አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሁቱትሲ


#በኢማኪዩሌ_ኢሊባጊዛ_እና_ስቲቭ #ኤርዊን

#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ

#ቀዳሜ_ቃል

ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ከስቲቭ ኤርዊን ጋር በመተባበር የጻፈችው #ሁቱትሲ የተሰኘው መጽሐፍ ምናልባት ስለ ሩዋንዳ ከተጻፉት መጻሕፍትም ሆነ ከታዩት ፊልሞች በላይ የፍጅቱን አሰቃቂነትና ዘግናኝነት ገላጭ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፉ ከሰሚ ሰሚ የወረደ ታሪክ ሳይሆን እጅግ ከሚዋደዱ ከስድስት ቤተሰብ አባላት ከግድያው የተረፈችው አንዲት ቱትሲ ወጣት ከአንድ ቁምሣጥን በማይበልጥ መጸዳጃ ቤት ከሰባት ቱትሲ ጓደኞቿ ጋር ከአሁን አሁን ተገደልኩ እያለች እየተጨነቀች የሃይማኖት ጽናቷ እንዴት ለሦስት ወር በሕያውነት እንዳኖራትና በኋላም እንዴት ነጻ ወጥታ ወልዳ ለመሳም የበቃች መሆኗን የሚተርክ ታሪክ ነው፡፡ የሩዋንዳ የዘር ፍጅት ተዋንያንን ፍርድ ቤት እንዳቀርብ በተባበሩት መንግስታት በከፍተኛ የሕግ አማካሪነት ተቀጥሬ በሠራሁበት ጊዜ ከሰማኋቸው በላይ ልብን ሰቅዞ የሚይዝና አእምሮን የሚያናውጥ ታሪክ ይኖራል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ መጽሐፍ አጋጥሞኛል፡፡
ስሜታዊነት አይነካኝም፣ መንፈሴ በሚያየውና በሚሰማው የማይረበሽ ጠንካራ ሰው ነኝ ባይ ይህንን መጽሐፍ በሚያነብበት ጊዜ ከአንዴም ሁለቴ ዓይኖቹ በእንባ ችፍ ችፍ ማለታቸው አይቀርም፡፡
የኢማኪዩሌ ታሪክ ምንጩ ወይንም የስቃይዋ ምክንያት የተወሳሰበ አይደለም፡፡ መንስኤው ርህራሄ የሚወልደውን የሰብአዊ ስሜትን ደምስሶ ከጥላቻ በላይ ጥላቻ ወልዶ ሰውን ከአውሬነት በታች የሚያውለው የዘር ጥላቻ ነው፡፡
የዘር ጠላቻ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር ለሌላው ሰብዓዊ ፍጡር ሊኖረው የሚገባውን ሐዘኔታና ርህራሄ ከሰው ልብ ፈልቅቆ አውጥቶ ከአውሬ በባሰ ጭካኔ ይተካዋል፡፡ በሩዋንዳው የዘር ፍጅት የተፈጸመውን አራዊት ከሚያደርጉት ጋር ማወዳደር የአራዊትን ስም ማጥፋት ይሆናል፡፡ የትኛው አውሬ ነው ሕጻናትን ከታትፎ እንደ ጌሾ በሙቀጫ የሚወቅጠው? የትኛው አውሬ ነው በኢማኪዩሌ ወንድም ላይ እንደተፈጸመው የሰውን አካላት ቆራርጦ ክምር ላይ የሚጥል? የትኛው አውሬ ነው የሰውን ጭንቅላት በገጀራ ለሁለት ሰንጥቆ ሰውዬውን በዝግታ እንዲሞት የሚያደርገው? የትኛው አውሬ ነው የአምስት ልጆችን እናት በልጆቿና በባሏ ፊት ደፍሮ ፊቷ አምስቱንም ልጆቿንና ባሏን አንድ በአንድ የሚከትፈው? ከአክራሪ ሁቱዎች በስተቀር የትኛውም አውሬ አያደርገውም፡፡
የሩዋንዳ የዘር ፍጅት የሰው ልጅ ጭካኔ ልክ የታየበት ነው፡፡ ተመሳሳይ ፍጅትና ጭካኔ የተፈጸመባቸው የናዚዎችና የአርመኖች እልቂቶች እንደሩዋንዳው መንስኤአቸው የዘር ጥላቻ ነበር፡፡
ኢማኪዩሌ በመጽሐፏ የጠቀሰችው የዘር ፍጅቱ ቀስቃሽና ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ቲዩኔስት ባጎስራ ፍርድ ቤት አቅርቤው ዳኞቹ ክሱን አንብበውለት ጥፋተኛ ነህ
አይደለህም ብለው ሲጠይቁት ፈገግ እያለ ‹‹ጥፋተኛ አይደለሁም›› ሲል ፈገግታው እንደ ጦር ይዋጋ ነበር፡፡
መጽሐፉ ከእንግሊዝኛ የተተረጎመ ሲሆን፤ ምናልባትም የአማርኛው ትርጉም ድርጊቶቹን ከእንግሊዝኛው በተሻለ ይገልጻቸዋል ማለት ይቻላል፡፡ ተርጓሚው የሥነጽሑፍ ምሁር እንደመሆናቸው መጠን አገላለጹ ከኢማኪዩሌ በልጦ ቢገኝ አይገርምም፡፡ የቃላቱ ገላጭነት፣ የአረፍተ ነገሮቹ አሰካክ፣ የቋንቋው አወራረድና በጠቅላላው የአማርኛው ውበት ከታሪኩ መሳጭነት ጋር ሆኖ መጽሐፉን ማንበብ ከተጀመረ መልሶ ማስቀመጥ አስቸጋሪ ነው፡፡
ይህ መጽሐፍ የብሔር ጥላቻ የሚፈጥሩ ፖሊሲዎችን ለሚቀርጹና በብሔረሰብ ስም ህዝብን ከፋፍለው ጥላቻ ለሚያስፋፉ ሰዎችም ሆኑ መዋቅርት የማስጠንቀቂያ ደወል ነው፡፡ መጽሐፉ ጥላቻ የሚያስከትለውን ሰቆቃ በግልጽ ስለሚያሳይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲያነበው በአጽንኦት ስማጠን በዓይኔ በብረቱ ካየሁት ተነሥቼ ነው፡፡

ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለ ማርያም
በተባበሩት መንግስታት የቀድሞ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት ከፍተኛ የሕግ አማካሪ

#መግቢያ

ኢማኪዩሌ እባላለሁ
ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰማኋቸው፡፡
እኔ በግንቡ በአንደኛው በኩል ስሆን እነሱ ደግሞ በሌላኛው አቅጣጫ ናቸው፤ አንድ ጋት የማይሞላ ውፍረት ያለው ጭቃና ዕንጨት ብቻ ይለያየናል፡፡ ንግግራቸው ጭካኔ የሚንጸባረቅበትና ቆርጠው መነሳታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
‹‹እዚህ ነች… እዚህ የሆነ ስፍራ እንዳለች እናውቃለን፡፡ …. ፈልጓት-ፈልጓት ኢማኪዩሌን፡፡››
አካባቢው በሁካታ ተሞላ፡፡ ብዙ ገዳዮች መጥተዋል፡፡ በአእምሮዬ ይታዩኛል - ሁልጊዜ በፍቅርና በደግነት ሰላምታ ይሰጡኝ የነበሩ የቀድሞ ወዳጆቼና ጎረቤቶቼ በቤቱ ውስጥ ጦርና ገጀራ ይዘው ስሜን እየጠሩ ይዘዋወራሉ፡፡
‹‹399 በረሮዎችን ገድያለሁ›› ይላል አንደኛው ገዳይ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ 400 ታደርግልኛለች፡፡ ይህን ያህል ከገደልኩ ምን እፈልጋለሁ!››
በትንሿ ምስጢራዊ መታጠቢያ ቤታችን ጥጋት አንድስ እንኳን የሰውነቴን ክፍል ሳላላውስ ተሸሽጌያለሁ፡፡ እንደኔው ሕይወታቸውን ለማትረፍ እንደተደበቁት ሌሎች ሰባት ሴቶች ሁሉ ገዳዮቹ ስተነፍስ እንዳይሰሙኝ ትንፋሼን ውጫለሁ፡፡ ድምጻቸው የሠራ አከላቴን ገማመሰው፡፡ በከሰል ፍም ላይ እንደተኛሁ፣ እሳትም ላይ እንደተጣልኩ ተሰማኝ፡፡ መላ ሰውነቴ የሕመም ውርጅብኝ ወረደበት፡፡ ሺህ የማይታዩ መርፌዎች ተቸከቸኩብኝ፡፡ ፍርሃት እንደዚህ የሚያርበደብድ ስጋዊ ሥቃይ ያስከትላል ብዬ አስቤ አላውቅም፡፡
ለመዋጥ ሞከርኩ፤ ጉሮሮዬ ግን ተዘግቷል፡፡ ምራቅ አልነበረኝም፤ አፌም እንደ ኩበት ደርቋል፡፡ ዓይኖቼን ጨፈንኳቸው፤ ራሴንም ለመደበቅ ሞከርኩ፤ ንግግራቸው ግን እየጎላ መጣ፡፡ ምንም ዓይነት ምኅረት እንደማያደርጉልኝ አውቃለሁ፤ በአእምሮዬም አንድ ሐሳብ ያስተጋባ ጀመር - ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ
ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል…
ገዳዮቹ በራፉ ላይ አሉ፤ በማንኛዋም አፍታ እንደሚያገኙኝ አውቃለሁ፡፡ ገጀራው ቆዳዬን አልፎ ሲገባና አጥንቴ ድረስ ሲቆራርጠኝ የሚሰማኝ ስሜት ምን እንደሚመስል አሰብኩት፡፡ ወንድሞቼና ወላጆቼም ትዝ አሉኝ፤ ሞተው ወይንም በሕይወት እየኖሩ እንደሆነ፣ በገነት ከአፍታ በኋላ እንገናኝም እንደሆነ አለምኩ፡፡

እጆቼን እርስ በርሳቸው አጣመርኳቸው፤ የአባቴን መቁጠሪያም ጥብቅ አድርጌ ያዝኩ፤ በለሆሳስም መጸለይ ጀመርኩ - እባክህ እግዚአብሔር ሆይ፣ እባክህ እርዳኝ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ እንድሞት አታድርገኝ፣ እንደዚህ አይሁን፡፡ እነዚህ ገዳዮች እንዲያገኙኝ አታድርግ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስህ ከጠየቅን እንደሚሰጠን ትነግረናለህ… እንግዲህ ጌታዬ እየጠየኩህ ነው፡፡ ወይ በለኝ፡፡ እባክህን እነዚህን ገዳዮች ወዲያ እንዲሄዱ አድርጋቸው፡፡ ኧረ በዚህ መታጠቢያ ቤት እንድሞት አታድርገኝ፡፡ እባክህ፣ እግዚአብሔር፣ እባክህ፣ እባክህ፣ እባክህ አድነኝ፡፡
ገዳዮቹ ከቤቱ ወጥተው ሄዱ፡፡ እኛም እንደገና መተንፈስ ጀመርን፡፡ ሄደዋል፤ ሆኖም ግን በቀጣዮቹ ሦስት ወራት ውስጥ ብዙ ጊዜ ይመላለሳሉ፡፡ ሕይወቴን እግዚአብሔር እንዳተረፋት አምናለሁ፤ ሆኖም ቁምሣጥን በምታክል መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ከሰባት ሌሎች ሰዎች ጋር በፍርሃት እየተርበደበድኩ ባሳለፍኳቸው 91 ቀናት መትረፍ ከመዳን በጣም የተለየ አንደሆነ እማራለሁ… ይህ ትምህርትም ለዘለቄታው ለውጦኛል፡፡ ይህ ትምህርት በጅምላ ጭፍጨፋ ውስጥ የሚጠሉና
👍32
#ሁቱትሲ


#በኢማኪዩሌ_ኢሊባጊዛ_እና_ስቲቭ_ኤርዊን


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ

#ክፍል_አንድ


#ክፉ_ቀን_ዳር_ዳር_ሲል

#ምዕራፍ_አንድ

የዘላለማዊ ፀደይ ምድር
የተወለድኩት በገነት ነው፡፡ስለ ትውልድ ሀገሬ በልጅነት ዘመኔ የሚሰማኝ ይህ ነበር፡፡ሩዋንዳ በመካከለኛው አፍሪካ እንደጌጥ ጣል የተደረገች ትንሽ ሀገር ነች፡፡ በጣም ማራኪ ውበት ስላላት፣ በለምለም ሸንተረሮቿ፣ ጭጋግ በሸፈናቸው ተራሮቿ፣ በአረንጓዴ ሸለቆዎቿና በአንጸባራቂ ሐይቆቿ ተማርኮ ለምስጋና ወደ አምላክ አለማንጋጠጥ የማይታሰብ ነው፡፡ ከተራሮቿ ቁልቁል የተለያየ ዝርያ ወዳላቸው የጽድ ጫካዎቿ የሚወርደው ነፋሻ አየር በልዩ ልዩ አበቦች መዐዛ የተሞላ ነው፡፡ የአየሩም ሁኔታ ዓመቱን ሙሉ በጣም ተስማሚ በመሆኑ በ19ኛው ክፍለዘመን መጨረሻ አካባቢ ወደ ስፍራው የመጡት የጀርመን ሰፋሪዎች ሀገሪቱን ‹‹የዘላለማዊ ፀደይ ምድር›› ብለው ሰየሟት፡፡
ውድ ሀገሬን በደም ጎርፍ እንድትታጠብ ያደረጓት ለጅምላ ጭፍጨፋ መነሻ የሆኑት ርኩሳን ሃይሎች በልጅነቴ ተሰውረውብኝ ነበር፡፡ በልጅነቴ የማውቀው ነገር የከበበኝን አማላይ መልከዓምድር፣ የጎረቤቶቼን ደግነት፣ የወላጆቼንና የወንድሞቼን ጥልቅ ፍቅር ነበር፡፡ በቤታችን ዘረኝነትና ምክንያት የለሽ ጥላቻ በፍጹም አይታወቁም፡፡ ሰዎች የተለያየ ጎሳና ዘር እንዳላቸው እንኳ ግንዛቤው አልነበረኝም፤ ቱትሲና ሁቱ የሚሉትን ቃላትም ቢሆን ትምህርት ቤት እስከገባሁበት ጊዜ ድረስ አልሰማኋቸውም፡፡
በሰፈሬ ትንንሽ ልጆች ከቤት ወደ ትምህርት ቤት ብቻቸውን ጭር ባለው አሥራ ሦስት ኪሎሜትር መንገድ ሲመላለሱ ወላጆቻቸው ልጄ ይጠለፍብኛል ወይንም በማናቸውም መንገድ ይጎዳብኛል ብለው አይጨነቁም፡፡ ልጅ ሆኜ በጣም የምፈራው ነገር በጨለማ ብቻዬን መሆንን ሲሆን፤ ከዚያ በስተቀር ግን ሰዎች የሚከባበሩበት፣ የሚተሳሰቡበትና ደስተኛ ይመስለኝ በነበረ መንደር ውስጥ ከደስተኛ ቤተሰብ ጋር የምኖር በጣም ፍልቅልቅ ልጅ ነበርኩ፡፡
የተወለድኩት በምዕራብ ሩዋንዳዋ የኪቡዬ ክፍለ-ሀገር፣ በማታባ መንደር ነው፡፡ ቤታችን ከኪቩ ሐይቅ ትይዩ በሚገኝ ኮረብታ ላይ ያለ ሲሆን፤ ሐይቁም ከፊታችን እስከ ዓለም ጠርዝ የተዘረጋ ይመስላል፡፡ ጠዋት ሰማዩ ከጠራ በሐይቁ በሌላኛው ጠርዝ በጎረቤት ሀገር ዛየር፣ በአሁኑ አጠራሩ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ያሉትን ተራሮች አያለሁ፡፡ ከቤታችን ወደ ሐይቁ የሚወስደውን አስቸጋሪ ቁልቁለት መውረድ ከአስደሳች የልጅነት ትዝታዎቼ አንዱ ነው፡፡ የማለዳው ጤዛ በንጋቷ ጸሐይ ተኖ የሚያልቅበት ጊዜ ሲቃረብ ከአባቴና ከወንድሞቼ ጋር ወደ ዋና እወርዳለሁ፡፡ ውሃው ሞቃት፣ የአየሩ ቅዝቃዜ ውርር የሚያደርግና ከሐይቁ ዳርቻ ያለው የቤታችን እይታ ዘወትር አማላይ ነበር፡፡
አቀበቱና በእግራችን የምንረግጠው አሳሳች ልል አፈር ወደ ቤት የምናደርገውን የመልስ ጉዞ አስፈሪም አስደሳችም ያደርጉታል፡፡ ብዙውን ጊዜ ስለሚያንሸራትተኝ ገደል ገብቼ ሐይቁ ውስጥ እንዳልወድቅ እፈራለሁ፡፡ አባቴም ሁልጊዜ ስፈራ ስለሚያውቅ እቤት እስክንደርስ ድረስ በእጁ ይደግፈኛል፡፡ ትልቅና ጠንካራም በመሆኑ በእነዚያ ትላልቅ እጆቹ በመያዜ ደህንነት ይሰማኛል፤ እንደተወደድኩም ይገባኛል፡፡ እንደዚያ በፍቅር ጢል መደረግ ደስ ያሰኘኛል፡፡ ለዚህም ምክንያት የሆነው በተለይ አባቴ ምንም እንኳን እንደሚወደን ብናውቅም በዘልማዳዊው መንገድ የሚያምን፣ ስሜቱን ብዙውን ጊዜ አውጥቶ የማያሳይና ወንድሞቼንም ሆነ እኔን እንደሚወደን የማይነግረን በመሆኑ ነው፡፡
ከዋና ስንመለስ ቆንጆዋ እናቴ በየቀኑ ወደ ትምህርት ቤት ከመሄዳችን በፊት የምትመግበንን ትኩስ የሩዝና የፎሶሊያ ቁርስ እየሠራች በኩሽና ስትባትል እናገኛታለን፡፡ ብርታቷ እኔን ከማስደነቅ ቦዝኖ አያውቅም - እማማ ሁልጊዜ ከቤተሰባችን አባላት ሁሉ ከእንቅልፍ ለመነሳት የመጀመሪያዋና ወደ መኝታ ለመሄድ የመጨረሻዋ ነበረች፤ ቤቱን እንደሚጠበቀው ለማሠጋደድ፣ ልብሶቻችንን ለማስተካከል፣ መጻህፍታችንንና በትምህርት ቤት የሚጠበቁብንን ጉዳዮች ለማዘገጃጀትና የአባቴን የሥራ ወረቀቶች ለማደራጀት ከሁላችንም በፊት ቀድማ እየተነሣች ትለፋለች፡፡ ልብሶቻችንን ሁሉ እሷው በልካችን ትሰፋለች፣ ጸጉራችንን ትቆርጣለች፤ ቤቱንም በእጅ ሥራዎች ጌጦች ታሸበርቀዋለች፡፡ ለቁርሳችን የምትሠራው ፎሶሊያ የሚለማው እኛ ጠዋት ከመኝታችን ሳንነሳ እማማ በምትንከባከበው በጓሮ አትክልት ማሳችን ነው፡፡ እህሉን ቃኝታ ለቀን ሠራተኞቹ የእርሻ መሣሪያዎች ታከፋፍልና ላሞቻችንና ሌሎቹ እንስሶቻችን እንዲቀለቡና እንዲታጠቡ ታደርጋለች፡፡ እነዚህን የማለዳ ሥራዎቿን ከጨራረሰች በኋላ እኛን ወደ ትምህርት ቤት ትሸኝና በእግሯ ቁልቁል መንገዱን ይዛ የሙሉ ጊዜ የማስተማር ሥራዋን ለመጀመር በአቅራቢያችን ወዳለው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትሄዳለች፡፡
ወላጆቼ መምህራን ነበሩ፡፡ ድህነትንና ርሃብን ብቸኛው መመከቻም ትምህርት እንደሆነ በጽኑ ያምናሉ፡፡ በቆዳ ስፋቷ ከሞላ ጎደል ጂቡቲን የምታክለው ሩዋንዳ ከአፍሪካ ትናንሽ ሀገራት አንዷ ብትሆንም በአህጉሩ በከፍተኛ የሕዝብ ጥግግት ተጠቃሽና ከዓለምም ደሃ ሀገራት አንዷ ነች፡፡ እናቴና አባቴ ከየቤተሰቦቻቸው የመጀመሪያዎቹ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቁ ሰዎች ሲሆኑ ልጆቻቸው እነርሱ ከደረሱበትም በላይ እንድንደርስላቸው ቆርጠዋል፡፡ አባባ ጠንክሮ በመሥራትና በሕይወቱ ሙሉ በማጥናት አርዓያ ሆኖናል፡፡ በሥራ ሕይወቱ ብዙ ክብሮችንና ዕድገቶችን ያገኘ ሲሆን፤ በአጭር ጊዜም ከአንደኛ ደረጃ መምህርነት ወደ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርነት አድጓል፡፡ በኋላም በአውራጃችን ላሉት ለሁሉም የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች ዋና አስተዳዳሪ ሆኖ ተሾሟል፡፡ በሩዋንዳ እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ልዩ የሆነ መጠሪያ ስም አለው፡፡ ለእያንዳንዱ ልጅ ወላጆች ልጁ ሲወለድ እናቱ ወይንም አባቱ መጀመሪያ ባዩት ጊዜ የተሰማቸውን ስሜት የሚያንጸባርቅ ስም ይሰጡታል፡፡ ኪንያሩዋንዳ በሚባለው ያገራችን ቋንቋ የኔ ስም (ኢሊባጊዛ) ትርጉሙ ‹‹መንፈሰ-ብሩህና ግሩም ጸዳል ያላት›› ማለት ነው፡፡ ይህን ስም ያወጣልኝ አባቴ ከተወለድኩባት ቅጽበት ጀምሮ ምን ያህል እንደሚወደኝ ስሜ ሁልጊዜ ሲያስታውሰኝ ይኖራል፡፡
የአባቴ ስም ሊኦናርድ፣ የእናቴ ደግሞ ማሬ ሮዝ ሲሆን፤ እናቴን ባልንጀሮቿ ሮዝ እያሉ ይጠሯታል፡፡ በ1963 ክረምት በአንደኛዋ የአክስቴ ልጅ ቤት ወላጆቼ ወደጋራ ጓደኛቸው ሰርግ ሲሄዱ ይገናኛሉ፡፡ ሲተዋወቁ አባቴ ጸጉሩ አድጎ እንደነገሩ ስለነበር እናቴ አየት አድርጋው ከንፈሯን መጠጠችለት፡፡
‹‹ጸጉርህ እንደዚህ ሆኖ ሰርግ ልትሄድ ነው?›› በማለት በቁጭት ጠየቀችው፡፡ አባቴ ጸጉር አስተካካይ ማግኘት እንዳልቻለ ገልጾ ‹ምን ላድርገው ብለሽ ነው› በሚል ስሜት ትከሻውን ነቀነቀ፡፡ ወዲያውኑ እዚያው እናቴ መቀስ ፈልጋ አባቴን አመቺ ስፍራ አስቀመጠችና ጸጉሩን ማስተካከል ጀመረች፡፡ ጸጉር ቆረጣውን እንዳሳመረችው አይጠረጠርም - ከዚያ ጀምሮ አልተለያዩምና፡፡ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ታጋብተው አባቴ ከዚያ በኋላ እናቴ እንጂ ሌላ ማንም ሰው ጸጉሩን እንደማያስተካክለው አረጋገጠ፡፡
ወላጆቼ በማስተማር ሥራቸውና አያቴ የሰጣቸውን መሬት በማረስ (ባቄላ፣ ሙዝና ቡና እያመረቱ ይሸጡ ነበር) ከሚያገኙት ገቢ ትንሽ ገንዘብ መቆጠብ ቻሉ
3👍3
#ሁቱትሲ


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#ምዕራፍ_ሁለት

#ከመቀመጫችን_ሲያስነሡን

‹‹ቱትሲዎች ከመቀመጫችሁ ተነሡ!››
አንድ ቀን አራተኛ ክፍል ሆኜ እማርበት በነበረው መማሪያ ክፍል ውስጥ ስድስት ልጆች ከመቀመጫቸው ተስፈንጥረው ሲቆሙ ግማሽ ደርዘን ወንበሮች ወደ ኋላ ተንጓጉ፡፡ ከዚያ በፊት ሁልጊዜ እናቴ በምታስተምርበት አነስተኛ ትምህርት ቤት ውስጥ እማር ስለነበር ምን እየተከሰተ እንደነበር ልገምት አልቻልኩም፡፡ በዚያን ወቅት አሥር አመቴ ስለነበርና ትንሽ አደግ ላሉ ልጆች የሚሆን ትምህርት ቤት ውስጥ ስማር የመጀመሪያ ቀኔ በመሆኑ የልጆቹ መራበሽ ግራ አጋብቶኛል፡፡ ከዚያ በፊት አስተማሪ የዘውግ ጥሪ ሲያካሂድ በፍጹም አይቼ አላውቅም፡፡
‹‹ቱትሲዎች በሙሉ ከመቀመጫችሁ ተነሡ!›› መምህራችን፣ ቡሆሮ፣ አምባረቀ፡፡ በትልቅ እርሳስ ከዝርዝሩ ላይ ከተማሪዎች ስም አጠገብ ምልክት እያደረገ ነበር፡፡ ከዚያም አቆመና በቀጥታ እኔ ላይ አፈጠጠ፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ፣ ሁቱ ስል አልተነሣሽም፤ ትዋ ስል አልተነሣሽም፤ አሁንም ቱትሲ ብል ልትነሺ አልቻልሽም፡፡ ለምንድነው?›› ቦሆሮ ፈገግ እያለ ቢሆንም ድምጹ ግን ክፋቱን ያሳብቅበታል፡፡
‹‹አላውቅም መምህር፡፡››
‹‹ምን ዘውግ ነሽ?››
‹‹የት አውቃለሁ፣ መምህር?››
‹‹ሁቱ ነሽ ቱትሲ?››
‹‹እኔ - እኔ አላውቅም፡፡››
‹‹ካላወቅሽ ውጪያ! ከዚህ ክፍል ውጪ፤ እና ምን እንደሆንሽ ሳታውቂ ተመልሰሽ አትምጪ!››
መጻሕፍቴን ሰበሰብኩና በሃፍረት አንገቴን ደፍቼ ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ ገና ያልታወቀኝ ቢሆንም በሩዋንዳ የዘውግ ክፍፍል ላይ የመጀመሪያዋን ትምህርቴን
ተማርኩ፤ ይህም ክው ነበር ያደረገኝ፡፡
ወደ ትምህርት ቤቱ ጓሮ ሮጬ ወንድሜ ዳማሲን የዕለቱን ትምህርት እስኪጨርስ ድረስ ከቁጥቋጦ ጀርባ ተደብቄ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ እንባዬን ማቆም ተስኖኝ ሰማያዊ የትምህርት ቤት የደንብ ልብሴ እስኪረጥብ ድረስ ነፈረቅሁ፡፡ ምን እንደተከሰተ ስላልገባኝ ወደ ክፍል ሄጄ የቅርብ ጓደኛዬን ዣኔትን ጉዳዩን ታብራራልኝ ዘንድ ለመጠየቅ በጣም ፈለግሁ፡፡ መምህሩ ሁቱ የሚለውን ስም ሲጠራ ተነሥታለች - ምን አልባትም መምህሩ ለምን እንዳመናጨቀኝ ታውቅ ይሆናል፡፡ በቁጥቋጦው ውስጥ ተኮራምቼ ዳማሲን እዚያ እስኪያገኘኝ ድረስ እንባዬን ሳዘራ ቆየሁ፡፡
‹‹ማን መታሽ ኢማኪዩሌ?›› ሲል ታላቅ ወንድሜ ባለችው የ13 ዓመት ሥልጣን ጠየቀኝ፡፡ አለኝታዬ ዳማሲን አንድ ሰው ጫፌን ከነካኝ ለመፋለም የተዘጋጀ ልጅ ነው፡፡ ቡሆሮ ያለኝን ነገርኩት፡፡
‹‹ቡሆሮ ጥሩ ሰው አይደለም›› አለ ወንድሜ፡፡ ‹‹ቢሆንም አትጨነቂለት፡፡ ሌላ ቀን ስም ሲጠራ እኔ የማደርገውን አድርጊ፤ ከጓደኞችሽ ጋር ተነሺ፡፡ ጓደኛሽ ዣኔት ስትነሳ ተነሺ፡፡››
‹‹ዣኔት ሁቱ ብሎ ሲጠራ ነበር የተነሣችው፡፡››
‹‹በቃ እንደዚያ ከሆነ ሁቱ ሲሉ ተነሺ፡፡ ጓደኞቻችን የሆኑት ያንን ከሆነ መቼም እኛም የምንሆነው እንደዚያው መሆን አለበት፡፡ ሁላችንም አንድ ሕዝብ ነን፣ አይደል?››
በዚያን ወቅት የማውቅበት መንገድ አልነበረኝም፤ ዳማሲንም እንደኔው በሩዋንዳ ስለነበረው ዘውገኝነት ግንዛቤ አልነበረውም… ይህም በአካባቢው በጥሩ ሁኔታ ይማሩ ከነበሩት ልጆች ውስጥ ከመመደባችን አንጻር እንግዳ ነገር ነው፡፡ በየዕለቱ ከትምህርት መልስ ወንድሞቼና እኔ ወደ ቤታችን በእናታችን ተቆጣጣሪነት የቤት ሥራችንን እንድንሠራ ከመጠራታችን በፊት የ90 ደቂቃ የእረፍት ጊዜ ነበረን፡፡ አባታችን ከራት በፊት የትምህርት ቤታችንን ሰሌዳዎች የምታክል ጥቁር ሰሌዳ በቤታችን መካከል አድርጎ ከአንድ ሰዓት ለሚበልጥ ጊዜ ያስጠናናል፡፡ የሒሳብ፣ ሰዋስውና መልክዓምድር ጥናት ጠመኔ እየሰጠ ያለማምደናል፡፡
ይሁን እንጂ ወላጆቻችን ስለራሳችን ታሪክ አላስተማሩንም፡፡ ሩዋንዳ የሦስት ዘውጎች፣ ማለትም የሚበዛው ሁቱ፣ አናሳ ቱትሲዎችና በጣም ትንሽ ቁጥር ያላቸው በጫካ ውስጥ የሚኖሩት ትዋዎች ስብስብ እንደሆነች አላስገነዘቡንም፡፡ የጀርመን ቅኝ ገዥዎችና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ቤልጅየሞች የሩዋንዳን ነባር ማኅበራዊ አወቃቀር ማለትም ሩዋንዳን ለምዕተ-ዓመታት ሰላምና ስምምነት የሰጣት ቱትሲ ንጉሥ የሚመሩትን ዘውዳዊውን ሥርዓት በአግላይ ዘውግ-ተኮር የመደብ ሥርዓት ቀይረውት እንደነበር አልተማርንም፡፡ ቤልጅየማውያኑ የቱትሲውን ገዥ መደብ ደግፈውና በመሪነት ደረጃ ያለውን አስተዋፅኦም ተቀብለው፣ አገሪቱን በተሻለ መንገድ ለማስተዳደርና ለቤልጅየማውያኑ ከፍተኛ ትርፍ ለማስገኘት ያግዝ ዘንድ ቱትሲዎች የተሻለ ትምህርት እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡ ቤልጅየሞች በሁቱና ቱትሲ መካከል ፈጥረውት የነበረውን ክፍተት በማባባስ ሁለቱን ዘውጎች በቀላሉ ለመለየት የዘውግ መታወቂያ ደብተር አስተዋውቀዋል፡፡ እነዚያ የማይረቡ ስህተቶችም በሁቱዎች ዘንድ ዘላቂ ቁጭት በመፍጠር ለዘር ጭፍጨፋ መሠረት ለመጣል አገዙ፡፡ ቱትሲዎች የተሻለ ነጻነት በጠየቁ ጊዜ ቤልጅየማውያኑ በጠላትነት አዩአቸው፡፡ በ1959 ደም-አፋሳሽ የሁቱ አመፅን ደግፈው ዘውዳዊው ሥርዓት እንዲገረሰስ አደረጉ፡፡ ከ100 000 በላይ ቱትሲዎች በበቀል በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት ውስጥ ተገደሉ፡፡ በ1962 ቤልጅዬም ከሩዋንዳ ለቃ ስትወጣ የሁቱ መንግሥት አንቀጥቅጦ በመግዛት ላይ ሲሆን ቱትሲዎችም በሁቱ አክራሪዎች ማሳደድ፣ ሽብርና ግድያ የሚፈጸምባቸው ሁለተኛ ዜጎች ለመሆን በቁ፡፡ በብዙ አሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች ግድያዎች የዕለት ከዕለት ክስተት በነበሩባቸው አሥርት ዓመታት ውስጥ ሞቱ፡፡ የሽብር ዑደቱ ተጧጡፎ መድሎ መፈጸሙ ቀጠለ፡፡ የሁቱው መንግሥት ከቤልጅየሞች የአገዛዝ ዘመናት የወሰደው የዘውግ መታወቂያ ደብተር አሠራር መድሎውን የበለጠ ይፋና ቀላል አደረገው፡፡
ወላጆቻችን እኔና ወንድሞቼ ቢያንስ በልጅነታችን እንዳንማራቸው ያልፈለጓቸው የታሪክ ትምህርቶች እነዚህ ነበሩ፡፡ ስለ መድሎም ሆነ ስለ ግድያ ዘመቻዎቹ፣ ስለ ዘር ማጽዳቱም ሆነ የዘር መታወቂያ ካርዶቹ አላወሩንም - እነዚህ ነገሮች ፈጽሞ የልጅነቴ አካል አልነበሩም፡፡
ዘርን፣ ሃይማኖትን ወይንም ዘውግን ከግምት ውስጥ ሳናስገባ በቤታችን ማንንም ሰው በደስታ እንቀበላለን፡፡ ወላጆቼ የእርስዎን ሁቱ ወይንም ቱትሲ መሆን ከስብዕናዎ ጋር አያገናኙትም፡፡ ጥሩ ጸባይ ካለዎትና ገራገር ከሆኑ እጆቻቸውን ዘርግተው ሰላምታ ያቀርቡልዎታል፡፡ ወላጆቼ ራሳቸው ግን በሁቱ ጽንፈኞች የደረሱባቸው የተወሰኑ አሰቃቂ ችግሮች ነበሩ … እንዲያውም አንደኛውን ትንሽ ትንሽ አስታውሳለሁ፡፡ ያኔ የሦስት ዓመት ልጅ ነኝ፡፡ ነፍስ ባለማወቄ ምን እየተከሰተ እንደነበር አልገባኝም፡፡ የምሽቱን ሰማይ እሳት ሲንቦገቦግበት፣ እናቴም በእጆቿ ጥብቅ አድርጋ ታቅፋኝ ከቤታችን ስትሮጥ ይታወሰኛል፡፡ ይህ የሆነው ብዙ ቱትሲዎች በተሳደዱበት፣ ከቤቶቻቸው በተነዱበትና በየመንገዱ በተገደሉበት የ1973ቱ መፈንቅለ-መንግሥት ወቅት መሆኑ ነው፡፡ በኛ ክፍለሀገር ሁቱ ጽንፈኞች የቱትሲዎችን ቤቶች በየተራ አቃጥለዋል፡፡ እሳቱ ወደኛ ሽቅብ ሲገሰግስ መላው ቤተሰቤ አብሮ ቆሞ ወደ ኪቩ ሐይቅ ቁልቁል በማስተዋል ላይ ነበረ፡፡ ሩታካሚዜ ወደተባለው ጥሩ ሁቱ ወዳጅ ጎረቤታችን ቤት ሸሸን፡፡ እርሱም ግድያዎቹና ቃጠሎው እስኪያቆሙ ድረስ ሸሸገን፡፡ ወደ ቤታችን ስንመለስ የሚጫጫስ
👍21
#ሁቱትሲ


#ምዕራፍ_ሦስት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ

#ቅድመ_ከፍተኛ_ትምህርት

በሦስተኛውና በመጨረሻው ዓመት ጦርነት ከመፈንዳቱ በቀር ሕይወት በሊሴ ጥሩ ነበር፡፡
የ1990 የጥቅምት ወር የመጀመሪያዋ ቀን ከሰዓት ቆንጆና ብሩህ ነበረች፡፡ የክፍል ጓደኞቼና እኔ የግብረገብ ትምህርት ክፍለጊዜያችን እስኪጀምር እየጠበቅን መምህሩ ለምን እንደዘገየ እናስባለን፡፡ አቶ ጋሂጊ ለመግባባት የማያስቸግር፣ የተረጋጋና ምናልባትም ካገኘኋቸው ሰዎች ሁሉ ልስልስ ጸባይ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም በመጨረሻ እጆቹን አያይዞ ሲመጣና በክፍሉ ፊትለፊት ወደፊትና ወደኋላ ሄድ መለስ ሲል አንዳች ነገር እንደተከሰተ ገምተናል፡፡ አንደኛዋ ተማሪ ችግሩ ምን እንደሆነ ብትጠይቀውም ወደ እኛ ሳያይ መለስ ቀለስ ማለቱን ቀጠለ፡፡
መምህራችን አንዳች መጥፎ ዜና እንደደበቀንና ምን አልባትም የተንቀሳቃሽ ምስል ትዕይንት ምሽትን መነኩሲቶቹ ሰርዘውት እንደሆነ ሊነግረን ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ጉዳዩ ግን ከዚያ የባሰ ነበር፡፡ በትምህርት ቤት ውስጥ የዜና ዘገባዎችን ማዳመጥ ስለማይፈቀድልን በመኖሪያ ቤቴ እንደነበረው ሁሉ ከዓለም ወሬ ተነጥያለሁ፡፡
‹‹በሀገሪቱ ላይ ጥቃት እንደተፈጸመ ሰማሁ›› ሲል አቶ ጋሂጊ በሃዘኔታ ነገረን፡፡ ‹‹በጣም አደገኛና በሁላችንም ላይ ለረጅም ጊዜ ተጽዕኖ የሚኖረው ይሆናል ብዬ እፈራለሁ፡፡››
ክፍሉ በጸጥታ ተዋጠ - ከዚያ ሁሉም ባንዴ ማውራት ጀመረ፣ ጥያቄ መጠያየቅ፣ ሩዋንዳን ማን ለምን እንደሚያጠቃት ለማወቅ መጠባበቅ፡፡
‹‹በዩጋንዳ የሚኖር የአማጽያን ቡድን የአገሪቱን ድንበር አቋርጧል›› ሲል መለሰልን፡፡ ‹‹በዋነኝነት ከሩዋንዳ የሄዱ ጥገኞች ልጆች ሲሆኑ ተሰባስበው ወደ ሀገሪቱ ለመግባት እየተዋጉ ነው፡፡ ከዚህ ስፍራ በስተሰሜን በኩል በአሁኑ ሰዓት በአማጽያንና በሩዋንዳ መንግሥት ወታደሮች መካከል ከባድ ውጊያ በመካሄድ ላይ ነው፡፡›› አቶ ጋሂጊ ፍርሃትና ንዴትን የሚያንጸባርቅ የጥያቄዎች ዝናብ ወረደበት፡፡ ‹‹ቱትሲዎቹ ሽፍቶች ግን ምንድን ነው የሚፈልጉት? ለምን ጦርነት ይከፍቱብናል? ትምህርት ቤቱ ጋር ከደረሱስ ምን ያደርጉን ይሆን?››
የሃፍረት ሙቀት በማጅራቴ ተሰማኝ፤ በማስደገፊያዬም ስር ለመደበቅ ፈለግሁ፡፡ በክፍሉ ውስጥ ካለነው 50 ተማሪዎች 47ቱ ሁቱዎች ናቸው፡፡ በጣም ስለፈራሁና ስለራሴ ስለተጨነቅሁ ሌሎቹን ሁለት ቱትሲ ልጃገረዶች ማየት እንኳን ተሳነኝ፡፡ በቱትሲነቴ ሳፍርና በሊሴም ተለይቼ ስታይ የመጀመሪያዬ ነው፡፡
‹‹አማጽያኑ ራሳቸውን የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር (ሩአግ) ብለው አደራጅተዋል፡፡ ቡድኑ ሩዋንዳን ከዓመታት በፊት ለቀው የሄዱና እንዳይመለሱ የተከለከሉ የቱትሲዎች ድርጅት ነው፡፡ እነዚህ የውጪ ዜጎች ወደ ሩዋንዳ በመግባት መንግሥታዊውን ለመያዝ ጦርነት አውጀውብናል›› አለ፡፡
ስለ ሩአግ ምንነት ግንዛቤው ነበረኝ፡፡ አባላቱ መንግሥትን ለመጣል ሲሉ ብቻ እንደማይዋጉም አውቃለሁ፡፡ እኩልነት በሰፈነባትና በነጻ ሀገር መኖርን ይፈልጋሉ፡፡ አብዛኞቹ የሩአግ ወታደሮች ስደተኞች ቱትሲዎች ወይንም ልጆቻቸው ናቸው፡፡
በ1959ና በ1973ቱ ችግሮች እንዲሁም ሁቱ ጽንፈኞች የግድያ ዘመቻዎችን ባካሄዱባቸው ሌሎች በርካታ ጊዜያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሕይወት ለማዳን ከሩዋንዳ ሸሽተዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ አማጽያኑን ‹‹የውጪ ዜጎች›› ያላቸው አብዛኞቹ እንደ ዩጋንዳና ዛየር ባሉ ጎረቤት ሀገራት ስላደጉ ነው - ያ የሆነው ግን ርዕሰ-ብሔር ሃብያሪማና ስደተኞች ፈጽሞ ወደ ሀገራቸው አንዳይመለሱ የሚከለክል ሕግ ስላወጡ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ግዙፍ የቱትሲ ስደተኞች ስብስብ እንዲፈጠር ያደረጉ ሲሆን አንድ ሙሉ የሩዋንዳ ቱትሲዎች ትውልድንም አንዴ እንኳን የእናት አገሩን አፈር ሳይረግጥ እንዲያድግ አስገድደዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ ያንን ፈጽሞ ባይገልጽም ቱትሲዎች ራሳቸውን ከጽንፈኛ ሁቱዎች ለመከላከል በሞከሩ ቁጥር ግን ምን እንደሚከሰት ያውቃል፡፡ ለእኛ መጨነቁን ‹‹ይህ ለቱትሲዎች በጣም አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል - ይህን ዓይነት ነገር ወደ ብዙ ግድያዎች ሊያመራ ስለሚችል መንግሥትና አማጽያኑ ችግራቸውን እንዲፈቱና ደም መፋሰስ እንዲቆም እንጸልይ፡፡››
የዕለቱ ትምህርታችን በዚሁ አበቃ፡፡ ሴቶቹ ልጆች ግን የሚያወሩት ስለጥቃቱና ቱትሲ ወታደሮቹ ወደ ትምህርት ቤታችን ቢደርሱ ምን ማድረግ እንደሚኖርባቸው ብቻ ሆነ፡፡ ከሁለት ቱትሲ የክፍል ጓደኞቼ ጋር ጸጥ ብዬ ላለመታየት እየሞከርኩ ተቀመጥሁ፡፡ ቱትሲዎች እንዴት ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደተያዙ ሳስብ ሃፍረቴ ወደ ንዴት ተለወጠ፡፡ የመንግሥት ወታደሮችን አሸንፎ ለመድሎው ፍጻሜ ያበጅለት ዘንድ ተስፋ በማድረግ በልቤ ለሩአግ አጋርነቴን አሳየሁ፡፡ በመጨረሻ ግን ንዴቴ ወደ ፍራቻ የተቀየረው ስለመንደሬና ስለቤተሰቤ በተጨነቅሁ ጊዜ ነው፡፡ አምላኬ ቤተሰቤን ሰላም ያደርግልኝ ዘንድ ዓይኖቼን ጨፍኜ ተማጸንኩት - በወቅቱ ያለ-ነሱ እንዴት በሕይወት እንደምቆይ ስለማላውቅ፡፡
ብዙዎቹ ተማሪዎች ጦርነቱ አስከፊ በነበረበት በሰሜኑ ክፍል ዘመዶች ስለነበሯቸው የትምህርት ቤቱ ርዕሰ - መምህር የሬድዮ ዘገባ እንድናዳምጥና ስለ ክስተቱ እንድንረዳ ፈቀደልን፡፡ ብሄራዊው ሬድዮ የሚያስተላልፈው ዘገባ ከሞላ ጎደል የጥላቻ ውትወታ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዘጋቢዎቹ አማጽያኑ እንደ አውሬ በጫካ እንደሚኖሩ፣ የሰው ስጋ እንደሚበሉና ከዝንጀሮዎች ጋር ወሲብ እንደሚፈጽሙ አተቱ፡፡ የለየላቸው ሰይጣኖች ስለሆኑ ቀንድ አብቅለዋል ተባለ፡፡ ‹‹አማጽያን በረሮዎቹ›› በማናቸውም ስፍራና ጊዜ ሊተናኮሉ ስለሚችሉና መሰሪ ስለሆኑ ሩዋንዳውያን ራሳቸውን እንዲጠብቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው፡፡ እነዚህ ዘገባዎች ቀድሞውንም የተዛባ አመለካከት የነበራቸውን ልጃገረዶች አቀጣጠሏቸው፡፡ አንዷማ በጣም ፈርታ ስለነበር ልታስገድለኝ ነበር፡፡
ዳኒዳ ከመኝታ ቤት እህቶቼ አንዷ ስትሆን ስለአማጽያን ወታደሮቹ የተነገሩትን ሁሉንም አስፈሪ ገለጻዎች አምናቸዋለች፡፡ አንድ ምሽት ከመኝታ ቤቱ ውጪ ወደሚገኘው መታጠቢያ ክፍላችን ለመጠቀም ስሄድ ከእንቅልፏ ሳልቀሰቅሳት አልቀርም፡፡ ምሽቱ በጣም ይቀዘቅዝ ስለነበር እንዲሞቀኝ ትልቅ ፎጣዬን በራሴ አስሬ የሚረዝምብኝ የነበረ የሌሊት ልብስ ለብሻለሁ፡፡ ትንሽ ሳላስፈራ አልቀርም፣ ተመልሼ ለመግባት በሩን ለመክፈት ስሞክር ዳኒዳ ፊቴ ላይ በኃይል ዘጋችብኝ፡፡ ኡኡታዋን ስታቀልጠው ግቢው ተሸበረ፡፡
‹‹አድኑኝ! እርዱኝ! ወይኔ አምላኬ! ኧረ እርዱኝ፡፡ የሩአግ ወታደር ነው - ሊገድለን፣ ሊበላን መጣ፡፡ አቤት ቀንዶቹ!››
የዳኒዳን ጆሮ ሰንጥቆ የሚገባ ድምፅ ስላወቅሁት በእርጋታ ‹‹ዳኒዳ፣ እኔ እኮ ነኝ፣ ኢማኪዩሌ ነኝ፡፡ ወታደር አይደለሁም፡፡ ቀንድም የለኝ፤ ፎጣዬን ነው እኮ ራሴ ላይ ያሰርኩት!›› አልኳት፡፡
ሞቅ አድርገው የሚረግጡ እግሮች ከኮረኮንቹ ጎዳና በኩል ሰምቼ ዘወር ስል የትምህርት ቤታችን ትልቁ ዘበኛ በደረቴ ትይዩ ያነጣጠረ ጦር ይዞ በጨለማው ወደኔ ይገሰግሳል፡፡ ብርክ ይዞኝ ጉልበቴ ተሽመድምዶ መሬት ላይ ቁጭ አልኩ፡፡ ዘበኛው ከእኔ መጠነኛ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ! ኢማኪዩሌ፣ ገድዬሽ ነበር እኮ! ማናባቷ ነች እንደዚያ የምትጮኸው?›› አለ፡፡
በወቅቱ
#ሁቱትሲ


#ምዕራፍ_አራት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#ወደ_ዩኒቨርሲቲ

በ1991 ክረምት መጨረሻ የማይቻለው ተከሰተ - በቡታሬ በሚገኘው ብሄራዊው ዩኒቨርሲቲ መማር የሚያስችለኝ የትምህርት ዕድል ተሰጠኝ፡፡ በሕይወቴ ሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትን በጽኑ ስመኝ ነበር፡፡ በመሆኑም በፊቴ እነዚያ ሁሉ መሰናክሎች ቢጋረጡብኝም በድንገት ሕልሜ እውን ሆነ፡፡
ወላጆቼ ዜናውን ሲሰሙ በጣም ተደስተው ተቁነጠነጡ፡፡ በትክክለኛው የሩዋንዳ ደንብ - ያው በድግስ መሆኑ ነው - እናከብረው ዘንድም ምግብና መጠጥ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ይሉ ጀመር፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከቤታችን የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ነሽ፣ ስለሆነም አሁኑኑ ይህን ለሁሉም ሰው ማሳወቅ አለብን!›› ሲል አባቴ በኩራት ተናገረ፡፡ በማግስቱ ረጅም መንገድ ተጉዤ ለአያቴ፣ ለአክስቶቼ፣ ለአጎቶቼና ለሁሉም በአቅራቢያችን መንደሮች ለሚኖሩት ልጆቻቸው ወሬውን እንዳበስር አመቻቸልኝ፡፡
ሌሊቱን ሙሉ ስንስቅ፣ ስንበላና ወደፊት ስለሚኖሩት በጎ ነገሮች ሁሉ ስናወጋ አሳለፍን፡፡ ወላጆቼ በዚያ ምሽት ሸክም ከትከሻዎቸው እንደወረደላቸው ሁሉ ወደ ወጣትነት የተመለሱ መሰሉኝ፡፡
እናቴ በደስታ ፈክታ አመሸች፡፡ ‹‹ሁሉም ነገር ላንቺ ብሩህ የሆነልሽ ይመስላል፣ ኢማኪዩሌ›› አለችኝ፡፡ ‹‹ከአሁን በኋላ ሙሉ በሙሉ የራስሽን መንገድ ማበጀት ትችያለሽ፤ ቀና በይ፤ ማንም ሌላ ሰው በገበታሽ ላይ በፍጹም ምግብ እንዲያስቀምጥልሽ አትጠባበቂ፡፡››
አባቴም ከኔ ጋር መጠጫ አጋጭቶ ብዙ አባታዊ ምክር ለገሰኝ፡፡ ‹‹ብዙውን ጊዜ በዩኒቨርሲቲ የሚማሩት ወንዶች ሲሆኑ እነርሱም አንቺን እንደነርሱ ጎበዝ ነች ብለው አያስቡም፡፡ ግን እንደነሱ መትጋት እንደምትችዪ አውቃለሁ፤ አንዲያውም ከማንኛውም ወንድ በተሻለ፡፡ አንቺ ቱትሲ ስለሆንሽ ዩኒቨርሲቲ መግባት ፈተና ሆኖብሽ ቆይቷል፤ ይኸው አስቸጋሪው ወቅት አለፈ፡፡ እንግዲህ የራስሽ ድርሻ ነው - በደንብ አጥኚ፣ ጸልዪ፤ ስታድጊ በስስት እናይሽ እንደነበርሽው ምስጉን፣ ደግና ቆንጆ ልጅ መሆንሽን ቀጥዪበት፡፡››
በጣፋጭና ፍቅር የተሞላባቸው ቃላቱ ልቤ ሐሴት አደረገች፡፡ ‹‹ሃሳብ አይግባህ አባባ›› አልኩት፡፡ ‹‹አንተንም ሆነ እማማን አላሳፍራችሁም፡፡ አኮራችኋለሁ፡፡››

ስለ ሰው ልቦናና አእምሮ አሠራር ለመማር ሥነ ልቦናንና ፍልስፍናን ለማጥናት ብፈልግም የትምህርት ዕድሉ በተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች ባሉ ክፍት ቦታዎች የተወሰነ ስለነበር ራሴ የምፈልገውን የጥናት መስክ እንድመርጥ አልተፈቀደልኝም፡፡ በተግባራዊ ሳይንስ መርሃ-ግብር መመደቤ ተስማምቶኛል፡፡ በሊሴ ለወንድሞቼ ችሎታዬን ለማሳየት ስል ራሴን በሒሳብና ፊዚክስ አብቅቼ ስለነበር አሁን ያ ሥንቅ ይሆነኛል፡፡ ሻንጣዎቼን አዘገጃጅቼ ወዲያውኑ ከመንደሬ ደቡብ ምሥራቅ አራት ሰዓት ወደሚያስነዳውና ፍጹም አዲስ ሕይወት ወደሚጠብቀኝ ወደ ቡታሬ አቀናሁ፡፡

ትምህርት ቤቱ ቅጥር-ግቢ ስደርስ ክሌሜንታይንን ጨምሮ ከሊሴ ስድስቱ የሴት ጓደኞቼ፣ የትምህርት ዕድሉን ማግኘታቸውን ተረዳሁ፡፡ ጓደኛዬ ሳራ እዚያው አንድ ዓመት ቀድማ ገብታ ስትማር የቆየች ሲሆን አንድ መኝታ ክፍል ውስጥ አብረን እንድንኖር ስትጠብቀኝ ኖሯል፡፡ በተጨናነቁ ክፍሎች ውስጥ ከተኛሁባቸው ከእነዚያ ዓመታት በኋላ ከአንዲት ሴት ልጅ ጋር ብቻ አንድ ክፍል መጋራት እጅግ ይመቻል፡፡ ክሌሜንታይን ብዙ ጊዜ የኛን ክፍል ትጎበኝ የነበረ ሲሆን በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን ራሳችንን በኤሌክትሪክ የማቃጠሉን ዕቅዳችንን ባለመፈጸማችን እንዴት ዕድለኞች እንደነበርን በጨዋታ መካከል እናነሳለን፡፡ ያ ቢሆን ኖሮ የዩኒቨርሲቲን አስደሳች ነገሮች ሁሉ መች እናይ ነበር?
ትምህርቱን ወደድኩት፤ በጣም ጠንክሬም አጠና ጀመር፡፡ የዩኒቨርሲቲን አስደሳችነትና ነጻነት እንዴት እንደወደድኩት! የትምህርት ዕድሉ ለእኔ ትልቅ ነገር የነበረውን ወደ 30 የአሜሪካን ዶላር የሚሆን ወርሃዊ የኪስ ገንዘብንም ይጨምራል፡፡ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ትልቅ ሰው ነጻነት ተሰማኝ፡፡ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ መልበስ ቀረልኝ፤ ከተማም ሄድ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር ቆንጆ ቆንጆ ልብሶችን መግዛት ቻልኩ፡፡ አቤት ሲያስደስት!
ቡና ተፈልቶ በሚሸጥባቸው ስፍራዎች፣ በሰንበት ተንቀሳቃሽ ምስል በሚታይባቸው ቦታዎችና በየአሥራ አምስት ቀኑ ቅዳሜ ምሽት በሚካሄዱት የትምህርት ቤት አቀፍ የዳንኪራ ጊዜያት እስከመገኘት ደርሼ በማኅበራዊ ሕይወት በጣም ንቁ ተሳታፊ ሆንኩ፡፡ የትዕይንት ማሳያ ቡድንንም ተቀላቅዬ ብዙውን ጊዜ የቡታሬ ከንቲባ በሚገኙባቸው በሁሉም ትዕይንቶች እዘፍንና እጨፍር ነበር፡፡ ሃይማኖታዊ ገጸባህርያትን ወክሎ መተወን ምርጫዬ በመሆኑ እንዲያውም አንድ ጊዜ የምወዳትን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወክዬ ተጫውቻለሁ፡፡ ሁልጊዜ ለጸሎት የሚሆን ጊዜ እተዋለሁ፡፡ ያንን ጽናት ማግኘቴና ጸሎት ማድረጌ እጅጉን አረጋግቶኝና አትኩሮቴን እንድሰበስብ ረድቶኝ ነበር፡፡ ቤተ-ክርስቲያን በሳምንት ብዙ ጊዜ እሄዳለሁ፤ ከሴት ጓደኞቼም ጋር የጸሎት ቡድን አቋቁሜያለሁ፡፡
ለናፍቆት ጊዜ ባይኖረኝም ከአባቴ የሚላኩልኝ ብቸኝነት የሚንጸባረቅባቸው ደብዳቤዎች ቤተሰቤን ቶሎ ቶሎ መጎብኘት እንዳለብኝ አስገነዘቡኝ፡፡ በወቅቱ ቪያኒ በአዳሪ ትምህርት ቤት ስለነበር ወላጆቼ ብቸኝነትን መላመድ አቅቷቸዋል፡፡ ‹‹ከልጆቼ አንዳቸውም እዚህ ሳይኖሩ ሕይወቴ እንደ ዱሮው ሊሆን አይችልም›› ሲል አባቴ ጻፈልኝ፡፡ ‹‹ቤቱ በጣም ጭር ብሏል፡፡ አንዳንዴ እኔና እናትሽ እርስ በርሳችን እንተያይና እንገረማለን፣ ‹ያ ሁሉ ሣቅ የት ሄደ?› እንላለን፡፡ የራስሽ ልጆች ሲኖሩሽ፣ ኢማኪዩሌ፣ ሳትጠግቢያቸው ስለሚሄዱብሽ አብረውሽ እያሉ እያንዳንዷን ደቂቃ በደስታ ማሳለፍሽን እርግጠኛ ሁኚ፣ …››
በማታባ ያሉትን የተወሰኑትን ጓደኞቼን የሚያውቅ ዮሃንስ የሚባል ተማሪ ጓደኛም አገኘሁ፡፡ ከእኔ ሦስት ዓመት ይበልጥ የነበረና ‹‹ድንገት›› ከኔ ጋር በትምህርት ቤቱ የተለያዩ ስፍራዎች ግጥምጥም የማለት የተለየ ጸባይ የነበረው ልጅ ነው፡፡ መጽሐፍቴን ይይዝልኝ፣ የትምህርት ቤታችንን ግቢ ያሳየኝና ከጓደኞቹ ጋር ያስተዋውቀኝ ጀመር፡፡ አማላይ፣ ታጋሽና ለሰው አሳቢ ልጅ ነበር፡፡ በጫካው ውስጥ ለረጅም የእግር ጉዞ አብረን እየሄድን ለእኛ አስፈላጊ ስለሆነው ጉዳይ እናወራለን - ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ ቤተሰብና ስለ ጥሩ ትምህርት፡፡ በኋላም ላይ ፍቅር ለመጀመር በቃን፤ በመጭዎቹም ዓመታት ውስጥ አንዳችን ለሌላችን በጣም እንተሳሰብ ጀመር፡፡ ዮሃንስ ሁቱ ቢሆንም ግን ይህ ጭራሽ ጉዳያችን አልነበረም፡፡ ለአባቴ ይልቁን ዮሃንስ ወንጌላዊ ክርስቲያንና የሰባኪ ልጅ መሆኑ ያሳስበዋል፡፡
‹‹ካቶሊክ መሆንሽን አትርሺ›› እያለ አባቴ ያስታውሰኛል፡፡ ‹‹ዮሃንስ ጥሩ ልጅ ይመስላል፤ እንድታፈቅሪውም መርቄሻለሁ - ግን ወደ እርሱ ኃይማኖት ሊቀይርሽ እስካልሞከረ ድረስ ነው፡፡›› አባቴ በጣም ታጋሽ ሰው ሲሆን ሃይማኖተኛም ነው በዩኒቨርሲቲ የቆየሁባቸው ሁለቱ የመጀመሪያ ዓመታት በረሩ፤ ሁሉም ነገር መልካም ሆነልኝ - ውጤቴ ጥሩ፣ ቤተሰቤ ጤነኛ፣ ሕይወቴም አስደሳች ሕይወት ስለሚመች አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ጦርነት መኖሩን ለመርሳት አይከብደንም፡፡ አልፎ አልፎ የሚካሄዱ የሰላም ድርድሮችና የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢኖሩም በቱትሲ አማጽያንና በመንግሥት
👍1
#ሁቱትሲ


#ክፍል_አምስት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#ወደ_ሀገር_ቤት

ሁልጊዜ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ የጥላቻ ድምፅ እሰማለሁ፡፡ የአር.ቲ. ኤል. ኤም. ሬድዮ የጥላቻ ድምጾች በመኝታ ቤቴ መስኮት ገብተው ህልሞቼ ውስጥ እስኪደነቀሩ ሌሊቱን በሰላም ተኝቼ አሳልፋለሁ፡፡ ልብ ይበሉ፣ በሦስተኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ አር. ቲ. ኤል. ኤም. በጽንፈኛ ሁቱዎች ዘንድ አዲሱና በጣም ታዋቂው ሬድዮ ጣቢያ ለመሆን ችሏል፡፡ ጸረ-ቱትሲ መርዝን የሚረጭ የተለየ የጥላቻ መሣሪያ ወጥቶታል፡፡
ሁሌ ‹‹ስለ ሁቱ የበላይነት›› የሚጮህ አካል-አልባ ክፉ ድምፅ ሆነ፡፡ የሁቱ የበላይነትም ሁቱዎችን በቱትሲ ወዳጆቻቸውና ጎረቤቶቻቸው ላይ እንዲነሱ የሚያደርግ ተናዳፊ ተርብ ለመሆን ቻለ፡፡ ‹‹እነዚያ በረሮ ቱትሲዎች ሊገድሉን ወጥተዋል፡፡ አትመኗቸው… እኛ ሁቱዎች ቀድመናቸው ልንነሳ ይገባናል! መንግሥታችንን ገልብጠው ሊያሳድዱን እየዶለቱብን ነው፡፡ በርዕሰ-ብሔራችን ላይ አንዳች ነገር ቢከሰት ሁሉንም ቱትሲዎች ወዲያውኑ ማውደም ግድ ይለናል! እያንዳንዱ ሁቱ ሩዋንዳን ከነዚህ ቱትሲ በረሮዎች ለማጽዳት እጅ ለእጅ መያያዝ
አለበት! የሁቱ የበላይነት! የሁቱ የበላይነት!››
ይህን በመሰለ አጉለኛ ሁኔታ ከእንቅልፌ እነቃለሁ፡፡ በእርግጥ ዘገባዎቹ እጅጉን በሚያስጠላ ሁኔታ እንጭጭ በመሆናቸው አልፎ አልፎ ያሥቃሉ፡፡ እነዚያን የልጅ ስድቦችና ልቅ ማስፈራሪያዎች ማንም ሰው ከምር ይቀበላቸዋል ብሎ ማመን አሰቸጋሪ ሲሆን መንግሥቱም የሕዝብ ንብረት የሆነውን የአየር ሰዓት ቱትሲዎችን ለማስፈራሪያ መፍቀዱን ማወቁ ይረብሻል፡፡ በወቅቱ ግን በሀገሪቱ በርካታ ስፍራዎች ቱትሲዎች በጽንፈኞች እየተገደሉ መሆኑን በሚገልጹ ወሬዎች ይበልጡን ተረበሽኩ፡፡ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እንዳሉት ጓደኞቼ ሁሉ በመገናኛ ብዙሃን ስለሚተላለፉት ዘገባዎች ብዙ ላለማሰብና ላለማውራት ሞከርኩ፡፡ ቤተሰቤ ሁሌ አስደሳችና ልዩ ጊዜ የሚያሳልፍበት የትንሣኤ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ ይህን የበዓል ወቅት ጎረቤቶቻችንን በመጋበዝና ወዳጅ-ዘመዶቻችንን በመጠየቅ እቤታችን እናሳልፋለን፡፡ የቤተሰቡ አባላት በሙሉ የምንገናኝበትን የትንሣኤን በዓል እቤቴ ማሳለፍ አምልጦኝ የማያውቅ ቢሆንም እየቀረቡ መጥተው ለነበሩት ፈተናዎቼ ለመዘጋጀት ያግዘኝ ዘንድ በትምህርት ቤቱ ለመቆየት ፈለግሁ፡፡ በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት ቆርጫለሁ፡፡ ወላጆቼ ስልክ ስላልነበራቸው ለአባቴ ለምን እቤት እንደማልሄድ የሚያብራራ ደብዳቤ ጻፍኩለት፡፡ ወላጆቼ ሁልጊዜ ልጆቻቸው የተሻለ ውጤት ያመጡ ዘንድ

ከሚጠበቀው በላይ እንዲያጠኑ ስለሚፈልጉ ቅር እንደማይሰኙብኝ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይህ ለካ ትልቅ ስህተት ኖሯል!
አባቴ እቤት እንድሄድ የሚለምን ደብዳቤ ጻፈልኝ፡፡ እንዲያውም የጠየቀኝ የትምህርት ቤት እረፍቴ እስኪደርስ ሳልጠብቅ ወዲያውኑ እንድሄድ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንድሆን እንደሚፈልግና እቤት ያላንዳች ረብሻ ማጥናት እንደሚቻለኝ ቃል ገባልኝ፡፡ ልባዊ ተማጽኖው በዓይኖቼ እንባ ሞላባቸው፡፡ ውድ ልጄ፣
ትምህርት አንቺን ከኛ እንደነጠቀን ይሰማኛል፡፡ እናትሽና እኔ እረፍትሽ እስኪጀምር በጉጉት እየጠበቅን ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀመረ አንቺ እቤት መጥተሽ እንደገና እንደ ቤተሰብ ስለምንኖር ነው፡፡ መምጣትሽን እንፈልገዋለን፤ ወላጆችሽ ነን፤ እንወድሻለን፤ በእጅጉ እንናፍቅሽማለን - ይህን ሃቅ በፍጹም አትርሺው! ለሁለት ቀናት ቢሆንም እንኳን ልታዪን ልትመጪ ግድ ይልሻል፤ ጊዜውን ለሌላ ለምንም ጉዳይ መስዋዕት እንዳታደርጊው፡፡ ነዪልን፤ አብሮነትሽን እንፈልገዋለን …
ደብዳቤውን አንብቤ ሳልጨርሰው ወደ ቤት ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ ከወላጆቼ ጋር ስድስት ቀናትን አሳልፌ ለፈተናዎቼ በሳምንቱ መጨረሻ ትምህርት ቤት ለመመለስ አቀድኩ፡፡ የጉዞ ዝግጅቴን ሳደርግ የሳራ ታናሽ ወንድም የሆነው ኦገስቲን ከእኔ ጋር ለበዓሉ ወደ ወላጆቼ ቤት ሄዶ መዋል ይችል እንደሆን ጠየቀኝ፡፡ ኦገስቲን የወንድሜ የቪያኒ የልብ ጓደኛ ሲሆን የመንፈቀ-ዓመቱን ትምህርቱን ኪጋሊ ላይ ካገባደደ በኋላ በትምህርት ቤት መኝታ ቤታችን ውስጥ ቆይቷል፡፡ መለሎው፣ መልከ-ቀናውና አስደሳቹ የ18 ዓመቱ ኦገስቲን ከቪያኒ በቀር ማንም ሰው ፊት አያወራም፡፡ እንግዳችን ቢሆንልን እንደምንደሰት ነገርኩት፡፡

ኦገስቲንና እኔ ማታባ ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ደረስን፤ የቤተሰቤም አባላት በመምጣቴ በእጅጉ ተደሰቱ፡፡ በሳይንስ የድህረ-ምረቃ ትምህርቱን ለመከታተል ዓለም አቀፍ የትምህርት ዕድል ካገኘው ከኤይማብል በስተቀር ቤተሰቡ ተሟልቷል፡፡ ኤይማብል አገሪቱን ለቆ ከ5 000 ኪሎሜትሮች በላይ ወደምትርቀው ሴኔጋል ሄዷል፡፡ ዳማሲን በበኩሉ በታሪክ በሁለተኛ ዲግሪ ከተመረቀ ጀምሮ ከሚያስተምርበት ከኪጋሊ ተሳፍሮ መጥቷል፡፡ ቪያኒም ከአዳሪ ትምህርት ቤት ተመልሷል፡፡
የመጀመሪያዋን ቀን ከዳማሲን የመንደር ወሬ ስሰማ፣ ጓደኞቼን ስጠይቅ፣ ከቪያኒ ጋር ስንጫወትና ስንከራከር አሳለፍኩ፡፡ በመጭው ቀን፣ በትንሳኤ እለት፣ አብረን ጥሩ ምግብ በላን፡፡ አምላክን ስለሰጠን ነገር ሁሉ አመስግነን በቤተሰባችንና በመንደራችን ስላለው ስለ ሁሉም ሰው ደህንነት ጸለይን - በተጨማሪም ስለብቸኛው ቀሪ አባላችን ስለ ኤይማብል ልዩ ጸሎት አደረስን፡፡ በላያችን ያንዣብብ ከነበረው የፖለቲካ ውጥረት በስተቀር አዝናኝ ጊዜ በማሳለፍ ላይ ነን፡፡ ከወላጆቼ ጋር በመሆኔ ደህንነትና ችግር-አልባነት ተሰማኝ - ይህም የሆነው ምንም ነገር ቢከሰት ታጽናናን ዘንድ እናቴ ስለምትኖርና አባቴም እኛን የመከላከሉን ሥራ ስለሚሠራ ነው፡፡ ቢያንስ ያንን ነው ያሰብኩት ፡፡
ይህ ምሽት የኛ ዓለም እስከዘላለሙ ልትቀየር ትንሽ የቀራት መሆኑን ለመገመት የሚያዳግትበት እንደወትሮው ያለ ምሽት መሆኑ ነው፡፡ ስለ ትምህርት፣ ሥራና በመንደሩ እየተከሰተ ስላለው ነገር እቤት ቁጭ ብለን እናወራለን፡፡ እናታችን ስለ ሠብሉ ስትነግረን አባታችን ደግሞ የቡና ኅብረት-ሥራው የትምህርት ወጪያቸውን ስለሚሸፍንላቸው ሕፃናት ያወራልናል፡፡ ኦገስቲንና ቪያኒ ይቃለዳሉ፡፡ እኔ በበኩሌ እየተዝናናሁና ሁሉንም ነገር እየታዘብኩ እቤት በመሆኔ ደስተኝነት ተሰምቶኛል፡፡ ያልተደሰተው ዳማሲን ብቻ ነው፡፡ ሁልጊዜ በዓል ላይ ሕይወት የሚዘራው እሱ የነበረ ቢሆንም ምሽቱን ሙሉ ሲብሰለሰልና በሥጋት ሲናጥ ቆይቷል፡፡
‹‹ዳማሲን ምን ሆነሃል?›› ስል ጠየኩት፡፡
ወንድሜ ቀና ሲል ዓይኖቻችን ተገጣጠሙ፡፡ ከዚያም በኋላ ዝም ብሎ መቆየት አልተቻለውም፡፡ በተጣደፈ ቃላትና ስሜት ሸክሙን እኔ ላይ አቃለለ - ‹‹ኢማኪዩሌ አይቻቸዋለሁ፤ ገዳዮቹን አይቻቸዋለሁ፡፡ ወደ ቦን ቤት ስንሄድ በርቀት አይተናቸዋል፡፡ የኢንተርሃምዌን ባለ ደማቅ ቀለማት ልብሶች ለብሰዋል፤ የእጅ ቦምቦችንም ይዘዋል፤
ቦምቦች ነበሯቸው ኢማኪዩሌ!›› ሲል ድምጹ አሰቀቀኝ፡፡
ሁሉም ሰው ንግግሩን ስለሰማው ቤቱ እርጭ አለ፡፡ ወላጆቼ እርስ በርሳቸው ተያዩና ዳማሲንን አዩት፡፡
አባቴ ልጁን ለማረጋጋት ሲል ‹‹ምናልባት ሐሳብህ አሸንፎህ እየወጣ እንዳይሆን›› አለው፡፡ ‹‹ብዙ መጥፎ ወሬ ይሰማል፡፡ ሰዎችም አደጋን በሌለበት እያዩት ነው፡፡››
‹‹አይ፣ ዝም ብዬ እኮ እየቃዠሁ አይደለም›› አለ ዳማሲን በድንገት ቆሞ የጉዳዩን አጣዳፊነት በሚያንጸባርቅ መልኩ በመናገር፡
👍2😁1
#ሁቱትሲ


#ምዕራፍ_ስድስት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#መመለስ_አይታሰብም

እናቴ፣ አባቴ፣ ዳማሲን፣ ቪያኒ፣ ኦገስቲንና እኔ ቀኑን ሙሉ በግቢያችን ውስጥ በፍርሃት ተቆራምደን ሬድዮ ስናዳምጥ ዋልን፡፡ ከሀገራችን ውጪ የሚተላለፉት ዘገባዎች ተራ ሁቱ ዜጎች የመንግሥቱን ሰራዊትና የኢንተርሃምዌ ታጣቂዎችን ያልታጠቁ ንጹሃን ቱትሲዎችን በመግደሉ ተግባር ላይ እየተቀላቀሏቸው እንደሚገኙ ዘገቡ፡፡ የሀገር ውስጥ ጣቢያዎች በበኩላቸው ሁቱዎች ገጀራ እያነሱ ቱትሲ ጎረቤቶቻቸውን እንዲያጠቁ ያበረታቱ ገቡ፡፡
እንደ ትንሽ ልጅ አደረገኝ - ወላጆቼ ምን እንደማደርግ እንዲመሩኝ ተመኘሁ፡፡ ከ1959 ጀምሮ ከፖለቲካ አለመረጋጋቶችና ከቱትሲ ጭፍጨፋዎች ስለተረፉ መቼም ምን ማድረግ እንዳለባቸው ማወቃቸው አይቀርም ስል አሰብኩ፡፡ ብሔራዊው ሬድዮ ጣቢያ ሕዝቡ በየቤቱ እንዲቆይ አስጠነቀቀ፤ እኛም የወላጆቻቸውን ምክር እንደሚሰሙ ማለፊያ ልጆች ተቀበልነው፡፡ ከአጥራችን ውጪ ምን እየተከሰተ እንደነበር ለማወቅ በራችንን ለመክፈት እንኳን በጣም ፈራን፡፡ ከቅጥር-ግቢያችን ውጪ መንቀሳቀስ አደጋ ይኖረዋል ወይንም ሞት ያስከትላል ብለን እንደ እስረኛ እንቅስቃሴያችንን በቤት ውስጥ ገደብን፡፡
ስልክ አልነበረንም፤ ቢኖርም ኖሮ እንኳን አብዛኞቹ የሀገሪቱ የስልክ መስመሮች ዝግ ናቸው፡፡ ሬድዮናችን ከሚያደርሰን ወሬ በቀር ከማንም ጋር ግንኙነት የምናደርግበት መንገድ አልነበረም፡፡ ራሴን ልስት መሆኑ አስኪሰማኝ ድረስ ስለ አሰቃቂዎቹ ግድያዎች ስንሰማ ለሰዓታት ተቀመጥን፡፡ ጥላ በረድ ሲል መጻሕፍቴን ሳብ አድርጌ ለፈተናዎቼ መዘጋጀት ጀመርኩ፡፡
‹‹እንዴት ይሆንልሻል ኢማኪዩሌ?›› ሲል ዳማሲን ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ለማጥናት የሚሆንሽን ጽናትስ ከየት አመጣሽው? ተመልሰሽ ትምህርት ቤት እንደምትገቢስ ለምን ታስቢያለሽ?››
ወንድሜ ከሰዓታት በፊት ተስፋ ስቆርጥ ሲያጽናናኝ እንዳልነበር አሁን ራሱም ተስፋ ቆረጠ፡፡ ለመበርታት ተራው የኔ ስለሆነ ‹‹መጨነቅህን ተው›› አልኩት፡፡ ‹‹ይህን እናልፈዋለን፤ ሁኔታዎች ከተባባሱ በድንበሩ በኩል እንሾልካለን፡፡ እማማና አባባ ካሁን በፊት ይህን ዓይነቱን ችግር አልፈውታል፡፡ እምነት ይኑርህ፡፡››
ስለ እውነት ለመናገር ግን እኔ ራሴ ያለኝ እምነት ተሟጧል - የማጠናው ከቤተሰቤ ጭንቀት ላይ ሐሳቤን ለማንሳት አስቤ እንጂ ለፈተና ለመዘጋጀት አልነበረም፡፡
በእለቱ የሰማነው ብቸኛው አበረታች ዜና መነሻቸውን በዩጋንዳ ያደረጉት የቱትሲ አማጽያኑን መሪ የሩአጉን የፖል ካጋሜን መልዕክት ነው፡፡ በቱትሲዎች ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎች ካላቆሙ በስተቀረ እየተፋለሙ ሩዋንዳን ለመውረርና ቱትሲዎችን ለመታደግ እስከመጨረሻው እንደሚጸኑ ቃል ገቡ፡፡ ካጋሜ ያንን ሲሉ መስማቱ ያበረታታል፤ ሆኖም ግን ብቸኛው ‹‹መልካም›› ዜና የለየለት ጦርነት እንከፍታለን የሚል ማስፈራሪያ ብቻ በመሆኑ አዘንኩ፡፡ በዚያ ምሽት ማናችንም ከጥቂት ደቂቃዎች በላይ አልተኛንም፡፡ በሚቀጥለው ቀን በኪጋሊ ከሚኖሩት ከለዘብተኛ ሁቱዋ የሩዋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ከአጋቴ ጋር የተደረገ የቢቢሲን የስልክ ቃለ-መጠይቅ ሰማን፡፡ ምንም እንኳን የተ.መ.ድ ሰላም አስከባሪዎች እየጠበቋቸው ቢሆንም በቤታቸው ዙሪያ ሁሉ የጥይት እሩምታ ይሰማል፡፡ በዚህ ንግግራቸው ወቅት እርሳቸው፣ ባለቤታቸውና አምስት ልጆቻቸው ወለል ላይ መተኛታቸውንና የማምለጫ መንገድም እንደሌላቸው ገለጹ፡፡ ወዲውኑም ቃለ-መጠይቁ ሳያልቅ የስልክ መስመሩ ተቋረጠ፡፡ በኋላ እንደሰማነው ወታደሮች ወደ ቤታቸው ድንገት ገብተው እርሳቸውንና ባለቤታቸውን ገድለዋቸዋል፡፡ ትረፉ ሲላቸው ልጆቻቸው አልተገደሉም፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሯ ቃላት ስሜታችንን በእጅጉ ነኩት፤ በዚህ ወቅት ሁኔታዎች ይሻሻላሉ ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ ገዳዮቹ ሁቱዋን ጠቅላይ ሚኒስትር ከገደሉ እኛንስ ከመግደል ምን ያቆማቸዋል?
በነዚያ 24 ሰዓታት የነበረው ረፍት-አልባ ውጥረት ቤተሰቤን ጎዳው፡፡ እናቴ በደመ-ነፍስ ከክፍል ክፍል እየተዘዋወረች የነበረንን ማንኛውንም ሻንጣ እጇ በገቡላት እቃዎች ትሞላለች፡፡ ‹‹በስንት ልፋት ያሟላኋቸውን እቃዎች ሰዎች እንዲዘርፏቸው ትቼ አልሄድም›› አለችን፡፡ ‹‹አርቄ እደብቃቸዋለሁ፡፡ እንድ ቀን ተመልሰን እናገኛቸዋለን፡፡››
ወዴት ለመሄድ እንዳቀደች አላወቅሁም፡፡ ብቸኛው ሊያስኬደን የሚችለው የማምለጫው መንገዳችን (የኪቩ ሐይቅን አቋርጦ) በኢንተርሃምዌ ታጣቂዎች እንደተዘጋ ሰምተናል፡፡ ወደ ሐይቁ የሚጠጋን ማናቸውንም ቱትሲም ሆነ ለዘብተኛ ሁቱ በመግደል ላይ ናቸው፡፡
አባቴ በግራ መጋባት ነባራዊውን ሁኔታ ሊያምን አልቻለም፡፡ ‹‹ግድያው ከቀጠለ ሩአግ ሊያቆመው ጣልቃ ይገባል፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ እዚህ ይመጡና ያድኑናል›› ሲል ግምቱን ይነግረን ጀመር፡፡
ለማመን ተቸግሬ ‹‹አባባ ምን እያሰብክ ነው›› ስል ጠየኩት፡፡ ‹‹የሩአግ ወታደሮች ገና በስተሰሜን በዩጋንዳ ድንበር አቅራቢያ ናቸው፡፡ ተሽከርካሪ ስለሌላቸው በእግራቸው እየተጓዙ ጦሩንና ኢተርሃምዌን መዋጋት ግድ ይላቸዋል፡፡ እዚህ ለመድረስ ሳምንታት ይፈጅባቸዋል … ከነጭራሹ እዚህ መድረስ መቻላቸውንስ ማን ያውቃል!››
ከአባቴ ጋር የተከራከርኩባቸውን ውሱን ጊዜያት መጥቀስ እችላለሁ፤ ያለወትሮዬ መሟገቴ ሁሉም ነገር በመቀያየር ላይ በመሆኑ ነው፡፡ ወላጆቼ በትክክል እያሰቡ አይደለም፤ ኦገስቲንና ቪያኒም ልጆች ስለሆኑና ስለተደናገጡ ሊታመንባቸው አይችልም፡፡ በሕይወቴ ሙሉ የዳማሲንን መርህ እከተላለሁ፤ አሁን ግን ወደ ክፍሉ አፈግፍጎ ግድግዳ ላይ አፍጥጧል፡፡
ፈልጌው ወደ ክፍሉ እንደገባሁ ‹‹እስኪ እንዲያው የምታስቢውን ሳትደብቂ ንገሪኝ፤ ይችን ቀን የምናልፋት ይመስልሻል?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ይኸውልሽ በመጪው ዓመት የማደርገውን ነገር ተኝቼ ለማለም እየሞከርኩ ነው፤ ግን አልሆነልኝም፡፡ በሕይወት የምኖር አይመስለኝም፡፡ የወደፊት ሕይወት የለኝም፡፡››
‹‹ዳማሲን ከዚህ ነገር ውስጥ እንደምንም መውጣት አለብህ!›› ስል ጮህኩበት፡፡‹‹ትግሉን ገና ሳትጀምር ተስፋ መቁረጥ የለብህም!›› አንተ በመጭው ዓመት ምን እንደምትሠራ ማየት ካልቻልክ እኔ እችላለሁ! ከዩኒቨርሲቲ ስመረቅ ቡታሬ እኔ ጋ ትመጣለህ፡፡ ዲፕሎማዬን ስቀበል በፊት ወንበር ተቀምጠህ እያጨበጨብክ በደስታ ትጮሃለህ፡፡ ስለዚህ አሁን ተነሥና እነእማማን አግዛቸው!››
‹‹ምናለ ያንቺ እምነትና ጽናት ቢኖረኝ›› ብሎ ተነፈሰና መልሶ ግድግዳውን አተኩሮ ያይ ገባ፡፡
እኔ ብርታቱ ባይኖረኝም አንድ ሰው መልሶ ቤተሰቤን ማረጋጋት አለበት፡፡ ቤተሰቡ በለየለት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ እንዳይገባ ለመበርታትና ቢያንስ ጠንክሬ ለመሥራት ሞከርኩ፡፡
ለጠቅላይ ሚኒስትሯ ጥበቃ ያደርጉ የነበሩ አሥር ቤልጅየማውያን የተመድ ሰላም አስካባሪዎች በመንግሥት ወታደሮች እንደተገደሉና በሩዋንዳ የሚኖሩ የቤልጅዬም ዜጎች ሁሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ምሽት ላይ ሰማን፡፡ ቤልጅዬማውያኑና የሌሎች ሀገር ዜጎች አገሪቱን ለቀው ከወጡ ይህን የለየለትን ጭፍጨፋ ለማስቆም ዐቅሙ ያለው ሌላ ማንም ሊኖር እንደማይችል እናውቃለን፡፡ በዚህ ምሽትም ስላልተኛን ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሁላችንም እንቅልፍ አጣን ማለት ነው፡፡

ንጋት ላይ ጩኸት ይሰማን ጀመር፡፡
👍1
#ሁቱትሲ


#ክፍል_ሰባት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#ልጆቹን_ስሰናበት

ዳማሲን ከመሄዱ የቄሱ ግቢ የፊት በር ተንኳኳ፡፡ ያንኳኳው የቪያኒ የሁለተኛ ደረጃ መምህር የሆነው ንዚማ ሲሆን አመጣጡም ቄስ ሙሪንዚን ፈልጎ ነው፡፡ የሹክሹክታ ንግግር ከተደረገ በኋላ በሩ ተዘጋ፡፡ ወጥቼ ንዚማን በቄሱ ዛፍ ጥላ ስር ተቀምጦ አገኘሁት፡፡ በዚያ ደብዘዝ ባለው ብርሃንም ቢሆን በፊቱ ላይ የሚነበበውን ህመም ማየት አይከብድም፡፡
እንደፈራ ልጅ አድርጎታል - ‹‹ምን ያደርጉናል? የሚገድሉን ይመስልሻል?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡
በሩ ጋ መምጣቱን እንደሰማሁ በራስ ወዳድነት ስሜት ተውጬ የማበረታቻ ቃላት ይሰነዝርልኝና ጥንካሬ ይለግሰኝ ዘንድ ተመኝቻለሁ፤ ግን እርሱ ነው ሁለቱንም ላያገኛቸው ይሻቸው የያዘው፡፡
መምህር ንዚማ ሚስትና ልጆቹ ራቅ ባለ መንደር አማቱን ሊጠይቁ ሄደዋል፡፡ ደኅና ስለመሆናቸው ምንም የሚያውቅበት መንገድ ስላጣና ጥርጣሬ ስለገባው ተሰቃየ፡፡ ‹‹የማልተዋቸው ህልሞች አሉኝ›› አለ፡፡ ‹‹ሚስቴና ልጆቼ ሲታረዱና እፊቴ ሲቆራረጡ ይታየኛል፡፡ ይህን ለማስቆም እንደምታዪኝ ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ በአሁኑ ሰዓት እኮ ተገድለው መንገድ ላይ ተጥለው ነው የሚሆነው፡፡›› በቻልኩት መጠን ላጽናናው ሞከርኩ፤ ግን ምን ልለው እችላለሁ? እኔ ራሴ እርግጠኛ ባልሆንኩበት ሁኔታ ነገሮች ጥሩ ሊሆኑ እንደሚችሉ ስንት ጊዜ ልናገር?
በጣም አቃሰተና ‹‹የት አባቴ ልግባ? ውጪ ያለው ሁሉም ሰው ገጀራ ይዟል፤ ጠመንጃ የያዙም አይቻለሁ፡፡››
‹‹ግድያው እስኪያቆም ድረስ እዚህ ቆያ፤ ከዚያም ከቤተሰብህ ትገናኛለህ›› አልኩት መንፈሱን ለማረጋጋት፡፡
ራሱን ነቅንቆ ቆመና ‹‹ልጄ፣ እዚህ አልቆይም፤ ሌላ የምሄድበት ቦታም የለኝ፡፡››
‹‹እጸልይልሃለሁ፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ ኢማኪዩሌ፡፡››
ተሰናብቶኝ ቄስ ሙሪንዚ ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ቤቱ ፊት ለፊት ሄደ፡፡ ቄሱ ንዚማን እንደማይሸሽጉት ነግረውት ሳይሆን አይቀርም በሩን በእጃቸው ሲያመላክቱት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ወጣ፡፡ በኋላ እንደሰማሁት ይህ ምስኪን ሰው ተቆራርጦ የተገደለው ከቄሱ ቤት ጥቂት መቶ ሜትሮች ርቆ ባለ መንገድ ላይ ነው፡፡ ከተወሰኑ ሰዓታት በኋላ ብቻዬን በተቀመጥኩባት በአንዲት ትንሽ መኝታ ክፍል ቄስ ሙሪንዚ ሌሎች አምስት ቱትሲ ሴቶችን በጸጥታ አስገቡ፡፡ ሁሉም የአካባቢያችን ሰዎች እንደሆኑ ባውቅም አንዳቸውንም በደንብ አላወቅኋቸውም፡፡ ሴቶቹን ወደ ክፍሏ ሲያመጧቸው ቄሱ ተደናግጠዋል፡፡ ‹‹ፍጠኑ፣ ፍጠኑ!›› የሚንሾካሾኩት በጣም በፍጥነት ስለሆነ ልንሰማቸው አልቻልንም፡፡ ‹‹እዚህ ጠብቁኝ፤ ታዲያ ደሞ ዝም በሉ እሺ›› አሉን በሩን ዘግተው ሲወጡ፡፡ አብረን የነበርነው ስድስት ቱትሲ ሴቶች ከሞላ ጎደል እርስ በርስ የማንተዋወቅ ቢሆንም ሁለት ነገሮች ግን ያመሳስሉናል - እየታደንን መሆናችንና የምንደበቅበት ምንም ስፍራ የሌለን መሆኑ፡፡ ለመናገርም ሆነ ለመተዋወቅ በጣም ፈርተን እርስ በርሳችን እየተያየን ቆመናል፡፡ ውጪ ምን እየተከሰተ እንዳለ አናውቅም፣ ከቄሱ ድንጋጤ እንደተረዳነው ግን ነገሮች ተበለሻሽተዋል፡፡
ከቤቱ ውጪ ድንገት ጩኸቶች ይሰሙ ጀመር - በእጆቻችን ላይ ያሉትን ጸጉሮች እንዲቆሙ ያደረጉ እጅግ የሚያስጨንቁ የሲቃ ጩኸቶች፡፡ ከዚያ በኋላ አሰቃቂዎቹ ንዴት የሚንጸባረቅባቸው ድምጾች መጡ፣ ‹‹ግደሏቸው! ግደሏቸው! ሁሉንም ግደሏቸው!››
ብዙ መጯጯህና የድረሱልኝ ጥሪ ይሰማል፤ ‹‹ግደለው! ግደሉት! ግደላት!›› የሚልም ድምፅ ይከተላል፡፡
ፈራን፡፡ ከሴቶቹ አብዛኞቹ መሬት ላይ ተኙ፣ አልጋም ስር ተደበቁ፡፡ በጣም ከመንዘፈዘፌ የተነሣ መሬቱም ጭምር የሚንቀጠቀጥ መሰለኝ፡፡ ዓይኖቼ ቤቱን መደበቂያ ፍለጋ ሲያስሱ በኮርኒሱ ላይ ባለች አንዲት ቀዳዳ ላይ አተኮሩ፡፡
‹‹እዚያ ላይ መደበቅ እንችላለን›› አልኩ ወንበር ወደ ቀዳዳዋ ስር እየሳብኩና በእጆቼ ወደላይ እየተንጠራራሁ፡፡ አንዷን ሴትዮ ወደ ላይ ስቤ አወጣኋት፡፡ ሁለታችን ደግሞ አንድ ላይ ሌሎቹን በቀዳዳዋ ሽቅብ ሳብናቸው፡፡ ከዚያም ቄሱን እስኪመለሱ እንጠብቃቸው ያዝን፡፡ በዚያች በተጨናነቀችና በምታፍን ቦታ ልብሶቻችን በላብ እስኪጠመቁና አየር እስኪያጥረን ድረስ ጭብጥ ብለን ተቀመጥን፡፡ ቄስ ሙሪንዚ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ተመልሰው በቤቱ መካከል ቆመው ራሳቸውን በግራ-ግባት ያኩ ገቡ፡፡
‹‹የት ይሆኑ? አይ አምላኬ እዚህ ነበር የተውኳቸው!››
በጣም ባልፈራ ኖሮ ሳቄን እለቀው ነበር፡፡ በቀዳዳዋ ራሴን አውጥቼ ‹‹እዚህ ነን!›› ስል አንሾካሾክሁ፡፡
ቄሱ ራሳቸውን ነቅንቀው ሊያናግሩን መፈለጋቸውን ገልጸውልን ወዲያውኑ እንድንወርድ አዘዙን፡፡ ፊታቸው አሁንም በጣም እንደተቸገሩ ያስታውቃል፡፡ ‹‹ሁላችሁም እንደፈራችሁ አውቃለሁ፤ በእርግጥ ልትፈሩም ይገባችኋል›› አሉን፡፡ ‹‹ውጪ ላይ ነገሩ ሁሉ ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል፡፡ ገዳዮቹ በሁሉም ሰው ቤት እየዞሩ ነው፡፡ ዛሬ እኔ ቤት አልመጡም፤ በማናቸውም ሰዓት ግን ሊመጡ ይችላሉ፡፡ እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ምን እንደማደርጋችሁ አላውቅም… እስኪ ላስብበት፡፡››
ፍራቻችንን አይተው ወዲያውኑ መፍትሔ አመጡ፡፡ ‹‹አይዟችሁ አላስወጣችሁም›› ሲሉ አረጋገጡልን፡፡ እስኪ በጥሞና አዳምጡኝ፡፡ ነገ ሲነጋጋና ማንም ከመኝታው ሳይነሳ ግድያው እስኪያቆም ድረስ ወደምትቆዩበት አንድ ሌላ ክፍል እወስዳችኋለሁ፡፡ በቤቱ ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዳስወጣኋችሁ እነግራቸዋለሁ፡፡ የእናንተን እዚህ መኖር የማውቀው ብቸኛ ሰው እኔ ብቻ እሆናለሁ፡፡ ተራ ሐሜት እንኳን ሁላችንንም ሊያስገድለን ይችላል፡፡ እነዚህን የግድያ ዘመቻዎች ካሁን በፊት አይቻቸዋለሁ - አንዴ የደም ጥማቱ ከጀመረ ማንንም አታምኑም፣ የራሳችሁንም ልጆች ሳይቀር፡፡ አንድ ሰው ካገኛችሁ አለቀላችሁ! ስለዚህ በእግዚአብሔር ደማችሁ በቤቴም ሆነ በጄ እንዲፈስ አልፈልግም፡፡››
ከዚያ ቄሱ ወደኔ ዞረው እንደ ቢላዋ የቆረጡኝን ቃላት ነገሩኝ - ‹‹ወንድምሽና ጓደኛው እዚህ መቆየት አይችሉም፡፡ አሁኑኑ ሄደው ሕይወታቸውን ያትርፉ፡፡ ወንዶችን ማስጠለል ለኔ በጣም አደገኛ ነው፡፡ እንደምታዪው እናንተ ሴቶቹም በዝታችሁብኛል፡፡››
በሙሉ ዓይናቸው ሊያዩኝ አልቻሉም - ቪያኒንና ኦገስቲንን በዚያ ሰዓት ማባረሩ በእርግጠኝነት ማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ወደ ሞታቸው መላክ ማለት እንደሆነ ሁለታችንም እናውቃለን፡፡
‹‹እንዴ! ቄስ ሙሪንዚ ኧረ እባክዎት! እንዴት -››
ጸጥ በይ በሚል ዓይነት ምልክት ጣታቸውን ከንፈራቸው ላይ አድርገው ንግግራችንን ቋጩት፡፡ ‹‹መሄድ አለባቸው፣ ኢማኪዩሌ፡፡ ልወስዳችሁ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ስመጣ ወደ በሩ ወስደሽ ታስወጫቸዋለሽ፡፡ ታዲያ ማንም እንዳያይሽ ተጠንቀቂ፡፡››
ቄሱ ቤቱን ለቀው ሲሄዱ በሹክሹክታ ረገምኳቸው፡፡ ለኛ ከለላ በመስጠት እንደ ቅዱስ እየሰሩ እንዴት እንደገና ተገልብጠው ወንድሜንና ኦገስቲንን ወደ ገዳዮቹ እጆች ያስገቧቸዋል?
እያዳኑን የነበሩትን ሰው ልቆጣቸው አልፈለግሁም፣ ቢሆንም ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም - የባሰውንም ጠረጠርኩ፡፡ በሌሎች የግድያ ዘመቻዎች አንዳንድ የሁቱ ወንዶች ወንድ ቱትሲዎችን ትተው ሴት ቱትሲዎችን
👍1
#ሁቱትሲ


#ምዕራፍ_ስምንት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#ቁጣዬን_ስጋፈጥ


በአንጻራዊ መረጋጋት በርካታ ቀናት አለፉ፡፡ አልፎ አልፎ ገዳዮቹ ውጪ ላይ የእብድ መዝሙራቸውን ሲዘምሩ እንሰማቸዋለን፡፡ ቀኑን ሙሉ በጽሞና እንጸልያለን፤ እርስ በርሳችንም በምልክት ቋንቋ እንግባባለን፡፡ ከሞላ ጎደል በየ12 ሰዓታቱ የተወሰኑ ተናፋቂ የሰውነት ማፍታቻዎችን እናደርጋለን፡፡ ከዚያ በስተቀረ ቀንና ሌሊት በአንድ ቦታ በመቀመጥ እንቅስቃሴዎቻችንን በተቻለን መጠን እንገድባለን፡፡ መጸዳጃ ቤቱን በቄስ ሙሪንዚ ትዕዛዝ መሠረት ውሃ እንለቅበታለን፡፡ ይህም ሌላ ሰው በዋናው ቤት ውስጥ ያለውን ሌላውን መጸዳጃ ቤት ውሃ ሲለቅበት መሆኑ ነው፡፡ መጸዳጃውን መጠቀሙ ፈተና ሆነብን፡፡ ስፍራው በቂ ስላልሆነ የምትጠቀመው ሰው ከእብነበረድ በተሰራው መጸዳጃ ላይ ቁጢጥ ለማለት ትገደዳለች፤ ስለሆነም አንደኛችን ስንጸዳዳ ሁላችንም ቦታ መቀያየር አለብን፡፡ ያም ድምፅ የማሰማትና በገዳዮቹ የመገኘት አደጋን ጋርጦብናል፡፡
ባልተለመደ ሁኔታ በመታጠቢያ ቤቱ በቆየንበት ጊዜ ማንም መጸዳጃውን ሲጠቀም ማየቴን አላስታውስም፡፡ መጸዳጃው ከእብነበረድ የተሠራና እላዩ ላይ አስቀምጦ የሚያጸዳዳው ዓይነቱ ነው፡፡ ያለው በዚያች ትንሽ ቦታ መካከል ቢሆንም ሽታው ያስቸገረኝ ወቅት ትዝም አይለኝ፡፡ የወር አበባችንም ይደርሳል፤ ያንዳችን ሲሄድ የሌላችን ከተፍ ይላል፡፡ በመሆኑም ቄሱን ተጨማሪ የንጽሕና መጠበቂያ ወረቀት አምጡ እያልን እናስቸግራቸዋለን፡፡ ማንኛችንም ብንሆን ባለው ሁኔታ አንሸማቀቅም፤ እነዚህን ሁኔታዎች ረስተናቸዋል፤ የብቸኝነትም ጥሩ ጎኖች ትዝ አይሉን፤ በተለይ ይህ ችግር በሕይወት ከመኖራችን አንጻር ሲታይ ከግምት ውስጥ አይገባምና፡፡
ቄሱ ምግብ ይዘው በመጡ ቁጥር እንበላለን - የሚያመጡልን አልፎ አልፎ ቢሆንም፡፡ አንዳንድ ቀንማ ያለ ሌሊት 9 ወይንም 10 ሰዓት አይመጡም፡፡ (ሊያዩን ወይንም ምግብ ሊያመጡልን በፈለጉ ቁጥር ቁምሳጥኑን ገፍተው ይገባሉ፡፡ ሁልጊዜ ግን ሌላ ሰው እንዳይሰማቸው በጣም ይጠነቀቃሉ፡፡ ከቁምሳጥኑ ሲንቀሳቀስ ድምጹን ለማፈን የሚሆን ጨርቅ ከስሩ ተደርጎበታል፡፡ በዚህም እግዚአብሔር እንደገና ይጠብቀን ይዟል፡፡) ተጨማሪ ምግብ ቢያዘጋጁ ሌላ ሰው እንዳያውቅባቸው የልጆቻቸውን ትርፍራፊ ወይንም ሠራተኞቻቸው የሚበሉትን አሸር ባሸር ያመጡልናል፡፡ አንዳንዴ ምንም ብንራብም አንበላም እንላለን - የሚሰጡን የአሳማ ምግብ ይመስላላ፡፡ (እቤቴ ምን ዓይነት ምግብ አማራጭ እንደነበርኩ በማስታወስ በራሴ ላይ እሥቃለሁ፡፡) የምንጠጣውም ውሃ ይመጣልናል፡፡

የማይቻል ቢመስልም ከቀናት ጸጥታ በኋላ ትንሽ ዘና አልን፡፡ ያለንበትን ሁኔታ የሚያስታውሱን ቄሱ ብቻ ናቸው፡፡
አንድ ሌሊት ቄሱ መጥተው ገዳዮቹ ባቅራቢያችን ከቤት ወደ ቤት በመዘዋወር ቤቶችን እየፈተሹ ያገኙትን ቱትሲም እየገደሉ እንደሆነ ነገሩን፡፡ ‹‹በተወሰኑ ደቂቃዎች ውስጥ ሊመጡ ይችላሉ፤ ምናልባትም እስከ ነገ ወይንም ከነግወዲያ ድረስም ላይመጡ ይችላሉ፡፡ በእርግጠኝነት ግን ይመጣሉ፤ ስለዚህም ዝም በሉ›› ሲሉ አስጠነቀቁን፡፡ በዚያች መታጠቢያ ቤት ውስጥ ትንሽ የአእምሮ ሰላም ለማግኘት የነበረን ተስፋ ተነነ፡፡ ስለገዳዮቹ መመለስ ያደረብን ሥጋት አዕምሯዊና አካላዊ ውጋት ሆነብን፡፡ ወለሉ ላይ ድምፅ በሰማሁና ዉሻ በጮኸ ቁጥር አንድ ሰው በስለት እንደወጋኝ ይሰማኛል፡፡ በአንዴ መተኛት የምንችለው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ስለሆነ ቆዳዬ መድረቅና መላጥ አመጣ፡፡ ሁልጊዜም የማይተወኝ ራስ ምታትም ይዞኝ ተቸገርኩ፡፡ የአእምሮ ሥቃዬማ እንዲያውም በጣም ያይላል፡፡ በሃሳቤ ወጥመድ ውስጥ ብቻዬን እሰቃያለሁ፡፡ ከደረስኩ ጀምሮ የሚያስቸግሩኝ ጽኑ ፍርሃቶችና ቅዠቶች በልቤ ውስጥ እየተመላለሱ የእምነቴን መሠረት አናጉት፡፡ ገዳዮቹ ድምጻቸው ለኛ በሚሰማን ርቀት ሲጠጉ ሐሳቤ ከፈጣሪ ራቀና በአሉታዊው ሐሳብ ተጠመድኩ፡፡ በጸለይኩ ቁጥር ግን ወዲያውኑ ፍቅሩን አገኘዋለሁ፤ ስጋቴም ይቀልልኛል፡፡
ስለዚህ ሌሊት ከ10 ወይም 11 ሰዓት ጀምሬ በማንኛዋም እንቅልፍ ባልያዘኝ ሰዓት ለመጸለይ ወሰንኩ፡፡ ሁልጊዜ የመጀመሪያ ጸሎቴ የቄሱ ቤት ስለተሠራልንና በዘር ጭፍጨፋው ወቅት ስለተጠለልንበት አምላክን ማመስገን ነው፡፡ ከዚያም የቤቱ ንድፍ-አውጪ ከተጨማሪ መታጠቢያ ቤት ጋር እንዲነድፈው ስላደረገው፣ ብሎም ለቄሱ የኛን መደበቂያ ስፍራ መሸፈኛ የሚሆን ልከኛ ቁምሣጥን እንዲገዙ ስለገፋፈ
ወቸው አመሰግነዋለሁ፡፡
ከመጀመሪያው የምስጋና ጸሎቴ በኋላ በመቁጠሪያዬ መጸለይ እጀምራለሁ፡፡ ጸሎቶችን በቀዮቹና ነጮቹ ዶቃዎች አደርሳለሁ፡፡ አንዳንዴ በጣም ስለምጸልይ ያልበኛል፡፡ ሰዓታትም ያልፋሉ… ዶቃዎቹንና ጸሎቴን ስጨርስ የምወዳቸውን
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በማለት ‹‹እረፍት›› አደርጋለሁ፡፡ እምነቴ በአደጋ ላይ እንደወደቀ ስለማስብ ከማርቆስ ወንጌል የማስታውሳቸውን ስለ እምነት ጉልበት የሚያወሱ ሁለት ጥቅሶች በመደጋገም ሰዓታትን አሳልፋለሁ፡፡ መጀመሪያ ይህ ነው - ‹‹ስለዚህም እላችኋለሁ፣ አምናችሁ ብትፀልዩ የምትለምኑትን ሁሉ ታገኛላችሁ፤ ይሆንላችሁማል›› (ማርቆስ 11፡ 24)፡፡ ከዚያም ሌላውን እላለሁ - ‹‹እውነት እላችኋለሁ፣ ይህን ተራራ ተነሥተህ ወደ ባህር ተወርወር ብትሉት፣ በልባችሁም ባትጠራጠሩ፣ ብታምኑም እንደተናገራችሁት ይሆናል›› (ማርቆስ 11፡23)፡፡ ሳልጸልይና ስለ እግዚአብሔር ሳላስብ የማሳልፋት ጥቂት ደቂቃ እንኳን ብትኖር ሰይጣን መንታ ጫፍ ባለው የጥርጣሬና በራስ የማዘን ቢላዋው ይወጋኝ ዘንድ መጋበዝ ይሆናል፡፡ ጸሎት መከላከያዬ በመሆኑ ልቤን አጥብቄ እጠቀልልበታለሁ፡፡

ቄሱ ሁልጊዜ ያልሆነ ስህተት ሰርተን ድምፅ እንዳናሰማ ይፈራሉ፡፡ ስለሆነም ወደ መኝታ ክፍላቸው ሰው የሚያመጡት እጅግ አልፎ አልፎ ነው፡፡ አንዳንዴ ግን ከልጆቻቸው አንዷ ወይንም አስተናጋጃቸው ሊጠይቋቸው ሲመጡ እስኪሄዱ ድረስ እንደነዝዛለን፡፡ እዚህ ከመጣን ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ ቄሱ ከልጃቸው ከሴምቤባ ጋር ሲያወሩ ሰማናቸው፡፡
‹‹አባባ፣ ስለዚህ ግድያ ምን ትላለህ? ጥሩ አይመስልህም - እኛ ሁቱዎች ማድረግ ያለብን ትክክለኛው ነገር አይመስልህም? ማለቴ በትምህርት ቤት ሲያስተምሩን ከመቶዎች ዓመታት በፊት ቱትሲዎች በእኛ ላይ ተመሳሳይ ነገር አድርሰዋል፤ ስለዚህ እያገኙት ያለው ነገር ይገባቸዋል አይደል?››
‹‹ሴምቤባ ስለምን እያወራህ እንደሆነ አታውቅም፡፡ በል ተወኝ አሁን፤ ልተኛበት›› ሲሉ መለሱ ቄሱ፡፡
‹‹ቱትሲዎች ሲባሉ ሁልጊዜ የበላይ ነን ብለው ያስባሉ… ሁሌ ሁቱዎችን ዝቅ አድርገው ያዩናል፡፡ ዛሬም ድረስ ሥልጣን ላይ ቢሆኑ ኖሮ አሁን እየገደሉን አይሆንም ነበር? ስለዚህ እነርሱን መግደል ራስን መከላከል ነው፣ አይደለም?›› ድምጹ በጣም በመጉላቱ ሴምቤባ ቁምሳጥኑ ጎን እንደቆመ መገመት እችላለሁ፡፡ የቁምሳጥኑንም መንቀሳቀስ ያውቅብናል ብዬ በጣም ተሸበርኩ፡፡ እንደፈራሁም ቢሆን ተነሥቼ ልጩህበት የሚለውን ሃሳቤን መቋቋም ነበረብኝ - ቃላቱ በጣም አናደዱኝ፡፡ ይህን ለቱትሲዎች ያለውን ንቀት የተማረው በትምህርት ቤት እንደሆነ ስለማውቅና እኔም እዚያ ትምህርት ቤት ስለተማርኩ ለድንቁርናው ብቸኛው ተጠያቂ እንዳልሆነ ይገባኛል! ወጣት ሁቱዎች ከልጅነታቸው ጀምሮ ቱትሲዎች የበታችና
👍2