋጋውን ምድር፣በሰላም ለዘመናት ተኮፍሶ የኖረን የአለት ተራራ ሽቅብ ፈነቃቅሎት ሲወጣ፣ ብናኝና ጭሱ አካባቢውን ይሸፍነዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ገሞራ የፈነዳበት ምድር ወደነበረበት
ተፈጥሮው አይመለስም:: እዚያ ግቢ የዚያን ጊዜ የሆነው እንደዚያ ነበር፡፡ የፍቅር ገሞራው ሲፈነዳ፣ ብናኙ የሐኑንን ፊት ሸፈነው፡፡ረጋ ያለችው ልጅ፣ የምትይዝ
የምትጨብጠውን አጣች፡፡ ብናኙ ፈገግታ ሆኖ ፊቷን ሸፈነው…ብናኙ የመሻት ነበልባሉን ወደቤቴ ልኮ አለት ብቸኝነቴን አቀለጠው፡፡ የሐዘን ደመና ከውብ ፊቷ ላይ ተገፎ እንደጥዋት ፀሐይ ውብ ፈገግታ ሲረጭ ግቢውን እሳት ሞላው፣ደግሞ ግቢውን ውሃ ሞላው ግቢው በረሃ ሆነ ደግሞም ግቢዉ የኤደን ገነት ሆነ፣ በአንድ ጊዜ ሁሉም ነገር ሆነ፡፡ በዚህ ፍንዳታ ውስጥ ተረጋግተው ጫታቸውን የሚቅሙት አባቷ
ልጅ ትንሽ አትሞክርም? ይሉኛል ጫታቸውን እያሳዩኝ፡፡ “በዚህ ላይ ጫት
ተጨምሮበት” እላለሁ በውስጤ፡፡ አለመታመንኮ ነው ሰው ግቢ ገብቶ የሰው ሴት ልጅ - ያውም ያመኑት የአንድን ትልቅ ተቋም ሥራ አስኪያጅ ነው፣ ራሱን የገዛ ሰው ነው ያሉትን ሰው … ግን ደግሞ ቦታና ጊዜ፣ ሥራና ደረጃ፣ ፍቅር ፊት ምን ጉልበት አላቸው? ዋናው ጥያቄ ይኼ እብደት ፍቅር ነው ወይ ነው? ራሴን አላምነውም!
ሐኑን ጋር ዓይኖቻችን ተንሰፍስፈው ይፈላለጋሉ፡፡ ግድቡን እንደጣሰ ጎርፍ ራሷን መቆጣጠር አቅቷት ነበር፡፡ አንዳንዴ አባቷ እቤት እያሉ ጭምር ድንገት እቤቴ
ትመጣለች ፡፡
ኧረ አባባ እላለሁ በጭንቀት ድምፄን ቀንሸ፡፡
እየሰገደ ነው ትለኛለች፡፡ ከዛ እቅፌ ውስጥ ናት፡፡
ኧረ አባባ እላለሁ፣
ውጭ ስልክ እያወራ ነው ትላለች፡፡ ይሉኝ ነካክቼ እንደ አልኮል ያስከራትን ፍቅር
በምን ላረጋጋው? ዓይኗንም ልቧንም የሠወረው ፍቅር፣ሁለታችንንም አባቷ ዓይን ላይ ሊጥለን እያዳፋ የሚነዳ ደራሽ ጎርፍ ሆነብኝ፡፡ ፈጣን ነበር_ሁሉም ነገር በጣም ፈጣን እየተጨነቅሁ እሰማታለሁ፡፡ እያሰብኩ በደመነፍስ እጓዛለሁ፡፡ አንዳንዴ ሌሊት ትደውልልኛለች፡፡ ፍቅር ከጊዜ ሥርዓት ያፈነገጠ ስሜት መሆኑ የገባኝ ያን ጊዜ ነበር፡፡ ብዙ ከዛ በፊት ያልገባኝ ነገር የገባኝ ያኔ ነበር፤ ብዙ ከዛ በፊት ገብቶኛል ያልኩት ነገር የጠፋብኝም ያኔ ነበር፡፡ የመኝታ ቤቷ መስኮት እና የሳሎኔ መስኮት ትይዩ ስለሆነ መጋረጃችንን ሰብስበን ዝም ብለን እንተያያለን እስር ቤት ያሉ ነፍሶች ነበር የምንመስለው፡፡
እነዚያ ሌሊቶች መቼም የሚረሱኝ አይደሉም አንድ ምሽት ደረቅና ሞቃታማዋ ድሬዳዋ፣በድንገተኛ ዶፍ ዝናብ ተጥለቀለቀች፡፡ የድሬደዋ ሰማይ ግፏን አፍና እንደኖረች ሴት፣ ድንገት ነው አስፈሪ ዶፉን እንደ እንባ የሚዘረግፈው፡፡ ዝናቡ ከሰማይ ብቻ ሳይሆን፤ከምድርም ይፈልቅ ይመስል፣ ከምኔው ምድሩ በጎርፍ እንደሚጥለቀለቅ ይገርመኛል፡፡ የዚያን ቀን ዝናቡ ሌሊቱን ሙሉ አላቋረጠም፡፡ በየመኻሉ ሰማዩን ሰንጥቆ
አካባቢውን በብርሃን የሚያጥለቀልቅ የመብረቅ ብልጭታ የመስኮቴን መጋረጃ እያለፈ ቤቴን በብርሃን ይሞለዋል፡፡ በተደጋጋሚ ወገግ ይላል፡፡ ምን እንደገፋኝ እንጃ ፣ተነስቼ የመስኮት መጋረጃዬን ሰበሰብኩት፡፡ ሐኑን ልከ የተቀጣጠርን ይመስል መጋረጃዋን ስብስባ ውብ ጉርድ ፎቶ ግራፍ መስላ መስኮቱ ጋ ቆማ ነበር …በእያንዳንዱ ብልጭታ፣ የሐኑንን ውብ ፊት አእምሮየ እንደፎቶ እያተመ ያስቀምጣል፡፡ በግራ ትከሻዋ በኩል
አልፎ ጡቷ ላይ የሚርመሰመሰዉ ጸጉሯ ግማሽ ፊቷን የከበበ ጥቁር ፍሬም መሰሏል፡፡ እስከ ዛሬ ሐኑንን ሳስብ፣ ያ መልኳ ነው ቀድሞ የሚታወሰኝ፡፡ እንደ ቲማቲም የቀሉ ከንፈሮች ከመቅላቱ ብዛት በወርቃማ ቆዳ የተለበጠ የሚመስል ደረት…ሥዕል፡፡
በየመስኮት መስታዎቶቻችን ላይ የሚንኳለለው የዝናብ ውሃ፣ ነጋችንን አውቆ እርሙን የማያወጣ የዘመን እንባ ይመስል ነበር፡፡ ጡቶቿ ቢጫ የሚበዛበትን ባለብዙ አበባ ሥዕል፣ ስስ የሌሊት ልብሷን ወጥረው፣ ከተደገፈችዉ መስተዋት ጋር ጫፋቸው ተነካክቷል፡፡ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ አፍንጫዋ በመስተዋቱ እየተደፈጠጠ ያስቀኛል፡፡
እኔን በፈገግታ እያየች መስተዋቱን ስትስመው፣ቀያይ ውብ ከንፈሮቿ መስተዋቱ ላይ በክቡ ተለጥፈው፣ ትንፋሽዋ መስተዋቱ ላይ ጭጋግ ይፈጥራል፡፡ በትንፋሽዋ ጉም
በተሸፈነው መስተዋት ላይ፣በጣቷ የልብ ቅርጽ ትሥልበታለች ፡፡ትንፋሽዋ መስተዋቱ ላይ በሚፈጥረው ላቦት ምስሏ መደብዘዝ ሲጀምር፣ መስተዋቱን በመዳፏ ትወለውለዋለች፡፡ በዚህ ጊዜ የደበዘዘዉ ምስሏ ቦግ ብሎ ይወጣል፡፡ በቃ እንተያያለን፣ ያለድምፅ ዝም ብለን
መተያየት…በምልከት ልተኛ ነው ስላት በእጇ ትንሽ እንድቆይ ትለምነኛለች፡፡ያ ሌሊት በተደጋጋሚ ሕልሜ ይመጣል፡፡
መስተዋት ተደግፌ አድሬ፣ ሊነጋጋ ሲል ድብን ያለ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ጧት የቤቴ በር ሲከፈት እንኳን አልሰማሁም፡፡ በጧት እንደ እሳት የሚፋጅ ላሰላሳ ገላዋ፣ የሞቀ አልጋዬ ውስጥ ገብቶ ስትለጠፍብኝ ነበር የነቃሁት፡፡ በእንቅልፍ በሰከረ አእምሮዬ ላይ በሽቶ ባበደ ጠረኗ የታጀበ ሰውነቷ ሲያቅፈኝ፡ ነገሩ ሕልም ይሁን እውነት በወጉ እንኳን ሳይገባኝ፣ የሐኑን የሚንቀጠቀጡ ትኩስና ለስላሳ ከንፈሮት፣ ከንፈሬ ላይ አርፈው ነበር፡፡
ሰውነቴ ከእእምሮዩ ቀድሞ ነቃ፤ ረዥም በሰመመን የተሞሉ ደቂቃዎች ይሁኑ ሰዓታት ከሥሬ ሆና በለስላሳ ቀይ ፊቷ ቆዳ ላይ እንባዋ ኮለል ብሎ ወደ ጆሮዋ ሲወርድና በሕመም ስትቃትት፡ ሥጋዊ ወንድነቴ ከሚሰማው አብሮነት ይልቅ፡ አንዳች የነፍሴ ክፍል ላይ ነፍሷ ለዘላለም ሲነቀስ ይሰማኝ ነበር፡፡ አእምሮዬ በአንድ ጊዜ ሁለት ተቃራኒ ሐሳቦችን እያሰበ ነበር፡፡ እየተሳሳትኩ ነው” እና “ልክ ነኝ” የሚሉ ሐሳቦች፡፡ እንደዚያ ነበር የማስበው፡፡ አእምሮየ ምንም ያስብ ምን፡ ገና ከጅምሩ ሰውነቴ ለአእምሮዬ መታዘዙን ትቶት ነበር፡፡ ብዙ ሰው የሆንኩ እስኪመስለኝ ድረስ
👍1🔥1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ለመጀመሪያ ጊዜ ከወንድ ጋር የተኛች ሴት፣ እንዲህ ቁጭ ብድግ ስትል፣ ምን የተለየ ነገር ይሰማት ይሆን? የሚል ምርመራዬን በዓይኔ እየተከታተልኩ፡አባቷ ጋር የባጥ የቆጡን እናወራለን፡፡ የሚበዛው ወሬ ሱቃቸው ዉስጥ
ስለገባው ጎርፍ ነበር፡፡ ሐኑን ማረፍ ባለመቻሏ፣ የሆነ ደስ የማይል ነገር ቢፈጥርብኝም፣ አጠገቧ መሆኔ ግን ምቾት ሰጥቶኝ ነበር፡፡እርሷም ገብቷታል፡፡ አባባ ጎን ተቀምጣ፣ ሳወራ ታየኛለች፡፡ አስተያየቷ ሥጋን ዘልቆ ነፍሴ ድረስ የሚሰማ ሐዘን ይለቅብኝ ነበር፡፡ ዓይኖቻችን ሲጋጩ ዓይኖቿ ማረፊያ ያጣሉ፡፡
ከዚያን ቀን ጀምሮ፣ ሐኑን የምታደርገው ነገር ሁሉ ያስደነግጠኝ ነበር:: አንድ ቀን ድንገት የሥራ ቦታዬ መጣች፤ ደስታም ድንጋጤም ተቀላቀለብኝ፡፡ሰዎች እንዳይሰሙ ድምፅዋን ቀንሳ ናፈከኝ!” አለችኝ፤ እንዲያዉ የአባቷ ነገር እያስጨነቀኝ እንጂ፣ እኔም የምይዝ
የምጨብጠውን ነገር አላውቅም ነበር፡፡ እንደትኩስ ፍቅር ምን አደገኛ ነገር
አለ?…ፍቅራችን በጭንቀትና በጥንቃቄ የተሞላ ደስታ ነበር፡፡ ልክ የተከሰከሰ ጠርሙስ የተዘራበት ወለል ላይ በባዶ እግር እንደሚራመድ ሰው፣ እጅግ በጥንቃቄ፣ ግን ደግሞ ትንፋሽ የሚያሳጣ፣ አብረው ሆነው የሚያነፋፍቅ አንዳች ነገር፡፡ አንዳንዴ ከሐኑን ጋር
አንድ ግቢ ውስጥ ከመኖራችን እና ብዙውን ጊዜ አብረን ከማሳለፋችን የተነሳ፣ ግንኙነታቸን ከፍቅረኝነት ይልቅ ትዳር የሚመስል ቅርፅ ይይዝ ነበር፡፡ ልብሶቼን ላውንደሪ ወስዳ ትሰጥልኛለች፣ ምግብ አባባም ቢኖሩ ባይኖሩም ውጭ በልቼ ካልገባሁ እነሱ ጋር ነበር የምበላው፡
አንዳንድ ቀን አባባን ነግረናቸው ፣አብረን ወደ ገበያ እንሄዳለን፡፡ አባባ ሐኑንን ብቻዋን ከቤት አያስወጧትም፤ ወይ አብረዋት ይወጣሉ፣ አልያም አትወጣም፡፡ እኔ ጋር ግን ስትወጣ “ልጅ መንገድ ላይ እንዳትጠፋፉ እጇን ይዘህ አደራ! ከማለት ውጭ ምንም ቅሬታ ፊታቸው ላይ አይታይም ነበር፡፡ እንደውም አንዳንዴ 'አንች ልጅ ሰው ጋር
እንዳታጋጭው” ብለው ለእኔ ያስባሉ፡፡ ከግቢው እንደወጣን ሐኑን “
እጇን ያዛት ተብለሃልኮ ትልና ክንዴን ይዛ በሳቅ እየተፍለቀለቀች፣ በጋሪ ተሳፍረን ቀፊራ ወደሚባለው ገበያ እንሄዳለን፡፡ ንፋሱ ክንብንቧን ሊገፉት ሲታገል፣ ክንዴን ይዛ አንገቴ ስር ትሸጎጣለች፡፡ አብረን እስከሆንን ድረስ ጋሪው የትም ቢወስደን ግድ አልነበረንም፡፡ ቀፊራ ወርደን ከቴምር እስከጭሳጭስ፣ ከዶሮ እስከ ብርቱካን እንገዛለን፤ የሚበዛውን ጊዜ ግን እንዲሁ በመዞር ነበር የምናሳልፈው፡፡ እየተነሳ ፊት ላይ በሚሞጀረው አቧራ ውስጥ፣
በጫጫታውና ግርግሩ ውስጥ፣ በእነዛ ጎሊቶች መሃል ሐኑን ቀይ ሽቲ በቀይ ሻርፕ
ለብሳ(ብዙ ጊዜ ስትወጣ እንደዛ ነበር የምትለብሰው) ተያይዘን ስንዞር ውለን
የሸመትነውን ጭነን፣ በጋሪ ወደ ቤት ስንመለስ በደመና ሰረገላ ላይ ተጭነን ወደ ሰማየ ሰማያት የምንመጥቅ እስኪመስለኝ፣ደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡
ሁሉም ነገር የተረጋጋ፣ ደሰ የሚልና ሰላም የሰፈነበት፣ ሕልም የሚመስል ሕይወት ነበር፡፡የሐኑን አባት እልፎ አልፎ አልጋ ላይ ከሚጥላቸው ሕመም በስተቀር፣ሁሉ ሰላም ነበረ:: የሰላም ትክክለኛ ትርጉም ረብሻ አለመኖር እይደለም፣ መነሻው ፍቅር የሆነ ረብሻ በነፍስ ውስጥ እንደመዓበል መተራመሱ ነው፡፡ ፍቅር የሌለው ሰላም ውሃው እንደደረቀ ወንዝ
ነው፡፡ በሰላም ውስጥ ወንዝ መፍሰስ አለበት ፣ወንዙን ሊሻገሩ የሚታገሉ ነፍሶት መኖር አለባቸው፤ በውሃው ውስጥ የሚጋጩ የሚሳሳሙ ድንጋዮች መኖር አለባቸው፣አሳዎች መኖር አለባቸው፡፡ ሰላም ነበረን እኔና ሐኑን፡፡
አባቷ ህመማቸው ቶሎ ቶሎ ባይነሳባቸውም ሲያማቸው ግን የሚያስደነግጥ ነበር፡፡ ደግሞ ለከፉቱ ቀድሞ አፋቸውን ነው የሚይዛቸው፡፡ እኔ እዛ ቤት ከተከራየሁ እንኳን ይኸው ሕመም ሁለት ጊዜ ሲያማቸው አጋጥሞኝ ነበር፡፡ ከስኳር ሕመም ጋር የተያያዘ
መሆኑን ነግረውኛል፡፡ደግነቱ ብዙ አይቆይባቸውም ነበር፡፡ ሐኑን የአባቷ ነገር
እይሆንላትም፡፡ በምድር ላይ ያሏት ብቸኛ ዘመድ እሳቸው ናቸው ፡፡ አባቷ ከወንድሞቿና ከእህቶቿ ጋር እንድትቀራብ ያላደረጉት ጥረት የለም፡፡ ይሄንኑ ነገር አንድ ጊዜ፣ በጣም ከተቀራፈብን በኋላ በሐዘን ነግረውኛል
“መቼስ! ሰው ይሳሳታል፤ አንዴ እጠፋሁ፣አባት ላይ ይጨከናል? እሷስ እህታቸው እይደለችም? ቤቱ እንደሆነ እንኳን ለነሱ ለባዳውም ይበቃል፡፡ እንዴት እህታቸውን ካለዘመድ ያስቀሯታል? ዕድሜዬም ገፍቷል፡ በሽታውም እየበረታብኝ ነው፡፡ድንገት
አላሀ በቃህ ካለኝ እች ልጅ ብቻዋን እንዳትቀር ብየ፣ እኔ ቁልቁል ወደ ልጆቼ ታረቁኝ ብዬ ሽማግሌ ብልክክ አከላፍተው መለሷቸው፡፡ መቼስ በእኔ አይጨከኑም ብዬ ራሴዉ ብሄድ፡ የተቀመጥኩበት እየጣሉኝ ወጡ፡፡ ልቤ አዘነ፤ ግን ኤልረገምኳቸውም፣ሥጋ
ናቸዋ አባት ቢያጠፋስ ይኼ ተገቢ ነው? ድፍን ድሬዳዋ ይጠየቅ፣ አንቀባርሬ ነው
ያሳደኳቸው፡፡ አሜሪካ ሲሉ፤ አውሮፓ … እንሂድ ሲሉ ልኬ፣ ካለወጉ ከድሬደዋ አሜሪካ ብር እየላኩ ያስተማርኳቸው እኔ ነኝ፡፡ እኔስ እሺ፡ በድያቸው ይሆናል፣ እዚች አንድ ፍሬ ልጅ ላይ ይጨከናል? እንኳን ሥጋው ሁና፣ ይችን ልጅ አያቶ የሚጨከን መገደኛ አለ አነጋገራቸው ያሸብራል ሽማግሌ ፊታቸው ላይ የሚያንዣብበው ሐዘን…ማረፊያ አጥተው ዙሪያ ገባው ላይ የሚንከራተቱት ዓይኖቻቸው፣ አንጀት ይበሉ ነበር፡፡
ከአራት ዓመታት የድሬዳዋ ቆይታ በኋላ፣ ዋናው መሥሪያ ቤት ድንገት ወደ አዲስ አበባ ሲጠራኝ ትንሿ ገነታችን ጨለማ አጠላባት፡፡ ከሐኑን ጋር መለያየት ገደል ቢሆንብኝም፣ ወደ አዲስ አበባ መመለስ የረዥም ጊዜ ምኞቴ ነበርና ማቄን ጨርቄን አላልኩም፡፡
ሐኑንም እንደምሄድ ካወቀችበት ቀን ጀምሮ ከቤቴ ቀረች፡፡ ድንገት ግቢ ውስጥ ስንገናኝ እንኳን፣ ድንብርብሬ ወጥቶ ትሸሸኛለች፡፡ አንድ ቀን ታዲያ አባባ ወጣ ሲሉ ጠብቄ ወደ ትልቁ ቤት ሄድኩ፡፡ ስገባ የተንጣለለው ሳሎን ውስጥ፣ አልጋ የሚያክለው ሰፊ ሶፋ ላይ ኩርምት ብላ ተቀምጣ አገኘኋት፡፡ ምንም እየሰራች አልነበረም፡፡እንደ ወትሮው
ቴሌቪዥን አልተከፈተም፤ በቃ ቁጭ ብላ ባዶው ላይ አፍጥጣለች፡፡ እጇ ላይ
የምታምር፣ እንደሷ ፊት ብርሃን የሚረጩ ጠጠሮች የተሰከሰኩባት መቁጠሪያ ይዛ
ነበር፡፡ ድንገት ስገባ የምታደርገው ግራ ገብቷት፣ ተነስታ ቆመችና ዝም ብላ ስታየኝ ቆይታ በቆመችበት እንባዋ መውረድ ጀመረ፡፡ አቀፍኳት! ለረዥም ደቂቃ አቅፈያት ቆምኩ፡፡ ደረቴ ላይ ሸሚዜን አልፎ የትኩስ እንባዋ እርጥበት ይሰማኝ ነበር፡፡
ሐኑን አዲስ አበባ እንደደረስኩ ቤት እከራያለሁ፣ ነገሮችን አመቻችቶ በአንድ ወር ውስጥ እመለሳለሁ”
“ለምን?”
“ምን ማለት ነው ለምን አባባን እንነግራቸዋለን እንጋባለን!
በቁጣ ከእቅፌ ወጥታ ራቅ አለችና፣ በትልልቅ ዓይኖቿ አፍጥጣብኝ "አትዋሸኝ እኔ እዚህ ባዶ ግቢ ውስጥ ሌላ ተስፋ የለኝም፣ የምጠብቀው አንተን ነበር የማትመለስ ከሆነ እኔን ለማጽናናት ብለህ አትዋሽ”
እልዋሽሽም እዚህ ሁልጊዜ በስጋት ከመኖር፣ አዲስ አበባ እወስድሽና ተጋብተን በሰላም እንኖራላን፣ እመለሳለሁ፡ ቶሎ እመለሳለሁ፣በጣም ቢበዛ ሁለት ወር፣ ለአንቺ ስል አይደለም፣ ለራሴ ነው፤ አፈቅርሻለሁ! ያላንቺ መኖር አልችልም፡፡አንቺ ጋር ስሆን ደስተኛ ነኝ ሐኑን ከልቤ ነበር፡፡ ያልኳትን ሁሉ ያልኳት ከልቤ ነበር፡፡
“ታዲያ ካፈቀርከኝ ለምን ትሄዳለህ? ደስተኞች ነን፣ ጥሩ ስራ አለህ አባባን ንገረውና
“መማር አለብኝ፡ መለወጥ አለብኝ፣ ከተጠራሁ ደግሞ መሄድ ግዴታዩም ነው”
“ለምንድነው ከተጠራሁ የምትለው?እነሱ ብዙ ሠራተኛ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ለመጀመሪያ ጊዜ ከወንድ ጋር የተኛች ሴት፣ እንዲህ ቁጭ ብድግ ስትል፣ ምን የተለየ ነገር ይሰማት ይሆን? የሚል ምርመራዬን በዓይኔ እየተከታተልኩ፡አባቷ ጋር የባጥ የቆጡን እናወራለን፡፡ የሚበዛው ወሬ ሱቃቸው ዉስጥ
ስለገባው ጎርፍ ነበር፡፡ ሐኑን ማረፍ ባለመቻሏ፣ የሆነ ደስ የማይል ነገር ቢፈጥርብኝም፣ አጠገቧ መሆኔ ግን ምቾት ሰጥቶኝ ነበር፡፡እርሷም ገብቷታል፡፡ አባባ ጎን ተቀምጣ፣ ሳወራ ታየኛለች፡፡ አስተያየቷ ሥጋን ዘልቆ ነፍሴ ድረስ የሚሰማ ሐዘን ይለቅብኝ ነበር፡፡ ዓይኖቻችን ሲጋጩ ዓይኖቿ ማረፊያ ያጣሉ፡፡
ከዚያን ቀን ጀምሮ፣ ሐኑን የምታደርገው ነገር ሁሉ ያስደነግጠኝ ነበር:: አንድ ቀን ድንገት የሥራ ቦታዬ መጣች፤ ደስታም ድንጋጤም ተቀላቀለብኝ፡፡ሰዎች እንዳይሰሙ ድምፅዋን ቀንሳ ናፈከኝ!” አለችኝ፤ እንዲያዉ የአባቷ ነገር እያስጨነቀኝ እንጂ፣ እኔም የምይዝ
የምጨብጠውን ነገር አላውቅም ነበር፡፡ እንደትኩስ ፍቅር ምን አደገኛ ነገር
አለ?…ፍቅራችን በጭንቀትና በጥንቃቄ የተሞላ ደስታ ነበር፡፡ ልክ የተከሰከሰ ጠርሙስ የተዘራበት ወለል ላይ በባዶ እግር እንደሚራመድ ሰው፣ እጅግ በጥንቃቄ፣ ግን ደግሞ ትንፋሽ የሚያሳጣ፣ አብረው ሆነው የሚያነፋፍቅ አንዳች ነገር፡፡ አንዳንዴ ከሐኑን ጋር
አንድ ግቢ ውስጥ ከመኖራችን እና ብዙውን ጊዜ አብረን ከማሳለፋችን የተነሳ፣ ግንኙነታቸን ከፍቅረኝነት ይልቅ ትዳር የሚመስል ቅርፅ ይይዝ ነበር፡፡ ልብሶቼን ላውንደሪ ወስዳ ትሰጥልኛለች፣ ምግብ አባባም ቢኖሩ ባይኖሩም ውጭ በልቼ ካልገባሁ እነሱ ጋር ነበር የምበላው፡
አንዳንድ ቀን አባባን ነግረናቸው ፣አብረን ወደ ገበያ እንሄዳለን፡፡ አባባ ሐኑንን ብቻዋን ከቤት አያስወጧትም፤ ወይ አብረዋት ይወጣሉ፣ አልያም አትወጣም፡፡ እኔ ጋር ግን ስትወጣ “ልጅ መንገድ ላይ እንዳትጠፋፉ እጇን ይዘህ አደራ! ከማለት ውጭ ምንም ቅሬታ ፊታቸው ላይ አይታይም ነበር፡፡ እንደውም አንዳንዴ 'አንች ልጅ ሰው ጋር
እንዳታጋጭው” ብለው ለእኔ ያስባሉ፡፡ ከግቢው እንደወጣን ሐኑን “
እጇን ያዛት ተብለሃልኮ ትልና ክንዴን ይዛ በሳቅ እየተፍለቀለቀች፣ በጋሪ ተሳፍረን ቀፊራ ወደሚባለው ገበያ እንሄዳለን፡፡ ንፋሱ ክንብንቧን ሊገፉት ሲታገል፣ ክንዴን ይዛ አንገቴ ስር ትሸጎጣለች፡፡ አብረን እስከሆንን ድረስ ጋሪው የትም ቢወስደን ግድ አልነበረንም፡፡ ቀፊራ ወርደን ከቴምር እስከጭሳጭስ፣ ከዶሮ እስከ ብርቱካን እንገዛለን፤ የሚበዛውን ጊዜ ግን እንዲሁ በመዞር ነበር የምናሳልፈው፡፡ እየተነሳ ፊት ላይ በሚሞጀረው አቧራ ውስጥ፣
በጫጫታውና ግርግሩ ውስጥ፣ በእነዛ ጎሊቶች መሃል ሐኑን ቀይ ሽቲ በቀይ ሻርፕ
ለብሳ(ብዙ ጊዜ ስትወጣ እንደዛ ነበር የምትለብሰው) ተያይዘን ስንዞር ውለን
የሸመትነውን ጭነን፣ በጋሪ ወደ ቤት ስንመለስ በደመና ሰረገላ ላይ ተጭነን ወደ ሰማየ ሰማያት የምንመጥቅ እስኪመስለኝ፣ደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡
ሁሉም ነገር የተረጋጋ፣ ደሰ የሚልና ሰላም የሰፈነበት፣ ሕልም የሚመስል ሕይወት ነበር፡፡የሐኑን አባት እልፎ አልፎ አልጋ ላይ ከሚጥላቸው ሕመም በስተቀር፣ሁሉ ሰላም ነበረ:: የሰላም ትክክለኛ ትርጉም ረብሻ አለመኖር እይደለም፣ መነሻው ፍቅር የሆነ ረብሻ በነፍስ ውስጥ እንደመዓበል መተራመሱ ነው፡፡ ፍቅር የሌለው ሰላም ውሃው እንደደረቀ ወንዝ
ነው፡፡ በሰላም ውስጥ ወንዝ መፍሰስ አለበት ፣ወንዙን ሊሻገሩ የሚታገሉ ነፍሶት መኖር አለባቸው፤ በውሃው ውስጥ የሚጋጩ የሚሳሳሙ ድንጋዮች መኖር አለባቸው፣አሳዎች መኖር አለባቸው፡፡ ሰላም ነበረን እኔና ሐኑን፡፡
አባቷ ህመማቸው ቶሎ ቶሎ ባይነሳባቸውም ሲያማቸው ግን የሚያስደነግጥ ነበር፡፡ ደግሞ ለከፉቱ ቀድሞ አፋቸውን ነው የሚይዛቸው፡፡ እኔ እዛ ቤት ከተከራየሁ እንኳን ይኸው ሕመም ሁለት ጊዜ ሲያማቸው አጋጥሞኝ ነበር፡፡ ከስኳር ሕመም ጋር የተያያዘ
መሆኑን ነግረውኛል፡፡ደግነቱ ብዙ አይቆይባቸውም ነበር፡፡ ሐኑን የአባቷ ነገር
እይሆንላትም፡፡ በምድር ላይ ያሏት ብቸኛ ዘመድ እሳቸው ናቸው ፡፡ አባቷ ከወንድሞቿና ከእህቶቿ ጋር እንድትቀራብ ያላደረጉት ጥረት የለም፡፡ ይሄንኑ ነገር አንድ ጊዜ፣ በጣም ከተቀራፈብን በኋላ በሐዘን ነግረውኛል
“መቼስ! ሰው ይሳሳታል፤ አንዴ እጠፋሁ፣አባት ላይ ይጨከናል? እሷስ እህታቸው እይደለችም? ቤቱ እንደሆነ እንኳን ለነሱ ለባዳውም ይበቃል፡፡ እንዴት እህታቸውን ካለዘመድ ያስቀሯታል? ዕድሜዬም ገፍቷል፡ በሽታውም እየበረታብኝ ነው፡፡ድንገት
አላሀ በቃህ ካለኝ እች ልጅ ብቻዋን እንዳትቀር ብየ፣ እኔ ቁልቁል ወደ ልጆቼ ታረቁኝ ብዬ ሽማግሌ ብልክክ አከላፍተው መለሷቸው፡፡ መቼስ በእኔ አይጨከኑም ብዬ ራሴዉ ብሄድ፡ የተቀመጥኩበት እየጣሉኝ ወጡ፡፡ ልቤ አዘነ፤ ግን ኤልረገምኳቸውም፣ሥጋ
ናቸዋ አባት ቢያጠፋስ ይኼ ተገቢ ነው? ድፍን ድሬዳዋ ይጠየቅ፣ አንቀባርሬ ነው
ያሳደኳቸው፡፡ አሜሪካ ሲሉ፤ አውሮፓ … እንሂድ ሲሉ ልኬ፣ ካለወጉ ከድሬደዋ አሜሪካ ብር እየላኩ ያስተማርኳቸው እኔ ነኝ፡፡ እኔስ እሺ፡ በድያቸው ይሆናል፣ እዚች አንድ ፍሬ ልጅ ላይ ይጨከናል? እንኳን ሥጋው ሁና፣ ይችን ልጅ አያቶ የሚጨከን መገደኛ አለ አነጋገራቸው ያሸብራል ሽማግሌ ፊታቸው ላይ የሚያንዣብበው ሐዘን…ማረፊያ አጥተው ዙሪያ ገባው ላይ የሚንከራተቱት ዓይኖቻቸው፣ አንጀት ይበሉ ነበር፡፡
ከአራት ዓመታት የድሬዳዋ ቆይታ በኋላ፣ ዋናው መሥሪያ ቤት ድንገት ወደ አዲስ አበባ ሲጠራኝ ትንሿ ገነታችን ጨለማ አጠላባት፡፡ ከሐኑን ጋር መለያየት ገደል ቢሆንብኝም፣ ወደ አዲስ አበባ መመለስ የረዥም ጊዜ ምኞቴ ነበርና ማቄን ጨርቄን አላልኩም፡፡
ሐኑንም እንደምሄድ ካወቀችበት ቀን ጀምሮ ከቤቴ ቀረች፡፡ ድንገት ግቢ ውስጥ ስንገናኝ እንኳን፣ ድንብርብሬ ወጥቶ ትሸሸኛለች፡፡ አንድ ቀን ታዲያ አባባ ወጣ ሲሉ ጠብቄ ወደ ትልቁ ቤት ሄድኩ፡፡ ስገባ የተንጣለለው ሳሎን ውስጥ፣ አልጋ የሚያክለው ሰፊ ሶፋ ላይ ኩርምት ብላ ተቀምጣ አገኘኋት፡፡ ምንም እየሰራች አልነበረም፡፡እንደ ወትሮው
ቴሌቪዥን አልተከፈተም፤ በቃ ቁጭ ብላ ባዶው ላይ አፍጥጣለች፡፡ እጇ ላይ
የምታምር፣ እንደሷ ፊት ብርሃን የሚረጩ ጠጠሮች የተሰከሰኩባት መቁጠሪያ ይዛ
ነበር፡፡ ድንገት ስገባ የምታደርገው ግራ ገብቷት፣ ተነስታ ቆመችና ዝም ብላ ስታየኝ ቆይታ በቆመችበት እንባዋ መውረድ ጀመረ፡፡ አቀፍኳት! ለረዥም ደቂቃ አቅፈያት ቆምኩ፡፡ ደረቴ ላይ ሸሚዜን አልፎ የትኩስ እንባዋ እርጥበት ይሰማኝ ነበር፡፡
ሐኑን አዲስ አበባ እንደደረስኩ ቤት እከራያለሁ፣ ነገሮችን አመቻችቶ በአንድ ወር ውስጥ እመለሳለሁ”
“ለምን?”
“ምን ማለት ነው ለምን አባባን እንነግራቸዋለን እንጋባለን!
በቁጣ ከእቅፌ ወጥታ ራቅ አለችና፣ በትልልቅ ዓይኖቿ አፍጥጣብኝ "አትዋሸኝ እኔ እዚህ ባዶ ግቢ ውስጥ ሌላ ተስፋ የለኝም፣ የምጠብቀው አንተን ነበር የማትመለስ ከሆነ እኔን ለማጽናናት ብለህ አትዋሽ”
እልዋሽሽም እዚህ ሁልጊዜ በስጋት ከመኖር፣ አዲስ አበባ እወስድሽና ተጋብተን በሰላም እንኖራላን፣ እመለሳለሁ፡ ቶሎ እመለሳለሁ፣በጣም ቢበዛ ሁለት ወር፣ ለአንቺ ስል አይደለም፣ ለራሴ ነው፤ አፈቅርሻለሁ! ያላንቺ መኖር አልችልም፡፡አንቺ ጋር ስሆን ደስተኛ ነኝ ሐኑን ከልቤ ነበር፡፡ ያልኳትን ሁሉ ያልኳት ከልቤ ነበር፡፡
“ታዲያ ካፈቀርከኝ ለምን ትሄዳለህ? ደስተኞች ነን፣ ጥሩ ስራ አለህ አባባን ንገረውና
“መማር አለብኝ፡ መለወጥ አለብኝ፣ ከተጠራሁ ደግሞ መሄድ ግዴታዩም ነው”
“ለምንድነው ከተጠራሁ የምትለው?እነሱ ብዙ ሠራተኛ
👍1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
በእርግጥ አባቴን ፍሪ መሠረተ ትምህርት እስከ ሦስተኛ ከፍል ተምሯል ውብ ሳቋ
ቤቱን ሞላው፡፡
''ቡና ላፍላልህ ?” አብሪያት ብዙ እንድቆይ ስትፈልግ መደለያዋ ቡና ነበር፡፡ ቡና ሲፈላ ተረጋግቼ ቁጭ እላለሁ፡፡ ታውቃለች።
አባባ ሲመጡ አፍልተሸ ከጠራሽኝ - እመጣለሁ
ልጅ ዛሬ የሰንብት አትቅምም…” ብላ ቀለደች
እንኳን ጫት ጨምሬበት ልጅዎን ሳያት እየመረቀንኩ ተቸግሬያለሁ' አልኩ፣ በአባባ ድምፅ፡፡ከንፈሯን እንደገና ስሚያት ወጥቼ ወደ ቤቴ ገባሁ፡፡ በቀጣዩ ቀን ከእንቅልፌ ስነሳ ሐኑን አልጋየ አጠገብ ወንበር ላይ ተቀምጣ ትክ ብላ እያየችኝ ነበር፡፡
ትተኸኝ አትሂድ!”
ድፍን ሦስት ዓመታት ከድሬዳዋ ሰማይ ሥር፣ አንዲት እንደ ላባ የለሰለሰች ነፍስ፣
እንዲህ በፍቅር አውሎ ንፋስ እየተንሳፈፈች ነበር፡፡ በሰላም በምትኖርበት ግቢ እንደነፋስ
በሽንቁር ገብቼ ነፍሷን በአየር ላይ እንዳንሳፈፍኳት፣ በዚያው በተስቀለችበት የኋሊት ትቻት፣ ወደ አዲስ አበባ ተመለስኩ፡፡የሚወስደኝ መኪና በር ላይ
መጥቶ ሲቆም፣ አንድ ሽማግሌ ከቆንጆ ልጃቸው ጋር፣ ትልቁ የግቢ በር ላይ ቁመው እጃቸውን ለስንብት
ሲያውለበልቡልኝ ከእንባዬ ጋር እየታገልኩ ነበር፡፡ “ምን ፈልጌ ነው የምሄደው? ምን? እያልኩ ለራሴ፡፡ ድሬዳዋን ለቅቄ ስወጣ እንደ ጥይት ከምትወነጨፈው መኪና ግራና
ቀኝ ወደ ኋላ የሚሮጡ የሚመስሉት ቁጥቋጦና ድንጋዮች፣ አንዲት ሚስኪን አፍቃሪ ባዶ ግቢ ዉስጥ ትቼ መሄዴን ሰምተው ሊያፅናኗት ወደ እሷ የሚሮጡ ይመስሉ ነበር፡፡ ከሩቅ አፍቃሪ የቅርብ ድንጋይና ቁጥቋጦ ይሻላል የሚሉ ዓይነት፡፡
አዲስ አበባ የጠበቀኝ ገና አዲስ ተከፍቶ ውጥንቅጡ የወጣ ቅርንጫፍ ነበር፡፡ ሙሉ ቀን የማያባራ ችግር የደንበኞች ንጭንጭ የማይለየው ባንክ፡፡ ለዚሁ ቅርንጫፍ ነው እንግዲህ እድግት ብለው ያመጡኝ፡፡ ገና ከመድረሴ በሥጋም በነፍስም ሥራየ ላይ ተጠመድኩ፡፡ ሠራተኞቹ በሙሉ አዲስ ነበሩ፡፡ ሚስኪን የኒቨርስቲ ተመራቂዎች። ሁሉም ነገር ላይ የተሳሳቱ የሚመስላቸው፤ ሁሉም ደንበኛ ብር ሊያወጣና ሊያስገባ
ሳይሆን ሊያጭበረብርና ሊዘርፍ የመጣ የሚመስላቸው ስጉ ነፍሳት፡፡ እእምሯቸው ቁጥር ስፍር በሌለው ሕግ ማስጠንቀቂያ ተሞልቶ በፍርሀት የተሸበበ፡፡ የማይጠይቁኝ ጥያቄ አልነበረም፡፡ እንዳንዴማ ከረባት አስተሳሰር ሁሉ ይጠይቁኝ ነበር።
በተደጋጋሚ ዋናው መሥሪያ ቤት የሚያግዘኝ ሰው እንዲልኩልኝ ብወተውትም፣ ለአንድ ወር ብቻየን ፍዳዩን አበሉኝ፡፡ሲሳካልህ ለማጨብጨብ ከወደቅህም ትችታቸውን
እንደለይፍ ለመምዘዝ ጥጋቸውን ይዘው እንደሚመለከቱ ሥራ አሥኪያጆች የሚያስጠላኝ ፍጥረት የለም፡፡ የኔዎቹ እንደዛ ነበሩ፤ ስልክ እየደወሉ “በአንተ እንተማመናለን ይሉኛል አድናቆት እንደሙዳ ስጋ እየወረወሩ የቢዝነስ አጥራቸውን ሲያስጠብቁኝ ሊያድሩ
ይዳዳቸዋል፡፡ እያመሸሁ ከመሥራት አልፎ ቅዳሜ ሳይቀር እየገባሁ ለመሰራት ተገድጄ ነበር፡፡ በእነዚህ ጊዚያት እንኳንስ ለሐኑን ቃል እንደገባሁት ቤት ልከራይ ቀርቶ፣ ቀልቤን ሰብስቤ ጓደኞቼን እንኳን ማግኘት አልቻልኩም ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ ሲብስብኝ፡ ወደ ሥራ እስኪያጁ ቢሮ በአካል ሄጀ ከዚህ በኋላ ሰው ካልመደባችሁ ምንም ማድረግ አልችልም አልኩት፡፡
በቀጣዩ ሳምት በወረቀት ተከብቤ ባቀረቀርኩስት፣ በመስተዋት የተከለለች በር አልባ ቢሮዬን አልፋ አንዲት ሴት እፊቴ ተገተረች፡፡ መጀመሪያ ያየሁት፣ ከጉልበቷ በላይ በቀረ ጉርድ ጥቁር የቢሮ ቀሚሷ ምክንያት የተጋለጡትን ጠይምና ውብ እግሮቿን ነበር፡፡ ቀና ብዬ ፈገግ ለማለት ሞከርኩ፡፡ ፈገግ ብላ በስሜ ጠራችኝ፡፡ ግር እያለኝ “አቤት! ምን ልታዘዝ? እልኳት፡፡ እየተፍለቀለቀች
"እራስህ ምን ልታዘዝ ከሰላም ቢሮ አፈናቅልህ ያስመጣሃኝ አንተኮ ነሆ" ተሳሳቅን፡፡
ከዋናው መሥሪያ ቤት አዲስ የተላከች ልጅ ነበረች፡፡ ቀደም ብዬ አንዲት ሴት
እንደምትመጣ ብሰማም እንዲህ ወጣት ትሆናለች ብዬ አልጠበኩም ነበር፡፡ ምክንያቱም ስለሷ ጉብዝና አጋነው ነበር የነገሩኝ፡፡ “ሔራን እባላለሁ ቦስ! ትርፍ ወንበር ነገር የላችሁም” ብላ ዙሪያውን ተመለከተችና፣ ጥግ ላይ ከተቀመጡት ተሽከርካሪ ወንበሮች አንዱን ራሷ እየገፋች መጥታ፣ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች፡፡ እንደ ደም የቀላ ትልቅ የቆዳ ቦርሳዋን ከስሯ አሰቀመጠችና እሺ እንዴት እየሄደ ነው? ብላ ፈገግ አለች፡፡ ጠይም ቆዳዋ ጥራቱ የሚገርም ነው፡፡ጠይም ነበልባል፡፡ ደስ የሚል ወርቃማ ቀለም የተቀባዉ
ረዥም ጸጉሯ፡ መጀመሪያ ላይ የራሷ አልመሰለኝም ነበር …ስትስቅ እስከ ጆሮ ግንዷ ደርሰው የሚመለሱ ትልልቅ እና የሚያምሩ ከንፈሮቿ ከውብ ጥርሶቿ ጋር ተዳምረው ፈገግታዋ የልብ ያደርሳል” የሚባልላት ዓይነት አድርገዋታል፡፡ ቁመቷ ዘለግ ያለ ነው፡፡ በዝያ ላይ ውብ ቅርጽ፤ ስትናገርም ስትንቀሳቀስም ፈጣን፡፡ እንዲህ ነበር የመጀመሪያዉ ትውውቃችን፡
ሔራን ባንከ ውስጥ ተወልዳ ያደገች እስኪመስለኝ፣ እያንዳንዱ ሥራ በደም ሥሯ ውስጥ የሚፈስ ነበር የሚመስለው፡ በዛ ላይ ላለሁበት ቦታ የነበራት አክብሮትና ስርዓት እስገራሚ ነበር፡፡ በአጭር ቃል ብቻዬን ከመራወጥ አሳረፈችኝ፡፡ ተመድባ በመጣትች
በአስራ አምስት ቀኗ፣ አስር ጊዜ እየተቆራረጠ ካስመረረኝ የኮምፒውተር ሲስተም እስከ ፋይል ዝግጅት፣ ነገሮችን በሚገርም ፍጥነትና ብቃት ቦታ ቦታቸዉን አስያዘችልኝ፡፡ በተለይ እነዚያን ውሃ ቀጠነ ብለው የሚጨቃጨቁ ደንበኞች፣ በዛ ውብ ፈገግታዋ ውሃ ቸልሳባቸው፣ አረጋግታ ስታባርራቸው ተገርሜ እመለከት ነበር፡፡ ሲጀመር ከእሷ ጋር
ሲያወሩ፣ ከሌሎቹ ጋር እንደሚያወሩት አይቆጡም ኃላፊዎቻችንም ሴት ሳይወዱ
አይቀሩም መሰለኝ፤ እኔ ለሳምንት ተነዛንዤ ምላሽ የሚሰጡበትን ጉዳይ፣ ሔራን ደውላ ምን እንደምትላቸው እንጃ፡ ጠዋት ደውላ ከሰዓት በኋላ ይጨርሱታል ስንት ጊዜ ስነዛነዝ ቸል ያሉኝ የኮምፒውተር ባለሙያዎች ተንጋግተው መጥተው ሲስተሙን
አስተካክለውልን የሄዱት በአንድ ስልከ ጥሪ ነበር፡፡ በእርግጥ እኔ በኃላፊነት
በተቀመጥኩበት ቦታ አንዲት የበታች ሰራተኛ የበለጠ መሰማቷ የፈጠረብኝ ለስላሳ ቅሬታ ነበር፡፡ ምናልባት ከአንዱ ኃላፊ ጋር ነገር ይኖራት ይሆናል” ብዬ እስክጠረጥር፡፡ በኋላ በደንብ ሳውቃት ነው ልጅቱ ለማሳመን የተፈጠረች መሆኗን ያመንኩት፡፡
ከሐኑን ጋር በየቀኑ እናወራ ነበር፡፡ ባለኝ ክፍት ሰዓት ሁሉ እደውልላታለሁ፣ ያለውን
ነገር እነግራታለሁ፡፡ ይግባት አይግባት ባላውቅም፣ ዝም ብላ ትሰማኛለች፡፡ ምንጊዜም ከወሪያችን በኋላ ጥያቄዋ የታወቀ ነበር፡፡ ግን ትመጣለህ አይደል?” እውነት ነበራት::
በአንድ ወር ውስጥ ቤት ተከራይቼ እመለሳለሁ ያልኩት ልጅ፣ ቤተሰቦቼ ቤት እየኖርኩ ሦስት ወራት አለፉ፡፡ በመጨሻ እሷ ሰው አታጣም ብዬ ቤት መከራየት እንደምፈልግ ለሔራን ነገርኳት፡፡ አብረን ምሳ መብላት ጀምረን፣ ተቀራርበን ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን እየተፍለቀለቀች መጥታ እንኳን ደስ ያለህ ቦስ… ቤት ተገኝቶልሃል፡፡ አሪፍ ባለ አንድ መኝታ፣ አንደኛ ፎቅ ላይ ከሥራ እንደወጣን ወሰደችኝ፡፡ቤቱን ወደድኩት፡፡ በቀጣዩ ቀን የሶስት ወር የቤት ኪራይ ከፍዬ ተገላገልኩ፡፡ ቤት መከራየቴን ለቤተሰቦቼ ስነግራቸው እዚህ ምን አጥተህ ነው በኪራይ የምትገፈገፈው ?” ብለው ትንሽ
አጉረመረሙ፡፡ ግን ብዙ አልተጫኑኝም “
ለሥራውም ለምኑም ብቻውን መሆን
ካስፈለገው አለች እናቴ “ለምኑም” ስትል ድምፅዋ ውስጥ ትንሽ አሽሙር ነበረች
“ይሁና ብሉ ዝም አለ! አባቴ፡፡
ሔራን እና እቃህን መቸ ልታስገባ ነው?” አለችኝ፤እቃ መግዛቱንም ረስቼው ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
በእርግጥ አባቴን ፍሪ መሠረተ ትምህርት እስከ ሦስተኛ ከፍል ተምሯል ውብ ሳቋ
ቤቱን ሞላው፡፡
''ቡና ላፍላልህ ?” አብሪያት ብዙ እንድቆይ ስትፈልግ መደለያዋ ቡና ነበር፡፡ ቡና ሲፈላ ተረጋግቼ ቁጭ እላለሁ፡፡ ታውቃለች።
አባባ ሲመጡ አፍልተሸ ከጠራሽኝ - እመጣለሁ
ልጅ ዛሬ የሰንብት አትቅምም…” ብላ ቀለደች
እንኳን ጫት ጨምሬበት ልጅዎን ሳያት እየመረቀንኩ ተቸግሬያለሁ' አልኩ፣ በአባባ ድምፅ፡፡ከንፈሯን እንደገና ስሚያት ወጥቼ ወደ ቤቴ ገባሁ፡፡ በቀጣዩ ቀን ከእንቅልፌ ስነሳ ሐኑን አልጋየ አጠገብ ወንበር ላይ ተቀምጣ ትክ ብላ እያየችኝ ነበር፡፡
ትተኸኝ አትሂድ!”
ድፍን ሦስት ዓመታት ከድሬዳዋ ሰማይ ሥር፣ አንዲት እንደ ላባ የለሰለሰች ነፍስ፣
እንዲህ በፍቅር አውሎ ንፋስ እየተንሳፈፈች ነበር፡፡ በሰላም በምትኖርበት ግቢ እንደነፋስ
በሽንቁር ገብቼ ነፍሷን በአየር ላይ እንዳንሳፈፍኳት፣ በዚያው በተስቀለችበት የኋሊት ትቻት፣ ወደ አዲስ አበባ ተመለስኩ፡፡የሚወስደኝ መኪና በር ላይ
መጥቶ ሲቆም፣ አንድ ሽማግሌ ከቆንጆ ልጃቸው ጋር፣ ትልቁ የግቢ በር ላይ ቁመው እጃቸውን ለስንብት
ሲያውለበልቡልኝ ከእንባዬ ጋር እየታገልኩ ነበር፡፡ “ምን ፈልጌ ነው የምሄደው? ምን? እያልኩ ለራሴ፡፡ ድሬዳዋን ለቅቄ ስወጣ እንደ ጥይት ከምትወነጨፈው መኪና ግራና
ቀኝ ወደ ኋላ የሚሮጡ የሚመስሉት ቁጥቋጦና ድንጋዮች፣ አንዲት ሚስኪን አፍቃሪ ባዶ ግቢ ዉስጥ ትቼ መሄዴን ሰምተው ሊያፅናኗት ወደ እሷ የሚሮጡ ይመስሉ ነበር፡፡ ከሩቅ አፍቃሪ የቅርብ ድንጋይና ቁጥቋጦ ይሻላል የሚሉ ዓይነት፡፡
አዲስ አበባ የጠበቀኝ ገና አዲስ ተከፍቶ ውጥንቅጡ የወጣ ቅርንጫፍ ነበር፡፡ ሙሉ ቀን የማያባራ ችግር የደንበኞች ንጭንጭ የማይለየው ባንክ፡፡ ለዚሁ ቅርንጫፍ ነው እንግዲህ እድግት ብለው ያመጡኝ፡፡ ገና ከመድረሴ በሥጋም በነፍስም ሥራየ ላይ ተጠመድኩ፡፡ ሠራተኞቹ በሙሉ አዲስ ነበሩ፡፡ ሚስኪን የኒቨርስቲ ተመራቂዎች። ሁሉም ነገር ላይ የተሳሳቱ የሚመስላቸው፤ ሁሉም ደንበኛ ብር ሊያወጣና ሊያስገባ
ሳይሆን ሊያጭበረብርና ሊዘርፍ የመጣ የሚመስላቸው ስጉ ነፍሳት፡፡ እእምሯቸው ቁጥር ስፍር በሌለው ሕግ ማስጠንቀቂያ ተሞልቶ በፍርሀት የተሸበበ፡፡ የማይጠይቁኝ ጥያቄ አልነበረም፡፡ እንዳንዴማ ከረባት አስተሳሰር ሁሉ ይጠይቁኝ ነበር።
በተደጋጋሚ ዋናው መሥሪያ ቤት የሚያግዘኝ ሰው እንዲልኩልኝ ብወተውትም፣ ለአንድ ወር ብቻየን ፍዳዩን አበሉኝ፡፡ሲሳካልህ ለማጨብጨብ ከወደቅህም ትችታቸውን
እንደለይፍ ለመምዘዝ ጥጋቸውን ይዘው እንደሚመለከቱ ሥራ አሥኪያጆች የሚያስጠላኝ ፍጥረት የለም፡፡ የኔዎቹ እንደዛ ነበሩ፤ ስልክ እየደወሉ “በአንተ እንተማመናለን ይሉኛል አድናቆት እንደሙዳ ስጋ እየወረወሩ የቢዝነስ አጥራቸውን ሲያስጠብቁኝ ሊያድሩ
ይዳዳቸዋል፡፡ እያመሸሁ ከመሥራት አልፎ ቅዳሜ ሳይቀር እየገባሁ ለመሰራት ተገድጄ ነበር፡፡ በእነዚህ ጊዚያት እንኳንስ ለሐኑን ቃል እንደገባሁት ቤት ልከራይ ቀርቶ፣ ቀልቤን ሰብስቤ ጓደኞቼን እንኳን ማግኘት አልቻልኩም ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ ሲብስብኝ፡ ወደ ሥራ እስኪያጁ ቢሮ በአካል ሄጀ ከዚህ በኋላ ሰው ካልመደባችሁ ምንም ማድረግ አልችልም አልኩት፡፡
በቀጣዩ ሳምት በወረቀት ተከብቤ ባቀረቀርኩስት፣ በመስተዋት የተከለለች በር አልባ ቢሮዬን አልፋ አንዲት ሴት እፊቴ ተገተረች፡፡ መጀመሪያ ያየሁት፣ ከጉልበቷ በላይ በቀረ ጉርድ ጥቁር የቢሮ ቀሚሷ ምክንያት የተጋለጡትን ጠይምና ውብ እግሮቿን ነበር፡፡ ቀና ብዬ ፈገግ ለማለት ሞከርኩ፡፡ ፈገግ ብላ በስሜ ጠራችኝ፡፡ ግር እያለኝ “አቤት! ምን ልታዘዝ? እልኳት፡፡ እየተፍለቀለቀች
"እራስህ ምን ልታዘዝ ከሰላም ቢሮ አፈናቅልህ ያስመጣሃኝ አንተኮ ነሆ" ተሳሳቅን፡፡
ከዋናው መሥሪያ ቤት አዲስ የተላከች ልጅ ነበረች፡፡ ቀደም ብዬ አንዲት ሴት
እንደምትመጣ ብሰማም እንዲህ ወጣት ትሆናለች ብዬ አልጠበኩም ነበር፡፡ ምክንያቱም ስለሷ ጉብዝና አጋነው ነበር የነገሩኝ፡፡ “ሔራን እባላለሁ ቦስ! ትርፍ ወንበር ነገር የላችሁም” ብላ ዙሪያውን ተመለከተችና፣ ጥግ ላይ ከተቀመጡት ተሽከርካሪ ወንበሮች አንዱን ራሷ እየገፋች መጥታ፣ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች፡፡ እንደ ደም የቀላ ትልቅ የቆዳ ቦርሳዋን ከስሯ አሰቀመጠችና እሺ እንዴት እየሄደ ነው? ብላ ፈገግ አለች፡፡ ጠይም ቆዳዋ ጥራቱ የሚገርም ነው፡፡ጠይም ነበልባል፡፡ ደስ የሚል ወርቃማ ቀለም የተቀባዉ
ረዥም ጸጉሯ፡ መጀመሪያ ላይ የራሷ አልመሰለኝም ነበር …ስትስቅ እስከ ጆሮ ግንዷ ደርሰው የሚመለሱ ትልልቅ እና የሚያምሩ ከንፈሮቿ ከውብ ጥርሶቿ ጋር ተዳምረው ፈገግታዋ የልብ ያደርሳል” የሚባልላት ዓይነት አድርገዋታል፡፡ ቁመቷ ዘለግ ያለ ነው፡፡ በዝያ ላይ ውብ ቅርጽ፤ ስትናገርም ስትንቀሳቀስም ፈጣን፡፡ እንዲህ ነበር የመጀመሪያዉ ትውውቃችን፡
ሔራን ባንከ ውስጥ ተወልዳ ያደገች እስኪመስለኝ፣ እያንዳንዱ ሥራ በደም ሥሯ ውስጥ የሚፈስ ነበር የሚመስለው፡ በዛ ላይ ላለሁበት ቦታ የነበራት አክብሮትና ስርዓት እስገራሚ ነበር፡፡ በአጭር ቃል ብቻዬን ከመራወጥ አሳረፈችኝ፡፡ ተመድባ በመጣትች
በአስራ አምስት ቀኗ፣ አስር ጊዜ እየተቆራረጠ ካስመረረኝ የኮምፒውተር ሲስተም እስከ ፋይል ዝግጅት፣ ነገሮችን በሚገርም ፍጥነትና ብቃት ቦታ ቦታቸዉን አስያዘችልኝ፡፡ በተለይ እነዚያን ውሃ ቀጠነ ብለው የሚጨቃጨቁ ደንበኞች፣ በዛ ውብ ፈገግታዋ ውሃ ቸልሳባቸው፣ አረጋግታ ስታባርራቸው ተገርሜ እመለከት ነበር፡፡ ሲጀመር ከእሷ ጋር
ሲያወሩ፣ ከሌሎቹ ጋር እንደሚያወሩት አይቆጡም ኃላፊዎቻችንም ሴት ሳይወዱ
አይቀሩም መሰለኝ፤ እኔ ለሳምንት ተነዛንዤ ምላሽ የሚሰጡበትን ጉዳይ፣ ሔራን ደውላ ምን እንደምትላቸው እንጃ፡ ጠዋት ደውላ ከሰዓት በኋላ ይጨርሱታል ስንት ጊዜ ስነዛነዝ ቸል ያሉኝ የኮምፒውተር ባለሙያዎች ተንጋግተው መጥተው ሲስተሙን
አስተካክለውልን የሄዱት በአንድ ስልከ ጥሪ ነበር፡፡ በእርግጥ እኔ በኃላፊነት
በተቀመጥኩበት ቦታ አንዲት የበታች ሰራተኛ የበለጠ መሰማቷ የፈጠረብኝ ለስላሳ ቅሬታ ነበር፡፡ ምናልባት ከአንዱ ኃላፊ ጋር ነገር ይኖራት ይሆናል” ብዬ እስክጠረጥር፡፡ በኋላ በደንብ ሳውቃት ነው ልጅቱ ለማሳመን የተፈጠረች መሆኗን ያመንኩት፡፡
ከሐኑን ጋር በየቀኑ እናወራ ነበር፡፡ ባለኝ ክፍት ሰዓት ሁሉ እደውልላታለሁ፣ ያለውን
ነገር እነግራታለሁ፡፡ ይግባት አይግባት ባላውቅም፣ ዝም ብላ ትሰማኛለች፡፡ ምንጊዜም ከወሪያችን በኋላ ጥያቄዋ የታወቀ ነበር፡፡ ግን ትመጣለህ አይደል?” እውነት ነበራት::
በአንድ ወር ውስጥ ቤት ተከራይቼ እመለሳለሁ ያልኩት ልጅ፣ ቤተሰቦቼ ቤት እየኖርኩ ሦስት ወራት አለፉ፡፡ በመጨሻ እሷ ሰው አታጣም ብዬ ቤት መከራየት እንደምፈልግ ለሔራን ነገርኳት፡፡ አብረን ምሳ መብላት ጀምረን፣ ተቀራርበን ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን እየተፍለቀለቀች መጥታ እንኳን ደስ ያለህ ቦስ… ቤት ተገኝቶልሃል፡፡ አሪፍ ባለ አንድ መኝታ፣ አንደኛ ፎቅ ላይ ከሥራ እንደወጣን ወሰደችኝ፡፡ቤቱን ወደድኩት፡፡ በቀጣዩ ቀን የሶስት ወር የቤት ኪራይ ከፍዬ ተገላገልኩ፡፡ ቤት መከራየቴን ለቤተሰቦቼ ስነግራቸው እዚህ ምን አጥተህ ነው በኪራይ የምትገፈገፈው ?” ብለው ትንሽ
አጉረመረሙ፡፡ ግን ብዙ አልተጫኑኝም “
ለሥራውም ለምኑም ብቻውን መሆን
ካስፈለገው አለች እናቴ “ለምኑም” ስትል ድምፅዋ ውስጥ ትንሽ አሽሙር ነበረች
“ይሁና ብሉ ዝም አለ! አባቴ፡፡
ሔራን እና እቃህን መቸ ልታስገባ ነው?” አለችኝ፤እቃ መግዛቱንም ረስቼው ነበር፡፡
👍1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ለሐኑን ስነግራት በደስታ አበደች፡፡ እና መቼ ልትመጣ ነው?”
ፍቃድ ጠይቄ በዚህ ወር መጨረሻ አካባቢ” አልኳት፡፡ ግን ፈርቼ ነበር፡፡ ምን እንደሆነ ያልገባኝ ነገር፣ ውስጤን ያስጨንቀው ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ አውርጄና አውጥቼ ጉዳዩን ለታላቅ እህቴ ልነግራት ወሰንኩ አንድ ቅዳሜ ቀን “ምሳ ልጋብዝሽ” ስላት
ዛሬ ምን መልአክ ተጠጋህ ባክህ!?” እያለች የተቀጣጠርንበት ቦታ መጣች፡፡ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ስለ ሐኑን ነገርኳትና፣ ፎቶዋን አሳየኋት። “ውይይይይ!! የኔ ቆንጆ! እንዴት
ታምራለች!? ብላ አዳነቀችና “ምንም የሚካበድ ነገር የለውምኮ፤ ከወደድካት፣ እርግጠኛ ከሆንክና ከተግባባችሁ…በቃ እቤት እንነግራቸዋለን፤ አለቀ! እንደውም እኔ እነግራቸዋለሁ” ብላ ድንገት ከት ከት ብላ ሳቀችና
“ግን ልጅ ምናምን ወልደህ፣ አልደበክም አይደል …? እኔኮ እዚያ ሂደህ ድምፅህ ሲጠፋ
ባክሽ ምንም ነገር አልጀመርንም " ትክ ብላ በማሾፍ አየችኝና፣
“ይችን የመሰለች ልጅ ጋር አንድ ግቢ እየኖራችሁ ምንም ካልጀመራችሁ መልአክ ወንድም አለኝ እያልኩ ማውራት እጀምራለሁ" ተሳስቀን ተለያየን፡፡ በቀጣዩ ቀን እቤት ስገባ፣ የሁሉም ፊት ሳቅ አፍኖት ጠበቀኝ፡፡ በመጨረሻ አባቴ አላስችለው ብሎት እስቲ ና አንተ! … እዚህ ቁጭ በል! የምን የዙሪያ መሄድ ነው?” እናቴ ለወሬ ቸኩላ፣ ልታጥብ ያዘጋጀችውን እንቁላል የተጠበሰበት መጥበሻ እንዳንከረፈች ከውስጥ ወጥታ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች፡፡
ፎቶዋ ታለህ ወዲህ በል እንያት አለኝና ፎቶዋን እየተቀባበሉ አይተው፣
ቆንጆ ልጅ ቆንጆ ልቅም ያለች ቆንጆ እያሉ አዳነቁ፡፡ ማነው ስሟ?
ሐኑን
“ምንኛ ነው ደሞ የዛሬ ልጆች ስማቸው
አረብኛ
እረብኛ ? እስላም ናት እንዴ? አለ አባቴ ፊቱን ኮስተር አድርጎ
እዎ” ሁሉም ተያይተው ዝም አሉ፡፡
“ምነው? ችግር አለው”
አይ! ከወደድክ ምናሻን፤ግን እንደው እምነት አንድ ዓይነት ቢሆን ጥሩ ነበር፡፡ ነገ ልጆች ይወለዳሉ፣ ብዙ ነገር አለ፤ፍቅር እንደሆነ ሁልጊዜ እንዳጀማመሩ አይሆንም …”
አይ! እንግዲህ አታሟርቱበት” ብላ እህቴ ጣልቃ ገባች፤ ቤታችን ውስጥ የምትፈራ
ዓይነት ናት፡፡ አባቴ ፊቱ ላይ ቅሬታው እንዳረበበ ይሁን፣ ዋናው መፈቃቀዱ ነው
ብሎ ተነስቶ ወደመኝታ ቤቱ ገባ፡፡ ግን ደስተኛ እንዳልነበረ ፊቱ ላይ ያስታውቅበት
ነበር፡፡
ሁሉንም ነገር ጨራርሼ ወደ ድሬዳዋ ለመመለስ ተዘጋጀሁ፡፡ ዋና ሐሳቤ ድሬዳዋ እንደደረስኩ እዚያዉ ካፈራኋቸው ጓደኞቼና የሥራ ባልደረቦቼ መካከል ቀድሜ በስልክ ያዋራኋቸውን፣ ለሽምግልና ወደሐኑን አባት መላከ ነበር፡፡ሐኑን ድምፅዋ ውስጥ የምሰማው የደስታ ሲቃ፣ የእኔንም ጉጉት ጨምሮት፣ ቀኑን በጉጉት ነበር የጠበቅሁት፡፡
እንደነብሰ ጡር ቀን እየቆጠርን ቆይተን ቀኑ ሲደርስ ወደ ድሬደዋ በረርኩ፡፡ ድሬደዋ ራቀችብኝ፡፡ በመነሻና መድረሻ መካከል መንገድ የሚባል እንቅፋት አለ፡፡ ጉዞ ማለት አብሮ ለመሆን ለሚፈላለጉ ነፍሶች መሃል የተዘረጋን መንገድ የሚባል መጋረጃ ቀዶ መጣል ነው ፡፡ ርቀትም በመነሻና በመድረሻ መሃል ያለ የመንገድ ዕድሜ፡፡ የመንገድን ዕድሜ የሚያሳጥረው ጥሩ እርግማን፣ መጓዝ ብቻ ነው፡፡ ተጓዝኩ፡፡
የድሬዳዋ ሙቀት የሐኑን እቅፍ ይመስለኛል፡፡ለስለስ ያለ እና ምቾት ያለው፡፡ እንደደረስኩ ወደያዝኩት ሆቴል ገብቼ ሰውነቴን ተለቃለኩና ለባብሼ ወደማታ አካባቢ ለሽምግልና ከመረጥኳቸው ጓደኞቼ ጋ ወደተቀጣጠርንበት አቀናሁ፡፡ እንደሙሽራ
ተንካባክበው ራት ጋበዙኝ ፡፡እኔ ለማገባው ፣ የእነሱ ደስታ ወደር አልነበረውም፡፡ ባንክ
ውስጥ አለቃቸው ሆኜ ለአራት ዓመታት ሠርተናል፡፡ በእነዚያ አራት ዓመታት ዉስጥ ለሥራ ጉዳይ ተነዛንዘናል፣ ተጣልተናል፣ ባስ ሲልም እስከ ጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የሰጠኋቸው ነበሩ፡፡ ዛሬ ላይ እንዱም ነገር በልባቸው ውስጥ የለም፡፡ የእውነት ተደስተው ነበር፡፡ ከጥንት ጀምሮ በሽምግልና ታሪከ ውስጥ ያጋጠሙ ታሪኮችና ገጠመኞት፣ ሲነሱ ሲጣሉ አመሹ፡፡ ብዙ ሳቅ እንዲች ብለህ እንዳትጨነቅ፣ እንቢ ካሉ፣ አንድ ገጣባ የጋሪ ፈረስ አዘጋጅተንልሃል፤ ጠልፍሃት እየጋለብ መሄድ ነው ሃሃሃሃሃሃሃ
በማግስቱ ሽማግሌዎቼ ወደነሐኑን ቤት ሄዱ፡፡ ቀድመው አባባን ቀጥረዋቸው
ስለነበር፣ነገሩ ሽምግልና መሆኑን አውቀዋል፡፡ ልጃቸውን ጠያቂው ማን መሆኑን ብቻ ነበር ያላወቁት፡፡ ሆቴሌ ውስጥ እየተቀመጥኩ እየተነሳሁ ስንቆራጠጥ ዋልኩ፡፡ከብዙ
እንዲህ ተብለው ይሆናልና እንደዛ ተብለው ይሆናል” ከሚል መላ ምት ጋር፡፡
የላክኋቸዉ ሽማግሌዎች ካሰብኩት በላይ አምሽተው፣ ወደያዝኩት ከፍል መጡ፡፡
በጉጉት አፍ አፋቸውን ስመለከት፣ አንተ ተናገር አንተ በሚል እየተያዩ ግራ አጋቡኝ፡፡ ሲሄዱ የነበራቸው ፈገግታና ሞራል ፊታቸው ላይ አልነበረም፡፡
አልተሳካም!” አለ አንዱ፣
“ምን ማለት ነው አልተሳካም”
እባቷ አልተስማሙም፡፡ ልናሳምናቸው የቻልነውን ሁሉ ሞከርን፣ ግን አልሆነም?”
ሁሉም እንደ ሐዘን ቤት ፊታቸውን አጨፍግገው እንዳቀረቀሩ ዝም አሉ፡፡ እየቀለዱ መስሎኝ ነበር፡ትንሽ ቆይተው በሳቅ እየተፍለቀለቁ፣ እንኳን ደስ ያለህ እንዲሉኝ ጠበቅሁ፤ ግን የጠበቀኝ የመርዶው ዝርዝር ነበር፡፡ፈጽሞ ያልታሰበ
ነገር፡፡ ሽማግሌምቹ እንደደረሱ፣ አባባ አክብረው ነበር የተቀበሏቸው፡፡ የሄዱበትን ጉዳይ ሲነግሯቸውም ደስ ነው ያላቸው፤ ችግሩ የመጣው የእኔን ማንነት ሲሰሙ ነበር፡፡
“አይይይይይይይ…" ብለው ተከዙ፡፡ “ምንም የማይወጣለት ጥሩ ልጅ ነው፣ ሰውንም ሥራውንም የሚያከብር፣ ብታመም አስታማሚ፣ ቢከፋኝ እህ ብሎ የሚሰማ፣እንደ ልጅ የማየው ልጅ፡ ግን አይሆንም! እሱ ክርሰቲያን፣ እኛ ሙስሊሞች፣ እንዴት ይሆናል አይ
ግዴለም ይቅር አስተዋይ ልጅ አልነበር፣ ምን ነካው…?
“አባባ ይኼኮ ችግር የለውም፣ ከተዋደዱ ተቻችሎ መኖር…"
አባባ በቁጣ ገነፈሉ፡፡ “ይኼኮ ቦለቲካ አይደለም፣ ምን ነካችሁ ልጆች? …የነፍስ ጉዳይ ነው፡፡እንዴት እንዴት ነው የምትናገሩት? የአላህን ትዛዝ እኔ አልሽረው፤ ዓይኔ እያየ ልጀ ገሃነም እሳት ስትገባ፣ እንዴት ነው እሽ የምለው!? ሃይማኖታችን አይፈቅድም፣ በቃ!
ይሄን ሁሉ ዓመት አብረን እንደ አባትና ልጅ ስንኖር፣ አንድ ቀን ሐይማኖቱን ጠይቄው አውቃለሁ?አላውቅም መቻቻል እሱ ነው! አብረን ስንበላ፣ አብረን ስንጠጣ፣ ሐይማኖታችን ከልክሎናል? አልከለከለንም! መቻቻል እሱ ነው! እቤቴ ሲኖር ከዚች ከልጄ ነጥዬ አላየሁትም፤ መቻቻል ይኼ ነው። ጋብቻ ግን የማይሆን የማይታሰብ ነው!! ጀሀነብ ቀልድ እንዳይመስላችሁ ልጆቼ እንኳን እንዲህ እንዳሻን ኑረን፣ በጥፍራቸው ቁመው ተንቀጥቅጠው…ትዛዙን አክብረው ለኖሩትም አስፈሪ ናት ያች ቀን፡፡ ጥሩ ልጅ
ነው ወላሂ ጥሩ ልጅ ነው በዚህ ዘመን እንደሱ ያለ ሰው አይገኝም፤ የተማረ
አስተዋይ፣መጠጥ በአፉ አይዞር፣ጫት እንኳ እይቀምስም ግን በኋላ ይች ነፍስ ለጥያቄ መቅረቧ አይቀር! ጥሩ ልጅ ነው ሲባል፣ ወድጄ ነው ሲባል የአላህ ቃልና ትዛዝ አይሰረዝ አይከለስ ግዴላችሁም እንዳማረብን ቀጉርብትናችን እንቀጥል”
ቢጨንቀው አንዱ ሽማግሌ፣ “አባባ፣ በቃ
ከወደዳት ይሰልማላ አቦ!” ይላቸዋል
አባባ ከመጀመሪያውም ኮስተር ብለው፣” የአላህን መንገድ ነፍስያችን ወዷትና ፈቅደን እንጂ ሴት ተከትለን የምንሄድባት አይደለችም ካስቀየምኩት አፉ በሉኝ፣ ከኔ አቅም በላይ ሲሆንብኝ ነው ልጆቼ፣ በዚህ አትምጡብኝ እንደው ብታርዱኝ እሽ አልልም ወላሂ ብለው ተነስተው ቆሙ ሽማግሌዎቹም ተሰናብተው ከመውጣት ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበራቸውም
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ለሐኑን ስነግራት በደስታ አበደች፡፡ እና መቼ ልትመጣ ነው?”
ፍቃድ ጠይቄ በዚህ ወር መጨረሻ አካባቢ” አልኳት፡፡ ግን ፈርቼ ነበር፡፡ ምን እንደሆነ ያልገባኝ ነገር፣ ውስጤን ያስጨንቀው ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ አውርጄና አውጥቼ ጉዳዩን ለታላቅ እህቴ ልነግራት ወሰንኩ አንድ ቅዳሜ ቀን “ምሳ ልጋብዝሽ” ስላት
ዛሬ ምን መልአክ ተጠጋህ ባክህ!?” እያለች የተቀጣጠርንበት ቦታ መጣች፡፡ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ስለ ሐኑን ነገርኳትና፣ ፎቶዋን አሳየኋት። “ውይይይይ!! የኔ ቆንጆ! እንዴት
ታምራለች!? ብላ አዳነቀችና “ምንም የሚካበድ ነገር የለውምኮ፤ ከወደድካት፣ እርግጠኛ ከሆንክና ከተግባባችሁ…በቃ እቤት እንነግራቸዋለን፤ አለቀ! እንደውም እኔ እነግራቸዋለሁ” ብላ ድንገት ከት ከት ብላ ሳቀችና
“ግን ልጅ ምናምን ወልደህ፣ አልደበክም አይደል …? እኔኮ እዚያ ሂደህ ድምፅህ ሲጠፋ
ባክሽ ምንም ነገር አልጀመርንም " ትክ ብላ በማሾፍ አየችኝና፣
“ይችን የመሰለች ልጅ ጋር አንድ ግቢ እየኖራችሁ ምንም ካልጀመራችሁ መልአክ ወንድም አለኝ እያልኩ ማውራት እጀምራለሁ" ተሳስቀን ተለያየን፡፡ በቀጣዩ ቀን እቤት ስገባ፣ የሁሉም ፊት ሳቅ አፍኖት ጠበቀኝ፡፡ በመጨረሻ አባቴ አላስችለው ብሎት እስቲ ና አንተ! … እዚህ ቁጭ በል! የምን የዙሪያ መሄድ ነው?” እናቴ ለወሬ ቸኩላ፣ ልታጥብ ያዘጋጀችውን እንቁላል የተጠበሰበት መጥበሻ እንዳንከረፈች ከውስጥ ወጥታ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች፡፡
ፎቶዋ ታለህ ወዲህ በል እንያት አለኝና ፎቶዋን እየተቀባበሉ አይተው፣
ቆንጆ ልጅ ቆንጆ ልቅም ያለች ቆንጆ እያሉ አዳነቁ፡፡ ማነው ስሟ?
ሐኑን
“ምንኛ ነው ደሞ የዛሬ ልጆች ስማቸው
አረብኛ
እረብኛ ? እስላም ናት እንዴ? አለ አባቴ ፊቱን ኮስተር አድርጎ
እዎ” ሁሉም ተያይተው ዝም አሉ፡፡
“ምነው? ችግር አለው”
አይ! ከወደድክ ምናሻን፤ግን እንደው እምነት አንድ ዓይነት ቢሆን ጥሩ ነበር፡፡ ነገ ልጆች ይወለዳሉ፣ ብዙ ነገር አለ፤ፍቅር እንደሆነ ሁልጊዜ እንዳጀማመሩ አይሆንም …”
አይ! እንግዲህ አታሟርቱበት” ብላ እህቴ ጣልቃ ገባች፤ ቤታችን ውስጥ የምትፈራ
ዓይነት ናት፡፡ አባቴ ፊቱ ላይ ቅሬታው እንዳረበበ ይሁን፣ ዋናው መፈቃቀዱ ነው
ብሎ ተነስቶ ወደመኝታ ቤቱ ገባ፡፡ ግን ደስተኛ እንዳልነበረ ፊቱ ላይ ያስታውቅበት
ነበር፡፡
ሁሉንም ነገር ጨራርሼ ወደ ድሬዳዋ ለመመለስ ተዘጋጀሁ፡፡ ዋና ሐሳቤ ድሬዳዋ እንደደረስኩ እዚያዉ ካፈራኋቸው ጓደኞቼና የሥራ ባልደረቦቼ መካከል ቀድሜ በስልክ ያዋራኋቸውን፣ ለሽምግልና ወደሐኑን አባት መላከ ነበር፡፡ሐኑን ድምፅዋ ውስጥ የምሰማው የደስታ ሲቃ፣ የእኔንም ጉጉት ጨምሮት፣ ቀኑን በጉጉት ነበር የጠበቅሁት፡፡
እንደነብሰ ጡር ቀን እየቆጠርን ቆይተን ቀኑ ሲደርስ ወደ ድሬደዋ በረርኩ፡፡ ድሬደዋ ራቀችብኝ፡፡ በመነሻና መድረሻ መካከል መንገድ የሚባል እንቅፋት አለ፡፡ ጉዞ ማለት አብሮ ለመሆን ለሚፈላለጉ ነፍሶች መሃል የተዘረጋን መንገድ የሚባል መጋረጃ ቀዶ መጣል ነው ፡፡ ርቀትም በመነሻና በመድረሻ መሃል ያለ የመንገድ ዕድሜ፡፡ የመንገድን ዕድሜ የሚያሳጥረው ጥሩ እርግማን፣ መጓዝ ብቻ ነው፡፡ ተጓዝኩ፡፡
የድሬዳዋ ሙቀት የሐኑን እቅፍ ይመስለኛል፡፡ለስለስ ያለ እና ምቾት ያለው፡፡ እንደደረስኩ ወደያዝኩት ሆቴል ገብቼ ሰውነቴን ተለቃለኩና ለባብሼ ወደማታ አካባቢ ለሽምግልና ከመረጥኳቸው ጓደኞቼ ጋ ወደተቀጣጠርንበት አቀናሁ፡፡ እንደሙሽራ
ተንካባክበው ራት ጋበዙኝ ፡፡እኔ ለማገባው ፣ የእነሱ ደስታ ወደር አልነበረውም፡፡ ባንክ
ውስጥ አለቃቸው ሆኜ ለአራት ዓመታት ሠርተናል፡፡ በእነዚያ አራት ዓመታት ዉስጥ ለሥራ ጉዳይ ተነዛንዘናል፣ ተጣልተናል፣ ባስ ሲልም እስከ ጽሑፍ ማስጠንቀቂያ የሰጠኋቸው ነበሩ፡፡ ዛሬ ላይ እንዱም ነገር በልባቸው ውስጥ የለም፡፡ የእውነት ተደስተው ነበር፡፡ ከጥንት ጀምሮ በሽምግልና ታሪከ ውስጥ ያጋጠሙ ታሪኮችና ገጠመኞት፣ ሲነሱ ሲጣሉ አመሹ፡፡ ብዙ ሳቅ እንዲች ብለህ እንዳትጨነቅ፣ እንቢ ካሉ፣ አንድ ገጣባ የጋሪ ፈረስ አዘጋጅተንልሃል፤ ጠልፍሃት እየጋለብ መሄድ ነው ሃሃሃሃሃሃሃ
በማግስቱ ሽማግሌዎቼ ወደነሐኑን ቤት ሄዱ፡፡ ቀድመው አባባን ቀጥረዋቸው
ስለነበር፣ነገሩ ሽምግልና መሆኑን አውቀዋል፡፡ ልጃቸውን ጠያቂው ማን መሆኑን ብቻ ነበር ያላወቁት፡፡ ሆቴሌ ውስጥ እየተቀመጥኩ እየተነሳሁ ስንቆራጠጥ ዋልኩ፡፡ከብዙ
እንዲህ ተብለው ይሆናልና እንደዛ ተብለው ይሆናል” ከሚል መላ ምት ጋር፡፡
የላክኋቸዉ ሽማግሌዎች ካሰብኩት በላይ አምሽተው፣ ወደያዝኩት ከፍል መጡ፡፡
በጉጉት አፍ አፋቸውን ስመለከት፣ አንተ ተናገር አንተ በሚል እየተያዩ ግራ አጋቡኝ፡፡ ሲሄዱ የነበራቸው ፈገግታና ሞራል ፊታቸው ላይ አልነበረም፡፡
አልተሳካም!” አለ አንዱ፣
“ምን ማለት ነው አልተሳካም”
እባቷ አልተስማሙም፡፡ ልናሳምናቸው የቻልነውን ሁሉ ሞከርን፣ ግን አልሆነም?”
ሁሉም እንደ ሐዘን ቤት ፊታቸውን አጨፍግገው እንዳቀረቀሩ ዝም አሉ፡፡ እየቀለዱ መስሎኝ ነበር፡ትንሽ ቆይተው በሳቅ እየተፍለቀለቁ፣ እንኳን ደስ ያለህ እንዲሉኝ ጠበቅሁ፤ ግን የጠበቀኝ የመርዶው ዝርዝር ነበር፡፡ፈጽሞ ያልታሰበ
ነገር፡፡ ሽማግሌምቹ እንደደረሱ፣ አባባ አክብረው ነበር የተቀበሏቸው፡፡ የሄዱበትን ጉዳይ ሲነግሯቸውም ደስ ነው ያላቸው፤ ችግሩ የመጣው የእኔን ማንነት ሲሰሙ ነበር፡፡
“አይይይይይይይ…" ብለው ተከዙ፡፡ “ምንም የማይወጣለት ጥሩ ልጅ ነው፣ ሰውንም ሥራውንም የሚያከብር፣ ብታመም አስታማሚ፣ ቢከፋኝ እህ ብሎ የሚሰማ፣እንደ ልጅ የማየው ልጅ፡ ግን አይሆንም! እሱ ክርሰቲያን፣ እኛ ሙስሊሞች፣ እንዴት ይሆናል አይ
ግዴለም ይቅር አስተዋይ ልጅ አልነበር፣ ምን ነካው…?
“አባባ ይኼኮ ችግር የለውም፣ ከተዋደዱ ተቻችሎ መኖር…"
አባባ በቁጣ ገነፈሉ፡፡ “ይኼኮ ቦለቲካ አይደለም፣ ምን ነካችሁ ልጆች? …የነፍስ ጉዳይ ነው፡፡እንዴት እንዴት ነው የምትናገሩት? የአላህን ትዛዝ እኔ አልሽረው፤ ዓይኔ እያየ ልጀ ገሃነም እሳት ስትገባ፣ እንዴት ነው እሽ የምለው!? ሃይማኖታችን አይፈቅድም፣ በቃ!
ይሄን ሁሉ ዓመት አብረን እንደ አባትና ልጅ ስንኖር፣ አንድ ቀን ሐይማኖቱን ጠይቄው አውቃለሁ?አላውቅም መቻቻል እሱ ነው! አብረን ስንበላ፣ አብረን ስንጠጣ፣ ሐይማኖታችን ከልክሎናል? አልከለከለንም! መቻቻል እሱ ነው! እቤቴ ሲኖር ከዚች ከልጄ ነጥዬ አላየሁትም፤ መቻቻል ይኼ ነው። ጋብቻ ግን የማይሆን የማይታሰብ ነው!! ጀሀነብ ቀልድ እንዳይመስላችሁ ልጆቼ እንኳን እንዲህ እንዳሻን ኑረን፣ በጥፍራቸው ቁመው ተንቀጥቅጠው…ትዛዙን አክብረው ለኖሩትም አስፈሪ ናት ያች ቀን፡፡ ጥሩ ልጅ
ነው ወላሂ ጥሩ ልጅ ነው በዚህ ዘመን እንደሱ ያለ ሰው አይገኝም፤ የተማረ
አስተዋይ፣መጠጥ በአፉ አይዞር፣ጫት እንኳ እይቀምስም ግን በኋላ ይች ነፍስ ለጥያቄ መቅረቧ አይቀር! ጥሩ ልጅ ነው ሲባል፣ ወድጄ ነው ሲባል የአላህ ቃልና ትዛዝ አይሰረዝ አይከለስ ግዴላችሁም እንዳማረብን ቀጉርብትናችን እንቀጥል”
ቢጨንቀው አንዱ ሽማግሌ፣ “አባባ፣ በቃ
ከወደዳት ይሰልማላ አቦ!” ይላቸዋል
አባባ ከመጀመሪያውም ኮስተር ብለው፣” የአላህን መንገድ ነፍስያችን ወዷትና ፈቅደን እንጂ ሴት ተከትለን የምንሄድባት አይደለችም ካስቀየምኩት አፉ በሉኝ፣ ከኔ አቅም በላይ ሲሆንብኝ ነው ልጆቼ፣ በዚህ አትምጡብኝ እንደው ብታርዱኝ እሽ አልልም ወላሂ ብለው ተነስተው ቆሙ ሽማግሌዎቹም ተሰናብተው ከመውጣት ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበራቸውም
👍1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
"እና ምንድን ነው ሐሳብሽ!?"
እወድሃለሁ!.. እኔ በቃ እኔ ዕድሌ ይኼ ነው፣ ሂድ እርሳኝ ሂድ አትደውል፣ እኔን አታስብ፡ እርሳኝ፣ አባባን ባዶ ቤት ትቼው ብሄድ ርግማኑ ለአንተም ይተርፋል፡፡ ቁም ነረኛ ነህ፣የቻልከውን አድርገሃል፣ በአንተ የማዝንበት ምንም ነገር የለም፡፡ በቃ ሂድ፡ ሂድ ወደ አገርህ፣ ከወደድካት ጋር በሰላም ኑር"
"በቃ"
“አትዘንብኝ"
ስልኩን ዘጋችው ቀልድ መሰለኝ፡የሆነ ጨዋታ ነገር፡፡ የሆቴሉን መጋረጃ ከፍቼ ቁልቁል በሰፊው የድሬደዋ ከተማ ጨለማ ላይ፡ ኮከብ መስለው የተዘሩት አምፑሎች
ሲብለጨለጩ እየተመለከትኩ በሐሳብ ነጎድኩ: ነገሮች ሁሉ እንደሳሙና አረፋ እጄ ላይ ሲሟሙ ታወቀኝ፡፡ ለትንሽ ለትንሽ… በቃ ለትንሽ! ጥሩ ቀን እንደንጥላ ከበላዩ ሲታጠፍና፣ የብቸኝነት፣ የመለየት የባዶነት ዶፍ ሲወርድብኝ፣ ነፍሴ ስትኮራመት ተሰማኝ ፍቅር ከሽፎ እንኳን ሰው ያድናል፡፡ ሞቶ ራሱ ሕይወት ይሰጣል፡፡ የእኔና የሐኑን ፍቅር እጣው የወደቀው እዛው ላይ ነበር፡፡አንድ ሚስኪን ሽማግሌ በሰላምና በጤና ይኖሩ ዘንድ፣ የእኔና የሐኑን ፍቅር መሞት እና መሰዋት አለበት። አንድ ሽማግሌ አይደሉም ደግሞ አባት ናቸው ትዳራቸውንና ልጆቻቸውን በትነው፣ አንድ እሷን ብቻ
መርጠው ያሳደጉ ደግ አባት፤ እውነት አላት፣ያለችው ሁሉ እውነት ነው፡፡ ሌላም አንድ እወነት ደግሞ እለ፡ እኔ ሐኑንን ማፍቀሬ!
ውስጤ ቅጥል አለ፣ተንገበገብኩ፡፡ “ይሄ ነገር ፍቅር ነው ወይ? እያለች የኖረች ነፍሴ፣በዚያች ምሽት ለራሷ እንዲህ አለች “እዎ ፍቅር ነበር” ፍቅር ማለት በዚህ
በምትመለከተው ጨለማ ውስጥ ከሚብለጨለጩት ቁጥር ስፍር የሌላቸው እምፑሎች መሀል፣ ነፍስ አንዷን መርጣ ብርሃኗ ስትደምቅ ነው፡፡ ብርሃን ሁሉ የነፍስን ጨለማ አይገፍም ሲበዛ የራስህን ብርሃን ትፈልግ ዘንድ ያግዝህ ይሆናል፡፡ራሳችንን፣ አካባቢያቸንን፣ ዓለምን፣ መላውን የሰው ልጅ ሁሉ እንድናይ የሚረዳን ብርሃን ተመርጦ
በልባችን ጓዳ ይበራል ሰው የቱንም ያህል በደማቅ ብርሃን ቢከበብ፣ እውነተኛውን
የራሱን ብርሃን እስካላገኘ ድረስ ነፍሱ ጨለማ ውስጥ ናት
ሐኑን ሀሳቧን ብትቀይር ብዩ ሆቴሌ ውስጥ ሁለት ቀን በዝምታ ጠበኩ፡፡ ምንም አልነበረም፡፡ እንደዚያ ደረቴን ነፍቼ እንደ አንበሳ ገዳይ እየፎከርኩ የሄድኩት ሰውዬ እንደተነፈሰ ትልቅ ፊኛ መንፈሴ ተጨማትሮ ወደ አዲስ አበባ እየተጎተትኩ ተመለስኩ፡፡ ያውም እመለሳለሁ ካልኩበት ቀን አንድ ሳምንት ቀድሜ፡፡ በቀጥታ ወደ ቤቴ ሄጀ ተኛሁ ሳምንቱን ሙሉ ለማንም ሳልደውል፣ ስልኬን ዘግቼ እቤቴ ተቀመጥኩ፡፡ ቅዳሜ
ማታ ስልኬን ስከፍት፣ በርካታ የጽሑፍ መልእክትና የከሸፉ ጥሪዎች ስልኬን ሞልተውት ነበር ዓይኔ ተስገብግቦ የሐኑንን ስም ፈለገ፡፡ ይቅርታዋን ፈለግሁ፡፡ ሐሳቤን ቀይሬያለሁ የሚል ቃሏን ናፈቅሁ፡፡ምንም የለም አልቅስ አልቅስ የሚል ስሜት ተናነቀኝ አልቻልኩም ደወልኩላት፤ስልኳ አይጠራም፣ ዝግ ነበር፡፡ እስከ እኩለ ሌሊት ደጋግሜ
ስሞከር አመሸሁ፤ ዝግ ነበር፡፡ ስልኬን እንደያዝኩ እንቅልፍ ገላገለኝ! ጧት ስነሳ በጉጉት ስልኬን ተመለከትኩ፣ ምንም! ደጋግሜ ደወልኩ፣ ድካም ነበር ትርፉ!
እራሴን እንደምንም አነቃቅቼ ሻወር ወሰድኩና፣ ልብስ ቀያይሬ ወጣሁ፡፡ አዲስ አበባ የተለመደ ሕይወቷን ቀጥላለች፡፡ ሕዝቡ ሁሉ፣መንገደኛው ሁሉ፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥን የሆንኩት ነገር በአዋጅ ተነግሮት የራሱ ጉዳይ!” ብሎ ችላ ያለኝ መሰለኝ፡፡ አንድ ካፌ ገብቼ ቁርስ አዘዝኩ! ቡና ጠጣሁ፡፡ እናም እንደገና ስልኬን መቀጥቀጥ ጀመርኩ! ሊሰለቸኝ እና ድከም ሲለኝ ለሔራን ደወልኩ፡፡ በአንድ ጊዜ አንስታ፣
አንተ! ምን ሆነህ ነው እንዲህ የጠፋኸው ባክህ ? ሰው ይሰጋልም አይባልም?
“ደህና ነኝ!
“ምን ሆነሃል ደግሞ፣ ድምፅህ የሰካራም ድምፅ መስሏል የምትናገርበት ፍጥነትና
አእምሮዬ የሚረዳበት ፍጥነት አልመጣጠን አለኝ
“ትንሽ አሞኛል፣ ነገ አልገባም
“ምነው? የት ነው ያለኸው?
"እቤት ነኝ"
“ወደዚያው የምመጣበት ጉዳይ አለኝ፣ በዛው ብቅ ብዬ ልይህ ?”
“አይ አትቸገሪያ"
ትግር የለውም! ብቅ እላለሁ፤ እንደጨረስኩ እመጣለሁ ቻው ሳትለኝ ስልኩን ዘጋችው እንዳለችው ወደ አሥራ አንድ ሰዓት አካባቢ እቤት መጣች፤ ቤቱ ተተረማምሶ፣ ሻንጣዬ ሳይከፈት በሩ ሥር ቁሞ ስታይ፣
እና የሆነ የተሳሳተ ነገርማ አለ፣ልትጠፋ ነበር እንዴ?ሂሂሂ” እያለች ገብታ ተቀመጠች አንድም ነገር ተንፍሽ የማላውቀውን የሐኑንን ጉዳይ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ
ሳትጠይቀኝ ዝርግፍ አድርጌ ነገርኳት፡፡ በግርምት ስታዳምጠኝ ቆየችና፣ እንደ ሕፃን ልጅ ተነስታ መጥታ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ፤ ታቀፍኩላት። የዚያን ቀን ስታወራኝ እና ስታጽናናኝ አመሽች፡፡ ችግር የለውም፣ አሞኛል ብለህ ሳምንቱን እረፍ
ብላኝ ተስናብታኝ ሄደች እንዲያውም ልደር ብላኝ ነበር፡፡ ጧት ሥራ ገቢ ነሽ ሂጂ ብዬ ሸኘኋት፤ እውነቱን ለመናገር፣ ብታድር ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ብቸኝነቴን እንደጉድ ነበር
የፈራሁት።
ጧት አንድ ሰዓት ላይ የቤቴ በር ሲንኳኳ፡ ተነስቼ ከፈትኩ ሔራን ነበረች፡፡ ቁርስ
ይዛልኝ መጥታ፡
ከሥራ እንደወጣሁ፣እመጣለሁ ውጣና ምሳ ብላ፣ እደውልልሃለሁ” ብላኝ
እየተጣደፈች ሄደች ከሥራ መልስ ለትልቅ የፕላስቲክ ዘንቢል የታሸገ አዲስ ብርድ
ልብስና፣ ሌላ ትልቅ ቦርሳ ይዛ መጣች፡፡ቤት የቀየረች ነበር የምትመስለው፡፡ ያንን ሁሉ ተሸክማ ደረጃ በመውጣቷ፣ በድካም ቁና ቁና እየተነፈሰች እበር ላይ ቁማ ሳያት
አሳዘነችኝ፡፡ ራት አምጥታልኝ ነበር፡፡ የዚያን ቀን ስታወራኝ አምሽታ፣ ያመጣችውን
ብርድ ልብስ ለብሳ ሶፋ ላይ አደረች፡፡ ቦታ
እንድንቀያየር ብለምናት እምቢ አለች፡፡
ሳምንቱን ሙሉ እኔጋ ነበር ያደረችው እዚያች ሶፋ ላይ ኩርምት ብላ፡፡ የእውነትም አጽናናችኝ፡፡ በቀጣዩ ሳምንት ምንም እንዳልተፈጠረ ሥራዋ ላይ ተገኘሁ፡፡ ሕይወት ጠባሳችን ዕድሜ ልክ አብሮን እንዲኖር እንጂ ዕድሜ ልክ ስናለቅስበት እንድንኖር አትፈቅድልንም፡፡ ካለቀስንም እየኖርን እንድናለቅስ ነው የምታደርገን፡፡
በተከታታይ ለአንድ ወር አካባቢ ለሐኑን ብደውልም፣ ስልኳ ዝግ ነበር፡፡ እንዲያውም በመሀል ተነስና ሂድ ሂድ ይለኛል፡፡ የመለያየት ቀፋፊ ገጹ ድምፃችንን ለመስማት ለሚንሰፈሰፉ ውዶቻቶን፣ ግድ ስሙን ብለን ደጅ መጥናታችን ላይ ነው ፡፡ ግን ምን
አደረኳት?” እላለሁ በየቀኑ በተቃራኒው ከሔራን ጋር ቅርበታችን ከፍ እያለ፣ ሥራ ቦታ አብሮ ምሳ ከመብላት አልፎ፣አብረን ለእራት መውጣት ጀመርን፡፡ እራሴን ክፍትፍት አድርጌው ነበር፡፡ለወትሮው ቁጥብ የሆነው ባሕሪየ ዝርክርክ ያለ እስኪመስለኝ ድረስ እያንዳንዷን ዝርዝርና በአእምሮየ ውስጥ የሚመላለሰዉን ሐሳብ ሁሉ፣ ሳትጠይቀኝ ለሔራን እናዘዝ ነበር፡፡ ሔራን ጥሩ ልጅ ነበረች፤ ከሐኑን ጋር እንደገና እንድንገናኝ የቻለችውን ሁሉ ብታደርግም፣ አልተሳካም፡፡ አይደለምና ብሶቴን ፣ሥራዬን ሳይቀር እሷ እየሠራች ለፊርማ ብቻ ታመጣልኝ ነበር፡፡ ፈጣሪ ጠብቆኝ እንጂ፤ ባቀረበችልኝ ጊዜ ሁሉ ሳላይ የፈረምኩበት የብር መዓት አገር ይገዛል፡፡
ድሬደዋ ጓደኞቼን “ሐኑን እንዴት ናት?” ብዬ ደውዬ ስጠይቃቸው፣ ደህና እንደሆነችና አልፎ አልፎ መንገድ ላይ አባቷ ጋር ሲሔዱ እንደሚያገኟቸው ይነግሩኛል፡፡ ብቸኛ ምክንያቷ ከእኔ መራቅ ከሆነ፣ እንደፈለገች ትሁን ብዬ እኔም መሞከሬን ርግፍ አድርጌ ተውኩት። በተቃራኒው ከሔራን ጋር ከቀን ወደ ቀን ቅርበታችን ከፍ እያለ፣ በየቀኑ በሚባል ሁኔታ እቤቴ መምጣት ጀመረች ከሥራ እንደወጣን አብረን
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
"እና ምንድን ነው ሐሳብሽ!?"
እወድሃለሁ!.. እኔ በቃ እኔ ዕድሌ ይኼ ነው፣ ሂድ እርሳኝ ሂድ አትደውል፣ እኔን አታስብ፡ እርሳኝ፣ አባባን ባዶ ቤት ትቼው ብሄድ ርግማኑ ለአንተም ይተርፋል፡፡ ቁም ነረኛ ነህ፣የቻልከውን አድርገሃል፣ በአንተ የማዝንበት ምንም ነገር የለም፡፡ በቃ ሂድ፡ ሂድ ወደ አገርህ፣ ከወደድካት ጋር በሰላም ኑር"
"በቃ"
“አትዘንብኝ"
ስልኩን ዘጋችው ቀልድ መሰለኝ፡የሆነ ጨዋታ ነገር፡፡ የሆቴሉን መጋረጃ ከፍቼ ቁልቁል በሰፊው የድሬደዋ ከተማ ጨለማ ላይ፡ ኮከብ መስለው የተዘሩት አምፑሎች
ሲብለጨለጩ እየተመለከትኩ በሐሳብ ነጎድኩ: ነገሮች ሁሉ እንደሳሙና አረፋ እጄ ላይ ሲሟሙ ታወቀኝ፡፡ ለትንሽ ለትንሽ… በቃ ለትንሽ! ጥሩ ቀን እንደንጥላ ከበላዩ ሲታጠፍና፣ የብቸኝነት፣ የመለየት የባዶነት ዶፍ ሲወርድብኝ፣ ነፍሴ ስትኮራመት ተሰማኝ ፍቅር ከሽፎ እንኳን ሰው ያድናል፡፡ ሞቶ ራሱ ሕይወት ይሰጣል፡፡ የእኔና የሐኑን ፍቅር እጣው የወደቀው እዛው ላይ ነበር፡፡አንድ ሚስኪን ሽማግሌ በሰላምና በጤና ይኖሩ ዘንድ፣ የእኔና የሐኑን ፍቅር መሞት እና መሰዋት አለበት። አንድ ሽማግሌ አይደሉም ደግሞ አባት ናቸው ትዳራቸውንና ልጆቻቸውን በትነው፣ አንድ እሷን ብቻ
መርጠው ያሳደጉ ደግ አባት፤ እውነት አላት፣ያለችው ሁሉ እውነት ነው፡፡ ሌላም አንድ እወነት ደግሞ እለ፡ እኔ ሐኑንን ማፍቀሬ!
ውስጤ ቅጥል አለ፣ተንገበገብኩ፡፡ “ይሄ ነገር ፍቅር ነው ወይ? እያለች የኖረች ነፍሴ፣በዚያች ምሽት ለራሷ እንዲህ አለች “እዎ ፍቅር ነበር” ፍቅር ማለት በዚህ
በምትመለከተው ጨለማ ውስጥ ከሚብለጨለጩት ቁጥር ስፍር የሌላቸው እምፑሎች መሀል፣ ነፍስ አንዷን መርጣ ብርሃኗ ስትደምቅ ነው፡፡ ብርሃን ሁሉ የነፍስን ጨለማ አይገፍም ሲበዛ የራስህን ብርሃን ትፈልግ ዘንድ ያግዝህ ይሆናል፡፡ራሳችንን፣ አካባቢያቸንን፣ ዓለምን፣ መላውን የሰው ልጅ ሁሉ እንድናይ የሚረዳን ብርሃን ተመርጦ
በልባችን ጓዳ ይበራል ሰው የቱንም ያህል በደማቅ ብርሃን ቢከበብ፣ እውነተኛውን
የራሱን ብርሃን እስካላገኘ ድረስ ነፍሱ ጨለማ ውስጥ ናት
ሐኑን ሀሳቧን ብትቀይር ብዩ ሆቴሌ ውስጥ ሁለት ቀን በዝምታ ጠበኩ፡፡ ምንም አልነበረም፡፡ እንደዚያ ደረቴን ነፍቼ እንደ አንበሳ ገዳይ እየፎከርኩ የሄድኩት ሰውዬ እንደተነፈሰ ትልቅ ፊኛ መንፈሴ ተጨማትሮ ወደ አዲስ አበባ እየተጎተትኩ ተመለስኩ፡፡ ያውም እመለሳለሁ ካልኩበት ቀን አንድ ሳምንት ቀድሜ፡፡ በቀጥታ ወደ ቤቴ ሄጀ ተኛሁ ሳምንቱን ሙሉ ለማንም ሳልደውል፣ ስልኬን ዘግቼ እቤቴ ተቀመጥኩ፡፡ ቅዳሜ
ማታ ስልኬን ስከፍት፣ በርካታ የጽሑፍ መልእክትና የከሸፉ ጥሪዎች ስልኬን ሞልተውት ነበር ዓይኔ ተስገብግቦ የሐኑንን ስም ፈለገ፡፡ ይቅርታዋን ፈለግሁ፡፡ ሐሳቤን ቀይሬያለሁ የሚል ቃሏን ናፈቅሁ፡፡ምንም የለም አልቅስ አልቅስ የሚል ስሜት ተናነቀኝ አልቻልኩም ደወልኩላት፤ስልኳ አይጠራም፣ ዝግ ነበር፡፡ እስከ እኩለ ሌሊት ደጋግሜ
ስሞከር አመሸሁ፤ ዝግ ነበር፡፡ ስልኬን እንደያዝኩ እንቅልፍ ገላገለኝ! ጧት ስነሳ በጉጉት ስልኬን ተመለከትኩ፣ ምንም! ደጋግሜ ደወልኩ፣ ድካም ነበር ትርፉ!
እራሴን እንደምንም አነቃቅቼ ሻወር ወሰድኩና፣ ልብስ ቀያይሬ ወጣሁ፡፡ አዲስ አበባ የተለመደ ሕይወቷን ቀጥላለች፡፡ ሕዝቡ ሁሉ፣መንገደኛው ሁሉ፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥን የሆንኩት ነገር በአዋጅ ተነግሮት የራሱ ጉዳይ!” ብሎ ችላ ያለኝ መሰለኝ፡፡ አንድ ካፌ ገብቼ ቁርስ አዘዝኩ! ቡና ጠጣሁ፡፡ እናም እንደገና ስልኬን መቀጥቀጥ ጀመርኩ! ሊሰለቸኝ እና ድከም ሲለኝ ለሔራን ደወልኩ፡፡ በአንድ ጊዜ አንስታ፣
አንተ! ምን ሆነህ ነው እንዲህ የጠፋኸው ባክህ ? ሰው ይሰጋልም አይባልም?
“ደህና ነኝ!
“ምን ሆነሃል ደግሞ፣ ድምፅህ የሰካራም ድምፅ መስሏል የምትናገርበት ፍጥነትና
አእምሮዬ የሚረዳበት ፍጥነት አልመጣጠን አለኝ
“ትንሽ አሞኛል፣ ነገ አልገባም
“ምነው? የት ነው ያለኸው?
"እቤት ነኝ"
“ወደዚያው የምመጣበት ጉዳይ አለኝ፣ በዛው ብቅ ብዬ ልይህ ?”
“አይ አትቸገሪያ"
ትግር የለውም! ብቅ እላለሁ፤ እንደጨረስኩ እመጣለሁ ቻው ሳትለኝ ስልኩን ዘጋችው እንዳለችው ወደ አሥራ አንድ ሰዓት አካባቢ እቤት መጣች፤ ቤቱ ተተረማምሶ፣ ሻንጣዬ ሳይከፈት በሩ ሥር ቁሞ ስታይ፣
እና የሆነ የተሳሳተ ነገርማ አለ፣ልትጠፋ ነበር እንዴ?ሂሂሂ” እያለች ገብታ ተቀመጠች አንድም ነገር ተንፍሽ የማላውቀውን የሐኑንን ጉዳይ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ
ሳትጠይቀኝ ዝርግፍ አድርጌ ነገርኳት፡፡ በግርምት ስታዳምጠኝ ቆየችና፣ እንደ ሕፃን ልጅ ተነስታ መጥታ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ፤ ታቀፍኩላት። የዚያን ቀን ስታወራኝ እና ስታጽናናኝ አመሽች፡፡ ችግር የለውም፣ አሞኛል ብለህ ሳምንቱን እረፍ
ብላኝ ተስናብታኝ ሄደች እንዲያውም ልደር ብላኝ ነበር፡፡ ጧት ሥራ ገቢ ነሽ ሂጂ ብዬ ሸኘኋት፤ እውነቱን ለመናገር፣ ብታድር ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ብቸኝነቴን እንደጉድ ነበር
የፈራሁት።
ጧት አንድ ሰዓት ላይ የቤቴ በር ሲንኳኳ፡ ተነስቼ ከፈትኩ ሔራን ነበረች፡፡ ቁርስ
ይዛልኝ መጥታ፡
ከሥራ እንደወጣሁ፣እመጣለሁ ውጣና ምሳ ብላ፣ እደውልልሃለሁ” ብላኝ
እየተጣደፈች ሄደች ከሥራ መልስ ለትልቅ የፕላስቲክ ዘንቢል የታሸገ አዲስ ብርድ
ልብስና፣ ሌላ ትልቅ ቦርሳ ይዛ መጣች፡፡ቤት የቀየረች ነበር የምትመስለው፡፡ ያንን ሁሉ ተሸክማ ደረጃ በመውጣቷ፣ በድካም ቁና ቁና እየተነፈሰች እበር ላይ ቁማ ሳያት
አሳዘነችኝ፡፡ ራት አምጥታልኝ ነበር፡፡ የዚያን ቀን ስታወራኝ አምሽታ፣ ያመጣችውን
ብርድ ልብስ ለብሳ ሶፋ ላይ አደረች፡፡ ቦታ
እንድንቀያየር ብለምናት እምቢ አለች፡፡
ሳምንቱን ሙሉ እኔጋ ነበር ያደረችው እዚያች ሶፋ ላይ ኩርምት ብላ፡፡ የእውነትም አጽናናችኝ፡፡ በቀጣዩ ሳምንት ምንም እንዳልተፈጠረ ሥራዋ ላይ ተገኘሁ፡፡ ሕይወት ጠባሳችን ዕድሜ ልክ አብሮን እንዲኖር እንጂ ዕድሜ ልክ ስናለቅስበት እንድንኖር አትፈቅድልንም፡፡ ካለቀስንም እየኖርን እንድናለቅስ ነው የምታደርገን፡፡
በተከታታይ ለአንድ ወር አካባቢ ለሐኑን ብደውልም፣ ስልኳ ዝግ ነበር፡፡ እንዲያውም በመሀል ተነስና ሂድ ሂድ ይለኛል፡፡ የመለያየት ቀፋፊ ገጹ ድምፃችንን ለመስማት ለሚንሰፈሰፉ ውዶቻቶን፣ ግድ ስሙን ብለን ደጅ መጥናታችን ላይ ነው ፡፡ ግን ምን
አደረኳት?” እላለሁ በየቀኑ በተቃራኒው ከሔራን ጋር ቅርበታችን ከፍ እያለ፣ ሥራ ቦታ አብሮ ምሳ ከመብላት አልፎ፣አብረን ለእራት መውጣት ጀመርን፡፡ እራሴን ክፍትፍት አድርጌው ነበር፡፡ለወትሮው ቁጥብ የሆነው ባሕሪየ ዝርክርክ ያለ እስኪመስለኝ ድረስ እያንዳንዷን ዝርዝርና በአእምሮየ ውስጥ የሚመላለሰዉን ሐሳብ ሁሉ፣ ሳትጠይቀኝ ለሔራን እናዘዝ ነበር፡፡ ሔራን ጥሩ ልጅ ነበረች፤ ከሐኑን ጋር እንደገና እንድንገናኝ የቻለችውን ሁሉ ብታደርግም፣ አልተሳካም፡፡ አይደለምና ብሶቴን ፣ሥራዬን ሳይቀር እሷ እየሠራች ለፊርማ ብቻ ታመጣልኝ ነበር፡፡ ፈጣሪ ጠብቆኝ እንጂ፤ ባቀረበችልኝ ጊዜ ሁሉ ሳላይ የፈረምኩበት የብር መዓት አገር ይገዛል፡፡
ድሬደዋ ጓደኞቼን “ሐኑን እንዴት ናት?” ብዬ ደውዬ ስጠይቃቸው፣ ደህና እንደሆነችና አልፎ አልፎ መንገድ ላይ አባቷ ጋር ሲሔዱ እንደሚያገኟቸው ይነግሩኛል፡፡ ብቸኛ ምክንያቷ ከእኔ መራቅ ከሆነ፣ እንደፈለገች ትሁን ብዬ እኔም መሞከሬን ርግፍ አድርጌ ተውኩት። በተቃራኒው ከሔራን ጋር ከቀን ወደ ቀን ቅርበታችን ከፍ እያለ፣ በየቀኑ በሚባል ሁኔታ እቤቴ መምጣት ጀመረች ከሥራ እንደወጣን አብረን
❤1👍1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
በዝምታ ገባን፡፡ ገና እንደገባን ሔራን አቅፉ ከንፈሬን ሳመችኝ፡፡ ድንገተኛ ነበር፡፡ እናም "ይበቀሃል፡ አንዳንዴ ነገሮች ካልተውካቸው ዛሬን ማየት አትችልም ብላ ሳቀች።
ዓይኖቿን እያየሁ፣ “ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ!" አልኳት፡፡
በቃ እንደዚህ ነው የምታመሰግነው ወደራሴ ሳብኳት፡፡ ሰፊው አልጋ ላይ ተያይዘን ወደቅን ለዓመታት እንደ ሐውልት ውስጤ ገዝፎ የቆመ የሐኑን ፍቅር፣ ትዝታ እና መሻት ሁሉ አብሮ የወደቀ የተንኮታኮተ መሰለኝ፡፡ ከአንዲት ሴት ወደ ሌላ ሴት መሄድ መዳረሻዬ ሳይሆን መንገዴ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ከአንዷ ወደ ሌላዋ ሲረማመዱ የመኖር ጅማሬ፤ ትንሽ ጸጸት ጋር፡፡ የሐኑን ነገር ግን የዚያን ቀን ፍጻሜው ሆነ አልኩ፡፡ ሔራን
አንገቴ ሥር ተሸጉጣ በሹክሹክታ የምታወራውን ብዙ ብዙ የፍቅር ቃል ወንድነቴ ያደመጠው፣ ለሞተው ፍቅሬ እንደሚነበብ የሕይወት ታሪክ ነበር፡፡ ዓይኖቼን ስከድናቸው የሒራን ጠይም ሰውነት የሐኑንን ቅላት ለብሶ ይታየኛል፡፡ማንን እንደምክድ እንጃ፤ የሆነ ክሕደት እየፈጸምኩ መስሎ ይሰማኛል ፡፡ ሔራንን በተለያየ ልብስ ላስባትና ሐሳቤን ልመልሰው በቁንጅናዋ እራሴን ላማልል እታገላለሁ፡፡ “ሔራንኮ ናት ከሥርህ
ያለችው፣ያቺ ምድረ ወንድ የሚያፈጥባት ጠይም ሳቂታ ሔራን ቆንጆዋ ሔራን
እለዋለሁ ለራሴ፡ ውብ ከንፈሮቿን፣ አንዳች ንዝረት የሚለቁ ዓይኖቿን፣ ማንንም ወንድ
የሚፈትኑ ጡቶቿን ባወጣ ባወርድ፣ በእጆቿ ፋይል ይዛ በጉርድ ቀሚስ ወዲያ ወዲህ ስትል ብቻ ነው የምትታየኝ፡፡ ከላያችን ላይ የደረብነውን አንሶላና ምናምን ብገልጠው፣ በግራና በቀኝ እጇ ፋይል እንደያዘች፡ ከነጉርድ ቀሚሷና ከተረከዘ ረጅም ጫማዋ፣ ከሥሬ የተኛች መስሎ ነበር የሚሰማኝ፡፡የሆነ ቢሯችን ውስጥ መሬት ለመሬት የሚሳብ
የኮምፒውተር ገመድ ጠልፎኝ እላይዋ ላይ የወደኩ ዓይነት፡፡
ከሔራን ጋር በአዲስ “ፍቅር መክነፍ ጀመርን፡፡ በተገናኘን ቁጥር የመጀመሪያ ሥራችን አልጋ ላይ መውደቅ ነበር፡፡ ለስሙ ፍቅረኞች ነን እንጂ በሳምንት ውስጥ የሚበዙት ቀኖች አዳሯ እኔ ጋር ነበር፡፡ ቅዳሜና እሁድ አብረን ነን፡፡ ቤቱን እየገዛች በምታመጣው እቃ ሞላችው፡፡ ከማብሰያ እስከመኝታ ቤት፡ የሔራን አሻራ ያላረፈበት እቃ የለም፡፡ቤቱ በወራት ውስጥ፣ አስር ዓመት በትዳር የቆዩ ባለትዳሮች ቤት መሰለ፡፡ ቁምሣጥኑን
ስከፍተው፣ ከእኔ ልብስ ይልቅ የሔራን ይበዛ ነበር፡፡ ወርቃማ የፀጉር ዘለላ የማይገኝበት የቤቱ ክፍል የለም፡፡ ከእሷ አልፎ እህቶቿ ቅዳሜና እሁድ እየመጡ፣ ቡና አፍልተው ሲያውካኩ ውለው ይሄዳሉ፡፡ ልክ ዛሬ እንደተወለደ ሰው፤ ነፍሳቸው ስለነገ ብቻ የሚጨነቅ፣ ወደኋላ የሚባል ነገር የማያውቁ ልጆች ናቸው፡፡ ሲመጡ ደስ ይለኛል፡፡አንዳንዴ እንዲያውም እራሴ እየደወልኩ “ምነው ጠፋችሁ?” እስከማለት ደርሼ ነበር፡፡
የሐኑን ነገር እየደበዘዘ ሄደ፣ ከአእምሮየ የጠፋ እስኪመስለኝ፣ የሐኑንን ጠረን በሔራን ጠረን የመለወጥ ትግል ላይ ነበርኩ፡፡ ወይም ሔራን እራሷ የነብሴ ጥጋጥግ የተገነባዉን የሐኑን መታሰቢያ ሁሉ እያፈራረሰች የራሷን አዲስ መንግሥት እየተከለች ነበር…እንጃ!
አንዴ ሜዳ ሁኛለሁ.…የፈለጉትን ሲተከሉ ሲነቅሉ ተው የሚል ወኔ አልነበረኝም፡፡
ሔራን ፈጣን ናት፡፡ ቆሜ ማሰብ እንኳን እስከሚያቅተኝ፣ ጥድፊያዋ ለጉድ ነበር፡፡ ምንም ነገር ትበለኝ አደርገዋለሁ፤ በራሴ አስቤ ግን አንድም ነገር አላደርግም፡፡ እንስፍስፍ ካለ ፍቅር ይልቅ፣ ራሴን እሷ ላይ ጥዬ ያደረገችኝን ታድርገኝ ወደሚል ስሜት ያዘነበለ ግንኙነት ነበር በመሃላችን የነበረው፡፡ “ከቤተሰቦችህ ጋር አሰተዋውቀኝ አለችኝ፣ ወስጄ
አስተዋወቅኋት፡፡ ወደዷት! አሁን ገና የምትሆንህን አገኘህ ተባለ፡፡ ከቤተሰቦቿ ጋር ወስዳ አስተዋወቀችኝ! የገደል ስባሪ የሚያካለዉ ወንድሟ ቀልቡ ወደደኝ፡፡ እውነቱን ለመናገር እኔም ወድጄው ነበር፡፡ የዓለም ቀልድ ሁሉ እሱጋ ነበር፡፡ ውሃ ቀጠነ ብሎ ከሰው ጋር ከመደባደብና ከመታሰር በተረፈው ጊዜ ሁሉ፣ መሳቅ ሥራው ነበር፡፡ በድፍን ከተማው
በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ስሜ በዋስትና ለመመዝገብ የበቃው፣ ይኼው ልጅ በታሰረ ቁጥር ለማስፈታት ስል ነበር፡፡ እሱም ታዲያ ለገላጋይ አስቸግሮ ዘራፍ ሲል፣ እኔ ከተናገርኩት ግን አደብ ይገዛ ነበር፡፡ እሰቲ ይሄንን ልጅ አንድ በለው፣ አንተን ነው መቼም የሚሰማው ትለኛለች ሔራን፡፡ የሆነ በቤተሰብ ድር የመተብተብ ሳላገባት በቤታቸው የምከበር ወሳኝ ሰው የሆንኩ መስሎ እንዲሰማኝ የማድረግ ጨዋታ፡፡ አልናገረው እንጂ በዙሪያየ የምታደራው ድር ነፍሴ ይገባታል፡፡ እጅ የሰጠን ሰው ለመማረክ የምትደክመው
ነገር ይገርመኛል፡፡
እንደሷው ፍጥን ካሉ ሁለት ቆንጆ እህቶቿ እና እናቷ ጋር ተዋወቅሁ፡፡እንደ አስከሬን
ለአራት ተሹመው ወደቀብሬ እያዳፉ የሚወስዱኝ እስኪመስለኝ ድረስ ወሬያቸው ሁሉ ሰርግና ጋብቻ ብቻ ነበር፡፡ በመጨረሻ ሔራን እራሷ እስከመቼ ነው እንዲህ የምንኖረው?ለምን አንጋባም!?” አለችኝ፡፡ ብንጋባ ከዚህ የተለየ ምን ይመጣል ብዬ ተስማማሁ፡፡ሔራንን ወድጃት ነበር፡፡ የማልወድበት ምንም ምክንያት አልነበረኝም፡፡ የማላገባባትም
እንደዚያው፡፡ እናም “ልክ ነሽ እንጋባ!” አልኳት፡፡ መውደድ ብቻ! ልክ እንደምወደው ምግብ፡ልክ እንደምወደው ፊልም፣ እንደምወደው ልብስ፣ እንድመወደው ምናም ሔራንን ወደድኳት እናም እንጋባ ስትለኝ እሽ አልኩ፡፡
“ጠይቀኛ ሽማግሌ ላክ፤ለምንድን ነው እኔ የሆነ ነገር እስከምል የምትጠብቀኝ?
ወደ ትዳር የሚወስደውን መንገድ እጄን ይዛ መራችኝ፡፡ ባለማመደችኝ ድገተኛ
አጠያየቅ፣ ሰው በተሰበሰበበት ታገቢኛለሽ ወይ? ብዬ ተንበርክኬ ጠየኳት፣ እስካሁን የሚገርመኝ ለምን እንዳለቀሰች ነው፡፡ ያዩን ሁሉ አጨበጨቡ፡፡ ወደቤተሰቦቿ ሽማግሌ
ላውሁ፡፡ ሽማግሌዎቹ ወደነ ሔራን ቤት ሲሔዱ ፣ሔራን እኔ እኔ ኤልጋችን ውስጥ
ነበርን፡፡ ሽማግሌዎቹ ደውለው እንኳን ደስ ያለህ ተሳክቷል” ሲሉኝ “ምኑ?” የሚል ቃል ሊያመልጠኝ ከከንፈሬ ጫፍ ነበር የመለስኩት፡፡ ሔራን ታዲያ ደረቴ ላይ እንደተለጠፈች
(የልብ ምቴን የምታዳምጥ ይመስል) ብዙም ደስ ያለህ አትመስልም” አለችኝ።
ቤተሰቦቻችን ደስታ አናታቸው ላይ ወጥቶ ሽር ጉድ ማለት ጀመሩ፡፡ እንደ ሰርግ
የሚያስጠላኝ ገር የለም፡፡ በሩቁም እፈራው ነበር፡፡ እየተጎተተ መጥቶ ቤቴ በር ላይ አንድ እግሩን አሳረፈ!!
አንድ ምሽት ከሔራን ጋር እራት እየበላን፣ ስለሚዜ ፡ ስለቬሎ፣ ስለኣዳራሽ፣ ስለ ጥሪ ካርድ ስለቀለስት ስናወራ (ስለ አንድ ነገር ሺህ ጊዜ ደጋግሞ ማውራት እንዴት
ይሰለቻል) ድንገት ስልኬ ጠራ፡፡ ዓይኔን እንደዋዛ ጠረጴዛው ላይ ድምፁን አጥፍቶ
ወደሚበራው ስልክ ላከሁ፤የልቤ ምት የቆመ ነበረ የመሰለኝ፡፡ሐኑን…! ስሟ አልነበረም፣ከስልኬ ላይ ካጠፋሁት ቆይቻለሁ፡፡ ቁጥሮቹ እነዚያ ስምንት ቁጥርን የትም ስመለከት፣ልቤ በኃይል እንዲመታ ያደረጉኝ ሦስት ስምንት ቁጥሮች ያሉበት ስልክ ቁጥሯ፡፡
ልጎርስ ያዘጋጀሁትን ጉርሻ ወደ ሰሃኑ መልሼ ተነስቼ ወጣሁና፣ አንድ ጥግ ላይ ቁሜ አነሳሁት፡፡
"ሄሎ"
ሄሎ" ያ በደም ሥሬ ውስጥ የሚፈስ የሚመስለኝ ድምፅ ከእግር ጥፍሬ እስከ እራስ ፀጉሬ ሲነዝረኝ ተሰማኝ፡፡ ሌላ ምንም ሳትተነፍስ አእምሮዬ ከተለያየንበት ቀን እስከዚያች
ቅጽበት ድረስ የነበረ ታሪኬን ሁሉ ሰርዞ ከቆመበት ማሰብ ጀመረ፡፡ መቸ ነው ከሐኑን ጋ የተለያየነው? ከትላንት ወዲያ?ትላንት? ቅድም? ወይንስ አልተለያየንም?
"ሐኑን!?
"አታውቀኝም ብዬ ፈርቼ ነበር” ድምፅዋን ስሰማ አለቀሰች፣ ሞተ፣ ያልኩት ትዝታዬ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
በዝምታ ገባን፡፡ ገና እንደገባን ሔራን አቅፉ ከንፈሬን ሳመችኝ፡፡ ድንገተኛ ነበር፡፡ እናም "ይበቀሃል፡ አንዳንዴ ነገሮች ካልተውካቸው ዛሬን ማየት አትችልም ብላ ሳቀች።
ዓይኖቿን እያየሁ፣ “ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ!" አልኳት፡፡
በቃ እንደዚህ ነው የምታመሰግነው ወደራሴ ሳብኳት፡፡ ሰፊው አልጋ ላይ ተያይዘን ወደቅን ለዓመታት እንደ ሐውልት ውስጤ ገዝፎ የቆመ የሐኑን ፍቅር፣ ትዝታ እና መሻት ሁሉ አብሮ የወደቀ የተንኮታኮተ መሰለኝ፡፡ ከአንዲት ሴት ወደ ሌላ ሴት መሄድ መዳረሻዬ ሳይሆን መንገዴ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ከአንዷ ወደ ሌላዋ ሲረማመዱ የመኖር ጅማሬ፤ ትንሽ ጸጸት ጋር፡፡ የሐኑን ነገር ግን የዚያን ቀን ፍጻሜው ሆነ አልኩ፡፡ ሔራን
አንገቴ ሥር ተሸጉጣ በሹክሹክታ የምታወራውን ብዙ ብዙ የፍቅር ቃል ወንድነቴ ያደመጠው፣ ለሞተው ፍቅሬ እንደሚነበብ የሕይወት ታሪክ ነበር፡፡ ዓይኖቼን ስከድናቸው የሒራን ጠይም ሰውነት የሐኑንን ቅላት ለብሶ ይታየኛል፡፡ማንን እንደምክድ እንጃ፤ የሆነ ክሕደት እየፈጸምኩ መስሎ ይሰማኛል ፡፡ ሔራንን በተለያየ ልብስ ላስባትና ሐሳቤን ልመልሰው በቁንጅናዋ እራሴን ላማልል እታገላለሁ፡፡ “ሔራንኮ ናት ከሥርህ
ያለችው፣ያቺ ምድረ ወንድ የሚያፈጥባት ጠይም ሳቂታ ሔራን ቆንጆዋ ሔራን
እለዋለሁ ለራሴ፡ ውብ ከንፈሮቿን፣ አንዳች ንዝረት የሚለቁ ዓይኖቿን፣ ማንንም ወንድ
የሚፈትኑ ጡቶቿን ባወጣ ባወርድ፣ በእጆቿ ፋይል ይዛ በጉርድ ቀሚስ ወዲያ ወዲህ ስትል ብቻ ነው የምትታየኝ፡፡ ከላያችን ላይ የደረብነውን አንሶላና ምናምን ብገልጠው፣ በግራና በቀኝ እጇ ፋይል እንደያዘች፡ ከነጉርድ ቀሚሷና ከተረከዘ ረጅም ጫማዋ፣ ከሥሬ የተኛች መስሎ ነበር የሚሰማኝ፡፡የሆነ ቢሯችን ውስጥ መሬት ለመሬት የሚሳብ
የኮምፒውተር ገመድ ጠልፎኝ እላይዋ ላይ የወደኩ ዓይነት፡፡
ከሔራን ጋር በአዲስ “ፍቅር መክነፍ ጀመርን፡፡ በተገናኘን ቁጥር የመጀመሪያ ሥራችን አልጋ ላይ መውደቅ ነበር፡፡ ለስሙ ፍቅረኞች ነን እንጂ በሳምንት ውስጥ የሚበዙት ቀኖች አዳሯ እኔ ጋር ነበር፡፡ ቅዳሜና እሁድ አብረን ነን፡፡ ቤቱን እየገዛች በምታመጣው እቃ ሞላችው፡፡ ከማብሰያ እስከመኝታ ቤት፡ የሔራን አሻራ ያላረፈበት እቃ የለም፡፡ቤቱ በወራት ውስጥ፣ አስር ዓመት በትዳር የቆዩ ባለትዳሮች ቤት መሰለ፡፡ ቁምሣጥኑን
ስከፍተው፣ ከእኔ ልብስ ይልቅ የሔራን ይበዛ ነበር፡፡ ወርቃማ የፀጉር ዘለላ የማይገኝበት የቤቱ ክፍል የለም፡፡ ከእሷ አልፎ እህቶቿ ቅዳሜና እሁድ እየመጡ፣ ቡና አፍልተው ሲያውካኩ ውለው ይሄዳሉ፡፡ ልክ ዛሬ እንደተወለደ ሰው፤ ነፍሳቸው ስለነገ ብቻ የሚጨነቅ፣ ወደኋላ የሚባል ነገር የማያውቁ ልጆች ናቸው፡፡ ሲመጡ ደስ ይለኛል፡፡አንዳንዴ እንዲያውም እራሴ እየደወልኩ “ምነው ጠፋችሁ?” እስከማለት ደርሼ ነበር፡፡
የሐኑን ነገር እየደበዘዘ ሄደ፣ ከአእምሮየ የጠፋ እስኪመስለኝ፣ የሐኑንን ጠረን በሔራን ጠረን የመለወጥ ትግል ላይ ነበርኩ፡፡ ወይም ሔራን እራሷ የነብሴ ጥጋጥግ የተገነባዉን የሐኑን መታሰቢያ ሁሉ እያፈራረሰች የራሷን አዲስ መንግሥት እየተከለች ነበር…እንጃ!
አንዴ ሜዳ ሁኛለሁ.…የፈለጉትን ሲተከሉ ሲነቅሉ ተው የሚል ወኔ አልነበረኝም፡፡
ሔራን ፈጣን ናት፡፡ ቆሜ ማሰብ እንኳን እስከሚያቅተኝ፣ ጥድፊያዋ ለጉድ ነበር፡፡ ምንም ነገር ትበለኝ አደርገዋለሁ፤ በራሴ አስቤ ግን አንድም ነገር አላደርግም፡፡ እንስፍስፍ ካለ ፍቅር ይልቅ፣ ራሴን እሷ ላይ ጥዬ ያደረገችኝን ታድርገኝ ወደሚል ስሜት ያዘነበለ ግንኙነት ነበር በመሃላችን የነበረው፡፡ “ከቤተሰቦችህ ጋር አሰተዋውቀኝ አለችኝ፣ ወስጄ
አስተዋወቅኋት፡፡ ወደዷት! አሁን ገና የምትሆንህን አገኘህ ተባለ፡፡ ከቤተሰቦቿ ጋር ወስዳ አስተዋወቀችኝ! የገደል ስባሪ የሚያካለዉ ወንድሟ ቀልቡ ወደደኝ፡፡ እውነቱን ለመናገር እኔም ወድጄው ነበር፡፡ የዓለም ቀልድ ሁሉ እሱጋ ነበር፡፡ ውሃ ቀጠነ ብሎ ከሰው ጋር ከመደባደብና ከመታሰር በተረፈው ጊዜ ሁሉ፣ መሳቅ ሥራው ነበር፡፡ በድፍን ከተማው
በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ስሜ በዋስትና ለመመዝገብ የበቃው፣ ይኼው ልጅ በታሰረ ቁጥር ለማስፈታት ስል ነበር፡፡ እሱም ታዲያ ለገላጋይ አስቸግሮ ዘራፍ ሲል፣ እኔ ከተናገርኩት ግን አደብ ይገዛ ነበር፡፡ እሰቲ ይሄንን ልጅ አንድ በለው፣ አንተን ነው መቼም የሚሰማው ትለኛለች ሔራን፡፡ የሆነ በቤተሰብ ድር የመተብተብ ሳላገባት በቤታቸው የምከበር ወሳኝ ሰው የሆንኩ መስሎ እንዲሰማኝ የማድረግ ጨዋታ፡፡ አልናገረው እንጂ በዙሪያየ የምታደራው ድር ነፍሴ ይገባታል፡፡ እጅ የሰጠን ሰው ለመማረክ የምትደክመው
ነገር ይገርመኛል፡፡
እንደሷው ፍጥን ካሉ ሁለት ቆንጆ እህቶቿ እና እናቷ ጋር ተዋወቅሁ፡፡እንደ አስከሬን
ለአራት ተሹመው ወደቀብሬ እያዳፉ የሚወስዱኝ እስኪመስለኝ ድረስ ወሬያቸው ሁሉ ሰርግና ጋብቻ ብቻ ነበር፡፡ በመጨረሻ ሔራን እራሷ እስከመቼ ነው እንዲህ የምንኖረው?ለምን አንጋባም!?” አለችኝ፡፡ ብንጋባ ከዚህ የተለየ ምን ይመጣል ብዬ ተስማማሁ፡፡ሔራንን ወድጃት ነበር፡፡ የማልወድበት ምንም ምክንያት አልነበረኝም፡፡ የማላገባባትም
እንደዚያው፡፡ እናም “ልክ ነሽ እንጋባ!” አልኳት፡፡ መውደድ ብቻ! ልክ እንደምወደው ምግብ፡ልክ እንደምወደው ፊልም፣ እንደምወደው ልብስ፣ እንድመወደው ምናም ሔራንን ወደድኳት እናም እንጋባ ስትለኝ እሽ አልኩ፡፡
“ጠይቀኛ ሽማግሌ ላክ፤ለምንድን ነው እኔ የሆነ ነገር እስከምል የምትጠብቀኝ?
ወደ ትዳር የሚወስደውን መንገድ እጄን ይዛ መራችኝ፡፡ ባለማመደችኝ ድገተኛ
አጠያየቅ፣ ሰው በተሰበሰበበት ታገቢኛለሽ ወይ? ብዬ ተንበርክኬ ጠየኳት፣ እስካሁን የሚገርመኝ ለምን እንዳለቀሰች ነው፡፡ ያዩን ሁሉ አጨበጨቡ፡፡ ወደቤተሰቦቿ ሽማግሌ
ላውሁ፡፡ ሽማግሌዎቹ ወደነ ሔራን ቤት ሲሔዱ ፣ሔራን እኔ እኔ ኤልጋችን ውስጥ
ነበርን፡፡ ሽማግሌዎቹ ደውለው እንኳን ደስ ያለህ ተሳክቷል” ሲሉኝ “ምኑ?” የሚል ቃል ሊያመልጠኝ ከከንፈሬ ጫፍ ነበር የመለስኩት፡፡ ሔራን ታዲያ ደረቴ ላይ እንደተለጠፈች
(የልብ ምቴን የምታዳምጥ ይመስል) ብዙም ደስ ያለህ አትመስልም” አለችኝ።
ቤተሰቦቻችን ደስታ አናታቸው ላይ ወጥቶ ሽር ጉድ ማለት ጀመሩ፡፡ እንደ ሰርግ
የሚያስጠላኝ ገር የለም፡፡ በሩቁም እፈራው ነበር፡፡ እየተጎተተ መጥቶ ቤቴ በር ላይ አንድ እግሩን አሳረፈ!!
አንድ ምሽት ከሔራን ጋር እራት እየበላን፣ ስለሚዜ ፡ ስለቬሎ፣ ስለኣዳራሽ፣ ስለ ጥሪ ካርድ ስለቀለስት ስናወራ (ስለ አንድ ነገር ሺህ ጊዜ ደጋግሞ ማውራት እንዴት
ይሰለቻል) ድንገት ስልኬ ጠራ፡፡ ዓይኔን እንደዋዛ ጠረጴዛው ላይ ድምፁን አጥፍቶ
ወደሚበራው ስልክ ላከሁ፤የልቤ ምት የቆመ ነበረ የመሰለኝ፡፡ሐኑን…! ስሟ አልነበረም፣ከስልኬ ላይ ካጠፋሁት ቆይቻለሁ፡፡ ቁጥሮቹ እነዚያ ስምንት ቁጥርን የትም ስመለከት፣ልቤ በኃይል እንዲመታ ያደረጉኝ ሦስት ስምንት ቁጥሮች ያሉበት ስልክ ቁጥሯ፡፡
ልጎርስ ያዘጋጀሁትን ጉርሻ ወደ ሰሃኑ መልሼ ተነስቼ ወጣሁና፣ አንድ ጥግ ላይ ቁሜ አነሳሁት፡፡
"ሄሎ"
ሄሎ" ያ በደም ሥሬ ውስጥ የሚፈስ የሚመስለኝ ድምፅ ከእግር ጥፍሬ እስከ እራስ ፀጉሬ ሲነዝረኝ ተሰማኝ፡፡ ሌላ ምንም ሳትተነፍስ አእምሮዬ ከተለያየንበት ቀን እስከዚያች
ቅጽበት ድረስ የነበረ ታሪኬን ሁሉ ሰርዞ ከቆመበት ማሰብ ጀመረ፡፡ መቸ ነው ከሐኑን ጋ የተለያየነው? ከትላንት ወዲያ?ትላንት? ቅድም? ወይንስ አልተለያየንም?
"ሐኑን!?
"አታውቀኝም ብዬ ፈርቼ ነበር” ድምፅዋን ስሰማ አለቀሰች፣ ሞተ፣ ያልኩት ትዝታዬ
👍2❤1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
"የአባባ ጓደኞች ሳይቀሩ በቤተሰብ ጉዳይ አንገባም እያሉ ሸኙኝ...ትምህርት አቤት የማውቃት ልጅ ቤት ዓይኔን አፍጥጬ ሄድኩባት እሷ ጋር ነኝ"
ትንሽ ቆይቼ እደውልልሻለሁ ጠብቂኝ' ብዬ ስልኩን ዘጋሁና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አሰብኩ፡፡ ነፍሴ ተጨነቀች ውስጤ ርብሽብኝ አለ። የምይዝ የምጨብጠውን አጣሁ ምን ማድረግ እንዳለብኝ፣ ምኑም አልመጣልኝ አለ፡፡ እናም በደመነፍስ መልሸ ደውዬ
በሕይወቴ ማድረግ የሌለብኝን የእብድ ሥራ ሠራሁ፣ “ሐኑን ምንም አትጨናነቂ፣ብር እልክልሻለሁ፣ ወደ አዲስ አበባ ትመጫለሽ .…እሺ?”
እሺ!" አለች።እሺታዋ ውስጥ እፎይታ፣ ከስጋት የማረፍ፣ ተስፋ ነበር፡፡ አንድ ቃል
አእምሮዬ ውስጥ ደጋግሞ ይጮህብኝ ነበር፡፡ ከዚያስ? ከመጣች በኋላስ…? ከዚያስ? ከዚያስ ? ከዚያስ …? ከዚያስ ? መልሼ ደግሞ እና ምን ማድረግ ነበረብኝ? ሀብትና ጥላቻ እንደ አሸዋ ሞልቶ ከተረፋቸው ወንድሞቿ ጋር ለምን ከአባቷ ቤት አባረራችኋት? ብየ ልፋለም? ወይስ በሌለኝ አቅምና ጊዜ ጠበቃ ቀጥሬ ልሟገት? ምንም ይሁን ምንም
በሕይወት ውስጥ ተገናኝተናል፣ እንዲሁ ከመገናኘት ያለፈ ታሪክ ያለን ሰዎች ነን፣ ሥራ አለኝ፤ ሥራ የላትም፡ ብር አለኝ፡ ብር የላትም፣ የማርፍበት ቦታ አለኝ፤ የምታርፍበት ቦታ የላትም ከአንዲት ግቢ ወጥታ የማታውቅ ሚስኪን ልጅ፣ ከአባቷ ቀጥሎ በዚህች ምድር ላይ ወደምትቀርበው አንድ ሰው አድነኝ ብላ ደወለች፤ ማዳኑ ቢቀር፣ ትድን ዘንድ ትንሽ
የማሪያም መንገድ መክፈት ከቻልኩ፣ ችግሩ ምንድነው…. ከእራሴ ጋር እየተሟገትኩ ወደ ሔራን ስመለስ ፊቴ ሁሉ ተቀያይሮ ነበር፡፡
“ስላም ነው?” አለችኝ፣ ወደ ስልኬ በአገጯ እየጠቆመች፡፡ ነፍሷ ንቁ ነው፡፡ ትክ ብዬ አየኋት፤ ልዋሻት አልፈለግም፡፡
ከድሬዳዋ ነው አልኳት፡፡ መብላቷን አቁማ ትክ ብላ አየችኝ፡፡ ፊቷ ላይ ስጋት ነበር፡፡
ከድሬዳዋ ማን?
ሐኑን?
ሹካዋን ሰሃኑ ላይ አስቀመጠችና በጉጉት ወሬዬን እንድቀጥል ጠበቀችኝ፡፡ አንድም ነገር ሳልደብቅ የተነጋገርነውን በሙሉ ነገርኳት፡፡ በመጨረሻም “ግራ ስለገባኝ የማይሆን ነገር ቀባጠርኩ፡፡ ብር እልከልሻለሁ ወደ አዲስ አበባ ነይ አልኳት፤ ይቅርታ ሳላማክርሽ …"
በረዥሙ ተንፍሳ እጇን ልካ እጄን ያዘችኝና “የምን መመካከር ነው፣ እኔም ብሆን
ይኼንኑ ነው የማደርገው፤ ልጅቱኮ ችግር ላይ ነች ምን ነካህ? …ማንም ሰው ላይ ሊደርስ የሚችል ነገር ነው!አትጨናነቅ፣ ትምጣ። ዕድሉን ከሰጠኸኝ እኔም እረዳታለሁ፡፡ ነገሮች እስኪስተካከሉ ዙፌ ጋር ታርፋለች” አለች: ዙፋን እህቷ ናት ፡፡
ኖ ይኼን ነገር ከእኔና ከአንች ውጭ ማንም መስማት የለበትም፤ ማንኛችንም ቤተሰብ ጋር እንዲደርስ አልፈልግም”
ኦኬ፡ የተሻለ ነገር ካለ ገረኝ?”
የምታውቂው ደላላ በዚህ ሳምንት አነስ ያለ ቤት እንዲፈልግልን ንገሪው፡፡
እስከዚያው ዋጋው አነስ ያለ ሆቴል ታርፋለች” ሔራን ወዲያው ስልኳን እንስታ ወደ ደላላው ደዎለች ድንገት ዘለን ከገባንበት አረንቃ ለመውጣት የማንጨብጠው ነገር የለ መቸስ ሐኑንን ነይ”የሚለው ቃሌ ምጽአት ከመጥራት እኩል ዓለሜን እንደሚገለባብጠው
የገባኝ ተናግሬ ሳልጨርሰው ነበር፡፡ ግን አሁን ራሱ ጊዜው ወደ ኋላ ተመልሶ ደግማ ብትደውል … እንደገና ልላት የምችለው ነገር ነይ!” ነው!
ሐኑን ከአውቶብስ ወርዳ ከሩቅ ሳያት፣ ውስጤ ሐዘን ይሁን ደስታ ባልገባኝ ስሜት ሲናወጥ ይሰማኝ ነበር፡፡ በግርግሩ ውስጥ ዓይኗን እያንከራተተች ስትፈልገኝ፣ ዝም ብዬ ለደቂቃዎች ከሩቅ አየኋት፡፡ እስቲ አሁን በምን አምናኝ እዚህ የማታውቀው ከተማ ድረስ መጣች!? ሐሳቤን ቀይሬ የራሷ ጉዳይ ብዬ ብተዋት የት ትሄዳለች? ኦህ! ከዚህ ሁሉ ችግር
በኋላም እጅግ ውብ ነበረች፡፡ሁሉን ነገር ድንገት አጥታ፣ ከዚያ ውብና ቅንጡ ኑሮ ተሰዳ የመጣች ምጻተኛ ፍቅር ተሰዶ የተንከራተተ መሰለኝ፣ ሰላም ተሰዶ የተንከራተተ መሰለኝ፣ እኔ ራሴ ውስጧ ተቀምጨ የተሰደድኩ መሰለኝ፡፡ ቀጥ ብዬ ወደ ቆመችበት ሄድኩ፤ ስታየኝ ተንደርድራ አቀፈችኝና ስቅስቅ ብላ ማልቀስ ጀመረች፡፡ ጠረኗ በቅጽበት የአእምሮዬን የተቆለፈ ስር በርግዶ፣ እያንዳንዷን ያሳለፍናትን ቅጽበት ልቤ ላይ
ዘረገፈው። የልብስ ሻንጣዋን ይዝለች፣ መኪና ወዳቆምኩበት ስወስዳት በግርግሩ ውስጥ እንዳልጠፋባት ክንዴን ጨምድዳ ይዛ ትከተለኝ ነበር፡፡ አያያዟ ፍርሐቷን ነግሮኛል፡፡
አያያዟ ጭው ካለ ገደል ጫፍ ላይ የተንጠለጠለ ሰው፣ ላለመውደቅ እንደያዘው ገመድ፣ የመጨረሻ አማራጭ እኔ መሆኔን ነግሮኛል፡፡ ቃል አላወጣችም፡ አያያዟ ነው ጩሆ ይችን ልጅ አደራ ያለኝ!! ያኔ ነው ለራሴ ብቻ በሚሰማ ድምፅ አይዞሽ!” ያልኩት፡፡ውስጤ የከበበኝን ስጋት ሁሉ ረስቶ በደስታ ይዘል ጀመር፡፡ ኑሮ ሁሉንም ነገር ያዘበራረቀባት ሐኑን መኪናዬ ውስጥ ገብታ እጎኔ ስትቀመጥ፣ ሲንቀዥቀዥ የኖረ ነፍሴ ሲረጋጋ ይታወቀኝ ነበር፡፡ ዙሪያዋን የማይታይ ሞግድ አለ፡፡ ስቀርባት ንዝረቱ በደም
ሥሬ የሚያልፍ፡፡
ወደያዝኲላት ሆቴል ስወስዳት፣ ምንም አልተነጋገርንም፡፡ አልፎ አልፎ እየዞርኩ
አያታለሁ፡፡ የዋህና ንጹህ ፈገግታዋ በሐዘን ደመና በተከበበ ፊቷ ላይ ብልጭ ብሎ ይጠፋል፡፡ ከመምጣቷ በፊት ስለ ማረፊያዋ ስለ ነገርኳት አልተደናገጠችም ወዲያው ስልኬ ጮኸ፡ ሔራን … “ሔራን የምትባል እጮኛ አለችኝ" አልኩ ለራሴ፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ በመደወሏ ውስጤ ሲበሳጭ ይሰማኝ ነበር፡፡ ሐኑንን ከተቀበልኩ በኋላ፣ ቀለበት ለማየት እንሄዳለን ተባብለን ተቀጣጥረናል: ሐኑን እረፍ እንድትል ነግሪያት፣ የፈለገችውን ክፍሏ ውስጥ ሆና በስልክ እንድታዝ፣ እንዴት ማዘዝ እንዳለባት አሳይቻት፣
በዚያውም ምሳ አዝዤላት፣ ከቻልኩ ማታ፣ ካልሆነም ነገ እመለሳለሁ ብያት ልወጣ ስል እፊቴ ቁማ እጆቿን እርስ በእርስ እያፍተለተለቾ እነዚያን ዓይኖቿን እያንከባለለች እንደ ሕጻን ልጅ የምላትን ሁሉ እሺ! እሺ' ስትለኝ ውስጤ ተንሰፈሰፈ ድንገት ወደ ራሴ ስቤ አቀፍኳት፡፡ ስቅስቅ ብላ ስታለቅስ፣ እንባዩን ለመቆጣጠር እየታገልኩ ነበር፡፡ ፊቴን ሳላዞር እዚያዉ በቆመችበት ትቻት ወጣሁ፡፡ ያረፈችበትን ሆቴል ሕንጻ ከውጭ ስመለከተው ፣ አንዳች ቤተመቅደስ ነገር መስለኝ፡፡ ድፍን ዓለም ቢታሰስ፣ በዚያች ሰዓት የልቤ መሻት ደስታዬ የተቀመጠበት ከዚህ የተሻለ ቦታ አይገኝም።
ከሆቴሉ እንደወጣሁ ወደ ፒያሳ ከነፍኩ፡፡ ሔራንን ከእህቷ ጋር አገኘኋት፡፡ ስለሐኑን
ብዘም ኤልጠየቀችኝም:እህቷ እንዳትሰማ ወደጆሮዬ ጠጋ ብላ ሰላም ገባች?” ብቻ
ብላኝ፣ ወደቀለበት መረጣችን ሄድን። ይኼን የሰርግ ጉዳይ እያንዳንዷን ጥቃቅን ቅጽበት በደንብ እየተዝናናችበት ነበር፡፡ በሚያምር ጣቷ ላይ ቀለበት ስትለካና ስታወልቅ እያየኋት፣ “ሕይወት እንዲህ ናት? እላለሁ፡፡ ጥቂቶች ብቻ ይመስሉኛል ትከከለኛው ጣት ላይ የቃል ኪዳን ቀለበታቸውን ለመሰካት የታደሉ፡፡ እንደ አገር ባይጮኽለትም፣ምክንያቱ ይለያይ እንጂ የሚበዛው ትዳር ቅኝ ግዛት ነው! “ማን አስገደደህ? ወደህ ነው የገባህበት” የሚለው ጀግና መሳይ ችቶት፣ ራሱ የፈሪ ዱላ ነው፡፡ ማንም ያስገድድህ፣ ያውልህ መውጫ መንገዱ፤ የሚል ጀግና ወዳጅ እምብዛም ነው፡፡
እንዴት ነው?” ትለኛለች ቀለበት በሰካች ቁጥር፤ ጣቷን እንደሹካ ፊቴ ላይ
እንጨፍርራ
“ጥሩ ነው” እላለሁ፡፡ በዚያ ሰዓት እንኳን ቀለበቷን ልመለኮት ይቅርና፣ የቀለበት ጣቷ ቦታው ላይ ባይኖር የማስተውል አይመስለኝም ሥጋ ነበር የሚንገላወደው ፤ ነብሴ አጠገቧ ኤልነበረም፡፡ የፖሊስ ካቴና እጇ ላይ አጥልቃ እንዴት ነው?
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
"የአባባ ጓደኞች ሳይቀሩ በቤተሰብ ጉዳይ አንገባም እያሉ ሸኙኝ...ትምህርት አቤት የማውቃት ልጅ ቤት ዓይኔን አፍጥጬ ሄድኩባት እሷ ጋር ነኝ"
ትንሽ ቆይቼ እደውልልሻለሁ ጠብቂኝ' ብዬ ስልኩን ዘጋሁና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አሰብኩ፡፡ ነፍሴ ተጨነቀች ውስጤ ርብሽብኝ አለ። የምይዝ የምጨብጠውን አጣሁ ምን ማድረግ እንዳለብኝ፣ ምኑም አልመጣልኝ አለ፡፡ እናም በደመነፍስ መልሸ ደውዬ
በሕይወቴ ማድረግ የሌለብኝን የእብድ ሥራ ሠራሁ፣ “ሐኑን ምንም አትጨናነቂ፣ብር እልክልሻለሁ፣ ወደ አዲስ አበባ ትመጫለሽ .…እሺ?”
እሺ!" አለች።እሺታዋ ውስጥ እፎይታ፣ ከስጋት የማረፍ፣ ተስፋ ነበር፡፡ አንድ ቃል
አእምሮዬ ውስጥ ደጋግሞ ይጮህብኝ ነበር፡፡ ከዚያስ? ከመጣች በኋላስ…? ከዚያስ? ከዚያስ ? ከዚያስ …? ከዚያስ ? መልሼ ደግሞ እና ምን ማድረግ ነበረብኝ? ሀብትና ጥላቻ እንደ አሸዋ ሞልቶ ከተረፋቸው ወንድሞቿ ጋር ለምን ከአባቷ ቤት አባረራችኋት? ብየ ልፋለም? ወይስ በሌለኝ አቅምና ጊዜ ጠበቃ ቀጥሬ ልሟገት? ምንም ይሁን ምንም
በሕይወት ውስጥ ተገናኝተናል፣ እንዲሁ ከመገናኘት ያለፈ ታሪክ ያለን ሰዎች ነን፣ ሥራ አለኝ፤ ሥራ የላትም፡ ብር አለኝ፡ ብር የላትም፣ የማርፍበት ቦታ አለኝ፤ የምታርፍበት ቦታ የላትም ከአንዲት ግቢ ወጥታ የማታውቅ ሚስኪን ልጅ፣ ከአባቷ ቀጥሎ በዚህች ምድር ላይ ወደምትቀርበው አንድ ሰው አድነኝ ብላ ደወለች፤ ማዳኑ ቢቀር፣ ትድን ዘንድ ትንሽ
የማሪያም መንገድ መክፈት ከቻልኩ፣ ችግሩ ምንድነው…. ከእራሴ ጋር እየተሟገትኩ ወደ ሔራን ስመለስ ፊቴ ሁሉ ተቀያይሮ ነበር፡፡
“ስላም ነው?” አለችኝ፣ ወደ ስልኬ በአገጯ እየጠቆመች፡፡ ነፍሷ ንቁ ነው፡፡ ትክ ብዬ አየኋት፤ ልዋሻት አልፈለግም፡፡
ከድሬዳዋ ነው አልኳት፡፡ መብላቷን አቁማ ትክ ብላ አየችኝ፡፡ ፊቷ ላይ ስጋት ነበር፡፡
ከድሬዳዋ ማን?
ሐኑን?
ሹካዋን ሰሃኑ ላይ አስቀመጠችና በጉጉት ወሬዬን እንድቀጥል ጠበቀችኝ፡፡ አንድም ነገር ሳልደብቅ የተነጋገርነውን በሙሉ ነገርኳት፡፡ በመጨረሻም “ግራ ስለገባኝ የማይሆን ነገር ቀባጠርኩ፡፡ ብር እልከልሻለሁ ወደ አዲስ አበባ ነይ አልኳት፤ ይቅርታ ሳላማክርሽ …"
በረዥሙ ተንፍሳ እጇን ልካ እጄን ያዘችኝና “የምን መመካከር ነው፣ እኔም ብሆን
ይኼንኑ ነው የማደርገው፤ ልጅቱኮ ችግር ላይ ነች ምን ነካህ? …ማንም ሰው ላይ ሊደርስ የሚችል ነገር ነው!አትጨናነቅ፣ ትምጣ። ዕድሉን ከሰጠኸኝ እኔም እረዳታለሁ፡፡ ነገሮች እስኪስተካከሉ ዙፌ ጋር ታርፋለች” አለች: ዙፋን እህቷ ናት ፡፡
ኖ ይኼን ነገር ከእኔና ከአንች ውጭ ማንም መስማት የለበትም፤ ማንኛችንም ቤተሰብ ጋር እንዲደርስ አልፈልግም”
ኦኬ፡ የተሻለ ነገር ካለ ገረኝ?”
የምታውቂው ደላላ በዚህ ሳምንት አነስ ያለ ቤት እንዲፈልግልን ንገሪው፡፡
እስከዚያው ዋጋው አነስ ያለ ሆቴል ታርፋለች” ሔራን ወዲያው ስልኳን እንስታ ወደ ደላላው ደዎለች ድንገት ዘለን ከገባንበት አረንቃ ለመውጣት የማንጨብጠው ነገር የለ መቸስ ሐኑንን ነይ”የሚለው ቃሌ ምጽአት ከመጥራት እኩል ዓለሜን እንደሚገለባብጠው
የገባኝ ተናግሬ ሳልጨርሰው ነበር፡፡ ግን አሁን ራሱ ጊዜው ወደ ኋላ ተመልሶ ደግማ ብትደውል … እንደገና ልላት የምችለው ነገር ነይ!” ነው!
ሐኑን ከአውቶብስ ወርዳ ከሩቅ ሳያት፣ ውስጤ ሐዘን ይሁን ደስታ ባልገባኝ ስሜት ሲናወጥ ይሰማኝ ነበር፡፡ በግርግሩ ውስጥ ዓይኗን እያንከራተተች ስትፈልገኝ፣ ዝም ብዬ ለደቂቃዎች ከሩቅ አየኋት፡፡ እስቲ አሁን በምን አምናኝ እዚህ የማታውቀው ከተማ ድረስ መጣች!? ሐሳቤን ቀይሬ የራሷ ጉዳይ ብዬ ብተዋት የት ትሄዳለች? ኦህ! ከዚህ ሁሉ ችግር
በኋላም እጅግ ውብ ነበረች፡፡ሁሉን ነገር ድንገት አጥታ፣ ከዚያ ውብና ቅንጡ ኑሮ ተሰዳ የመጣች ምጻተኛ ፍቅር ተሰዶ የተንከራተተ መሰለኝ፣ ሰላም ተሰዶ የተንከራተተ መሰለኝ፣ እኔ ራሴ ውስጧ ተቀምጨ የተሰደድኩ መሰለኝ፡፡ ቀጥ ብዬ ወደ ቆመችበት ሄድኩ፤ ስታየኝ ተንደርድራ አቀፈችኝና ስቅስቅ ብላ ማልቀስ ጀመረች፡፡ ጠረኗ በቅጽበት የአእምሮዬን የተቆለፈ ስር በርግዶ፣ እያንዳንዷን ያሳለፍናትን ቅጽበት ልቤ ላይ
ዘረገፈው። የልብስ ሻንጣዋን ይዝለች፣ መኪና ወዳቆምኩበት ስወስዳት በግርግሩ ውስጥ እንዳልጠፋባት ክንዴን ጨምድዳ ይዛ ትከተለኝ ነበር፡፡ አያያዟ ፍርሐቷን ነግሮኛል፡፡
አያያዟ ጭው ካለ ገደል ጫፍ ላይ የተንጠለጠለ ሰው፣ ላለመውደቅ እንደያዘው ገመድ፣ የመጨረሻ አማራጭ እኔ መሆኔን ነግሮኛል፡፡ ቃል አላወጣችም፡ አያያዟ ነው ጩሆ ይችን ልጅ አደራ ያለኝ!! ያኔ ነው ለራሴ ብቻ በሚሰማ ድምፅ አይዞሽ!” ያልኩት፡፡ውስጤ የከበበኝን ስጋት ሁሉ ረስቶ በደስታ ይዘል ጀመር፡፡ ኑሮ ሁሉንም ነገር ያዘበራረቀባት ሐኑን መኪናዬ ውስጥ ገብታ እጎኔ ስትቀመጥ፣ ሲንቀዥቀዥ የኖረ ነፍሴ ሲረጋጋ ይታወቀኝ ነበር፡፡ ዙሪያዋን የማይታይ ሞግድ አለ፡፡ ስቀርባት ንዝረቱ በደም
ሥሬ የሚያልፍ፡፡
ወደያዝኲላት ሆቴል ስወስዳት፣ ምንም አልተነጋገርንም፡፡ አልፎ አልፎ እየዞርኩ
አያታለሁ፡፡ የዋህና ንጹህ ፈገግታዋ በሐዘን ደመና በተከበበ ፊቷ ላይ ብልጭ ብሎ ይጠፋል፡፡ ከመምጣቷ በፊት ስለ ማረፊያዋ ስለ ነገርኳት አልተደናገጠችም ወዲያው ስልኬ ጮኸ፡ ሔራን … “ሔራን የምትባል እጮኛ አለችኝ" አልኩ ለራሴ፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ በመደወሏ ውስጤ ሲበሳጭ ይሰማኝ ነበር፡፡ ሐኑንን ከተቀበልኩ በኋላ፣ ቀለበት ለማየት እንሄዳለን ተባብለን ተቀጣጥረናል: ሐኑን እረፍ እንድትል ነግሪያት፣ የፈለገችውን ክፍሏ ውስጥ ሆና በስልክ እንድታዝ፣ እንዴት ማዘዝ እንዳለባት አሳይቻት፣
በዚያውም ምሳ አዝዤላት፣ ከቻልኩ ማታ፣ ካልሆነም ነገ እመለሳለሁ ብያት ልወጣ ስል እፊቴ ቁማ እጆቿን እርስ በእርስ እያፍተለተለቾ እነዚያን ዓይኖቿን እያንከባለለች እንደ ሕጻን ልጅ የምላትን ሁሉ እሺ! እሺ' ስትለኝ ውስጤ ተንሰፈሰፈ ድንገት ወደ ራሴ ስቤ አቀፍኳት፡፡ ስቅስቅ ብላ ስታለቅስ፣ እንባዩን ለመቆጣጠር እየታገልኩ ነበር፡፡ ፊቴን ሳላዞር እዚያዉ በቆመችበት ትቻት ወጣሁ፡፡ ያረፈችበትን ሆቴል ሕንጻ ከውጭ ስመለከተው ፣ አንዳች ቤተመቅደስ ነገር መስለኝ፡፡ ድፍን ዓለም ቢታሰስ፣ በዚያች ሰዓት የልቤ መሻት ደስታዬ የተቀመጠበት ከዚህ የተሻለ ቦታ አይገኝም።
ከሆቴሉ እንደወጣሁ ወደ ፒያሳ ከነፍኩ፡፡ ሔራንን ከእህቷ ጋር አገኘኋት፡፡ ስለሐኑን
ብዘም ኤልጠየቀችኝም:እህቷ እንዳትሰማ ወደጆሮዬ ጠጋ ብላ ሰላም ገባች?” ብቻ
ብላኝ፣ ወደቀለበት መረጣችን ሄድን። ይኼን የሰርግ ጉዳይ እያንዳንዷን ጥቃቅን ቅጽበት በደንብ እየተዝናናችበት ነበር፡፡ በሚያምር ጣቷ ላይ ቀለበት ስትለካና ስታወልቅ እያየኋት፣ “ሕይወት እንዲህ ናት? እላለሁ፡፡ ጥቂቶች ብቻ ይመስሉኛል ትከከለኛው ጣት ላይ የቃል ኪዳን ቀለበታቸውን ለመሰካት የታደሉ፡፡ እንደ አገር ባይጮኽለትም፣ምክንያቱ ይለያይ እንጂ የሚበዛው ትዳር ቅኝ ግዛት ነው! “ማን አስገደደህ? ወደህ ነው የገባህበት” የሚለው ጀግና መሳይ ችቶት፣ ራሱ የፈሪ ዱላ ነው፡፡ ማንም ያስገድድህ፣ ያውልህ መውጫ መንገዱ፤ የሚል ጀግና ወዳጅ እምብዛም ነው፡፡
እንዴት ነው?” ትለኛለች ቀለበት በሰካች ቁጥር፤ ጣቷን እንደሹካ ፊቴ ላይ
እንጨፍርራ
“ጥሩ ነው” እላለሁ፡፡ በዚያ ሰዓት እንኳን ቀለበቷን ልመለኮት ይቅርና፣ የቀለበት ጣቷ ቦታው ላይ ባይኖር የማስተውል አይመስለኝም ሥጋ ነበር የሚንገላወደው ፤ ነብሴ አጠገቧ ኤልነበረም፡፡ የፖሊስ ካቴና እጇ ላይ አጥልቃ እንዴት ነው?
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ሔራን ሐኑንን ለመጀመሪያ ጊዜ ስትተዋወቃት፣ስሜቷን መደበቅ አልቻለችም ነበር፡፡ ስንመለስ ገና መኪና ውስጥ ከመግባታችን በጣም ቆንጆ ናት! እንደዚህ አልጠበኳትም ነበር አለች፡፡ ጠይም ፊቷ ማንም መንገደኛ በሚያነበው ቅናት ተሸፍኖ፣እጇ ሁሉ
በብስጭት እንደመንቀጥቀጥ ሲል አይቼው ነበር፡፡ “በጣም ልጅ ነች፣ ቆንጆ ነች ብታፈቅራት አይገርምም !እኔጃ እንደዚህ አልጠበኳትም ነበር ደገመችው የሆነ ነገር አንድላትና የምትጮኸበት ምክንያት እንዲፈጠር ፈልጋ እንደነበር ገብቶኝ ዝም ብዬ ቆየሁና “በአሁኑ ሰዓት በዚች ምድር ላይ የማውቃት ቆንጆ ሴት አንድ ብቻ ነች ያው ላገባት ነው!”
የእውነት ግን አንድ ነገር ልጠይቅህ፣ እሰቲ አቁመው…መኪናውን የሆነ ቦታ አቁመው “ፕሊስ አቁመው እንደ ዕብድ አድርጓት ነበር፡፡
እቤት እንሄዳለን፤ እቤት እናወራለን”
"ኖ ዛሬ ከአንተ ጋር መሄድ አልፈልግም፣ ወደ ቤቴ ነው የምሄደው፡፡ እዚሁ አቁመው
እንዳልሰማ ዝም ብዬ ወደቤቴ ወሰድኳት ገና እንደገባን… እንደ እንግዳ ሶፋው ጫፍ ላይ ቁጭ አለች፡፡ የተቀመጠችበት ሄጄ ሳምኳት፡፡ ባላሰብኩት ፍጥነት ጥፊዋ ጉንጬ ላይ ሲያርፍ፣ ሰማይና ምድሩ ዞረብኝ፡፡
ንገረኝ! … ያረፈችበት ሆቴል ስትሄድ ምንም አላደረጋችሁም? እ?”
ወገቤን ይዤ ከፊቷ ለፊቷ ቆምኩ፤ እናም “ከፈለግሁ አሁንም አታቆሚኝምኮ!” ብዬ
አፈጠጥኩባት፡፡
ዘላ አቀፈችኝ እና ዓይኔን፣ ጆሮዬን፡ያገኘትውን ሁሉ እየሳመች ወደ አልጋው ስትገፋኝ ተያይዘን ወደቅን፡፡ ሸሚዜን ስትጎትተው አንዱ ቁልፍ ተበጥሶ በረረ፡፡ አነር ነበር የሆነቸው እንደ እብድ ልብሳችንን እያወለቅን ወረወርነው ተንጠራርታ መብራቱን አጠፋችውና፣ በጨለማዉ ውስጥ ድክም ባለ ድምፅ ሳያት ቀናሁ…! እንደ ዛሬ በሕይወቴ የበታችነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ የሆነ ኩትት ያልኩ ባልቴት የሆኑኩ
ነው የመሰለኝ ንገረኝ
“ምን ልንገርሽ? ሔር'
ቆንጆ ነሽ በለኝ - እወድሻለሁ በለኝ…ወንዶች ጋር ሳወራ እንደምትቀናብኝ ንገረኝ እንደምትፈልገኝ ንገረኝ የሆነ ነገር በል፣ በቃ የፈለከውን ጠንካራዋ ሔራን
ከተዋወቅን ጀምር ለመጀመሪያ ጊዜ እያለቀሰች ነበር፡፡
እንደዚያን ቀን ሁለታችንም በስሜት ጡዘን አናውቅም፡፡ ጨለማው ውስጥ በዚያ ሁሉ ላለመበለጥ በሚደረግ የሴትነት ትንቅንቅ ውስጥ፡በዘያ ሁሉ የአትርሳኝ ተማጽኖ መሃል፣
ጨለማው ላይ ገዝፎ የታየኝ የሐኑን መልክ ነበር። ልክፍት ነው! መብራቱን ድንገት ባበራው ከስሬ የምትንፋረቀው ሔራን፣ በሆነ ተአምር ሐኑን ሆና በቀይ ፊቷ ላይ እንባ ሲንኳለል የማገኛት እስኪመስለኝ፡፡ በሕይወት ውስጥ ግን፡ ማሸነፍ የሚባል ነገር የእውነት ይኖር ይሆን? ሔራን አሸንፋ እኔን ልታገባ ነው እኔ ተሸንፌ ሐኑንን ከነፍቅሯ ተነጥቂያለው ሐኑን በወንድሞቿ ተሸንፋ ሁሉንም ነገሯን ተነጥቃ እኔ እጅ ላይ ወድቃለች፡፡በኑሮ የተሸነፈችው ሐኑን ኑሮ እሹሩሩ የሚላትን ሙሽራ አሸንፍ እያስለቀሰች ነው፡፡እኔ ያቀፍኳት ሴት ጠይምነት በቀይ ቅዠት ተሸንፎ ያቀፍኩትና ያሰብኩት የሚምታታብኝ ደንጋራ ሁኛለሁ። ሁሉም አሸናፊ ከጭብጨባ ኋላ የሚያነሳው
የሽንፈት ዋንጫ አለ፡፡ ማሸነፍ የሚባል ነገር እዚያ መለኮታዊው ዓለም ላይ ካልሆነ በስተቀር ምድር የተሸናፊዎች ርስት ናት፡፡ ሁለታችንንም እንቅልፍ አሸንፎ ይዞን ጭልጥ አለ፡፡ ጧት ስንነሳ ሔራን ዓይኔን ማየት አፍራ ነበር፡፡
ቁርስ ልጋብዝሽ አልኳት ዝቅ ባለ ድምፅ፡፡
እሺ አለችኝ፡፡ ሰውን ሁሉ ምን ነካው? እሺ ብቻ! ቁርስ እየበላን ሰሃኗ ላይ አቀርቅራ
እንዲህ አለትኝ፣
ዓይኗ ከአንተ ላይ አይነቀልም፣እንስፍስፍ ብላ ነው የምታይህ፤ አውቃለሁ ሰው
ሲያፈቅር ምን እንደሚሆን፡፡በተለይ ሴት ስታፈቅር፣ ታፈቅርሃለች ማንም ሴት ብትሆን የእኔ ያለችው ወንድ በሌላ ሴት ተፈቅሮ ማየት፣ ግማሽ ስጋት ነው፡፡ ሳት ቢልህ ፣እምቢ የምትል ዓይነት አይደለችም” እናም የቀረበውን ቁርስ ንክች ሳታደርገው፣ ገፋ አደረገችው።
ሔራን የበላይነቷን ለማሳየት፣ በሐኑን ላይ የማታደርገው ነገር አልነበረም፡፡ የሚገባኝ እኔ ብቻ ነበርኩ፡፡ ሐኑን ራሷ “ይኼማ ወደር የሌለው በጎነት ነው” ልትለው የምትችለውን ድርጊት፣ ዓይኔን ጨፍኜ የሔራን ሰይጣናዊ ቅጣት እንደሆነ መናገር እችላለሁ፡፡እንደዓይኔ ብሌን ነበር ሐኑንን የምጠብቃት፡፡ አንድ ቀን ሰርጋችን ሲቃረብ፣ ሔራን ሐኑን ሥራ ታግዘን፣ ለዛውም ብቻዋን እንዳይደብራት እኛ ጋር ትሁን በሚል ሰበብ እቤታቸው ወሰደቻት የሔራን እህቶች፣ የእኔ ሁለት ጓደኞች (ለሚዜነት ሽር ጉድ የሚሉ) ቤቱን ሞልተን እናወራለን ሔራን ድንገት አንድ ጅንስ ሱሪ አንጠልጥላ ሐኑን ነይ ይሄን ለኪው እስኪ፣ ብዙም እለበስኩትም ጠቦኝ ነው፣ ልክሽ ከሆነ ትወስጅዋለሽ አለቻት። በሰው ፊት አሮጌ ሱሪዋን ለሐኑን በመመጽወት የበላይነቷን ለማሳየት
ያደረገችው መሆኑን በደንብ ነው የገባኝ። ምንም ነገር በፍቅር ቢያደርጉት ነውር
አይደለም፤ እንዲህ ዓይነት ጋጠወጥነት ግን ያቅለሸልሻል …ሐኑን ሻንጣ ተከፍቶ እጅ እንዳመጣ ቢላክ፣ሔራን እንደ ቅርስ የምትኮራበትን ዓይነት አስር ጅንስ ሱሪ የሚገዛ የቱርክ ቀሚስ ተመዞ ይወጣል፡፡ ነውረኛ!
እኔና ሔራን እንዲህ አይጥና ድመት ድብብቆሽ ላይ ሆነን ድል ባለ ሰርግ ተጋባን፡፡ እኔ ባልፈልግም፣ ሔራን ጠርታት ስለነበር ሐኑን ሰርጌ ላይ ተገኘት፡፡ ይኼም እንደ ቅስም መስበሪያ መሆኑ ነው፡፡ የሔራን አስቀያሚ ፖለቲካ፡፡ እንዲያውም እሁቶቿ ሆነ ብለው ሐኑንን ከሌሎች ወንዶች ጋር ለማቀራረብ ሲሞከሩ፣ ከሙሽራ ወንበሬ ላይ ሆኜ በጭፈራው መሃል እታዘብ ነበር፡፡ ከጎኔ በቬሎ ደምቃ ካሜራው ወደኛ በዞረ ቁጥር
ሠላሳ ሁለት ጥርሷን የምታሳየውን ሒራንን፣ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብዬ “ሐኑንን ወደ ቤት እንዲሸኞት ንገሪያቸው አልኳት፡፡ ፈገግ እንዳለች “ምንድን ነው በሰርግህ ቀን እንኳን የዚች ልጅ ስም ከአፍህ የማይጠፋው? ተዋት ትጨዋት፣ ከሰዎችም ጋር ትቀላቀል፣ ባዶ
ቤት አፍነህ ምን ልታደርጋት ነው? ሆሆአለችኝ፡፡ ቁጣዬን መደበቅ አልቻልኩም ኮስተር ብዬ
ሔራን እንዲሸኟት ንገሪያቸው" አልኳት፤ እያንዳንዱን ፊደል ርግጥ አድርጌ:: መኮሳተሪ አስፈርቷት ይሁን፤ ሰርጓ እንዳይበላሽ ፈርታ፣ ፈገግ እንዳለች ሚዜዋን ጠርታ፣ ጆሮዋ የሆነ ነገር ነገረቻት፡፡ ሐኑንን ወዲያው ወደ ቤቷ ወስዷት። ማታ እልል እየተባለልን
የገባንስት ጫጉላ ቤት ውስጥ የመጀመሪያ ንግግራችን ወደንዝንዝ ያደላ ነበር፡፡ “ቆይ የፈለገችው ጋር ብታወራ አንተ ምን አስጨነቀህ…? ሕፃን ልጅ አይደለችም! የቤት ኪራይ ስለከፈልክላት ብቻ፣ ከማን ጋር ማውራት፣ ማንን አለማውራት እንዳለባት መወሰን
ትችላለህ ማለት አይደለምኮ!…ተዋት በቃ! ልጅቱን….ነፃነቷን ስጣት! ሌላ ነገር ውስጥህ ከሌለ በስተቀር ይኼን ያህል
“በቃ! ሲጀመር የአንቺ እህቶችም ሆኑ የኔ ቤተሰቦች ስለ ሐኑን ምንም እንዲያውቁ
አልፈልግም ብዬ ነግሬሻለሁ፡፡ አንቺ ግን ለእህቶችሽ ነግረሻቸዋል፡፡ እናም ገፋፍተው አንዱ ወንድ ላይ ስላጣበቋት፣ በአንቺ ሴት ትዳርሽ ከስጋት ነፃ ይሆናል! ደግሜ እነግርሻለሁ…ከሐኑን ጋር ምንም ጐዳይ የለኝም! ምንም! የዚህ ዓይነቱን ተንኮላችሁን አቁሙ፤አንቺም እህቶችሽም ለአንዲት ሚስኪን ይኼን ያህል ርብርብ ምንድነው?እኔ የሚያስፈልጋትን ከመስጠት ያለፈ ምንም አላደረኩም፤ ከሰው ጋር አታውሪም አላልኩም፡፡
አንቺ ነሽ ዙሪያዋን እየዞርሽ የማይረባ ድብብቆሽ የምትጫዎችው…በቃ ተያት!»
እንደተኮራረፍን ወደ አልጋችን አመራን፡፡
ሌላ ዓለም ነበር ይኼንኛው በለስላሳ እጆቿ ሰውነቴን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ሔራን ሐኑንን ለመጀመሪያ ጊዜ ስትተዋወቃት፣ስሜቷን መደበቅ አልቻለችም ነበር፡፡ ስንመለስ ገና መኪና ውስጥ ከመግባታችን በጣም ቆንጆ ናት! እንደዚህ አልጠበኳትም ነበር አለች፡፡ ጠይም ፊቷ ማንም መንገደኛ በሚያነበው ቅናት ተሸፍኖ፣እጇ ሁሉ
በብስጭት እንደመንቀጥቀጥ ሲል አይቼው ነበር፡፡ “በጣም ልጅ ነች፣ ቆንጆ ነች ብታፈቅራት አይገርምም !እኔጃ እንደዚህ አልጠበኳትም ነበር ደገመችው የሆነ ነገር አንድላትና የምትጮኸበት ምክንያት እንዲፈጠር ፈልጋ እንደነበር ገብቶኝ ዝም ብዬ ቆየሁና “በአሁኑ ሰዓት በዚች ምድር ላይ የማውቃት ቆንጆ ሴት አንድ ብቻ ነች ያው ላገባት ነው!”
የእውነት ግን አንድ ነገር ልጠይቅህ፣ እሰቲ አቁመው…መኪናውን የሆነ ቦታ አቁመው “ፕሊስ አቁመው እንደ ዕብድ አድርጓት ነበር፡፡
እቤት እንሄዳለን፤ እቤት እናወራለን”
"ኖ ዛሬ ከአንተ ጋር መሄድ አልፈልግም፣ ወደ ቤቴ ነው የምሄደው፡፡ እዚሁ አቁመው
እንዳልሰማ ዝም ብዬ ወደቤቴ ወሰድኳት ገና እንደገባን… እንደ እንግዳ ሶፋው ጫፍ ላይ ቁጭ አለች፡፡ የተቀመጠችበት ሄጄ ሳምኳት፡፡ ባላሰብኩት ፍጥነት ጥፊዋ ጉንጬ ላይ ሲያርፍ፣ ሰማይና ምድሩ ዞረብኝ፡፡
ንገረኝ! … ያረፈችበት ሆቴል ስትሄድ ምንም አላደረጋችሁም? እ?”
ወገቤን ይዤ ከፊቷ ለፊቷ ቆምኩ፤ እናም “ከፈለግሁ አሁንም አታቆሚኝምኮ!” ብዬ
አፈጠጥኩባት፡፡
ዘላ አቀፈችኝ እና ዓይኔን፣ ጆሮዬን፡ያገኘትውን ሁሉ እየሳመች ወደ አልጋው ስትገፋኝ ተያይዘን ወደቅን፡፡ ሸሚዜን ስትጎትተው አንዱ ቁልፍ ተበጥሶ በረረ፡፡ አነር ነበር የሆነቸው እንደ እብድ ልብሳችንን እያወለቅን ወረወርነው ተንጠራርታ መብራቱን አጠፋችውና፣ በጨለማዉ ውስጥ ድክም ባለ ድምፅ ሳያት ቀናሁ…! እንደ ዛሬ በሕይወቴ የበታችነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ የሆነ ኩትት ያልኩ ባልቴት የሆኑኩ
ነው የመሰለኝ ንገረኝ
“ምን ልንገርሽ? ሔር'
ቆንጆ ነሽ በለኝ - እወድሻለሁ በለኝ…ወንዶች ጋር ሳወራ እንደምትቀናብኝ ንገረኝ እንደምትፈልገኝ ንገረኝ የሆነ ነገር በል፣ በቃ የፈለከውን ጠንካራዋ ሔራን
ከተዋወቅን ጀምር ለመጀመሪያ ጊዜ እያለቀሰች ነበር፡፡
እንደዚያን ቀን ሁለታችንም በስሜት ጡዘን አናውቅም፡፡ ጨለማው ውስጥ በዚያ ሁሉ ላለመበለጥ በሚደረግ የሴትነት ትንቅንቅ ውስጥ፡በዘያ ሁሉ የአትርሳኝ ተማጽኖ መሃል፣
ጨለማው ላይ ገዝፎ የታየኝ የሐኑን መልክ ነበር። ልክፍት ነው! መብራቱን ድንገት ባበራው ከስሬ የምትንፋረቀው ሔራን፣ በሆነ ተአምር ሐኑን ሆና በቀይ ፊቷ ላይ እንባ ሲንኳለል የማገኛት እስኪመስለኝ፡፡ በሕይወት ውስጥ ግን፡ ማሸነፍ የሚባል ነገር የእውነት ይኖር ይሆን? ሔራን አሸንፋ እኔን ልታገባ ነው እኔ ተሸንፌ ሐኑንን ከነፍቅሯ ተነጥቂያለው ሐኑን በወንድሞቿ ተሸንፋ ሁሉንም ነገሯን ተነጥቃ እኔ እጅ ላይ ወድቃለች፡፡በኑሮ የተሸነፈችው ሐኑን ኑሮ እሹሩሩ የሚላትን ሙሽራ አሸንፍ እያስለቀሰች ነው፡፡እኔ ያቀፍኳት ሴት ጠይምነት በቀይ ቅዠት ተሸንፎ ያቀፍኩትና ያሰብኩት የሚምታታብኝ ደንጋራ ሁኛለሁ። ሁሉም አሸናፊ ከጭብጨባ ኋላ የሚያነሳው
የሽንፈት ዋንጫ አለ፡፡ ማሸነፍ የሚባል ነገር እዚያ መለኮታዊው ዓለም ላይ ካልሆነ በስተቀር ምድር የተሸናፊዎች ርስት ናት፡፡ ሁለታችንንም እንቅልፍ አሸንፎ ይዞን ጭልጥ አለ፡፡ ጧት ስንነሳ ሔራን ዓይኔን ማየት አፍራ ነበር፡፡
ቁርስ ልጋብዝሽ አልኳት ዝቅ ባለ ድምፅ፡፡
እሺ አለችኝ፡፡ ሰውን ሁሉ ምን ነካው? እሺ ብቻ! ቁርስ እየበላን ሰሃኗ ላይ አቀርቅራ
እንዲህ አለትኝ፣
ዓይኗ ከአንተ ላይ አይነቀልም፣እንስፍስፍ ብላ ነው የምታይህ፤ አውቃለሁ ሰው
ሲያፈቅር ምን እንደሚሆን፡፡በተለይ ሴት ስታፈቅር፣ ታፈቅርሃለች ማንም ሴት ብትሆን የእኔ ያለችው ወንድ በሌላ ሴት ተፈቅሮ ማየት፣ ግማሽ ስጋት ነው፡፡ ሳት ቢልህ ፣እምቢ የምትል ዓይነት አይደለችም” እናም የቀረበውን ቁርስ ንክች ሳታደርገው፣ ገፋ አደረገችው።
ሔራን የበላይነቷን ለማሳየት፣ በሐኑን ላይ የማታደርገው ነገር አልነበረም፡፡ የሚገባኝ እኔ ብቻ ነበርኩ፡፡ ሐኑን ራሷ “ይኼማ ወደር የሌለው በጎነት ነው” ልትለው የምትችለውን ድርጊት፣ ዓይኔን ጨፍኜ የሔራን ሰይጣናዊ ቅጣት እንደሆነ መናገር እችላለሁ፡፡እንደዓይኔ ብሌን ነበር ሐኑንን የምጠብቃት፡፡ አንድ ቀን ሰርጋችን ሲቃረብ፣ ሔራን ሐኑን ሥራ ታግዘን፣ ለዛውም ብቻዋን እንዳይደብራት እኛ ጋር ትሁን በሚል ሰበብ እቤታቸው ወሰደቻት የሔራን እህቶች፣ የእኔ ሁለት ጓደኞች (ለሚዜነት ሽር ጉድ የሚሉ) ቤቱን ሞልተን እናወራለን ሔራን ድንገት አንድ ጅንስ ሱሪ አንጠልጥላ ሐኑን ነይ ይሄን ለኪው እስኪ፣ ብዙም እለበስኩትም ጠቦኝ ነው፣ ልክሽ ከሆነ ትወስጅዋለሽ አለቻት። በሰው ፊት አሮጌ ሱሪዋን ለሐኑን በመመጽወት የበላይነቷን ለማሳየት
ያደረገችው መሆኑን በደንብ ነው የገባኝ። ምንም ነገር በፍቅር ቢያደርጉት ነውር
አይደለም፤ እንዲህ ዓይነት ጋጠወጥነት ግን ያቅለሸልሻል …ሐኑን ሻንጣ ተከፍቶ እጅ እንዳመጣ ቢላክ፣ሔራን እንደ ቅርስ የምትኮራበትን ዓይነት አስር ጅንስ ሱሪ የሚገዛ የቱርክ ቀሚስ ተመዞ ይወጣል፡፡ ነውረኛ!
እኔና ሔራን እንዲህ አይጥና ድመት ድብብቆሽ ላይ ሆነን ድል ባለ ሰርግ ተጋባን፡፡ እኔ ባልፈልግም፣ ሔራን ጠርታት ስለነበር ሐኑን ሰርጌ ላይ ተገኘት፡፡ ይኼም እንደ ቅስም መስበሪያ መሆኑ ነው፡፡ የሔራን አስቀያሚ ፖለቲካ፡፡ እንዲያውም እሁቶቿ ሆነ ብለው ሐኑንን ከሌሎች ወንዶች ጋር ለማቀራረብ ሲሞከሩ፣ ከሙሽራ ወንበሬ ላይ ሆኜ በጭፈራው መሃል እታዘብ ነበር፡፡ ከጎኔ በቬሎ ደምቃ ካሜራው ወደኛ በዞረ ቁጥር
ሠላሳ ሁለት ጥርሷን የምታሳየውን ሒራንን፣ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብዬ “ሐኑንን ወደ ቤት እንዲሸኞት ንገሪያቸው አልኳት፡፡ ፈገግ እንዳለች “ምንድን ነው በሰርግህ ቀን እንኳን የዚች ልጅ ስም ከአፍህ የማይጠፋው? ተዋት ትጨዋት፣ ከሰዎችም ጋር ትቀላቀል፣ ባዶ
ቤት አፍነህ ምን ልታደርጋት ነው? ሆሆአለችኝ፡፡ ቁጣዬን መደበቅ አልቻልኩም ኮስተር ብዬ
ሔራን እንዲሸኟት ንገሪያቸው" አልኳት፤ እያንዳንዱን ፊደል ርግጥ አድርጌ:: መኮሳተሪ አስፈርቷት ይሁን፤ ሰርጓ እንዳይበላሽ ፈርታ፣ ፈገግ እንዳለች ሚዜዋን ጠርታ፣ ጆሮዋ የሆነ ነገር ነገረቻት፡፡ ሐኑንን ወዲያው ወደ ቤቷ ወስዷት። ማታ እልል እየተባለልን
የገባንስት ጫጉላ ቤት ውስጥ የመጀመሪያ ንግግራችን ወደንዝንዝ ያደላ ነበር፡፡ “ቆይ የፈለገችው ጋር ብታወራ አንተ ምን አስጨነቀህ…? ሕፃን ልጅ አይደለችም! የቤት ኪራይ ስለከፈልክላት ብቻ፣ ከማን ጋር ማውራት፣ ማንን አለማውራት እንዳለባት መወሰን
ትችላለህ ማለት አይደለምኮ!…ተዋት በቃ! ልጅቱን….ነፃነቷን ስጣት! ሌላ ነገር ውስጥህ ከሌለ በስተቀር ይኼን ያህል
“በቃ! ሲጀመር የአንቺ እህቶችም ሆኑ የኔ ቤተሰቦች ስለ ሐኑን ምንም እንዲያውቁ
አልፈልግም ብዬ ነግሬሻለሁ፡፡ አንቺ ግን ለእህቶችሽ ነግረሻቸዋል፡፡ እናም ገፋፍተው አንዱ ወንድ ላይ ስላጣበቋት፣ በአንቺ ሴት ትዳርሽ ከስጋት ነፃ ይሆናል! ደግሜ እነግርሻለሁ…ከሐኑን ጋር ምንም ጐዳይ የለኝም! ምንም! የዚህ ዓይነቱን ተንኮላችሁን አቁሙ፤አንቺም እህቶችሽም ለአንዲት ሚስኪን ይኼን ያህል ርብርብ ምንድነው?እኔ የሚያስፈልጋትን ከመስጠት ያለፈ ምንም አላደረኩም፤ ከሰው ጋር አታውሪም አላልኩም፡፡
አንቺ ነሽ ዙሪያዋን እየዞርሽ የማይረባ ድብብቆሽ የምትጫዎችው…በቃ ተያት!»
እንደተኮራረፍን ወደ አልጋችን አመራን፡፡
ሌላ ዓለም ነበር ይኼንኛው በለስላሳ እጆቿ ሰውነቴን
❤1
#ሐኑን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እንደው ነገሩን አልኩ እንጂ፤ እኔማ ምናሻኝ! አንተም እሷም ድምፃችሁ የማይሰማ ጨዋ ናችሁ ውሃ አታፈሱ፣ሰው አታንጋትቱ! እኔ ውስጥ ለውስጥ ማማት ስለማልወድ ነው፣ፊት ለፊት ነው ነገሬ...
ሐኑን በጨንቃት ካፍቴሪያ ማስተናገድም ቢሆን እቀጠራለሁ አለች፡፡ ግራ ገባኝ::
ምን እንደማደርጋት ጨነቀኝ፡፡ ነገሮችን ትረዳለች የምላት እህቴ እንኳን፣ “ይኼኮ የአንተ ችግር አይደለም፣ በሕግም ይሁን በምን ወንድሞቿን ትጠይቅ የራሷ ወንድሞች። የጨከኑትን፣ እተ ምን ባይ ነህ ታዲያ? ለአንዲት ኖረችም አልኖረችም በሕይወትህ ውስጥ ምንም ለማታመጣ ሴት ብለህ፣ ትዳርህን ትበትናለህ? ምንድነው ዓላማህ በእውነት ደስ የማይል ነገር ነው፡፡ አፍ አለኝ ብለህ አታውራው፡፡ የአንተ ብር ማለት የሔራንም ነው፡፡ እያነሳህ ለአንዲት ሴት የቤት ኪራይና እስቤዛ ምን የሚሉት እብደት ነው...?!
በዙሪያዬ ያለው ቤተሰብ እና ጓደኛ፡ ልክ አንገት ላይ እንደገባ ሸምቀቆ አንቆ ትንፋሽ አሳጣኝ፡፡ የማውቃቸውን ጓደኞች ሁሉ የጽዳትም ሥራ ቢሆን ለሐኑን እንዳፈልጉላት ወጣሁ ወረድኩ፣ አልተገኘም፡፡ ቢጨንቀኝ ሔራንን እሺ እናስተምራት፣ የሆነ የአጭር ጊዜ ሥልጠና ነገርም ቢሆን ቢሆን ትማር የምግብ ዝግጅት ምናምን… ትንሽ ጊዜ ስጭኝ ብየ ተማጸንኳት፡፡ ይኼም ተአምር ሆኖ በመላ ቤተሰቡ ተወራ “እርፍ! ጭራሽ ላስተምር አለ? ያስነካችው ነገርማ አለ እየተባለ፡፡ በዚህ ጭንቀት ላይ እያለሁ ነበር የሔራን ወንድም ሐኑን ወደ ተከራየችበት ቤት ሄዶ ሐኑንንም አከራይዋንም ሴትዮ እንዳይሸጡ
እንዳይለወጡ አድርጎ ሰድቦና አስፈራርቶ መመለሱን የሰማሁት፡፡ አከራይዋን “ቤትሽ ውስጥ ባለትዳር የምታማግጥ ሴት አከራይተሽ ቆርቢያለሁ ትያለሽ! አንቺ ብሎ ቆራቢ አላቸው አሉ፡፡
ሐኑን፡ ደውላ፣ አከራይዋ ቤት ፈልጊ እንዷላት ነግራኝ፤ ለምን? ምን አደረገች? ብየ ስሄድ ነበር ይኼን ድንፋታውን የሰማሁት፡፡ እየተንቀጠቀጠች ነበር ሐኑን፡፡ “እንደገና ከመጣ ይገድለኛል የሚያስፈራራ ልጅ ነው አለችኝ፡፡ ለእኔ ግን እንደትቢያ እፍ ብለው የሚበትን ተራ ሰው ሁኖ ቀለለብኝ፡፡ እቤቱ ድረስ ሄጄ ኡኡ አልኩበት፡፡ ያ! የገደል ስባሪ የሚያክል
ሰው፣ ምንም ዱርየ ቢሆን ያደረኩለት ነገር ከብዶት ይሁን፡አልያም የእህቱ ባል መሆኔ ይሉኝታ አስይዞት ብቻ ጩኸቴንም ስድቤንም ጠጥቶ ዝም አለ፡፡ እኔ ግን እንደእብድ አድርጎኝ ነበር፡፡ ሔራንን ዓይኗን ማየት አስጠላኝ፡፡ እስስትነቷ አበሳጨኝ፡፡ ለሌሎች ያሳጣችብኝ መንገድ አንገበገበኝ፤ አዎ እውነት አላት፣ በአደባባይ ማንንም የሚያሳምን
እውነት አላት፡፡ ቀና ብዬ እንኳን ማስረዳት የማልችለው ውስብሰብ ታሪክ፣ ነገሬ
ለአደባባይ የሚሆን አይደለም.እንኳን የሰጡትን ሳያላምጥ የሚውጥ ማኅበረሰብ መሃል ለምን እና እንዴት የሚል ታዛቢም ቢመጣ፣ በእኔ ላይ መፍረዱ አይቀርም፡፡ ብቸኛ እውነቱን የምታውቀው ሔራን እወገር ዘንድ አሳልፋ በመስጠት ወገራውን ፈርቼ ከተራ
ስጋቷ ስሸሽ፣ በሽሽቴ ልትፈወስ አንድ አገር ወሬኛ አዝማች ሆና ከፊት ተሰለፈች።
በየሄድከብት ሽሙጥ፣ በየሄድኩበት አንገት ደፊ አገር አጥፊ” ተረት ከቦኝ የምኖር ሰው ሆንኩ፡፡ ባጠገባቸው ሳልፍ የሚሽቆጠቆጡ ባልደረቦቼ ሳይቀሩ፣ ከምር ሐሜትና ወሬ ላይ ቁመው ቁልቁል ሊመለከቱኝ ሲዳዳቸው እየተመለከትኩ እገረም ነበር፡፡ አንድ ሰው ከስንት ሺህ ሕዝብ ጋር ይከራከራል? ወይ ፊት ለፊት ደፍረው አያወሩ፣ አላስረዳቸው፡፡ በተለይ የወንዶቹ የሐሜተኝነት ሱስ ይሽከከኝ ነበር፡፡ ኮታቸውን እያርገበገቡ በየቡና
መጠጫው ስሜን ሲቦጭቁ፣ ይህው ሥልጣን ሆና ከእነሱ በአንድና በሁለት እርከን ከፍ ማለቱ፣ ህሊናቸው ላይ የለደፈባቸውን የበታችነት እድፍ፣ በጎደፈ የስም ውሃ የሚለቃለቁት ይመስላቸዋል፡፡ ደግሞም ሌላ የሚያማቸው ቁስልም ነበር፡፡ ለእነሱ በቁንጅናዋ እንደህልም የራቀች፣ በሙያዋ እንደተራራ የገዘፈች ሔራን፣ ለዓመታት ሲመኟት የኖሯት ሔራን፣ የእኔ ሚስት መሆኗ ሳያንስ እሷን ንቄ ሌላ ሴት ጋር መሄዴ በተወሳሰበ ሒሳብ “እሱ የናቃት እንኳን ማግኘት የማንችል ተራዎች ነን ወደሚል
አዘቅት ወርውሯቸው ነበር፡፡ እሱ ምን ስለሆነ ነው በሚል ማስታገሻ ራሳቸውን
እያስታመው ነበር፡፡ ፊት ለፊት እኔን መጋፈጥ ስለማይሆንላቸው ሔራንን በማጀገን በእሷ ግዳይ ላይ እንደጅብ ተረባርበው የድርሻቸውን ክብር ሊወሰዱ!
ሔራን በዘመድ አዝማድ ፊት ይቅርታ ተጠይቃ፣ ትንሽ እውነት ላይ የካበችውን የውሸት የበደል ታሪክ ተቀብየው እንድኖር ማድረግ ትፈልጋለች፡፡ ማንም የማይገባው ነገር፣ ከአንሶላችን ሥር የተናዘዘችው የዚህ ሁሉ ነገር መነሻ፣ የእኔ አለመታመን ሳይሆን የሐኑን ውበት ያንኮታኮተው የበታችነቷ ነበር፡፡ አሰብኩ፣ ብዙ አሰብኩ ሕዝብ በወሬ ተዛዝሎ የሚወድቅ ናዳ ነው፡፡ ከዚህ ናዳ የሚያድነው መሮጥ አይደለም፣ከዚህ ናዳ የሚያድነው
አብሮ መናድ አይደለም፣ ከዚህ ናዳ የሚያድነው ወገብ ይዞ መከራከር አይደለም፣ ይኼ ናዳ ሕዝብ ራሱን ብልህ ሲያደርግ፤ ለአንድ ሞኝ ገጸ ባህሪ ከተረተው ተረት፣ ከራሱ ከናዳው መሃል ነበር መፍትሔውን ያገኘሁት …
.
እንዱ ሞኝ ናዳ መጣብህ ሲሉ ተከናንቢያለሁ አለ አሉ ካሉት ተረት! ለእኔ
እንደዚህ “ሞኝ” እንደተባለ ሰው ብልህ ሆኖ ያገኘሁት ፍጥረት የለም፡፡ የሕይወት
ግብግብ ዓላማው፣ ከሞት መዳን አይደለም። ሰው ፈጠነም ዘገየም እንድ ቀን የሞት ዕጣ የሚወድቅበት ፍጡር ነው፡፡ በዚህ የማይቀር ዕጣ ከናዳ ያድነኛል ብለን የምንለብሰው ከንብንብ፣ ማኅበረሰቡ የብረት መዝጊያ፣ ቅብርጥስ የሚለው ትዳር አይደለም፣ ትምህርት
እይደለም፣ ሥልጣን ቤተሰብ አይደለም፤ ሳያድንም ያድነኛል የሚል እምነት ተከናንቦ ሞትን እንደመጠበቅ ውብ ነገር የለም ፡፡ ያ እምነት ፍቅር ይባላል … ! ሐኑንን ሃብታም ቤተሰብ ከሕይወት ናዳ አልታደጋትም፡፡ እኔን ድል ባለ ሰርግ የተመሠረተው ትዳር ከሐሜት ናዳ አልታደገኝም ያንን ኢዮብ የሚባል ቦዘኔ፡ የዓመታት የድብድብ ታሪኩና ጡንቻው ከእኔ የቁጣ ናጻ አላዳነውም፡፡ ብቸኛው ታዳጊ፣ እንደክንብንብ ስስ የሆነው
በልባችን ያለው ፍቅር ብቻ ነው፡፡ እናም ወሰንኩ፡፡ ለየትኛውም የማኅበረሰብ እንቶፈንቶ የይሉኝታ ሕግ አልኖርም፤ማን ለኔ ኖረ? ቀሪ ዘመኔን ከናዳው ባያተርፈኝም እንኳን፣ የፍቅር ከንብንቤ ውስጥ ብቻ አሳልፋለሁ! ያ ክንብንብ ደግሞ የት እንዳለ ጠንቅቄ አውቃለሁ እንዴት እንደምለብሰውም ጭምር !!
ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ሄድኩና አለቃዬን እንዲህ አልኩት ቅያሬ እፈልጋለሁ፤ወደ ክፍለ ሐገር ወደ ባህር ዳር ፣ እባክህ ተባበረኝ..."
“ከአዲስ አበባ ወደባህር ዳር!"
“ማንም እንዲህ ዓይነት ዝውውር ጠይቆ አያውቅም፡፡ እዚያ ያሉት ይኼን ቢሰሙ እልል በቅምጤ ነው የሚሉት። በማንኛውም ሰዓት ይቀይሩሃል፡፡ ጠረጴዛዬን ያጣበበው ማመልከቻ ከከፍለ ሐገር ወደ አዲስ አበባ ቀይሩን የሚል ጥያቄ ነው፡፡ ከፈለግህ ብዙም ከባድ እይደለም ልንልክህ እንችላለን
ቀጥሎ አብሮኝ ወደ ተማረና የግል ቢሮ ወደከፈተ ጠበቃ ጓደኛዬ ጋ ሄድኩ፡፡ እናም
ፍቺ እፈልጋለሁ” አልኩት፡፡ …ሰርጌ ላይ ልቡ እስኪፈርስ የጨፈረ ነውና፣ ይሉኝታ
ይዞት የወጉን ምክር አደረሰ፡፡ ትንሽ ብትታገስ፣ ብትነጋገሩ፣ እንኳን ባልና ሚስት ምንትስ ይጋጫል …' እንደ ጠጠር የሚፈናጠሩ የምከር ናዳዎቹን እንደዝንብ ከፊቴ እሽ ብዬ የፍቺ ወረቀት አስጻፍኩ፡፡ ገና በቅጡ ሁለት ዓመት ያልሞላው በሽተኛ ትዳሬን፣
ሙሉ ዘመኔን እንደ ጋንግሪን ከመበከሉ በፊት፣ ቆርጨ ለመጣል ወሰንኩ፡፡ የፍቺ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እንደው ነገሩን አልኩ እንጂ፤ እኔማ ምናሻኝ! አንተም እሷም ድምፃችሁ የማይሰማ ጨዋ ናችሁ ውሃ አታፈሱ፣ሰው አታንጋትቱ! እኔ ውስጥ ለውስጥ ማማት ስለማልወድ ነው፣ፊት ለፊት ነው ነገሬ...
ሐኑን በጨንቃት ካፍቴሪያ ማስተናገድም ቢሆን እቀጠራለሁ አለች፡፡ ግራ ገባኝ::
ምን እንደማደርጋት ጨነቀኝ፡፡ ነገሮችን ትረዳለች የምላት እህቴ እንኳን፣ “ይኼኮ የአንተ ችግር አይደለም፣ በሕግም ይሁን በምን ወንድሞቿን ትጠይቅ የራሷ ወንድሞች። የጨከኑትን፣ እተ ምን ባይ ነህ ታዲያ? ለአንዲት ኖረችም አልኖረችም በሕይወትህ ውስጥ ምንም ለማታመጣ ሴት ብለህ፣ ትዳርህን ትበትናለህ? ምንድነው ዓላማህ በእውነት ደስ የማይል ነገር ነው፡፡ አፍ አለኝ ብለህ አታውራው፡፡ የአንተ ብር ማለት የሔራንም ነው፡፡ እያነሳህ ለአንዲት ሴት የቤት ኪራይና እስቤዛ ምን የሚሉት እብደት ነው...?!
በዙሪያዬ ያለው ቤተሰብ እና ጓደኛ፡ ልክ አንገት ላይ እንደገባ ሸምቀቆ አንቆ ትንፋሽ አሳጣኝ፡፡ የማውቃቸውን ጓደኞች ሁሉ የጽዳትም ሥራ ቢሆን ለሐኑን እንዳፈልጉላት ወጣሁ ወረድኩ፣ አልተገኘም፡፡ ቢጨንቀኝ ሔራንን እሺ እናስተምራት፣ የሆነ የአጭር ጊዜ ሥልጠና ነገርም ቢሆን ቢሆን ትማር የምግብ ዝግጅት ምናምን… ትንሽ ጊዜ ስጭኝ ብየ ተማጸንኳት፡፡ ይኼም ተአምር ሆኖ በመላ ቤተሰቡ ተወራ “እርፍ! ጭራሽ ላስተምር አለ? ያስነካችው ነገርማ አለ እየተባለ፡፡ በዚህ ጭንቀት ላይ እያለሁ ነበር የሔራን ወንድም ሐኑን ወደ ተከራየችበት ቤት ሄዶ ሐኑንንም አከራይዋንም ሴትዮ እንዳይሸጡ
እንዳይለወጡ አድርጎ ሰድቦና አስፈራርቶ መመለሱን የሰማሁት፡፡ አከራይዋን “ቤትሽ ውስጥ ባለትዳር የምታማግጥ ሴት አከራይተሽ ቆርቢያለሁ ትያለሽ! አንቺ ብሎ ቆራቢ አላቸው አሉ፡፡
ሐኑን፡ ደውላ፣ አከራይዋ ቤት ፈልጊ እንዷላት ነግራኝ፤ ለምን? ምን አደረገች? ብየ ስሄድ ነበር ይኼን ድንፋታውን የሰማሁት፡፡ እየተንቀጠቀጠች ነበር ሐኑን፡፡ “እንደገና ከመጣ ይገድለኛል የሚያስፈራራ ልጅ ነው አለችኝ፡፡ ለእኔ ግን እንደትቢያ እፍ ብለው የሚበትን ተራ ሰው ሁኖ ቀለለብኝ፡፡ እቤቱ ድረስ ሄጄ ኡኡ አልኩበት፡፡ ያ! የገደል ስባሪ የሚያክል
ሰው፣ ምንም ዱርየ ቢሆን ያደረኩለት ነገር ከብዶት ይሁን፡አልያም የእህቱ ባል መሆኔ ይሉኝታ አስይዞት ብቻ ጩኸቴንም ስድቤንም ጠጥቶ ዝም አለ፡፡ እኔ ግን እንደእብድ አድርጎኝ ነበር፡፡ ሔራንን ዓይኗን ማየት አስጠላኝ፡፡ እስስትነቷ አበሳጨኝ፡፡ ለሌሎች ያሳጣችብኝ መንገድ አንገበገበኝ፤ አዎ እውነት አላት፣ በአደባባይ ማንንም የሚያሳምን
እውነት አላት፡፡ ቀና ብዬ እንኳን ማስረዳት የማልችለው ውስብሰብ ታሪክ፣ ነገሬ
ለአደባባይ የሚሆን አይደለም.እንኳን የሰጡትን ሳያላምጥ የሚውጥ ማኅበረሰብ መሃል ለምን እና እንዴት የሚል ታዛቢም ቢመጣ፣ በእኔ ላይ መፍረዱ አይቀርም፡፡ ብቸኛ እውነቱን የምታውቀው ሔራን እወገር ዘንድ አሳልፋ በመስጠት ወገራውን ፈርቼ ከተራ
ስጋቷ ስሸሽ፣ በሽሽቴ ልትፈወስ አንድ አገር ወሬኛ አዝማች ሆና ከፊት ተሰለፈች።
በየሄድከብት ሽሙጥ፣ በየሄድኩበት አንገት ደፊ አገር አጥፊ” ተረት ከቦኝ የምኖር ሰው ሆንኩ፡፡ ባጠገባቸው ሳልፍ የሚሽቆጠቆጡ ባልደረቦቼ ሳይቀሩ፣ ከምር ሐሜትና ወሬ ላይ ቁመው ቁልቁል ሊመለከቱኝ ሲዳዳቸው እየተመለከትኩ እገረም ነበር፡፡ አንድ ሰው ከስንት ሺህ ሕዝብ ጋር ይከራከራል? ወይ ፊት ለፊት ደፍረው አያወሩ፣ አላስረዳቸው፡፡ በተለይ የወንዶቹ የሐሜተኝነት ሱስ ይሽከከኝ ነበር፡፡ ኮታቸውን እያርገበገቡ በየቡና
መጠጫው ስሜን ሲቦጭቁ፣ ይህው ሥልጣን ሆና ከእነሱ በአንድና በሁለት እርከን ከፍ ማለቱ፣ ህሊናቸው ላይ የለደፈባቸውን የበታችነት እድፍ፣ በጎደፈ የስም ውሃ የሚለቃለቁት ይመስላቸዋል፡፡ ደግሞም ሌላ የሚያማቸው ቁስልም ነበር፡፡ ለእነሱ በቁንጅናዋ እንደህልም የራቀች፣ በሙያዋ እንደተራራ የገዘፈች ሔራን፣ ለዓመታት ሲመኟት የኖሯት ሔራን፣ የእኔ ሚስት መሆኗ ሳያንስ እሷን ንቄ ሌላ ሴት ጋር መሄዴ በተወሳሰበ ሒሳብ “እሱ የናቃት እንኳን ማግኘት የማንችል ተራዎች ነን ወደሚል
አዘቅት ወርውሯቸው ነበር፡፡ እሱ ምን ስለሆነ ነው በሚል ማስታገሻ ራሳቸውን
እያስታመው ነበር፡፡ ፊት ለፊት እኔን መጋፈጥ ስለማይሆንላቸው ሔራንን በማጀገን በእሷ ግዳይ ላይ እንደጅብ ተረባርበው የድርሻቸውን ክብር ሊወሰዱ!
ሔራን በዘመድ አዝማድ ፊት ይቅርታ ተጠይቃ፣ ትንሽ እውነት ላይ የካበችውን የውሸት የበደል ታሪክ ተቀብየው እንድኖር ማድረግ ትፈልጋለች፡፡ ማንም የማይገባው ነገር፣ ከአንሶላችን ሥር የተናዘዘችው የዚህ ሁሉ ነገር መነሻ፣ የእኔ አለመታመን ሳይሆን የሐኑን ውበት ያንኮታኮተው የበታችነቷ ነበር፡፡ አሰብኩ፣ ብዙ አሰብኩ ሕዝብ በወሬ ተዛዝሎ የሚወድቅ ናዳ ነው፡፡ ከዚህ ናዳ የሚያድነው መሮጥ አይደለም፣ከዚህ ናዳ የሚያድነው
አብሮ መናድ አይደለም፣ ከዚህ ናዳ የሚያድነው ወገብ ይዞ መከራከር አይደለም፣ ይኼ ናዳ ሕዝብ ራሱን ብልህ ሲያደርግ፤ ለአንድ ሞኝ ገጸ ባህሪ ከተረተው ተረት፣ ከራሱ ከናዳው መሃል ነበር መፍትሔውን ያገኘሁት …
.
እንዱ ሞኝ ናዳ መጣብህ ሲሉ ተከናንቢያለሁ አለ አሉ ካሉት ተረት! ለእኔ
እንደዚህ “ሞኝ” እንደተባለ ሰው ብልህ ሆኖ ያገኘሁት ፍጥረት የለም፡፡ የሕይወት
ግብግብ ዓላማው፣ ከሞት መዳን አይደለም። ሰው ፈጠነም ዘገየም እንድ ቀን የሞት ዕጣ የሚወድቅበት ፍጡር ነው፡፡ በዚህ የማይቀር ዕጣ ከናዳ ያድነኛል ብለን የምንለብሰው ከንብንብ፣ ማኅበረሰቡ የብረት መዝጊያ፣ ቅብርጥስ የሚለው ትዳር አይደለም፣ ትምህርት
እይደለም፣ ሥልጣን ቤተሰብ አይደለም፤ ሳያድንም ያድነኛል የሚል እምነት ተከናንቦ ሞትን እንደመጠበቅ ውብ ነገር የለም ፡፡ ያ እምነት ፍቅር ይባላል … ! ሐኑንን ሃብታም ቤተሰብ ከሕይወት ናዳ አልታደጋትም፡፡ እኔን ድል ባለ ሰርግ የተመሠረተው ትዳር ከሐሜት ናዳ አልታደገኝም ያንን ኢዮብ የሚባል ቦዘኔ፡ የዓመታት የድብድብ ታሪኩና ጡንቻው ከእኔ የቁጣ ናጻ አላዳነውም፡፡ ብቸኛው ታዳጊ፣ እንደክንብንብ ስስ የሆነው
በልባችን ያለው ፍቅር ብቻ ነው፡፡ እናም ወሰንኩ፡፡ ለየትኛውም የማኅበረሰብ እንቶፈንቶ የይሉኝታ ሕግ አልኖርም፤ማን ለኔ ኖረ? ቀሪ ዘመኔን ከናዳው ባያተርፈኝም እንኳን፣ የፍቅር ከንብንቤ ውስጥ ብቻ አሳልፋለሁ! ያ ክንብንብ ደግሞ የት እንዳለ ጠንቅቄ አውቃለሁ እንዴት እንደምለብሰውም ጭምር !!
ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ሄድኩና አለቃዬን እንዲህ አልኩት ቅያሬ እፈልጋለሁ፤ወደ ክፍለ ሐገር ወደ ባህር ዳር ፣ እባክህ ተባበረኝ..."
“ከአዲስ አበባ ወደባህር ዳር!"
“ማንም እንዲህ ዓይነት ዝውውር ጠይቆ አያውቅም፡፡ እዚያ ያሉት ይኼን ቢሰሙ እልል በቅምጤ ነው የሚሉት። በማንኛውም ሰዓት ይቀይሩሃል፡፡ ጠረጴዛዬን ያጣበበው ማመልከቻ ከከፍለ ሐገር ወደ አዲስ አበባ ቀይሩን የሚል ጥያቄ ነው፡፡ ከፈለግህ ብዙም ከባድ እይደለም ልንልክህ እንችላለን
ቀጥሎ አብሮኝ ወደ ተማረና የግል ቢሮ ወደከፈተ ጠበቃ ጓደኛዬ ጋ ሄድኩ፡፡ እናም
ፍቺ እፈልጋለሁ” አልኩት፡፡ …ሰርጌ ላይ ልቡ እስኪፈርስ የጨፈረ ነውና፣ ይሉኝታ
ይዞት የወጉን ምክር አደረሰ፡፡ ትንሽ ብትታገስ፣ ብትነጋገሩ፣ እንኳን ባልና ሚስት ምንትስ ይጋጫል …' እንደ ጠጠር የሚፈናጠሩ የምከር ናዳዎቹን እንደዝንብ ከፊቴ እሽ ብዬ የፍቺ ወረቀት አስጻፍኩ፡፡ ገና በቅጡ ሁለት ዓመት ያልሞላው በሽተኛ ትዳሬን፣
ሙሉ ዘመኔን እንደ ጋንግሪን ከመበከሉ በፊት፣ ቆርጨ ለመጣል ወሰንኩ፡፡ የፍቺ
👍1