አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
569 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#እንዳለ_ይቀመጥ

ተፋቅረን አየሁ ብልሽ
መጣላት አረግሽው
መሳሳቃችንንም
አላቅሰሽ አረፍሽው
በጥሩ መፍታት ሲቻል
ሁሉን ተቀራርቦ
እኔ አራምባ ስልሽ

አንቺ ካልሽኝ ቆቦ
ህልሜን ከፍቅሬ ጋር
ከምትፈቺው አብረሽ
ከሰለሞን ጥበብ
ካዋቂ ዘንድ ወስደሽ
ሳይቀንስ ሳይጨምር
አስቀምጪው አስቋጥረሽ፡፡
#መንፈስና_ስጋ

ከትናንቱ ዛሬን
ከዛሬም ነገን
ቢሆነኝ ብዬ
ስጣጣር ስደክም
እበዛ እበዛ
እበዛ እያልኩ
አንደ ጨው ሟሙቼ
መንምኜ አለኩ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
Forwarded from አትሮኖስ (...) via @Qualitymovbot
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_አምስት


#በጥላሁን

"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ •••
ገብቼ ሊሊዬ ያለችን ስነግረው ያ እንደሀምሌ ወር የፍቅር ደመና የጠቆረው ስሜቱ ፈጎ እንደመስከረም ፀሀይ አብራ።
ወድያው በድጋሚ ሊሊዬ ጋር ደውዬ በነገው ቀጦሮአችን ላይ ኬርያንም ይዛት እንድትመጣ ነገርኳት።

በንጋታው ተገናኝተን ሁሉም ነገር በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቀቀ። ሁለቱም አብረው ሆኑ።
አራታችንም የይንቨርስቲ መግቢያ ፈተና እስክንፈተን እና እስክንበታተን ድረስ ሁለት አመታትን አስደሳች የፍቅር ግዜ በዛው ትምህርት ቤታችን ውስጥ አሳለፍን ።
የማትሪክ ውጤት እኔ ሊሊዬ እና ስናመጣ ኬርያ አልተሳካላትም
እኔ አዳማ ዩንቨርስቲ ስመደብ ሊሊዬ ድሬ ዳዋ ዩንቨርስቲ ደረሳት ቢሆንም አባቷ ከአጠገቡ ርቃ እንድትሄድ ስላልፈለገ ውጪ ሀገር ልኮ እንደሚያስተምራት ቃል ገብቶ አስቀራት። ጋደኛዬ ጅማ ዩንቨርስቲ ደረሰው ። በተመደበልን ግዜ እኔ ወደ አዳማ እሱ ወደ ጅማ ተጓዝን ።
ፍቅራችን ካለበት ሞቅታ ሳይቀዘቅዝ ጭራሽ መነፋፈቅ እያጋለው ቀጠለ።
ዩንቨርስቲ ገብተን ስድስት ወር ሳንማር አለምን ባስጨነቀው ባዲሱ ወረርሽኝ በኮሮና ምክንያት ሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ዩንቨርስቲዎች ተዘግተው ወደየቤታችን እንድንሄድ ተደረገ።
ሊሊዬ ያደገችበት ቤተሰብ እና እኔ ያደኩበት ቤተሰብ ለየቅል ነው ።
በዚህ ምክንያት ፍቅር ሀ ብለን ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ የማይዋጥላት ነገር አባቴን አብዝቼ መፍራቴ ነው። ባትረዳኝ አልፈርድባትም። አሁን ከዩንቨርስቲ እቤት ተቀመጡ ተብለን ከመጣን በሳምንቱ ደውላ
"እኔ ዝም ብሎ በስልክ ብቻ አንተን እያገኙ መኖር ከበደኝ ሶልዬ ሳምንት ሆነን እኮ እዚሁ አንድ ከተማ ውስጥ ሆነን ሳምንት ሙሉ አለመገናኘት ምን ማለት እንደሆነ አስበከዋል ቆይ አልናፍቅህም ግን ?
" ኧረ ሊሊዬ በርግጠኝነት የኔን ያህል አትናፍቂም ግን ምን ላድርግ ያባዬን ባህሪ ታውቂው የለ እንኳን ወረርሽኝ ገባ ከቤት አትውጡ ብሎ መንግስት አውጆለት ድሮም ቢሆን መች ያለ ምክንያት መዞር ይፈቀድልኛል?
"ሶልዬ እኔ ጋር መምጣት በቂ ምክንያት ነው ከዚህ በላይ ምን ምክንያት አለ ደሞ ልዙር ፍቀድልኝ በላቸው መች አልኩህ እንገናኝ ልትለኝ ካልሆነ እንዳትደውልልኝ አኩርፌሀለሁ በቃ በቃ የምሬን ነው! "
ሊሊዬ እንዲህ ነች ተናግራ ነው እምታኮርፈው።

እውነቷን ነው ናዝሬት ትምህርት ላይ በነበርኩበት ባለፉት ወራት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ እንገናኝ ነበር ።
የምሯን እንደሆነ እንደተናደደችብኝ አውቃለሁ ግን ምን ላድርግ ።
አባዬ እንደሆነ ድሮም ድሮ ነው እሄ ወረርሽኝ ሀገራችን ገባ ከተባለበት ግዜ ጀምሮ መንግስት ብቻ ሳይሆን አባዬም ቤቱን ወደ ቤተሰብ ለይቶ ማቆያ የቀየረው እስኪመስለን ድረስ እኔም እህቴም እናቴም እንኳን ወደ ውጪ ልንወጣ የውጪ በር ሲንኳኳ እንኳን እንድንከፍት አይፈቀድልንም።

አባዬ ከቁጥጥሩም ባልተናነሰ ለኛ ለልጆቹ ያለው ፍቅር እስከጥግ ነበርና ቁጥጥሩ በፍቅሩ ስለሚጣፋ በጭራሽ ላስቀይመው አልፈልግም በኔ አዝኖ ከማየው ሞቴን እምመርጥ ይመስለኛል ።
መቆጣት ሲኖርብት የሚቆጣ ፍቅር መመገብ ሲኖርበት ፍቅሩን ሳይሰስት ለልጆቹ የሚመግብ አባት ነው አባቴ በቁጣው በቁጥጥሩ ውስጤ ሲነድ በፍቅሩ ዝናብ እያጠበ ያበርደኛል።
የተመጣጠነ ምግብ ብቻ ሳይሆን የተመጣጠነ ባህሪ መግቦ ነው ያሳደገን።
ምንም ብለው ስለማይፈቅድልኝ ሊሊዬን ሳልፈልግ ዝም አልኳት ። ስልክም አልደወልኩም ሶስት ቀን ሳንደዋወል ስንቆይ ጨነቀኝ ቢሆንም ቻልኩት።
አምስት ቀን ሞላን።
በአምስተኛው ቀን ልክ ከቀኑ በስምንት ሰአት አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ በፊት ተገናኝተን ደብረዘይት ሀዋሳ እየሄድን በምንዝናናበት ወቅት የተነሳናቸውን ፎቶዎች በተመስጦ እየተመለከትኩ ከፎቶው ጋር ሳወራ ድንገት የጮኸው ስልኬ አስደንግጦ ከሄድኩበት የትዝታ አለም ጎትቶ አወጣኝ።

ሊሊዬ ነበረች የደወለችው ።
የኔ ፍቅር በኔ እንደማይስችልሽ እኮ አውቃለሁ ግን ደናነሽልኝ ስላት •••
" አንተ ግን አስችሎህ ዘጋከኝ አደል ?" አልች ድምጿ ውስጥ መከፋታ ያስተጋባል ።
ምን ላድርግ ሊሊዬ አባዬን ከማስቀይመው ብዬ እኮ ነው
ልክ ነህ አባትህን ከምታስቀይመው እኔን ብታስቀይመኝ ይሻላል ተረዳሁህ
ይቅርታም አረኩልህ ግን ከነገወድያ ልደቴ ነው ልደቴ እንዴት እንደሚከበርልኝ ታውቃለህ የፈለገውን ያህል ቢከበርልኝ አንተ ከሌለህ ግን ምኑም ደስ እንደማይለኝም ታውቃለህ ታድያ ልደቴንም ልትቀር ነው ?
ስትለኝ መሀል አናቴን በዘነዘና የተረከኩት እስኪመስለኝ በቆሙኩበት ስንጥቅ አልኩ። አዋ ልደቷ እንዴት እንደሚከበርላት በደንብ አውቃለሁ ። ለሷ ልደት የሚወጣው ወጪ ሶስት መለስተኛ የድሀ ሰርግ ይሸፍናል ብል አልተጋነነም ።። ቀን የተጀመረ ሲበላ ሲጠጣ ተመሽቶ ማታ ለዚሁ ልደት በተዘገጀው ሌላ ክፍል ውስጥ በድጄው ልብ የሚሰውሩ ሙዚቃዎች ለጉድ ሲቀውጥ ሲጨፈር ይታደራል ።

ትልቁን የህይወት ፈተና እየተፈተንኩ መሰለኝ። ሊሊዬን ልደትሽ ላይ አልገኝም ብላት በተገኘሁበት ላትደርስ ምላ እንደምትለየኝ አልጠራጠርም።
አባዬ ደግሞ በዚህ ግዜ እንኳን ውሎ እና አዳር ልሂድ ልለው ከቤታችን ፊት ለፊት ካለው ሱቅ የሞባይል ካርድ ገዝቼ ልምጣ ስለው ቁጭ በል እኔ አመጣላሀለሁ ብሎ ያረጀች ቮልስ ዋገን መኪናውን እያስጮኸ ሄዶ ያመጣልኛል እንጂ ገዝተህ ና ብሎ እንደማይፈቅድልኝ አውቃለሁ።

ኮሮና ብሎ የተረገመ በሽታ መጥቶ ገና አንድ ወር ሳይሆነው ሂወቴን ፈተና አደረጋት ።
ሊሊዬ በዚህ ሰአት ልክ አምና እንዳከበርሽው ያ ሁሉ ሰው ተጠርቶ ሊከበር ነው ማለቴ ለሊት ጭፈራ ምናምን እኮ በዚህ ግዜ ስል ገና ካፌ ቀብል አድርጋ•••
"ቲቭው ላይ ሰልችቶን ያጠፋነውን በአስቸኳይ በአስገዳጅ የሚሉት አዋጅ የተከለከሉትን ምናምን አንተም ልደግምልኝ ነው ሶል
ደሞ ብዙ ሰው የሚመጣ አይመስለኝም የማታው የጭፈራ ብሮግራም ግን የማይቀር ነው!"
ቲቪውን ከምታጠፉት በሽታውን ባጠፋችሁት ይሻል ነበር እያልኩ ስልጎሞጎም
"ምን አልከኝ ?"አለችኝ ።
አይ ምንም !
"እሺ ትመጣለህ አትመጣም?
መምጣት መጣለሁ ግን ቀን አልመጣም ተረጅኝ ሊሊዬ እኛ ቤት እራት በግዜ ሁለት ሰአት አከባቢ ሁላችንም አብረን ስለምንበላ የግድ እራት ላይ መገኘት አለብኝ ከዛ ክፍሌ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በማስመሰል የበሩን ቁልፍ ሰርቄም ቢሆን ውጥቼ ለመምጣት እሞክራለሁ። አልኳት ደርሶ ሊሂድ አልሂድ ባላውቅም እንደዛ ከማለት ውጪ አማራጭ አልነበተኝም።
"እሺ ይሁን የኔ ፍቅር ፍቅር እኮ ነህ ዋናው መምጣትህ ነው ግን እሞክራለሁ ሳይሆን እመጣለሁ ነው የሚባለው ኪኪኪኪ ደሞ ልትወጣ ቢያንስ ሀያ ደቂቃ ሲቀርህ ደውልልኝ ዳጊን እልከውና ይዞህ ይመጣል እሺ?"
እሺ አልኳት። ዳጊ ሹፌራቸው ነው። ተስነባበትን።ሁለቱን ቀናት እማዬ•••
"ልጄ ትናንት እና ዛሬ በአካል እዚህ ከኛው ጋር ቁጭ ብለህ በሀሳብ ብን ብለህ ስትጠፋ እያስተዋልኩ ነው ምንድን ነው እሱ ምን ሆነሀል?"
ብላ እስክትጠይቀኝ ድረስ በጭንቀት አሳለፍኳቸው የሊሊ ቤተሰቦች ስራቸው በሙሉ ከውጪ ሀገር ጉዞ ጋር የተያያዘ ነው ወንድማ ዱባይና ሳውዲ እየሄደ እቃ ያመጣል አጎቷ አባቷ ከንግድ ስራቸው ጋር በተያያዘ ውጪ
👍1
ሀገር መሄድ ክፍለ ሀገር እንደመሄድ ቀላል ነው ለነሱ።
አምና እንዳየሁት ከሆነ በልደቷ ላይ የሚገኙ የማላውቃቸው ጓደኞቿ እና ዘመድ አዝማዶቿ በሙሉ
ተመሳሳይ ስራና ተመሳሳይ ኑሮ ውስጥ ያሉ ናቸው እኔስ በገዛ ቅብጠቴ የደረሰው ይድረስብኝ ብቻ ወደቤተሰቦቼ ሌላ ጣጣ ይዤ እንዳልመጣ እያልኩ ስወዛወዝ ስላስተዋለችኝ ነበር እማዬ እንደዛ ያለችኝ።
ተደነባብሬ አይ በስንት ናፍቆት እና ትጋት ዩንቨርስቲ ገብቼ አንድ አመት እንኳን ሳልማር በዘመኑ አዲስ በሽታ ምክንያት መቋረጡ ገርሞኝ እሄን ሁለት ቀን ዝም ብዬ አስበዋለሁ አልኳት አፌ ላይ የመጣልኝን።

አባዬ ብድግ ብሎ በመጠጋት ፀጉሬን እያሻሸ አይዞህ የኔ ልጅ ሁሉም ነገር በጎ ይሆናል በርግጥ በጎም መጥፎም የምናረገው እኛው ነን እኛ ተጠንቅቀን ፈጣሪም ታክሎበት በጎ እንደሚሆን እና ሁሉም በነበረበት እንደሚቀጥል ግን ይታይኛል ልጄ!አለኝ።

ጭራሽ ጭንቅላቴ ተበጠበጠ ክፍሌ ገብቼ ተጋደምኩ በጭንቀት ደና እንቅልፍ ሳልተኛ ስላደርኩ ነው መሰለኝ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ።
ማታ ላይ እናቴ ክፍሌ መጥታ
"ሰለሞኔ ተነስ እንጂ ምንድን ነው እንደዚህ እንቅልፍ ማብዛት በል ተነስ ባይሆን እራትህን ብላና ተመልሰህ ትተኛለህ!" ብላ ስትቀሰቅሰኝ ተፈናጥሬ በመነሳት ሰአቴን ተመለከትኩ ከምሽቱ አንድ ተኩል ሆኗል
ስልኬን ከፍቼ ስመለከት ጋደኛዬ አራት ግዜ ደውሎ አላነሳ ስለው መልእክት ልካል
"አረ ባክህ ሼም ነው አትመጣም እንዴ እኔና ፍቅር እንኳን ከደረስን ስንት ሰአት አለፈን እኮ !" ይላል መልክቱ።
በረጅሙ ተነፈስኩና የምለብሰውን ናብስና ጫማ አዘገጃጅቼ ወደ ሊሊ ሚስኮል አድርጌ ሳሎን በመሄድ ምንም ሳላወራ በዝምታ ከነማዬ ጋር እራት በልቼ ተመለስኩ እንቅልፉ የተጫጫነኝ ስለመሰላቸው ዝምታዬ አልገረማቸውም ።
ቀን ነበር ተለይቶ የተቀመጠውን የውጪውን በር አንድ ትርፍ ቁልፍ የወሰድኩት። ክፍሌ ገብቼ ልብሴን ቶሎ ቶሎ በመቀየር በመስኮት ዘልዬ በመውጣት ኮቴም የውጪው በር ሲከፈት ድምፅም ሳላሰማ ከፍቼ ስወጣ መኪናው ድሮ መጥቶ ቆሟል ሰላም ብየው ገቢና ገባሁ።
እነ ሊሊ ቤት ደርሼ ገና ሊሊ ወዳለችበት ክፍል ሳልገባ እህቷ ይዛኝ ወደውስጥ ስንገባ ደረጃውን ሽቅብ እየወጣሁ ዘወር ስል ከታች በኩል ድንገት በተከፈተችው በር ታሞ የተኛ ሰው ተመለከትኩ
በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ
ታድያ ሀኪም ቤት ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ! እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#በድን_ላይነሳ

ሞኝ ነው ተላላ
ሰው ተብየው ፍጥረት
ጥብቅና የሚቆም
በ'ጁ አጥፍቶ ህይወት
እፅዋት ጨፍጭፎ
አምርቶ ወረቀት
ከመጥረቢያ በደለደመው
በብዕሩ ስለት
ቀለማት አጣቅሶ
ሙቱን አንተርሶ
ህግ ደነገጎ
መመሪያም አወጣ
በድኑ ላይነሳ
ዳግመኛ ላይመጣ፡፡

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍1
#ሽፍታው_አዕምሮአችን

በበርሃ ተጓዥ
ሽፍታው አዕምሮአቸን
ስንቅና ትጥቅ ይዞ
ምስኪኑን ገላችን
ደምን ከስጋ ጋ
በልቶ የሚፋፋ
አጥንት ምርኩዝ ሆኖት
የሚጓዝ በተስፋ
ነቀዝ ነው አምሳያው
ጠቅላላው ተፈጥሮ
አመንምኖ የሚያስቀር
አካልን ሽርሽሮ፡፡

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ስድስት


#በጥላሁን

በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን
"አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ!"
ታድያ ሀኪም ቤት አልወሰዳችሁትም ?
"ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ!"
እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል።
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
ገና ብቅ ስል ያየችኝ ሊሊ እየተርገበገበች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ብዙ ሰው አይመጣም ብላኝ አልነበር እንዴ እያልኩ በሀሳብ ቢዥታ ውስጥ ሆኜ እኔም አቀፍኳት የሷስ ይሁን ከታዳሚው ተገንጥለው አብረዋት የነበሩ አራት ጓደኛቿ በየተራ "ሰላም ነህ?" ቅብርጥሶ እያሉ በጉንጮቻቸው ጉንጬን ደበደቡት "አትሳሳሙ" የሚለው ማስታወቂያ ትዝ አለኝ ወደ ቤት ከመጣሁና ባባዬ ቁጥጥር ስር ከዋልኩ ወድሂ የመጀሚሪያውን የአትሳሳሙ ህግ ለመጀመሪያ ግዜ ጣስኩ።

በተለይ መጨረሻ ላይ የሳመችኝ የምግብ ብዛት እና አይነቱ እየዘጋት እህል በልታ የማታውቅ የምትመስለው ቅጭጭ ያለች ቀጫጫ ልጅ የፀጉር አሰራራ ነው መሰለኝ እሱን እንድትመስለኝ ያደረገኝ ብቻ የጉንጫ አጥንት ጉንጬን ሲወጋው እራሱ ኮረና ዛሬ አታመልጠኝም አገኘሁህ ያለኝ ነው የመሰለኝ።

ኪሴ ውስጥ ያለችውን በትንሽ ብልቃጥ የያዝኳትን ሳኒታይዘር አውጥቼ እጄን ሳይሆን ፊቴን ልታጠብበት ፈለኩ። ለካ ለእጅ እንጂ ለፊት አይሆንም። ቢሆን ኖሮስ ቤት በኩል ልታጠብ
እንኳን ለመታጠቢያ ለመተንፈሻም ግዜ ሳይሰጡኝ
ሊሊ እና ጓደኞቿ መሀላቸው አስገብተው እያዋከቡ እቤት ውስጥ ወዳሉት ታዳሚዎች መሀል ወሰዱኝ።
እነዛ እቤታቸው ግርግዳ ላይ አንዲት በረሮ ቢያዩ እርርርይ እያሉ ቤቱን ጥለው የሚጠፉ የሀብታም ልጆች ኮሮናን አይፈሩትም ብቻ ሳይሆን ትዝም አይላቸውም ማለት ነው ብዬ እራሴን ጠየኩ ሌላ ማንን እጠይቃለሁ ብጠይቅስ ማን ይመልስልኛል?።

ሁሉንም ሳያቸው ሀገራችንን ጨምሮ በአለም ዙርያ ስለዚህ በሽታ በሚድያ የሚለፈፈውን የሚስበው የኛ ቴሌቭዥን እና ዲሽ ብቻ ነው እንዴ አልኩ።የሚያዳምጠውም የሚያየውም አባዬ ብቻ መስሎ ተሰማኝ።
ጭራሽ ሊሊዬን ሞቀኝ ወደ በሩ አከባቢ ብንሆንስ ብዬ ስጠይቃት የሰመችው ያቺ ኮሮና ስጋ ለብሶ መስላ የታየችኝ ቀጭኗ ልጅ ያጋመሰችውን ቢራ ወደ አፌ እያስጠጋች •••
"እንካ ጎንጨት በልበትና ሞቅ ይበልህ ሞቅ ሲልህ የቤቱ ሙቀት አይታወቅህም ክክክክክክ" አለች። ተከትለዋት ሁሉም ሳቁ ። እኔ እንኳን የምስቅበት የማገጥበትም ጥርስ አልነበረኝም።
አመሰግናለሁ ግን አልጠጣም ብዬ ቢራዋን ከነጇ ከአፌ አከበቢ ገፋ አደረኩት።

ጓደኛዬንና ፍቅረኛውን ከሩቅ አየኋቸው እራሳቸውን አያውቁም በራሳቸው አለም ርቀው ሄደዋል ሊሊዮዬን ጠጋ አልኩና በድጋሚ •••
ስገባ አጎትሽን አየሁት ልበል? አሞታል እንዴ ሊሊዬ? ለምን አልነገርሽኝም እንዳስተዋወቅሽኝ ረስተሽው ነው። መጥቼ እጠይቀው ነበርኮ ።
ዘንድሮ በሽትኛ መጠየቅ ቀርቷል እኮ አልሰማህም እንዴ ኧረ በክህ በልደቷ ቀን ጓደኛዬን ስለበሽታ ስለጥየቃ ምናምን ማውራቱን ተውና ዘና በል " አለችኝ። አሁንም ያችው ልጅ። ወይ ጣጣ ልጅቷ ሊሊ በፊርማዋ አረጋግጣ ውክልና የሰጠቻት ነው እምትመስለው ገና ሊሊን ማናገር ስጀምር ወሬዬን ሳልጨርስ እሷ መልስ እየሰጠች አላስወራ አለችኝ።
ከዛ ቡሀላ አንዳች የሚገላግል ነገር ከዛች ልጅ ካልገላገለኝ በቀር ላለማውራት ወሰንኩ።

ሊሊዬ ከዛም ከዛም እየጠሯት ውክብክብ ስላለች ፍቴን ማየትና መረዳት እንኳን አልቻለችም ነበር።ሁለተኛውን ህግ ጥሻለሁ ርቀቴን ሳልጠብቅ በብዙ የሊሊ ልደት ተጋባዦች መሀል ሆኜ ድንገት ወጥመድ ውስጥ ገብታ መውጫ እንዳጣች ጦጣ ግራ ተጋብቼ ግራ እና ቀኝ ስቁለጨለጭ ቆየሁና በሚጠጡ ፣በሚደንሱ፣ በሚሳሳሙ፣ በሚተሸሹ ሰዎች መሀል ሆኖ በተጨነቀ ፊት መቆየት ከባድ ሆነብኝ።
ይለይለት ብዬ ይሁን ይለይልኝ ብቻ ከቢራውም ከውስኪውም ከወይኑም ቀላቅዬ ስጠጣ ፍርሀት እና ደስታ የተቀላቀለበት ስካር ሰከርኩ።
መጠጡ በላይ በላይ ሲመጣ ፍርሀቱ ጠፍቶ ጊዛዊው ጀግንነት መጣ ድፍረቴ ጨቅ አለ።
ባንድ ግዜ እንደማያ ተለዋውጬላችሁ ቁጭ አልኩ።ኧረ የምናባቱ ኮሮና ሺ አመት አይኖር ሙዚቃውን ከፍ አድርገው ዲጄው ምንድን ነው ለቅሶ ቤት አስመሰለው እኮ ሊሊዬ ዲጄውን ከሰልስት ላይ ነው እንዴ አስነስታችሁ ያመጣችሁት ኬኬኬኬኬኬኬኬ"
እሷም ተከትላኝ
" ኪኪኪኪኪኪኪኪ እሄንን ሶል ነው ስፈልገው የነበረው!" ሊሊም ጓደኞቻም ሳቁ።
ቤቱ አልበቃ አለኝ ከላይ የለበስኩትን ጃኬት አውልቄ ጣልኩት።
ተቀላቀልኩ ፣ ጨፈርኩ ፣ዘለልኩ፣ እየተቀባበልኩ ጠጣሁ፣ ከሊሊዬ ጋር በየደቂቃው መሳሳም፣ መደነስ እስኪደክመን ከጓደኛቿም ጋር ተራ በተራ ጨፈርን አበድን ፣ ከነፍን በረርን ፣
እነሱ የረሱትን ሁሉ ረሳሁ። እነሱ የናቁትን ሁሉ ናቅሁ! እነሱ የሆንኩትን ሁሉ ሆንኩ።
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ?

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1👏1
#ዝማሬ

በሽንቁር ሰማይ ሥር፣ በስንጥቅ ምጣድ ላይ
ባ'ንድ ላይ ጠልቆባት፣ ጀንበር እና ሲሳይ
ምድጃው ሥር ኾና፣ ስትተክዝ ነፍሴ
ራት ኾኖ መጣ፣ የመሸበት ቁርሴ፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ፈረቃ

ሞት እና ሰውነት ሁሌም ይነቃሉ
ነፍስ እና ነፋስ ግን ወቅት ይጠብቃሉ፡፡
ሁሌ ሕያው መኾን አከተመ በቃ
የኛ ሕያውነት ኾኗል በፈረቃ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ግዞት

እፍኝ ተበድሮ ነፍሱን ሊያድናት
ባርያ ሆኖ ሞተ ያባቴ አባት
እዳው ተጭኖት
ባርነት ሲመረው ሲያቅት ለግዞት
የጭሰኛ ክብር ሰጡት ለኔ አባት
አርሶ፣ ዘርቶ፣ አጭዶ ጭሰኛው አባቴ
ምርቱን ሲገብረው ለመሬት ከበርቴ
መሬት ለአራሹ ” መፈክር አንስቼ

ታግዬ አሸነፍኩ ከጫካ ገብቼ
ወገኖቼ ሁሉ ቀድመው የተገፉት
በኔ በልጃቸው አሁን ገና አረፉት
ብዬ በተስፋ ስንቅ ቃላት ስደረድር
አንደበት ሳደድር
ከኔም ለካ አልጠፋም የጭቆናው ቀንበር
ካ'ብታም ግዞት ስር ነኝ ተብዬ “ወዝ አደር”
መደብ ከታች እላይ ጎባጣው ሳይቀና
ነጻነት ከቃላት መቼስ አልፎ ያቅና፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ሰባት (የመጨረሻው ክፍል)


#በጥላሁን

ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።

ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።

ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ••••
እምለው እማረገው ሁሉ ጨነቀኝ ቀና ብዬ እዛው አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩና ሁለቱን እጄቼን ወደ ፊት ዘርግቼ እያየኋቸው •••
ማታ እንዳልተለከፍኩ በምን እርግጠኛ ነኝ እራሴን ጠየኩት?
በምንም ደሞ ጉሮሮህ አከባቢ ህመም እየተሰማህ ነው ይዞህ ይሆን እንዴ ? አለኝ ውስጤ
ጉሮሮዬ እንኳን ማታ ብዙ አይነት መጠጥ እየቀላቀልኩ ስለጠጣሁ ሊሆን ይችላል ያመመኝ ።

ላይሆንም ይችላል በሽታውም አንዱ ምልክቱ እንደዛ ነው?
እስቲ አስበው በዚህ እጅህ ስንቱን ነገር ነክተሀል፣ ከስንቱ ጋር ተጎራርሰህ በልተሀል ፣ከስንቱ ጋር እየተቀባበልክ ጠጥተሀል ፣ ስንቱ የተቀባበለውን ቢራ መክፈቻ ተጠቅመሀል
ውስጤ ሌላ ሰው ተቀምጦ የሚያስፈራራኝ መሰለኝ በሁለት ሀሳብ ተከፍዬ ከራሴ ጋር ስከራከር እራሴን አመመኝ።
አንድ ሰው የማንፈልገውን ወይም የሚረብሸንን ወሬ ቢያወራብን ዝም እንዲል አልያም ወሬ እንዲቀይር እንነግረዋለን ካልሆነ ካጠገቡ ተነስተን እንሄዳለን ከሚድያ ላይ የሚወራውን መስማት ካልፈለግን ተነስተን እንጠረቅመዋለን።
ከደጅ የሚመጣን ጩኸት መስማት ካልፈለግን ጆሮአችንን እንይዛለን
ከውስጣችን የሚመጣውን ጩከት መስማት ባንፈልግ ምናችንን እንይዘዋለን ወዴትስ እንሸሻለን?
እማዬ ድጋሚ የክፍሌን በር አንኳኩታ "ኧረ አባትህ እየጠበቀህ ነው ሰለሞኔ ቁርስ ቀርቧል እኮ!" አለችኝ።
ወጥቼ ሻወር ቤት ገባሁና ከሰዉነቴ ክፍሎች ሁሉ እጄን ደጋግሜ ታጠብኩት።
"ውስጥህንስ በምን ታጥበዋለህ ይዞህ ከሆነ በትንፋሽም እኮ ይተላለፋል አለኝ ከበሽታው በላይ ውጋት የሆነብኝ የውጤ ሀሳብ ነው።

እናባዬ ወዳሉበት ሳሎን ገባሁ ። ግን ሳልጠገቸው ፈንጠር ብዬ ብቻዬን ተቀመጥኩ።
"ዛሬ ምን ሆኗል ልጄ ና እንጂ ቁርስ እንብላ አንተን አይደለም እንዴ የምንጠብቀው" አለ አባዬ።
አይ አይሆንም አባ ካሁን ቡሀላ እሄ ክፉ በሽታ ከሀገራችን ተጠራርጎ እስኪወጣ ምግብም ቢሆን አብረን ለመብላት ስንል መቀራረብ የለብንም ። ለብቻዬ ብታቀርብልኝ ይሻላል አይሻልም አባ? ስል•••
እማ ጣልቃ ገብታ " አበስኩ ገበርኩ የደጁን ይሁን ስል ልጆቼንም ከጉያዬ ሊያርቅብኝ ነው እሄ በሽታ ከመች ወዲህ ነው ልጄ መአድ ተነጣጥለን በልተን የምናውቀው መአድ በአንድ ላይ ቀርቦ መብላት ፍቅርን ያደረጃል ልጄ።
ደሞ በኛ መሀል ኬት ይመጣል ከቤት ወጥተን አናውቅ የምንፈልገውን እቃ እንኳን የባታችሁ ወንድም ነው ገዝቶ የሚያመጣልን እቃ ገዝቶ መጥቶ እንኳን በር ላይ አስቀምጠህ ሂድ እንጂ ግባ ብሎት አያውቅ አባታችሁ።
ዛሬ ድንገት ተነስተህ ለብቻዬ አቅርቡልኝ ማለቱን ምን አመጣው ጥሩ ህልም አላየህም ልጄ እስቲ ንገረኝ?" ብላ ዝም ብዬ ሳያት እኔን ትታ ወደአባዬ ፍቷን መለሰችና
"፣እሄው ልጆቼን የፀሀይ ብርሀን እስኪናፍቃቸው ድረስ አላላውስ ብለህ ተጭነህ ስታስጨንቃቸው በጭንቀት ብዛት የልጄን አይምሮ እንዲቃወስ አድርገከው አረፍክ " ብላ ስታፈጥበት
ደና ነኝ እማዬ ምንም የሆንኩት ነገር የለም አባንም እንደዛ ማለት የለብሽም አባ ልክ ነው ። በቃ ተራራቁ ተብሏል እንራራቅ ነው ያልኩት ቀለል አርጋችሁ እዩትና እሺ በሉኝ እናንተ አንድ ላይ ብሉ ለኔ ለብቻዬ ስጪኝ። ስል እህቴ ከነበረችበት ተነስታ •••
"ባክህ የሌለ ነገር እያወራህ አታጨናንቃቸው ተነስና እንብላ!" እያለች እጄን ይዛ ልትጎትተኝ ነው መሰለኝ ወደኔ ስትጠጋ
ከተቀመጥኩበት ተፈናጥሬ በመነሳት እንዳትጠጊኝ እህቴ ነግሬሻለሁ እንዳትጠጊኝ በቃ ስል አባም ግራ ተጋብቶ ተነስቶ ሲቆም
ተጠግቶ ሳይዘኝ ቤቱን ጥየላቸው ብን ብዬ ልጠፋ አሰብኩና እናቴ ልጄ አበደ ብላ እራሷን ከማጥፋት እንደማትመለስ ሳስበው ፈራሁ።
አንተም እንዳትጠጋኝ አባ በቃ ተረዱኝ አትጠጉኝ አልኩ አትጠጉኝ እያልኩ ወደ ክፍሌ በመግባት ከውስጥ ዘጋሁት።
በስንት ውዝግብ አሳምኛቸው ምግብ መስኮት ላይ እየተደረገልኝ በልቼ አጥቤ እየመለስኩ ስምንት ቀን ሆነኝ ። በዘጠነኛው ቀን ጥዋት ጋደኛዬ ደውሎ
የነ ሊሊ ቤተሰቦች በሽተኛ እቤት ውስጥ መኖሩ ተጠቁሞባቸው ቤተሰቡን በሙሉ አፋፍሰው ካስገባቸው ቡሀላ በምርመራ ሌሎቹ የቤተሰብ አባላት ላይም ስለተገኘ ያን ቀን የሊሊ ልደት ላይ የተገኙት በሙሉ እየታደኑ ወደማቆያ እየተወሰዱ ነው አሉ እኛ ጋም መምጣታቸው አይቀርም አልቆልናል ሶል!"
ሲለኝ እኔ እዛው በተኛሁበት አለቀልኝ ። የተኛሁበት በላብ ሲዘፈቅ ትዝ ይለኛል ካልጋዬ ላይ መነሳት አቃተኝ ካንድ ቀን ቡሀላ ብንን ስል መስኮት ላይ ያስቀመጡትን ምግብ ወስጄ አለመብላቴ ያስጨነቃቸው ቤተሰቦቼ እህቴን በመስኮት አዘልለው በማስገባትና ከውስጥ እንድትከፍት በማረግ አልጋዬ ላይ ዙሪያዬን ከበውኝ እስክነቃ በጭንቀት ሲጠባበቁ ተመለከትኩ ። በሂወቴ እንደዛች ቅፅበት መሪር ሀዘን እና የነብሰ ገዳይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ። እርርይ አልኩ።
በንጋታው ሁላችንንም ወደ ማቆያ ወሰዱን ከቀናት ቡሀላ የምርመራ ውጤቱ ሁላችንም እንዳለብን አመለከተ።
ውጤቱን ስሰማ በተለይ ቤተሰቦቼን በመሉ ማስያዜን ስሰማ ድጋሚ እራሴን ሳትኩ ከሳምንታት ቡሀላ ወደራሴ ስመለስ እና ስነቃ እቤታችን ውስጥ ነኝ።
ሶስታችን አገገምን አባዬ ግን ከመሀላችን
ጎድሏል ።
በነበረበት ስኳር እና ሌላ ተጓዳኝ ህመም ምክንያት በሽታውን መቋቋም አቅቶት በሀገራችን በዚህ በሽታ ከሞቱት ሰዎች መሀል አንዱ ሆነ ።
ይህ ሁሉ በኔ ነው በኔ የደረሰ በማንም አይድረስ!!

💫ተፈፀመ💫

እስቲ ሁላችሁም ይቺን ፅሁፍ በዚች ደቂቃ እያነበባችሁ ያላችሁ #ኮረና የመጣ ጊዜ #ጥንቃቂያችሁ እንዴት ነበር#አሁንስ መልሱን ለራሳችሁ
ግን አሁንም በሽታው ምንም የተቀየረ ነገር የለም መድሃኒት አልተገኘለትም አሁንም የኛ ብቻ ሳይሆን የአለም ስጋት ነው። በየቤታችን እስኪገባ አንጠብቅ እናም ይሄ ታሪክ አንድ ሰው ያስተምራልና #Share እያደረጋቹ።

🛑አሁንም ግን🛑

#እርቀታችንን_እንጠብቅ
#ማክስ_በአግባቡ_እናድርግ
#እጃችንን_በአግባቡ_እንታጠብ
#ከቻልን_ቤት_እንቆይ #ውዶቼ

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#አልወጣም_ተራራ

አልወጣም ተራራ
ደመናን ልዳብስ
ቀስተ ደመናውን፣ ሽቅብ ልቀለብስ
አልዋስም እኔ
ካ'ቡነ ተክሌ ክንፍ
ከያዕቆብ መሰላል
እኔ መውጣት ሳስብ
ሰማዩ ዝቅ ይላል፡፡

🔘በዕውቀቱ ሰዪም🔘
#ፍግ_ላይ_የበቀለች_አበባ

አበባዪቱም አለች፣
ፍግ ላይ የበቀለች
«ምንድን ነው ጥበቡ?»
ሄክታር ማጣፈጠ
አደይን ማስዋቡ፣
እኔም መለስኩላት፣
"ይብላኝ ለንብ እንጂ ዝንብማ ይተጋል
ከቆሻሻ ዓለም ውስጥ ጣ'ምን ይፈልጋል፡፡››

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ክልክል ነው!

ማጨስ ክልል ነው!
ማፏጨት ክልክል ነው!
መሽናት ክልክል ነው!
ግድግዳው በሙሉ ተሠርቶ በክልክል
የቱ ነው ትክክል?
ትንሽ ግድግዳ እና ትንሽ ኀይል ባደለኝ
"መከልከል ክልክል ነው! » የሚል ትእዛዝ አለኝ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ፍሬሙ

ፎቶዋ
የወጣትነቷ
ግድግዳው ላይ ያለ
በኔና በሷ ፊት የተንጠለጠለ
ስንቱን አሳሰበኝ

የሚያምሩት ዐይኖቿ
የሚያምሩት ጉንጮቿ
የሚያምሩት ጭኖቿ
አሉ አሁንም አምረው
በፍሬም ውስጥ ታጥረው፡፡

አጠገቧ ሁኜ
ሶፋ ላይ ቁጭ ብላ
እርጅናዋን አቅፋ
ለጋነቷን ሰቅላ
እኔም ተአምር ሳይ
«ነው» ሶፋ ላይ ኾኖ
«ነበር» ግድግዳ ላይ፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#መልክአ_እናት

ሰላም ለኪ እናታችን
ባለሽበት እንዳለሽ
ከዘመኑ ሴቶች ተለይተሽ
አንቺ የተባረክሽ ነሽ
ሰላም ለዐይኖችሽ
ከጭስ ጋራ ለሚሟገቱ
ከእንቅልፍ ጋራ ለተፋቱ
ተቅበዝባዥ ፍጡር ኾኜ ኑሮዬን ከምገፋ
ምነው እንባሽን በኾንኩ
ካይኖችሽ ሥር እንዳልጠፋ፡፡
ሰላም ለከንፈሮችሽ
ትላንት ለማውቃቸው
ዛሬ ለምናፍቃቸው
ውዳሴ ክብር ምርቃት
ጭብጨባ ሙገሳ ሽልማት በተረፈበት ቀዬ
ምነው ያንቺን እርግማን - ይናፍቃል ጆሮዬ
ከሌሎች ውዳሴና ክብር እልፍ ጊዜ የተሻለ
ለካ በ'ርግማንሽ ውስጥ እናትነትሽ አለ፡፡
ሰላም ለጣቶችሽ
ለሰዎች የቀረቡ፣ ከራስሽ ግን የራቁ
መስጠት መለገስ እንጂ መቀበልን ለማያውቁ
ሰላም ለኪ!
ባለሽበት እንዳላሽ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_አንድ


#በጥላሁን

የጫካ ስሜ ፍልፈሉ ይባላል ። አሁን ካለሁበት የሰው ጫካ ከሞላበት ከተማ ውስጥ መኖር ከመጀመሬ በፊት በየዱራዱሩ እና ጫካ ውስጥ ባሉ የተያዩ ዋሻዎች ከ ስምንት እመት በላይ ኖሪያለሁ። ጫካ የምኖረው አውሬ አልያም ከሰው ተቀላቅሎ መኖር የማይችል ልዩ ፍጡር ስለሆንኩ
አልነበረም ።

በግዜውና በነሱ ምልከታ ትክክል የመሰላቸውን እኔም በግዜው ትክክል የመሰለኝን ፈፅሜ ልፈፅም እንጂ።
አስተሳሰብ የሚያቀና እውቀትን አልያም ሀብትና መሬትን ሳይሆን ከፊቱ አደራ የታከለበት በቀልን አውርሰውኝ ከሞተው አባቴ የተቀበልኩትን ገሎ የመበቀል ውርስ ለመፈፀም ባጠፋሁት ነብስ ምክንያት ከሚደርስብኝ የበቀል ዱላና ቅጣት ለመደበቅ መኖሪያዬን በዱር እንዳደርግ ግድ ሆኖብኝ እንጂ ።

ገና አስራ ስምንት አመት ሳይሞላኝ ከሁለት አመት በፊት ከተለየኝ አባቴ የተሰጠኝን ነገር ቢኖር የምበቀለው እነማንን እንደሆነና የት አከባቢ ሊኖሩ እንደሚችሉ እና መሳርያ ብቻ ነበር።

18 አመት እንደሞላኝ ካባቴ የተሰጠችኝን መሳሪያ ጠራርጌ እናቴን ተሰናብቼ ከቤት ወጣሁ ለስድስት ወራት በአከባቢው ካለ ጫካ ውስጥ ተደብቄ የበቀል ኢላማዬ የሚያርፍባቸውን ካባቴ ዘር ነብስ አጥፍተው የተሸሸጉ ሁለት ሰዎችን መውጫያ መግቢያ ሳጠና እና አመቺ ግዜ ስጠብቅ ቆየሁ።

በሶስተኛው አመት መገባደጃ ላይ ግዳጄን እንደፈፀምኩ ከሶስት ቀን በላይ በግር ተጉዤ ከነበርኩበት ራቅ ወዳለ ሌላ ጫካ ገባሁ።
እልፎ እልፎ ከምኖርባት የጫካ ዋሻ በቅርብ ርቀት ባለች አንዲት ተራራማ መንደር እየሄድኩ የሚያስፈልገኝን ይዤ እመለሳለሁ ።

በአምስት አመት ውስጥ በአሳቻ ሰአት እራሴን ቀይሬ ሁለት ግዜ ብቻ እናቴን ጠይቂያታለሁ።
ወደዚች ከተሸሸኩበት ጫካ በቅርብ ርቀት ወዳለች የገጠር መንደር ግን በሳምት ውስጥ ከሁለት ግዜ ብላይ መሄድ ጀመርኩ።

በ አንድ የገና አውዳ አመት እለት ወደ መንደሯ ጎራ ብዬ በግሬ ሳዘግም አንድ ጠላ ቤት በር ላይ እንደደረስኩ ሽታው አወደኝ የሚያውቀኝ ሰው እንዳይኖር ፈራ ተባ እያልኩ ዘው ብዬ ስገባ አመት በአል ስለነበር ከሶስት ጎረምሶችና ካንድ በድሜ ጠና ካለ ሽማግሌ ውጪ ብዙም ሰው አልነበረም። ጥጌን ይዤ እንደተቀመጥኩ አንድ እድሚያቸው በሀምሳዎቹ አፋፍ ላይ የሚሆናቸው ባልቴት ጠላውን ፊት ለፊቴ ባለችው ትንሽ ጠረጴዛ ላይ እያስቀመጡ ደና ዋልህ ልጄ አሉኝ።

ለሰላምታው ምላሽ ሰጥቼ ጠላውን አንስቼ ጎንጨት አልኩት አላወረድኩትም ግሩም ነበርና ባንድ ትንፋሽ ግማሽ አደረስኩት።
እቤቱ ውስጥ ያሉት ሶስት ጎረምሶች ስለ ባለጠላ ቤቷ ሴትዬ ልጅ ቁንጁና ከሚገባው በላይ እያደነቁ ያወራሉ ።

ያን ያመሰለ ውበት ይዛ እስካሁን ባለማግባታ ይደመማሉ። እሷ እዛ የገጠር መንደር ውስጥ ዘናጭ የሆነ ቤት ሰርታ ለብቻዋ እየኖረች የሳቸው ጠላ መሸጥ አይገርምም እያሉ ያሽማጥጣሉ። ሴትዬዋ ጠላውን ሊቀዱላቸው ጠጋ ሲሉ ወሬያቸውን ያቋርጣሉ። ልጅቷን የማየት ጉጉቴ ጨመረ ።አልፎ አልፎ ወደዛ ጠላ ቤት እንድምትመጣ ስለሰማሁ ላይን ያዝ እስኪያደርግ ጠላውን እየደጋገምኩ ብጠብቅም እሷ ሳትመጣ እኔ ሰከርኩ።
ጠላው በሳምት ውስጥ ማክሰኛ እና ቅዳሜ ብቻ ነው የሚኖረው ። የኔም የማክሰኛና ቅዳሜ ውሎ ጫካ ሳይሆን እዛ ቤት ሆነ ከሶስት ሳምንት የማክሰኛና ቅዳሜ ምልልስ ቡሀላ በአራተኛው ሳምንት ቅዳሜ ቁጭ ብዬ ጠላዬን ሳጣጥም ድንገት ዘው ብላ የገባችውን ሴት ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ከዛ በፊትም ከዛ ቡኋላም እስከዛሬ ድረስ ተሰምቶኝ አያውቅም።

ምድር ላይ ካሉ ሴቶች ሁሉ ውበት ቀምቶ ለሷ የሰጣት ነው የምትመስለው አይኖቿ ልብ ያሸብራሉ።
ሀር የመሰለው ቀጭን ወገባ ላይ የሚንከባለለው ጥቁር አንፀባራቂ ፀጉሯ ለካ እስከዛሬ ፀጉር አይቼ አላውቅም ያስብላል።

ወደ ውስጥ ስትዘልቅ ከቀጭን ወገባ ቁልቁል ግዛቱን እያሰፋ የሄደው ዳሌዋ ሲውረገረግ ቁጭ ብድግ ያሰኛል። ጥርት ያለው ጠይምነቷ እንኳንም ነጫጭባ ፈረንጅ አልሆንኩ እንኳንም ኢትዬጲያዊ ሆንኩ ያሰኛል ።
ፈገግታዋ ልብ ላይ የተተኮሰ ጥይት ይመስል ልብ ይንዳል ። አንድ ባል አይደለም አንድ ክፍለጦር በውበት አንበርክኮ የሚያስከትል ይሄን ሁሉ ውበት ይዛ ያላገባችበት ምስጢር ምን ይሆን አልኩ ለራሴ።

ተወልጄ ባደግኩበትም ይሁን በሄድኩበት ሁሉ እስከዛሬ ይችን የመሰለች የውበት ሚስጥሩን የገለጠባት ከ
ኮረዳ ተመልክቼ አላውቅም።
ወይ ጣጣ ከፊቴ ተቀምጣ አይኔን እንዴት ከሷ ላይ ልንቀልና ልጠጣ ።

የምትኖርበት መንደር በመሀላቸው ጫካ እርሻ እና ተራራ ያራራቃቸው እዚህም እዛም ተራርቀው ካሉት ውስን ቤቶች በቀር ብዙም ነዋሪ የለም ።
ለመንደሩ አዲስ እንደሆንኩ ታውቋታል መሰለኝ ከናቷ ጋር እያወጋች አልፎ አልፎ እነኛን ውብ እይኖቿ ከብለል እያረገች ትመለከተኛለች ።
እንደተቆጡት ህጣን ልጅ እርበተበታለሁ።
አለባበሷ ግን ከተሜ ቀመስ ትመስላለች እንደው ወደ ከተማ ባል ይኖራት ይሆን? ካላት ታድያ እዚህ ለምን ትኖራለች ?።
ስፈራ ስቸር ቆይቼ አንድ ቃል ካፌ ወጣ።
እናት አለም ጠላ እንጠጣ?
"አባት አለም አልጠጣም! ክክክ"
ደነገጥኩ ስደነግጥ አይታ ይባስበት ይደንብር ብላ ነው መሰል ሳቋን ለቀቀችው።

ስትስቅብኝ ወንድነቴ ኬት እንደመጣ እንጃ ፍርሀቱን ትቼ ደፈር ብዬ አጫውታት ጀመር በስም ብቻ እማውቀው ፍቅር እኔን ለመቆጣጠር ቀጠሮም አላስፈለገው አልቻልኩም ከማክሰኛና ከቅዳሜ ውጪ ጠላ ኖረም አልኖረም ከተደበቅሁበት ዋሻ ወደሷ መሮጥ የየለት ተግባሬ ሆነ እኔ ቀድሜ በፍቅሯ ብወድቅም እሷ ቀስ በቀስ ለምዳኝ ይሁን ወዳኝ እርግጠኛ ባልሆንም ስንለያይ " ነገ ትመጣለህ ?" ማለት ጀመረች።

ማን እንደሆንኩ አንድም ቀን ሳትጠይቀኝ ለምን እስካሁን እንዳላገባች እንድጠይቃት ሳትፈቅድልኝ ከሶስት ወር ምልልስ ቡሀላ ጠቅልዬ ቤቷ ገባሁ። ተጋባን ።

ተጋብተን በሁለተኛው ቀን ግራ የሚያጋባ ነገር ገጠመኝ ማታ አጠገቤ የተኛችው ፍቅሬ እኩለ ለሊት ካለፈ ቡሀሏ ድንገት ስነቃ አጠገቤ የለችም •••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#እንደ_ሚስት_አውለኝ

በእንቁ ተሽሞንሙኜ ገነት ባያውለኝ
ከቸነፈር ከ'ሳት ከሲኦል ባይጥለኝ
እንደ እናቴ ግን አይሁን
እንደ ሚስቴ አውለኝ
ርሃብ ጉስቁልና አንዳችም ሳይነካኝ
በደስታና ሃሴት ሳውካካ እንድገኝ፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ዘመን_በወፍ_በረር

ነበረ ወጉማ የመተጫጨቱ
ሎሚ ተወራውሮ ደረት መማታቱ
ወንዝ ወረድም ብሎ ውሃ ማቃዳቱ
እኔን ግን ከበበኝ ዘመኑ ለወጠኝ
የግዜ ጥበቡን መነጽሩን ሰጠኝ
እኔም ዘመንኩና ለውጥን ተቀበልኩት
አይኔን ብወረውር ደረቷን መታሁት፡፡

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘