አትሮኖስ
282K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
491 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ

...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡

ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡

“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡

ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....

ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡

ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡

እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡

በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡

እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
👍3