አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#
#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#በክፍለማርያም

...ፍፁም ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ
ቤዛዊት በተቀመጠችበት ቦታ በሀሳብ እሩቅ ተጉዛ ስለ ፍፁም መቅረት ትብከነከናለች

"ምን ሆኖ ቀረ?"

በአይምሮዋ የሚመላለስ ጥያቄ ነዉ።
ሀሳቧ ሁለት ፅንፍ ይዞ ይጋጫል
"ይመጣል አይቀርም"
የሚል የመፅናኛ እና የጤነኝነት ሀስብ በተቃራኒዉ
"አይመጣም ቀርቷል"
የሚል በህመም የገነነ ዉጥረት ባላቸዉ ጥያቄወች ተዉጣ በቀኝ እጇ አገጯን ደገፍ አርጋ
አይኖቿን አሁንም ፊት ለፊቷ አሻግራ ተስፋ ባለነቁረጥ የፍፁምን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ
ቆይታ አሉታዊዉ ሀሳቧ የፍፁምን መቅረት አሳምኗት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ዘላ ተነስታ እንደወታደራዊ አቋቋም በተጠንቀቅ ከቆመች በኋላ ለመራመድ መንቀሳቀስ ስትጀምር
በርቀት ሁኔታዋን ሲታዘቡት የነበሩት እማማ ስንቅነሽ ፈጠን እያሉ ተራምደዉ አስቆሟት

"የት ልትሄጂ ነዉ ልጄ?"

በእድሜ ብዛት የደከመ በሚመስል አሳዛኝ የእናትነት ድምፅ
የቤዛዊትን እጆች ለመያዝ እጃቸዉን እየሰደዱ
"ቀረ በቃ አይመጣም"
ቆጣ ብላ እጆቿን እያወናጨፈች ሊይዟት የቀረቡትን የእማማ ስንቅነሽን እጅ እየገፋች
"ማን ..."
ካሉ በኋላ እማማ ስቅነሽ ይመጣል እየጠበኩት ነው ያለቻቸዉን አስታዉሰዉ
"ፍፁምን ነዉ ምን አለ ትንሽ ብትጠብቂዉ ታድያ ልጄ ወዴት ልትሄጂ ነው የተነሳሽዉ.."
ከጎናቸዉ እንዳትርቅ እየፈለጉ ቤዛዊትን ማባበል ጀመሩ
የት እንደምትሄድ ያላረጋገጠችዉ ቤዛዊት ግን የእማማን ተማፅኖ ከቁብ ሳትቆጥር
ሂጂ ሂጂ የሚላትን ስሜት እየተከተለች እማማን
"እመለሳለሁ እመለሳለሁ እሺ"
እያለች በእርጅናና በህይወት የጎበጠ ትከሻቸዉን በእጇ ዳበስ አርጋ
እማማ ስንቅነሽን ወደ ኋላ ትታ እስዋ ወደ ፊት መራመድ ጀመረች።
ፍፁም ፍቃዱን አመልጣለሁ ብሎ ዘዉ ብሎ የገባበት ቤት መኖርያ ቤት መስሎት እየተሳቀቀ የያዝኩትን ክራንች ማነከሴንም አይተዉ ያዝኑልኛል ብሎ ሰተት እንዳለ
ቤቱ ዉስጥ በቁጥር የሚቆጠሩ ሰወች ሰብሰብ ብለዉ ስላየ በፍርሀት እና ተመልሼ ልዉጣ አልዉጣ እያለ በቆመበት
ሲያስብ አንዲት ደርባባ ሴትዮ ከቤቱ ዉስጠኛ ክፍል መጋረጃ ገልጣ ስትወጣ ፊት ለፊት ሲገጣጠሙ ፍፁም እንደምንም ብሎ
"ሰላም ዋልሽ"
አንገቱን ለሰላምታ ያክል ዝቅ እያረገ
ሴትየዋ ፊት ለፊቷ አይታዉ የማታዉቀዉ ሰዉ በማየቷ ጥቂት ተገርማ ክራንቹን አቋቋሙን ፊቱን በገረፍታ አይታዉ ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ
"እንዴ ምን አስቆመህ አረፍ በል እነጂ..."
በአይኖቿ ሰወቹ ከተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ክፍት ቦታ እያሳየችዉ መቀመጡን ስታይ ተመልሳ ወደ ጓዳዋ ፈጠን እያለች ገባች
ፍፁም የተቀመጡትን ሰወች ቃኛቸዉ የራሳቸዉ ጨዋታ ላይ ናቸዉ ሁሉም እግራቸዉ ስር ንኬል ተቀምጧል መሀል ላይ ጆግ ሙሉ ጠላ መኖሩን አስተዋለ ወድያዉ ሴትየዋ በጣሳ ዉሉ ጠላ ይዛ መጥታ ፊት ለፊቱ አስቀመጠች
ጠላ ቤት መግባቱ ስለገባዉ ፈገግ እያለ አመስግኖ ተቀብሎ መጠጣት ጀመረ።
ቤዛዊት የመንገዱን ጠርዝ ይዛ በለሆሳስ እያወራች ከንፈሮቿ እየተንቀሳቀሱ አንዴ ቆም
ብላ እያሰበች ሲላት ፈጠን ፈጠን እያለች እየተራመደች ነዉ
"ቀረ !!"
አንገቷን ከግራ ወደ ቀኝ እያንቀሳቀሰች
"ቤቱ ለምን አልሄድም እንደዉም እሄዳለሁ"
እጇን ከንፈሯ ላይ ጣል አርጋ ትንፋሽ እየሳበች አሰበች
"ይሄኔ ከእህቴ ጋር ይሆናል"
ንዴቷ እየጨመረ ሄዶ እጆቿን ለቡጢ በሚመስል አኩዋሀን ጨበጠቻቸዉ
ወደ ፍፁም ቤት ሄዳ ፍፁም እና እህቷን አብረዉ ሆነዉ ስታገኛቸዉ ምን ልታረግ እንደምትችል እያሰበች
"ኪኪኪኪኪ ኪኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
እየተንከተከተች ስትስቅ መንገደኛ ሰዉ አይቷት እጆቹን ለማማተብ አንዴ ግንባሩን ቀጥሎ ወደ ሆዱ በስተመጨረሻ ሁለቱን ትከሻወቹን አስነክቶ እየዞረ እያያት ሲያልፍ ሳቋን አቁማ ኮስተር ለማለት እየሞከረች ወደ ፍፁም ቤት አመራች።

ፍቃዱ በንዴት ብዛት ተበሳጭቷ ባዶ ሜዳ ላይ ቆሞ ይዉረገረጋል
"እንዴት ይሄ ያመልጠኛል የት ሊገባ ይችላል"
እያለ በቆመጠት ዙርያዉን ይቃኛል ነገር ግን ፍፁምን ማየት ስላልቻለ እና ፀሀይዋም አቅም አሳጥታዉ ስለደከመዉ ለመመለስ እያሰበ ጥቂት ወደ ኋላ ሲራመድ
አንድ ጎልማሳ ሰዉዬ የጣሳ ምልክት ከተሰቀለበት ቤት በመጠኑ ገድገድ እያለ ሲወጣ ተመልክቶ ቆመ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።

ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።

እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።

የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።

“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"

“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?

አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።

“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።

« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”

ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።

“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።

ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።

ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።

“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-

ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።

“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣

እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "

ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።

“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።

“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።

ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።

አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?

“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው

ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።

“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ

“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።

አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።

“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር

“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።

“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”

" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”

በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።

እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል

እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።

ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።

"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ

“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።

ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ

...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡

ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡

“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡

ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....

ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡

ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡

እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡

በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡

እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
👍3
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....እንደ ድንጋይ ከተጫናት ሰመመን ውስጥ ቀስ በቀስ እየወጣች ስትመጣ… እላይዋ ላይ ተጭኖ የያዛት ድቅድቅ ጨለማ እንደ ጭስ እየሳሳ እየበነነ ለቋት ሲጠፋ በመጀመሪያ የተቀበላት በእግሮቿ መሃል የሚነዝራት የደነዘዘ ስቃይ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ እየጠራ ሲመጣም አይኖቿን ለመክፈት አልደፈረችም፡፡ ሌላ ዱላ፣ ሌላ ስቃይ ሌላ የጋለ ሽቦ የሚችል
አካል አልነበራትም። በክፍሉ ውስጥ ብቻዋን ትሁን አትሁን እርግጠኛ
አልነበረችም፡፡ አይኖቿን ለመክፈት ግን አልደፈረችም፡፡

እጆቿ ግራና ቀኝ ተወጥረው ከታሰሩሰት ተፈተው በድን እንደሆኑ ሁሉ በግራና በቀኝ ተዘርረዋል፡፡ በተኛችበት ልብስ ደርበውላታል፡፡ እግሮቿ ግን አሁንም ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ተወጥረው እንደታሰሩ ናቸው፡፡ ቁስሏን ለማዳመጥ ሞከረች፡፡ በጭኖቿ መሃል የሚሰማትን ስቃይ ለማዳመጥ ዝም አለች የተዳፈነ... የደነዘ… የደበዘዘ ስቃይ፡፡ ግራ ክንዷ ላይ ህመም ተሰማት:: ለመነቃነቅ ግን አልደፈረችም፡፡ በአይነ ህሊናዋ ሁኔታውን
ለመቅረፅ ሞከረች። መቼ ነበር በጋለ ሽቦ ጭኖቿ መሃል ሰውነቷን ያቃጠሏት? ዛሬ? ትላንት? ዛሬ ምንድነው? ቀን ነው ሌሊት? ሰዓታትና ቀናት ትርጉም ካጡባት ቆይተዋል፡፡

ድምፅ የሰማች መስላት። ዓይኖቿን እንደከደነች ጆሮዎቿን ኣስልታ ተጠባበቀች፡፡ የበር ድምፅ ተሰማት… የሚከፈት የበር የሚያሰማው ድምፅ..

“አልተነሳችም፡፡” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ፡፡

“ኮለኔል” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ “ዙርያውን አጥረነዋል።በርም ላይ አንድ ሰው አቁመን እየተጠባበቅን ነው::”

“መጣሁ” ሲል ተሰማት ማርቆስ፡፡

ሁለት የእግር ኮቴዎች በግራና በቀኟ ተስሟት…በስተቀኝ ኣንድ መዳፍ ግንባሯ ላይ አረፈ::

“ከነቃች የመርፌ ማደንዘዣውን ስጣትስቃይ ሊኖርባት ይችላል።” የማርቆስ ድምፅ ነበር።

“ካስቸገረችኝስ ልምታት?” አለ በስተግራዋ የቆመ ሌላ ሰው፡፡

“ረጋ ብለህ አባብለህ ውጋት። ለምን ትመታታለህ? ደግሞ አታስቸግርህም.. ከተወራጨችብህ ግን ግሉኮሱን ንቀልላት፡፡” አለ እጁን ግንባሯ ላይ የጫነው ማርቆስ በጣቶቹ ፀጉሯን ወደኋላ እያበጠረ፡፡ “ጠዋት እቀየርልሃለሁ፡፡”

ኮቴ ተሰማት፡፡ ተከታትለው ሲወጡ ሰማች። በሩ ሲዘጋ በክፍሉ ውስጥ ፀጥታ ሲነግስ ስትፈራ ስትቸር አይኖቿን ገለጠቻቸው::መኝታ ክፍሏ ውስጥ ብቻዋን አስተኝተዋታል፡፡ በቢጫው የብርድ ልብሷ ከአንገቷ እስከ
እግሯ ጫፍ ድረስ ሸፍነዋታል፡፡ በተንጋለለችበት ዙሪያዋን ተመለከተች፡፡
ግራ ክንዷ ላይ የሚሰማት ህመም ከራስጌዋ ከተንጠለጠለው የግሉኮስ
ከረጢት ጋር የተያያዘው መርፌ ክንዷን ጠልቆ የገባበት ላይ መሆኑን ተረዳች። የክፍሉ መጋረጃ ተዘግቷል፡፡ በጥግና ጥግ የታየው ሰማይ ጨልሟል... መሽቷል፡፡ ሰመነቃነቅ ስትሞክር ግራና ቀኝ የታሰሩት እግሮቿ መሃል የተዳፈነው ስቃይ እንደ ጦር ወጋት፡፡ ከስሱ የብርድ ልብስ በታች ያለው እራቁት ሰውነቷ ተንሰፈሰፈ፡፡

ድምፅ ተሰማት የመኝታ ቤቷ በር ተከፈተ፡፡ ቶሎ ዓይኖቿን ጨፈነቻቸው፡፡ : እንደነቃች ማወቅ የለባቸውም፡፡ ዝም ብላ መተኛት ነው ያለባት፡፡ መረበሽ የለባትም! አለበለዚያ ይመቷታል፡፡ ዝም ብላ መተኛት። በሩ ሲዘጋ ተሰማት: የእግር ኮቴ እየቀረባት መጣ. አንድ በላብ የረጠበ እጅ
እራቁት ትከሻዋ ላይ ሲያርፍ ተሰማት… ትንፋሼ እላይ እታች የሚል ትንፋሽ እላይዋ ላይ የነበረው ስስ የብርድልብስ ፡ ተገፈፈ፡ መረበሽ የለባትም… መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም... አለበለዚያ ድጋሚ
ያስቃይዋታል. , ትከሻዋ ላይ ያረፈው በላብ የራሰ መዳፍ ወደታች ወደ
ደረቷ ተንሸራተት…. እልተንቀሳቀሰችም ጡቶቿ ሲዳስሱ ተሰማት እላይ እታች የሚል ትንፋሽ… ፍርሃት ወረራ ግራ ክንዷ ላይ የተሰካውን መርፌ አስሮ የያዘው ፕላስተር ተላጠ.. ክንዷ ላይ የተሰካው መርፌ ተነቀለ መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም… አለበለዚያ ይመቷታል... እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ቀረባት፡፡ ብርድ ልብሷ ወደታች ተጎተተ ፍርሃቷ
እየጨመረ መጣ እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ወደ አንገቷ ስር ሲጠጋ ተሰማት.. ብርድ ልብሱ ከላይዋ ላይ ተንሸራቶ ወደ መሬት ወደቀ፡፡ ራሷን መቆጣጠር አቃታት… አይኖቿን ገለጠቻቸው፡፡

ጺማሙ ሰውዬ ነበር፡፡ እላይዋ ላይ እንዳንገርበበ ድንገት አይኖቿን ስትገልጥ ደንገጥ አለ፡፡ ወዲያው ፈገግ አለላት... የሸሚዙን ቁልፎች መፍታት ጀመረ… ፈገግ አለላት ድጋሚ… ሸሚዙን ከላዩ ላይ ወርውሮ ተጠጋት… እጆቹን ጡቶቿ ላይ ጫናቅው ድንገት ተወራጨች፡፡ ሙቅ
እርጥብ እጆቹን ከላይዋ ላይ ገፍትራ ተሸማቀቀች ፈገግ አለላት፡፡ አልጋዋ
ላይ የተንጋለለውን እራቁት ገላዋን ከላይ እስከታች በተራሱ ኣይኖቹ ዳሰሰው፡፡ ምራቁን ሲውጥ ትልቅ ማንቁርቱ እላይ እታች ሲመላለስ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡ ድንገት ዘሉ አፏን በመዳፉ ኣፈናት… ታገለችው…
እጆቿን እያፈራረቀች እንደብረት የደደሩ ሁለት ክንዶቹን ደበደበቻቸው
ቧጠጠቻቸው... ያለብዙ ችግር እፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሶ ለጎማት

ትንፍስ ትንፍስ እያለ ቁልቁል ተመለከታት፡፡ አይኖቹ የሚያርፉበት
ቦታ ያጠ ይመስላል፡፡ መላ ሰውነቷ ላይ ተንቀዠቀዡ።

ሱሪውን ማውለቅ ጀመሬ በተንጋለለችበት በምሬት… ጭንቅላቷን አወራጨችው… እንባዋ ደረሰላት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ቢሮው ትዕግስቱ አልቋል፡፡” አለ ከቴልአቪቭ የገባው ይሁዳ አሚ
የብርቱካን ጭማቂውን ተጎንጭቶ ብርጭቆውን ካስቀመጠ ሰኋላ ረጅም
ጺሙን እየዳሰሰ፡፡

የአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴልኝ የመዋኛ ስፍራ በስተቀኛቸው አድርገው ተቀምጠዋል፡፡ በርካታ እንግዶች በመዋኛ ልብሶቻቸው ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡ የተቀሩት በደረትና በጀርባቸው እየተገላበጡ ጭል ጭል የምትለውን ለስላሳ የጳጉሜ ፀሐይ ይሻማሉ፡፡

ይሁዳ አሚ በሆቴሉ ውስጥ ከያዘው የመኝታ ክፍል ወጥቶ ከቀጠሮኣቸው ስፍራ የደረሰው ልክ በሰዓቱ ነበር። ከቀጠሮው ሰዓት ቀደም ብሎ የደረሰው አሃሮን የእንግዳውን ፀባይ ስለሚያውቅ የብርቱካን ጭማቂ አዝዞ ከፊት ለፊቱ አስቀምጦ ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሚ የሌሊት ልብሱን ሳይቀይር በላዩ ላይ ወፍራም የጠዋት ልብሱን ደርቦ ወገቡ ላይ ቀበቶውን ሽብ አድርጎ ከጥጥ የተሰራ ወፍራም የእግር ሹራብና የቤት ነጠላ ጫማዐእንዳደረገ ወደ መዋኛው ስፍራ የሚወስደውን ደረጃ በእርጋታ ወርዶ ወደዐአሃሮን አመራ፡፡

“እንኳን ደህና መጣህ፡፡” አለ አሃሮን ተነስቶ እንደቆመ የአሚን እጅ
ጠበቅ አድርጎ እየጨበጠ፡፡

“እንኳን ደህና ጠበቅኸኝ።” አለ አሚ ነጫጭ ውብ ጥርሶቹን ለአንድ አፍታ ብልጭ አድርጎ የጓደኛውን እጅ እየወዘወዘ፡፡

አሚ “ ኪዶን” በሚል ስያሜ በሚታወቀው የሞሳድ ገዳይና አፋኝ
ክፍል ውስጥ ለአስራ ሰባት ዓመታት የሰራና አትግደል እና አትዋሽ
ከሚሉት ከሙሴ ትዕዛዛት በስተቀር በተቅሩት በስምንቱ ትዕዛዛት ላይ ፌዝ
የማያውቅ ጥብቅ ሃይማኖተኛ አይሁዳዊ ነው። በሌሊት ልብሱ ላይ የደረበው
ወፍራም የጠዋት ልብስና ቡፍ ካለ ጥጥ መሳይ የቤት ጫማው ጋር ሲያዩት
ጺማሙ ሰው በቤት ውስጥ ተቀምጦ የሳጠራ ዘንቢሉችን ሲሰራ የሚውል
የዋህ በሬ ይመስላል፡፡

“የብርቱካን ጭማቂ፡፡” አለ አሚ ፈገግ ብሉ ከጎኑ የቆመውን የሆቴሉን አስተናጋጅ እየተመለከተ፡፡

የአልኮል መጠጥ ፍጹም የማይቀምስና የአሳማ ስጋ አፉ የማይገባ ጥብቅ ሃይማኖተኛ የሆነው አሚ በመስከረም 5 1972 በሙኒክ ሃያኛው ኦሎምፒክ ዝግጅት ላይ የብላክ ሴፕቴምበር ቡድን የእሥራኤል ስፖርተኞችን ሰፈር በመውረር አስራ አንድ ተጨዋቾችን ከገደለ በኋላ የጠቅላይ ሚኒስትር ጎልዳሜይርን የብቀላ ትዕዛዝ
👍2
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው


....ከግንባሯ እና ከብብቷ ስር ላቧን እየጠረገች አኔ ቤታማን ከሶል ሳይክል
የዳንስ ትምህርቷ ወደ ብሬንት ውድ ፀሃያማ ቀን በጥሩ ስሜት ውስጥ ሆና
ወጣች፡፡

የስትራንቨስኪ ኮንሰርት ላይ ባሳየችው ብቃቷ የተነሳ በሁሉም ቦታዎች ላይ ቫዮሊን እንድትጫወት ግብዣዎች እየቀረቡላት ይገኛሉ። በዚህም የተነሳ
ምንም የገንዘብ ችግር እንደማይገጥማትና ቀጣይ ሥራ አላገኝ ይሆን ከሚል ሃሳብ ወጥታለች፡፡

በግላዊ ህይወቷም ቢሆን ሁሉም ነገር ሰላም የሆነ ይመስላል።ምክንያቱም ባሏ በስልክ መልዕክቶች፣ በስልክ ጥሪዎች እና ስጦታ አበባዎች እሷን ማስጨነቁን ትቶታል፡፡ በዚህም የሃዘኔታ ስሜት ቢሰማትም በመጨረሻ ግን ልቧ እረፍት ሊያገኝ ችሏል፡፡ አሁንም ቢሆን የሆነ የልቧ ክፍል እሱን ያፈቅረዋል፡፡ ግን ደግሞ ኒኪ ትክክል ናት፤ የሁለቱ መፋቀር
ብቻ በቂ አይደለም፡፡

አሁን ጥሩ ስሜት እንዲስማት ያደረገው ሌላ ነገር ከኒኪ ጋር መስማማት መቻላቸው ነው፡፡ ኮንሰርቱን ባቀረበችበት አዳራሽ የመልበሻ ክፍል ውስጥ እያሉ ባሏ በላከላት ብዙ አበቦች የተነሳ የማይገባ ነገር ከተነጋገሩ በኋላ አኔ መልሳ ኒኪን ማየት አፍራለች፡፡ ስለሆነም ከኒኪ ጋር ያላትን የህክምና ቀጠሮ ደውላ ሳታሳውቅ ሰረዘችው፡፡ ቀጣዩንም የህክምና ቀጠሮ ሳትሄድ ቀረች፡፡ ቀጠሮውን ሳታሳውቅ በመሰረዟ ከኒኪ የስልክ ጥሪ ወይም ደግሞ በኢ-ሜይል ቀጠሮውን ሳታሳውቅ በመሰረዟ የቀጠሮዎችን ክፍያዎች እንደምትከፍል የሚያስጠነቅቅ መልዕክትም አልተላከላትም፡፡ኩራቷን ውጣ ለኒኪ ልትደውልላት እና ባለፈው ምሽት ስላሳየቻት ያልተገባ ባህሪ ይቅርታ ልትጠይቃትም ነበር። በዚያ ላይ ደግሞ በጣት የሚቆጠሩ ጓደኞችን እያጣች ነው፡፡ እና ብቸኝነት እየተሰማት ነው በዚህ ስሜት ውስጥ እያለች በነበረችበት ወቅት ነበር እንግዲህ የኒኪ በወረቀት ላይ የተፃፈ ይቅርታን ያዘለ መልዕክት አፓርትመንቱ ድረስ የመጣው፡፡
ሌላ አዲስ ቴራፒስት ጋ ብትሄጅ እረዳሻለሁ፡፡ ምንም ዓይነት መጥፎ
ስሜትም አይሰጠኝም፡፡ ነገር ግን ሌላ ቲራፒስት ጋር እንዳልሄድሽ ይሰማኛል፡፡ ምክንያቱም አብረን ስንሠራቸው የነበሩ ነገሮች እየረዱሽ እንደሆነም አስባለሁ፡፡ አንቺም በውስጥሽ ይሄ እንደሚሰማሽ እርግጠኛ ነኝ ይላል መልእክቱ፡፡ አኔ ምን እንደሚሰማት እርግጠኛ አይደለችም፡፡ ማለትም ኒኪ ወደ እሷ ስለተመለሰች ደስ ብሏታል፡፡

የሆነ ያልተለመደ ነገር እየተሰማት እንደሆነ ይገባታል፡፡ ለዚህ ደግሞ
ዋነኛዋ ተጠያቂ እሷ ኒኪ ናት፤ ምክንያቱም የአካሚና የታካሚ የግንኙነት
መስመርን አልፋ እሷም እንድታልፍ ያደረገቻት እራሷ ናት፡፡

ከፊት ለፊቷ ከሚገኘው ካፌ ገብታ ውድ የፍራፍሬ ጭማቂ ጠጣች፡፡ እና መኪናዋ ውስጥ ዘልላ ገባች እና ወደ ኒኪ ቢሮ በሚወስዳት መንገድ ላይ መኪናዋን ማሽከርከር ጀመረች፡፡ የተለመደው የህክምና ቀጠሮዋ ከሰዓት ላይ ቢሆንም አኔ የኒኪን ፊት ለማየት ስለጓጓች ነው በአሁኑ ሰዓት ወደዚያ ለመሄድ የፈለገችው፡፡ ምናልባትም ቢሮዋ ውስጥ ታካሚ ከሌለ ወጣ ብለው ወይንም እዚያው ቢሮ ውስጥ ለጥቂት ጊዜ ያህል እያወሩ ሻይ ቡና ማለት ይችላሉ፡፡

የመኪናዋን ጣሪያ ከፈተችና ንፋሱ ሰውነቷ ላይ ያለውን ላብ እንዲያደርቅላት አደረገች፡፡ የጠራው ሰማያዊ ሰማይንም ቀና ብላ ስትመለከት ሰማዩ የእሷን ደስታ የተጋራት መሰላት፡፡ የኒኪ ቢሮ ከሚገኝበት ህንፃ ስትደርስ ከመኪናዋ ወርዳ ቁልፏን መኪናዋን በተገቢው ቦታ ለሚያቆምላት
ሰው ልትሰጠው ስትል የምታውቀው ድምፅ ከኋላዋ ሲያወራት ሰማች እና
በድንጋጤ ደርቃ ቀረች፡፡

“ሆላ የኔ መልአክ” የሚለው የባለቤቷን ድምፅ ስትሰማ ልቧ በአፏ የሚወጣ እስኪመስላት ድረስ ደነገጠች፡፡ ጥላው ከመጣች ጀምሮ ይሄ ነገር ሊከሰት እንደሚችል ስታስብ ነበር፡፡ በቃ እሷ ያለችበት ቦታ ድረስ በድንገትመጥቶ እንደሚያገኛት ስታስብ ነበር፡፡ በመጀመሪያ ላይ እነዚህ ሃሳቦች
በህልሟ እየመጡ ቅዠት ይሆኑባት ነበር፡፡ በህልሟ ትታው ወደመጣችው ባሏም ተገድዳ ስትመለስ ለብዙ ጊዚያት ስታልም ነበር፡፡ ከጊዜ ብዛት ግን ይሄ ስሜቷ እየጠፋ መጥቶ ነበር፡፡ አንዳንድ ቀን ስለእሱ ስታስብ እንዲህ ባለ ድንገተኛ ሁኔታ እንዳያገኛት የቀን ህልሟን ስታልም ነበር፡፡

ይኼው አሁን ግን እሱ አጠገቧ ይገኛል፡፡ እሷን ሊያገኝም እሷ ያለችበት
ቦታ ድረስ ለመምጣት ችሏል፡፡

ለጥቂት ጊዜ ትቷት የነበረው ሽብርም ከባሏ ጋር ተመልሶ መጣ ማለት
ነው፡፡ “ተወኝ ብዬሃለሁ! ከአጠገቤ ዞር በል!” ብላ የመኪናውን ቁልፍ
ለፓርኪንግ ሠራተኛው ለመስጠት ስብስብ ወዳሉት ጥቂት ሰዎች ተጠጋች::

“እኔ” ብሎ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ተወዳጅ ሚስቱን በፍቅሯ በተጎዳው ዓይኑ ተመለከታት፡፡ “ምን ሆነሻል ውዴ፤ ሉዊስ ነኝ እኮ ለምንድነው የፈራሽኝም
አላት፡፡

ድምፁ ውስጥ ንዴት አይሰማም፡፡ ከዚያ በላይ ግን የሃዘኔታ ድምፀት
ይነበብበታል፡፡ ይህንን ስታይ በሃይል ይመታ የነበረው ልቧ እየተረጋጋ
መምታት ጀመረ፡፡

እንደሁልጊዜውም ዝንጥ ብሎ ለብሷል። ምርጥ የሳቪሌ ሙሉ ልብስ፣ የሐር ከረቫትና የጉቺ አፍተር ሼቭ የተቀባው አዲስ የተላጨው ፂሙ እንኳን ሳታስበው ከእግሮቿ መሃል ንዝረትን ፈጠረባት፡፡ በግራ እጇ በደንብ ተደርገው የተሠሩ የእሷ ምርጫ የሆኑ አበቦችን ይዟል፡፡

“እዚህ ምን ትሠራለህ ሉዊስ?” ብላ ጥርጣሬ በማይነበብበት ለስላሳ
ድምፅ ጠየቀችው፡፡

“ኤል ኤ ውስጥ የሆነ ቢዝነስ አለኝ፡፡ እዚህ ለጥቂት ቀናት እቆያለሁ”
አላት፡፡

አኔም ዓይኗን አጥብባ “ወደ አሜሪካ መቼም ተመልሰህ እንደማትመጣ
ነግረኸኝ ነበር፡፡”

“ልክ ነሽ በጣም ሞክሬ ነበር... ግን ይሄ ነገር በጣም አስፈላጊዬ ነገር ነው፡፡”

ሉዊስ ቢዝነስ ሲል እሷን ይሁን ወይንስ የእውነት ለቢዝነስ ነው ወደ እዚህ የመጣው ብላ አስላሰለች እና ለቢዝነሱ ብሎ ወደ ኤል ኤ በመጣ ብላ ተመኘች፡፡ ፊቱንም ትክ ብላ እያየችው እርስ በርሳቸው የሚጋጩ ስሜቶችን
ማስተናገድ ጀመረች፡፡ ለቢዝነስ ነው እዚህ የመጣሁት ያለው እውነቱን
ነው? ደስ ሊለኝ ይገባል ወይስ ልፈራ?”
“አኔ በጣም እንደናፈቅኩሽ ታውቂያለሽ አይደል?” አላት በተሰበረ የፍቅር
ድምፅ፡፡

“እኔም ናፍቄሃለሁ” ብላ እውነቱን ተናገረች፣ እና በመቀጠልም “
ግን እንደዚህ በድንገት ልታገኘኝ አይገባም... ልትደውልልኝ ይገባ ነበር።
“ስልክሽ እኮ የለኝም”
“እኔ የምሠራበት ኦርኬስትራ ቢሮ በመሄድ መልዕክት ልታስቀምጥልኝ
ትችል ነበር፡፡ ደግሞ እኔን ማግኘት ያን ያህል አይከብድም፡፡ እንደዚህ

በድንገት መጥተህ መንገድ ላይ ከምታገኘኝ ይልቅ አስቀድመህ ብታስጠነቅቀኝ መልካም ነበር” አለችው፡፡

“አስቀድሜ ባሳውቅሽ ኖሮ እኔን ለማግኘት አትስማሚልኝም ነበር” አላት።

“ቢሆንስ እሱ የእኔ ውሳኔ አይደል?” ብላ አኔ ጠየቀችው፡፡

“በእርግጥ ባሳውቅሽ ችግር የለውም ነበር፡፡” አላት እና ፈገግ ብሎ “ይኼ
ደግሞ የእኔ ውሳኔ ነው፡፡ በዚህ
ውስጥ አንቺን ማግኘቴ ደግሞ
ተስማምቶኛል።”

አኔ ምንም ማድረግ ስላልቻለች ፈገግ አለችለት፡፡ ይኼ የሉዊስ አካሄድ
ነው። የለየለት ጥጋበኛነቱን ከጥሩ ስሜት ጋር ቀላቅሎ ስለሚያቀርበው ነገሮች ይሆኑለታል፡፡ እንደርሱ ያለ ወንድ ገጥሟት አያውቅም፡፡ በእርግጥ
ደግሞ ኒኪ እሱን ዳግመኛ እንዳታገኘው ማስጠንቀቂያ ልካ ነበር፡፡

“ምሳ አብረን እንብላ” አላት እድሉን ለመጠቀም በማሰብም አበባውን
እያቀበላት፡፡

አኔ አበባውን ስትቀበለው ጣቶቻቸው ሲነካኩም በጣም ነዘራት፡፡ ያን ምሽት በእሱ ላይ ከጮኸችበት በኋላ በአካል
👍1
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል


...«አባባ ትላንት ከሰዓት በኋላ ሔደ፡፡ ከሳምንት በላይ ይቆያል፡፡ሲያተራምስ ነው የሚሰነብተው:: ያሰብነው ጉዳይ እንደፈለግነው ሊፈጸም ይችላል ማለት ነው» አለች የውብነሽ ቅዳሜ ማለዳ በቁርስ ሰዓት የምሥራች ነው
የምትለውን ወሬ እያወራች፡፡

ለግብግቤ አንድ ተጨማሪ ርምጃ እንደሚሆን በማመኔ ደስ አለኝ።
ጠረጴዛውን ተደግፋ ወደ ቆመችው ባለቤቴ ዞር አልኩና ዛሬ ጋሻዬነህ አብሮኝ
ለቁርቁስ የሚሔድበት ቀን በመሆኑ አደይ አበባ እስመስለሽው ቆይኝ፣ የሚያምርበትን ልብስ አንቺ ታውቂዋለሽ፡፡ ወዴት እንደሚሄድና ጉዳዩ ምን እንደሆነ ነግሬሻለሁ» ብዬ ወደ ውስጥ ገባሁ፡፡ ልክ እንደ እዲስ ወፈፌ ያቅበዝብዝ
ያዘኝ፡፡ “ጭንቅላት በደስታ ሲሰክር! ለብሼ ስመለስ እኅቴና ባለቤቴ ወሬያቸውን
ተያይዘውታል፡፡ አልተጋራኋቸውም፡፡ መኪናይቱን እስከማሟሙቅ ድረስ ደረሱብኝ፡፡መንገድ ስንጀምር የወዲያነሽ ተመለሰች። «የውብነሽ፣ ሰባት ሰዓት ሲሆን እዚሁ ጠብቂኝ» ብያት ከመሥሪያ ቤቷ በር ላይ ተመለስኩ፡፡ የሥራ መግቢያ ሰዓት ሞልቶ ስለ ነበር ሠራተኛው በሙሉ ነጠላና ጥንድ ሆኖ እያውካካ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ገና ቁጭ ከማለቴ ቅናት እንደሚያንዘፈዝፈው ሰው መላ አካላቴ እየተንቀጠቀጠ አወከኝ፡፡ በአካባቢዬ ያለው ዕቃ ሁለ ጥያቄ የሚያቀርብልኝ እየመሰለኝ ”እስቲ አባክ! አንድ ቃል ይውጣህ! እንደሚል ሰው እጉርጩ አየሁት።

በጦርነት ዋዜማ እንደምትሸበር የፈሪ ልብ የልቤ ትርታ ከገደቡ በላይ ናረ፡፡ ለቆላ ቁስል የሆድ ቁርጠት መድኃነት መዋጥ ሆነብኝ፡፡ ብናኝ የምታህል የመንፈስ ጸጥታ ሳላገኝ ቀረሁ። የሰዓቴን ጠቋሚ ዘንግ ወደፊት በማስኬድ የጊዜን
ሥርዓታዊ ጉዞ ለመለወጥ ያስችለኝ ይመስል ሦስት ከኻያ የነበረውን አራት ከኻያ አደረግሁት፡፡ራሴን በማጭበርበሬና ሕሊናዬን በታለሌ ረቂቅ ኃፍረት ተሰማኝና
መልሼ አስተካከልኳት። እርሳሱ፣ ወረቀቱ፣ ብዕሩ፣ ወንበርና ጠረጴዛዉ ደመኛዩ
መሰሉኝ፡፡ ሒድ ሒድ ውጣ ውጣ የሚል ነገር ያዘኝ። በቀጥታ አለቃዬ ቢሮ ገባሁ፡፡
አእምሮው ተቃውሶ ሁኔታዎችን እንደ ዘነጋ ሰው ከፊታቸው ተገተርኩ፡፡ ቀና
ብለው ሲያዩኝ «ዛሬ በጣም አሞኛል ምናልባት ቢሻለኝ ብዬ ነበር የመጣሁት።
እያመመኝ ከመቀመጥ ብሄድ ይሻላል» አልኩና በዙሪያዬ የውሸት ገረገራ አጠርኩ።አለቃዩ ዘለው ለመግባት አልቻሉም። ካመመሕማ ሂድ፣ በጎ ካልሆንክ ደግሞ ሰኞ ሰው ላክ» አለና ያስደስተዋል ብለው ያሰቡትን በሞኝ ሰው ፊት ላይ የሚታይ የፈገግታ ዐይነት አቀረቡልኝ፡፡ ልቤ በደስታ ከመነረቱ የተነሣ ሣቄ ፈንድቶ አጉል እንዳያደርገኝ ነገር ሳላበዛ አመስግኜ ሹልክ አልኩ፡፡

ጭንቀትና ሥጋት ተንጠርዞ እንደ ከበደኝ በመኪናዩ ገሠገሥኩ። በራሴ
ለመተማመን ያልቻልኩበትን ምክንያት ፈልፍዬ ማውጣት ባለመቻሌ በውስጡ
ትልቅ ችግር ተፈጠረ። ከመኪናዬ ወርጄ ወደ ቤት ስራመድ ምንና የት
እንደምረግጥ የማውቅ አልመስልም። ማንም ሳያየኝ ሰተት ብዬ እንግዳ መቀበያ
ክፍላችንም ገባሁ፡፡ በቀስታ ሄጄ ከመስተዋቱ ፊት ለፊት ቆምኩ። አኳኋኔ
ስላላስደሰተኝ ምናልባት በፈገግታ ቢለወጥልኝ ብዬ ፈገግ አልኩ። ከውስጥ
ያልመነው ፈገግታ በመሆኑ ወዲያው ከሰመ፡፡ እንዲያውም ስካሩ ያልበረደለት
ሰው መሰልኩ እንጂ ጤነኛውን ጌታነህን ለመሆን አልቻልኩም፡፡ ከወደ መኝታ
ቤት እየኮረኮሩ የሚያሥት የልጅ ሣቅ አሁንም አሁንም ይሰማል። ወዲያው
ከሚከታተሉትና ሊይዙት ከተዘረጉት እጆች ለማምለጥ ግማሽ ኃይሉን ለሣቅ ያዋለ
ልጅ ከወደጓዳ እየሮጠ መጣ። ከእኔ ራቅ ብሉ ድካም የዋጣት ሣቅ እየሣቀ ቆመ፡፡
አላየኝም። የወዲያነሽ ጥቂት ዘግየት ብላ ጫጩቷን ተከትላ እንደምትሄድ ዶሮ
እሱን ለመያዝ እየሮጠች መጣች።
በልፊያ የተበታተነው ጸጉሯ እንደ ጋሽበ አዝመራ የራሱን ግላዊ ውበት ፈጥሯል። በዚያች ሰዓት ወደ ቤት ይመለሳል ብለው ስለማይጠረጥሩ እናትና ልጅ አላዩኝም፡፡ ፊቷ እንደ በጋ ወራት ሙሉ ጨረቃ ደምቆ «መጣሁብህ! ያዝኩህ!» ብላ ወደ እርሱ ተራመደች፡፡

በመሮጥ ፈንታ ሆዱን ወደ ውስጥ እጥፍ ሣቁን ለቀቀው። አፈፍ አደረገችው:: ከቡችላዋ ጋር እንደምትላፋ እናቲት ወሻ ጎበስ ብላ ወገቡን ያዘችውና ትግል ገጠሙ:: ከወዲያ ወዲህ አባተለችው፡፡ የጋሻዬነህ ሣቅ ገነነች፡፡ ትርዒቱ እንዲቀጥል እንጂ እንዲቋረጥ ባለመፈለጌ እንደ ምሰሶ ጸጥ ብዩ
ተገተርኩ፡፡ ወደ ላይ እንሥታ አንጋጣ ስትመለከተው ውብ ጥርሶቿ ተፈለቀቁ፡፡
ስለ ከበዳት አወረደችው:: ወለሉ ላይ ስታቆመው ጸጉሯን በጣቶቹ በተነባት፡፡
ሲናከሱና ሲናጩ ውለው እንደ ደከሙ አውራ ዶሮዎች እናትና ልጅ ፊት ለፊት
ቆመው ተያዩ። ጋሻዬነህ በአጋጣሚ እኔ ወዳለሁበት ዐይኑን መለስ ሲያደርግ
ድንገት አየኝና «አባብዬ! » ብሉ በሩጫ መጥቶ እግሬ ላይ ተጠመጠመ፡፡
አንሥቼ ታቀፍኩት፡፡ የወጂያነሽ ባደረገችው ልፊያ ፍቅራዊ ኃፍረት ስለ ተሰማት ከበስተጀርባዬ ቆማ አንገቴ ላይ ተጠመጠመች፡፡ በአፍንጫዋ በኩል የሚወጣው ትንፋሽ እየተናጠች እንደምትስቅ ያስታውቃል። ወደ መስታወቱ ላይ የፊተኛው ጨምዳዳ ገጽታዩ ጠፍቶ በአዲስ ፈገግታ ተተክቷል። ከግራናከቀኝ አማከለውኝ ተቀመጡ፡፡ ያ ሲያዋክበኝ የነበረው ጭንቀት ለጊዜው ገለል ስላለልኝ ጥቂት ተዝናናሁ፡፡ . የጋሻዩነህ ወለላ አንደበትና የየወዲያነሽ ለዛሚ ቃላት አያረኩኝ አምስት ተኩል ሆነ። ከዚያ በኋላ ግን እሷ ወደ ማድ ቤት፣ ልጃችን ከቤት ውጪ ወጣ፡፡ ወጣ ከማለታቸው ሥጋትና ጭንቀት ተቃረጡኝ:: እንቅልፍ የሥጋትን
እድፍ አጥቦ ይወስድልኝ ይመስል ገብቼ ጋደም አልኩ፡፡ ዳሩ ግን አስጨናቂ
ሐሳብ ከጣራው ላይ የተንጠባጠበ ያህል ልዩ ልዩ ሐሳብ እንደ ጉንዳን ወረረኝ።
ታገልኩት፡፡ በመጨረሻ ግን «ዛሬ ድል ማድረግ አለብኝ የሕሊናዩ ትክክለኛ ወኔ
መገንፈል አለበት። ምንም እንኳ ከንትርክ ይልቅ መግባባት ለመቀራረቢያ የተሻለ
ቢሆንም ዛሬ ደግሞ አንድ ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ሰፊ የኑሮ ምዕራፍ
የምደመድምበት ቀን ነው» አልኩ፡፡ አእምሮዬ ጥቂት ሰከን በማለቱ ለዐርባ
ደቂቃ ያህል ደህና እንቅልፍ ወሰደኝ። ከሩቅ የሚሰማው የኤሌትሪክ እምቢልታ
በወፍራሙ ጀምሮ በቀጭኑ በመዉረስ ሰባት ሰዓት መሙላቱን አሰማ፡፡ የጋለ ሽቦ
እንዳ ነካው ሰው ደንግጬ ተነሳሁ። እመር ብዬ ወርጄ ጫማዬን አደረግሁና ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ገባሁ፡፡ ለካስ የውብነሽ ቀደም ብላ ገብታ ኖሮ የውጪ
አገር መጽሔት እያገላበጠች ተዝናንታ ትጠብቀኛለች፡፡ አንዳችም ሐሳብና ሥጋት
ያለባት አትመስልም፡፡

ከምሳ በኋላ የአለባበስ ችሎታዬን ሁሉ አጠቃልዩ በዕለቱ አለባበሴ ላይ
አዋልኩት፡፡ ሙሽራ ሆኜ ባላውቅም ሙሽራ መሰልኩ። አንጎሌ የኑሮ ፈተናውን
ውጤት ለማየት አሰፈሰፈ። የወዲያነሽ የመሄጃችን ጊዜ መዳረሱን በማወቋ
ጋሻዬነህን ይዛ ወደ መኝታ ቤት ገባች፡፡ አሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ
አጥቢያ ኮከብ አስመስላው መጣች። በእኔና በየውብነሽ ዝምታ ጭር ብሎ
የነበረው ክፍል በጋሻነህ የልብስ ውበት እንደገና ነፍስ ዘራ፡፡

«በሉ እንግዲህ በርቱ ይኸውላችሁ! ይቅናችሁ! አድባር ትቀበላችሁ ነው
የሚባለው» ብላ አስረከበችን፡፡ «ጨክነሽ?» አልኳት የምትለውን ለመስማት። ከዚህ አልፈ ምን ለማለት እችላለሁ በሚል አስተያየት አየችኝ። የውብነሽ ጋሻዩነህን ይዛ ፊት ለፊቴ ቆመች፡፡ ልማደኛው ሐሳቤ ተመሳቀለ፡፡ እኔንና ልጄን ወደ ሰው አለባ ምድረበዳ የምትገፈትረን መሰለኝ፡፡

«ተነሥ እንጂ ምን ትጠብቃለህ» ተባልኩ፡፡ በድካም እንደ ተጠቃ ሰው
በዝግታ ተነሣሁ።

የመጨረሻው ግብ ግብ የመጀመሪያው ምዕራፍ ተከፈተ፡፡
👍5
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


....በባላባት ቱሬ ሰፈር ሰርግና ምላሽ ሆነ፡፡ድብልቅልቁ ትርምስምሱ ወጣ፡፡ ባላባቱ ስሙ የተዋረደበትን ያክል ተካሰ፡፡ እሱ በሌለበት እንደ ዕቃ ተስርቃ እንደ ከብት ተነድታ የተወሰደች ሚስቱ ሌባዋ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ተመልሳ ከእጁ ገባች፡፡ ጎንቻ በለሊት ጨለማ ለብሶ ሌቱናን
ከሰንጋ ፈረሱ ላይ ከኋላው እንደ ዕቃ ጭኖ ሲገባ ፎከሪ! አቅራራ! ቱሪ በጣም ተደስተ። ጎንቻን ወደደው። አመለከው:: ብዙዎቹ እንፈፅምልሀለን እያሉ ገንዘቡን በልተው ጠፍተዋል፡፡ ጎንቻ ግን ካሰው፡፡ አስቦረቀው አስፈነደቀው እሱም ጎንቻን ሊክስው ሊያስፈነድቀው ፈለገና ከውላቸው
ውጪ አምስት መቶ ብር ጨምሮ ከነቀሪው ሶስት ሺ ብር ጀባ ብሎ
ጎንቻ ብሩ በእጁ እንደገባ ያንን ምኞቱን በቶሉ ሊፈፅም አሰበ፡፡ አዎን ገንዘቡን በሙሉ ለብቻው ካደረገ ጀሌዎቹ እንደማይለቁት ያውቃል።ታዲያ መላው ምንድን ነው? ጎንቻ ጥቅምና ጉዳቱን በጥሞና አሰላሰለ፡፡አለሚቱ ካልጠፋን ብለዋለች ወደደም ጠላም ከአለሚቱ ተነጥሎ መኖር
አይታሰብምና አብሯት መጥፋቱ ቁርጥ ነው። መጥፋቱ ካልቀረ ደግሞ ከጃኖ ቤት ያገኘውንና ከባላባት ቱሬ የተቀበለውን ገንዘብ የብቻው አድርጎ ማስቀረት አማራጭ የሌለው ነው። ጎንቻ ከመጨረሻ ውሳኔ ላይ ደረስ፡፡
ያንን የሚወደውን ጫካ ትቶ ከዓለሚቱ ጋር እሷ ወደምትፈልገው አገር
ቢሄዱ በእጃቸው በቂ ገንዘብ አለና ችግር እንደማይገጥማቸው ተማመነ፡፡እሷ ዘንድ ካስቀመጠው ጋር ሲደማመር ጥሩ አድርጎ ሊያቋቁማቸው እንደሚችል ገመተና ይህንኑ ሂዶ ሊያሳውቃት ተጣደፈ።

እነ ጊርቦ ደግሞ ከአሁን አሁን ያካፍለናል በሚል እምነት በጉጉት እየጠበቁት ነው። ያቀምሰናል ድርሻችንን ይጥልልናል ብለው እንደ ቀላዋጭ ውሻ ከንፈራቸውን እየላሱ ዓይን ዓይኑን እየተመለከቱት ነው። ጎንቻ
ግን ዝም አላቸው:: ለወትሮው እምብዛም የሚያረካቸው ባይሆንም ለአፍ መዝጊያ ያክል ከፀበሉ ረጨት ያደርግባቸው ነበር፡፡ የአሁኑ የአለቃቸው
ማድፈጥ ታዲያ ለምን ይሆን? ነገሩ ሆድ ሆዳቸውን ሲበላቸው ከረመ::ውሎ ሲያድር ጊርቦ እንደምንም ብሎ ወኔውን አሰባስቦ ትንፋሹን ውጦ
ጥያቄ አቀረበለት፡፡

“የምትደርሰንን አስበህ ወርውርልን እንጂ ምነው ዝም አልከን ጌታዬ?" ጭንቅላቱን እያከከ በአክብሮት ጠየቀው። ጎንቻ ጣቱን ከምንሽሯ ቃታ
ላይ እንዳደረገ በየድንጋዩ ውስጥ የሚሽሎኮለከውን እባብ ውር፣ ውር የሚሉ ሽኮኮዎችን እያስተዋለ ከአንድ ትልቅ ድንጋይ ላይ ደገፍ ብሎ ፀሃይ እየሞቀ ነበር፡፡ እንዳልሰማ ሆነ፡፡ ዐይኑ ሁሉ ቦታ ያያል። ቆቅ ወዲያ ማዶ የሚያይ ይምሰል እንጂ የጀሌዎቹን እንቅስቃሴ በንቃት ነበር የሚከታተላቸው፡፡ ሶስት መቶ ስልሳ ዲግሪ የምታይ እንስሳ
አህያ ነች ይባላል እንጂ ጎንቻም ቢሆን በዚህ ረገድ የሚታማ አይደለም፡፡ዐይኖቹ ፈጣንና ቀዥቃዦች ስለነበሩ አካባቢያቸውን በደንብ ይቆጣጠራሉ። ወዲያ ማዶ የሚያይ መስሎ...

"ምነው አሳሰባችሁ እንዴ? አውቄ ነው እኮ ችላ ያልኩት፡፡ ምን የሚያ
ጣድፍ ነገር አለ? አብረን አይደለም እንዴ ያለነው? ኢተያ ሄደን የልማዳችንን እየቀማመስን እንከፋፈላታለን እንጂ ብቻዬን አልበላው?! ምነው ሰጋችሁ?” በፌዝ መልክ ጥርሶቹን ፈልቀቅ አደረጋቸው፡፡ መቼም የጥርሶቹ ነገር አይነሳ! ሲበዛ ነጫጮች በመሆናቸው ከጥቁረቱ ውስጥ እንደ ወተት ፍልቅ እያሉ ለየት ያለ ውበትን ይፈጥሩለታል፡፡ ጊርቦ ይህንን የተስፋ ቃል ከአለቃው አንደበት ሲስማ ልቡ መለስ የሱም ጥርሶች የአለቃውን ተከትለው ብልጭ አሉ፡፡ ጥርሶቹን ብርድ ማስመታቱን አላወቀም
ነበር፡፡ ጎንቻ ብቻውን ዋጥ ስልቅጥ ሊያደርጋት ማሰቡን በፍፁም አልጠረጠረም ነበር፡፡ ሁለቱ ይህን ሲነጋገሩ ቱሲ ራቅ ብሎ ከአንድ ትልቅ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ ይመለከታቸው ነበር፡፡

“ዘራፍ የጎንቻ አሽከር!" አለና አፈሙዙን አዞረ፡፡ በጣም ትልቅ ርዝመቱ ከአስር ሜትር የሚበልጥ ዘንዶ በጎንቻ አናት በኩል ተምዘገዘገ...
“እረፍ!" አለና ጎንቻ ተቆጣ፡፡ ዘንዶው ከሰሰሰስ እያደረገ በጢሻው ውስጥ እየተሹለከለከ ሄደ። አሁን አሁን ጀሌዎቹ ሲፎክሩ በአለቃቸው ስም ሆኗል። የአለቃቸው ድፍረት፣ የአለቃቸው ወደር የማይገኝለት ጭካኔ፣ የአለቃቸው ተጠራጣሪነትና ጠንቃቃነት እነዚህ ሁሉ ተፅዕኖ አሳድረውባቸው የሚፎክሩት በራሳቸው ጀግንነት ሳይሆን በሱ አሽከርነት ሆኗል፡፡

በጃኖ ላይ አደጋ ጥለው ከተመለሱ በኋላ ለአንድ ሳምንት ያክል በኛሮ ጫካ ውስጥ የአውሬ ስጋ ብቻ እየበሉ ሰነበቱ፡፡ ጎንቻ የዓለሚቱ ጠረን መዓዛዋ በናፍቆት አውዶታል። በተለይ አሁን አሁን የምትቀባው ሽቱ አቤት ጠረኗን ማጣፈጡ! ድሮም ለሱ ማር የነበረችው ዓለሚቱ በውበቷ
ውስጥ ሌላ ውበት በጣፋጭነቷ ውስጥ ሌላ ጣፋጭነት በመአዛዋ ውስጥ ሌላ መአዛ እያመነጨች ነፍስና ስጋውን በፍቅር እያነደደቻቸው ነው።ዛሬ ግን የአንድ ሳምንት ናፍቆቱን በተለይም ደግሞ የመጥፋቱን ነገር ካብሰለሰለ በኋላ ውሳኔውን ሊነግራት ሳምንቱ እንደ ዓመት ረዝሞበት ከምንግዜውም የበለጠ በናፍቆቷ እየተሰቃየ ነው፡፡ይሄንኑ ናፍቆቱን ሊወጣ፣ ሚስጢር ሊያጫውታት፣ ውሳኔውን ሊገልፅላትና ረብጣ ገንዘብ ሊያስታቅፋት የሚሄድበት ዕለት ስለሆነ መንገዱ ሁሉ አላልቅልህ አለው፡፡ ሶስቱም በጥድፊያ እየተዋከቡ ገና ከምሽቱ
አራት ሰዓት ሳይሆን ኢተያ ከተማ ገቡ፡፡ ጮማው ተቆረጠ፡፡ አረቄው
ተጨለጠ፡፡ ተሰከረ። ተፈነደቀ። ለጀሌዎቹም ሴቶች መጡላቸውና ለብዙ ጊዜ የዘነጉትን ወንድነታቸውን ፈተሹ፡፡ በደስታ አበዱ፡፡
"እንዲህ ነው እንጂ! ይሄ ነው አለቃ ማለት!" አለ ጊርቦ ባለፈው ጊዜ ብቻውን መደብ ላይ ተኮራምቶ ያደረበትን ደረቅ ምሽት አስታውሶ።ጎንቻና ዓለሚቱ ለሚስጢር ጨዋታ እንዲያመቻቸው ለብቻቸው ሆነና
ጨዋታቸውን ቀጠሉ...

"ስሞኑን ሳወጣ ሳወርድ ከረምኩ፡፡ ወደ ሻሽመኔ፣ወደ አሰላ፣ ወደ ናዝሬት፣ደብረ ዘይት ሁሉ ተመኘሁ እነኝህ ሁሉ አልተዋጠልኝም፡፡ ትንሽ ከተማ መግባት ትርፉ ለሰው ዐይን መጋለጥ ነው፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ከደጅ ወደ ጓሮ ነው፡፡ አሁን መጨረሻ ላይ ግን የት አስብኩ መሰለህ?"
እየሳቀች። በመጨረሻ ላይ የት ለመሄድ እንደወሰነች ጎንቻ መገመት እንዳለበት በማሰብ ጠየቀችው። እሱ ግን የአውሬ ኮቴ የማያይበት፣ የአራዊት ጩኸት የማይሰማበት ጠረናቸውን የማያሽትበት ዳገት ቁልቁለት
የሌለበት፣ ጫካ ዋሻ የሌለበት የከተማ ኑሮው የት ሊሆን እንደሚችል በፍፁም መገመት አልቻለም ነበር።

"ሸገር! ሸገር! አዲስ አበባ! አዲስ አበባ!" ተፍነከነከች።
“አዲስ አበባ?ሸገር? " ስሙን በአዕምሮው ደጋገመው። "ልክ ነው" አለ፡፡ ዝናውን የሚያውቀው ሸገር፣ በጣም ሰፊ የሆነው ሸገር ጥሩ ዋሻ መሸሸጊያ ሊሆናቸው እንደሚችል እሱም ርግጠኛ ሆነ፡፡
"በቃ ይሁን!" አለና አቀፋት። በሸገር ተስማሙ:: በከንፈር ማህተም የሸገር ኮብላዮች መሆናቸውን ተፈራረሙ:: እሷ ገንዘቡን ጠቅልላ ልታስቀምጥ እሱ ደግሞ በማግስቱ በለሊት ሊመጣ ወሰኑና ተለያዩ።

ወደ ኛሮ ሲመለሱ ገንዘቡን እነቱሲ ጠይቀውት ነበር፡፡ ሞቅታ ስላለብን ነገ ማታ እንከፋፈላን አላቸው፡፡ነገ ገንዘቡን እንደሚከፋፈሉ ተስፋ ሰንቀው አስደሳች እንቅልፍ ወስዷቸው አደረ።
ጠዋት ፀሃይዋ በኛሮ አናት ላይ ብቅ አለችና አካባቢውን በብርሃኗ ወለል አደረገችው።አራዊት ከጎሬአቸው ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል። ደስ የሚል ቀን ነበር፡፡ ያለወትሮው ብቅ ያላለው ያልነቃው ጎንቻ ነበር። ጊርቦና ቱሲ
እየተንጠራሩና እያዛጉ ተገናኙ ጌታው ሚስቱ አድክማ ነው የላከችው መስለኝ አልነቃም" አለ ጊርቦ፡፡
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

...ኑሮ በክበረ መንግስት ለሔዋን አልተመቸም፡፡ በእናት በአባቷ ቤት ደባል ብቸኛ ሆናለች፡፡ ተወልዳ ባደገችበት አገር ባይተዋር ሆናለች ዙርያዋን ብዙ ሰው እያለ ብቸኛ ሆናለች በሃሳብ እና በጭንቀት
ብዛት ራሷን ረስታለች፡፡ ብትበላ ብትጠጣ ሆዷ ይጥገብ እንደሆን እንጂ መንፈሷ ግን ረሀብተኛ ሆኗል።
ባህሪዋም ተለውጧል። ደስተኛ የነበረች ሔዋን ብስጩ ሆናለች። ፍልቅልቋ ሔዋን አኩራፊ ሆናለች፡፡ ታዛዥና ትሁት የነበረች ሔዋን ነጭናጫ ሆናለች።ተጨዋቿ ሔዋን በትካዜ ተውጣ በጭንቀት ተወርሳለች፡፡ ጤንነቷም ተጓደለ፡፡
ዘወትር 'ልቤን' ማለት አበዛች፡፡ ከመቆም ይልቅ መቀመጥን፣ ከመቀመጥም መተኛትን አዘወተረች።የምግብ ፍላጎት አጣች። ከምትብላው ምግብ ይልቅ የምትጠጣው ውሃ ያማራት ጀመር። ከቶም 'ብይ' ባትባል ደስታዋ ሆነ፡፡ - የግድ ብትበላም ብዙ አይስማማትም። እሷ ተቸግራ ቤተሰቦቿንም አስቸገረች፡፡ የህመሟ ጉዳይ
ቤተሰቦቿ በተለይ በአባትና እናቷ ዘንድ ሌላ ስጋት ፈጠረ፡፡ 'ያ የልጅነት ህመሟ ሊነሳባት እያሉ ይጨነቁ ጀመር።

ስጋታቸው መነሻ አለው፡፡ ሔዋን በህጻንነቷ እስከ ሁለት ዓምቷ ድረስ ፍፍት፣ ድንቡሽቡሽ ያለችና ፍልቅልቅ ነበረች። ከዚያ በኋላ ግን ምንነቱ ባልታወቀ በሽታ ሁለመናዋ ተለዋወጠ፡፡ ሰውነቷ እየከሳ ቆዳዋ እስከ መሸብሸብና እየጠቆረ መልኳ እስከ መቀየር ደረስ፡፡ በእግሯ መሄድ ከጀመረች በኋላ ወደ መዳህ! ቀጥሎም
ቁጭ ብላ ቀረች፡፡ ለቅሶ የማታውቀው ሔዋን መብሰክሰክ አብዝታ አልቃሻ ሆነች።
ወላጅ አባትና እናቷ ትሞትብናለች እያሉም መስጋት ጀመሩ።
የእሷን ህይወት ለማትረፍ ያልተደረገ ጥረት አልነበረም፡፡ በተለይ እናቷ ያልተሳለባት ቤተክርስቲያን ያልሄዱበት ጠበልና ያልጠየቁት ጠንቋይ አልነበረም።
ዘመናዊ ህክምናም እንዲሁ፡፡ የሔዋን ጤንነት ግን አንዳችም መሻሻል ሳያሳይ ድፍን ስድስት ዓመት ሞላት፡፡ እናቷ ሲፈጩም ሲጋግሩም፣ ሲያነፍሱም ሲቀቅሉም ገብያ ሲሄዱም እንኳ ልጃቸውን አቅፈው ወይ አዝለው መንከራተት ግድ ሆነባቸው።

የሔዋን እናት በዚሁ ሁኔታ በመልፋት ላይ ሳሉ ረንድ ቀን ያልታሰበ ሁኔታ ገጠማቸው:: ቤታቸው ከክብረ መንግስት ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ ከከተማው
ወጣ ብሎ በሚገኝ ገጠራማ ሥፍራ ስለሆነ የሱቅ ዕቃ ሊገዙ ሔዋንን ታቅፈው መደ ከተማ ሄዱ፡፡ ከአንድ ሱቅ ደርሰው የግዢ ወረፋ ሲጠብቁ ሔዋንን በሱቁ
ባንኮኒ ላይ አስቀመጧት:: ሔዋን ምንም እንኳ በህመም ምክንያት ሰውነቷ ቢጥመለመልም ነፍስ እያወቀችና አፏን እየፈታች በመሄዷ በሱቁ መደርደሪያ ላይ
የሚታዩ የሸቀጥ ዓይነቶችን ለእናቷ እየጠቆመች “ያ ምንድነው እማ? ያስ? ያኛውስ?… እያለች ትጠይቃቸዋለች፡፡ እሳቸውም ያወቁትን ያህል ያስረዷታል።
በሰቁ ውስጥ ዕቃ ሊገዙ የገቡ አንዲት ዕድሜያቸው ወደ ስልሳ የሚጠጋ ሴት አዛውንት ሔዋንና እናቷ የሚመላለሱትን እያዳመጡ በተለይ ሔዋንን አየት ያደርጓት ኖሯል፡፡ ጤነኛ እንዳልሆነች ከሁኔታዋ እየተረዱ ከንፈራቸውን እየመጠጡ ሲያዝኑላት ቆይተው የገዙትን ዕቃ በመቀነታቸው ላይ ከቆጣጠሩ በኋላ «ይቺ ልጅ ስንት ዓመቷ ነው የኔ እህት? ሲሉ የሔዋንን አናት ጠየቋቸው።
«እድሜዋ እንኳ ስድስት ዓመት ሞላት፡፡»
«ጤና የላትም?»
«የላትም የኔ እናት! በጣም ተቸግሪሃለው። ከሁለት ዓመቷ ጀምሮ ይኸው ተንገላታባኛለች።
ይኸው አራት ዓወት በሙሉ እሷን አዝዬ እኖራለሁ።
«እምም...ም» አሉና ሴትየዋ ቤትዎ የት ነው?» ሲሉ ጠየቋቸው
የሔዋን እናት በምልክት ሲነገራቸው። «እስቲ አንድ ቀን ብቅ ብዬ እጠይቆታለሁ ምናልባት መዳኒት ያገኘሁላት እንደሆን።» አሏዋቸው።
«ሆኖ ነው የኔ እናት!» ብለው፧ የሔዋን እናት ፍንድቅድቅ እያሉ «አገርዎ የት ነው?»ሲሉ ጠየቋቸው።
«ቅርብ ነው:: ተሲያት ላይ ብነሳ እርስዎ ቤት መድረስ እችላለሁ፡፡»
«አደራ የኔ እናት! እንደው አደራ እንደው አደሪ» በማለት የሔዋን እናት ሴትዮዋን አጥብቀው ተማፀኗቸው::»
«አላህ ከፈቀድ ሳምንት እመጣለሁ::"»
«እሺ የኔ እናት፤ እጠብቅዎታለሁ::»
እዛውንቷ ሴት ቀጠሮአቸውን አክብረው ከሔዋን ወላጆች ቤት መጡና የባህል ህክምናቸውን ጀመሩ ሔዋን አካላቷን እንድትታጠብ ከአደረጉ በኋላ
ራሳቸው ታቅፈው ቅባት መሰል በሆነ ነገር መላ አካላቷን እየቀሱ ያሿት ጀመር፡፡ ያን ሲጨርሱ ሌላ መድሃኒት በማር እየበጠበጡ ያጠጧታል። እምቢ ስትላቸው
የግድ ይግቷታል። በዚህ ዓይነት ለሰባት ቀናት እራሳቸው ከአከሟት በኋላ ለሚቀጥሉት ሰባት ቀናትም እናቷ እንዲያደርጉላት መክረዋቸው ወደ አገራቸው ተመለሱ።የሔዋን እናትም በተመከሩት መሰረትም ፈፀሙ።

ዘመናዊ የህክምና ጠበብቶች እንዴት ሆኖ? ምኑ ከምን ተገናኝቶ? ለሜን ዓይነት በሽታ ያ
ምን ዓይነት መድሃኒት? አወሳሰዱስ? መጠኑስ? ወዘተ እያሉ አመክኒየአቸውን እንደ ስጋ እየዘለዘሉ ሊጠያየቁ ይችሉ ይሆናል፤ የሔዋን ጤንነት
ግን ከዕለት ወደ ዕለት እየተሻሻለ ሄደ። የተሸበሸበ ቆዳዋ ወጠር፣ ፊቷ ፈካ፣ እያለ ከመምጣቱም በላይ መዳህ ጀመረች። ህክምና በተደረገላት በሁለተኛው ወር ቆማ
መሄድ ቻለች፡፡ ሦስት ወር ሲሞላት ሙሉ ጤነኛ ሆነች::
የሔዋን እናትና አባት የተሰማቸው ደስታ ወሰን አልነበረውም። ሔዋን
እንደገና እንደ ተፈጠረች ቆጠሯት፡፡ እየተመላለሱ የሚጠይቋትን ሀኪሟን ሴት
የሚያደርጉላቸውን አጡት ሰጥተዋቸው አልረካ አሉ፡፡ አመስግነዋቸው አልጠግብ
አሉ። ሁሉም ነገር ሳያረካቸው ቢቀር ቅድስት የነበረውን የሔዋን ስም 'ሀዋ" ብለው በአዛውንቷ ስም ቀየሩት። ነገር ግን በዘር ማንዘራቸው ክርስቲያን ስለሆኑ ከዚያው ሳይርቁ «ሔዋን» በሚል ተኩት፡፡ እነሆ ቋሚ ስሟ ሔዋን ሆኖ ቀረ::
ዛሬ ታዲያ 'ልቤን' እያለች ስትሰቃይባቸው፣ ድካም እየተሰማት ድፍት ብላ
ስትውልባቸው፣ ምግብ በአግባቡ መመገብ አቅቷት ሲያዩ፣ ፍዝዝ ትከዝ ስትል እየተመለከቱ እጅጉን ይሰጉ ጀመር፡፡ ወደ እመት ሐዋ አይሮጡ ነገር እመት ሐዋ
መሞታቸውን ከሰሙ ቆይተዋል። ወደ ዘመናዊ ሀኪም ቤት ወስደው
ሊያስመረምሯት ሀኪሞቹ የልብ ችግር እንዳለባት አረጋግጠው ክኒን ብቻ ሰጥተው የራሷ ሃኪም ራሷ ናት፡፡ ሃሳብና ጭንቀት ካለባት ያንን ትታ መንፈሷን ማረጋጋት እረፍት ማድረግ ይኖርባታል አሏቸው። ይሄ ደሞዝ በሔዋን በኩል የሚሞከር አልሆነም፡፡ ከሀሳብ " ከትካዜና ከጭንቀት ማን ጎትቶ ያውጣት?
ከህመሟ በተጨማሪ ያለባትን የውስጥ ችግር የሚያውቁላት እናቷ ግን ተስፋ አልቆረጡም' ሔዋንን የማረጋጋት ጥረታቸውን ቀጠሉ፡፡ መጀመሪያ ፍላጎቷን አጠኑ። ሔዋን ቤት ውስጥ ከሆነች መደብ ላይ ጋደም ማለት ነው ቤቱ ሲጨንቃት ወደ ጓሮ ሄዳ ከዛፍ ስር መቀመጥ ነው
ጓሮአቸወ ደግሞ ሰፊና በትላልቅ ዛፎች የተሞላ ነው። ሔዋን ከዛያ ውስጥ በአንዷ ዛፍ ስር መቀመጥ ታዘወትራለች ያንንም አጠኑ።
አቀማመጧ ይመቻት ዘንድ የዛችን ዛፍ ዙርያ በአፈር ደለደሉ፡፡ በፀሃይ ጊዜ አቧራ በዝናብ ጊዜ ጭቃ እንዳይሆንባት ሳር ተክለው ውሃ እያጠጡ አለመለሙላት ይበልጥ
👍91
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....የሕዳር ቁስቋም ዕለት ነው። ምንትዋብ ትልቅ ግብር ጥላለች። ምግቡም፣ወይን ጠጁም፣ ጠጁም፣ አረቄውም በገፍ ተዘጋጅቷል። አስቀድማ፣
ዛሬ ሊቃውንቱና ካህናቱ ከገቡ ወዲያ ዋናውን ሆነ የስርቆሹን በር
እንድትዘጉ። የወይን ጠጅም እየደጋገማችሁ እንድትሰጧቸው” ብላ ትዕዛዝ አስተላልፋለች።

“ይኸ ሁሉ ስለምንድርነው?” ሲል ጠየቃት፣ ኢያሱ።

“ዛሬ ካህናቱንና ሊቃውንቱን ጉድ ሠራለሁ።”

“እንዴት አርገሽ... ደሞስ ስለምን?”

“እነሱ ሁልግዝየ በቅኔው፣ በተረትና ምሳሌውና በመጠጥ ያቸንፉኛል።
ዛሬ ግን እኔ አቸንፋቸዋለሁ ብዬ ተነስቻለሁ።”

ሳቀ ኢያሱ ።
ከቅዳሴ በኋላ፣ ከየደብሩ የተጋበዙት ካህናትና ሊቃውንት ወደ ቤተመንግሥት ተመሙ። ሠዓሊዎችና ሙዚቀኞችም ጎረፉ። የግብር ሥርዐት ተጠብቆ ምግብ ተበላ። የወይን ጠጅ ተቀዳ ። የካህናቱና የሊቃውንቱ ዋንጫ ሲጎድል አጋፋሪዎች በታዘዙት መሠረት እየተመላለሱ ሞሉ።

እንግዶቹ ፊኛቸው አስቸገራቸው። ሊወጡ ፈልገው ቢነሱ ከፊት
ከኋላ በሩ ዝግ ነው። የሚከፍት የለም። ተጨነቁ፤ ተጠበቡ። እየተያዩ መቅበጥበጥ ብቻ ሆነ። በመጨረሻ መለኛው ሊቅ አለቃ ኢሳያስ ተነሥተው እናትና ልጁን እጅ ነሱና፣ “እቴጌ አንድ ነገር እንድጠይቅ ይፈቀድልኝ” አሏት።

“ይበሉ ይጠይቁ።”

“እቴጌ አምስት መቶና አምስት መቶ ስንት ነው?”

ያልጠርጠረችው ምንትዋብ፣ “ምን ያለ ጥያቄ ነው? ይኸ ሊያቅተኝ? ሽ ነዋ!” አለች።

አለቃ ኢሳያስ፣ “እቴጌ “ሽናዋ' ብለዋል” ሲሉ ያ ፊኛው አስጨንቆት የነበረ ሊቅና ካህን ሁሉ የተቀመጠበትን ከህንድ ሃገር የመጣ ስጋጃ አረሰረሰ።

ምንትዋብ በመሸነፏ ሳቀች፣ ተንኮሏ እንዳልሠራ ተገነዘበች።
በእርግጥም ሊቃውንቱን ማሸነፍ እንደማትችል ተገነዘበች። አለቃ
ኢሳያስን ለብልሐታቸው ሽለመቻችው። አዲሱ የግብር ኣዳራሽም በሕዝብ ዘንድ “ሽናዋ” የሚል ስያሜ አተረፈ።

ከሽናዋ በኋላ፣ የሴቶች ሙያ ትምህርት ቤቱ ግንባታ ተጀመረ።
ግንባታው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ሴቶች ተመርጠው እንደ
ፈትል ያሉ ልዩ ልዩ የእጅ ጥበባትና ዶሮ መገነጣጠል እንዲማሩ ሆነ።
ተማሪዎቹ ዶሮ አስራ ሁለት ብልት እንዳላት አወቁ። ፊደልና የቁም
ጽሕፈት እንዲከታተሉ ተደረገ። ምንትዋብ ልትጎበኛቸው በሄደች
ቁጥር በሙያና በትምህርት በርትተው እንዲማሩ አስጠነቀቀች።ከዓመታት በፊት አያቷ የነገሥታት ዝርያዎች ወህኒ ይላካሉ እዛው አርጅተው ይሞታሉ፣ ብለው ሲነግሯት፣ “ክፉ ነገር። እኼማ መሆን የለበትም” እንዳለችው ከጸሎት ቤቷ በስተቀኝ በኩል የአፄ በካፋ ዘመዶች ሆኑ የሌላ ነገሥታት ዝርያዎች ወይንም የራሷ ዘመዶች መኖሪያና መማርያ የሚሆን ህንፃ አሠርታ፣ ልጆቹ ወህኒ አምባ በእግር
ብረት ታስረው ከመማቀቅ ይልቅ ፊደል፣ የቁም ጽሕፈትና ፍትሖ
ነገሥት እንዲማሩ ሆነ።

ምንትዋብና ኢያሱ ስማቸው ከአጥናፍ አጥናፍ ገነነ።

ምንትዋብና ዳግማዊ ኢያሱ ስማቸው ቢገንም፣ አልፎ ኣልፎም ቢሆን በመኳንንቱ ዘንድ “ቋረኞች” ላይ ጥርጣሬ ስላለ፣ ምንትዋብም ብትሆን ያለነሱ ድጋፍ ርቃ እንደማትሄድ ስለምታውቅ በጉዳዩ ከኢያሱ ጋር መምከር ፈለገች።

“ኢያሱ እንዳው አንድ ነገር ላጫውትህ ብየ” አለችው፣ አንድ ቀን እንቁላል ግንብ ውስጥ ተቀምጠው እየተጫወቱ ሳለ።

“ምን ነገር?”

“እንደምታውቀው “ቋረኞች” ሚሉ ዘይቤ እንደ ዱካ ይከተለናል።
ሥልጣኑን ሁሉ ቋረኞች ይዘውታል ይላሉ። ይሰንብት እንጂ ቀን
ጠብቀው በኛ ላይ መነሳታቸው አይቀርም። የጎዣም፣ የትግሬ፣
የቤገምድርና የስሜን መኳንንት ዋዛ ማዶሉ። ይመስገነው እስታሁን ሰላም ነን። ወደ ፊት ግን እንጃ ሰላማችን ሊደፈርስ ይችላል ብየ ሰጋለሁ።ሰላም ማጣት ብቻ ሳይሆን አልጋውን ሊፈታተኑ ይችላሉ። የወህኒዎቹ
እንደሆኑ ዐይናቸው መቸም ግዝየ ኻልጋው ላይ ተነስቶ አያውቅም።
ተዘጋጅቶ መቀመጡ አይከፋም። ሥልጣን አይበቃቸው፣ ጉልት፣
ርስትና ርስተ ጉልት ለስንቱ መኳንንት ሰጠን። አይጠቅማቸውም።ኢያሱ ጥቂቱ እኮ ነው ላገሬ ሚለው። ኻለነሱ ድጋፍ ደሞ አይሆን።እነሱን ለማስታገስ ስንቱን ድሬ ጨረስሁ። አሁንም ቢሆን አርቀን ማሰብ አለብን። ነገ አንዱ ቢነሳ አጋዥ ያስፈልገናል። እና አሳቤ ምን
መሰለህ ይኸ የስሜን፣ የጎዣም፣ የቤገምድርና የትግሬ ባላባት ሁሉ
ቀልቡን ሰብስብ እንዲያረግ ወሎዎች ጠንካራ ጦር አላቸውና ኸነሱ ጋር በጋብቻ ብንተሳሰር ምን ይመስልሀል?”

“ኣሳብሽ መልካም ነው። ማነን ልታጋቢ አሰብሽ?”

“አንተን።”

“እኔን?” ከት ብሎ ሳቀ።

“አዎ አንተን:: ብዙ አስቤበት ነው። አሁን ኸወሎች ጋር መጋባት
ያስፈልጋል። የልገሮችህ እናት...” ዕቁባት ሆና ትቀመጣለች ማለት
ፈልጋ ዝም አለች።?
“እና እኔን ኸማን ልታጋቢ ነው?” አላት፣ ዝም ስትል ።

“ውቢት ምትባል የወሎ ባላባት ልዥ አለች። አጠያይቄ አለላ ናት
አሉ። ብቻ የወሎ ልዥ ስለሆነች በድብቅ መሆን አለበት።”

ኢያሱ ስለመኳንንቱ ያለችው አሳስቦት ነበርና ዝም አለ። ምንትዋብ ዝምታውን እንደ እሺታ ቆጠረች።

ብዙም ሳይቆይ ምንትዋብ የወሎ ባላባት ልጅ የሆነችውን ውቢትን
ከኢያሱ ጋር አጋባች። ውቢትን ክርስትና አስነስተው ወለተቤርሳቤሕ አሰኝተው፣ የመኳንንቱን ጉምጉምታ ለማቀዝቀዝ በድብቅ ኣስቀመጡ።
ውቢት ኢዮአስ የተባለ ወንድ ልጅ ወለደች።

ምንትዋብና ኢያሱ ምንም እንኳን ራስ ቢትወደድ ወልደልዑል
መንግሥታቸውን ከዘመዶቹ ጋር አስከብሮና አጠናክሮ ቢይዝላቸውም፣ባላባቶች ከወሎ በማምጣት ሥልጣን ላይ አስቀመጡ። ሲያንገራግር
የነበረውን የጎጃሙን ባላባት ዮሴድቅን ደግሞ፣ ደጃዝማች ብለው፣ይዞታውን ጨምረው፣ በኋላ ሞጣ ጊዮርጊስን የደበረችውን ወለተእስራኤልን ድረውለት አረጋጉት።

እናትና ልጅ ያሰቡትን ሥራ ላይ ከማዋል አልቆጠብ አሉ። በተለይም ኢያሱ ለአትክልት ቦታ ልዩ ፍቅር ስለነበረው፣ ጐንደርን አፀድ በአፀድ አደረጋት። ሎሚና ሌሎች ፍሬዎች ጐንደርን የመዓዛ ባለፀጋ አደረጓት።

አብያተ ክርስቲያናትን በጭልጋ፣ አለፋ ጣቁሳና ጐንደር በኖራ
አሠሩ። ሌሎችን አሳደሱ። ጣና ሐይቅ በታንኳ እየተመላለሱ ኢያሱ
ክብራን ገብርኤልን ሲያሳድስ፣ እሷ ደቅ ውስጥ “ስሞት እቀበርበታለሁ” ያለችውን ናርጋ የኛ - ሥላሤን በጡብና በጐንደርኛ ይዘት አሠራች። ናርጋ ሥላሤን ስታሠራ፣ ሥሙር የተባለውን የራሷን ምስል የላከላትን ሠዓሊ አስታወሰች። እንዴት ሊገኝ እንደሚችል አሰበች።ሌሎች ሠዓሊዎች በሥዕል ሥራው ተሳተፉ። ናርጋ ሥላሤ በሥዕል
አሸበረቀች። ምንትዋብ አክብሮቷን ለመግለፅ ከማርያምና ከክርስቶስ
እግር ሥር የራሷን ምስሎች አሠራች። አብያተ ክርስቲያናቱ የሥዕል ባለቤት ሆኑ።

ብርሃን ሰገድ ኢያሱ “ብዙው መጻሕፍት ወደ ክብራን ገብርኤል
እንዲሄዱ ፈቃዴ ነው” ባለው መሠረት ከተለያዩ የሃገሪቱ ከፍሎች የተሰበሰቡ በሺህ የሚቆጠሩ መጻሕፍት ክብራን ገብርኤል ገብተው
ተቀመጡ።

“አንተ ደሞ ሁሉ ነገር ወደዛ እንዲኸድ ትፈልጋለህ” ብላ ፈገግ
አለች፣ ምንትዋብ አንድ ቀን። ቀጠል አድርጋ፣ “ለየደብሩ እኩል
ማከፋፈል ነው እንጂ” አለችው።
👍11