አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ስምንት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ


#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

..ለቀናት የተጓዝን ይመስለኛል። ሁለት ስዎች ድንገት ግንባራችን ላይ መሳሪያ ደቅነው ተንቀሳቀሱ እስከ ሚሉን ድረስ
ምንም አላስታውስም:: ከባድ መሳሪያ AK 47፣03 እና HPG ይዘው በሁለት ረድፍ ነዱን:: ፊታቸው በጣም ጥቁር ከመሆኑ የተነሳ ክስል የተቀቡ ነበር ሚመስለው። ቀይ በርበሬ በሚመስሉ
አይኖቻቸው አፈጠጡብን። በመንገዳችን የደንብ ልብሳቸው በደም የተጨማለቀ አራት ሰዎች መሬት ላይ ወድቀዋል። ፊቴን
ለማዞር ስሞክር ራሱን የተመታ ሌላ ሰው ተመለከትኩ።አጥወለወለኝ፡፡ ሁሉም ነገር በዙሪያዬ ሲሽከረከር፤ ሲዞርብኝ አንዱ ወታደር ተመለከተኝ። የውሃ ዕቃውን አውጥቶ ትንሽ ከተጎነጨ በኋላ የቀረውን ፊቴ ላይ ደፋብኝ፡፡

“ትለምደዋለህ ፤ ሁሉም ሰው በመጨረሻ ይለምደዋል” አለ።

የተኩስ ድምፅ ድንገት አካባቢውን አናወጠው። ወታደሮቹ ስድስታችንን ይዘው ተንቀሳቀሱ፡፡ የወታደር ጀልባ ከመተረጊስ ጋር የሚንሳፈፍበት አንድ ወንዝ ደረስን :: በወንዙ ዳርቻ የአስራ
አንድ ፣ አስራ ሁለት አመት የሚሆናቸው ታዳጊ ወታደሮች አስክሬን ወድቋል:: ፊታችን አዙረን ጉዞችንን ቀጠልን። የተኩሱ ድምጸ እየጨመረ መጣ፡፡ ወደ ጀልባው ስንወጣ ተኩሱ ወደ እኛ
ተቃረበ። ሮኬት ይወረውራሉ፤ የወንዙ የላይኛው ክፍል በተኩስ ተናወጠ፡፡ እሳት ላይ እንደተጣደ ወሃ ወንዙ በጥይት ናዳ ፈልቶ ይፈለቀለቃል:: የወታደር ልብስ የለበሰ ሰው ወደ ጀልባዎች እየሮጠ ወደ ወታደሮቹ መተኮስ ጀመረ:: ከእኛ ጀልባ ካሉት ወታደሮች አንዱ ተኩሶ ሰውየውን ጣለው:: ጀልባዎቹ ወደ ታች ሲወርዱ ዘለን ወጣን፡ ወታደሩ ጦር ወደ ሰፈረበት የል ወደ ሚባል መንደር ይዞን መራን። ከአስር ቤቶች በላይ ያሉበት ትልቅ
ሰፈር ነው። አብዛኞቹ ቤቶች በወታደሮቹ የተያዙ ናቸው።ወታደሮቹ እኛ በገባንበት በወንዝ ዳርቻ በኩል ካሉት ዛፎች
በስተቀር በአካባቢው ያሉ ዛፎችን ቆርጠዋል። ከድንገተኛ ጥቃት
ራሳቸውን ለመታደግ እንዳደረጉት አስረዱን::

በመጀመሪያ በዚህ በ የል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ደህንነት ያገኘን መስሎን ነበር። መንደሩ ሞቅ ደመቅ ያለ ሳቅ
እናጨዋታ የሞላበት ነበር፡፡ አዋቂዎች፣ የታጠቁ እና ያልታጠቁ የመንደሩ ሰዎች ስለ አየር ንብረት፣ ስለ አዝመራ እና ስለ አደን ያወራሉ። ስለ ጦርነቱ ግን ምንም ማውራት አይፈልጉም አያወሩም፡፡ በመጀመሪያ ሰዎች ለምን እንደዚህ እንደሚሆኑ አልገባኝም ነበር፡፡ ቀስ በቀስ የሰዎች ፈገግታ ስለ ምንም ነገር
መጨነቅ እንደሌለብኝ እምነት አሳደረብኝ፡፡ የሰፈሩ ቀልብ ግን
ያለ አባት እና እናት በቀሩ ልጆች የደበዘዘ ይመስላል።እድሜቸው ከስድስት እስከ አስራ ስድስት የሚሆኑ ወደ ሰላሳ
የሚጠጉ ልጆች ነበሩ። አንዱ እኔ ነበርኩ። ልጅነታችን ለጊዜው ችግር ይግጠመው ወይም ሙሉ ለ ሙሉ እንሰረቅ አናውቅም።

ተሰርቶ ባላላቀ የጡብ ቤት ውስጥ ከሌሎች ልጆች ጋር ማደር ጀመርን። ወታደሮቹ ከእኛ ራቅ ብሎ ባለ አንድ ትልቅ ቤት ውስጥ ፊልም ያያሉ፣ሙዚቃ ያደምጣሉ፣ ይስቃሉ ማሪዋና ያጨሳሉ
ሽታው ስፈሩን ሁሉ ያዳርስ ነበር። ቀን ቀን ከህዝቡ ጋ ተደባልቀው ምግብ እየሰሩ ያሳልፋሉ። ኬን እና እኔ ውሃ በመቅዳት ስሃን በማጠብ እናግዝ ነበር። ሌሎቹ ጓደኞቻችን ሽንኩርት ከተፋ እና መሰል የማዕድ ቤት ስራዎችን ይረዱ ነበር፡፡ ሙሉ ቀን በስራ መጠመዴን ወደድኩት፥
ወንዝ መውረድ፣ መመለስ እና ስሃን ማጠብ፡፡ ከባድ ራስ ምታት
ከሚያስከትልብኝ ሃሳቦች መራቂያ መንገዱ ይሄ ብቻ ነበር።
እኩለ ቀን ሲሆን ሁሉም ስራ አልቆ ምግብ ይቀርባል። ወላጆች ደጃፍ ላይ ተቀምጠው የልጆቻቸውን ፀጉር ይሰራሉ፣ ሴቶች ይዘፍናሉ ወንዶች ደግሞ ኳስ ይጫወቱ ነበር። ደስታው ጫጫታው ከወንዙ ባሻገር ሳይሰማ አይቀርም። በዚህ መንደር ህይወት በፍርሃት አይኖርም፡፡

የኳስ ጨዋታው በማጊቦ የነበረውን የሊግ ጨዋታ አስታወሰኝ፡፡ የእኔ ቡድን ማለትም እኔ እና የተወሰኑ ጓደኞቼ ያሸነፍንበት የዋንጫ ጨዋታ ትዝ ይለኛል። ወላጆቼ ጨዋታውን ለመመልከት ታድመው ነበር፡፡ ጨዋታው ሲጠናቀቅ እናቴ ኩራት እና ደስታ በተደባለቁበት ስሜት ፊቷ በርቶ ተነስታ አጨበጨበች፡፡ አባቴ ደግሞ እኔ ወዳለሁበት ከመጣ በኋላ ራሴን
አሻሽቶ ቀኝ እጄን ወደ ላይ በማንሳት አሸናፊነቴን አወጀ፡፡ ለጁንየርም ተመሳሳይ አደረገ። እናታችን ቀዝቃዛ ውሃ በኩባያ
አመጣችልን። ደስታው የልብ ምቴን ጨመረ፤ ሰውነቴ በላበት ተጠመቆ ነበር። ከጨዋታው በላይ የአባቴ እና እናቴ ደስተኛ መሆን ደስታየን ጨመረው፡፡

አሁን ግን ራሴን ከጨዋታው አገለልኩ። ከቤቱ ጀርባ ተቀምጨ የራስ ምታቴ እስኪበርድ ድረስ ሰማዩን ስመለከት
ቆየሁ፡፡ የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን እንደሚያሰቃየኝ ለማንም አልተናገርኩም፡፡ የወታደሮቹ ሐኪም ጠዋት ጠዋታ ልጆችን ስብስቦ ጉንፋን እና ሌሎችን በሽታዎች እንደተሰማቸው ጠይቆ ህክምና ይሰጣል፡፡ አንድም ቀን ግን ቅዥት ወይም የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን የሚያስቃየው ልጅ ካለ ብሎ ጠይቆ አያውቅም!ማታ አል ሃጂ፣ ጁማህ፣ ሞሪባ እና ኬን በትናንሽ የአለት
ድንጋዮች ገበጣ ሲጫወቱ ነበር። ሙሳ በሰፈሩ ታዋቂ ለመሆን ብዙም ጊዜ አልፈጀበትም። ልክ እንደ ዛሬው ሙሳ ሁሌም ማታ ማታ ለሰፈሩ ልጆች ተረት ተረት ያወራል። እኔ ግን በቤቱ ጥግ
ላይ ቁጭ ብየ ጥርሴን ነክሼ ስቃየን ውጭ አያቸዋለሁ። በአይነ ህሊናየ የእሳት ነበልባል፤ በመንገዴ ያየሁዋቸው አስቃቂ ነገሮች በጨረፍታ እና የህጻናት እና ሴቶች መራራ ጩኸት ይመጣል።ጭንቅላቴ እንደ ደወል ሲደበደብ በዝምታ አለቅሳለሁ። አንዳንዴ የራስ ምታት በሽታው ማይግሬኔ ሲበርድልኝ ለአፍታ ቢሆንም እንቅልፍ ይወስደኛል። ብዙም ሳልቆይ በቅኝዥት እባንናለሁ።
አንዴ ጭንቅላቴ ላይ በጥይት ሲመታ በህልሜ አየሁ። በደም ተጨመለቄ ወድቄለሁ ሰዎች ግን በጥድፊያ ያልፉኛል። ዉሻ መጥቶ ደሜን ይልሳል። ላባርረው ብፈልግም አቅም አልነበረኝም
መንቀሳቀስም አልቻልኩም። በመጨረሻ የፈራሁትን ነገር ከማድረጉ በፊት ከእንቅልፌ ባነንኩ። ከዛ በኋላ የቀሪውን ለሊት መተኛት አልቻልኩም:: አልቦኝም ነበር።

አንድ ቀን የመንደሩ ሁኔታ ድንገት ተለወጠ። ወጥረት ሆነ የውጥረቱ ምክንያት ባይታወቅም አንድ ከባድ
ነገር እንደሚከተል መገመት ይቻላል። በመንደሩ የሚገኙ ሁሉ ወታደሮች የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ትጥቃቸዉ
አሟልተው ተሰበሰቡ፡፡ “ተጠንቀቅ” “አሳርፍ” “ተጠንቀ “አሳርፍ” :: ከአል ሃጂ ጋር ውሃ ለመቅዳት ወንዝ ስወርድ ነው
የአሰልጣኙን ድምፅ የሰማሁት። ስመለስ ልምምድ አብቅቶ መቶ አለቃ ጃባቲ በወታደሮቹ ፊት ቁሞ ይናገራል። ለምሳ
እስከሚለቀቁ ድረስ ለስዐታት ንግግር አደረገ። መቶ አለቃ በሚናገርበት ወቅት የዕለት ተዕለት ስራችንን እየሰራን ምን
እንደሆነ በልጅ አዕምሮችን ለመረዳት እንሞክር ነበር።

ማታ ወታደሮቹ ጠበንጃዎችን ሲያጸዱ ፤ አልፎ አልፎ ወደ ሰማይ በመተኮስ አሳለፉ። ህጻናት ተኩሱን ሲስሙ ወደ ወላጆች እቅፍ ሮጡ። ወታደሮቹ ገሚሶቹ ሲጋራ ማሪዋና ሲያጨሱ የቀሩት ቁማር ሲጫወቱ እና ፊልም ሲያዩ ለሊቱ ተቃረበ።
መቶ አለቃ ጃባቲ ቤቱ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሐፍ ያነብ ነበር።ቀና ብሎ አያይም። ቢጮሁ ቢያፏጩ ቀና ብሎ አያይም።ያለ ወትሮው ፀጥታ ሲሰፍን ድምጸ ሲጠፋ ግን ቀና ብሎ አካባቢውን ይቃኛል። ወደ እሱ ስመለከት አይናችን ተጋጨ እና ወደ እሱ እንድመጣ ጠራኝ፡፡ ቁመቱ ረጂም፣ ፀጉሩ የሳሳ፣ አይኖቹ ትልልቅ እና ጉንጩ ወፍራም ነበሩ። ዝምተኛ ነገር ግን በዝምታው
👍21
ውስጥ ጉልበቱ ስልጣኑ የሚታይ ሞገሱ የሚያስፈራ አለቃ ነበር። ከፊቱ ጥቁረት የተነሳ ሙሉ ፊቱን ለማየት ድፍረት
ይጠይቃል።

በቂ ምግብ እያገኘህ ነው?› ሲል ጠየቀኝ፡፡

“አዎ አልኩ” የሚያነበውን መፅሃፍ ለማየት እየሞከርኩ።

“ሼክስፒር ነው”:: ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ብሎ የመፅሃፉን ሽፋን አሳየኝ። “አንብበህዋል?

ትምህርት ቤት እያለሁ አንብቤው ነበር አልኩት።
የምታስታውሰው ነገር አለ? ብሎ ጠየቀኝ።

“ፈሪ ከመሞቱ አስቀድሞ ብዙ ጊዜ ይሞታል , ብየ ስጀምር ሙሉ ቃለ ተውኔቱን ከእኔ ጋር ደገመ። ልክ እንደጨረስን ፊቱን መልሶ ተኮሳተረ:: እኔን ትቶኝ ትኩረቱን ወደ መፅሃፉ መለሰ።
በሚያነበው መፅሃፍ ይሁን ወይም በአዕምሮ ውስጥ ባለ ሃሳብ ምክንያት ግንባሩ ላይ ያሉ የደም ስሮቹ ሲገታተሩ አየሁ። ቀስ ብዬ ከእሱ ተለይቼ ስሄድ ሰማዩ ከፀሃይ ብርሃን ወደ ጨለማ
እየተሸጋገረ ነበር...

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
በአንዱ ቀን ነው
ሃያ ሁለት ማዞሪያ ጋር የሜክሲኮ ታክሲ
ያዝኩና እስኪሞላ እጠብቃለሁ "በሃሎ ሃሎ" ሜጋፎን የሚለፍፍ የሚመስል ከኋላዬ ያለ ተሳፋሪ ስልክ ይዞ ከጣሪያ በላይ ይጮሃል።

በአማርኛ ፣ ከዚያ ደግሞ በእንግሊዝኛ ፤ በእንግሊዝኛ ፣ መልሶ ደግሞ በአማርኛ : :

አልኩህ እኮ... ዊዝ አውት አይሰጡም : : ዊዝ ይሰጣኩ : :...እ... እ... ኖ... ኖ ሊስን፣ ሚ እንጂ ኖ...! ..ኖ.፣ ... ሊስን ሚ.....መልዕክቱ ቢደርሰው ብዬ ሁለት ሦስቴ እየዞርኩ እንደ ማያትም
እንደመገላመጥም አደርግሁት እሱ እቴ!
"ሊስን ሚ! አይ ቴል ዩ... ሊንስ ሚ ! ... ፈርስት ... ራስህ ሂድ...ሰከንድ ለሬጀስትራር ቶክ አደርጋቸውና ኖ ቤዛ ጋር አይደለም : : ቤዛ ጥርስ የሌለው ላየን' ማለት ናት ... ሊስን ሚ! ሊስን፣
ሚ እንጂ ! ”
እንደዚህ የተሳፋሪውን ጆሮ አስገድዶ ሲደፍር ቆይቶ ታክሲው ሊሞላ አንድ
ሰው እየቀረው መንገድ ጀመር : : ስልኩም ተዘጋ : :

እፎይ አልኩ ።

ትንሽ ዝቅ እንዳልን ታክሲው ቆመና የቀረችው ቦታ ላይ ከባለ ሞባይሉ
ሰውዬ አጠገብ አንድ ፈረንጅ ጫነ : :

እደ ገና መሄድ ጀመርን፡፡

ረዳቱ ሒሳብ እየተቀበለ ፈረንጁ ጋር ሲደርስ ፈረንጁ ፣ “ኢትዮጵያ ሆቴል” ሲል ተሰማኝ ።

ረዳቱ "አይሄድም ይለዋል ፈረንጁ ደጋግሞ "ኢትዬጵያ ሆቴል ይለዋል ”
ከብዙ ወዲህና ወዲያ በኋካ ፣ “ኢትዮጵያ ሆቴል ኖ ጎ” ብሎ ረዳቱ መለሰ።

ነገሩ በዚሁ ያበቃ መስሎኝ ነበር ግን ፈረንጁ ሆድ ብሶት ይምጣ ወይ ሌላ "ለምን አይሄድም" አይነት ጠንካራ ክርክር ሲጀምር ተሳፋሪ ሁሉ የራሱን አስተያየት መስጠት ጀመረ።

“አይ...ያታለልከው መስሎት እኮ ነው... መንገዴ አይደለም ብለህ
አስረዳው።

“ኢትዮጵያ ሆቴል በዚህ ጋር አይደለም ... እኔ ሜክሲኮ ነኝ በለው : "
“አታስብ ፣ የፍልውሃ ታክሲ እዚህ ጋር አስይዝዓhሁ አትለውም? ”
ቋቋ እንጂ ሐሳብ ላልቸጀረው ሰው ፣ የሐሳብ መዓት ያዋጣል : :
እኔ ግን ተንኮል ቅልቅል ሐሳብ መጣልኝ ፡ ታክሲው ሳይነሳ በእንግhዝኛው “ሲያስደንቀን፣” ወደነበረው ባለ ሞባይል ሰው ዞር አልኩና ፣
ወንድሜ ፣ አንድ በለን እንጂ ?” አልኩት :
በአንድ ጊዜ ሰው ሁኩ ወደ እሱ ዞረ: : ትንሽ ካቅማማ በኋካ ፣
"ዘ ታክሲ ኢትዮጵያ ሆቴል ኖ ጎ” ሲል ረዳቱ ተቀበለና ፣ “ ይህንንማ እኔም ብይዋhሁ ... ምን አይነቱ ነው!
ብሎ አሣቀን: :
ለካስ የአቶ ፣ “ሊስን ሚ ” እንግሊዝኛ ሀግርግር እንጂ ለችግር አይሆንም!
ለጉራ እንጂ ለስራ የማይሆን እንግሊዘኛ ይዘን ከተማው ውስጥ የምንሸልል ሰዎች ወዮልን!

🔘በሕይወት እምሻው🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ዘጠኝ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


የሰባት አመት ልጅ እያለሁ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን ለማቅረብ ወደ ከተማ አዳራሽ እሄድ ነበር፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ
አዋቂዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ። ረጂም ጣውላ ወንበር ላይ ተቀምጠው ውይይታቸው ሲያልቅ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን እንዳቀርብ እጠራለሁ። አባቴ ጸጥታ እንዲሰፍን እና
ተውኔቱ እንዲጀምር ደመቅ አርጎ ያነጥሳል። እጁን አጣምሮ ከደማቅ ፈገግታ ጋር ፊት ለፊት ይቀመጥ ነበር። ወንበር ላይ እወጣና ረጂም ዱላ እንደ ሰይፍ በመጠቀም እጀምራለሁ።
ከጅሊየስ ቄሳር “ጓደኞቼ፣ ሮማዊያን፣ የሃገሬ ልጆች እስኪ ጀሮችሁን ስጡኝ፡፡ ብየ እጀምራለሁ። አዋቂዎች የሚወዷቸው
ስለነበሩ ብዙ ጊዜ ማክቤዝ እና ጅሊየስ ቄሳርን ነበር ማቀርበው።የእንግሊዝኛ ቋንቋን የመናገር ችሎታየ የዳበረ እና ጥሩ የሆነ ስለሚመስለኝ በከፍተኛ ጉጉት እና ደስታ ነበር ማቀርበው::

ወታደሮቹ በእኩለ ለሊት ሲገሰግሱ ነቅቼ ነበር። የኮቴቸው ድምጸ በሙሉ መንደሩ አስተጋባ። ቀኑን ሙሉ ጆሮዎየ ላይ
ሲያቃጭልብኝ ዋለ። አስር ወታደሮች ሰፈሩን እንዲጠብቁ ከእኛ ጋር ቀሩ። በየምድብ ቦታቸው ቀኑን ሙሉ ሲጠብቁ ዋሉ። ምሽቱ ፥ሲቃረብ ወታደሮቹ ወደ ሰማይ በመተኮስ እና የመንደሩ ሰዎች
ወደ “ቤት እንዲገቡ” እንዲሸሸጉ በማዘዝ የስዓት እላፊ አወጁ።ያን ምሽት ሙሳ ተረት አላወራም ሞሪባም ከልጆች ጋር ገበጣ አልተጫወተም፡፡ በዝምታ ጀርባችንን ለግድግዳው ሰጠን
ተቀምጠን የተኩስ እሩምታ ሲዘንብ ከርቀት እናዳምጥ ነበር።ለሊቱ እስኪገባደድ የመጨረሻ ስዓት፤ ጨረቃ በጉም መሃል አልፋ ፊቷን በክፍቱ የቤታችን መስኮት እስከምታሳይ እና
በአውራ ዶሮ ጩኅት ለሊቱ እስከሚባረር ድረስ ተኩሱ ቀጠለ።

ፀጠዋት ከፀሐይዋ መውጣት ጋር መመለስ የቻሉ የተወሰኑ ወታደሮች ብቻ ወደ መንደር መጡ። የተወለወለ ኮሬ ጫማቸው በጭቃ ተበላሽቷል። ፈንጠር ፈንጠር ብለው መተማማኛ የመሰላቸውን መሳሪያቸውን አቅፈው ተቀምጠዋል። ብሎኬት ላይ ተቀምጦ የነበረ አንድ ወታደር እጁን በራሱ ላይ ጭኖ
ተርገፈገፈ። ተነስቶ መንደሩን ዙሮ ወደነበረበት ተመለሰ።በተደጋጋሚ እንደዚህ ሲያረግ ቆየ። መቶ አለቃ ጃባቲ ሬዲዮ ላይ መልዕክት ሲያስተላልፍ ከቆየ በኋላ ሬዲዮውን ወረውሮ ወደ ቤቱ ገባ። መንደርተኛው ምንም አላወራም:: ዝም
ብሎ የወረደውን መዓት ታዘበ።

እኩለ ቀን ሲሆን ከሃያ የሚበልጡ ወታደሮች ወደ መንደሯ መጡ። መቶ አለቃ ሲያቸው ማመን አልቻለም ተገረመ ተደሰተ ብዙም ሳይቆይ ቁጥብ ሆነ። ወታደሮቹ ራሳቸዉን እንደገና ካዘጋጁ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ወረዱ። ምንም መደበቅ አላስፈለገም ጦርነቱ ቅርብ ነው። ብዙም ሳይቆይ የተኩስ እሩምታ መስማት ጀመርን። መንደሩን የሚጠብቁት ወታደሮች ወደ ቤት እንድንገባ አዘዙን። ተኩሱ ከወፎችን እና ዶሮዎች ጩኅት ጋር እስከ ምሽት ድረስ ቀጠለ። ለሊት ጥይት ለማምጣት እና ለአጭር ረፍት ጊዜ ወታደሮች እየሮጡ ወደ መንደር መጡ። የቆሰሉ ወታደሮች በፋኑስ የታገዘ ቀላል ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም አብዛኞቹ ይሞታሉ። ወታደሮቹ የሞቱ ጓዶቻቸዉን ወደ መንደር
አያመጡም። ምርኮኛዎችን አሰልፈው ግንባራቸውን በጥይት በመምታት ይገድሉዋቸዋል።

ጦርነቱ ለቀናት ቀጠለ።ወታደሮች ቀስ በቀስ ቁጥራቸው እየቀነሰ ሄደ፡፡ ወታደሮቹ እረፍት አጡ ፤ ኮሽ ካለ የመንደሩ ሰዎች
ላይ ሳይቀር መተኮስ ጀመሩ:: መቶ አለቃዉ የመንደሩን ነዋሪዎች ወደ አደባባይ ወጥተው እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ሰጠ።
“ጫካው ውስጥ ህይወታችንን ሊያጠፉ ዕድላችንን ሊያበላሹ የሚጠብቁ ወታደሮች ተዋግተናቸዋል። በቁጥር ግን ይበልጡናል። መንደሩን በሙሉ ከበው አሉ። ይሄን መንደር እስከሚይዙ ድረስ ተስፋ አልቆርጥም:: የእኛን ምግብ እና መሳሪያ የራሳቸው ማድረግ ይፈልጋሉ።” ብሎ ንግግሩን ገታ አደረገና ቀስ ብሎ እንደገና ቀጠለ። አንዳንዶቻችሁ ከዚህ የምትገኙት ወላጆቻችሁን ቤተሰቦቻችሁን ስለገደሉባችሁ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ አስተማማኝ መጠጊያ መሸሸጊያ ነው ብላችሁ ነው:: እንግዲህ ከዚህ በኋላ
አስተማማኝ አይደለም:: ለዚህ ነው ጠንካራ ወንዶችን ታደጊዎችን የምንፈልገው:: እነዚህን እንድታግዙን የሰፈሩን ሰላም እና ደህንነት እንድንጠብቅ
እንፈልጋለን። መዋጋት ወይም ማገዝ ካልፈለጋችህ ምንም አይደል፡፡ ነገር ግን ቀለብ አይሰፈርላችሁም በመንደሩም መቆየት አትችሉም። መሄድ ትችላላችሁ ከዚህ የምንፈልጋቸው ምግብ
በማብሰል መሳሪያ በማዘጋጀት ጥይት በማቀበል የሚረድን የሚዋጉ ናቸዉ። ለምግብ ማብሰል በቂ ሴቶች አሉ። ስለዚህ ብቁ የሆኑ ታዳጊ ወንዶች እና ወጣቶች ነው እነዚህን አማጺዎች
እንዲዋጉ ምንፈልገው:: አሁን ነው የወላጆቻችሁን ደም የምትመልሱት፤ ሌሎች ልጆችንም ወላጆቻቸውን ከማጣት
ማስቀረት የምትችሉት::” ትንፋሽ ወሰደ። “ ነገ ጠዋት ሁላችሁም ከዚህ ቦታ እንድትሰለፉ ለተለያዩ ስራዎች ሰዎችን
እንመርጣለን።” አደባባዩን ለቆ ሲሄድ ጠባቂዎቹ ተከተሉት።

ለተወሰነ ጊዜ ደርቀን ባለንበት ቁመን ቀረን። ከዛ የስዓት እላፊው ሲቃረብ ወደየ ምኝታ ቦታችን ተበተን። ቤት ውስጥ
ጁማህ፣ አል ሃጂ ሞሪባ፣ ሙሳ እና እኔ ምን ማድረግ እንዳለብን ድምጻችንን ቀንሰን ተወያየን፡፡

“አማጺዎች ከዚህ መንደር የሆነ ማንም ሰው ጠላት ወይም ስላይ ነው ብለው ስለሚገምቱ ሁሉንም ይገድላሉ። ይሄን
ነው ያለው አምሳ አለቃው።” አለ አል ሃጂ የገጠመንን ኣጣብቂኝ ለማስረዳት ሲሞክር። ሌሎቹ ወንዶች ከተጋደሙበት ስጋጃ ተነስተው ውይይቱን ተቀላቀሉ። አል ሃጂ ቀጠለ “የሚሻለው ለጊዜውም ቢሆን ከዚህ መቆየት ነው።” ሌላ ምርጫ
አልነበረንም። መንደሩን ለቆ መሄድ ማለት መሞት ማለት ነው::

“አዳምጡ! ይህ ከመቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው፡፡ ሁላችሁም አሁንኑ ወደ አደባባይ በመውጣት ተሰብሰቡ።” ብሎ በድምጽ ማጉያ ለፈለፈ። ተናግሮ ሳይጨርስ አደባባዩ በሰዎች ሞላ፡፡
ሁሉም ሰው ለደህንነቱ ምን ማድረግ እንዳለበት የሚወስነውን ይህን ጊዜ በጉጉት ይጠብቅ ነበር። ከአዋጁ በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኩሽና ቤቱ ውስጥ ተቀምጬ ነበር። ፊታቸው ባዶ ምንም ስሜት የማይታይበት አይናቸው ግን በሃዘን ገርጥቶ ነበር። አይን ለ አይን ላያቸው ብሞክርም ፊታቸውን አዞሩ። ቁርሴን ለመብላት ብሞክርም ፍርሃት የመብላት ፍላጎቴን ነጥቆኛል።

በሰልፍ መሃል ቦታ ስናገኝ የተኩስ እሩምታ አየሩን ተቆጣጠረው:: ከዚያ ከተኩሱ የሚከብድ ጸጥታ ሆነ።

መቶ አለቃ ለሁሉም ለመታየት ከተደረደረ ጡብ ላይ ወጣ።አጥንት ከሚሰብር ዝምታ በኋላ ወደ ወታደሮቹ እጁን
አመለከተ:: ወታደሮቹ የአንድ ወጣት እና ሌላ ታዳጊ አስክሬን ከፊታችን አስቀመጡ፡፡ የመንደሩ ነዋሪዎች ነበሩ። ልብሳቸው በደም ተጠምቋል አይናቸው እንደተከፈተ ነው፡፡ ሰዎች ፊታቸውን ለማዞር ሲሞክሩ ትንንሽ ልጆች ማልቀስ ጀመሩ።መቶ አለቃው ጉሮሮውን አጥርቶ መናገር ጀመረ፡፡እነዚህን አሰቃቂ አስክሬን በተለይ ልጆች ባሉበት
👍1
ስላሳየኋችሁ ይቅርታ። ነገር ግን ከዚህ ያለነው ሁላችንም ሞትን አይተናል ወይም አፋፍ ላይ ደርሰንም እናውቃለን።” ወደ
አስክሬኖቹ እያመለከተ ይህ ሰው እና ልጁ አደገኛ እንደሆነ ብነግራቸውም በጠዋት ተነስተው ለመሄድ ወስነው ነበር።ሰውየው በዚህ ጦርነት መካፈል እንዳማይፈልግ ነግሮኝ ነበር።
ስለዚህ የፍላጎቱን ያደርግ ዘንድ ተውኩት፤ ለቀቁት። ምን እንደሆነ አሁን ተመልከቱ። አማጺዎች በምንጥሩ ቦታ ሲደርሱ
ተኩሰው ገደሉዋቸው። አሁን የማስያችሁ ያለንበት ሁኔታ እንዲገባችሁ ነው። መቶ አለቃው ለአንድ ስዓት የሚሆን ንግግር
አደረገ። አማጺዎች የፈጸሙዋቸውን ግፉዎች ዘረዘረ። አንገት መቅላት፣ እጅ መቁረጥ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ሙሉ መንደር ነዋሪዎች እያሉ ማቃጠል እያለ ሰዎችን እንዴት እየጎድ እንደሆነ
ለተሰብሳቢዎች ገለጸ።

“ስውነታቸውን አጥተዋል። መኖር የለባቸውም:: ለዚህ ነው አንድ በ አንድ ሁሉንም መግደል ያለብን። ክፉ ነገርን
እንዳጠፋችሁ ቁጠሩት። ለሃገራችሁ ትልቅ ውለታ ዋሉ።” መቶ አለቃው ሽጉጡን አውጥቶ ወደ ሰማይ ሁለት ጊዜ ተኮስ። ሰዎች መጮህ ጀመሩ ሁሉንም ልንገድላቸው ይገባል። በምድር ላይ
ከዚህ በኋላ እንዳይራመዱ ልናደርጋቸው ይገባል።” ሁላችንም አማጺዎችን አምርረን ጠላን ከመቼውም ጊዜ በላይ
መንደራችንን ላለማስደፈር ቆርጠን ተነሳን፡፡ የሁሉም ስው ፊት ላይ ቁጣ ይነበባል፡፡ ከንግግሩ በኋላ የሰፈሩ ስሜት በፍጥነት ተቀይሯል፡፡ እኔ እና ጓደኞቼ ደግሞ ተቆጥተናል ፈርተናልም።
ሁሉም ሴቶች ወደ ምግብ ማብሰል ሲሄዱ ወንዶች ደግሞ ወደ ጦር መጋዝን አመሩ።ወደ ህንጻው ስንቀርብ G3 የታጠቀ ወታደር ከህንጻው ወጥቶ
በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#መልክአ_ሰዋሰው

መንገድ የሚያበጁ
አቅጣጫ 'ሚያስቱ
ብኩን አመልካቾች ፣
ጎዳና አሳምረው
መኼጃን ያጠፉ
እልፍ ባለጸጎች ፣
ሰዉን ቤት ከልክለው ፤
በድንኳን ያኖሩ ከጎጆ ነጥለው
እንደ ጲላጦስም
እውነትን የሸሹ ፣ እጃቸውን ታጥበው
ፍርድን የሚያዛቡ ፣ ዙፋን ተከልለው።
“ከደሙ ንጹሕ ነኝ. . .
እያሉ በድፍረት ፣ በደም የረጠቡ ፣
ስንቶች ስንት ናቸው . . . ?
ለሞት ጥቀር ወተት! ሕይወት የሚያጠቡ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የዘልማድ_እውነት

ዶፍ ዝናብ ከጣለ . . .
በጠራራ ፀሓይ በቀን እኩሌታ፣
ካ'ገጣጠማቸው . . .
ቍርና ሐሩሩን በልዩነት ዋልታ፣

(ጠርጥር! ትርጉም አለው)
የተፈጥሮ ኹነት ከተዘባረቀ . . .
ትውልድ የሚበላ ሕዝብን አስጨንቆ
ጅብ ልጅ ተወልዶ ነው ! በዘልማድ ረቆ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስር

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

...በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።

አንድ ፊሽካ ባንገቱ ላይ ያንጠለጠለ ነገር ግን መለዮ ያልለበስ ወታደር AK-47 ካለበት ሳጥን በማውጣት አንድ አንድ ለሁላችን አደለን። ወደ እኔ ሲደርስ ቀና ብየ ላየው ስላልቻልኩ ራሴን ቀና
አድርጎ ነበር የሰጠኝ። እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር።

“ሁላችሁም በሁለት ነገሮች ትመሳሰላላችሁ” አለ ወታደሩ።
“ስው ቀና ብላችሁ አይን ለአይን ማየት አትችሉም እና መሳሪያ መያዝ ያስፈራችኋል። ራሳችሁ ላይ የተደቀነ ይመስል ትንቀጠቀጣላችሁ። ይሄ መሳሪያ ከእንግዲህ የናንተ ነው።እንዴት መያዝ እንዳለባችሁ ከአሁኑ ተማሩ። ለዛሬ ይበቃል”አለ ወታደሩ።

ያ ለሊት በድንኳኔ መግቢያ ላይ ለተወሰነ ደቂቃ ቆምኩ።ጓደኞቼ መጠው ያወሩኛል ብየ ስጠብቅ ነበር። ማንም ከድንኳኑ
አልወጣም:: እጄን ራሴ ላይ ጭኜ ተቀመጥኩ። የራስ ምታቴ ያን ምሽት ጠፋ።

ከእኔ ጋር ድንኳን የሚጋሩት ሼኩ እና ጆሲያህ ደወል እስከ ሚደወል ንጋት 12 ስዓት ድረስ ተኝተው ነበር።ለስልጠና
መነሳት ነበረብን። ኑ እንሂድ” ብየ ቀስ አድርጌ ልቀሰቅሳቸው ሞከርኩ። ወደ ሌላ ጎናቸው እየተንከባለሉ ከእንቅልፋቸው ሊነሱ አልቻሉም፡፡ ከዛ ሰሌኑን አንስቼ መትቼ አስነሳሁዋቸው።

አዲስ የወታደር ጫማ፣ ሱሪ እና ዝንጉርጉር ቲሸርት ተስጥቶን ልምምዳችን ጀመርን። ሱሪ ስቀይር ወታደሩ ወደ እኔ
መጥቶ አሮጌውን ሱሪ ወደ እሳት ጨመረው። አሮጌው ሱሪ የራፕ ካሴቴን ይዞ ስለነበር ወደ እሳቱ ሩጬ ላተርፈው ሞከርኩ።ካሴቱ ግን መቃጠል ጀምሯል። አይኔ እንባ አቀረረ።

ወደ ጎን ረድፍ ሰርተን እግራችን ከፍተን እጃችንን አጣምረን መጠበቅ ጀመርን። አንዳንድ ወታደሮች ከጦር ሜዳ ተመልሰው የጦር መሳሪያቸውን አስተካከሉ ጥይቶችን በጎናቸው ባለ
ከረጢት ያዙ። አንዳንዶቹ ልብሳቸው እና ፊታቸው ደም ይታይበታል። ቁርሳቸውን በፍጥነት በልተው ተመለሱ::

ሼኩ እና ጆሲያህ ከእኔ ጎን ነበሩ። አንድ ድንኳን መጋራታችን እንደ ትልቅ ወንድም እንዲሰማኝ አድርጓል። በልምምድ መሃል
እኔን ያያሉ፤ ከአሰልጣኝ በላይ እኔ የማደርገውን ያደርጉ ነበር፡፡አሰልጣኙ ራሱን አስር አለቃ ጋዳፊ ብሎ ነበር ያስተዋወቀን ከመቶ አለቃ ጃባቲ እና ከሃምሳ አለቃው ጋር ሲነጻጸር በእድሜ
ያንሳል፤ ራሰ በራ መሆኑ እና ኮስታራ ፊቱ ግን ትልቅ ሰው ያስመስለዋል ::

መጀመሪያ በህንጻው ዙሪያ ለተወሰነ ደቂቃ ሮጥን። ቀጥሎ በዱር ውስጥ አድብቶ መግባት ተማርን። ዛፎ ላይ መውጣት መውረድ፣ ድምጸ ሳናሰማ መንቀሳቀስ እና ተመልሶ ወደ ነበሩበት
ሩጦ መመለስ በተደጋጋሚ ሰራን። አስር አለቃ ጋዳፊ ብዙ አይናገርም:: “መጥፎ አይደለም”፣ “መጥፎ” እና “ፍጥነት” ብቻ
ይል ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ በምልክት ይጠቀማል። ወደ ጫካው ከገባን
በእጃችን እንቅስቃሴ መግባባት እንዳለብን ነገረን። “ቃላት ተናገራችህ ማለት ግንባራችሁን ለጥይት አሳልፋችሁ ሰጣችሁ ማለት ነው” ይላል፡፡ በስልጠና መሃከል ቁርስ እንድንበላ አንድ ደቂቃ ብቻ ይሰጠናል። በመጀመሪያ ቀን ብዙ ሳንበላ ነበር ምግቡ የተነሳው። ከሳምንት በኋላፀ በፍጥነት መብላት ለመድን።
ከስዓት AK-47 ያደለንን አስር አለቃ ፊት ለፊት ገጥመን ተሰለፍን። የእኔ ተራ ሲደርስ አፍጥጦ አየኝ እና ከእንጨት ሳጥን ውስጥ መሳሪያ አውጥቶ ደረቴ ላይ አስታቀፈኝ፡፡ መሳሪያየን
ይዥ ወደ ሰልፉ ተመለስኩ፡፡ እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር፡፡ በእጆቼ
ይዤው እንኳ ላየው ፈራሁ። እኔ ማውቀው በቅርቅሃ ሚስራ የአሻንጉሊት ሽጉጥ ነበር። እኔ እና ጓደኞቼ ከቅርቅሃ ሰርተን በቡና ማሳ ወይም በግንባታ ላይ ባሉ ቤቶች መሃል እንጫወት ነበር። አሁን የዕቃ ዕቃ ጨዋታ አይደለም የእውነት AK-47 ይዘናል። ለጊዜው ያለ ጥይት መሳሪያውን ይዘን መሮጥ መንከባለል ተማርን። ቀጥሎ ወደ ሙዝ ማሳ በመውረድ ሙዙን በሰንጢ መውጋት ጀመርን፡፡ “ሙዙን እንደ ጠላት ተመልከቱት።ወላጃችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን እንደገደሉት አማጺዎች” አስር አለቃ ጮኸ። “ቤተሰቦቻችሁን የገደለን ሰው እንደዚህ ነው ምትወጉት?” እንደዚህ ነው ብሎ እየጮኸ መውጋት ጀመረ።

መጀመሪያ ሆዱን፣ ከዛ አንገቱ ላይ፣ ልቡን” እያለ ቀጠለ። እኛም በንዴት ስሜት ሙዙን መውጋት ቀጠልን:: ምሽት ላይ አልሞ መተኮስ ሰለጠን። ሼኩ እና ጆሲያህ መሳሪያቸውን ለማንሳት
አቅም አልነበራቸውም:: አስር አለቃ ከፍ ያለ ኩርሲ ነገር ሰጣቸው እና ልምምዳቸውን ቀጠሉ። በመጨረሻ መሳሪያ ፈቶ መጠገን እንደይዝጉ ዘይት መቀባት ተማርን፡፡ ያ ምሽት ሁላችንም ደክሞን ስለነበር በቀጥታ ወደ ምኝታችን አመራን።

ሼኩ እና ጆሊያህ ቀን የሰሙትን “አንድ ሁለት” “ፓው ፓው ቡም” ድምጾች በእንቅልፍ ልባቸው ይሉ ነበር።

እሁድ ጠዋት ነበር አስር አለቃ ያን ቀን ስልጠና እንደሌለ እና እንድናርፍ ሲነገረን፡፡ “ሃይማኖተኛ ከሆናችሁ ማለት
ክርስቲያን ከሆናችሁ ዛሬ አምላካችሁን የማምለኪያ ቀን ይሁናችሁ ፤ ምን አልባት ሌላ ጊዜ ላይኖራችሁ ይችላል። ሂዱ”

የወታደር ልብሳችንን እንደለበስን ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣን። ኳስ መጫወት ስንጀምር መቶ አለቃ ከቤቱ ደጃፍ ወጥቶ
ሊቀመጠ ነበር። ጨዋታውን አቁመን ለመቶ አለቃ ሰላምታ ሰጠን። “ጨዋታችሁን ቀጥሉ። አሁን የምፈልገው ወታደሮቹ ኳስ ሲጫወቱ ማየት ነው።” ብሎ ባርጩሜ ላይ ተቀመጦ
ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ን ማንበቡን ቀጠለ ::

ኳስ ጨዋታው ሲበቃን፤ ለመዋኘት ወሰን እና ወደ ወንዝ ወረድን። ፀሐይማ ቀን ነበር፡፡ ወደ ወንዝ ስንወርድ ሰዉነታችን
ላይ የነበረው ላብ እየደረቀ ነበር። ለተወሰኑ ደቂቃዎች ከተንቦጫረቅን በኋላ በሁለት ቡደን ተከፍለን መወዳደር
ጀመርን።

እንሂድ ጓዶች: በዓሉ አብቅቷል።” ብሎ አስር አለቃ ከወንዙ ዳር ሁኖ ጮኸ። ጨዋታውን አቁመን አሱን ተከትለን
ወደ መንደራችን ሄድን።

መንደር እንደደረስን መሳሪያችንን እንድጠግን ትዕዛዝ ተሰጠን። መሳሪያችንን እያጸዳን የወገብ እና የጀርብ ቦርሳ ተሰጠን። ጥይቶችንን የፈለግነውን ያህል እንድንወስድ ተነገረን።
መሸከም ከምንችለው በላይ ከሆነ በፍጥነት መሮጥ እንደማንችል
ነገረን። ከአል ሃጂ እና ከእኔ በስተቀር ሌሎች ደስተኛ ነበሩ።ፀተጨማሪ ልምምድ የሚሄድ ነበር የመሰላቸው። አል ሃጂ መሳርያውን አጥብቆ ያዘ።

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#አኮረፈች_መሰል...?

አኮረፈች መሰል . . . ?
ተፈጥሮ ንክ ኾነች
ቀኙን ግራ አረገች።

አኮረፈች መሰል . . .?
ሰማይ ደም መሰለ፤
ነጸብራቅ ተሞልቶ በጥቀረት ተሣለ።
ፍም መሳይ ደመና፣ እንባውን እረጨ
ዑደቱን ሳይጨርስ፣ ዘመንም ተቋጨ።
ጀንበር ተሸሸገች፤ ቀትር ተጠልላ
ከዋክብት አንድ ኾኑ፣ ፀሓይ ተጠቅልላ።
ፀሓይ እኩለሌት፣
ጨረቃም ታስያት፣
ኾኑ ተቀያይረ፤
ምድር ቀን ብታግድ፣ ጸዳልን ረስተው።

አኮረፈች መሰል . . . ?
የምድር ዘልማድ፣
ታሪክ ተረተረት ፣ በ'ውን ተሳከረ
እሳተ ጎመራ በረዶ ጋገረ።

( ሐሩር ቆፈን ኾነ! )
ዛፎች ፣ ዕለት ኾኑ . .
ዕለት ፣ ዛፍ አፈራ
ደርቆ ታየ ፤ ወይራ።
ቅጠልም ያለ ግንድ፣ ያለውም ከሰመ
ግንድም ሥር ሳይኖረው፣ ደርቆ ለመለመ።

አኮረፈች መሰል . . . ?
ባሕሮች ፣
ባ'ርምሞ ተዋጡ
ቅን ፋታን መረጡ።
ከጽሞና ዕብረዉ ፣ ጎርፎችም ዝም አሉ!
ጅረት ሽቅብ ወጣ . . .
ውቅያኖስ ጠብታ ፣ ወንዞች ጤዛ አከሉ።

አኮረፈች መሰል . . .?
አዎ . . . !
አኩርፋ ነው እንጂ፣
የሚኾነው ቀርቶ የማይኾን የኾነው
'ያቺ 'ምወዳት ሴት . . .
ምን ነገር ፈልጋ ፣ ምን ነገር አጥታ ነው ?!

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የመልስ_ጥያቄ

በዚች ምድር ዓለም.....
የመምጣትን ትርጉም
ዘልቆ ያለማወቅ፤
ወይም እንደጅረት ......
በውድም በግድም
ፈስሶ ያለማለቅ።
ወይ እንደ አውሎ ንፋስ.....
የሚንሳፈን ኃይል
በዱር ፣ በገደሉ
ምንድን ነው ያልገባኝ....
ወዳንቺ ሚመራኝ
የተፈጥሮ ውሉ።
#የእሳት_እራት

በፍቅርሽ ነበልባል ነፍሴ ተቃጠለ
እቶኑ ውበትሽ ገጹን አከሰለ።
ቀልቤ ብትንትኑ ትርምስምሱ ወጣ
የልጅነት ወዜ በመውደድ ገረው።
ከዕልቆ ሥፍር ራቀ ፤ ባ'ንቺው ተመሽገ
ጕያሽ ሥር ተቀብሮ ፣ ካ'ለም ተሸሽገ።

አቤት ይኼ ልቤ . . .
ስትኼጂ ሲሟሽሽ ፣ ጠውልጎ ሲወድቅ
ስትመጪ ሲፈካ ፣ አብቦ ሲጸድቅ።
መከነ ንዳዱ ጠረንሽ አራሰው፤
ለምልሞ ጸደቀ ፤ ዙሪያሽን ሲያስሰው።

እናም ይኼ ልቤ . . .
ወጋገን ኾነችው ጸዳል እንዳለመ፣
ብርሃን ገላሽ ላይ ሲያርፍልሽ ከሰመ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_አንድ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

“ተነሱ ወታደሮች” አለ አስር አለቃ፡፡ የደንብ ልብሱን ለብሶ ሙሉ ትጥቁን ታጥቆ ነበር የመጣው። በተጠንቀቅ ተሰልፈን ነበር። አረንጓዴ ከረባት ሰጠን እና “ይሄን ከረባት ያላደረገ ወይም እንደ እኔ አይነት ባርኔጣ ያላደረገ ካያችሀ ተኩሳችሁ ምቱት” አለ በጩኸት። አሁን ለስልጠና እንደማንሄድ ለሁሉም
ግልጸ ነው። “አሁን ዘና በሉ፤ ከተወሰኑ ከደቂቃዎች በኋላ ጉዞ እንጀምራለን።”

አስር አለቃ ትቶን ሄደ፡፡ መሬት ላይ ተቀመጥን፤ ሁላችንም በየግል ሃሳባችን ተውጠን ነበር፡፡ሼኩ እና ጆሲያህ ከጎኔ
ተቀምጠዋል ፤ አይናቸው ውሃማ ነበር የተከፉ ይመስላሉ።ማድረግ የምችለው ራሳቸውን እያሻሽሁ አይዙዋችሁ ማለት ብቻ ነበር። ተነስቼ ወደ አል ሃጂ እና ሌሎች ጓደኞቼ ሄድኩ። ምንም
ቢፈጠር አንድ ላይ ለመሆን ተስማማን።

ወጣት ወታደር የፕላስቲክ ቦርሳ ይዞ ወደ እኛ መጣና ክኒን የሚመስል ነጭ ነገር ስጠን፡፡ “አስር አለቃ ተጨማሪ ሃይል
ይሰጣችኋል ፦ያበረታችኋል” ብሏል አለ። ክኒኖቹን ከወሰድን በኋላ መንቀሳቀስ ጀመርን። መሳሪያችንን ይዘን አዋቂ
ወታደሮችን ተከትለን መራመድ ጀመርን። ምሽት ላይ እንመለሳለን ተብሎ ስለታሰበ ምግብ እና መጠጥ አልያዝንም፡፡
ጫካው ውስጥ ብዙ ኩሬዎች አሉ።” አለ መቶ አለቃ:: ብዙ ምግብ እና ውሃ ይዞ ከመምጣት ጥይት እና መሳሪያ መሸከም
ይሻላል ለማለት ይመስላል :: “በብዙ ጥይቶች ውሃ እና ምግብ ማግኘት እንችላለን። ምግብ እና ውሃ ብንዝ ግን እስከ ማታ እንኳ አያቆየንም::” አለ አስር አለቃ መቶ አለቃ ጃባቲ የጀመረውን
ሃሳብ ሲያስረዳ፡፡

ሴቶች እና ትልልቅ ሰዎች ቤታቸው ደጃፍ ሁነው ስንሄድ ይመለከቱ ነበር። አንድ ህጻን የት እንደምንሄድ ምን እንደሚገጥመን ያወቀ ይመስል ስቅ ስቅ ብሎ አለቀሰ።ፀሐይዋ አንፀባራቂ ከመሆኗ የተነሳ ጥላችን መሬት ላይ ይታይ ነበር።

በህይወቴ እንደዛን ቀን መንቀሳቀስ ወደ ማንኛውም ቦታ ለመሄድ ፈርቼ አላውቅም። አይኖቼ እንባ ሲያቀርሩ ለመዋጥ እታገል ነበር። መሳሪያየም አጥብቄ ያዝኩ።

ወደ ጫካው አንድ ክፍል ስንገባ መሳሪያችንን እንደብቸኛ የጥንካሬ ምንጭ ይዘን ነበር። በጥንቃቄ በቀስታ ነበር የምንተነፍሰው። መቶ አለቃ በሚመራው ረድፍ ነበርኩ። እጁን
ወደ ሰማይ ሲያነሳ ጉዟችንን ገተን ቆምን። ቀስ አድርጎ እጁን ሲያወርድ በአንድ እግራችን ሸብረክ ብለን ከተቀመጥን በኋላ አካባቢን ቃኘን። ወዲያው ተነስተን ረግረጋ ጥግ እስክንደርስ ድረስ በፍጥነት መንቀሳቀስ ጀመርን። ረግረጉ ላይ መሳሪያችንን አስተካክለን ጠላት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ለመሰንዘር ተዘጋጀን።
በዝምታ እንደ አዳኝ አድፍጠን ጣታችንን ቃታ ላይ አሳርፈን ጠበቅን፡፡ ፀጥታው ግን አስጨነቀኝ።

አማጺዎች በረግረጉ በኩል ሲያልፉ በአካባቢው የነበሩ ትናንሽ ዛፎች ተንቀሳቀሱ። ገና አይታዩም መቶ አለቃ ግን “ሳዛችሁ ተኩሱ” አለ። ከደቂቃዎች በኋላ የተወሰነ ቡድን ሲመጣ
አየን። እጃቸውን አንስተው ተጨማሪ ታጣቂዎችን ጠሩ።አንዳንዶቹ እንደ እኛ ታዳጊዎች ነበሩ። መቶ አለቃ RPG
እንዲተኮስ አዘዘ፡፡ የአማጺዎች አዛዥ ግን ለመተኮስ ስንዘጋጅ ድምፅ ስምቶ ስለነበር ወታደሮቹን “በማፈግፈግ!” “ሸሹ”
“አምልጡ” አለ። ስለዚህ ፈንጁ የተወሰኑትን ብቻ ነበር ያገኘው።
ከፍንዳታው በኋላ በሁለቱም በኩል የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ።

መሳሪያየን ፊት ለ ፊት ደቅኜ ደርቄ ቀረሁ፡፡ መተኮስ አልቻልኩም። ጠቋሚ ጣቴ ደነዘዘ፡፡ ጫካው ይዞርብኝ ጀመር።
የምወድቅ ስለመሰለኝ ከጎኔ የነበረውን የዛፍ ግንድ በአንድ እጄ ያዝኩ። ማስብ አልቻልኩም ግን ከሩቅ ተኩስ ይሰማኛል ፤ ሰዎች በስቃይ እየጮሁ ይሰማኛል። ቅዥት በሚመስል ስሜት ውስጥ
እያለሁ የደም ርጭት ፊቴን መታኝ፡፡ ደሙን ከፊቴ ላይ እያበስኩ አንድ ወታደር ወደ እኔ ሲመጣ አየሁ::

ፀሐዮዋ የመሳሪያ ጫፍ እና ወደ እኛ የሚመጡ ጥይቶችን ታሳይ ነበር። ጆሲያህን መፈለግ ጀመርኩ፡፡ ጆሲያህን ግን መድፉ አግንቶት ነበር፡፡ ዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ ሰውነቱ በደም ተጨማልቆ አገኘሁት። እጆቹን ትክሻየ ላይ እንዳደረገ
መንቀሳቀስ አቆመ። አይኖቹን ዘግቼ መሬት ላይ አሳረፍኩት።ከጎኔ የሆነ ሰው እንደቆመ ይሰማኝ ነበር። አስር አለቃ ነበር።
“ዝቅ በል” “ተኩስ” አለኝ። ፊት ለ ፊት ሙሳን አየሁት ጭንቅላቱ በደም ተሸፍኗል እጆቹ ግን ዘና ያሉ ይመስላሉ።ወደ ረግረጉ ስዞር አማጺዎች እየሮጡ ነበር። ድንገት መሳሪያየን አንስቼ ተኮስኩ።
አንድ ሰው ገደልኩ፡፡ ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ ያየሁት እልቂት በጨረፍታ በአዕምሮየ ይመላለስ ጀመር። የሁለት ጓደኞቼ ሞት ውስጤን እየረበሸኝ ነበር የምተኩሰው። ብዙ ሰው ገደልኩ።
እንድናፈገፍግ ትዕዛዝ እስከሚሰጠን ድረስ መተኮሴን አላቆም ኩም ነበር።
የተሰው ጓደኞቻችንን መሳሪያ እና ጥይት ከወሰድን በኋላ ከዛው ጫካ ትተናቸው መጓዝ ጀመርን፡፡በዱር መሃል ቀስ ብለን
አድብተን ለተወሰነ ሜትሮች ከተጓዝን በኋላ ለሌላ የደፈጣ ውጊያ ተዘጋጀን። አሁንም አድፍጠን ጠበቅን፡፡ ጊዜው በምሽት እና ለሊት መሃል ነበር። አንድ ድንቢጥ ወፍ መዘመር ብትጀምርም
ሌሎች ሊከተሉዋት አልቻሉም:: እሱዋም አቆመች፤ ለሊቱ በፀጥታ ተዋጠ፡፡ ከአስር አለቃ ጎን ነበርኩ፡፡ አይኖቹ ከተለመደው
በላይ ቀልተዋል። የሚመጡ ሰዎችን ኮቴ ስንሰማ በተጠንቀቅ መጠበቅ ጀመርን። የተወሰኑ ታጣቂዎች ከቁጥቋጦ በመውጣት በዛፎች መሃል ራሳቸውን ከለሉ። ወደ እኛ ሲቀርቡ መተኮስ
ጀመርን። ፊት ለ ፊት የነበሩት ተኩሰን ከጣልነው በኋላ ሌሎቹን በረግረጉ በኩል ከተከተልናቸው በኋላ ጠፉን። ብዙ
አማጺዎችን ገደልን። ደማቸው የረግረጉን ውሃ ወደ ደም ለወጠው። አስክሬናቸውን
መሳሪያዎችን ወሰድን፡፡

አስክሬናቸውን አልፈራሁም ነገር ግን ተፀየፍኳቸው።በእግሬ አገላብጬ G3 መሳሪያ፣ ጥይቶች እና ሽጉጥ አገኘሁ::
ሽጉጡን አስር አለቃ ለራሱ አደረገ።ሟቾቹ አንገታቸው እና እጃቸው ላይ ጌጣ ጌጦች አድርገው ነበር። አንዳንዶቹ ከአምስት
በላይ የወርቅ ስዓቶችን እጃቸው ላይ አስረው ነበር። አንድ ፀጉሩ ያልተበጠረ ታዳጊ ደግሞ 'All eyes on me “ሁሉም አይኖች ወደ እኔ( ይመለከታሉ)” የሚል Tupac Shakur ቱፓክ ሻኩር ቲሸርት ለብሶ ነበር፡፡ የተወሰኑ አዋቂ ወታደሮች እና ጓደኞቼን ሙሳ እና ጆስያህን አጥተናል። ተረት አዋቂው ሙሳ አልፏል።
አጫዋቻችንን፥ ቀልድ አዋቂ እና ተረት ነጋሪው አሁን በምንፈልገው ጊዜ የለም! ተነጥቀናል። ጆስያህቱ ያኔ ከእንቅልፉ ባልቀስቅሰው እና የመጀመሪያው ስልጠና ቢያልፈው ዛሬ ባልዘመተ ነበር።

አመሻሽ ላይ መንደራችን ደርሰን የጦር መጋዝኑን ግድግዳ ተደግፈን ተቀመጥን፡ መንደሩ ጸጥታ ወርሶት ነበር። ጸጥታው
ያስፈራን ይመስል መሳሪያዎቻችንን ማፅዳት ዘይት መቀባት እና መገጣጥም ጀመርን። አዳዲስ መሳሪያዎችንን ወደ ሰማይ በመተኮስ ስንሞክርም ነበር። መክሰስ መብላት ብፈልግም አልቻልኩም ውሃ ጠጣሁ ግን ምንም አልተሰማኝም። ወደ ድንኳኔ ስገባ ከስሚንቶ ግድግዳ ጋር ተጋጪቼ ጉልበቴ ደማ።
አሁንም ምንም አልተሰማኝም ደንዝዥ ነበር፡፡ መሳሪያየን ድንኳኔ መውጫ ላይ አድርጌ በጀርባየ ተንጋልየ ተኛሁ።
አዕምሮየ ባዶ ሆነ፤ ምንም አይነት ሃሳብ ስሜት አልነበረኝም፡፡
በተዓምር እስክተኛ ድረስ የድንኳኑን ጣራ አንጋጥጬ ለደቂቃዎች አየሁ። በህልሜ ጆስያህን ከዛፍ ጉቶ ላይ ላነሳው ስሞክር አንድ ሰው ከበላየ ላይ ወጣብኝ። ግንባሬ ላይ መሳሪያ ሽጉጥ ደቀነ። ወዲያው
👍2
ከእንቅልፌ ባንኜ ነቃሁ እና ድንኳኔ
ውስጥ እንዳለሁ መተኮስ ጀመርኩ ጥይቶቼን እስከምጨርስ ለስላሳ ዙር ተኮስኩ። መቶ አለቃ እና አስር አለቃ መጥተው ወደ ውጭ ወሰዱኝ። አልቦኝ ነበር፤ ፊቴ ላይ ውሃ ከደፉብኝ በኋላ
ክኒን ስጡኝ። ሙሉ ለሊቱን ቁሜ አደርኩ። ለሳምንት ያህል መተኛት አልቻልኩም። ለተጨማሪ ሁለት ቀናት ለውጊያ
ወጥተን ነበር፤ መሳሪያየን ለመተኮስ አልተቸገርኩም::

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
😱1
#ዐዲስ_ገጽ

ያላለምኩት
ያልጠየኩት ኾነ !
ልቤ ጥበብ ገባው . . ፤
ምስጢርን ዐወቀ
ዐውቆ ተራቀቀ
ተራቆም ራቀ።

ሐሳቡን አፍታታ ፤ ሐሳቡን አናኘው
ጥያቄው ምሶ ፣ ምላሹን አገኘው።
በሐሳብ ተሞልቶ
በሐሳብ ተመርቶ
መጠየቅ ጀመረ ፤
ያልተፈቀደውን
የተደበቀውን
እየመረመረ።
እየመረመረ፤

በከፍታ ጕዞ . . .
ሽቅብ ተምዘግዝጎ ከኅዋው ላይ ዋለ
ከእርሱ ተገናኘ ከዚያም ይኼን አለ።
ጠቢቡ ሠለሞን . . .
“ከፀሓይዋ በታች ዐዲስ ነገር የለም ! "
ብሎ በመናገር .
የተሰጠው ኹሉ በከንቱ ከኾነ ፣
ከታችኛው ሳይኾን . . .
ከከፍታው ላይ ነው ፤ ሕልሙ የመከነ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍1
#ውሉድ_ወወላድ

የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ!ምግባሩን ካለየ።

ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መኾን ክብር በከንቱ አይሰጥም!
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም!

እፍኝትን እይዋት .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣በፍትወት መቃጠል።
አንበሳም ደቦሉን .
በጊዜው ካልቀጣ ንግሥናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል።

አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ፣
ካልተነጻጸረ፣
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የመኖር_ልኬ

ሰይጣን ከፈጣሪ እንዴት ይፏከራል?
እግዜርስ ከሰው ጋር እንዴት ይማከራል?

ድንቢጥ ሐሳብ ይዞ ከሰማይ ጋር መዋጋት
ደመና ላይ ምሎ ነፋስን መዘንጋት።

መርከብ ሳያበጁ መልሕቅ መወርወር
ከውቅያኖስ ጠልቆ ከውሃ መሰወር።

ጭላንጭሏ ኩራዝ ፀሓይን ረስታ
ጣራ አልባ ጎጆዋ ዝናብ ተመኝታ
ከማይችሉት መግጠም ከማይደርሱት ቦታ።

ውስጤ እንደዚህ ነው! የሚያግደረድረው
ሐሳቤ እንደዚህ ነው! የሚወዳደረው።
ስሜቴ ከልቤ እየተደበቀ
ነፍሴ ከምኞቴ እየተሳበቀ ፣

(ልቤ ትቢያ ቀረ . . .!)

ሚዛኑን ረስቶ እየተመዘነ
መመዘኛ ስቶ እየተተመነ ፣
ከማያሸንፈው እየተጋጠመ
የሽንፈቱን ጕዞ እየደጋገመ ፣
እየደጋገመ እየደጋገመ . . .
እያልጎመጎመ . . .!
ይኸው አለኹ አለ. .!

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሁለት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


ቀኖቼን በወታደራዊ ስራዎች ተጠምጄ ባሳለፍኩ ቁጥር የራስ ምታቴ እየተሻለኝ መጣ፡፡ ቀን ቀን ኳስ መጫወት ትቼ ጥበቃ
ላይ እሰማራለሁ። ነጩን ክኒን በብዛት አዘውትሬ እወስድ ነበር።
ክኒኖቹ ሱስ ሁነውብኛል። ብዙ ኃይል ይሰጡኛል። መጀመሪያ አብዝቼ የወሰድኩ ቀን በጣም አልቦኝ ሁሉንም ልብሶቼን አውልቄ ነበር። ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል፤ ዕይታየ ደበዘዘ ብዥታ
ለደቂቃዎች ያህል መስማትም አልቻልኩም። ያለ ምንም ስራ
መንደሩን እዞረዋለሁ፤ እረፍት የለኝም ብዙ ኃይል ይሰማኛል ነገር ግን ደንዝዣለሁ ስሜት አይሰማኝም፡፡ ክኒኑን አብዝቼ
መውሰዴን ቀጠልኩ።ምንም ነገር አይሰማኝም ብዙ ኃይል ከማግኘት እና ለሳምንት እንቅልፍ ካለመተኛት በስተቀር። ማታ ማታ ፊልም እናያለን። የጦርነት ፊልሞች፥ራምቦ፣ ፈርስት ብለድ፣ ራምቦ ሁለት፣ ኮማንዶ እና ሌሎች በጄነሬተር ወይም በመኪና ባትሪ በመታገዘ እንመለከት ነበር። ሁላችንም እንደ
ራምቦ መሆን እንፈልግ ነበር። እሱ ያደረጋቸውን እንቅስቃሴዎች ለመተግበር እንጓጓ ነበር።

ምግብ፣ መድሃኒት፣ ጥይቶች እና ጋዝ እያለቀብን ሲመጣ በከተማ፣ በገጠር መንደሮች እና በጫካ ውስጥ የሚገኙ
በር የአማጺዎችን ካምፖችን መውረር ጀመርን። ያልታጠቁ ሰዎች የሚገኝባቸውን ሌሎች መንደሮችን በማጥቃት ወታደሮችን መለመልን፡፡

“መልካም ዜና ደርሶናል ከመልዕክተኞቻችን የተወሰኑ አማጺዎችን ለመግደል እና በመጀመሪያም የእኛ የሆነውን ቁሳቁሳቸውን ለመውሰድ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ከዚህ እንቀሳቀሳለን” አለ መቶ አለቃ አዋጁን ሲነግር። ፊቱ ላይ ልበ ሙሉነት ይነበባል። ግንባራችን ላይ አረንጓዴ ጨርቅ አስረን
ነበር ታዳጊዎች ይመሩ ነበር። ምንም አይነት ካርታ ምንም አይነት ጥያቄም አልተነሳም:: ቀጣይ ትዕዛዝ እስከሚሰጠን ድረስ እንዲሁ መንገድ እንድንከተል ነበር የተነጋገርነው ሰርዲን ለመብላት እና ነጩን ክኒን ለመውሰድ ከቆምንበት ውጭ ለብዙ ሰአታት
ያለማቋረጥ ተጓዝን፡፡ ክኒኖቹ ብዙ ኃይል
ከመስጠታቸውም በላይ ደፋር አደረጉን፡፡ የሞት ሃሳብ በጭራሽ ወደ አዕምሮዬ አልመጣም፡፡ መግደል ግን ውሃ እንደመጠጣት ቀላል ሆነ። የመጀመሪያውን ሰው ስገድል ብቻ ልቤ ተነክቶ ነበር። ከዛ በኋላ ግን ምንም አይነት ሃዘን ፀፀት አልተሰማኝም::
ከበላን በኋላ መድሃኒቱን ወስደን አዋቂዎች ለተወሰነ ደቂቃ እረፍት እስኪወስዱ ዙሪያውን ለጥበቃ እንሰማራለን። ከ አልሃጂ ጋር ነበርኩ፡፡ የጥይት መያዣውን በፍጥነት መቀየርን
እየተወዳደርን ነበር።

“ቆይ አንድ ቀን ልክ እንደ ራምቦ ብቻየን አንድ ሙሉ መንደር እቆጣጠራለሁ” አል ሃጂ ፈገግ እያለ እቅዱን ነገረኝ።

ልክ እንደ ኮማንዶ ፊልም የራሴ ባዙቃ እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ። ያምራል።” አልኩ እና አንድ ላይ ሳቅን፡፡

ወደ አማጺዎች ካምፕ ከመግባታችን በፊት መንገዳችን ቀይረን በጫካው ውስጥ በመጓዝ አሰሳ አናደርጋለን፡፡ ካምፑ ዕይታችን ውስጥ ከገባ በኋላሸ ከበባ እናደርግ እና የመቶ አለቃን ትዕዛዝ
እንጠብቃለን። አማጺዎች ከአንዱ ወደ አንዱ ይንቀሳቀሳሉ ፣ሌሎቹ ግድግዳ ተገድፈው ሲቀመጡ እንደእኛ ያሉ ታዳጊዎች ደግሞ ይጠብቃሉ:: አማጺዎችን ባየኋቸው ቁጥር ደሜ
ይፈላል፤ እናደዳለሁ። አማጺዎቹ ቤተሰቤን ያጣሁበትን መንደር አውድመው ካርታ የተጫወቱት ይመስሉኛል። ስለዚህ መቶ አለቃ ትዕዛዝ ሲሰጥ የቻልኩትን ያህል እተኩሳለሁ። ንዴቴ አይወጣልኝም! ከተኩስ በኋላ ወደ ካምፑ እንገባለን፡፡ የቆሰሉትን
እንገድላለን ፤ ቤት ውስጥ ገብተን ጋዝ፣ አደንዛዥ እፆች፣ ጫማ፣የእጅ ስዓቶች፣ ሩዝ፣ ዓሳ፣ ጨው እና ሌሎች ነገሮችን
እንሰበስባለን።ያልታጠቁ ሰዎችን (ሲቪል) ሰብስበን የዘረፍነውንእንዲሸከሙ እናደርጋለን።

“እኛ” መቶ አለቃ ወደ እኛ እየጠቆመ ” ልንጠብቃችሁ ነው እዚህ ያለነው። ምንም አይነት ጉዳት እንዳይደርስባችሁ የምንችለውን እናደርጋለን።” አለ ወደ ያልታጠቁት ሰዎች እየጠቆመ።
“የእኛ ስራ ጥብቅ ነው፤ ሃገራቸውን ለመጠበቅ ምንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ጎበዝ ወታደሮችም
አሉን። እኛ እንደ አማጺዎች አይደለንም። እነዛ ነፍስ ገዳዮች ያለ ምንም ምክንያት ሰው ይገድላሉ፤ ሁሉንም ሰው በጅምላ
ይጨፈጭፋሉ። እኛ ግን የሃገራችንን ለመጠበቅ፤ አገራችን ከእነሱ ክፋት እና ጥፋት ለማዳን ስንል ብቻ እንገድላቸዋለን።ስለዚህ ለእነዚህ የሃገራችሁ ጠባቂዎች ክብር ስጡ” ብሎ መቶ አለቃ ረጂም ንግግር አደረገ። ንግግሩ ሁለት ዓላማ ነበረው።
አንዱ በሲቪሎች ስለ እኛ ጥሩ አመለካከት እንዲኖራቸው ማድረግ ሲሆን ሌላው ደግሞ የእኛን ሞራል መገንባት ነበር።ጠበንጃየን ይዤ ቁሜለሁ። ልዩ የመሆን ስሜት ተሰማኝ፣የተፈላጊነት ፤ አንድ ትልቅ እና ጥብቅ ነገር ተሳታፊ መሆን እና ከአሁን በኋላ ደግሞ ከማንም አልሸሽም።ሽጉጤ አለኝ አስር አለቃ ሁልጊዜ እንደሚለው “ ይሄ መሳሪያ በዚህ ጊዜ የሃይላችሁ ምንጭ ነው:: ይጠብቃችኋል! እንዴት መጠቀም እንዳለባችሁ ካወቃችሁ ደግሞ የምትፈልጉትን ሁሉ ይሰጣችኋል።
መቶ አለቃ ንግግሩን ለማድረግ ምን እንደገፋፋው አላስታውስም። ብዙ ነገሮች ያለ ምንም ምክንያት ወይም ማብራሪይ ይሰሩ ነበር። አንዳንዴ ፊልም እያየን መሐል ላይ ድንገት ለጦርነት እንድንቀሳቀስ እንጠየቃለን። ከስዓታት በኋላ እንዳልተፈጠረ ከማስታወቂያ በኋላ እንደተመለስ ፊልሙን ካቆምንበት
እንቀጥላለን። ሁሌም ውጊያ ላይ ነን ወይ የጦርነት ፊልም እየተመለክትን ነው ወይ ደግሞ አደንዛዥ ዕፅ እየወሰድን ነው።
ብቻችን የምንሆንበት የምናስብበት ምንም አይነት ጊዜ የለም::እርስበርሳችን ስናወራ የምናወራው ስለተመለከትነው የጦርነት ፊልሞች እና መቶ አለቃ፣ አስር አለቃ ወይም ከእኛ አንዳችን ስለፈፅምነው ጀብድ ብቻ ነበር። ከዛ ውጭ ሌላ አለም ያለ አይመስለንም ነበር።

ከመቶ አለቃ ንግግር በኋላ ተራ በተራ ምርኮኞችን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደልን። አማጺዎችን ስንገድል የቤተሰቦቻችን ገዳዮች የተበቀልን ይመስለን ነበር። በፍጥነት የመግደልም ውድድር
ነበር፡፡እኔ አንዱን ምርኮኛ በፍጥነት ስለገደልኩ ተጨበጨበልኝ።ትልቅ ገድል እንደፈፀምኩ ተሰማኝ ። ለእኔ እና ኬን ታናሽ መቶ አለቃ እና ታናሽ ሐምሳ አለቃ የሚል ማዕረግ በቅደም ተከተል
ተሰጠን። ደስታችንን አደንዛዥ ዕፅ እና የጦርነት ፊልም በማየት ገለፅን፡፡

የግሌ ድንኳን ነበረኝ እንቅልፍ ስሌለኝ ተኝቼበት አላውቅም።አንዳንድ ቀን በውድቅት ለሊት ለስለስ ያለው ንፋስ ላንሳ የሚባል ጓደኛየን ዝማሬ ያስታውሰኛል። ዛፎቹ የእሱን ዝማሬ
ሚያንሾሻሽኩ ይመስላሉ:: ትንሽ ካዳመጥኩ በኋላ ደጋግሜ
እተኩስ እና ድምጹን አስወግዳለሁ ።

በምርኮ ይዘን ወደ ዋና ማዕከላችን የቀየርነው መንደር እና በጉዞችን የምናድርባቸው ጫካዎች ቤቴ ሆኑ፡፡ የጦር ጓዶቼ ቤተሰቤ ! መሳሪያዬ የፈለኩትን ማገኝበት እና ጠባቂየ ሲሆን
መግደል ወይም መገደል ደግሞ የምኖርበት ህግ ወይም ደንብ ሆነ። ሃሳቤ ከዚህ በላይ አይሻገርም። ከሁለት አመታት በላይ ተዋጋን መግደል የሌተ ቀን ተግባራችን ሆነ፡፡ ለማንም አላዝንም:: እንደልጅ ሳልኖር ልጅነቴን ሳላውቀው ሳላጣጥመውም ነጎደ። የቀን እና ለሊቱን መፈራረቅ ማውቀው በፀሐይ እና
ጨረቃ መውጣት ወይም መጥለቅ ብቻ ነው። እሁድ ይሁን አርብ ግን አላውቅም::

ህይወቴ ጤናማ ይመስለኝ ነበር። ጥር 1996 አስራ አምስት አመት ሲሞላኝ ግን ይሄ መቀየር ጀመረ

አንድ ቀን ሃያ የሚሆኑ የጦር ጓዶቼን ይዤ ጥይት ለማግኘት ባውያ ወደ ምትባል
👍1
ትንሽ ከተማ ሄድኩ፡፡ በደቡብ በኩል የአንድ ቀን የእግር ጉዞ ነበረ። ጓደኞቼ አል ሃጂ እና ኬን ም ከእኔ ጋር ነበሩ።ከዛ የተመደበውን ጁማህን ለማየት ጓጉተን ነበር። የውጊያ ገጠመኞቹን እና ስንት ሰው እንደገደለ መስማት ፈልገናል። መቶ
አለቃንም ማግኘት ፈልጌ ነበር። ስለ ሼክስፔየር ለማውራት ጊዜ ይኖረናል የሚልም ተስፋ ነበረኝ፡፡

በአቧራማው መንገድ ዳር እና ዳር ሁለት ረድፍ ሰርተን ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ደም በለበሱ አይኖቻችንን እያየን መጓዝ
ጀመርን። ጀንበሯ ስትዘቀዝቅ ወደ ባውያ ከተማ ዳርቻ ተቃረብን። እኛ እዛው ስንቆይ አዛዣችን ወደፊት ሄደ። ከተወሰኑ
ደቂቃዎች በኋላ ወደ ከተማው እንድንገባ ምልክት ሰጠን፡፡


ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሶስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን
ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን ሰላምታ ከተሰጣጣን በኋላ ጁማህን መፈለግ
ጀመርን። ፊቱን ወደ ጫካው ያዞረ ጡብ ቤት ደጃፍ ላይ ዥዋዥዌ ላይ ተቀምጦ ነበር። ከጎኑ መሳሪያ ነበር። ቀስ ብለን ወደ እሱ ስንጠጋ ፊቱን አዞሮ አየን።

ከባድ መሳሪያ ይዘህ ነው ምትዞረው ማለት ነው?” ብሎ አል ሃጂ ቀለደ።

“እንግዲህ ምን ታረገዋለህ! ከ AK ከፍ እያልኩ ነው” ብሎ መለሰ።ሁላችንም ሳቅን።

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እንደምንመለስ ነግረነው ጥይት እና ምግብ ልንጭን ወደ መጋዝን ሄድን።መጋዝን እያለን አዛዣችን፥ መቶ አለቃ “ዛሬን ከዚህ እደሩ፤ እራት ተዘጋጅቷል” እንዳለ ነገረን፡፡ አልራበኝም፡ ስለዚህ ኬን እና አል ሃጂ ወደ እራት
ሲሄድ እኔ ተለይቼ ወደ ጁማህ ተመልሼ ሄድኩ። ማውራት ከመጀመሩ በፊት ለደቂቃዎች ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡

ነገ በጥዋት ለውጊያ ስለምወጣ ከመሄዳችሁ በፊት አላይህም” ብሎ ዝም አለ እና መሳሪያውን እየነካካ ቀጠለ:
የዚህን መሳሪያ ባለቤት ገደልኩት።
ብዙዎቻችንን ከገደለ በኋላ ነበር የደረስኩበት። ከዛ በኋላ ነበር እኔ የያዝኩት ”ብሎ ፈገግ አለ፡፡ እጃችንን አጋጨንና ሳቅን።ወዲያውኑ እንድንሰበሰብ ተጠራን:: ተሰባስቦ መጫወቻ እና
የአዛዦችን መተዋወቂያ ማህበራዊ ፕሮግራም ነበር። ጁማህ መሳሪያውን በአንድ እጁ ከያዘ በኋላ በሌላ እጁ ጫንቃየ ላይ አድርጎ አቅፎኝ ወደ መሰብሰቢያው ሜዳ ሄድን።ኬን እና አል
ሃጂ ከዛው እያጨሱ ነበሩ። መቶ አለቃም በቦታው ነበር። ትንሽ ፈንጠዝያ ነበር። የመቶ አለቃ ጓደኞች አብዛኞቹ ማለትም ሃምሳ አለቃ ማንሳራይ እና አስር አለቃ ጋዳፊ ሙተዋል። እሱ እንዴት
እንደተረፈ አይታወቅም። በተዕምር ምኑም ሳይነካ የለአንዳች ጠባሳ ተርፎ ሌሎች ሃይለኛ እና ታዛዥ ጓዶችን በሞቱ ጓደኞቹ ምትክ ለማፍራት በቅቷል።መቶ አለቃ ጋር ስለ ሼክስፔየር ማውራት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን እሱ በማስተባበር ፤ ሰላም በመስጠት ተጠምዶ ነበር። በመጨረሻ እኔ ፊት ለ ፊት ሲደርስ
እጄን ጥብቅ አርጎ ያዘና “ማክቤዝ አይበገርም፧ ታላቁ የብሪያም ጫካ ዶንከን ኮረብታ እስኪደርስ ድረስ ማክቤዝ እጅ አይሰጥም አለ።

ጮክ ብሎ ”ልለያችሁ ነው ጓዶች” አለ። እጅ ከነሳን በኋላ እጁን እያውለለበ ሄደ። እኛም መሳሪያችን ከፍ አድርገን በጩኸት
ሰላምታችን ገለጸን። መቶ አለቃ ከሄደ በኋላ የሴራሊዮንን ብሄራዊ መዝሙር መዘመር ጀመርን። “ከፍ አድርገን
እናከብርሻለን፤ የነጻ ህዝቦች ሃገር፤ ጥልቅ ነው ለአንቺ ያለን ፍቅር” ለሊቱን ሙሉ ስንጫወት ስናወራ አሳለፍን።
ከመንጋቱ በፊት ጁማህ እና የተወሰኑ ወታደሮች ለውጊያ ሄዱ። አል ሃጂ፣ ኬን እና እኔ በሚቀጥለው ጥየቃ ብዙ
እንደምንጫወት ቃል ገብተን ተሰናበትነው:: ጁማህ ፈገግታ ካሳየን በኋላ መሳሪያውን ጠበቅ አድርጎ ከያዘ በኋላ ወደ ጫካው ገባ፡፡

ከትንሽ ስዓታት በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ወደ መንደር መጣ፡፡ ዩኒሴፍ UNICEF የሚል ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ የለበሱ
አራት ሰዎች ከመኪናው ወርደው ወደ እኛ መጡ። አንድ ነጭ እና ቆዳዋ ነጣ ያለ ምንአልባት የሊባኖስ ሰው እና ሌሎቹ የሃገሩ ሰዎች ሴራሊዎናውያን ናቸው:: ጦርነቱን ያዩ አይመስሉም የተመቻቸው ነበሩ። ወደ መቶ አለቃ ተልከው የመጡ ይመስላሉ። እሱም ሲጠብቃቸው ነበር፡፡ ቤት ደጃፍ ተቀምጠው ሲያወሩ ከማንጎ ዛፍ ስር ተቀምጠን መሳሪያችንን
እየወለወልን እናያቸው ነበር። በኋላ መቶ አለቃ ከሁለቱ የውጭ ሃገር ሰዎች ጋር እጅ ተጨባበጠ፡፡ ጠባቂው ወደ እኛ መጣ እና እንድንሰለፍ ነገረን። ሰፈሩን እየዞረ ከ “ መቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው!” ትዕዛዝ መቀበል እና የታዘዝ ነውን መፈፀም ለምደናል። ወደ ጎን መስመር ሰርተን መጠበቅ ጀመርን።

መቶ አለቃ ከፊታችን ቁሞ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠን፡፡ ሌላ ግዳጅ እየጠበቅን ነበር፡፡ “አሳርፍ” ብሎ ቀስ ብሎ መራመድ
መቃኘት ጀመረ፡፡ እንግዶቹ ከጀርባ ነበሩ።
“ስጠቁም ወደ ጠባቂየ በመሄድ ትሰለፋላችሁ ገብቷችሃል።”ሲል “አዎ! አለቃ” ብለን ጮህን፡፡

“አንተ፣ አንተ.....” መቶ አለቃ እየመረጠ እስከ ሰልፉ መጨረሻ ደረሰ፡፡ መቶ አለቃ እኔን ሲመርጠኝ አትኩሬ ተመለከትኩት።
እሱ ግን አላየኝም:: አል ሃጂም ተመረጠ። ኬን ግን ትልቅ ስለሆነ አልተመረጠም:: “መሳሪያችሁን የጥይት ካዝና አወላልቃችሁ መሬት ላይ አስቀምጡ” የሚል ትዕዛዝ ከመቶ አለቃ ሰጠ፡፡ መሳሪያችንን አወላልቀን መሬት ላይ አስቀመጥን።መቶ አለቃን ተከትለን እንግዶች ወደ የመጡበት ገልባጭ መኪና ሄድን። መቶ አለቃ ፊቱን ወደ እኛ ሲያዞር ቆምን “ ጎበዝ ጀግና
ወታደር ነበራችሁ! ታውቃላችሁ የዚህ ወንድማማችነት እና ሃገርን የማዳን ጥሪ አካል እንደነበራችሁ። ከእናንተ ጋር ሃገሬን
በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል። ኮርቼባችዋለሁ። አሁን ስራችሁ
እዚህ ጋ ያበቃል። ልለቃችሁ ይገባል። እነዚህ ሰዎች ትምህርት ቤት ያስገቧችኋል፤ ሌላ መልካም ህይወት እንዲኖሩዋችሁ ይረድዋችኋል።” ይሄን ብቻ ነበር ተናግሮ ትቶን ሄደ:: ቀጥሎ
ፍተሻ ነበር። ሰንጢ እና ቦምብ ይዤ ስለነበር መፈተሽ አልፈለኩም፡ ፈታሹን ብትነካኝ እገልሃለሁ ብየ ዛትኩበት። ከእኔ
ጎን ወደ አለው ቀጠለ።

ምን እየሆነ እንዳለ አልገባኝም? መቶ አለቃ ለእነዚህ ሰዎች ለምን አሳልፎ ሊሰጠን እንደወሰነ አልገባኝም። ጦርነቱ እስኪበቃ ድረስ የምንቀጥል መስሎን ነበር፡፡ ግን ያለምንም ማብራሪያ
ተወሰድን፡፡

መኪና ውስጥ የደንብ ልብሳቸው ንጹህ እና መሳሪያቸው አዲስ የሆነ ሶስት ፖሊሶች ነበሩ። ፖሊሶቹ ከገልባጩ ወርደው እኛ እንድንወጣ ጠቆሙን። ወጥተን ሁለት አግድም ወንበሮች
ላይ ፊት ለ ፊት ተቀመጥን። ፖሊሶች መውረጃው ላይ ተቀመጥን።

አል ሃጂ እና እኔ በመገረም በብስጭት ተያየን። የት እንደሚወስዱን እንኳ አናውቅም። ለስዓታት ተጓዝን። ያለምንም ስራ ቁጭ ብሎ መጓዙ አድካሚም
አሰልቺም ነበር፡፡ መኪናውን ጠልፎ ወደ ባውያ ለመመለስ አሰብኩ። መሳሪያውን ለመንጠቅ ስዘጋጅ መኪናው ለፍተሻ
ፍጥነቱን ቀንሶ ፖሊሶቹ ወረዱ።
መቀመጥ ስላልቻልኩ በጉዞ በሙሉ እረፍት አልነበረኝም ያቁነጠንጠኝ ነበር። የፍተሻ ጣቢያዎች ስንደርስ ትንሽ ፈታ እል ነበር። በመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያ ያገኘናቸው ወታደሮች የሚያምር ደንብ ልብስ የለበሱ መሳርያቸው አዲስ ነበር።

በኮሮኮንች መንገድ የመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያውን አልፈን እንደሄድን የተጨናነቀ የአስፓልት መንገድ ደረስን። ዙሪያውን
መኪኖች በተለያየ አቅጣጫ ሲጓዙ አየሁ፡፡ በህይወቴ የዚህን ያህል ብዙ መኪኖች አይቼ አላውቅም፡፡ መርሰዲሶች፣ቶዮታዎች፣ማዝዳዎች፣ቼርቮያለ ትዕግስት ሲያጮሁ ሙዚቃ ሲያጫውቱ ነበር፡፡ የት እንደምንሄድ አሁንም አላውቅም ነገር ግን Freetown ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ እንዳለን
አውቂያለሁ።ለምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም፡፡

ውጩ እየጨለመ ነው። መኪናችን በዝግታ ወደ ተጨናነቀው መንገድ ሲገባ የመንገድ መብራቶች ተራ በተራ
እንደፍንጣቂ ነገር ቦግ ቦግ እያሉ መብራት ጀመሩ። የሱቆች እና
የመጠጥ ቤት መብራቶች ሳይቆጠር ብዙ መንገድ መብራቶች ከተማዋን አንቆጥቁጠዋታል። የከተማዋ ፎቆቹም በብዙ ብርሃን የተንቆጠቆጡ ናቸው። ለተወሰኑ ደቂቃዎች በፍጥነት
👍1
ከተጓዝን በኋላ መኪናዋ ቆመች፡፡ ከመኪና ወርደን አራት የ ዩኒሴፍ UNICEF ሰራተኞችን ተከትለን አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ገባን።
ግቢው ብዙ ቤቶች አሉት:: በእኛ እድሜ የሚገኙ ታዳጊ ወንዶችን ደጃፍ ላይ ራሳቸውን አጉብጠው ተቀምጠዋል። ሊያዩን አልፈለጉም፧ ለምን ከዚህ እንደመጡ አላወቁም፥ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሊባኖሳዊ የሚመሰለው ሰውየ ወደ አንዱ ቤት በመውሰድ ከዛ እንደምንቆይ እና የምንተኛበትን አልጋ አሳየን።
በየኣንዳንዳችን ቁም ሳጥን ውስጥ ሳሙና፣ የጥርስ ሳሙና፣ የጥርስ ቡርሽ፣ ፎጣ እና ንጹህ ቲ ሸርት እንደተቀመጠ በደስታ ነገረን፡፡ ነገ ደግሞ ጫማ ትውስዳላችሁ አለ። ምንም አይነት
ስሜት አላሳየንም፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ