አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ከዛፍ_የተቀሰመ_ዜማ

ካ'ለም እቅፍ ወጥቶ
ካ'ለም እቅፍ ሸሽቶ
ወደ ገዳም ሲሄድ
ደክሞት ተዝለፍልፎ
ብላቴናው ያሬድ ካ'ንድ ዛፍ ሥር ዐርፎ
ከዛፉ ግንድ ሥር ትል ሲሸልል ሰማ
እንዲህ በሚል ዜማ
ዛፉ ነው ሕይወቴ
ቅጠሏም እራቴ
ሰባት ጊዜ ልውደቅ
ሰባቴ እንድወጣ
የኋላ ኋላ ራቴን ኣላጣ”
ይህን ስትሰማ ቅጠሊቱ ራደች
መሸሽ ባይኾንላት ሙሾን አወረደች
ዛፉ ሕይወቴ ነው
ግን ኀያል ቢመስልም
ተራራ ቢያክልም
የማታ የማታ
ከትል አያስጥልም”
ያሬድ ይኼን ሰምቶ
ትሉ በጥረቱ ራት ሲበላ አይቶ
ተስፋውን አጸናው
በቅጠሏ ዕጣ ግን ተነካ ልቡናው
ከዚያም ተመልሶ
የትሉን ፉከራ
የቅጠሏን ለቅሶ
ባ'ንድ ላይ ለውሶ
ዜማውን ቀመረ
ዜማው ተዘመረ
ከሰው ነፍስ ተስማማ
በሰው ድምፅ አማረ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
👍1
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_ሁለት


#በጥላሁን

ተጋብተን በሁለተኛው ቀን ግራ የሚያጋባ ነገር ገጠመኝ ማታ አጠገቤ የተኛችው ፍቅሬ እኩለ ለሊት ካለፈ ቡሀሏ ድንገት ስነቃ አጠገቤ የለችም።

ደነገጥኩ ቤቱ ሁለት ክፍል ነው ከተኛሁበት ክፍል ተነስቼ ሌላኛው ክፍል ውስጥ መኖር አለመኖሯን ለማረጋገጥ ባስብም ከማሰብ ውጪ ካልጋው ላይ መውረድ አቃተኝ አልቻልኩም።
በተፈጥሮ ከንቅልፍ ነቅተን ለመነሳት ከሚጫጫነን ስሜት እጅግ በላቀ ሁኔታ እንዳልነሳ ተጫጫነኝ ቀና ማለት እየፈለኩ ቀና ማለት ተሳነኝ እስርስር ድብት የሚያረግ መንፈስ ወረሰኝ። መነሳት እየፈለኩ መልሶ እንቅልፍ ጣለኝ።ወፍ ጭጭጭጭ ሲል ነቃሁ። አጠገቤ ተኝታለች። ግራ ተጋባሁ ለሊት ካጠገቤ ያጧኋት በህልሜ ይሁን በውኔ መለየት ፈተና እንደሆነብኝ መምሸቱ አይቀርም ዳግም መሸ።

ትናንት በነቃሁበት በተመሳሳይ ሰአት እኩለ ለሊት እንደተሻገረ ነቃሁ አጠገቤ ተኝታለች። ያን ቀን ደግሞ ከትናንቱ በተቃራኒ አንዴ ከነቃሁ ቡሀላ እንቅልፍ አልወስድ ብሎኝ ስገላበጥ ነጋ ።
አራተኛው ምሽት መጣ ስንጨዋወት አምሽተን እራት በልተን ተኛን። በተለመደው ሰአት በር ሲከፈት ይሁን ሲዘጋ እንጃ ብቻ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝና ብንን አልኩ። ኧእምሬዬ ከተኛበት ቢነቃም አይኔ አልተገለጠም ነበርና እጄን ወደ ጎን ልኬ ዳበስ ዳሰስ ሳደርግ ከፍራሹ ካንሶላ እና ከብርድልብሱ ውጪ ማታ አጠገቤ የተኛችው ሚስቴ የለችም ።ፈራሁ። አይኔን መግለጥ ፈራሁ።

በትግል የገለጥኩት አይኔ በፋኖሱ ብርሀን የኔዋ ጉድ አጠገቤም የተኛሁበት ክፍል ውስጥም ያለመኖሯን አረጋገጠልኝ። እቤቱ ውስጥ ምንም ድምፅ የለም ፀጥ ረጭ ብሏል። መነሳት እየፈለኩ አልነሳም መጣራት እየፈለኩ አልጣራም።ጭራሽ ከመነሳት ሀሳቤ ጋር ያልተናበበው አይኔ ካልተከደንኩ እያለ ይታገለኝ ጀመረ ። አይኔ እየተከደነ እንቅልፍ ሊጥለኝ ሲሞክር ላለመተኛት ያደረኩት ትግል ከውስን ደቂቃዎች መሻገር አልቻለም። መሸነፌ የገባኝ ጥዋት ስነቃ ነው ለሊት ያልነበረችው ሚስቴ አጠገቤ ጧ ብላ ተኝታ እራሷን አታውቅም ።

የኔ ፍቅር ማነሽ አቅሌን እስካጣ በፍቅርሽ መውደቄ ይሆን እያቃዥኝ ያለው ።
የፍቅሬ ደረጃ ይሆን ጥለሽኝ የወጣሽ ካጠገቤ የራቅሽ እየመሰለኝ እንድጨነቅ የሚያደርገኝ ነው ወይስ የእውነት ነቅቼ ካጠገቤ እያጣሁሽ ነው ።
እንደዛ ከሆነስ በውድቅት ለሊት የት እየሄድሽ ነው ? መቼስ ባዛ የሰይጣን ሰአት መብራት በሌለበት በዚህ የገጠር መንደር ውስጥ ከቤት መውጣት እንኳን ለሴት ለወንድም ያስፈራል ። ታድያ ምን እየሆንኩ ነው የእውነት ነቅቼ ካጠገቤ አጥቼሽ ከሆነስ ለምንድን ነው ተነስቼ ሁለተኛው ክፍል ውስጥም አለመኖርሽን እና ቤቱ ቤት በኩል እንደተዘጋ ከውጪ ይሁን ከውስጥ ማረጋገጥ ያቃተኝ ።

በለሊት ካጠገቤ ተነስተሽ የት ሄደሽ ነው አልነበርሽም ብዬ እንዳልጠይቅሽ ችግሩ ከኔ ከሆነ እንዳላስቀይምሽ ሰጋሁ። አልኩኝ በውስጤ ብርድልብስም አንሶላም ሳትለብስ ተዘረጋግታ በተኛችው ሚስቴ ላይ እንደጥዋት ፀሀይ ሰውነት የሚያሞቀውን የውበት መአት የፈሰሰበትን ገላ ከታች እስከ ላይ እያየሁ። ምን ዋጋ አለው የትዳር ጣእም የላይ ውበት ሳይሆን የውስጥ ሰላም መሆኑ አሁን ነው የገባኝ።

እሄ ነገር አንድ ቀን እየዘለለ በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጠለ። ተአምር የሆነብኝ ነገር ለሊት ስነቃ አጠገቤ ካለች ከነቃሁ ቡሀላ በጭራሽ እንቅልፍ አይወስደኝም ። በሚቀጥለው ቀን ስነቃ ደግሞ አጠገቤ አትኖርም ግን መነሳትም አልችልም በዛ ላይ ወድያው እንቅልፍ ይጥለኛል።ጭንቀቴን ለማን ላዋየው ያለሁት ከሷ ውጪ ማንንም በማላውቅበት ሀገር ነው ።
ጭንቀቴ እና ፍርሀቴ ለሊቱን ብቻ ሳይሆን ቀኑኑም አጨለመብኝ።
እሄን ግዜ ነበር እናቴ ያለችኝ ነገር ትዝ ያለኝ ።
ያባቴን የበቀል ውርስ ልፈፅም ስነሳ ብቻ ብርክክ አለችና ጉልበቶቼን ይዛ "ተው ልጄ የሰው ደም ደግ አይደለም በምድርም በሰማይም ሰላም አይሰጥም ።የሰው ነብስ ያጠፋ የሰላም እንቅልፍ የለውም።የገደለው ሰው ነብስ ታስጨንቀዋለች። አንድ ሰው ስትገድል በህይወት ዘመኑ የሰራው ሀጥያት በሙሉ ወዳንተ ይዞርና እሱ ይፀድቃል አንተ ትኮነናለህ ።
በምድርም በሰማይም ብኩን ሆነህ ትቀራለህ። እሄን ባለማድረግህ አባትህን እንደከዳኸው ቃሉን እንዳላከበርክ አይሰማህ። ይልቅ የነሱን ስተት አትድገመው ካለፈ ነገር ማስቀጠል ያለብን ደግ ደጉንና የሚጠቅመንን እንጂ ክፋቱንና የሚያጠፋንን መሆን የለበትም። ይህን የበቀል መንገድ አንተ ካላቆምከው ማን ያቆመዋል። ሰው በመግደል ጀግንነት ነው ብሎ ማሰብ ሗላ ቀር አመለካከት ነው ። ልጄ ተለመነኝ አትሂድ!"
ልመናዋን መቀበል ፈሪ መሆን ከወንድነት ዝቅ ማለት መስሎ ተሰማኝ ።
እማምዬን ከጉልበቴ ላይ አነሳሗትና ጥያት ወጣሁ። ታድያ አግብቼ ወር ሳይሞላኝ መቋጠሪያውም መፍቻውም የማይታወቅ ፈተና ሲገጥመኝ ። እማማ እንዳለችው ያ ያጠፋሁት ነብስ በቁሜ እያቃዥኝ እንጂ የኔ ንግስት በለሊት የምትወጣበት ምንም ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብዬ እራሴን ለማፅናናትም ለመኮነንም ሞከርኩ።

ከብዙ አስጨናቂ ቀናት ቡሀላ አንድ ቀን ወደ ጫካ ወርጄ ለብዙ ሰአት ተቀምጬ ያሳለፍኳት እያንዳንዷን አስጨናቂ ቀን ስፈትሽ ሚስቴ ማታ ማታ ከምታደርጋቸው ነገሮች እስካሁን የተጋረደብኝ እና ያላስተዋልኩት አንድ ነገር ብልጭ አለልኝ።
በድንጋጤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቆምኩ በለሊት ከአጠገቤ የሄደች በመሰሉኝ ቀናት በሙሉ ማታ ማታ ወደ ምኝታዬ ልሄድ ስል በንድ ከቀንድ በተሰራ የጠላ መጠጫ ቀላስ ሙሉ ጠላ ትሰጠኝ ነበር አጠገቤ በነበረችባቸው ለሊቶች ምሽት ግን ያ ጠላ ተሰጥቶኝ እንደማያውቅ ተገለጠልኝ ። ከምኝታዬ እንዳልነሳ ጠፍንጎ የሚይዘኝ ሚስጥር ከጠላው ጋር የተያያዘ መሆን አለበት አልኩ።

ከሩጫ በማይተናነስ እርምጃ ወደ ቤት አመራሁም። ያን ቀን ማታ ጠላው አልተሰጠኝም። እሳም ለሊት አጠገቤ ነበረች።
በሚቀጥለው ቀን ማታ ከራት ቡሀላ ልተኛ ስል "እንካ ጠጣ ለንቅልፍ ይሆንሀል"እያለች ጠላውን በዛው መጣጫ ይዛልኝ መጣች። ተቀብያት ወደ ውስጥ ገባሁና ሳታዬኝ ደፋሁት።
ምኝታዬ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በመምሰል እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር እየተጠባበኩ እኩለ ለሊት አለፈ። በግምት ከለሊቱ ስምንት ሰአት አከባቢ ድምፁ ቀጭን የሰው ሳቅ የሚመስል ጅብ ወደ አለንበት ግቢ ተጠግቶ ማስካካት ጀመረ ። ትንሽ ቆይቶ የማስካካቱ ድምፅ እየቀረበ የሚያሽካኩትም ጅቦች እየበዙ መጡ።
ድምፁን በሰማሁ በሰከንዶች ውስጥ ጉደኛዋ ሚስቴ ድንገት ብድግ አለች። ፊቴን አዙሬ በተኛሁበት በድንጋጤ ላብ አዘፈቀኝ ። ፋኖሱን ይዛ ወደ ሚቀጥለው ክፍል ስትገባ በቀስታ ተነስቾ በመሀለኛው በር ጠርዝ አጮልቄ መመልከት ጀመርኩ። ከመቅፅበት መሶብ ወርቅ ከሚባለው የመሶብ አይነት ውስጥ ቅጠል የመሰለ ነገር አንስታ አፏ ውስጥ ከተተችና ትርጉሙ ባልገባኝ ቋንቋ በጣም በፍጥነት እየለፈለፈች ከግንባሯ በላይ ያለውን የራስ ቅሏን ልክ እንደኮፍያ ከነፀጉራ አውልቃ መሶብ ወርቁን ከፍታ አስቀመጠችው። ወንድነቴ ተፈተነ እግሮቼ መቆም ተሳናቸው በሩን ከፍታ ስትወጣ ከቆምኩበት መንቀሳቀስ አቃተኝ•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ይድረስ_ላድርባይ_ጓዴ

እየለየ ጊዜ ቦታ እየመረጠ
እስስታማ መልክ ገጽኽ ተለወጠ
አህያ እዳልነበርህ በሰርዶዎች መሀል
አህዮች ሲበዙ ዛሬ ጅብ ኾነሀል፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#የለንበትም

ልብህ የወዳጅ ፤ ልብስህ የጠላት
በምን እንለይህ፤ በምን ብልሀት
መሳይ ልብስ'ንጂ፧ መሳይ ልቡና
ለይተን ማወቅ ፤ አንችልምና
ድንገት አግኝተን ብንገድልኽ የትም
የለንበትም! የለህበትም!

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#አፅናኝ_የጠፋ_ለት

የወላድ አንጀቷን
ሀዘን ሲያላውሰው
በእናት አይኖች ነው
ሀገር ምታለቅሰው።

🔘ኢዛና መስፍን🔘

#Stop_killing_Amhara
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_ሶስት


#በጥላሁን

የራስቅሏን ከነፀጉራ አውልቃ መሶብ ወርቁን ከፍታ አስቀመጠችው። ወንድነቴ ፈተነኝ እግሮቼ መቆም ተሳናቸው በሩን ከፍታ ስትወጣ ከቆምኩበት መንቀሳቀስ አቃተኝ•••

እዛው የተደገፍኩትን ግድግዳ ተደግፌ ቁልቁል ተንሸራተትኩ። ቁጭ አልኩ። ማን ነች? ምንድን ነች? ምን ላድርግ? ሳትመለስ ውልቅ ብዬ ልጥፋ? ያን ሁሉ አይቼ የማላውቀውን ልቤ ላይ የተቆለለውን የፍቅር ክምር ባንድ ግዜ መናድ ባንድ ግዜ መጥላት እችል ይሆን? ኧረ ፈራሁ! ጫካ ውስጥ ወይ ለመግደል ወይ ለመሞት ወስኜ ካባቴ ጠላቶች ጋር ልፋለም ስወጣ ከነሱ ጋር ፊት ለፊት ስጋፈጥ ቅንጣት ታክል ፍርሀት ስላልተሰማኝ ጀግና ነኝ ብዬ አስብ ነበር።ታድያ አሁን ያ ሁሉ ወኔዬ ወዴት ሄደ። ፍቅር ፈሪ ያደርገል እንዴ? ፍቅር ለካ ከጥይት በላይ ያስፈራል! ፍቅር ለካ ከሞትም በላይ ያስፈራል! ሞት ቢያስፈራኝማ ያኔ በፈራሁ ።አሁን የፈራሁት ሞትን አይደለም ማለት ነው? የፈራሁት በሆነው ምክንያት ያፈቀርኳትን ላጣት ግድ ሊሂንብኝ መሆኑ ነው።
ያስፈራኝ ካሁን ቡሀላ ያን ደስ የሚል የፍቅር ስሜት ቀስ በቀስ ከልቤ ተኖ ሊጠፋ መሆኑ ነው ።

ጨነቀኝ። በሂወቴ እንደዝች ቅፅበት ያስጨነቀኝ ነገር ኖሮ አያውቅም።
እሺ አሁን ምን ላድርግ? ! እዛ መሶብ ወርቅ ውስጥ ያስቀመጠችውን ነገር ላየው ፈለኩ ። ተነስቼ ወደ መሶብ ወርቁ ተጠጋሁ እንዴት ልክፈተው እጄ አልታዘዝ አለኝ። ወንድ ልጁ መሬት የጣለው ክንዴ መሶብ ወርቁን ለመክፈት ጉልበት አጣ። እራሴን አረጋግቼ እሷን ለመጥላትም ማድረግ ያለብኝንም ለመወሰን ግዜ እንደሚያስፈልገኝ አሰብኩ ።
ለብዙ ደቂቃ ግራ ተጋብቼ በቆምኩበት ከውጪ የሆነ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝ። በፍጥነት ወደ ምኝታዬ ተመለሼ የሚሆነውን ስጠባበቅ መልሶ ፀጥ ረጭ አለ ።
ከቆይታ ቡሀላ በሩ ሲከፈት ሰማሁ። በኮቴዋ ድምፅ ወደ መሶብ ወርቁ እንደሄደች ተረዳሁ። ወድያው ስትታጠብ ተሰማኝ ። ፍቴን ወደ ግድግዳው አዙሬ ወጪ ገቢ ትንፋሼን የተኛሁ እንዲመስል አደረኩት።
መጥታ አንሶላና ብርድ ልብሱን ገልጣ አጠገቤ ስትተኛ ያቺ የማፈቅራት ቆንጆ ሴት ሳትሆን የሆነ አውሬ አብሮኝ የተኛ መሰለኝ ። ቀፈፈኝ። ገላዩ ከገላዋ እንዳይነካካ ወደ ግድግዳው ተለጠፍኩ። ለደቂቃዎች ቁና ቁና እየተነፈሰች ቆየችና
"ለምንድን ነው ፊትህን አዙረህ ምተኛው ብላ ጎትታ በመገልበጥ በጀርባይ አንጋለለችኝ ።
ብድግ ብላ እላዬ ላይ ጉብ አለች ። ሆዴ ላይ ቁጭ አለች። አይኔን ለግለጥ ድፍረት አጣሁ ። ጎንበስ ብላ ከንፈሬን ጎረሰችው ትንፋሽ አጠረኝ። ከንፈሬን ደምደም እለኝ ከሄዴ ውስጥ አንዳች ነገር ሲገላበጥ ተሰማኝ ። ጥውልውል አደረገኝ። እንደፈለገች ስታደርገኝ እስክትጨርስ አይኔን ጨፍኜ መዝለቁ ከባድ የሚሆንበት ግዜ ላይ ደረስኩኝ።አይኔን ገለጥኩ። እላዬ ላይ የምትጨፍረውን ሴት ሽቅብ ተመለከትኳት ። እራሷ ነች ። ፀጉሯ ፍቷን ሸፍኗት ቁልቁል ይዘናፈላል አቤት ውበት! አቤት ጭንቀት! ወርዳ ተዘረረች ። በተኛችበት ጥያት ልጠፋ አሰብኩ። አሰብኩ እንጂ አላደረኩትም ነጋ ተነስቼ ቁርስ ሳልበላ ወደ ዋሻዬ ወደ ጫካ ሄድኩ ከራሴ ጋር ስማከር ከራሴ ጋር ስከራከር ከራሴ ጋር ስጣላ ቀኑ ተጋመሰ።

ወደ ቤት ተመለስኩ በጥዋት ተነስቼ መጥፋቴ አስቆጣት። ዝምታዬ አስጨነቃት " ምን ሆነሀል? እያለች በተደጋጋሚ ብትጠይቀይኝ መልሴ ምንም ብቻ ነበር። ሁለት የምጥ ቀናት አለፍ
ባፈቀርኳት የመጀመሪያው የፍቅር ሂይወቴ ላይ የተጫወተችውን ፍቅሬን በንጭጩ አምክና ልቤን የሰበረችውን ይቺን ሴት ማንነቷን አጋልጬ በኖረችበት መንደር ላሸማቅቃት ወስኜ ነበር ከጫካ የተመለስኩት። ያን ካደረኩ ቡሀላ ስፍራውን ለቅቄ እግሬ ወደወሰደኝ ልሰደድ ዝግጅቴን አጠናቀኩ።
እንደተለመደው በመጀመሪያው ቀን ያልተሰጠኝ ጠላ በሁለተኛው ቀን ማታ ልተኛ ስል ጠብቃ ሰጠችኝ። ሳታየኝ ደፋቼው ተጠቅልዬ ተኛሁ። እኩለ ለሊት እንዳለፈ ልክ እንደከትናንት ወድያው ጅቦቹ የጥሪ ድምፅ አሰሙ ቤቷን ከበው በጩኸት አነቃነቋት። ብድግ አለች አይኔን ገለጥኩ ። ተነስታ ወረደች ። ወደ ሚቀጥለው ክፍል ስትሄድ ተነሳሁና ተደብቄ ማየት ጀመርኩ። ቅጠሏን በልታ እየለፈለፈች የራስ ቅሏን ከቅንድቧ በላይ እንደ ጀሪካን ክዳን ከፍታ ፀጉሯን ጠቅለል አደረገችና መሶብ ወርቋ ውስጥ አስቀምጣ ወጣች ።

ውስጤ ፍርሀት የሚባል ነገር ሳይሰማኝ ፈጠን ብዬ ፋኖሱን አጠፋሀትና የቤቷን መስኮት በትንሹ ከፍቼ ወደ ውጪ ተመለከትኩ ከ ስድስት በላይ የሚሆኑ ነጭና ጥቁር መልክ ያላቸው ጅቦች ግቢው ውስጥ ተመለከትኩ ። እንደወጣች አንደኛው ጅብ ጀርባ ላይ ቂብ አለች ።

እየጋለበችው ቤቱን ሶስት ግዜ ከዞረች ቡሀላ ከወገቡ ላይ ስትወርድ ባለ ሁለት እግሯ ሴት ባለ አራት እግር ጅብ ሆነች። አይኔን ማመን አቃተኝ ጠፍቶ የነበረው ፍርሀቴ መልሶ ተቆጣጠረኝ።

እሷ ፊት ፊት ሌሎቹ ከጀርባ እየተከተሏት የስሪያ ድምፅ እያሰሙ ከግቢው ወጥተው ተፈተለኩ። እቤት ውስጥ ጥቁር ፌስታል ፈልጌ እንዳገኘሁ ቀጥታ ወደ መሶብ ወርቁ ሄጄ አይኔን ጨፍኜ ውስጥ ያስቀመጠችውን እንደኮፍያ የሚመስል የራስ ቅል ከነ ፀጉሩ አውጥቼ ፌስታሉ ውስጥ ከተትኩት ።
በሩን ከውጪ ስለዘጋችው ይዤው በመስኮት ወጣሁ ። ግቢ ውስጥ ወዳለው ማድ ቤት ገብቼ በፌስታል የያዝኩትን እዛው ማድ ቤት ውስጥ ጥግ ላይ ካለ አንድ ማዳበሪያ ውስጥ ደብቄ ቀድሜ ማድ ቤት ያስቀመጥኩትን መሳሪያዬን ይዤ ቁጭ አልኩ። ፍቅሯን ከነሰንኮፉ ከውስጤ ነቅዬ ለመጣል መጨረሻዋን ለማየት ቁጭ ብልም የተፈጠረው ያልጠበኩት ነበርና ክፉኛ አስደነገጠኝ ።

እንደመጣች ። ገብቷ ፀጉሯን እና እኔን ከነበርንበት ስታጣን በሯን ዘግታ እሪታዋን አቀለጠችው "እርርርይ ጉድ ሆኛለሁ እርርርይ ያዙልኝ እንዳያመልጥ እርርርይ !" በዛ በውድቅት ለሊት መንደሯን በጩኸት አናወጠቻት።

የመንደሩ ሰው ዱላ ያለው ድላውን መሳሪያ ያለው መሳሪያውን እየያዘ ግቢውን ወረረው ተጠግተው "ምን ሆነሻል ? ምን ተፈጠረ?" እያሉ በሩን ሊከፍቱ ሲሞክሩ እንደዛ ሆና እንዳይመለከቷት "በሬን እንዳትትነኩ ! እንዳትገነጥሉ ! ይልቅ ሂዱና ሰውየውን ካለበት ይዛችሁ አምጥሉኝ " ትላለች ዘመዷ ነው መሰለኝ ሁኔታው ገብቶት ይሁን አይሁን ባላውቅም በሯ ላይ ቆሞ በሩ እንዳይከፈት መከላከል ጀመረ ።
የተወሰኑ ሰዎች እኔን መፈለግ ጀመሩ ። አማራጭ ስላልነበረኝ መሳሪያዬን አቀባብዬ አንድ ሰው እንዳይጠጋኝ እያልኩ ከተደበቅሁበት ማድ ቤት ወጣሁ።

ድርጊቴ የማልወጣው ወጥመድ ውስጥ እንደከተትኝ የተረዳሁት እርርርይ ስትል ሰምቶ የተሰበበሰበው የመንደሩ ነዋሪ በሷ ማንነት ከመደነቅ ይልቅ ለኔ ህይወት ማዘናቸውን ሲገልፁልኝ ነው ። ግራ ገባኝ ፍርሀት መላ እኔነቴን እየናጠው ምንም አታረገኝም እኔ ለሷ አንሼ ነው ጭራሽ ለኔ የምታዝኑት እያልኩ ስጮህ
አንድ ፊቱን ስመለከተው ያዘነልኝ የሚመስል ሰው ጠጋ አለኝና •••

" እስቲ ና ወዳጄ ምን አይነት የማትወጣው ጉዱ ውስጥ እራስህን እንዳስገባህ የገባህ አልመሰለኝም ይልቅ ድምፅህን አጥፋና ፀጉሯን የት እንደደበከው ተናግረህ የምታመልጥበትን መንገድ ፈልግ።

ባንተ ቤት ስለነሱ መንደሩ የማያውቅ መስሎህ ጉዳቸውን አጋልጠህ በድንጋይ ተወግሯ የምትሞት መስሎህ ከሆነ ተሳስተሀል ወዳጄ እዚህ መንደር ውስጥ ዘር ማንዘሮቿ እንዳለ እኮ እንደዛ ናቸው ሰፈሩን ጥለህ ካልጠፋህ ከልብስህ በስተቀር ለቀብር እንኳን የሚተርፍ ነገር እንዳይኖርህ በጫጭቀው ደብዛህን ያጠፍቷል!

እየውልህ ቀስ ብለህ ወደዛ ተመልከት እነዛ እዛጋ አይናቸው ደም እንደለበሰ የቆሙት ሶ
👍2
ስት ሰዋች ሁሉም የሷ ዘሮችና እንደሷ ናቸው። እዛ ጋ ያሉት ሁለት አክስቶቿም እንደሷ ናቸው! እናቷም ያው ነች። እንዴት አድርገህ ነው ከነሱ መንጋግ የምትተርፈው! እኔ ያዘንኩት ለሷ ሳይሆን ላንተ ነው ሲለኝ ብርክ የዘኝ መሞት ካልቀረ አሟሟትም ይለመናልና የነሱ መጫወቻ ከምሆን የቆምኩባት ምድር ተከፍታ እንድትውጠኝ ለመንኳት አሁን ያከባቢው ሚንሻዎችም ስላሉ ምንም አያደርጉህም መኖር ከፈለክ እዚህ ቆመህ መነታረክህን ተውና ቀኑ ሳይጨልምብህ አሁኑኑ ርቀህ ጥፋ። አምልጥ!" አለኝ።ለዚህ ሰው ፀጉሯ ያለበትን ነግሬው አውጥቶ እንደሰጣቸው እንዳላመልጥ ከጀርባዬ የቆሙት ሰዎች ገለል አሉ።

መንደሩን ጥዬ ጠፋሁ። በሩጫም በርምጃም ሚዳ ተራራውን እያቋረጥኩ ቀኑን ሙሉ ተጉዤ ። ዛፍ ላይ ወጥቼ ለመተኛት ጫካ እስካገኝ ስጓዝ ለሊቱ ተጋመሰ ጫካው ሳይገኝ አጉል ቦታ ላይ! አውላላ ሜዳ ላይ! ከርቀት ድምፅ ሰምቼ ዘወር ስል ጥቁርና ነጭ መልክ ያላቸው አይናቸው የሚያበራ ከአምስት በላይ የሚሆኑ ጅቦች በከባድ ፍጥነት እየጮሁ ወደኔ አቅጣጫ ሲመጡ ተመለከትኩ መሮጥ ብፈልግም እግሬ አልላወስ አለኝ•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ባዶ_ድስት

ሌሊቱ ይነጉዳል!
እሳቱ ይነዳል ..
አልቦዘነም ጣቴ
ጊዜ እና ጭራሮን አፍሶ ይማግዳል
ባዶ ድስቴን ልጣድ ባዶ ለማገንፈል
ከንፍገት ይሻላል ዕጦትን ማካፈል፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#የመጻተኛው_አገር

አገር ድንኳን ትኹን
ጠቅልዬ የማዝላት
ስገፋ እንድነቅላት
ስረጋ እንድተክላት

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_አራት(የመጨረሻ ክፍል)


#በጥላሁን

ዛፍ ላይ ወጥቼ ለመተኛት ጫካ እስካገኝ ስጓዝ ለሊቱ ተጋመሰ ጫካው ሳይገኝ አጉል ቦታ ላይ አውላላ ሜዳ ላይ ከርቀት ድምፅ ሰምቼ ዘወር ስል ጥቁርና ነጭ መልክ ያላቸው አይናቸው የሚያበራ ከአምስት በላይ የሚሆኑ ጅቦች በከባድ ፍጥነት እየጮሁ ወደኔ አቅጣጫ ሲመጡ ተመለከትኩ መሮጥ ብፈልግም እግሬ አልላወስ አለኝ•••

በዛች በመጨረሻዋ የጭንቀትና የሞት ሽረት ሰአት እራሴን ማረጋግትና የቻልኩትን በሙሉ ማድረግ እንዳለብኝ ለማሰብ ግዜ አላጠፋሁም።
እየቀረቡ ሲመጡ እኔን ፍለጋ እንደመጡ ከሁኔታቸው እርግጠኛ ሆንኩ። ወደ ላይ ቀና ብዬ ፈጣሪዬን ለመለመን ብፈልግም በሰው ነፍስ : በሰው ደም የጎደፈውን ማንነቴን አስቤ ፀሎት እና ልመናዬ የመጀመሪያውን ሰማይ የማይሻገር መስሎ ተሰማኝ ቢሆንም ጨንቆኛልና ፈጣሪዬ እንዲረዳኝ ለመንኩት።

ሮጬ እንደማላመልጥ ስለገባኝ ለመሮጥ አልሞከርኩም። ከጀርባዬ ላይ ያጋደምኩትን መሳሪያ አውርጄ በማቀባበል በተጠንቀቅ ቆምኩ። ብዙ አመት ጫካ ኖሪያለሁ ጅቦች በባህሪያቸው መሬት ሳይጥሉ እንደማይበሉኝ አውቃለሁ። ላለመውደቅ የቻልኩትን አደርጋለሁ በዚህ መሀል የመሳሪያውን ድምፅ ሰምቶ የሚደርስልኝ አላጣም።

ከኔ በቅርብ ርቀት ላይ እንደደረሱ ቆሙ አንደኛው ወጣ አላና ከሁሉም ፊት ቆመ ይቺ የኔዋ ትሆን እንዴ አልኩ። ከፊት የቆመው ጅብ የሆነ ለየት ያለ ድምፅ ሲያወጣ ባንድ ላይ የነበሩት ስድስት ጅቦች ብትንትን ብለው ከበቡኝ።
ሁለቱ ከጀርባዬ ሁለቱ ከፊቴ አንዱ በስተግራዬ አንዱ ደግሞ በስተቀኜ ሆነው ከኔ በተመሳሳይ ርቀት ላይ ቆሙ።
ይህን ተንኮላቸውን ስመለከት "የሰው ጅብ እንደሰው ያስብ ይሆን እንዴ አልኩ ደንግጬ።

ለማመን በሚያስቸግር ሁኔታ ግራና ቀኝ ያሉት ከቆሙበት ሳይንቀሳቀሱ ከፊቴ እና ከጀርባዬ ያሉት በተመሳይ ግዜና ፍጥነት ወደኔ ሲወረወሩ እንኳን አልሞ ለመተኮስ ለማሰብ እንኳን ግዜ አላገኘሁም።
በንፋስ ፍጥነት ታከውኝ ሲተላለፉ ተንገዳግጄ ቆምኩ። አስደንግጠው ሊጥሉኝ ማሰባቸው ገባኝ። ወድያው በነዚህኛቹ ክው ያለውን ቀልቤን ሳላረጋጋ በስተግራና በስተቀኝ ያሉት በተራቸው ወደኔ ተምዘገዘጉ። በደመነፍስ ዝም ብዬ በስተቀኝ በኩል ወደ መጣው ፊቴን አዙሬ መተኮስ ጀመርኩ ሁለቴ እንደተኮስኩ በስተግራ የነበረው ደርሶ ገፍትሮኝ አለፈ አይወድቁ አወዳደቅ ወደኩ ተንደባለልኩ መሳሪያዬም ከጄ ወጣ ከመቅስፈት በወደኩበት ከበቡኝ ። ሁለቱ አልተጠጉኝም።

እሷ የትኛዋ እንደሆነች ባላውቅም አራቱ ዙርያዬን ከበው ቁልቁል ሲመለከቱኝ ነብስ ያዘኝ።ተስፋ ቆረጥኩ።
መግደል ምድራዊ ታሪኬን መደምደም በምትችልባት ቅስፅበት በዛች ውድቅት ለሊት እስትንፋሴን መቋጨት ስትችል እስከምሞት በስቃይ እንድኖር ስለፈለገች ነው መሰለኝ ሁለቱ ግራና ቀኝ እግሬን እያሰቃዩ ዘንጥለው ይዘው ሄዱ ።
አንዱ ግራ እጄን ገንጥሎ እንደሄደ። አንደኛው ግን ብዙም አጥብቆ ያልነከሰውን ቀኝ እጄ ተወልኝ።
እራሴን ከመሳቴ ከሰከንዶች በፊት ሁሉም ጅቦች ወደ መጡበት ሲመለሱ ቀኝ እጄን የተወልኝ ጅብ ተለይቶ በመቅረት ፊት ለፊቴ ቆሞ ሲመለከተኝ ትዝ ይለኛል ምናልባት እሷ ትሆናለች።
ከዛ ቡሀላ ከተማ ወጥተው መንገድ የመሸባቸ ገበሬዎች አግኝተውኝ የሚፈሰውን ደሜን አስረው እቤታቸው እንዳሳደሩኝና በአከባቢው ከነበረ ከአንድ የሀብታም ገበሬ የህል መጋዘን ውስጥ እህል ሊጭን ለመጣ የአይሱዙ ሹፌር ሁኔታውን ነግረው ወደዚህ ይዞኝ እንዲመጣ እንዳደረጉና ሆስፒታል አድርሶኝ እንደሄደ ወደ ራሴ ስመለስ ያገኘኋቸው ዶክተሮች ነገሩኝ ።

ከዛን ግዜ ጀምሮ ለነብሱ ባደረ አንድ ደግ ሰው በተሰጠችኝ በዚች ነገር እየተንቀሳቀስኩ እድሜዬን በልመና አሳለፍኩ።

ለምኜ ሳንቲም የምቀበልባትን
ቆርሼ የምጎርስባትን መቀመጫዬን የምገፋባትን እቺን እጄን ባትተውልኝ እንዴት እሆን ነበር እላለሁ አንዳንዴ።
ዛሬም እዛው የተለመደው ቦታዬ ላይ ስለምን አገኛችሁኝ። ከልመና ያውጣችሁ ልጆቼ ።

ከኔ ታሪክ ከተማራችሁ•••
መርጣችሁ ስሙ ልጆቼ !። መርጣችሁ እሺ በሉ!።
አሉ ፍለፍታቸው የተቀመጥነው እኔ እና እህቴ ፍታችን በእንባ ታጥቧል
ይህን ታሪክ ያጫወቱን ነገ በምንዘክረው የአባታችን ሰባተኛ ሙት አመት ወይም ተስካር ላይ እናቴ የኔቢጤዋችን ብቻ ለማብላት በመወሰኗ ከዛሬ ከዋዜማው ጀምረን እኔ እና እህቴ አዲስ አበባ ውስጥ በየቦታው የወደቁ የኔቢጤዋችን ወደ ቤት ይዘን እንድንመጣ ስላዘዘችን ። አቅማችን የፈቀደውን ያህል የኔቢጤዋች ወደ ሰፊው የመኖሩያችን ግቢ ስናመጣ መሀል ሚክሲኮ አከባቢ ዊልቸር ላይ ተቀምጠው ሲለምኑ ያገኘናቸው ሁለት እግርና አንድ እጅ የለላቸው እድሚያቸው ወደ ሰማንያዎቹ የሚጠጋ ጋሽ ፍልፍሉ ናቸው ።

ፈጣሪ እሄን ታሪክ ለኛ መማሪያ ይሆን ዘንድ እስኪነግሩን ያቆያቸው ይመስል እኔና ታናሽ እህቴ በአባ ፍልፍሉ ታሪክ ልባችንን እንዳዘነ እምባችንን ከፊታችን ላይ ጠራርገን ከጠላውም ከምግቡም ግቢ ውስጥ ላሉት የኔ ብጤዋች አባ ፍልፈሉን ጨምር ስናበላ ስናጠጣ አምሽተን ወደ ቤት ገባን ይህ በሆነ ከሰአታት ቡሀላ ከምሽቱ አምስት ሰአት ላይ ጠላ እየጠጡ በመሀል ትን አላቸው አባባ ፍልፍሉን ።

ትንታቸው እየባሰ ሲርርርር ሲርር ሲሉ አጠገባቸው የነበረ ሌላ የኔብጤ "ኧረ የሰው ያለህ " ጮኸ እኔና እህቴን ጨምሮ እቤት ውስጥ የነበርነው ተሯሩጠን አጠገባቸው ስንደርስ አባባ ፍልፈሉ እንዲህ አሉ •••

" ጠላው አይደለም ትን ያለኝ ልጆቼ እሷ ነች ያነቀችኝ ! አልተርፍም ልጆቼ! አልተርፍም ! ያልኳችሁን አትርሱ
ከኔ ታሪክ ከተማራችሁ•••
መርጣችሁ ስሙ ልጆቼ! መርጣችሁ እሺ በሉ!!።
አባቴን ከምሰማ እናቴን ሰምቻት ቢሆን ይሻለኝ ነበር!"
የአባ ፍልፈሉ የመጨረሻ እስትንፋሳቸው ንግግር።

💫ተፈፀመ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
ይድረሥ ለሰሜንዋ መከረኛ እናቴ
ልክያለሁ ሰላምታ ፡ ዝቅ ብዬ ካንገቴ ።
...
ምንም እንኳን እኔ
ሁኜ ባልገኝም
እንዳብራክ ልጆችሽ ፡ያካላትሽ ክፋይ
ምንም እንኳን እኔ
ሁኜ ባልገኝም
ፊትሽ ተቀምጬ ፡ዓይን ዓይንሽን የማይ፡
ይህን ግን አልክድም ፡
መልክሽን እንደማውቅ ፡በ'ናቴ መልክ ላይ

🔘ኤፍሬም ሥዩም🔘
#ፍጻሜ_ዓለም

ያዳም ልጆች ክፋት
በዝቶ ሲያስጨንቃት
ልክ እንደ ቅሪላ አብጣ አብጣ ሲበቃት
ፈንድታ ታርፋለች ብለን ስንጠበቃት
ዓለም አለሁ ብላ እኛን አዘናግታ
እንደ አንኳር በረዶ
አለቀች ቀስ በቀስ
እጃችን ላይ ሟሙታ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ምንቸት_እና_ጋን

ይኑሩ እንጂ ባገር
በቀዬ በሰፈር
ኩሬ ሙሉ ውኃ፣ ምድጃ ሙሉ ሳት
ዳውላ ሙሉ አፈር
የምንቸቶች ሰፍር መች በጋን ይለካል
ጋኖች እንኳ ቢያልቁ ሌላ ኣፈር ይቦካል፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#የአንድ_አፈር_አፈሮች

ፍቅራችንን ድንበር ወሰን ላይገድበው፥
ሁለት ክልል ላይመጥነው፥
መገዳደል ፍትህ ላይሆነው፥
በሽንፈትህ እሰይ ላልል፥
በሽንፈቴ እፎይ ላትል፥
ከቂም በቀር ፍቅር ላይበቅል፥
ልጅህ በእጄ ለምን ይሙት?
ልጄስ በእጅህ ለምን ትሙት?
እኔና አንተኮ የአንድ እናት ልጆች፥
ወንድማማቾች፥
የአንድ አፈር አፈሮች፥
ርስት አፈሩማ ይቅርም ከወደዚ ይሂድም ወደዚያ፥
ያውነው የኢትዮጵያ አንድ አፈር መጠሪያ፥
ወዲያ ካለው የቀድሞዋ፥
ወዲህ ካለው የስካሁንዋ፥
ግዳይ ጥዬ በልጅህ ደም በጀግንነት ላልጠራ፥
ግዳይ ጥለህ በልጄ ደም ላትፎክር ላታቅራራ፥
ወንድም ገድለው ላይፎክሩ፥
ጀብዱ ሰርተው ላይኩራሩ፥
የሀዘን ሙሾ ልዘምሩ፥
እንደ ማህተብ የእምነት ክር ፍቅር ድሩ ላይበጠስ፥
በሀዘናችን ላትዘፍኑ በሞታቹ ላንደንስ፥
ስውር አይሁን ነጭ ሴራው ደስ አይበለው የጠላት ነብስ፥
ልጅህ አይሙት በልጄ ጣት፥
ልጄም አይሙት በልጅህ ቀስት፥
እኔና አንተኮ ከዘመናት በፊት፥
በታሪክ በሀይማኖት፥
በባህል በትውፊት፥
በደስታ በችግር፥
ስም የሌሽ ስመጥር፥
በጋሻና በጦር፥
ጀብደኛ ባላገር፥
የአንድ አያቶች ዘር፥
የሁለት አፈር ሰፈር፥
ስምየለሽ በጥጋብ፥
ስመጥር በረሀብ፥
እያሉ ሲተቹህ እያሉ ሲተቹን፥
በሙጫ ስድብ አጣብቀውን፥
ሲተቹህ መተቸት ሲተቹን መተቸት፥
እንዳለ ስናውቀው እንዳለ ስታውቁት፥
በአንድ እናት ተወልደን፥
በሁለት አባት አድገን፥
አንድ ውሀ ተራጭተን፥
አንድ አፈር አቡክተን፥
ቃታ ስንሳሳብ እሺ ላይለው ልብህ ደስ ላይለው ልቤን፥
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን?
እኔና አንተኮ የአንድ እናት ልጆች፥
ወንድምና እህቶች፥
የአንድ አፈር አፈሮች፥
እናም ወንድም ስማኝ ልስማህ
ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከእኔ ፀብ ሲያቃባ፥
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ፥
በሞትህ ደስ ላይለኝ ወስጥ ልቤ እዥ ሊያነባ፥
የእናቱን ልጅ ልጄ ገድሎ ላያሰማ ጉሮወሸባ፥
ፍቅር እንጂ ግድባችን ወሰን አይኑር የደም ካባ፥
ይልቅስ ልንገርህ፥
ኩራቴ ኩራትህ፥
ታሪኬ ታሪክህ፥
የሚያመፃድቀኝ የሚያመፃድቅህ፥
የኔም የአባቴ ነው ያንተም የአባትህ፥
ከቢዘን ባስቀድስ፥
ከግሸን ብትሰልስ፥
ባክሱም ብትኮራ፥
ብሸልል ባስመራ፥
ያንተአባት አባቴ፥
አባቴ አባትህ፥
የሚያመፃድቀኝ የሚያመፃድቅህ፥
ታሪኬ ታሪክህ፥
መሆኑን ስናውቀው መሆኑን ስታውቁት፥
በደምና ባጥንት፥
በስጋ በጅማት፥
በታሪክ በትውፊት፥
መንታ ናቸው ሲሉን፥
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን?
በብቀላ ፀፀት በቀር፥
ወንድም ጥሎ ላይፎክር፥
ጀግና ተብሎ ሜዳይ ላይኖር፥
በእናቴ ልጅ በመጨከን እሺ ላይለኝ የልቤ በር፥
ወንድ ልጄን ግዳይ ጥለህ ላይፈታ የደምህ ስር፥
ካንድ ደብር አድገን፥
በአንድ አስቀድሰን፥
አንድ ዳዊት ደግመን፥
ካንድ መስጊድ ኖረን፥
በአንድ ሰላት አድገን፥
አንድ ቁርአን ቀርተን፥
እኮ እንዴት እኔና አንተ ዛሬ እንዲህ እንጫከን?
ለጉዳትህ ተሰውቼ፥
ላንተክብር ብዙ ሞቼ፥
ስላንተ ነፃነት ካገርህ ደሜ አለ፥
በናቅፋ ተራሮች እቅፍ የታዘለ፥
መጎዳቴን እምቢ ብለህ፥
ስለክብሬ ተሰውተህ፥
የሰጠህኝ ክቡር ደምህ፥
ያንተም አጽም አድዋ አለ፥
ለኢትዮጵያ ነፃነት ስለኔ የዋለ፥
መንታ ናቸው ሲሉን፥
ፍቅር ናቸው ሲሉን:
እያወቁት ልቦናችን፥
ሁለት ክልል ላይመጥነን፥
ድንበር ወሰን ላይገድበን፥
መገዳደል ፍትህ ላይሆነን፥
በሽንፈትህ ስንዘምር በለው ያሉህ ሊታዘቡን፥
ነጭ ሴራ ወጣው ሊሉን፥
ስጋ ክንድህ ሲደማብህ፥
ልቦናችን ሊያዝንብን፥
በአለም ዜና ድላችንን ደምጥማት ነው ብለው ሊሉን፥
ልጅህ በጄ ለምን ይሙት?
ልጄም በእጅህ ለምን ትሙት?
ስማኝ ወገን ደስ አይበለው ነገር ሰሪ አንተን ከኔ ፀብ ሲያቃባ፥
ስውር አይሁን ነጭ ሴራው የሸረበው የሞት ደባ፥
እንዘምር ባንድ እንዝለል ወሰን አይኑር የደም ካባ፥
እናም በሞቱት ሞት፥
እኔና አንተ አንሙት፥
እኔና አንተማ የአንድ እናት ልጆች፥
የአንድ አፈር አፈሮች፡፡

🔘ኤፍሬም ስዩም🔘
#እህቴን_ሸጥናት!!


#ክፍል_አንድ


#በጥላሁን

ወደ ሀዋሳ ለመሄድ ያኮበኮበው ሚኒባስ ሞጆ መስቀለኛ ላይ ቆሟል።
ጋቢና ሁለት ወጣት ሴቶች ተቀምጠዋል ከጋቢና ጀርባ ባለው ወንበር ላይ እድሚያቸው ገፋ ያለ ባልና ሚስቶች ሲቀመጡ•••

መሀለኛው ወንበር ላይ የ 18 አመት ልደቷን ካከበረች ከሶስት አመት ብዙ ያልተሻገረች ።
ከልጅነት ወደ አቅመ ሂዋንነት ገብታ ያላበቃች ። ለመላ አካላቷ ከፈጣሪ የተቸራት ውበት ተገልጦ ያላለቀ በመሆኑ ከእለት ወደ እለት ወገባ እየቀጠነ ዳሌዋ እንደፅጌሬዳ አበባ እየፈነዳ እንኳን ወጣት ወንድ ስድስት ልጅ የወለደ ሽማግሌ ባጠገቧ ካለፈ ቡሀላ አንገቱን ጠምዝዞ ዞሮ ደግሞ ደጋግሞ ለማየት የሚያስቆመው ምንም አይነት ሀይል እንዳይኖር የሚያስገድ ምትሀታዊ የውበት ሀይል ተላብሷል ይህ ውብ ዳሌዋ በተመጠነ ርቀት ግራና ቀኝ ሲንገጫገጭ አገጩ አብሮ የማይንገጫገጭ ወንድ በፀሀይም በባትሪም ተፈልጎ አይገኝም።

አይን ውስጥ ለመግባት ተቸግረው የኖሩት ጡቶቿ ዳርና ዳር ተቀባብለው ሲታዩ እይታን የሚፈትን ህቡእ ጨረር ይተፉ ይመስል ድንገት ያያቸው ወንድ ሁሉ•••
ልቡ ስንጥቅ አፎቹ ሳያስቡት ሙልት በምራቅ እስከዛሬ ከነበሩት ምራቆች እሷን እንዳየ አፉ ውስጥ የመነጨው ይህ ምራቅ ብሎት ጥፍጥ አጣጥሞ የማይውጥ ወንድ ማግኘት አይቻልም ባይባልም ይከብዳል ። ፀጉሯን አንዴ ወደ ምስራቅ አንዴ ወደ ምእራብ እየበተነች በውብ ጥርሶቿ ፍልቅልቅ ስትል እንኳን ያያት ወንድና ሴት እራሷንም ሳያስደነግጣት አይቀርም።

የጠየቃት የለም እንጂ ስለውበቷ ምን እንደሚሰማት የጠየቃት ቢኖር እሷ እራሷ የቁም መስታወት ፊት ለፊት ቆማ የራሷን ውበት ስትመለከት ያ ሁሉ የውበት ዝናብ እሷ ላይ መርከፍረፉን ማመን እየተሳናት መስታወት ውስጥ ያየችውን እይታዋን ለማረጋገጥ በእጆቿ ከላይ ወደታች •••
በመጀመሪያ አይኖቿን ነካ •••ዝቅ ትልና ከንፈሮቿን በሁለት ጣቶቿ ከፈት •••አንገቷን ዳበስ••• ቀልቁል ወርዳ ጡቶቿን ያዝ ለቀቅ••• ደሞ ወደ ታች ፈቀቅ ዳሌዋን ነቅነቅ••• በጣቶቻ ጨበጥ ጨመቅ እያደረገች መስታወት ውስጥ ያየችው ውበት በአካል እሷ ላይ መኖሩን ሳታረጋግጥ እንደማትተኛ ትነግረው ነበር።

ይቺ ልእልት ነች እንግዲህ ወደ ሀዋሳ ለመሄድ ሰው እስኪሞላ በሚጠባበቀው ሚኒባስ ውስጥ መሀለኛው ወንበር ላይ ብቿዋን የተቀመጠችው።
ረዳቱ ሚኒባሱ ሞልቶ እስከሚሄድ የቸኮለ ይመስላል ለሰከንዶች ሳያርፍ ይጣራል (ዝዋይ -ሻሸመኔ-ሀዋሳ የሞላ ነይ እሙዬ ሀዋሳ ግቢ ሞልቷል! አንዲት ቀጭን ጠቆር ያለች ሴት ገብታ የመጨረሻ ወንበር ጥግ ላይ እንደተቀመጠች ወድያው ሌሎች ሁለት ወንድ እና አንድ ሴት ባንድ ላይ መጥተው ተከታትለው ገቡ ።

ወንድ ቆንጂየዋን ልጅ ገና በመስታወት ውስጥ እንዳያት ነበር የደነገጠው አጠገቧ መቀመጥ ፈለገ ወደ ጫፍ ጠጋ አለች። ሆን ብሎ እየታከካት አልፎ ጥግ ላይ ተቀመጠ ።
ረዳቱ መጮሁን ቀጥሏል ። ከናዝሬት ወደ አዲስ አበባ የሚሄድ ዶልፊን እየተክለፈለፈ መጣና ቆሞ ሰው እሚጭነው ሚኒባስ አጠገብ እንደደረሰ ቆመ።

ሁለት ሴቶች ወረዱ ቀደም ብላ የወጣችው ሽቲ የለበሰች አይኗ ጎላ ጎላ ያለ መካከለኛ ቁመትና ውፍረት ያላት ሴት ስትሆን በቀኝ ጉንጯ የጫት ተርዚና እንደወጠረች ተከትላት ከወረደችው በዛ ያለ ጫት ከያዘች ጓደኛዋ ጋር መንገድ ላይ የጀመረችውን ወሬ እያወራችላት እና እየተሳሳቁ ወደ ሀዋሳ የሚሄደው ሚኒባስ ውስጥ ተያይዘው ገቡ ጫት የምትቅመው በፀጥታ የተሞላውን የዚህኛውን ሚኒባስ ድባብ ለመቀየር የፈጀባት ግዜ ተደላድላ እስክትቀመጥና አፏ ውስጥ ያለውን በውሃ ሉሉ አድርጋው ሌላ ጫት ቀንጥሳ እስክትጎርስ ብቻ ነበር።

"እዚህ ሚኒባስ ውስጥ የሚቅም ካለ ራብሳ መጠየቅ ይችላል ጫታችን ብዙ ነው !" አለች ሁሉም ወደሷ ተመለከቱና ተሳሳቁ። አብራት የመጣችው ሴት ረዳቱ በትርፍ ያስቀመጣት ቦታ አልመች ብሏት እየተቁነጠነጠች "ኧረ አንቺ ዝም በይ " የሚል መልክት በምልክት ስታሳያት
"ምን ችግር አለው የኛ ህዝብ ይሉኝታ ያጠቃዋል ጫቱን ሲያየው ለመቃም ተወስውሶ ፈርቶ ዝም ያለ አይጠፋም ብዬኮነው" ከማለቷ
"ልክ ብለሻል እንቅማለን ራብሽና ራብሽን " አሉ ከሴቷ ጋር የመጡት ሁለት ወጣት ወንዶች ። ባለጫቷ ፈጠን ብላ " እሄንን ነውኮ ያልኩት በሉ እንኩ" ብላ ስትሰጣቸው ሚኒባሱ ውስጥ ያልሳቀ ቢኖር ከሹፌሩ ጀርባ የተቀመጡት በድሜ ገፋ ያሉ ባልኖ ሚስቶችና በትርፍ ገብቶው አጠገባቸው ተንጠልጥለው የተቀመጡት ሙሉ ሽበት የወረሳቸው የድሜ ባለ ፀጋ አዛውንት ብቻ ናቸው። አዛውንቱ ሰውዬ ጫት የምትቅመውን ሴት ገልመጥ አደረጓት።

ፀጥ ብሎ የነበረው ሚኒባስ ተሟሟቀ ጫወታው ደራ ። ረዳቱ ገብቶ በር ዘጋ ሹፌሩ ቀበቶውን አስሮ ሞተር እንዳስነሳ ። አንድ ነጭ ላንድክሩዘር መኪና እያሽከረከረ የመጣ ፈረንጅ ወደ ሚኒባሱ እየተጠጋ እጁን በማውጣ ያዘው አትሂድ የሚል ምልክት ለሹፌሩ ስላሳየው ግራ በመጋባት ነዳጁ ላይ ያለውን እግሩን ሳይጫን ጠበቀው ።
ፈረንጅ በፕላስቲክ መሰል ማሸጊያ የያዘውን ኢንጆሪ ይዞ በሚኒባሱ በር በኩል ሲመጣ የሚኒባሱ ረዳት በሩን ከፈተው። ከወጣትነት ወደ ጉልምስና ሊሸጋገር ድንበር ላይ የደረሰው መልከመልካም ፈረንጅ ጠጋ አለና ኢንጆሪውን በሁለት እጆቹ ይዞ ሚኒባሱ ውስጥ መሀለኛው ወንበር ላይ ወደተቀመጠችው ቆንጆ ሴት በመዘርጋት " ካን ዩ አክሴፕት ማይ ጊፍት ፕሪቲ ገርል ፕሊስ!" ልጅታ እጃን ዘርግታ ከመቀበል ተቆጠበች ሁሉም ግራ ተጋባ ። ጥያቄውን ደገመው ልጅቷ አሁንም እጇን አልዘረጋችም አልተቀበለችውም።
እሄን ግዜ " ታውቂዋለሽ የኔ ልጅ?" አሉ ሽበታሙ አዛውንት " ኧረ አላውቀውም እኔም ከናንተው ጋር አሁን ገና ነው ያየሁት" አለች
" እንዴ ባታውቂውስ ፈረንጅ እኮ ነው ይልቅ በጥዋት ያለሽበት ድረስ ሰተት ብሎ የመጣውን አሜሪካ ወደ ምትባል ገነት ወደሆነች ሀገር መግቢያ ቁልፍ የያዘ ሪስቅ አትግፊ ተቀበይው እዚ እንደሰርዲን ሚኒባስ ውስጥ ታጭቆ መሄድ አልሰለቸሽም እንዴ ይልቅ ተቀበይውና ወርደሽ መኪናው ውስጥ ግቢ እሄ እድል አያማጥሽ!" አለች የምትቅመዋ ሴት

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍5
#የውበት_ጀርባው

አንተ እሚታይህ፣ የሚያምር ፈገግታ
ያበባ ጉትቻ
ላንተ እሚታይህ፣ ውብ ገጽታ ብቻ።

ጥርሷን ጉራማይሌ፣ የተነቀሰች ቀን
ያየቺው መከራ፣ ያየቺው ሰቀቀን
የጆሮዋን ጫፉን፣ በሾህ ስትበሳ
የበላችው ፍዳ፣ ያየቺው አሰሳ
የዋጠችው ሕመም፣ ከሬት የመረረ
የቀመሰው ማነው፣ ከሷ በስተቀረ?

አያንዳንዱ ታላቅ ውበት በስተጀርባ
ሲንዠቀዠቅ ኑሯል፣ ብዙ ደምና እንባ።

ይሄም ታላቅ ዜማ
ይሄም ታላቅ ሥዕል
ይሄም ታላቅ ተረት
ይሄም ታላቅ ድርሰት
ከፊትህ አልቆመም፣ እንደ መና ወርዶ
ሥቃይ ያቃልላል፣ ከሥቃይ ተወልዶ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#እህቴን_ሸጥናት!!


#ክፍል_ሁለት


#በጥላሁን

" እንዴ ባታውቂውስ ፈረንጅ እኮ ነው ይልቅ በጥዋት ያለሽበት ድረስ ሰተት ብሎ የመጣውን አሜሪካ ወደ ምትባል ገነት ወደሆነች ሀገር መግቢያ ቁልፍ የያዘ ሪስቅ አትግፊ ተቀበይው እዚ እንደሰርዲን ሚኒባስ ውስጥ ታጭቆ መሄድ አልሰለቸሽም እንዴ ይልቅ ተቀበይውና ወርደሽ መኪናው ውስጥ ግቢ ይሄ እድል አያማልጥሽ!" አለች የምትቅመዋ ሴት •••
እረ ልጄ ተይ ልጅቷን አታጣድፊያት በሰው ህይወት እንዲህ አቅልሎ መወሰን በጎም አይደል እናንተ ሰዎች እስቲ ቢያንስ በራሷ መንገድ ትወስን ይቺ ልጅ እኮ ሰው እንጂ እቃ አይደለችም !" አሉ አዛውንቱ ልጅቷ በመውረድና ባለመውረድ ስትወዛገብ ሲመለከቷት ሁኔታው አላምር ብሏቸው።
ሹፌሩ ተበሳጨ "ሰአት አትግደይብኝ እናቱ ወይ ተቀበይው ወይ ረዳቱ በሩን ይዝጋውና እንሂድ"
ከቦታዋ ላይ ሳትነሳ እንጆሪውን ተቀበለችው ፈረንጁም አመስግኖ ወደ መኪናው ሄደ።

የሚኒባሱ በር ተከረቸመ ።ጉዞ ወደ ሀዋሳ ተጀመረ።
ፈረንጁም ላንድክሩዘር መኪናውን ካቅም በታች እየነዳት ከሚኒባሷ ጀርባ በቅርብ ርቀት መከተል ጀመረ።

"እሄ ነጭ ፎንቃ ገብቶለታል የሚፋታሽ አይመስለኝ እየተከተለን ነው ሲል " ሁሉም ዞረው ተመለከቱ እውነትም ተጠግቶ እየተከተላቸው ነበር።
"ኧረ ተይ አንቺ ልጅ እሄ ፈረንጅ ትግስቱ አልቆ ካጠገባችን ከተሰወረ ቡሀል ቆጭቶሽ እንደ በረዶ ከምትማሚ አሁኑኑ ካይንሽ ሳይርቅ ወስኚ"
ልጅቷ ከውጪ እንደምታምረው ውስጣዊ ማንነታ ያን ያህል አልነበረም ምክንያቶቹ ደግሞ እድሜ ፣ አስተዳደግ እና አከባቢያዊ አመለካከት ያሳደሩባት ተፅእኖዎች ናቸው በዚህም ምክንያት ጫት ቃሚዋ ስታነሳሳት ለመሄድ ትነሳሳና ሽማግሌው ሲቃወሙ መልሳ በረድ ትላለች የራሷ የሆነ አቋም አልነበራትም ንፋሱ ወዳወዛወዛት ትወዛወዛለች።

ሁለቱ ከምትቅመው ላይ ጫት የተቀበሉት ወጣቶች እና ሴቷ ሂጂም አትሂጅም ቢሉ "ምናገባህ! ምናገባሽ! አናንተ ናችሁ እንዴ በኔ ሂወት ወሳኙ ብትለኝስ ብትለንስ " በሚል ሀሳብ ፈርተው ጥጋቸውን ይዘው ቢቆዩም ልጅቷ በውጪ ከሚታየው አስደንጋጭ ማራኪ ውበቷ ውስጥ ያለው ማንነቷ ገና ያልበሰለ መሆኑን ከሁኔታዋ ስለተረዱ የጫት ቃሚዋን ሀሳብ ደጋፊ ሆነው ክርክሩን ተቀላቀሉ።

ጫት እምትቅመው ወደአዛውንቱ ሰው እጇን እያወዛወዘች "አባባ እኔ በበኩሉ እሄ ወግ ባህል ስርአት እያላችሁ በማይመለከተው ቦታ ሁሉ እያስገባችሁ የራሳችሁን ግዜ ተጠቅማችሁ በኛ ግዜ እንደፈለግን እንዳንሆን በወግና ባህል ሰበብ በማይበጠስ ሰንሰለት እጅና እግራችንን አሳስራችሁ ቆማ ቀር ሴት የምታበረክቱበት አካሄዳችሁ በፍፁም አይመቸኝም አይገርሞትም።

በዚህ ግዜ! ሽበታሙ ሰውየ ብቻ ሳይሆኑ ከጎናቸው የተቀመጡት እስካሁን ያልተነፈሱት እድሜ ጠገብ ባልና ሚስቶች ተነሱባት ጫት ቃሚዋ ላይ ።
" ልጅሽ ብትሆን አንድም ቀን አይተሽው ለማታውቂው ሰው ይሁን አውሬ ላለየሽው ሰው አሳልፈሽ ትሰጫት ነበር ! ስላንቺ አይመለከተንም ልጅቷን ወደሳት ለመገፍተር? ምን አጣደፈሽ ?ሌላ አላማ አለሽ ? ተረባረቡባት•••

ፈረንጁ በዚህ መሀል ፍጥነት ጨመረና በሚንባሳ ጎን ትይዩ እየሄደ አንገቱን አውጥቶ በሚኒባሱ መስታወት ወደ ውስጥ ለልጅቷ ከንፈሮቹን የእጆቹ ጣቶች ላይ አስቀምጦ እፍፍፍ ብሎ ላከላትና እስም እንደንፋስ ካጠገባቸው እፍፍ ብሎ ጥሏቸው ሽምጥ ጋለበ ። የልጅቷ ፊት ተቀያየረ ።
በወጣቶቹ በኩል ጩኸት በረከተ •••
"አቦ ዝም ብላችሁ ነው እሄን የመሰለ እድል ያስመለጣቹሀት
አመት አወቀችው አንድ ቀን አወቀችው ምን ልዩነት አለው?
አመትም ቢሆን የሚጀምረው ባንድ ቀን ነው!
አንድ ብለው ሳይጀምሩ አመት የሞላቸው አሉ? እስቲ ንገሩን ?
"ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም ይላል የኛው አባባል እንዲህ ቢሆንስ እንዲያ ቢሆንስ ብሎ መጥፎ መጥፎውን ከማሰብ እሄ ሰውዬ እሷ ባታውቀውም እሱ ለብዙ ግዜ ሲከታተላት የቆየ አፍቃሪ ነው ብሎ ደግ ደጉን ማሰብስ አይቻልም ያለው ማነው?
በተለይ ጫት ቃሚዋ የፈረንጁ መሄድ እጅግ በሚገርም ሁኔታ ነበር ያንገበገባት ወደ ልጅታ ተነስታ ለመሄድ እየዳዳት •••
" ቆጨሽ አደል ፉትሽ ያስታውቃል አሁንም መጠቀም ከፈለግሽ እድሉ አለሽ ብዙ አራቀንም ሹፌር በናትህ በመጨረሻው ፍጥነት ንዳው እንድረስበት!" ስትል•••
"እንዴ ኧረ ልጆች አሳዳጊዎች ነን እንዳትገለብጠን !ቀስ ብለህ ንዳ ሹፌር ካበዱት ጋር አብረህ አትበድ የኔ ልጅ ቀስ እያልክ ንዳ!" አሉ ባልቴቷ
"እቦ መሞት ካለብን ሮጠም ቆመም መሞታችን አይቀርም " አለች ቃሚዋ በንዴት
ለደቂቃዎች ሁሉም በተከራከሩበት ሀሳብ ዙሪያ እያሰላሰሉ ፀጥታ ሰፈነ በመሀል አንድ ኩርባ መንገድ ላይ ሚኒባሱ እጥፍ እንዳለ ፈረንጁ መኪናውን ካንድ ዛፍ አጠገብ አቁሟት ጥቁር መነፀሩን እንደገረገደ እግሮቹን አጣሞሮ ዛፉን በመደገፍ የህንድ አክተር መስሎ ቆሟል ። ተቀወጠ ።
"ያውና!
ያውና!
ያውልሽ ያው ፈረንጅ "
ሚኒባሷን ሶስት እግሯን ሰቅለው ባንድ እግሯ አቆሟት ማለት ይችላል ።
ሚኒባሱ ፈረንጁን ሲያልፈው ተንጫጩ አቆመው ውረጂና ሂጅ ጨቀጨቋት አዛውንቱ ሰውዬ በሩን ተደግፈው አለቅ ሲሉ ጫት ቃሚዋ የሚኒባሷን የውሀላ በር ከፍታ ልጅታን በዛ በኩል አስወጧት
"ለማንኛውም ስልኳን ተቀበያት አለች ከወንዶቹ ጋር የመጣችው ሴት ጫት ቃሚዋን ።
ተቀበለቻት ።
ሚኒባሱ ፊት ፊት ፈሩንጅ እና አጠገቡ የተቀመጠችው ቆንጆ ሀበሻ ያሉበት መኪና ከውሃላ ሆኖ ጉዞ ቀጠለ።
" ግን በምን ይግባባሉ?" አለች ጋቢና ከተቀመጡት አንዷ
ጫት ቃሚዋ ዘወር ብላ ተመለከተችና " እሄው እየሳቀች እኮ ነው ባይግባቡ ትስቅ ነበር ደሞ የስ እና ኦኬ ማለት ምን ይከብዳል"
ፈረንጅ ከቆይታ ቡሀላ ያን ውሃ የመሰለ መኪና ባየር ላይ እያከነፈ ልጅቷን ይዞ ሚኒባሷን ጥሎ ከአይናቸው ተሰወረ። እሄን ግዜ ከልጅቷ አጠገብ የነበረው ወጣት•••
"እስቲ ለማንኛውም ስልኳን ስጪኝ ልደውልላት" አለ
"አዋ ደውልላት እስቲ በናትህ አልችና ስልኳን ሰጠችው ጫት የምትቅመዋ ሴት።
ቁጥሩን ስልኩ ላይ ከትቦ ሲደውል ያየውን ማመን አልቻለም ነበርና•••
" እንዴ ያባቴ ስም ወጣኮ ምንድን ነው እሄ ስልክ እስቲ ደግመሽ ንገሪኝ "
ደግማ ነገረችው ልክ ነው ያባቱ የድሮ ስልክ እየተርበተበተ ቁጥሩ ላይ ሲደውል ተነሳ
"ሄሎ " አለች ልጅቷ "
ያባቱን ስም በመጥራት ታውቀው እንደሆን ሲጠይቃት ።
"አዋ አባቴኮ ነው እንዴት አላውቀውም ምን አይነት ጥያቄ ነው !"አለችው •••
ስልኩን ከጆሮው ላይ ለቀቀውና "አባቴ ነው አለችኝ አባቴ ከናቴ ውጪ የወለዳት እህቴ ነች ማለት ነው ልጅቷ " አለ
ሹፌሩ በሰማው ነገር ደንግጦ ሲጢጢጢጥ አደረገና ሚኒባሷን ገተራት••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
አትሮኖስ pinned «#እህቴን_ሸጥናት!! ፡ ፡ #ክፍል_ሁለት ፡ ፡ #በጥላሁን " እንዴ ባታውቂውስ ፈረንጅ እኮ ነው ይልቅ በጥዋት ያለሽበት ድረስ ሰተት ብሎ የመጣውን አሜሪካ ወደ ምትባል ገነት ወደሆነች ሀገር መግቢያ ቁልፍ የያዘ ሪስቅ አትግፊ ተቀበይው እዚ እንደሰርዲን ሚኒባስ ውስጥ ታጭቆ መሄድ አልሰለቸሽም እንዴ ይልቅ ተቀበይውና ወርደሽ መኪናው ውስጥ ግቢ ይሄ እድል አያማልጥሽ!" አለች የምትቅመዋ ሴት ••• እረ ልጄ…»
#ዞሮ_ዞሮ_ዜሮ

በመኖሮ ውስጥ ያለ ፥ ያለመኖር ሚስጢር
ዞሮ ዜሮ መሆን!
የሰው ልጅ ክብ ነው ; እድሜውን ሲቆጥር።

ልደት ማለት ኦና ፥ እድሜ መቁጠር አልቦ
ሰው ግን ኖርኩኝ ይላል ፥ ወደ ሞቱ ቀርቦ።

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍1
#ኩል_እና_ጥላሸት (2)

የወጋ ከረሳ ፥ የተወጋም ይርሳ
መልክ የሰጡት ቁስል
“ንቅሳት” ነው ስሙ ፥ ጌጥ ሲሆን ጠባሳ

ይህንኑ ጉዳይ
ስንመለከተው ፥ በሌላኛው በኩል
ኩልም ጥላሸት ነው ፥ ጥላሸትም ነው ኩል!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘