አትሮኖስ
283K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
494 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ


#ፍሰሀ
===
እየጎተትኳት መኪናው ጋር ስንደርስ ቀጥ አልኩ…ለካ የመኪናዬን ቁልፍ አልያዝኩም ‹‹ሶሪ ፊናን ሁለት ደቂቃ››
‹‹ምነው››ግራ ገብቷት
‹‹የመኪና ቁልፍ ይዤ መጣሁ…››በማለት እዛው ጥያት በሶምሶማ ወደ መኝታ ቤቴ ሄድኩ…እመቤቲቱን እዳልቀሰቅሳ በቀስታ ከፍቼ ገባውና ወደ ኮመዲኖ ሄጄ የመኪናዬን ቁልፍና ሞባይሌን በቀስታ አንስቼ በዝግታ እየተራመድኩ ልወጣ በራፍ አካባቢ ስደርስ ‹‹ማሬ ››የሚል ድምጽ ወደ ኃላዬ እንድዞር አስገደደኝ..
‹‹ተነሳሽ እንዴ? ››
የተጨናበሰ አይኗን በእጆቾ እያሻሻች ‹‹አዎ ..ወዴት ነው…?››አለቺኝ
እየተንደረደርኩ ወደውስጥ ተመለስኩና ግንባሯን ስሜ ‹‹መጣው ተኝተሸ ጠብቂኝ..ወይንም እታች ወርደሽ ቁርስ መብላትም ትቺያለሽ››
‹‹እንዴ ምን ማለትህ ነው..? ምትሄድበት ቦታ አብሬህ እሄዳለው..አምስት ደቂቃ ጠብቀኝ……››
‹‹አይ ምን አስቻኮለሽ ..ዘና ብለሽ ተነሽ…ብዙም አልቆይም መጣው….››እልኳትና መልሷን ሳልሰማ ተንደርድሬ ወጣሁና በራፍን መልሼ በላይዋ ላይ ዘግቼባት እየተንደረደርኩ የሆቴሉን ደረጃ በመውረድ ወደምትጠብቀኝ አስደማሚዎ ፊናን ተመልሼ ሄድኩ….
ስደርስ‹‹እኔስ ሚስትህ አፍና አስቀረችህ ብዬ ወደ ክፍሌ ልመለስ ነበር››በሚል ሽርደዳ ተቀበለቺኝ
‹‹አይ ተርፌያለው›› አልኩና መኪናዋን ከፍቼ እሷን አስቀድሜ በማስገባት ዞሬ መሪውን በመጨበጥ ግቢውን ለቀን ወጣን… አስፓልቱን እንደያዝን ….‹‹ወዴት እንደምትወስደኝ ለማወቅ ጓጉቼለው››አለቺኝ
‹‹ይገርምሻል በጫወታሽ በመማረክ ከአንቺ ጋር ተጫማሪ የብቻችን ጊዜ ለማሳለፍ ስለፈሉኩ እንጂ ወደየት እንደምወስድሽ ምኑንም አላውቅም…››አልኳት…እውነትም በዚህ ጥዋት ለዛውም በለሊት ልብሷ ያለች ሴት ወዴት ይዣት ልሄድ እንደምችል ምኑንም አላውቅም…ሳቋን ለቀቀችው..ስትስቅ በጣም ታምራለች…ኪሊዬፓትራም ስትስቅ እንዲህ ታምር ነበር እንዴ ..?እሷም ስትስቅ የጁሊዬስ ቄሳር እና የማርክ አንቶኒዬን ልብ አሁን የእኔ ልብ ቀጥ እንዳለው ቀጥ ይልባቸው ነበር እንዴ…‹‹አንተ ይሄ ጥሩ ስነ-ምግባር ነው…?››አለቺኝ በትዝብት
‹‹እንዴት ምን አጠፋው?››ግራ ገብቶኝ ጠየቅኳት
‹‹ አንተን ብላ ኪሎ ሜትር አቋርጣ አምናህ የመጣችውን ፍቅረኛህን መኝታ ቤት ውስጥ ዘግተህባት ከሌላ ሴት ጋር ለብቻችን ሆነን ማውራት አማረኝ በሚል ተቀባይነት በሌለው ምክንያት እንዲህ ማድረግህ?››
‹‹በነገርሺኝ ታሪክ ነው የተማርኩት…ኪሊዬፓትራ ያፈቀሩት ሁለቱም ጀግኖች ባለትዳር ነበሩ..በእሷ ፍቅር ሲሸነፍ ትዳር ስላለን ይቅርብን አላሉም፡፡››
‹‹ጥሩ ተማሪ ነህ..ክፍ ክፉውን ብቻ መርጠህ አዕምሮ ውስጥ አስቀረህ….ደግሞ ፍቅር ያዘህ እንዴ?››
መኪናውን ዝም ብዬ በሰርክል አድርጌ ወደ ሆራ መስመር እየነዳውት ነው…
‹‹ማ እኔ ካንቺ ፍቅር…?››
‹‹አይ ድንገት እንደው ተሳስተህ አፍቅረኸኝ እንደሆነ ብዬ ነው?››
‹‹አይ እንደዚህ አይነት ስህተትማ አልሳሰትም……››አልኳት.
.እውነት አልተሳሳትኩም እንዴ..ካልተሳሳትኩ ታዲያ ምን እንደዚህ ያደርገኛል …?አንዴት ስለእሷ በየሰዓቱ የተዘበራረቀ አይነት ስሜት ሊሰማኝ ቻለ…?. ስታበሳጨኝ ምበሳጭላት ሳታስቀኝ ምስቅላት ምኔ ስለሆነች ነው ..?እራሴን የጠየቅኩትና በርግጠኝነት መልስ ላገኝላት ያልቻልኩት ጥያቄ ነው፡፡ምክንያቱም ከራስ ልብ ውስጥ እውነተኛ መልስ ማግኘት ከአንደበት ቃላት አውጥቶ ለሌላ ሰው ድንገተኛ መልስ እንደመመለስ ቀላል አይደለም፡፡
መከላከያ ኮሌጅ አካባቢ ስንደርስ ስልኬ ተንጫረረ…ሳየው የአባቴ ነው….‹‹ወይ ዳድ ነው የደወለው ማንሳት አለብኝ››አልኩን መኪናዬን ዳር ላይ አቆምኩ...ከምንቆም ቀይሪኝና አንቺ ንጂ ››አልኳትና ስልኩን አንስቼ እያዋራው ከገቢናው ወጥቼ ዞርኩ እሷም ዞረችና መሪውን በመጨበጥ በዝግታ ትነዳ ጀመር …እኔም አዕምሮዬን ሰብስቤ የናፈቀኝን አባቴን ማዋራት ቀጠልኩ….
‹‹እንዴ ዳድ አበዛሀው እኮ…በጣም ነው የናፈቅከኝ››ተነጫነጭኩበት….
‹‹ልጄ እኔም …..በጣም ነው የናፈቅከኝ››
‹‹አይ አይመስለኝም… ብናፍቅህማ ይሄን ያህል እትቆይም….››
‹‹አሁን መምጫዬ ደርሷል..ለመሆኑ ስራው እንዴት እየሄደልህ ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው አባዬ…. በጣም አስደሳች እየሆነ ነው….አሁን ሰራተኛችንም ሆነ ስራውን በደንብ ለምጄዋለው… አንዳንድ ውጤታማ ለውጦችንም ለማድረግ እያሰብኩ ነው››
‹‹አይ አሪፍ ነው…ለመሆኑ ሰራተኞቹ በአንተ ላይ እምነት ያሳደሩ ይመስልሀል….መቼም ታውቃለህ ልጄ የምትመራቸውን ሰራተኞች ቀልብ ማሸነፍ ሳትችል ውጤት ማምጣት አትችልም››
‹‹አዎ ትክክል ነህ ዳድ..ሀላፊዎቹም ሆኑ ተራ ሰራተኞች በጣም ታዛዥና ተግባቢ ናቸው..እርግጥ አልደብቅህም አልፎ አልፎ አልታዘዝ ባዬችና ስርአት የሌላቸው ሰራተኞች አሉ ..እነሱንም የሚገባቸውን ትምህርት የሚሰጥ ቅጣት እየቀጣው ሁሉንም ነገር መቆጣጠር ችያለው››ይሄንን ስናገር በቆረጣ ፊናንን እያየዋት ነው….ምን ያህል ትበሳጫለች የሚለውን ለማየት..በተቃራኒው የሹፈት ሳቅ እየሳቀች እንደሆነ ነው መታዘብ የቻልኩት ፡
‹‹ልጄ ሰራተኞችን በጥበብ ያዝ …ዝም ብለህ ቀጥታ አትላተም…››አባታ ምክሩን ቀጠለ
‹‹አይ አባ …ሁሉን የምታገስ ከሆነም እንዴት ብዬ ነው በሶስት ወር የምትፈልገውን ውጤት ማግኘት የምችለው..በዛ ላይ አንደኛው ወር እያለቀ ነው..››
‹‹ልጄ አሁን የደወልኩልህ ስለዛ ላወራህ ነው…ለዛ የሚሆን ጊዜ የለንም …ስብሰባው ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እንዲደረግ ተወስኗል..››
‹‹ብዥ ነው ያለብኝ….እንኳንም እኔ እየነዳው አልሆነ ….መኪናዋን መንገድን ስቼ ከሆነ ግንብ ጋር እላተም ነበር..
‹‹እንዴ አባ ..በአንድ ወር ምን አይነት ተአምር ልሰራ ነው…እሰከአሁን እኳን ሙሉ በሙሉ የካማፓኒውን አሰራር እና የእያንዳዱን ሰራተኛ ብቃትና ጉድለት አጥንቼ አልጨረስኩም…እነዚህን ነገሮች በጥልቀት ሳላውቅ ደግሞ የካምፓኒው ጥሩ ጎኑንና ለውጥ የሚያስፈልገውን ቦታ ለይቷ ማወቅ ያስቸግረኛል…..በሶስት ወር ምን አይነት የተለየ ነገር ማድረግ እችላለው ብዬ ስጨነቅ ጭራሽ አንድ ወር?፡፡..አልችልም አባ … የእውነት የመጣው ይምጣ እንጄ በአንድ ወር ውስጥ የምትፈልገው ነገር ላሳካው አልችልም ››
‹‹አውቃለው ልጄ..እኔም ያማትችለውን ነገር አድርግ ብዬ ላስጨንቅህ አልፈልግም››
‹‹እና ታዲያ እንሸነፍ…ዕድሜ ልክህን የለፋህበትን ካምፓኒ እጅ ሰጥተን ለሴትዬዋ እናስረክባት…እሷ ለሴት ልጄ ሰጥታ ድርጅታችንን ድምጥማጡን እንድታጠፋው እንፍቀድላት…እንዴ አባዬ አንዴት እንዲህ በቀላሉ ተሸናፊ ሆንክ…?. ህልሜንማ እነዲህ ፍቺ አልባ አታድርገው…››
‹‹ልጄ አሁን መስፈርቱ ተቀይሯል ..አንተም ሆንክ የሴትዬዋ ልጅ የምትወዳደሩት በምታቀርብት ፕሮፕዛል ጥራት እንዲሆን ተወስኗል….ክምፓኒውን በጥልቀት ምን ያህል አውቃችሁታል …ወደፊትስ የት እንዲደርስ ለማድረግ ትችላላችሁ… …በዛ ነው የእያንዳንዳችንን ድምጽ በተለይ ልዩነት የሚያመጣውን የሰውዬውን ድምጽ ማግኘት የምትችሉት››
‹‹እንደዛ ከሆነማ ቀላል ነው…››
‹‹እንዴት ቀላል ነው ልትል ቻልክ.?.››
‹‹እንዴ አባ አንደኛ አሁን በካምፓኒው እንድሰራ እድል በማግኘቴ ምክንያት ብዙ ዕውቀቶችን አግኝቼያለው….ይሄ ደግሞ ለፕሮፖዛሉ በቂ ግብአት እንዳገኝ ያግዘኛል..ሁለተኛ የካምፓኒውን ሀላፊዎች ሆነ ኤክስፐርቶችን ሁሉ ቀኑ እስኪደርስ ድረስ መጠቀም እችላለው፤ ከእነሱ የማገኘው እገዛም ሆነ ግብአት ቀላል አይደለም…ሌላው አስፈላጊወም ከሆን ረዳት
👍7
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ


❤️ፌናን

ህይወትን እንደፈለገው ያሽከረከራት ጀግና ማን ነው….….?ለሆነ የተገደበ ጊዜ አይደለም…ለሆነ ዓመታትም ብቻ ማለቴ አይደለም..የእድሜ ልክ የህይወት ዘመኑን በሙሉ ህይወትን በቁጥጥሩ ስር አድርጎ እያሾራት ያለው ወይንም ከታሪክ ማህደር ውስጥም ቢሆን እደዛ አድርጎ በፈለገው አይነትና ሁኔታ እስከወዲያኛው በመኖር የተሳካለት ማነው…….?አይ ሕይወትማ እንዲህ ልፍስፍስ አትመስለኝም… ፡፡በቃ እንዲህ እንደዋዛ በቀየስንላት መንገድ የምትጓዝ ወይም በቀደድንላት ቦይ የምትፈስ አይደለችም ..::እኛ በእሷ ላይ ባለን ፍላጎት ልክ እሷም ራሷ በእኛ ህይወት ላይ የሆነ መርምረን ልንደርስበት የማንችለው ስውር ሚስጥራዊ ፍላጎት አላትና …እኛ በህይወት ላይ ያለን ፍላጎትና ህይወት በእኛ ላይ ያላት ፍላጎት አንድ አይነት በሚሆንበት ጊዜ መንገዳችንም አንድ አይነት መነሻ እና ተመሳሳይ መዳረሻ ይኖረዋል ….እናም የኑሮ መስመራችን አልጋ በአልጋ የሚባል አይነት ስያሜ ይሰጠዋል..፡፡ይህ ግን ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ የሚከሰት አይደለም ፤የእኛ ፍላጎት እና ህይወት እየፈሰሰችበት ያለበት መስመር ብዙ ጊዜ ተቃራኒ መስመርም ስለሚይዝ ብዙዎቻችን ሁለት ምርጫ እንመራጣለን፡፡ አንድም የራሳችን የውስጥ ፍላጎትና ብቻ በማዳመጥ ሕይወት በተቃራኒው እየተጓዘች እደሆነ ብናውቅም ትግላችንን መቀጠል..ብንቆስልና ብንላላጥም ከዛም እልፎ እስከሞት የሚያደርስ መከራ ቢገጥመንም እስከመጨረሻዋ እስትንፋስ መፋለም …ሌሎቻችን ደግሞ ፍላጎታችንና ከህይወት ተቃራኒ መሆኑን በተረዳን ጊዜ ቆም ብለን በማሳብ እንዴት ነው የእኛ ፍላጎት ውጤታማ የሚሆንበት መንገዱ በዚህ ቢሆንም ህይወት ግን እየወሰደችን ያለው በዚህ ነው…እና ህይወት መንገዷን በእኛ ፍላጎት እስክታስተካክል ድረስ ፍሰታችንን ከእሷ ፍሰት ጋር አስተካክለን እንዴት መጓዝ እንችላለን..….?የእኛ ቀን እስኪመጣ ከእነ አቋማችን መቆየት ስለሚገባን ሳንቆስል ፤ ሳንላላጥና ስንሰባበር ለመቆየት ህይወት እስከ አስገደደችን ድረስ በማፈንፈልገውም መንገድ ቢሆን መጓዝ ብልህነት ነው በማለት ሁለተኛው መንገድ ይመርጣሉ….እና የትኛው ነው የተሸለ ዘዴ ….?የሚለው አጠያያቂ መልስ ነው ያለው….
ህይወትን እንደ ወንዝ ቁጠሩት ..እዛ ወንዝ ከመግባታችሁ በፊት ወንዙ በስክነት የሚፈስ የረጋ መሆኑን ስላያችሁ በቁጥጥራችሁ ውስጥ እደሚሆን ገምታችሁ ለመዋኘት ወደ ውስጥ ትገባላችሁ…ከዛም እንደ እናንተ ፍላጎት ስትፋልጉ ከወንዙ ፍሰት በተመሳሳይ አቅጣጫ በቀላል ጉልበት ወይንም ትንሽ ተጨማሪ ጉልበት በማውጣት ከወንዙ ፍሰት በተቃራኒ ወደላይ እየዋኛችሁ እያላችሁ ድንገት ሳታስቡት ደራሽ ወንዝ እየተስገመገመ ስራችሁ ቢደርስ ምንድነው ምታደርጉት..?ጥያቄው ያ ነው፡፡ በጀመራሁት መንገድ ከፍሰቱ በተቃራኒ መዋኘታችሁን ትቀጥላላችሁ ወይስ አቅጣጫ ትቀይራላችሁ…..?ውሳኔያችሁ በጽናት ወደፊት ለመሄድ ከሆነ ያንን የሚያስገመግም እየተገለባበጠ የሚመጣ ማዕበል እየሰነጣጠቃችሀ ወደፊት የምትቀጥሉበት በቂ ኃይል አላችሁ..? ማዕበሉ ይዞ እያገላበጠ የሚመጣቸውን ግንድና መሰል ባዕድ ነገር ጋር የሚፈጠረውን መጋጨትና መላተም ተቋቁማችሁ ለመዝለቅ ጉዞችሁን ትቀጥላላችሁ ..? ወይስ የትም ይወሰደኝ የትም ቢያንስ ድንገተኛው ደራሽ እስኪቀንስ ድረስ በህይወት መቆየት የምችለው ከፍሰቱ ጋር አብሬ በአንድ አይነት አቅጣጫ ስፈስ ነው፤ለዛም እንዲያግዘኝ አንድ ግንድ ጉማጅ ላይ ተጠምጥሜ የወሰደኝ ድረስ መሄድ አለብኝ ማዕበሉ እስኪቀንስ ወይም ወደ ዳር እስኪተፋኝ መታገስ ነው የሚጠቅመኝ ብላችሁ ያንን ታደርጋላችሁ …...?እንግዲህ በደራሽ ውሃ በሚናጠው ወንዝ መሀከል ሆኖ ከፍሰቱ በተቃራኒ አቅጣጫ መጓዝ መሞከር መጋጋጥን፤ በግንድ መገጨትን ፤ብሎም ሞትንም ጭምር የሚያስከትል ቢሆንም የወንዙ ፍሰትን ተከትሎ መጓዝም የት ድረስ ..?ለምን ያህል ጊዜ..? ይዞን እንደሚጓዝ ስለማናውቅ የማናውቀውና ዓለም፤ የማናውቀው ሀገር ድረስ መጓዝና፤ በማናውቀው ኑሮ ውስጥ ተጠምዶ መጣልን ሊያስከትልብን ይችላል……
ይሄ ሁሉ ምቀበጣጥረው ቸግሮኝ ነው…የቸገረኝ ከዚህ ፍሰሀ ከሚባለው ልጅ ጋር ሳላስበው ቀስ በቀስ እየሰመጥኩበት ያለው ውስብስ ጉዳይ ነው…እርግጥ እኔ እና እሱን ያገናኘችን ህይወት ነች..ምን ማለቴ ነው..? ሁሉንስ ሰው የምታገኛኘውም የምታለያየው ያቺው የህይወት አጋጣሚ አይደለች....?..ለማን
ኛው ከቢሾፍቱ የካማፓኒውን ዓመታዊ በዓል ከተመለስን አስር ቀን አልፎናል…በአስር ቀን ውስጥ ብዙ ነገሮች ሆነዋል…..ያው መቼስ ወደ ስራዬ እንደምመለስ ትገምታላችሁ..አዎ ተመልሼያለው ፡፡ለዛው በተለየ የስራ ዘርፍ…፡፡.አሁን በዋናነት እየሰራው ያለውት ግን እሱ ለረጂም ዓመታት የዚህ ካማፓኒ ስራ አስኪያጅ ለመሆን የሚያስችለውን ድምጽ ለማግኘት እያዘጋጀው ያለውን ፕሮፕዛል በረዳትነት ማገዝ ነው..በረዳትነት ያልኳችሁ እዲሁ ለእሱ ሞራል ነው እንጂ አብዛኛውን ስራ እየሠራው ያለውት እኔው ነኝ..እርግጥ ሙሉ ቀኑን አንዳንዴም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት እና አራት ሰዓት ድረስ ፊት ለፊት ተፋጠን ስንጨቃጨቅ ፤በሀሳብ ስንከራከተር ፤አንዱን ሀሳብ ስናፈርስ ደግሞም ሌላውን ስንገነባ ነው ውለን የምናመሸው……
በዚህ አስር ቀናት ውስጥ ከምነግራችሁ በላይ ተቀራርበናል…ከመቀራረብም አልፈን ተለማምደናል… ተለማምደናል ማለት ግን ምን ማለት ነው…?መለማመድ በጥልቀት ስሜትን መጋራትን የሚያመለክት ቃል ይመስለኛል…የግንባሩን ቋጠር ፈታ አይቼ ምን እየተሰማው እንዳሆነ ማወቅ ችላለው…..ሲፈግግ እንዴት ነው የፈገገው… ..?የሚለውን በማየት የደስታ መፍገግ ነው…....?የሽሙጥ ነው…...?የቅሬታ ነው…...? መተንተን ጀምሬያለው…እሱም እንደዛው ይመስለኛል፡፡ግን ችግሩ የዚህ ነገር ማብቂያው የት ነው የሚለውን መገመት አለመቻሌ ነው…?ለመሆኑ መጨረሻ አለው ወይ..? የሚለውም እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም ….ሁኔታዎች ወደ ወሰዱን ዝም ብለን እንሄዳለን ወይስ ከሁኔታዎች ጋር በመቃረን የየግላችን መዳረሻ በማሰብ እርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እንገባለን….
ይገርማችሆል !!አሁን ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አልፎል… ግን ቢሮ ነኝ ያለውት …እርግጥ አጠገቤ የለም ምንአልባት ወደ መጽዳጃ ቤት መሰለኝ የሄደው…. ወጣ ባለበት ሰዓት ነው እያወራዋችሁ ያለውት… ቆይ ምን እንኳን ለስራ ቢሆንም እስከዚህን ሰዓት ድረስ ስትቆዩ አንቺስ እሺ ይሁን አባትሽን አስረድተሸ ካሳመንሺው ሌላ ችግር የለብሽም… እሱ ግን ፍቅረኛው እንዴት ነው ይሄን ያህል ክፍተት ልትሰጣችሁ የቻለችው..? ካላችሁኝ ስለእሷ ልነግራችሁ የሚገባኝ ነገር አለ….የዛን ቀን ትዝ ይላችሆል አይደል....?ከእሱ ጋር ስንቀዠቀዥ በለሊት ልብሴ ተያይዘን የወጣን ቀን…ተመልሰን ሆቴላችን ስደርስ ሶስት ሰዓት ሆኖ ነበር…መኪናውን በስርዓት አቁመን ወርደን ጎን ለጎን ወደመኝታ ቤታችን እየሄድን ሳለ ፍቅረኛ የሆቴል በረንዳ ላይ ሆና ስጠብቀን ነበር ላካ..ተንደርድራ ፊታችን ገጭ…. ገና ወደ እኛ እየተንደረደረች ስትመጣ ሳያት ሁኔታዋ ጥሩ እንዳልሆነ ስለተረዳውና ስለከበደኝ ቶሎ ብዬ በፍቅራኛዋና በእኔ መካከል ያለውን ክፍተት ፈንጠር ብዬ በማስፈት እርምጃዬን ሽሽት በሚመስል መልኩ ሳራዝም …..አጅሪት እሱን ጥላ ወደእኔ በመንደርደር ፊቴ ገጭ ብላ አስቆመችኝ…
‹‹ምነው የወንድ ችግር አለብሽ እንዴ..?››ቀጥታ እንዲሁ ነው ያለቺኝ
‹‹ምን እያልሽ ነው..?››
‹‹በውድቅት ለሊት ፍቅረኛዬን ከጉያዬ ሰርቀሽ በመውሰድ ለምነሽ
👍1
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ


#ፍሰሀ
===
መቼስ ያለውበትን ሁኔታ በጥቂቱም ቢሆን ግንዛቤው ይኖራችሆል ብዬ አስባለው፡፡ለዚህ ለዓላማዬ መሳካት ቁልፍ ለሆነው የፕሮፖዛል ዝግጅት ሙሉ ጊዜዬን ሰጥቼ ጠብ እርግፍ እያልኩ ነው….በሌላ ጎን ደግሞ ይህቺ ፌናን የምትባል ልጅ እራሷን የቻለች የቤት ስራ ሆናብኛለች፡፡በቃ የሆነ ነገር ሳታውቁት ከቁጥጥራችሁ ውጭ በሆነ ስሜት ስተት ብሎ ከደምስራችሁ ጋር በመስረግ በመላ ሰውነታችሁ ጋር ተዋህዶባችሁ ያውቃል…በቃ ልቤ ላይም ፤ አዕምሮዬ ውስጥም፤ እታች የእግሯቼ ጥፍሮች ላይም በእኩል መጠን ያለች ነው የሚመስለኝ..፡፡እንደእዚህ እንዴት ሆነ ……?አላውቅም….፡፡በቃ አፍቅሬያታለው፡፡ማፍቀሬን ደግሞ በውስጤ ስላፈንኩት እየተጎዳው ነው...ህመሙ ልቤ ስር እስኪሰማኝ ድረስ የተጎዳውበት ነው….
ስራውን በተመለከተ ረዳቴ ሆና በጣም እያገዘቺኝ ነው..እርዳታዋ በጣም ጠቃሚና ወሳኝ ከመሆኑ የተነሳ እራሴን እስክታዘብ ድረስ ነበር ስደመምባት የነበረው፡፡ ….አሁን ተሰርቶ በመጠናቀቅ ላይ ያለው ፕሮፖዛል እሷ ባታግዠኝ ኖሮ በራሴ እሰራው ከነበረው ጋር በሀሳቤ ሳመዛዝነው ደነግጣለው..፡፡ልጅን እንደ ቁጥር አንድ ጀግና በሚያስበው አባቴ ፊት ተዋርጄ ነበር…፡፡አሁን ግን እድሜ ለፌናን አይደለም ከአንዲት ልምድ አልባ ወጣት ሴት ጋረ ይቅርና ከማንም በስራው እድሜ ጠገብ ልምድ ያለው ሰው ጋር ተወዳድሬ ቦታውን በእጄ ማስገባት እችላለው፡፡፡የዛን ያህል በራሴ እንድተማመን አድርጋኛለች ፡፡አሁን በዛ እርግጠኛ ሆኜያለው ፤ ይገርማችሆል ፌናን ጭቅጭቆ እራሱ ሱስ ይሆንባችኃል…….አሁንም ቢሮ ጭቅጭቅ ላይ ነን፡፡ ስለዚሁ የፕሮፖዛል አንዱ ክፍል የሆነ የሰራተኛ ደሞዝን በተመለከተ እየተነጋገርን ነው…
‹‹አሁን ለሰራተኟች እየተከፈለ ያለው ደሞዝ መስተካከል አለበት ..››የሚል ሀሳብ አቀረበች
ወዲያው ነው የተቃወምኳት‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ……?በተመሳሳይ የስራ መደብ በመንግስት ቤት ከሚከፈላቸው ሰራተኞች ጋር ሲነፃፀር ቢያንስ አርባና ሀምሳ ፐርሰንት የእኛ ጭማሪ አለው..እና በዚህ ላይ አሁን በምናደርገው ማሻሻያ ላይ የ5 ፐርሰንት ጭማሪ ማድረጋችን በጣም ምክንያታዊና በቂ ነው ብዬ አስባለው፡፡››
‹‹አልስማማም..››አለቺኝና ንግግሯን ማብራራት ቀጠለች‹‹ይሄውልህ በመጀመሪያ ደሞዝን በተመለከተ የመንግስትን እስኬል ማነፃፀሪያ ማድረግ ትክክል አይመስለኝም፡፡››
‹‹ለምን ………..?መንግስት እንደዛ ለምን እንደሚከፍል ታውቂያለሽ ፡፡ሀገሪቱ ደሀ ስለሆነች ነው፡፡እኛም ደግሞ መክፈል ሰለቻልን ብቻ ዝም ብለን መክፈል የለብንም ….ገበያውን ማበላሸት ነው የሚሆነው››
‹‹ላስቁምህ..ይህቺ ገበያውን ማበላሸት ነው የምትለው ቀሺም ምክንያት ነች ..እዚህ ሀገር ላይ የሰው ጉልበት ዋጋን በተመለከተ በጣም የተዛባ አመለካከት አለ…መንግስት ሀገሪቱ ደሀ ስለሆነች ከዚህ በላይ የተሻለ ደሞዝ መክፈል አልችልም ይላል..ግን እውነቱ ያ ብቻ ይመስልሀል…?፡፡እንደእኔ ግንዛቤ ዋናው ችግሩ ያመለካከት ነው……በየመስሪያ ቤት በቋሚ እና አላቂ ንብረቶች ላይ የሚከሰትን ብክነትና ብልሽትን የተወሰነ ግንዛቤ በመፍጠር እና የተወሰነ የጥንቃቄ እርምጃ በማድረግ ለዓመታዊ ዕቃ ግዢ የሚወጣውን ወጪ በ50 ፐርሰን መቀነስ ብንችል ከዛ በተገኘ ገንዘብ ቢያንስ የእያንዳንዱ የመንግስት ሰራተኛ ላይ የ25 ፐርሰንት የደሞዝ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም ብለህ ታስባለህ…?.ባለስልጣኗች በሙስና የሚቀራመቱትን ገንዘብ የተወሰኑ ክፍተት ያላቸውን አሰራሮች በማሻሻል እና የተወሰነ ቁጥጥር በማድረግ ቢያንስ 50 ፐርሰንቱን ማስጣል ቢቻል የሰራተኛውን ደሞዝ 200 ፐርሰንት ማሳደግ አይቻልም ትላለህ…?የተቀላጠፈ የስራ ቢሮክራሲ ተፈጥሮ የእያንዳንዱን ሰራተኛ የስራ ውጤታማነትን በተወሰነ ስልተና እና ማነቃቃት በአንድ እጥፍ ማሰደግ ቢቻልና አጠቃላይ የሀገሪቱን ዓመታዊ ምርታማነትን የእውነት 11 ፐርሰንት ማሳደግ ማይቻል ይመስልሀል? እንደዛ ከሆነ ድግሞ በየአመቱ ስንት ፐርሰንት ለሰራተኛ ደሞዝ መጨመር ይቻላል…?አየህ የሀገሪቱን የድህነት ችግር ለመቅረፍ እየሞከርን ያለነው በተሳሳተ የድህነት አመለካከት ነው….
‹‹እኔ እንጃ የምትያቸውን ነገሮች በቀላሉ ማድረግ ይቻላል የሚለውን መቀበል ይከብደኛል››አለኳት…
ተቃውሞዬን ችላ ብላ ቀጠለች‹‹አንዳንዴ ይገርመኛል አንድ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ስንት እና ስንት ለሀገር ደህነንነት ወሳኝ የሆኑ ጉዳዩችን ሲዳኝ ውሎ፤ የሚሊዬን እና ቢሊዬን ሙስና ወንጀሎችን ሲመረምር ቆይቶ ወደቤቱ የሚወስደው አንድ ቪትስ መኪና እንኳን አጥቶ በታክሲ ሰልፍ ይዞ እየተጋፋ ወይም በባስ ታጭቆ እየተንገላታ ወደቤቱ ሲሄድ የሚፈጥርበት ስሜት ይታይህ…ይሄ ሰው የሚከፈለውስ ደሞዝ ስንት ነው…?ልጁ ቢታመምበት የግለሰብ ሆስፒታል ወስዶ ማሳካም አቅም ይኖረዋል ወይ ….?እና ሄዶ ሄዶ ሙስና ውስጥ ሳይገባ ምን የህል ጊዜ በጽናት መቆየት ይችላል …?በእሱ ላይ የሚመጣውን የድህንት ችግር መታገስ አለበት ብለን እንፍረድበት በልጁ ላይስ ሲሆን …?ክፋቱ ደግሞ ማንም ሰው ለወቅቱ የሚያስፈልገውን ለችግሩ ሚበቃውን ያህል ብቻ ዘርፎ አያቆምም..፡፡አንዴ መዝረፍ ከተጀመራ ሱስ ነው የሚሆነው…ለዛውም አደገኛ የሀሽሽ ሱስ አይነት …፡፡ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው ዳኛ ዘራፋ ሲጀምር…ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው መሀንዲስ መዝርፈ ሲጀምር…. ለመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቹን ማሟላት ያቃተው የባንክ ማናጀር መዝረፍ ሲጀምር ..ሀገር ሁሉ በዘራፊዎች መነኸሪያ ሆና ታርፈዋለች….. በጣም የሚያስጠላው ደግሞ መዝረፍ ውስጥ የገባ ሰው በዘረፋው ብቻ አይደለም ሀገሪቱን የሚጎዳው የስራ ሞራሉም ቀን በቀን አየወረደ ስለሚመጣ ነው…ተጫሪ ገንዘብ በቀጥታ ለኪሱ የሚያስገባለት ገንዘብ የማያገኝበትን ስራ ዞር ብሎ ለማየት ፍላጎቱ ወደ ዜሮ እየተንደረደረ ይሄዳል …
አሁን እኮ ለሙሰኞችና ቀማኞች ይቅራታ እንዲባሉ ምክንያት እየሰጠሽላቸው ነው››
በፍጽም እንደዛ አይደለም ..ምንም ሳይቸግረው በስነምግባር ጉድለትና በስግብግብነት በሽታ ብቻ በመጠቃታቸው በሙስና የሚጨማለቁ ቡዙ ዜጎች እንዳሉ አውቃለው…ግን ሳይፈልጉ ችግርና እጦት አንደርድሮ እዛ አዝቅጠት ውስጥ የጨመራቸው የመንግስት ሰራተኞች ቀላል ቁጥር የላቸውም እያልኩህ ነው…እንደዚህ አይነት ሰዎች ደግሞ አንድ ንጽህ ህሊናቸው በሆነ ምክያት ከጨቆየ ይሰባራሉ… በራሳቸውም ስለሚያፍሩ ብኩን ዜጎች እንደሆኑ ይቀራሉ..እያወራውልህ ያለውት ስለእነዛ ሰዎች ነው..በነዛ ጠቃሚ ሰዎች ውድቀት መንግስት የደሞዝ ክፍያ ስርዓትና አሰስተሳሰብ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ፡፡እያልኩህ ነው…
‹‹ቆይ…. እንደምታውቂው የሰው ልጅ ፍላጎት ማብቂያ የለውም፡፡የሆነ ነገር በሰጠሸው ቁጥር ሌላ ተጨማሪ ነገር ይጠይቅሻል..ታዲያ ምን ያህል ቢከፈል ነው በቂ ሚባለው?፡፡››
‹‹ለችሎታውና ለአገልግሎቱ የሚመጥነውን ቢያንስ ዝቅተኛውን ክፍያ ማግኘት አለበት….አንድ ምሳሌ ልስጥህ በመዘጋጃ ቤት የሚሰራ መሀንዲስ 5 ሺብር ደሞዝ እየተከፈለው የሀምሳ ሚሊዬን ብር ባጀት ያለው ሰማይ ጠቀስ ህንፃ እንዲቆጣጠር ይመደባል…. እና መንግስን ወክሎ ባለሀብቱ በተሰጠው ቦታና በፀደቀለት ዲዛይን መሰረት ህንጻውን እየገነባ መሆኑን ለማረጋገጥ በሚሰማራበት ጊዜ ያገኘውን ስህተት ለባለቤቱ ተናግሮ የማሳገጃ ትዕዛዝ ሊፅፍ ሲል ባለሀብቱ 20 ሺብር ማለት የአራት ወር ደሞዙን በአንድ ቀን ቢሰጠው አልፈልግም ለማለት የሚያስችል ስብዕና ጽናት ከመቶ ሰው
👍1
ውድ አንባብያን ያለፈው ክፍል ላይ በስተት ክፍል 21 22 የተባለው በስተት ነው ምንም የታሪክ መቆራረጥ የለም መልካም ንባብ

#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ሦስት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ


#ፍሰሀ

‹‹አሁን ተስማምቼለው››
‹‹አመስግናለው››
‹‹አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር?››
‹‹አለቃ እኮ ለመጠየቅ ፍቃድ አይጠይቅም››
‹‹አሁን እኮ የስራ ሰዓት አይደለም …ስለዚህ አለቃ ምናምን ብሎ ነገር የለም..››አልኳት
‹‹እሺ ጠይቀኝ››አለቺኝ አቀማጧን እያስተካከለች
‹‹የዛን ቀን እሷን ለማናደድ ብለሽ ያደረግሺውን እንደሆነ ባውቅም ግን በምንም አይነት ከአዕምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም….ከአዕመሮዬም ብቻ አይደለም ከህልሜም ማስወገድ አልቻልኩም….ሙሉ አዕምሮዬ በአንቺ ከንፈር ተሞልቷል…ምነው አሁንም አንድ ሰው አበሳጭቷት በሳመቺኝ እያልኩ በየቀኑ ነው የምፀልየው…
‹‹እየቀለድክ ነው አይደል?››አለቺኝ በፈገግታ እና በመኮሳተር መካከል በሚዋልል ስሜት
‹‹አይደለም…››አልኩና እንደምንም እራሴን አደፋፍሬ እጇን በመዶፎቼ መካከል አስገባውና እያሻሸው ንግግሬን ቀጠልኩ..አልተቃወመችኝም፡፡
‹‹አይደለም..እውነቴን ነው…ከህይወቴ አንድ አመት ተቀንሶ ያንን አይነት መሳም አንድ ጊዜ ደግማ ትሳምህ ብባል እስማማለው …እና እባክሽ..››
‹‹እንዲህ አይጠየቅም እኮ …አንድን ሴት እንዴት ልሳምሽ ብለህ ትጠይቃታለህ…ነውር እኮ ነው፡፡ነው ወይስ ውጭ ስለኖርክ ነውር የሚባል ነገር እረስተሀል?››
‹‹እንደዛ ማለቴ አይደለም..ፍቅረኛዬ እንድትሆኚ እየጠየቅኩሽ ነው››
በጥያቄዬ ምንም የመገረም ስሜት አልታየባትም ‹‹ከዛም በፊት ፍቅረኛ አለሽ ወይ ተብሎ ይጠየቃል…በዛ ላይ አንተም ፍቅረኛ አንዳለችህ አውቃለው..ታዲያ ፍቅረኛ ያለችውን ሰው መጥበስ የምፈልግ ይመስልሀል…?››
‹‹የእኔን እርሺው አብቅቶለታል..አንቺን ፍቅረኛ አለሽ ወይ ብዬ ያልጠየቅኩሽ ግን መልሱን ስለፈራው ነው..አለኝ ካልሺኝ ምን እንደምሆን አላውቅም…››
‹‹የእውነት ልንገርህ አለኝ ብልህም ምንም አትሆንም ..ሁሉም ወንዶች አንዱን ሴት ለማሰመን እንዲህ ነው የሚሉት..››
‹‹እወነቴን ነው …ትክክለኛ የሚሰማኝን ነው እየነገርኩሽ ያለውት..እኔ እስከዛሬ የነበሩት የፍቅር ገጠመኞቼ በአጋጣሚ የተከሰቱ ስለነበሩ እንዲህ አይነት ውስብስብ ነገሮችን አላውቃቸውም…››
‹‹ይሁን ግን የእሳትእራትን የፍቅር ታሪክ ታውቃለህ
አላውቅም እስኪ ንገሪኝ…
የአሳት እራት ፍቅረኛው እየመሰለችው ነው አንፖል በበራ ቁጥር ሲሽከረከር እምታየው ….ሴቷ ለፍቅር ዝግጁ ስትሆን የራሷን ብርሀን ከሰውነቷ አመንጭታ በመርጨት ነው ምልክት የምትሰጠው.. በዛ ብርሀን ተስቦ ወደ እሷ ይሄድና ፍቅሩን ያጣጥማል…እና ይሄ የዋህ አፍቃሪ የሚያምር እና የሚንበለበል ብርሀን ባየበት ሁሉ አፍቃሪ ያገኘ እየመሰላው ተንደርድሮ ምስግ ነው…የሚንበለበል እወነተኛ እሷት ውስጥም ቢሆን ከመግባት ስሜቱን መግታት አይችልም…ከገባና ደግሞ ታውቃለህ እርር ክስም ማለቱ አይቀርም …
‹‹እና ምን ለማለት ነው..››አልኳት ምሳሌዋ ግራ አጋብቶኝ
‹‹ከእኔ ጋር የሚጠብቅህ ፍቅር መንደድ እና መክሰምንም ሊያስከትልብህ ይችላል ብዬ እያመከርኩህ ነው››
‹‹ሰምቼሻለው..እሺ በይኝ እንጄ መንደዱም መክሰሉም አያስጨንቀኝም››
‹‹ወደ እኔ ተሳበች እና ወደ ከንፈሬ ተጠጋች…ከበቀደም ለታው መሳም በላይ የጠለቀ..ከዛ በላይ የሚያደነዝነዝና ረጅም ትንፋሸ አስቋራጭ ነበር… ከተቀመጥኩበት ሶፋ ተንሸራትቼ ወለል ላይ በጉልበቴ እስከምንበረከክ ድረስ አቅል የሚያሳጣ አይነት መሳም ነበር የሳመቺኝ….ቆይ የአሳሳም ጥበብን በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የሚያሰለጥን ተቋም አለ እንዴ…?.እንደዛ ካልሆነማ እንዲህ አይነትን አደንዛዣ አሳሳም ጥበብ ልትጎናፀፍ ትችላለች፡፡
እንደምንም ገፍታ ነበር ከንፈሯን ከከንፈሬ ያለቀቀችው….
ትንፋሽ ወስጄ እራሴን ካረጋጋው ቡኃላ‹‹እና እሺ አልሺኝ ማለት ነው..ፍቅረኛሞች ሆነናል ማለት ነው››ስል በመንሰፍሰፍ አይነት ስሜት ጠየቅኮት
‹‹በፍጽም አልሆንም….ስብሰባው ተካሄዶ የዚህን የፕሮፖዛል ውጤት ካወቅክ ቡኃላ መልሰህ ምትጠይቀኝ ከሆነ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው››
ምን ማለቷ እንደሆነ ግልጽ ሊሆንልኝ አልቻለም‹‹ፕሮፖዛሉ ውጤትና የእኔ እና አንቺ ጉዳይን ምን አገናኘው…?.››
ተገናኘም አልተገናኘውም ያልኩህን ከማድረግ ውጭ ምንም ምርጫ የለህም…ከፈለክ ወይም ከዛ ቡኃላም ፍቅርህ የሚኖር ከሆነ እዚሁ አጠገብህ ጋር ስለምገኝ ጠይቀኝ….አንድ ሰምንት አይደል የሚቀረው..?ሳምንት መታገስ ያቅትሀል?
ይብላኝ ላንቺ እንጂ እኔስ ጠብቃለው….ስሜቴ በሳምንት የሚጠፋ መስሎሽ ነው…?ከአመታት ቡኃላም ብትይኝም ተመሳሳይ ጥያቄ ነው የምጠይቂኝ….የፍቅር ጓደኛዬ ሁኚ ብዬ…..
‹‹እናያለን…››አለቺኝ
‹‹እናያለን ››አባባሏ አስፈራኝ..የሆነ እሳት በውስጤ እንዲጫር አደረገብኝ….
❤️ፌናን
===
እለቱ እሁድ ነው…ያው ይሄ ዓረፍተ ነገር ብቻ የሚገልፀው ሀሳብ አለ አይደል…….?እለቱ ዕሁድ ከሆነ ብዙ ነገሮች የሚረጋጉበት ቀን ነው ማለት ነው..፡፡ወከባና መተረማማስ በጣም የሚቀንስበት ቀን…የስራ ስልክ ሲያወሩ ከመዋል ተገላግለው ቤተሰብን ወይም ወዳጅ ዘመድን በመደወል እንዴት ናችሁ….? የሚባልበት ቀን …የታመመ የሚጠየቅበት ፤ያዘነን የሚያፅናኑበት ለመንፈስ የቀረበ ስራ የሚሰራበት ቀን፡፡
በቤታችን ውስጥ ነው ምንገኘው..እኔ አባቴና እናቴ ብቻ ..ወይ ሳልነጋራችሁ እናቴ ከውጭ ተመልሳ ከመጣች ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነው…ደግሞ በዚህ ዘመን ከውጭ ተመልሶ መምጣት ብርቅ ነው እንዴ….? እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለው…
ለማኛውም የዛሬዋ ቀን ልዩ ቀን እንድትሆን ስለፈለኩ ለሁሉም የቤቱ ሰራተኞች ፍቃድ ሰጥቼያቸዋለው…ግን ከመሄዳቸው በፊት ቀኑን ሙሉ ሲያግዙኝ እና ለእለቱ የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ሲሰሩልኝ ነው የዋሉት ..ልክ እንደምፈልገው፡፡አሁን ሰዓቱ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ነው፡፡እናቴ የገዛ መኝታ ቤቷ እንደተኛች ነው..አባቴ ደግሞ ያው እንደልማዱ ላይብረሪው ውስጥ እራሱን ዘግቶ ወይ እያነበበ ነው ወይ ደግሞ እየጻፈ ነው..ብቻ እዛ ነው ያለው፡፡
እኔ ደግሞ የምግብ ጠረጵዛው በምግብ እየሞላው ነው….ልክ እንደጨረስኩና ነገሮች በፈለኮቸው መሰረት እንደተማቻቹና ቀልብ ሳቢ እንደሆኑ ካረጋገጥኩ ቡኃላ ወደእናቴ መኝታ ቤት አመራው
===
..በዝግታ ሳንኳኳ ‹‹ግቡ››የሚል የደከመ ድምጽ ፍቃድ ሰጠኝ… በራፉን ገፋ አድርጌ ገባው…እናቴ አልጋዋን በወረቀት ሞልታ አፍንጫዋ ላይ የሰካችው መነጻር ከፍ ዝቅ አያደረገች አንገቷን አቀርቅራ ወረቀቷቹ ላይ አፍጥጣለች፡፡
‹‹እንዴ እማ የተኛሽ መስሎኝ ነበር እኮ….?››
‹‹በዚህ ሰዓት…….?አረ አልተኛውም››
‹‹ይሄ ሁሉ ወረቀት ምንድ ነው….?››
‹‹የካምፓኒውን የስድስት ወር ሪፖርት ልከውልኝ ነው..እስኑ እያየውት ነው››
‹‹ምነው ተዲያ ተኮሳተርሽ ….….?የጠፋ ነገር አለ እንዴ…….?››
‹‹አይ የለም…..አንድ ብቻ ደስ ያላለኝ ነገር አለ…››
‹‹ልትነግሪኝ ትቺያለሽ….?››
‹‹የሰውዬው ልጅ ስር-አስኪያጅ ከሆነ ምን ያህል ጊዜ ሆነው….?››
‹‹ወር ከሀያ ቀን …››
‹‹እና ምን አድርጎ ነው በዚህ አጭር ጊዜ በጣም የተለየ ትርፍ ሊገኝ የቻለው…….?››
‹‹ጎበዝ ነው ብዬ ነግሬሻለው እኮ….›››አልኳት በፈገግታ ተሞልቼ
‹‹አይ ይሄንን ስራ ጥርሴን የነቀልኩበት ነው..የፈለገ ጎበዝ ቢሆን ሁለት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሊታይ የሚችል ልዩነት ማምጣት የሚችል ሰው አይኖርም… ምን አልባት ስራውን በደንብ የሚያውቅና ካምፓኒውን ቀድሞ
👍3
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_አራት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



‹‹የዛሬዋን ቀን ለዓመታት ሳስባትና ስዘጋጅባት የነበረች ቀን ነች::በምን አይነት ሁኔታ ላድርገው?እንዴት ቢሆን ይሻላል?ለብዙ ለብዙ ቀናት ሳብሰለስለው ነው የኖርኩት….እና ይቺ ቀን ዛሬ ነች ደቂቃዋም አሁን…..››
‹‹ይሄን ያህል ያሰጨነቀሽ ነገር ምን ቢሆን ነው?››እናቴ ነች
‹‹እዚህ ቤት ያለው ሚስጥር..በእናንተ ሁለታችሁ መካከል ያለው ሚስጥር……የማትጨቃጨቁበት፤ የማትለያበት ሚስጥር….?››
<<እንዴ ልጄ ምን እያልሽ ነው…….?እንዲህ ይባላል እንዴ..….? ሰው እኮ አባትና እናቴ እየተጨቃጨቁና እየተጣሉ እረበሹኝ እያለ ነው ሚሰቃየው..ለምን አልተጣላችሁም ብሎ መጨነቅ ምን የሚሉት ነው….?››አለች እናቴ
አባቴ እንዳቀረቀረ ነው..ምን ለማለት እንደፈለኩ ለእሱ በደንብ እደሚገባው አውቃለው…በጥልቀትም ባይሆን ብዙ ጌዜ እያነሳሳውበት ስጨቀጭቀው ስለነበር ከእናቴ በተሸለ ምን ለማለት እንደፈለኩ ማወቁ ብዙም አይግርምም….
‹‹በመሀከላችሁ የታፈነው ነገር ነዋ የሚያስጨንቀኝ…መቼ ይሆን የሚፈነዳው ….?እያልኩ ሁሌ እንቅልፍ እስካጣ ድረስ አስባለው…ሲፈነዳስ?የፍንዳታው ፍንጥርጣሪ እያዳንዳችንን ምን ያህል ይጎዳናል? ከፍንዳታው ቡኃላም እንዲህ አንድ ላይ በአንድ ቤት ጣሪያ ውስጥ መኖር እንቀጥላለን?ወይስ ብትንትናችን ይወጣል?ሁሌ ያስጨንቀኛል››
‹‹የምን መአት ነው የምታወሪው?እኔና አባትሽን እንዴት ይለያያሉ ብለሽ አሰብሽ….ወደ አባቴ ዞረችና በጥርጣሬና ግራ በመጋባት እየመረመረችው‹‹ምን አልካት…….?››ብላ ጠየቀችውና ወዲያው እራሷ መልሱን መመለስ ጀመረች ‹‹ይቅርታ አንተ ምንም ልትላት እንደማትችል አውቃለው››ብላ መልሳ እኔው ላይ አፈጠጠችብኝ
‹‹ቆይ እናንተ ምንድን ናቹሁ.?››
‹‹ምን ማለት ነው.?ሰዎች ነና››
‹‹አይደለም… የሁለታችሁ ግንኙነት ምን ስያሜ ነው የምትሰጡት?የውጭ ሰዎች እንደሚሉት ባልና ሚስት ናችሁ?.እኔ እንደማውቀው አንድ የጋራ ቤት ተጋርተው የሚኖሩ ደባል ናችሁ…..….የትኛውን ናችሁ….?››
‹‹ተረጋጊ….አባትሽ ለእኔ ምኔ እንደሆነ ታውቂያለሽ .. ….?ባሌ ብቻ እንድልሽ ትፈልጊያለሽ.?ባልማ ማንም ወንድ ባል ሊሆን ይችላል ..እሱ ህይወቴ ነው…፡፡ህይወቴን ለማቆየት በየሰው ሀገር እየተንከራተትኩ ሰውነቴን በየጊዜው እያስተለተልኩ መከራዬን እደማይ ታውቂያለሽ…ለምን ይመስልሻል?ለሀብቴ አይደለም..አሁን ለእኔ ገንዘብ ምን ያደርግልኝ ይመስልሻል?ያማረኝን የማልበላና ያሰኘኝን የማልጠጣ ሰው ነኝ…፡፡እና ለተጨማሪ ጊዜያቶች አብሬው ለመኖር ፍላጎት ባይኖረኝ ኖሮ ምን እንደማደርግ ታውቂያለሽ?አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር ያሰኘኝን በልቼ ያማረኝን ጠጥቼ ይህቺን ህይወት እሰናበት ነበር..ግን ከእሱ ላለመለየት ስለምፈልግ ነው እያዳንዳን የሀኪም ቃል ከፈጣሪዬ ቃል በላይ በየቀኑ እየደገምኩ በዛ መሰረት ለመጓዝ ምጥረው….እና ደግሞ ከእሱ በተጨማሪ አንቺም አለሽ››ንግግሯ ፀጥ አሰኘኝ…ሀሳቤን በታተነቺብኝ….እሷ እንደዛ በስሜት እየተንቀጠቀጠች ስትናገር አባቴ ደግሞ እንባውን በጉንጮቹ እያረገፈ ነበር…እኔ ደግሞ አባቴ ጉንጮች ላይ እንባ ሲወርድ ከማይ አለም አብቅቶላት ምጽአት ቢታወጅ ይቀለኛል….ግን ይገርማችሆል በዚህ የስሜት መጨፍገግ ላይም ሆኜ ምን እንደተዛብኩ ታውቃላችሁ?እማዬ ስለአባቴ የሚሳማትን ተንትና በስተመጨረሻ ደግሞም አንቺም አለሽ ስትል…ለእሷ እኔ የሆን እንጎቻ ነገር እንደሆንኩ ነው የተሰማኝ….ልጣፊ ነገር፡፡
ጥያቄዬን ቀጠልኩ ‹‹እና እንድምትይው አባቴን የምታፈቅሪው ከሆነ እንዴት እንዲህ ትጨክኚበታልሽ? ሀያ አምስት አመት ሙሉ ልጅን አቅፎ ሲተኛ ትንሽ ህሊናሽን አይቆረቁርሽም?ነው ወይስ የአንድ ሚስትን ግዴታና ኃላፊነት አታውቂም.?››
አባቴ ንግግሬ አስጨንቆት ይንቋራጠጣል….
‹‹ስለማታውቂው ነገር አትዘባርቂ…››
‹‹እኮ አሳውቂኝ… የሆነው ነገር ሁሉ እንዴት እንደዛ ሲሆን እንደኖረ የማወቅ መብት አለኝ…ንገሪኝና ልረዳው….ከለበለዛ…!!!››
‹‹ካለበለዛ ምን ….?››አይኗን አጉረጥርጣ ጠየቀቺኝ..ዛሬ ምንም ብትቆጣ …ምንም ያህል ብትኮሳተር ልፈራትና ልሸነፍላት አልችልም ….አባቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በመካከላችን ገባ
‹‹ወዴ በቃሽ….ይሄንን ነገር እንዳለ ተይው ››
‹‹አልተወውም አባ::ለአንተ ስል አልተወውም››
‹‹ለእኔ አስበሽ ከሆነ ብትተይው ነው በጣም የምትጠቅሚኝ…እናትሽ እንዳለቺው እስከዛሬም የኖርነው የፈለግነውን አይነት ኑሮ ነው …ሁለታችንም እየሆነ ባለው ነገር ደስተኞች ነን::ስለዚህ አንዳንድ ነገሮችን ባሉበት መተው መልካም ነው..››
‹‹አልተውም አልኩ እኮ..አባ ዛሬ እውነቷን ሳላውቅ አላድርም››
‹‹ተውሽም አልተውሽም እኛ ምንም የምንነግርሽም የምንልሽም ነገር የለም…እና ምን ልታደርጊ ነው?››እናቴ ነች…ምንም ልታመጪ አትቺይም በሚል ስሜት የተናገረቺው
‹‹አፋታችሁለው….አባቴ ካንቺ እንዲፋታና ይሄንን ቤት ለቆልሽ እንዲወጣ አደርጋለው::ከዛ በቅርብ ሌላ ሚስት እድረዋለው::እና ደግሞ ያንን ካምፓኒሽን አልፈልገውም::አንቺንም ጭምር አልፈልግሽም.››
ዝም አለች… ዝም ብሎ ማፈጠጥ ብቻ….የሆነ 5 ደቂቃ ያህል መሰለኝ ዝም ያለችው …ግን የ5 ዓመት ያህል ርዝመት ነበረው..አስፈሪ ምንጩ ከወደሲኦል ሚመስል ዝምታ….እና ከዝምታዋ ወደ መዳካምና አንገቷን ዘንበል አድርጋ ወደጎን ልትወቀድቅ ስትል አባቴ ፈጠን ብሎ ያዘት ..ከዛ ቡኃላ የነበረውን መሯሯጥና መተረማመስ አትጠይቁኝ..በስንት ማናፈስ …መዳሀኒቷ ከመኝታ ቤት አምጥተን አውጠናት በመከራ ነው አይኖቾን የገለጠችው….እና እንደገለጠች…
.‹‹ወደመኝታ ቤቴ ውሰደኝ …ደከመኝ ልተኛ >>አለችው አባቴን ስልምልም ባለ ድምጽ
‹‹እሺ›› አለና ከተቀመጠበት ተነስቶ ሰቅስቆ አቀፋትና የፎቁን ደረጃ ማውጣት ጀመረ….እኔም ቀደምኩና ከፊት ለፊቱ መኝታ ቤቷን ከፈትኩለት …ወደውስጥ ገባውና ብርድልብሱን ገለጥኩለት…. ቀስ ብሎ አስተኛት…
ወደእሷ ተጠጋውና ‹‹እማ ይቅርታ››እጆን አናሳችና ፊቴ ላይ እሰቀምጣ በመዳበስ‹‹‹..በጣም ነው የምወድሽ…የእኔ ልጅ በመሆንሽ ሁል ጊዜ እንደኮራውብሽ ነው…ግን እንድታውቂ የምፈልገው አባትሽን ደግሞ ካቺም በላይ ነው የምወደው››አለቺኝ …ከሳለፉነው ሁኔታ ጋር የማይገናኝና በተቃራኒ የሆነ ልስልስ ያለና ወደልብ የሚሰርግ የፍቅር ንግግር ነው ያሰማቺኝ…በመጠኑ ተንፈስ አልኩ
‹‹በቃ አሁን ሂዱ…ልተኛ ››
‹‹እኔ አብሬሽ ልቆይ››አባቴ ነው ተናጋሪው
‹‹አይሆንም… ካመመኝ መጥሪያውን እጫናለው…››
ባለችው ተስማምተን ለቀንላት ተያይይዘን ወጣን..ወደሳሎን ነበር የተመለስነው….‹‹አባ ውስኪውን መጠጣት ነው የምፈልገው›› አልኩት
ባዶ ብርጭቆ አናሳና ቀዳልኝ …የራሱንም ጎዶሎ ሞላ …..በዝምታ መጠጣት ጀመርን…እኩለ ለሊት ሊቃረብ ሲል ነበር አባቴ ማውራት የጀመረው….

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_አምስት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



❤️ፌናን
===
‹‹….ምን አልባት ትክክል ነሽ››አለኝ
‹‹ምኑን አባ…?››
‹‹እውነቱን የማወቅ መብት አለሽ …እናም ነገርሻለው››
አቀማመጤን አስተካከልኩ..በስካርና በድካም እየታጠፉ የነበሩ ጆሮዎቼን ሲነቃቁና ሲዘረጋጉ ይታወቀኛል…
‹‹በዚህ የታፈነ በምትይው የእኔ እና የእናትሽ ኑሮ ውስጥ ባጣም ተጎጂው እኔ ሳልሆን እናትሽ ነች››
‹‹ማለት…?››
‹‹የመፋታቱን ሀሳብ አንቺ ከመወለደሽም በፊት ሆነ ከተወለድሽ በኃላ ደጋግሜ አቅርቤላት ነበር::ግን ከተለየዋት እራሷን እንድምታጠፋ ደጋግማ ስላስጠነቀቀቺኝ ነው ጥያቄዬን አቁሜ ሀሳቤንም ቀይሬ ዝም ብዬ እንደምታይው መኖር የጀምርኩት..››
‹‹መኖራችሁ ካልቀረ ታዲያ እንደ ሰዎቹ በስርዓት አትኖሩም..…?እንደባልና ሚስት››
‹‹እንደዛ መኖር አንችልም..ታሪኩን ከመጀመሪያ ላስረዳሽ…እናትሽ የአዲስአባ ልጅ ብትሆንም የእናቷ ቤተሰቦች የአንቦ ኦሮሞዎች እንደሆኑ ታውቂያለሽ››የሚናገርውን ነገር ማስረዳት ስለከበደው ዙሪያ ጥምዝ እንደሚሽከረከር ገባኝ ..አሁን እያለኝ ያለው እኮ ያንቺ ሰም መቼስ ፌናን እንደሆነ ታውቂያለሽ አይደል …?ቢጤ ነው፡፡
‹‹…..እና ልክ እኔ እና እናትሽ እንደተጋባን ሰሞን የእናቷ ታናሽ ወንድም ስሙ ቶሌራ ይባላል ..በውድቅት ለሊት በራፋችንን አንኳክቶ ይመጣል….ሲመጣ ሰው አይመስልም…ልብሱ በጭቃና በከሰል ብናኝ በክቷ፤በደረቀ ደም ተለውሶ ነበር…ማንነቱን በመልኩ ሳይሆን በድምጹ ነበር እናትሽ የለየችው…ከዛ አፋፍሰን ወደቤት አስገብተን ሰውነቱን እንዲታጠብ አድርገን ልብሱን ቀይረን የቆሰለውን የተቻለንን ያህል የመጀመሪያ እርዳታ እንዲያገኝ አድርገን አስተኛነው…
‹‹ምን ሆኖ ነበር…?››
ይሄ ልጅ ብሩህ ጭንቅት ያለው ድንቅ ልጅ ነበር…ግን ያው እንደማንኛውም የዘመኑ ወጣት ፓለቲካ ውስጥ እስከአንገቱ ነበር የገባበት::እኔም ሆንኩ እናትሽ እንደው ባጋጣሚ ወይ እኛ ሄደን ወይ ደግሞ እሱ ሊጠይቃና በመጣ ቁጥር ነገሮችን በእርጋታ እንዲይዛቸው ልንመክረው ሞክረን ነበር::አዎ ያቅማችንን ጥረን ነበር:: ግን ያው ታውቂያለሽ አንዳንዴ ፓለቲካ ልክ እንደልክፍት ነው::ሰው ተይ ባለሽ ቁጥር ይበለጥ ይብስብሻል..እና ይሄ የማታውቂው አጎትሽ ሚስጥራዊ የኦነግ አባል ሆኖ በአንቦ ከታማ ይንቀሳቀስ ነበር::.እና ህዝቡን ያነሳሱና መንግስትን በመቃወም ከተማዋን ያምሶታል ::በዛም ምክንያት ብዙ የመንግስትና የግል ንብረት ይወድማል::ከወታደሩም ከኑዋሪውም ከ12 ሰዋች በላይ ይሞታሉ…እና የዚህ ጉዳይ መሪ ይሄ አጎትሽ እንደሆነ በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ደህነነቶች መረጃ ይደርሳቸውና ለሊቱን አድፍጠው ሊይዙት ወደቤት ሄደው ሲከቡት አንዱን ገድሎ ሁለቱን አቁስሎ አጥር ዘሎ ያመልጣል፡፡እድል ከእሱ ጋር ነበረችና ከሰል በጫነ መኪና መሀል በድብቅ ተወሽቆ በለሊት አዲስአበባ ይገባና እንደነገርኩሽ በውድቅት ለሊት ወደእኛ ቤት ይመጣል፡፡
‹‹ታዲያ እንዲት አደረጋችሁ…?››ጥያቄዬን ቀጠልኩ..እኔ መስማት ከምፈልገው የወላጆቼ የጋብቻ ታሪክ ውጭ የሆነ ሀገራዊ እና ፓለቲካዊ ታሪክ ለምን እንደሚነግረኝ ፍንጩን እንኳን ማወቅ አቅቶኝ ፡፡
‹‹ለጊዜው ምን አልባት የእኛ ቤት አስታማማኝ ላይሆን ስለሚችል እና በጥቆማ መጥተው ቢፈትሹ ሊያገኙት ስለሚችሉ ብለን ሊነጋጋ ሲል አቃቂ የሚኖር አንድ ጎደኛዬ ቤት ወስደን አስተኛነውና እዛው ህክምና እንዲያገኝ አድርገን በዘላቂነት ምን ማድረግ እንዳለብን ማሰብ ጀመርን::እናትሽ ለእሱ ያላት ፍቅር ይሄን ያህል ነው ተብሎ ከሚለካው በላይ ነበር…‹አይኔ እያየ አይገሉብኝም ወይም አስርቤት አይጥሉብኝም ብላ በድብቅ ከሀገር ይዛው ልትስወጣው ተነሳች…ቢያንስ እስከድንበር ልትሸኘው::ስሰማ ተቃወምኩ….የተቃወምኩት ለማድረግ ያሰበቸው ነገር አግባብ አይደለም ብዬ አይደለም..ለእሱ ያላትን ፍቅር ስለማውቅ ከዛ በላይም ላድርግለት ብትል የምቃወምበት ምክንያት አይኖረኝም ነበር::ችግሩ ግን በዛን ጊዜ አንቺን እርጉዝ ነበረች::የአራት ወር አርጉዝ ነበረች….‹‹ልጄን ይዘሽ ይሄንን የመሰለ አደጋ ልጋፈጥ ስትይኝ ቁጭ ብዬ አላይሽም ››አልኳት
‹‹ታዲያ ምን ይሁን? ግደሉት ብዬ ብቻውን ልልቀቀው ወይ…?››ብላ ህሊና የሚሞግት ጥያቄ አቀረበችልኝ
‹‹እኔ እስከፈለግሺው ቦታ ይዤው እሄዳለው::ይሄን አደጋ ለመጋፈጥ ካንቺ ይልቅ እኔ እሻላለው››የሚል ሀሳብ አቀረብኩላት
በወቅቱ አሻፈረኝ አይሆንም አለች….‹‹ለምን…?››ያቀረብኩላት ጥያቄ ነበር
‹‹የሆነ ነገር ከሆንክ ምን ብዬ አወራለው ነው ያለቺኝ…‹‹በእኔ ቤተሰብ ይሄንን ያህል መከራ እንድትጋፈጥ አልፈቅድም›› አለቺኝ ….በዚህ ጉዳይ ከሁለት ቀን በላይ ተጨቃጨቅን… ቡኃላ ሽማግሌም መሀላችን ገብቶ በእኔ መሄድ ተስማማን…
ከዛ እኔና አጎትሽ ጨላማን ተገን አድርገን ከአዲስ አበባ በእግር ወጣን .. ግማሽ መንገድ በግር ሲመቻችልን ደግሞ መኪና በመጠቀም ሞያሌ ድረስ ሸኘውት..እዛ ለመድረስ 8 ቀን ነበር የፈጀብን…ከዛ ደላሎች ወደኬንያ እንዲያሸጋግሩት አመቻችቼ…ድንበር ማቋረጡንም ካረጋገጥኩ ቡኃላ በስኬት ተመለስኩ….
‹‹ከዛስ…?››
‹‹ከዛማ…ከከተማ ይዤው ወጥቼ እንዳስመለጥኩት ደህነቶች መረጃ ደርሶቸው ነበረና እቤቴ ሳልገባ ከመንገድ ነው የጠለፉኝ…››
‹‹ወይ አባ አንተን..…?ታዲያ ምን አደረጉህ…?››
‹‹ከዛም አሁን ሙዚዬም ይሁን ተብሎ የተዘጋው ማዕከላዊ አስገቡኝ::በፊልም ላይ አይቼው ማለውቀውን..በመፃፍም ላይ እንኳን ማንበቤን ትዝ የማይለኝን አይነት ስቃይ አሰቃዩኝ::መፈጠሬን እስክጠላ…ሰው ምን አይነት ፍጡር ነው? ብዬ እስክጠይቅ ድረስ……?እግዜር እንዴት እንደዚህ አይነት ፍጡር ይፈጥራል…? ብዬ ሙግት ውስጥ እስክገባ ድረስ….‹‹እግዜር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ› የሚትለው መፃፍ ቅዱስ ላይ ከአመታት በፊት ያነበብኩት ጥቅስ ትርጉም በደንብ እስኪገባኝ ድረስ አሰቃዩኝ››
‹‹አንተን..?ስለአስመለጥከው ብቻ…?››
‹‹አዎ …የት ነው ያደረስከው..…?በድርጅቱ ውስጥ አንተስ የነበረህ ኃላፊነት ምንድነው?ውጭ ካሉት ጋር መመሪያ እየተቀበልክ ክፍለሀገር ላሉት አባሎቻችሁ ሽብር እዲፈፅሙ ምታሰማራቸው አንተ ነህ ወይ?ቀጣዩ የድርጅቱ እቅድ ምንድነው?ሌሎችስ እዚህ ከተማ ውስጥ ሆነ በሌሎች የኦሮሚያ ከተሞች ያሉ አባሎቻችሁን ዝርዝር ?›› የማይጠይቁኝ ጥያቄ የለም..እያንዳንዶ ነጠላ ጥያቄ ከብዙ ማሰቃየትና ገሀነማዊ ቶርቸር ቡኃላ ነበር የምትከተለው፡፡እንዴት አንድ ሰው በገዛ ወንድሙ ላይ በዚህ መጠን ሊጨክን ይችላል?ምን ለማግኘት …?ስንት ዓመት በዚህ ምድር ላይ ለመኖር?በፓለቲካ ልዩነት ብቻ የገዛ ወገንን በየምክንያቱ ከዚህም ከዛም እየሰበሰብ በጭለማ ቤት አጉሮ ጥፍር እየነቀሉ እና ብልት ላይ ሀይላንድ እያንጠለጠሉ በማሰቃየት የሚያስገኘው ውጤት ስልጣን ብቻ አይደለም ዘላለማዊነትስ ቢሆን ያዋጣል እንዴ?በእኔ ሚዛን አያዋጣም፡፡ያንን መከራ በራሴ ላይ ደርሶ ከማያቴ በፊት በሰው ልጅ ላይ የሚሰራ የመጨረሻው አሰቃቂ ወንጀል ወይም ግፍ ግድያ ይመስለኝ ነበር…አንድን ሰው ግንባሩን በጥይት አፍርሶ መግደል፡፡ለካ አሱ ቸር እና አዛኝ የሆኑ ወንጀለኞች የሚፈጽሙት ቀላል ከሚባሉ ቅጣቶች ውስጥ የሚካተት ነው?ብዙም ሊጨክኑበት የማይፈልጉትን ሰው በእንክብካቤ የሚያስወግዱበት ዘዴ…ይህንነ አሁን እየተነጋርኩ ያለውትን ንግግር ሴሜቱ በትክክል የሚሰማው ተመሳሳዩ ነገር የደረሰበት ሰው ብቻ ነው፡ግን ከሰው ውጭ ሌላ ፍጡር በራሱ ፍጡር ላይ ይሄንን ያህል ይጨክናል?ለምሳሌ አንበሳ በአንበሳ
👍5
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



#ፍሰሀ
===
በህይወቴ በጣም የተፈተንኩበት አንድ ሳምንት ነው እያሳለፍኩ ያለውት…በጣም አስጨናቂና ትንፋሽ የሚያሳጣ አይነት ሳምንት…. ደግነቱ ስራዎቼን ቀድሜ ማጠናቀቄ በጀኝ እንጂ በዚህ አይነት የጨፈገገ ስሜት እንዴት እሰራው እንደነበር ማሰቡ እራሱ ይከብደኛል ፡፡
ምክንያቱ አለመኖሯ ነው……ይሄው አይኖቼ አይኖቾን ካዩ አንድ ድፍን ሳምንት ተቆጠረ…የቤተሰብ ጉዳይ ስላጋጠመኝ ድሬደዋ ሄጃለው ነበር ያለቺኝ…እኔማ ደርሶ መልስም ቢሆን ልምጠና አንዴ አይቼሽ ልመለስ ብያት ነበር..ብትመጣም አታጋኘኝምና አትልፋ.. ይልቅ ዝግጅትህ ላይ አተኩር ፤ፍልሚያውን በድል ከተወጣህ ቡኃላ ደውልልኝ..እስከዛ እኔም እዚህ ያለውን ነገር ጨርስና እመለሳለው ካልሆነም ያለውበትን አድራሻ እነግርህና ትመጣለህ›› ስላለቺኝ… ምርጫ አጥቼ በናፍቆቷ እየተሰቃየሁ ባለቺው ተስማምቼ እጄን አጣጥፌ ቁጭ አላልኩም፡፡ምናልባት ድሬደዋ የሄደችበትን አድራሻዋን ባገኝ ብዬ ከሶስት ቀን በፊት በፊት ትሰራበት ወደነበረ ከዚህ በፊትም እንዲህ በጠፋችበት ጊዜ ወደአገኘዋት ሜክሲኮ መጽሀፍት ቤት ሄጄ ነበር ……መኪናዬን ቦታ አስይዤ በማቆም ወደ መጻሀፍ መደብሩ አመራው::ሁለት በአስራዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ናቸው ያሉት…አንደኛው ደንበኛ እያስተናገደ ስለነበረ ነፃ ወደሆነው ተጠጋሁ…
‹‹ምን መፃሀፍ ልስጥህ…..? ››አለኝ… እዚህ ቤት መፃሀፍ እንጂ ሴት ፍለጋ የሚመጣ ሰው ይኖራል ብሎ ስላልገመተ መሰለኝ ቀጥታ ስለመፃፍ የጠየቀኝ ፡፡
‹‹ፌናንን ፈልጌ ነበር..ሰሞኑን መጥታ ነበር?››
‹‹አይ ቆየች.. አስራ አምስት ቀን ሆኗታል››
‹‹ጓደኛዋ ነኝ …ማለቴ የመስሪያ ቤት ጎደኛዋ..ስልኳ አልሰራ ብሎኝ ነው ..ቢሮ ደግሞ እሷ ብቻ የምትሰራው አፋጣኝ ስራ ነበር..እና እቤቷን ልትጠቁመኝ ትችላለህ፡፡››
‹‹እቤታቸው ቤቴል አካባቢ እንደሆነ ነው እንጂ ትክክለኛውን ቦታ አላውቅም…ግን ትንሽ ብትጠብቅ እኮ ጋሼ ስለሚመጡ ትጠይቃቸዋለህ››
‹‹ጋሼ ማነው…..?››
‹‹አባቷ ናቸዋ››
‹‹እርግጠኛ ነህ ይመጣሉ?››
‹‹አዎ እንደሚመጡ ደውለው ነግረውኛል፡፡››
‹‹አይ እንደዛ ከሆነማ አሪፍ ነው.. እጠብቃቸዋለው ››አልኩ…ግን ደግሞ ወዲያው ሌላ ጥያቄ በውስጤ ተፈጠረ…‹‹ከአባቷ በጣም ትግባባላችሁ ማለት ነው?››ጠየቅኩት
‹‹እንዴ አሰሪዬ አይደሉ ለምን አንግባባም?››ሲለኝ እየገባኝ የመሰለኝ ጉዳይ መልሶ ድንግርግር አለብኝ
‹‹አሰሪዬ ስትል..…..?››
‹‹ይሄ የመፅሀፍ መደብር እኮ የእሷቸው ነው …ሌላም ቦታዎችም አላቸው››ሊያብራራልኝ ሞከረ…
‹‹ይሄ መጻሀፍ ቤት የፌናን አባት ነው?››
‹‹አዎ ››አለኝ ይሄን ሁሉ ሳታውቅ ነው እንዴ ጓደኛዋ ነኝ የምትለው በሚል ስሜት ..
ገረመኝ..ከዚህ በፊት እዚህ ባገኘዋት ጊዜ በትርፍ ጊዜዋ ተቀጥራ እንደምትሰራ ነበር የነገረቺኝ ፡፡ይሄ ሁሉ መዋሸት ለምን አስፈለገ?
በውስጤ የተፈጠረ የመደነቅ ጥያቄ ነበር…
‹‹አባቷ ጎበዝ ናቸው ማለት ነው?››አልኩት ልጁን….ስለእዚህች ሚስጥር ስለሆነች ልጅ ሌላ ተጨማሪ ሚስጥር እንዲነግረኝ በመፈለግ ለመጎትጎት ፈልጌ
‹‹እንዴ…!!!››አለና ዝም አለ
‹‹ምነው…..?››
‹‹ጋሼን አታውቃቸውም እንዴ?››
ነገሮች እንዳይበላሹ ዋሸውት‹‹አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ጎበዝ ናቸው ስትል ገርሞኝ ነው››
‹‹ለምን ይገርምሀል…..?››
‹‹ጎበዝ ናቸው ማለት ነው ስትል በጉብዝናቸው ጥርጣሬ ያለብህ ይመስላል..እሷቸው እኮ ይሄንን የከፈቱት እኛንም ለመርዳት ነው እንጂ ጎበዝ ለመሆን አይደለም…አስተማሪነታቸው እና ደራሲነታቸው ብቻ ለጉብዝናቸው በቂ ነው››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው››አልኩት ልክ አስተማሪም ሆነ ደራሲ መሆናቸውን እንደማውቅ ሆኜ…‹‹ አሀ የአስተማሪና የደራሲ ልጅ ነሻ?.ለዛ ነው ነገሮችን መበታተን እና መልሶ መሰብሰብ ሚያስደስታት….አሁን ገባኝ››ብዬ በወስጤ አብሰለሰልኩ…አሁን በዘዴ ብዙ ነገር እያወቅኩ ነው…ይበልጥ ለማወቅ ሌላ ዘዴ መጣልኝ፡፡
‹‹እስቲ የእሳቸው መፃሀፍ ይኖራል..…..?››
‹‹የቱን ልስጥህ……..?››
‹‹ሁሉንም የለኝም… አሪፍ ያልከውን …››
በፈገግታ ከዚህም ከዛም አየመዘዘ አምስት መፃሀፍ እጄ ላይ ዘረገፈ…
‹‹እንዴ…? ይሄን ሁሉ እንደፃፍ አላውቅም ነበር››መደነቄን መደበቅ አልቻልኩም
‹‹11 መፃሀፍ እኮ ነው ያላቸው..ይበዛብሀል ብዬ ነው የቅርቦቹን ብቻ መርጬ የሰጠውህ…. ልጁን እያዳመጥኩ ግን ደግሞ መፃሀፎቹን እያገላበጥኩ በማየት ላይ ሳለው አይኖቼ የመፃፍ ጀርባ ላይ የታተመ የደራሲው ፎቶ ላይ አረፈ ..ደነገጥኩ…. እባብ ሱሬው ውስጥ እንደገባበት ሰው አይነት ነው አደነጋገጤ ..ሰውዬውን አውቃቸዋለው፡፡ሌላውን መፃሀፍ ጀርባ ገለበጥኩ ፎቶ የለውም……ሌላውን ገለጥኩ አዎ እራሳቸው ናቸው…ከመቀመጫዬ ተነሳው….
‹‹ሂሳቡ ስንት ነው…..?››
‹‹የየትኛው…..? ››
‹‹የሁሉም››
መፃሀፎቹን ከእጆቼ ወሰደና ጀርባቸው ላይ ያለውን ዋጋ ደምሮ ነገረኝ..ከፍዬ መልስም ሳልጠይቅ ወጣሁ…
‹‹እንዴ አትጠብቃቸውም……..?››ልጁ ግራ ተጋብቶ ጠየቀኝ
‹‹ተመልሼ መጣለው ››ቻው..ተንደርድሬ መኪናዬ ውስጥ ገባውና አሁንም ድጋሜ የመጽሀፉን ጀርባ ላይ ያለውን ፎቶ አየሁት…ንዴትም ደስታም የተቀላቀለበት ስሜት ነው ተሰማኝ፡፡እኚን እኮ ነው ሹገር ዳዲዋ እንደሆኑ የነገረቺኝ ፡፡ለካ አባቷ ናቸው…?ሲያስደስት..ግን እንዴት ነው የምታስበኝ ?ይሄን ሁሉ ውሸት እንዴት ስትዋሸኝ ትከርማለች……? ስለእሷ የማላውቀው ሌላስ ምን አለ……?ይህቺ ልጅ እስከመቼ ነው እየራቀቀችብኝና እየጠለቀችብኝ የምትሄደው…?ለማንኛውም በእሷ በመታለሌ ከተበሳጨውት ይበልጥ ሹገር ዳዲዋ ናቸው ብዬ ለቀናት በንዴት ስንጨረጨር እና እንቅልፍ ሳጣበት የነበረው ጉዳይ ውሸት ሆኖ አባቷ በመሆናቸው የተደሰትኩት በእጥፍ ይበልጣል…
ከዛን ቡኃላም ስልኳ አይሰራም…ካላጋነንኩት ለመቶ የቀረብ መልዕክቶችን ልኬላታለሁ…ምንአልባት ከከፈተችው ወዲያው እድትደውልልኝ በማለት..ግን አንደዛ አልሆነም…ይገርማችሆል አንዳንዴ በውድቅት ለሊት ስምንትና ዘጠኝ ሰዓት ከእንቅልፌ ድንገት በርግጌ እነሳና ስልኬን አንስቼ እሞክርላታለው….ግን የተለወጠ ነገር አልነበረም፡፡ዛሬ ግን በተቻለኝ መጠን ስለእሷ ከማሰብ እራሴን መግታትና እና ትኩረቴን ሰብሰብ አድርጌ ስለፍፃሜው ጦርነት ብቻ ማሰብ ነው የምፈልገው፡፡ቀኗ ዛሬ ነች…ማንነቴን ለአባቴም ለሌላውም ሰው የማሳይበት ቀን፡፡ይህቺን ቀን አብራኝ ለወራት የለፋችው ፊናን ከጎኔ ብትሆን ኖሮ የበለጠ ጠንካራ የበለጠ ልበሙሉ እሆን ነበር…አይ የኔ ነገር አሁንም መልሼ ወደእሷ ወሰድኮችሁ አይደል፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ


#ፍሰሀ


ብቻ አሁን ከንጋቱ 12 ሰዓት ነው…መኝታዬን ለቅቄ ቢጃማዬን እያወላለቅኩ ወደሻወር ቤት አመራው…የሻወሩን ውሀ ለብ እንዲል አደረግኩና ገባውበት…አዎ ንጹህና ቀለል ብሎኝ መዋል ነው የምፈልገው፡፡
ዛሬ የምለብሰውን ልብስ ከአስር ቀን በፊት ነበር የተዘጋጀው…ሙሉበሙሉ በፌናን ምርጫ በጥንቃቄ ተመርጠው የተገዙ አዳዲስ ናቸው፡፡ከሻወር ወጥቼ እራሴን ካደራረቅኩ ቡኃላ ከቁም ሳጥኔ ውስጥ እያወጣው ሙሉ ቁመናዬን በጥራት የሚያሳየ መስታወት ፊት ቆሜ በጥንቃቄ ለበስኩ፡፡ፀጉሬን አስፈላጊውን ቅባት በተገቢው መጠን በመቀባት አስተካከልኩ፡፡ካሉኝ ሽቶዎች ምርጥ የተባለውን ሽቶ ሳይበዛም ሳያንስም ከተጠቀምኩ ቡኃላ ለመጨረሻ ጊዜ መስታወቱ ፊት አየተሸከረከርኩ..እየቀረብኩ ..እየራቅኩ የጎደለ ወይም የተዛነፈ ነገር ካለ አረጋገጥኩና ስልኬንና የመኪና ቁልፌን ይዤ ከመኝታ ቤቴ ወጣው
በዚህን ጊዜ ለአንድ አስር ጉዳይ ሆኖ ነበር፡፡ፕሮግራሙ የሚጀመረው ሶስት ሰዓት ስለሆነ ገና ቡዙ ጊዜ አለኝ፡፡አባቴ እየተዘጋጀ መሆኑን ለማረጋገጥ ወደእሱ መኝታ ቤት አመራው…፡፡አዎ ተንስቷል… ምክንያቱም መኝታ ቤቱ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡እየተቃረብኩ ስመጣ ድምጹን ሰማው …ያወራል፡፡ስልክ ላይ እንደሆነ ገባኝና ልመለስ ስል ከአንደበቱ ወጥተው ጆሮዬ የደረሱ ዓ/ነገር ጭራሽ ተጠግቼ እንዳዳምጥ ገፋፋኝ፡፡የኮቴዬን ድምጽ እንዳይሰማ ተጠንቅቄ ወደ በራፉ ቀረብኩና አጨንቁሬ ወደውስጥ እያየው ጆሮዬን ለጠፍኩ፡፡አባቴ ፊቱን ከበሩ በተቃራኒው አዙሮ የአልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ እያወራ ነው፡፡
‹‹ስሚኝ ክብረወርቅ …ዛሬም ድረስ እንደማፈቅርሽ አትዘንጊ››ይሄንን መስማቴ ነው በፈገግታ ቀሪውን የስልክ ልውውጥ እንዳዳምጥ የገፋፋኝ..‹‹አባዬ ውሽማ አለችው እንዴ..?..የሚገርም ነው….››
ከዛኛው ወገን የሚነገረው ከርቀቱ አንጻር አይሰማኝም…
‹‹ይሄውልሽ…አንቺ ለልጅሽ እንደምታዳይ ሁሉ እኔም ልጄ የፈለገውን እንዲያገኝ የማልፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም››
‹‹አይደለም..ፈፅሞ አንቺን ለመበቀል እየሰራው ያለውት ስራ የለም፡፡እርግጥ ለዓመታት እንድታገቢኝ ስማፀንሽ አሻፈረኝ ስላልሺኝ ሁሌ እንደተበሳጨውብሽ ነው፡፡አሁንም ከንዴቴ ጋር ነው ያለሁት…፡፡ቢሆንም ግን ላንቺ ያለኝ ፍቅር እዛው ድሮ ያለበት ቦታ እንደሆነ ልደብቅሽ የሚያስችል ጥንካሬ አይኖረኝም…
‹‹አዎ ባል እንዳለሽ አንድ ሺ ጊዜ ነግረሺኛል..አውቃለውም…፡፡ግን አንቺ ለእኔ የተፈጠርሽ ሴት ነበርሽ፡፡ባልሽ እኮ ምኑም ካንቺ ጋር አይሄድም፡፡አንቺን የምታህል ሚኒዬነር ነጋዴ አንድ ተራ የሀይ-እስኩል አስተማሪ አግብታ እድሜ ልኳን ከእሱ ጋር……….››
‹‹ይቅርታ ..ሁል ጊዜ ስለእሱ ሳወራ እንደምትበሳጪ አውቃለው፡፡ግን እይውእስቲ…እኔ እና አንቺ በጋራ ይሄን የመሰለ ካምፓኒ መመስረት ችለናል፡፡ለአመታት በጣም ውጤታማ ነን፡፡ይሄንን የቢዝነስ ስኬታችንን ለልጆቻችን አስተላልፈን እኔና አንቺ ወደ ፍቅር ውህደት ማለቴ ወደ ትዳር ብንገባና ቀሪ ዘመናችንን የተረጋጋ እና የሰከነ ኑሮ ብንኖር ደስ ይለኛል፡፡ምንኖረው ሀገር ውስጥም ላይሆን ይችላል ፡፡አንቺ ተስማሚ እንጂ የፈለግሽው የሀገር ጫፍ ብትይ ይመቸኛል፡፡ሰው ማይኖርበት አንታርቲካም ቢሆን ..››
‹‹የምሰማው ንግግር ከአባቴ አንደበት እየወጣ መሆኑን ማመን ተሳነኝ ‹‹…ወይ ጉድ!! ለካ ሼባው አደገኛ የፍቅር አክተር ነበረና…እኔ እንኳን እሱ በሚያወራው መጠን የማወራትና የምጀነጅናት ሴት ኖራኝ አታውቅም….. ደግሞ ተፈቃሪዋ እኮ የካምፓኒው አንዷ ባለድርሻ ነች …ለካ ይህ ጉዳይ ለእሱ ወሳኝ እንደሆነ ለመቶ ምናምነኛ ጊዜ ደጋግሞ ሲነግረኝና ሲያስጠነቅቀኝ የነበረው ሌላ ምክንያት ስላለው ነበር… አዎ አሁን ገባኝ … በመካከላቸው ያለው ጦርነት ቢዝነሳዊ ብቻ ሳይሆን ፃታዊም ነበር ማለት ነው…፡፡
‹‹ቀጥሏል አባቴ››
‹‹…በቃ እንግዲህ ….የልጅሽና የልጄ ፊልሚያ ላይ እንገናኝ፡፡እና የመጨረሻው ደስታ የእኔ ስለሚሆን ፅዋችንን በእኔ ወጪ ነው የምናነሳው…››
‹‹አታስቢ.. የልጄን ዕወቀትና ብቃት ስለማታውቂ ነው…እኔን ስለምታውቂኝ እሱንም ያወቅሽ እንዳይመስልሽ፡፡እኔን ቁጭ አድርጎ ሊያስተምረኝ ሚችል ጀግና ነው››
ከአባቴ አንደበት በዚህ አይነት ሁኔታ የራስን ልጅ ግነታዊ በሆነ ደረጃ ከፍ ከፍ እያደረገ ሲናገር መስማቱን አልወደድኩትም …ከዚህ የባሰ ነገር ተናግሮ ለወራት የገነባውትን ማንነቴን እና በራስ መተማመን እንዲሸረሽርብኝ ስለማልፈልግ ቀስ እያልኩ ወደኃላ አፈገፈግኩና ወደሳሎን ወረድኩ….
ሰራተኛዋ በምግብ ጠረጵዛው ላይ ቁርስ ደርድራ እንደጨረሰች አባቴም መጣ…
‹‹ፐፐፐፐ…ጠቅላይ ሚኒስቴር መስለሀል.››ብሎ ወደኔ ቀረበና ግንባሬን ሳመኝ..ደስ አለኝ…
ሌላውም ሰው እንደእሱ ከተሰማው አሪፍ ነው ስል አሰብኩ…በፌናን ምክር መሰረት አንዱ ነገር ተሳክቷል ማለት ነው…በዝግጅቱ ቀን የገምጋሚዎቹን ቀልብ ሰብስቦ የሚይዝ ፤በራስ መተማመንኔን በራሱ የሚያስረዳ አይነት አለባበስ መልበስ የመጀመሪያ መመሪያዋ ነበር…ሌላው ፕሮፖዛሉ ሙሉ ሰነድ እንደመሆኑ መጠን ከዛ ዋና ዋናውን ሀሳብ በአንድ ሰዓት ውስጥ ለሶስቱ ወሳኝ ሰዎች ለማቅረብ መከተል የሚገባኝን አካሄድ …
*
To make sticky idea you should be focuse on the following criteria
1/simplicity
2/un expected
3/Cridibel
4/concerete
5/Emotional
6/Story ……ትለኛለች
**
ሶስት ቀን ሙሉ ነው ስለእያንዳንዱ ነጥብ ምሳሌ በመስጠት ያስጠናቺኝ…፡፡እናም ጥናቱን ፍሬ ነገር ጨምቄ ቀላልና ግልጽ በሆነ አገላለጽ በገምጋሚዎች ላይ ያልጠበቁትን መደመም በመፍጠር ሚዛን ሚደፍ ሀሳቦችንና በሚያስምን አቀራረብ ሙሉ የጥናቱን ታሪክ በሚያስረዳ መልኩ የተጨመቀውን ሀሳብ በተሰጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ ማቅረብ እንድችል የተቻላትን ያህል አዘጋጅታኛለች… እኔም ብዙ ጊዜ እያፈረስኩ እየገነባው ሳምንቱን ሙሉ ተለማምጄዋለው፡፡እና አሁን ከአንድ ሰዓት ቡኃላ ይሄን የወራት ልፋቴን ውጤት የእኔም ብቻ ሳይሆን በዚህ መጠን እንድዘጋጅና ተፎካካሪዬን በብቃት እንድረታ በሚስችለኝ መጠን እንድዘጋጅ ለረዳችኝ ፊናን ልፋትም ፍሬው የሚለቀምበት ሰዓት ደርሷል፡፡ዝግጅቱን የማቀርብበት ሰዓት ….
በነገራችን ላይ ፕሮግራሙን ሳልነግራችሁ፡፡ከሶስት እስከአራት ሰዓት ባለው ጊዜ እኔ ሙሉ ሰነዱን አስረክቤ የተዘጋጀውበትን ሀሳብ በተሠጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ አቀርባለው…፡፡ከዛ ከአራት ሰዓት እስከ ተኩል ድረስ የምጠየቀውን ጥያቄ የምመልስበት ሰዓት ይሆናል፡፡. ከዛ የሻይ እርፍት ይኖርና፡፡ ከ5 እስከ ስድስት ሰዓት ደግሞ የሴትዬዋ ልጅ ትገባና በተመሳሳይ እንደ እኔ ያዘጋጀችውን ሰንድ አስረክባ በአንድ ሰዓት ውስጥ አቅርባ ስድስት ሰዓት ትጨርሳለች፡፡ከስድስት እስከ ስድስት ተኩል ልክ እንደእኔ በተመሳሳይ የጠየቋትን ጥያቄ የምትመልስበት ወቅት ይሆናል…፡፡
ከዛ አምስታችንም ወደምሳ ፕሮግራም እንሄዳለን፡፡ከ 6:30 እስከ 8 ሰዓት የምሳ ሰዓታችን ነው፡፡ከ8 እስከ 10 ሰዓት ሶስቱ የካምፓኒው ባለቤቶች ለብቻቸው ሰብሰባ ያደርጋሉ፡፡ በሰነዱና በቀረበላቸው ሀሳብ ላይ ይወያያሉ፡፡ለተኩል ሰዓት ሻይ ይወጣና ተፎካካሪዎቹም ባሉበት የመጨረሻ ድምጽ ይሰጣል፡፡የተሰጠው ድምጽ በግልጽ ሁሉም እያየ ይከፈታል አሸናፊው ይለይና ሙሉ ፕሮግራሙ ይጠናቀቃል፡፡
አሁን ከጥዋቱ 2፡40 ሆኗል እኔና አባቴ ቢሮ ደርሰናል፡፡ጋሼ ከበደ ከእኛ አምስት ደቂቃ ዘግይተው
👍4
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



#ፍሰሀ
===
ልዩ የሆነ ቆይታ ነበር፡፡ሶስቱንም ፈታኞቼን እንዳስደመምኮቸው እርግጠኛ ነኝ፡፡መድረኩን በስነስርዓት፤ ባጠናውት እና በተዘጋጀውት መጠን ነበር የተወጣሁት፡፡በመጨረሻ ሁሉም ወ/ሮ ክብረወርቅም ጭምር ቆመው ነበር ያጨበጨብልኝ፡፡እኔም በደስታ ሰክሬ ከወገቤ ሽብርክ ብዬ አመሰገንኳቸው፡፡
ለመውጣት ቸኩያለው ቀልቤ ያለው ፌናን ጋር ነው፡፡እስከአሁን ከቤቷ መጥታ ውጭ በረንዳ ላይ ወይም ቢሮዬ ቁጭ ብላ እደምትጠብቀኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡አዎ አይኖቼ መላ እሷነቷን ተርበዋል፡፡ከራሴ በላይ እወደዋለው፡፡ ብዬ የማስበው አባቴ እንኳን ከስድስት ወር ባላይ ተለይቶኝ ሲኖር በዚህ መጠን ናፍቆኝና ተርቤው አላውቅም…
ናፍቆቴ የቱንም ያህል ቢሆን ግን እነሱን ቀድሜ መውጣት በአይን አውጣነት የሚያስፈርጀኝ መስሎ ስለተሰማኝ እንደምንም ስሜቴን ተቆጣጥሬ እየታገስኩ ነው፡፡እነሱ በእርጋታ የሚንቀሳቀሱትን ሽማጊሌውን አስቀድመው እየተጎተቱ ክፍሉን እስኪለቁልኝ መጠበቅ ግድ ሆነብኝ፡፡ይባስ ብሎ አባቴ ወደእኔ መጣ፡፡ተጠመጠመብኝ ፡፡ምን ላድርግ …?መልሼ በተመሳሳይ አቀፍኩት፡፡ለዚህች ቀን አይደል ስንት ወር ሙሉ ሲወተውተኝ የነበረው?እሱ ያልተደሰተ ማን ይደሰታል……?ግን እሱ ያላወቀው እንዲህ መታቀፍ ያለብኝ እኔ ሳልሆን ፌናን መሆኗን ነው፡፡ግድ የለም ..እሱ እኔን ባቀፈኝ መጠን እኔ ደግሞ ከደቂቃ ቡኃላ እሷን አቅፋታለው፡፡.ጭምቅ አድርጌ አቅፋትና ምስጋናዬን አቀርብላታለው፡፡ምስጋናዬን ብቻ ሳይሆን ዛሬ ማታ አፕል አበረክትላታለው፡፡አዎ ጥንት ግሪካዊያን ለሚያፈቅሩት ሰው አፕል ነበር የሚልኩት አንተም የምታፈቅረኝ ከሆነ ከዝግጅቱ ቡኃላ አፕል ላክልኝ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው አይደለ ያለቺኝ?ዋው..ማታ እራት ጋብዛታለው::ከዛ አፕል እሰጣታለው::አፕሉ ውስጥ ደግሞ ቀለበት ይኖርታል::አብረቅራቂ የአልማዝ ቀለበት::ይህንን በማሰቤ ውስጤ ዘላለማዊ በሚመስል ደስታ ተጥለቀለቀ
‹‹በጣም ነው ያኳራኸኝ…እጅግ በጣም ከጠበቅኩት በላይ ጀግና ሆነህልኛል ለካ?አሁን እርግጠኛ ሆነህ ካማፓኒውን በቋሚነት ለመረከብ ተዘጋጅ..››አለኝ አባቴ ሌሎቹ ሊሰሙት በማይችሉት ዝቅተኛ ድምጽ
‹‹እሺ አባዬ አመሰግናለው፡፡››
‹‹ና እንውጣ›› አለኝና ትከሻዬን በኩራት አቅፎ ወደውጭ ይዞኝ ወጣ::በራፍ ላይ እንደደረስን በሃያ ሜትር ርቀት ፌናን ቀድመውን ከወጡት ጋሽ ከበደ እና ከወ/ሮ ክብረወርቅ ጋር ሲያወሩ ለዛውም እየተሳሳቁ ተመለከትኩ
እኔም አባቴም ሳንነጋገር እርምጃችንን እዛው በራፍ ላይ ገታነው::እንዴት አምሮባታል ?ይህ ሁሉ ውበት እንዲህ ጎልቶ እና ፈክቶ የወጣው ከእራሷ ከአፈጣጠር ነው ወይስ ከአለባበሷ…?ልቤ እንደለመደችው ቅልጥልጥ አለች…ግን ከሰዎቹ ጋር የት ተዋውቃ ነው እንዲህ በመፈንጠዝያና በፈገግታ የምታወራቸው……?
‹‹አንተ ተፋላሚህ መታልሀለች::ደግሞ እንዴት ታምራለች……?ልክ እንደእናቷ ››አባቴ ነው በአድናቆትና በስጋት መሀከል በሚዋልል ስሜት የተናገረው…
‹‹አባ እሷ አይደለችም::ይህቺ እኮ የእኔ ረዳት ነች››አረምኩት
‹‹እርግጠኛ ነህ…?ፎቶዋና እኮ እናትዬው ያሳየቺኝ መሰለኝ..ለማንኛውም ና ወደ እነሱ እንሂድ..››አለኝና ተያዘን ስራቸው ደረስን …ፌናን ዞር ብላ እንዳየችኝ ተሸከርክራ ተጠመጠመችብኝ….በጣም እንደናፈቀቺኝ ያወቅኩት ሁሉም እያዩኝ ያለይሉኝታ ልክ እንደ ህጋዊ እጮኛዬ አቅፌ በአየር ላይ ሳንጠለጥላት ነው….
አባቴ ‹‹ክብረወርቅ ልጅሽ ነች እንዴ…?››ብሎ ሲጠይቅ በጆሮዬ ገባ..
‹‹አዎ ልጄ ነች::ፌናን ሰላም በይው…››የሰማውትን መልስ ማመን አቃተኝ….. ምንድነው እየተካሄደ ያለው..?.ከእሷ ሸሸት እልኩና እናትዬው ላይ አፈጠጠኩባት
<<…ምን ተፈጠረ …?በሚል ግራ በተጋባ አሰተያየት ንግግሯን ቀጠለች‹‹እንዲህ ምትግባቡ አይመስለኝም ነበር››ለእኔ ነው የምትለኝ ፡፡
‹‹ፌናን ያንቺ ልጅ ነች…?››አንቱነታውንን እረስቼ የአባቴን ጥያቄ መልሼ ደገምኩ
‹‹አዎ ..ፌናን ልጄ ነች..ምነው …?አልነገረችህም እንዴ……?››
ወደ እሷ ተንደረደርኩና ሁለት ትከሻዋን ጨምድጄ ያዝኳት …ሶስትም ደነገጡ‹‹በጣም ባለጌ ነሽ..በጣም አታለሺኛል..መቼም ይቅር አልልሽም….››
ይሄን ሁሉ ስላት እሷ ምንም እንዳልተፈጠረ በግማሽ ፈገግታ እያደማጠቺኝ ነው…ገፍትሬ አባቴ ትከሻ ላይ ወረወርኳትና ወደቢሮዬ ተንደረደርኩ…
‹‹ምንድነው ነገሩ?ልጄን ምን አደረጋችሁት…?››የአባቴ ድምጽ እየተሰማኝ ነው…ቤሮዬን ገባውና ከውስጥ ቀረቀርኩ.. ቢያንኳኩም ልከፍትላቸው አልፈለኩም..ትንሽ ይብረድለት ብለው መሰለኝ ትተውኝ ዞር አሉ….እኔም ምፈልገው ያንን ነበር፡፡
…….ታንቄበት የዋልኩትን ከረባት ከአንገቴ ፈትቼ ጥዬ ኮቴን አውልቄ በመወርወር ወንበሬ ላይ ቁጭ ብዬ አንገቴን ጠረጳዛ ላይ ደፍቼ አነባው ጀመር::እንዲህ አይነት ለቅሶ ካለቀስኩ ስንት ዓመት እንዳለፈኝ ትዝ አይለኝም::ንፍጤ እስኪዝረከረክ ድረስ ነው ያለቀስኩት፡፡በህይወቴ አንድ ሰው በዚህ መጠን ተጫውቶብኝና አታሎኝ አያውቅም::እንዴ አምኜያት ነበርኮ..?በአድናቆት ፈዝዤያለት አፍቅሬያትና ብዙ ብዙ ህልም አልሜላት ነበር…?እንዴት አንዲህ ትሰብረኛለች?ይህችን ካምፓኒ ለማስተዳደር ብላ……?እኔ እኮ ከካምፓኒው ስራ በላይ ነበር ያፈቀርኳት…
…እያንዳንዷን የሰራዋትን ጥናት ቃል በቃል ታውቀዋለች፤ ምክንያቱም አብረን ነው የሰራነው.፡፡ስለዚህ የእሷ ዝግጅት የእኔን ጥናት አይታና ከእዛ በበለጠና ያንን በሚያጠቃ መልኩ ለማዘጋጀት እድሉን አግኝታለች… .በዛ ላይ ችሎታዋን አውቃዋለው..እና እንዴት ነው ከእሷ በልጬ ይሄን ቦታ የማገኘው…?ተዋረድኩ….፡፡በቃ ሁሉ ነገር አስጠላኝ ::ስራው አስጠላኝ ..ካምፓኒውም አስጠላኝ ..ያፈቀርኮት ልጅ አስጠላቺኝ…ሀገሬም አስጠላቺኝ …፡፡መመለስ አለብኝ…አዎ ወደመጣውበት ሀገር እመለሰላው..ስደት ይሻለኛል..ስራዬን እየሰራው ሶስትኛ ዲግሪዬን ብማር ይሻለኛል..::እንደውም በተጨማለቀ ሀገር የተጨማለቀ ኑሮ ለመኖር ምንድነው እንደዚህ አፈር የሚያስግጠኝ..…?ወሰንኩ…እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረግኩ…ኮምፒተሬን ከፈትኩና መጻፍ ጀመርኩ…ለቦርድ አባላቱ ነው::የካምፓኒውን ስራ ስለማልፈልገው ውድድሩ እንዲቀርና ስራውንም በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን የሚገልጽ ደብዳቤ …ፕሪንት አድርጌ ፈረምኩበትና ኮቴን መልሼ በመልበስ ወጣው…ሰራተኞቹ ሁሉ ለምሳ የወጡ ቢሆንም ጸሀፊዬ ግን ስጠብቀኝ ነበር….
‹‹አሁን የቦርድ አባሎቹ ሲመጡ ይሄንን ማመልከቻ አስገቢልኝ›› አልኩና በካኪ ፓስታ የታሸገውን ማመልከቻ ሰጠዋት
‹‹አባትህ ደጋግመው ሲደውሉ ነበር…ምሳ እየጠበቅንህ ነው ፤ደውልኝ ብለውሀል…››
‹‹ዝም በይው::ስልኬን ዘግቼዋለው …ከደወለ ወጥቼ እንደሄድኩና እንደማልመለሰም ንገሪው……››
‹‹አንተ ግን ሰላም ነህ…?›ሁኔታዬ ስላላማራት መሰለኝ የጠየቀቺኝ
‹‹ሰላም ነኝ ….አመሰግናለው…››ጥያት ወጣው…..

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
.:
#ፍቅር_ከፈላስፋ





ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ (የመጨረሻ ክፍል)


❤️ፌናን
===
ይሄ እንደሚፈጠር ቀድሞውኑም ጠብቄያለው::ቀድሜ መናገር
ነበረብኝ …ግን ልረብሸው ስላልፈለኩ ነበር እንደዚህ ያደረኩት
::.ሁኔታውን እንዳወቀ አባቱ ትከሻ ላይ ገፍትሮኝ እየተመናጨቀ
ቢሮው ገብቶ ከዘጋ ቡኃላ ሶስቱም ነበር ያፈጠጡብኝ….
‹‹ምንድነው ልጄን ያደረጋችሁት…? ››አሉ አባቱ…..ያው
ያደረግሽው ለማለት ፈልጎ ነው፡፡
‹‹ምንም ያደረኩት ነገር የለም::ግን ተወዳዳሪው እኔ ትሆናለች
ብሎ ስላልጠበቀ ነው የተበሳጨው››መለስኩ
‹‹በዛማ አይበሳጭም::ጥናቱን ሲሰራ ምትረጂው አንቺ ነበርሽ
አይደል…?››
‹‹አዎ …በሙያዬ ፕሮፌሽናል በሆነ ደረጃ
ረድቼዋለው::የማውቀውን ምንም ወደኃላ አላልኩም::ምነው
ጥናቱ አሪፍ አልነበረም እንዴ…?››
‹‹ጥናቱማ ሁላችንንም ያስደመመ እንከን አልባ ነበር…››መለሱ
አባቱ ግራ በተጋባ ስሜት
‹‹ስለዚህ ምንም ያጠፋውት ነገር የለም ማለት ነው››መለስኩ
‹‹ልጄን አባሳጭተሸዋል…የክብረወርቅ ልጅ መሆንሽን አለመናገርሽ
አግባብ ስራ አልነበረም..››በጋለና በሞቀ የንዴት ስሜት
‹‹በቃ ልጄ ላይ አትጩሁባት ..ካልፈለገች አለመናገር መብቷ
ነው::የበደለችው ነገር ከለ ወይም ጥናቱ ላይ ያሳሳተችው ነገር
ካለ ለቦርዱ አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል…››እናቴ ተንዘረዘረች
‹‹በቃ አቀዝቅዙት..አሁን እሱ ትንሽ ይረጋጋ እኛ ወደ ምሳው
እንሂድ››አቶ ከበደ ናቸው የተናገሩት
‹‹ሂዱ እኔ ከልጄ ጋር ነው የምበላው ..ጠብቀዋለው››
‹‹ተው አንተ ደግሞ ሰው ሚልህን ስማ ..ትደውልላታለህ ፡፡ቀለል
ብሎት በወጣ ሰዓት ይቀላቀለናል..››ብለው አሳመኑትና የቢሮውን
ህንፃ ለቀን ወጣን..እኔ ግን አብሬያቸው ወደ ሆቴል አልሄድም
አልኩ::ቢቆጡኝም አለሰማዋቸውም::ብቻዬን መሆን ነው
የፈለኩት::የሰራውትን ነገረ ሁሉ አምኜበትና አስቤበት ቢሆንም
ፍሰሀን የመከፋት መጠን ባየው ጊዜ ከፋኝ::ይሄን የመከፋት
ስሜት ደግሞ ብቻዬን ነው ማጣጣም የምፈልገው….
እንግዲህ ለአምስት ሆነን ልንቋደስ የነበረው የምሳ ፕሮግራም
ወደ ሶስት ሰው ዝቅ አለ ማለት ነው፡፡
ሰዓቱ ከቀኑ 8፡10 ሆኖል ፡፡አሁን እራሴን አረጋግቼ ቅድመ
ዝግጅቴን ጨርሼ ሶስቱ የቦርድ አባላት ፊት ለፊት
ቆሜያለው::የጥናት ወረቀቴን ከቦርሳዬ አወጣውና ለሶስቱም
አደልኩ::ሶስቱም ላይ ግራ መጋባት አየው::ሽማግሌው አቶ ከበደ
ግራ ገብቷቸዋል::የፍሰሀ አባት ፈገግ አሉ ::እናቴ ፊቷን
ጨመደደች እና እንደውም ይባስ ብላ በንቀት መልክ ከ10 ገጽ
የማይበልጠውን የጥናት ወረቀቴን በሁለት ጣቷ አንጠልጥላ
እያወዛወዘች‹‹በቃ››አለቺኝ
‹‹ምኑ…?››
‹‹ለወራት ውስጥ ያዘጋጀሽው የመወዳደሪያ የጥናት ወረቀትሽ
ይሄው ብቻ ነው…?››ምን ታርግ መቶ ገፅ ሊሞላ ትንሽ ገጽች
ከሚጎድሉት የፍሰሀ የጥናት ወረቀት ጋር ስታነፃፅረው ከወዲሁ
ሀሞቷ ፈሶ ነው፡፡
‹‹አንዴ የቀረበው ቀርቦል…. እንስማው››አለ የፍሰሀ አባት
ጨፍግጎት የነበረው ስሜት ለቆትና ኩርፊያውንም ረስቶት..
‹‹እሺ ቀጥለላው.. ››ስል..በራፉ ተንኳኳ::ፍሰሀ ሊበጠብጥን
መጣ ይሆን እንዴ……?ወዲያው በሀሳቤ የተሰነቀረ ክፉ ሀሳብ
ነበር
‹‹ይቅርታ… ››አልኩን ሄጄ ስከፍት የፍሰሀ ፀሀፊ ነች
‹‹ይቅርታ ይሄን ለእነሱ ልሰጥ ነበር››አለቺኝ የሆነ ካኪ ፖስታ
አንከርፍፋ
‹‹አንጪ እኔ ልስጥልሽ››
እንደማቅማማት እያለች ሰጠቺኝ..በራፉን ዘጋውና ሂጄ ለጋሽ ከበደ
ሰጠዋቸው..
‹‹ምንድነው…?››
‹‹እኔ እንጃ የፍሰሀ ፀሀፊ ነች ያመጣችው››
<<.አባትዬው ከጋሽ ከበደ እጅ ፓስታውን መንጭቀው ተቀበሉትና
ሸረከቱት …ከዛ ለብቻቸው ያነቡት ጀመር…ምን ይፈጠር ይሆን…?
ብለን ሌሎቻችን በንቃት እየጠበቅን ነው ‹‹ያው ደስ ይበልሽ
ያለውድድር አሸንፈሻል››አሉኝ አንብበው እንደጨረሱ እኔ ላይ
አፍጥጠው
‹‹ምንድነው እሱ…?›› ጋሽ ከበደ ናቸው ጠያቂው
‹‹ያው ስራውን አልፈልግም የሚል ማመልከቻ ነው ያስገባው…
መቼስ ይሄንን አይነት ስውር ብልሀት ከእናትሽ ነው
የወረሺው::ሳትፋለሚ በብልጠት ማሸነፍን ››
‹‹ሰውዬ ምን እያወራህ ነው…?››እናቴ ነች በእሱ ልክ ግላና
እየተንዘረዘረች ዘራፍ ተደፈርኩ በሚል ሰሜት የተናገራቸው
‹‹በቃችሁ…››እኔ ነኝ መሀከል የገባውት..‹‹ይሄ የልጆች ጫወታ
አይደለም::እናንተ በመሀከላችሁ ያለውን የግል ንትርክ በአኔ
አሳባችሁ ማወራረድ አትችሉም::እኔ የተዘጋጀውበትን ሳለቀርብ
ከዚህ አልወጣም::ሳልወዳደርም ማሸነፍ የምፈልግ ሰው
አይደለውም::ምክንያቱም የፍሰሀ አባት አንድ የማያውቁት ነገር
ያለ ይመስለኛል… እኔ የእናቴ ልጅ ብቻ ሳልሆን የአባቴም ልጅ
ነኝ::አባቴ ደግሞ ገነትም ቢሆን በአቋራጭ እንድገባ አድርጎ
አላሳደገኝም…. ››
ጋሽ ከበደ በዛ እርገታቸው መሀከል ገቡ‹‹እወነቷን ነው…የፍሰሀን
ጉዳይ ቡኃላ እንዴት ማድረግ እንዳለብን እንመክራለን::ፕሮግራሙ
ግን በዕቅዱ መሰረት መቀጠል አለብን::ትልልቅ ሰዎች አይደለን
እንዴ…? ስሜታዊ መሆን አሁን ምን ይረባል……?››
‹‹መልስ እንዲመልሱ እድል ሳልሰጣቸው ቀጠልኩ
‹‹አመሰግናለው::ምን አልባት ያቀረብኩት የጥናት ወረቀት መጠን
አነስ ያለች በመሆኗ ከተመደበልኝ ጊዜ ውስጥም ስልሳ ፐርሰንቱን
ብቻ ተጠቅሜ ሙሉውን ዝግጅት ለማጠናቀቅ
እሞክራለው::ስለዚህ ሁላችሁም ምናባችውን ሰብሰብ አድርጋችሁ
በትኩረት እንድትከታተሉኝ እየጠየቅኩ ቀጥታ ወደ ገለፃዬ
እገባለው፡፡››
ካምፓኒው የተቋቋመበት ዓላማ ምንድነው…?ለካምፓኒው
ባለቤቶች ደለብ ያለ ትርፍ በየዓመቱ ማስገኘት?መቶና ሁለት መቶ
ለሆኑ ዜጎች ቋሚ ስራ መፍጠር .. …?ከ5መቶ እስከ 1 ሺ
ለሚሆን ጊዜያዊ ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠር..…?ለመንግስት
ግብር በማስጋባት የዜግነት ግዴታን መወጣት…? በቃ ይሄ ነው
…..…?
እርግጥ ሶስት ሰዎች ያቋቋሙት ካምፓኒ እንዲህ ውጤታማ ሆኖ
በዚህ መጠን ለሌሎችም ሆነ ለሀገር ጥቅም ከሰጠ አስደሳች
ነው…ስኬታማ የሚያሰኝ ነው…ግን በእኔ አስተያየት ተራ ስኬትና
ተራ አላማ ነው፡፡….እኔ ይሄ ካምፓኒ ልዩ እና የማይቻለውን ነገር
አስችሎ ለመላ ሀገሪቱ እንዲያሳይ ነው የምፈልገው…
ኢትዬጵያ 20 ሚሊዬን ዜጎቾ ከድህነት ወለል በታች የሚኖሩባት
ሀገር መሆን ነበረባት…?ዘወትር በስደት በየባህሩ የምናልቅ
ህዝቦች መሆን አለብን…? ፡፡ይሄ ቁጭት በውስጤ አለ ፡፡ከዚህም
ቁጭት የተመዘዙ የራሴ የሆኑ ሁለት እቅዶች አሉኝ፡፡አንደኛ
በሚቀጥሉት አስር አመት ውስጥ ውጤታማ የቢዝነስ ሰው
በመሆን ሀገሬንና ህዝቤን መርዳት …ሁለተኛ ከአስርአመት ቡኃላ
በቢዝነስ ያገኘውትን እውቅና እና ጥበብ ይዤ ወደፓለቲካ
መግባት እና የዛሬ ሀያ አመት ከተራዘመም ሀያ አምስት አመት
ድረስ ይህቺን ሀገር መምራት …
‹‹ማለት…?››አለች እናቴ በአግራሞት..
‹‹ጠቅላይ ሚኒስቴር መሆን…እና ይህን የሀብት ምንጫችሁ ብቻ
ሳይሆን የስማችሁ መጠሪያ የሆነውን ካማፓኒያችሁን የምፈልገው
መጀመሪያ ለራሴ አላማ ነው…፡፡ካፓኒውን በተለየ መልኩ
ውጤታማ አድርጌ ለዚህች ሀገር የቢዝነስ ሞዴል እንዲሆን
በማድረግ የራሴን ስም መገንባት::ያንን ማድረግ ከቻልኩ
የእናንተን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የራሴንም ህልም ነው
የማጨልመው…
እና እንዴት አድርገሽ ነው የተለየ ካምፓኒ የምታደርጊው……?.በእኔ
እምነት በአሁኑ የካማፓኒ አካሄድ ለሀገሪቱ እድገት እየተጋለ እና
የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው? አዎ ትክክል ነው…
በተቃራኒውን ለሀገሪቱ ውድቀትም በተመሳሳይ አስተዋጽኦ ቀላል
አይደለም…
ንግግሬን ገታ አድርጌ የሶስቱንም ፊት ሳይ ልጅቷ አብዳለች እንዴ
👍8
#ፍቅር_አለማማጁ!


እኔና ቤቲን ያገናኘን እንጀራ ነው እህል ውሃ። Destiny ወይም እጣፈንታ ልትሉት ትችላላችሁ፡፡ እኔ የድርጅቱ የሂሳብ ሹም ሆኜ በተቀጠርኩ በመንፈቄ፣ ቤቲ ፀሐፊዬ ሆና ተቀጠረች፡፡
የሚያስደነግጥ መልክና ቁመና የላትም፡ ግን ከዚያ የማይተናነስ ቀልድና ጨዋታ አዋቂ ናት፡፡
ወንዶችንም ሴቶችንም እኩል መማረክ የሚችል አንደበት ተችሯታል እኔንም የማረከችኝ በዚሁ
አንደበቷ ነበር ቤቲ ሲበዛ ቀልደኛ ናት የዕድል ጉዳይ ሆኖ ነው እንጂ ቦታዋ የእኔ ቢሮ ሳይሆን የኮሜዲ መድረክ ነበር እሷ ከመጣች በኋላ
መ/ቤታችን የሳቅ አዝመራ ሆኗል በእርግጥ አንዳንድ አስደንጋጭ ቀልዶች ተናገራለች፤ አጥንት ከሥጋ የሚለያዩ በቀልዶቿ ደንግጠው
የሸሹ ግን አላየሁም ከልጅነት ባልንጀራዬ ከቢኒ በቀር እኔና ቢኒ እንደወንድማማቾች ነው
ያደግነው። አንድ ሰፈር ብይ ተጫውተን፣ አንድ ት/ቤት ተምረናል ዩኒቨርስቲ ስንገባ
ተለያየን፡፡ እሱ ኢንጂነሪንግ ሲያጠና፣ እኔ አካውንቲንግ አጠናሁ። እሱ ባህርዳር ሥራ
አግኝቶ ሲሄድ፣ እኔ አዲስ አበባ ቀረሁ፡፡ እሱ ከሥራ ባልደረባው ጋር ፍቅር ሲጀማምር፣ እኔ የፍቅር ጓደኛዬን አለምኩ በሁለተኛ ወሬም፣ ቤቲን ጣለልኝ ቢኒ በዓመቱ ነው ዳጎስ ያለ ደሞዝ የሚያስከፍለውን የባህርዳር
ሥራውን ጥሎ ሸገር የመጣው ምን ሥራውን ብቻ! ፍቅረኛ ያላትንም ጭምር እንጂ የድሮ ሸጋ ባህርዩንም ባህርዳር ጥሎት የመጣ ይመስለኛል ተግባቢና ተጫዋች የነበረው ቢኒ፤ በዓመት
ጊዜ ውስጥ እልም ያለ ተጠራጣሪ ሆኖ ነው የመጣው፡፡ ብዙ የእሱ ያልነበሩ እንግዳ ጠባዮችም አምጥቷል መቆጣት
መነጫነጭ፣ ማማረር እና ሌሎችም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሆኖ ሆኖ ግን አዲስ አበባ መምጣቱን ከሰማሁ ጊዜ ጀምሮ ፍቅረኛዬን ላስተዋውቀው ብዙ
ለፋሁ። ለእኔ የበኩር ፍቅረኛዬን ለልጅነት ባልንጀራዬ ማስተዋወቅ ትልቅ ትርጉም ነበረው፡፡ ሸጋ የህይወት ጓደኛ መምረጤን እየነገረኝ፣ ቢያደንቅልኝ ደስታዬ ነበር፡፡ድሮ የማውቀው ቢኒ ደግሞ የአድናቆት ስስት የለበትም፡፡ አሁን
እሱ ራሱ መች ጭራው ተይዞ! ከስንት ጊዜ በኋላ እንደምንም እሺ አሰኘሁት፡፡
የተቀጣጠርንበት ሆቴል ቀድመን የደረስነው እኔና ቤቲ ነበርን፡፡ ከ20 ደቂቃ በኋላ ቢኒ መጣ። ከወደፊቷ የትዳር አጋሬ ጋር አስተዋወቅሁት፡፡
እሱቴ! አልሞቀውም አልበረደውም፡፡ ቤቲ ከፍቅር ጋር የተገናኙ ቀልዶችን በተከታታይ አዘነበችልን። ብዙዎቹን እኔ ራሴ ሰምቻቸው አላውቅም ይሄን ሁሉ ያደረገችው የልጅነት ባልንጀራዬ ዘና እንዲልና የመግባባት ስሜት ለመፍጠር ነበር ግን
አልተሳካላትም፡፡ በቀልዶቿ የምንስቀው እኔና እሷ ብቻ ነበርን ቢኒ ተሳስቶ እንኳን ጥርሱን ብልጭ አላደረገም፡፡ እሷ ግን ተስፋ ሳትቆርጥ በኩመካዋ
ገፋችበት “ምነው…የተደበርክ ትመስላለህ? እኔ እኮ መቼ ተዋውቄው ስል ነው
የከረምኩት”አለችው፤ ዓይን ዓይኑን እያየችው፡፡
ደንገጥ አለና ተመለከታት፤ ኮስተር
ብሎ፡፡“የምሬን ነው… ትላንት ሳሚ እንደቀጠረህ ሲነግረኝ ጉጉቴ ጨመረ፤ የቀጠሮ ሰዓቱ አልደርስ
አለኝ” ስትል አከለችለት፡፡ ይኼኔ የተለጎመው አፉ ተፈታ “ምነው በደህና?” ጠየቃት፤
በጥርጣሬና በጉጉት ስሜት ተሞልቶ “ምን መሰለህ… ሳሚ፤ ፎቶህን ሲያሳየኝ በአካልም እንዲህ ከሆነ ወደ እሱ እቀየሳለሁ ብዬው ነበር…” አለች ቤቲ - በዓይኗ እየጠቀሰችኝ፡፡ እንዲህ አይነት ኩምክና ለእኔ የተለመደ ስለሆነ ምንም አልመሰለኝም ቢኒ ግን
እንደአራስ ነብር ቱግ አለ የባሰ አታምጣ ማለት ይሄኔ ነው “የሴት ቀልደኛ ደሜን ነው የምታፈላው!” እያለ ከተቀመጠበት ተነሳ “ሳሚ፣ ህይወቴን ያበላሸችብኝ እንደዚህች ያለችው ፎጋሪ ነኝ ባይ ናት…እቺም ጉድ እንዳታደርግህ!”
አለና ከሆቴሉ የማምለጥ ያህል ተጣድፎ ወጣ፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን እምብዛም ድንጋጤ የማይጐበኛት ቤቲ፤ ለአፍታ በዝምታ ተውጣ
ቀረች፡፡ ለማጫወት ያደረገችው
ሙከራ እንዲህ በጠብ ይጠናቀቃል
ብላ አላሰበችም ነበር “ሳሚዬ ፈተናውን ወድቋል…
አንተው ትሻለኛለህ!” ስትል እየቀለደች፣ ከንፈሬ ላይ ከንፈሯን አሳረፈች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከወር በኋላ ቢኒ ጋ ደውዬለት እንድንገናኝ ጠየቅሁት “የሴት ቀልደኞች እጣ ክፍሌ
አይደሉም … ካለች ግን ከበር ነው የምመለሰው!” ሲል አስጠነቀቀኝ ባህርዳር በመሃንዲስነት
በተቀጠረበት የግል ኮንስትራክሽን ድርጅት ውስጥ ለጥቂት ወራት እንደሰራ ነበር አንዲት ልጅ እግር መሃንዲስ ከሌላ ቅርንጫፍ
ተዛውራ፣ ወደ እነቢኒ ክፍል የመጣችው ማህሌት ትባላለች፡፡አለቃው እንደቀልድ
“አለማምዳት” ብለው ለእሱ
አስረከቡት እሱ ግን የምር አደረገው፡፡
የኪስ ቦርሳውን አውጥቶ ሁለት ፎቶዎቿን አሳየኝ፡፡ ውበቷ እንደሰማይ ክዋክብት ይንቦገቦጋል።
በዚያ ላይ ሽቅርቅር ናት! ቢኒ እሷን ማለማመድ ዋናው ስራው አድርጐት ቁጭ አለ ጠዋት ከቤት
ወደ ቢሮ ይዟት ይመጣል- በኮንትራት ታክሲ፡፡ በሻይ ሰዓት አብሯት ነው ማታ በውድ ሆቴሎችና
ሬስቶራንቶች እየጋበዘ ህልሟን፣ ተስፋዋንና ቅዠቷን ሰምቶ ወደ ቤቷ ይሸኟታል፡፡ የማታ ማታም
አለማምዳለሁ ብሎ ተለማመዳት በልቡ ፍቅር አረገዘ፡፡ እሷ ደግሞ ቀልዷና ቁምነገሯ አይለይም፡እንደልጅነት ዘመኑ “ባሌ” እያለች
ልታሳፍረው ትሞክራለች። ፍቅረኛ
ይኑራት አይኑራት የሚያውቅበት
ፍንጭ አልነበረውም “አለማምዳት” ያለው አለቃ “ራት ልጋብዝሽ” ሲላት “ቢኒ
ቦይፍሬንዴ ነው” ብላ እንዳስደነገጠችው ነግራዋለች ለቢኒ ነግራዋለች አንድ ቀን
ያረገዘውን እንደምንም አምጦ ተገላገለው። ለማህሌት እውነቱን ነገራት የሚገርመው ግን
ነገርየው ዱብዕዳ አልሆነባትም ቢኒ…“ጊዜ ስጠኝ፤ ላስብበት” ለቢኒ ይሄም ቢሆን አስፈንጥዞታል ምላሿ አዎንታዊ ይሆን ዘንድም
ነፍስ ካወቀ ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ
ቤተ ክርስቲያን ሄዶ ስለት ተሳለ ወራት እንደዘበት ነጎዱ፡፡ በእርግጥ የተለመደው ግንኙነታቸው
አልተቋረጠም፡፡ ግን ምላሽ የለም ቢኒያም ፍቅሩን
ልታረሳሳው የሁሉ ፈለገች መሰለው ከራሱ ጋር ብዙ ከተማከረ በኋላ ፍቅሩ አስታወሳት
“ቢኒዬ… አልወሰንኩም እኮ!” አለችው፤ በሚንቆረቆር ድምጿ“እስካሁን?” አላት፤ ተገርሞ፡፡
“ያጣደፉት ፍቅር…” የሚለውን ዘፈን በሚወድላት ድምጿ አቀነቀነችለት (አትቸኩል ለማለት!)
ቢኒ ራሱን ታዘበ “እውነቷን እኮ ነው … ምን አጣደፈኝ?” አለ፡፡ ግን ምን ያህል ጊዜ እንደሚስፈልጋት ቢያውቅ አይጠላም ነበር፡፡
የዛን እለት እንደወትሮው ወደ ቤቷ ከሸኛት በኋላ ወደ ቤቱ አልሄደም ቢመሽም ቤተክርስቲያን ሄዶ
ፈጣሪውን ተለማመነ ጠዋት ከእንቅልፉ የቀሰቀሰው የሞባይሉ ቴክስት ሜሴጅ (SMS)
ነበር፡፡ እየተጨናበሰ ሞባይሉን ከኮመዲኖው ላይ አንስቶ መልሶ
አስቀመጠው። ትንሽ ቆይቶ ግን
ከአልጋው ላይ ተስፈንጥሮ ተነሳና
ሞባይሉን አፈፍ አደረገ፡፡ የሜሴጅ
ሳጥኑን የሚከፍተውን ቁልፍ ተጫነ፡፡ ዓይኑን አላመነም ጽሑፉን ትክ ብሎ ተመለከተው፡፡ ያው ነው። “ቢኒዬ… የህይወት ዘመን ሽልማት ትፈልጋለህ?
አሸንፈሃል! እኔን!!” ይላል - የማህሌት መልእክት። ስሜቱ ድብልቅልቅ አለበት፡፡ ደስታ…ድንጋጤ..ጭንቀት… ብዙ
ስሜቶች አፈኑት፡፡ ሁሉንም አስተናግዶ ሲጨርስ ወደ አቅሉ ተመለሰ፡፡ ስልክ ሊደውልላት ወይም መልእክት ሊልክላት አሰበ። ከዚያ በፊት ግን አንድ ነገር ትዝ አለው - ስለቱ! ከመቅፅበት ከአልጋው ወርዶ ልብሱን መለባበስ ጀመረ “ስለቴ
ሰመረልኝ”ን በልቡ እያዜመ፡፡ በቀጥታ ያመራው ወደ ቤተክርስቲያን ነበር፡፡ ስለቱን የቤተክርስቲያኑ ሳጥን ውስጥ
ለማስገባት ሲታገል፣ ሌላ ቴክስት

ሜሴጅ አንቃጨለ፡፡ ስለቱን ታግሎ
አስገባና ሞባይሉን ከኪሱ አወጣ
👍2
እንዴት ናቹ #የአትሮኖስ ቻናል ቤተሰቦች እንደሚታወቀው #ሁቱትሲ የተሰኘው ድርሰት በትላንትናው እለት ተጠናቋል ያላችሁንም አስተያየት በውስጥ መስመር እየገለፃችሁልኝ ነው ለዚህም ከብዛቱ የተነሳ ለሁሉም መልስ መስጠት ስላልቻልኩ ይቅርታ እየጠየኩ ባጠቃላይ ግን ሁላችሁንም ከልቤ ማመስገን እፈልጋለሁ። 🙏

ሌላው በቅርብ ቀን ልንጀምረው ያሰብነው
ረጅም ታሪክ አለ ከነዚህም ውስጥ ለጊዜው 3 አሉ ከነዚህ ውስጥ አንዱን መርጦ ለመጀመር የናተ ከፍተኛ ትብብር ያስፈልጋል

መጀመርያ ከታች ከማስቀምጣቻው ምርጫዎች ውስጥ በናተ በከፍተኛ መጠን የተመረጠውን ቅድምያ አቀርባለው

ሌላው #MUTE አድርጋችሁ የምትጠቀሙ የቻናሉ ቤተሰቦች ፅሁፍ ማዘጋጀት በጣም ከባድ ነው አንዳንድ ቻናሎች ላይ እንደምታዩት ሌላ ቻናል ላይ ያሉትን ታሪኮች Cope paste አደለም የማደርገው በተቻለ መጠን አዳዲስ ታሪኮችን ይዤ ለመምጣት እሞክራለሁ ለዚህም ደሞ ለናተ በሚመች መልኩ ለማቅረብ ከፍተኛ ልፋት አለው እንዲህ የተዘጋጀውን ደሞ እናተ ካላያችሁት ልፋት ብቻ ነው የሚሆነው እናም እባካችሁ #UNMUTE አድርጋችሁ ተጠቀሙ እኔም ሳልሰለች ለናተ ምርጥ ምርጥ ታሪኮችን ይዤ እመጣለሁ

ከታች ካሉት ምርጫዎች ቅድምያ ይቅረብ የምትሉትን በመምረጥ ተሳተፉ

💚 #ፍቅር_እስከ_መቃብር

💛 #ሮዛ

❤️ #የአና_ማስታወሻ
#ፍቅር_ሲሸሽ

አንድም ፍጡር ላይኖር ከስ'ተት የጸዳ
ሆድሽ እጅግ ጠቦ ልብሽ እጅግ ከብዳ
ጠርጥረሽ ላትበይው
አኝከሽ ላትውጪው
በማላመጥ ብዛት ኮስሶ አኮሰስሽው
ጓዴ የሆነውን ዘርዝሬ ብነግርሽ
በጉዳቱ አዝነሽ
እጅግ ተቆጭተሽ
እምዬ ማሪያምን አብረሽው በቆረብሽ
የጨረቃ ወጋገን ፈክቶ በሰማይ ላይ
አንቀላፍታ ሳለች ምድሪቷ በአንድ ላይ
ፍቅርን ሲለግስሽ ስትሰጪው ፍቅርን
ድንገት አውሬ አይቶ በቁም ሲባንን
ነግረሽው ነበረ ውሻ መሆኑን
ነገር ግን . . . ነገር ግን . . .
ሽሽትን መረጠ ከነፈ ከቤቱ
አንድያ ነውና ለናትና አባቱ
አንቺ ግን . . . አንቺ ግን .
ደብቀሽ ሳትይዥ ይሄ ሚስጥሩን
ሃገር እንዲያውቅ አርገሽ ትንሹ ልቡን
“ ጥንቸሊቱ ” አስባልሽው መጠሪያ ስሙን
ውቢት . . .ውቢት .
ሊሳሳት ይችላል ማንም በቀን ውሎ
ቢሮጥ ምን ነበረ እኔን አስከትሎ
ብለሽ ተቀይመሽ ልብሽን አትዝጊው
ለበጎ ነው ብለሽ ሁሉንም አስቢው
ደ'ሞም ዱብ እዳ ነው አስጨናቂ ብርቱ
አውሬ ሲያጋጥመው ሳያስብ ከፊቱ
ሊሆን ደ'ሞ ይችላል የደፈጣ ስልቱ
ይህን አውሬ ፍጡር ሊያቆስለው በብርቱ
ብለሽ አስቢና አፍቅሪው ካ'ንጀትሽ
ታድያ ምኑ ላይ ነው ሩሩ ሴትነትሽ
ውቢት........
ምን አልባት . . .ምን አልባት . . .
የወሬ ነጋሪ ጭራሽ እንዳይጠፋ
ይሆናል መሮጡ ሳይነግር ከፊትሽ
ሲያወራው ለመኖር ዝነኛውን ፍቅርሽ፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ፍቅር_እንደ ...

የሻማ መብራት ነው
ፍቅር እያልኩሽ
አንቺ ግን የአምፖል ነው
ብለሽ ተቆጣሽ
ቁጣሽን በመፍራት
ድንገት ተጨንቄ
ከመቅረዝ ላየሁት
እኔስ ምን አውቄ
አፍታ እንኳ ሳንቆይ
ሳይጠፋ መብራት
ጨለማ ተዋጥን
አላፊው አግዳሚው እፍ እፍ እንዳሉት፡፡

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#ፍቅር_አያሸንፍም

ህፃን
ልጅ
አዋቂው
ወጣት ሽማግሌው ፥ ረጋሚ መራቂው
በአንደበቱ ማህፀን
ፍቅር ያሸንፋል”
የሚል ጥቅስ አርግዞ ፥ በምላስ ይወልዳል
ፍቅር ግን ሁል ጊዜ
እየተሸነፈ ፣ መሸነፍ ይወዳል።

አቅመ ቢስ ነው አቅሙ ፥ ወዋረድ ነው ልኩ
ሁሌም መሽነፍ ነው
ሁልጊዜ መውደቅ ነው ፥ የፍቅር ታሪኩ።
ርሐብተኛ ነው
አይበላም አይጠጣም ፣ ንብረት አያፈራም
አይደፍርም አይፈራም
አይጠፋም አይሰራም
ፎቅ አይደረድርም ፥ ቪላ ቤት አይሰራም
ማደሪያው በረት ነው ፥ ሲታይ ስጋ ለብሶ
ባሪያ ነው አንግሶ
ሁሌም ዝቅ ያለ ነው ፥ ከፍታ ላይ ደርሶ።

ፍቅር ይሸነፋል!
መንገድ ምራን ላሉት ፥ መንገድ ሆኖ ያርፋል
ሁሉ ይረግጠዋል
መልኮት ኋይል አለው ፥ በሰው ይገረፋል
በሰማይ ሲሾሙት ፥ ወደምድር ይጠፋል
አንድ ሀገር የለውም
የትም ቦታ አለ ፥ እየተሰደደ
ሁሌ እንደተገፋ ፥ እንደተዋረደ
ዝቅ ይሎ ይኖራል
ዝቅ ብሎ ያድራል
ቃል አይናገርም ፥ ስንጥለው ጠልፈን
እርቃን ስናስቀረው
ልብሱን ከአደባባይ ፥ ከገላው ላይ ገፍፈን
ፀሐይ ላይ ተጥደን
ውርጭ ስናስመታው ፥ ስናለብሰው ቆፈን
ከሀገር ስናስወጣው ፥ ካንጀት ተፀይፈን
ጥለነው ስንሔድ ፥ ስናገኘው አልፈን
ትንፋሽ አይወጣውም
ለሁሉ መንገድ ነው ፥ መሔጃ የለውም።
ሁሉን ይከተላል
ለሁሉ ዝቅ ይላል
እረኛ ሲያደርጉት ፥ በግ መሆን ይመርጣል
ዘጠና ዘጠኝ በግ
ሜዳ ላይ በትኖ
አንድ የጠፋ በጉን ፥ ፍለጋ ይወጣል
አይቀድም ይሮጣል
አይሸሽም ያመልጣል
አይተኛም ያደፍጣል
ሲሰድቡት ቃል ያጣል
ቃል ሆኖ ይመጣል
ህያው ነው ስንለው
መቃብር ይወርዳል ፥ በሙታን ተገድሎ
ይነሳል ሲቀብሩት ፥ ከሞት ተነጥሎ
ባሪያ ነው ለሁሉ
መንግስቱን የሚያወርስ ፥ ከምንዱባን ውሎ።

አቅሙ አቅመ ቢስ ነው ፥ ሽንፈት ነው እድሉ
ወርዶ መገኘት ነው
ማጎንበስ ነው እጣው ፥ መረታት ነው ውሉ
ዝቅ ብሎ መኖር ነው ፥ እቅድና አቅሉ
ዝም ነው ስንገርፈው
ዝም ነው ስንዘልፈው
ጭጭ ነው ስንጠልፈው
ቃላት አይወጣም
ራሱ ግን ቃል ነው ፥ የቃሉ እስረኛ
ፍቅር ሲሸነፍ ነው
ፍቅር ያሸነፈ ፥ የሚመስለን ለኛ!

ያንሳል ስናገዝፈው
ቀድሞ ይጠብቃል ፥ ትተነው ስናልፈው
እየተሸነፈ
በመሸነፉ ነው ፣ ፍቅር ያሸነፈው።

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር

ያሳለፍነዉ ሁሉ
አሁን ትዝታ እንጂ
ዉስጡ ህይወት የለም እያልሽ ላገሩ
ታወሪያለሽ አሉ


(እኔ ግን ልንገርሽ)
የሁለታችን ፍቅር
ምን እንደሚመስል. . .
እንዴት እንደነበር
በሶስት ምስክር
1
አሁን በቀደም ለት
የሆነ ቦታ ላይ
ድምጻችን ከፍ አርገን የሳቅንበት ቦታ
ፒያሳ አደባባይ
ድንገት
በቀደም ለት
በዛ ቦታ ስሄድ
ከሰባት ወር በፊት
ስቀሽ የነበረዉ
ያንቺ ሳቅ ተሰማኝ
መራመድ አቃተኝ
የሚገርምሽ ነገር
ያለፈ ነዉ ያልሺዉ
ትዝታ ነዉ ያልሽዉ
ፍቅርሽና ሳቅሽ
ከሰባት ወር ኋላ እንደ ወንዝ ፍሳሽ
ይሰማል ልንገርሽ

(ታዲያ ለምንድን ነዉ)
የወንዝ ዉሀ ሳቅሽ
ያለፈ ትዝታ ምናምን ነዉ ብሎ
ማንም ተራ ዘፋኝ የሚሸነግልሽ
(ይልቅ እኔን ስሚኝ)

ወደየትም ሳይሆን
ወዴትም ተመለሽ
የትም ሳትደርሺ
ጊዜን እንዳቆምነዉ
እንኳን ጊዜ ቀርቶ ሰዓት እንዳልሄደ
ደቂቃ እንዳልሄደ
አስረጂ ሊሆንሽ
ምስክር ሊሆንሽ
ከምንም አቅጣጫ. . . የትም ሳትመለሽ
አደባባይ መሀል
ከቡና ጠረን ጋር
እንደወንዝ የሚፈስ
ሳቅሽን ትሰሚያለሽ

2
ትዝ ይልሽ እንደሆን
ካንቺ መኖሪያ ቤት
(የመጣሁኝ ጊዜ)
የመራራቅ ናፍቆት
አስክሮን ቸኩለን
ሰማያት ለመዝለቅ
ከመሬት ላይ ወድቀን
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ፍቅር ስንሰራ
ከሴት ወዝሽ ጋራ
የጡትሽ ስር ሽቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ሸሚዜ ላይ ቀርቶ
ምወደዉን ሸሚዝ
ለመልበስ እርም አልኩኝ
ለብሼዉ እንዳልሄድ
ከበደኝ ጨነቀኝ
ያንቺን ጠረን ማጠብ. . .
ነፍስ የማጥፋት ያህል
ሀጥያት መስሎ ታየኝ
(የሚገርምሽ ነገር)
እስከ ዛሬ ድረስ
በመስኮቱ ዘልቆ. . .በበሬ
የሚወጣዉ የማለዳዉ ነፋስ
በሽቶሽ ጠረን ነዉ መንደሩን የሚብስ

3
ታስታዉሽ እንደሆን
የሆነ ቅዳሜ
የሆነ ዉብ ሆቴል
ደግሞም አትረሺዉም. . .ፍጻሜ ምሳ ነዉ
ይኼ እንኳን ትዝ ይላል
እና. . .
እኔና አንቺ ብቻ
የተቀመጥንበት ወንበር ጠረጴዛዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ. . .
እዛዉ ቤት ዳግመኛ ተመልሼ ባየዉ
የሚገርምሽ ነገር
ጻፊዉን ባላዉቅም
#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር
የሚል ጽሁፍ ሰቅለዉ
ከዘጠኝ ወር ኋላ
አንድ ለብቻዬ ካንድ አንቺ ናፍቆት ጋር
ነበር ለምትይዉ ለሁለታችን ፍቅር
(ምስክር ሊሆኑን)
ያኔ ሁለታችን የጠጣነዉ ወይን
ከወይንም. . . Two Ocean
እኔ የጨለጥኩት
አንቺ ያጋመስሽዉ
እኛ ያስተረፍነዉ
እስከዛሬ ድረስ
ያተረፍነዉ ማዕድ. . .
ጠርሙስና ጽዋዉ
በክብር ተቀምጧል
ማንም ሳያነሳዉ. . .ያኔ እንደነበረዉ
(ታዲያ ምን ማለት ነዉ)



ፒያሳ አደባባይ
የወንዝ ዉሃ ሳቅሽ
ከቡና ጠረን ጋ
ከኔ መኖሪያ ቤት. . .
የምወደዉ ሸሚዝ ላይ
የሽቶ መአዛሽ
ከሴት ላቦትሽ ጋር
ደግሞም
እዚያ ዉብ ሆቴል ስር
ያስተረፍነዉ . . .
ማዕድ ጠርሙስና ጽዋ
አንጀት ከሚበላ
ከቆንጆ ጥቅስ ጋር
‘’#ፍቅር_እዚህ_ቦታ_ፈገግ_ብሎ_ነበር::’’

ነበርን እስካሁን
በመሆን እያየሽ
ሳቅሽ ፈሶ ሳያልቅ
ከምወደዉ ሸሚዝ
የሽቶ መዓዛሽ ዉብ ጠረኑ ሳይለቅ
ማዕድ ሳይነሳ ጽዋዉ ሳይታጠብ
ሦሥቱን ምስክሮች በዓይንሽ ፊት እያየሽ
(ታዲያ ለምንድን ነዉ)
ያሳለፍነዉ ሁሉ
"አሁን ትዝታ እንጂ .....
ዉስጡ ህይወት የለም"
ብለሽ ለመንደሩ
ላገሩ ማዉራትሽ
እዉነት ለምንድን ነዉ?




ኤፍሬም ስዩም
(ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር)
😱1
#ፍቅር_ይዞኝ_እንጂ

መች አስቤው እንደ ሥራ
መች ቆጥሬው እንደ እንጀራ
ጭው ባለው በረሃ ውስጥ
መንከራተቴ ያለ እፎይታ
ቀጥ ባለው ተራራ ላይ
ላቤን ማፍሰሴ ጠዋት ማታ
መች አስቤው እንደ ስራ
መች ቆጥሬው እንደ እንጀራ
የልጆቼ ዓይን በዓይኔ ላይ
ያለ እረፍት ሲመላለስ
ልቻለው ከሃገሬ አይበልጡም
እያልኩኝ የምንከላወስ
ዘመን በዘመን ሲቀየር
በዓል አውድ ዓመት ሲመጣ
ለእንጀራዬ ብዬ ነው እንዴ
ከበረሃ የማልወጣ?
ከዘመድ አዝማድ የማልበላ
ከአብሮ አደጎቼ የማልጠጣ
የያዘ ይዞኝ እንጂ
የሀገር
ፍቅር----- የሚሉት ልክፍት
እኔ ሁለት ሆድ የለኝ
እስክሞት የሚንከራትት
መች አስቤው እንደ ሥራ
መች ቆጥሬው እንደ እንጀራ
ላቤ በጀርባዬ ላይ
የጨው አምድ መስሎ እስኪታይ
ከእረፍት ከእንቅልፍ ተፋትቼ
የማጣው የቅጽበት ፋታ
ቀናትን በእግሬ የምኳትን
ጫማዬን ከእግሬ ሳልፈታ
ለእንጀራዬ ብዬ ነው እንዴ
ቀዝቃዛ ውሃ እየናፈቀኝ
ትኩስ መመገብ እያማረኝ
ጨዋማ ውሃ እየጠጣሁ
በድካም ጨው የሚያልበኝ
ለእጀራዬ ብዬ አይደለም
ርቄ ከመሃል ማዶ
በቀበሮ ጉድጓድ ሆኜ
ምሰማው የናቴን መርዶ
ለእንጀራዬ ብዬ አይደለም
በእህቴ ሰርግ የማልገኝ
በወንድሜ ህመም የማልመጣ
ከሃገሬ አስተሳስሮኝ እንጂ
ወታደር የመሆኔ እጣ
ለእንጀራዬ ብዬ አይደለም
የምቃጠል በበረሃ
የሚያነደኝ ቦምብ ፈንጂ
ቃልኪዳኔ ከሆነችው
ከሀገሬ
ፍቅር ይዞኝ እንጂ

🔘ሻለቃ ወይን ሐረግ በቀለ🔘
#ፍቅር_ከራስ_ያልፋል

በሕይወት ጎዳና ዕጣ ሲደለደል
ላንዱ ሜዳ ሆኖ ለሌላኛው ገደል
ግማሽ ግራ ገብቶት የቀረው ሲበደል
እኔ ዝምተኛው ካንቺ ሆንኩኝ አይደል?
ምርቃቱ ደርሶ ፍቅር ያጠመቀኝ
በየትኛው ዘመን ማነው የመረቀኝ?
በሚሆነው ሁሉ
ግራ ለተጋባው ለዚህ #ላገሬም_ሰው
ከማይሆነው መንገድ ይዞ እንዲመልሰው
መርቆ ሰምሮለት ፍቅር እንዲዳብሰው
ባወኩት ባወኩት ባወኩት ያንን ሰው።

🔘ሰለሞን ሀይሌ🔘
👍13
#ፍቅር_ከራስ_ያልፋል

በሕይወት ጎዳና ዕጣ ሲደለደል
ላንዱ ሜዳ ሆኖ ለሌላኛው ገደል
ግማሽ ግራ ገብቶት የቀረው ሲበደል
እኔ ዝምተኛው ካንቺ ሆንኩኝ አይደል?
ምርቃቱ ደርሶ ፍቅር ያጠመቀኝ
በየትኛው ዘመን ማነው የመረቀኝ?
በሚሆነው ሁሉ
ግራ ለተጋባው ለዚህ ላገሬም ሰው
ከማይሆነው መንገድ ይዞ እንዲመልሰው
መርቆ ሰምሮለት ፍቅር እንዲዳብሰው
ባወኩት ባወኩት ባወኩት ያንን ሰው

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍96👏2
#ፍቅር_የመሸባት_ሀገር


እዛ ሰው ይሞታል፣ እዛ ደም ይፈሳል
እዚህ ይጨፈራል ፣ እዚህ ይደነሳል
እዛ ሰው ያለቅሳል፣እዚህ ሳቅ ይነግሳል።
፨፨፨
እዛም እኛዎች ነን፣አዚም እኛ ባዮች
የደላን እኛው ነን ፣ እኛው ተበዳዮች
አንድነትን ሰብከን፣የምንሆን ብዙዎች፡፡
እኛው ነን የሞትነው፣እኛው ነን ቀባሪ
እኛው ነን ሙሾ አውራጅ፣እኛው ነን ጨፋሪ
አንድ ነን እያልን ፣ ልዩነት ፈጣሪ፡፡
፨፨
እዛ እኛ ስንሞት፣ እዚ እኛ ስንጨፍር
እዛ እኛን ስንቀንስ፣እዚ እኛን ስንደምር
ሙሾን ከደስታ ጋር የምንደባልቀው
እኛው እያነባን ፣ እኛው የምንስቀው
እኛው ለነፃነት ፣ ታግለን የምናልቀው
እኛው ባርነትን፣ፈቅደን የምንሞቀው
እዚ እየረሳን ፣ እዛ ም'ናፍቀው
ፍቅር መሽቶብን ነው፡፡
፨፨
እንዲህ ነው ሚኖረው....
ፍቅር የመሸበት፣ሀቅ ያልገባው ሀገር
እዛ እኛ ሙሾ አውራጅ ፣ እኛ አዚ ምንጨፍር፡፡

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢20👍11👏43🔥2