ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.82K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
393 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ ድሮም ፍለጋቸው እናቱ #ማርያምን ሳይሆን #የተወለደውን #የአይሁድ #ንጉስ ነው {ማቴ 2፥2፣ 11}። #ሄሮድስም #ህጻኑን #ለመግደል አቅዶ እንደተነሳና #ህጻኑን ግን እንዳላገኘው ያሳይና ወዲያውም ወደ 30 ዓመት #ዕድሜው ተምዘግዝጎ ወደ #አገልግሎቱና #ዋና ወደ ሆነው #ሰፊ #ክፍል ውስጥ ይገባል።

▶️ በሉቃ 1፥26፣ እስከ 2፥52 ብንመለከትም #መልአኩ #ገብርኤል #ማርያምን #ትጸንሻለሽ ብሎ ከገለጸ ቡኋላ በሚወለደው #ህጻን #ልጅ ላይ ብቻ #አትኩሮት ሰጥቶ <<ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም።. . . መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።>> የሚል #በልጁ #ታላቅነት ላይ ያነጣጠረ ነበር። ወዲያው #ኢየሱስ #ክርስቶስ ከተወለደ ቡኋላ "መጽሐፍ ቅዱስ" #የማርያምን #ሁኔታ ወደ ጎን ይተወውና <<ሕፃኑም አደገ በመንፈስም ጠነከረ፥ ለእስራኤልም እስከ ታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ።. . ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።>> ብሎ ወደ #ልጁ አጠቃላይ #አገልግሎቱ ገብቶ እስከ #እርገቱ በስፋት ያትታል።
▶️ ወደ #ቅድስተ #ቅዱሳኑ (ቤተ መቅደሱ) ውስጠኛ #ክፍል ለአገልግሎቱ የሚገባው #ሊቀ ካህኑ ብቻ ሆኖ #በአመት 1 ቀን እርሱም #በማስተሰርያ ቀን #ስለራሱና #ስለህዝቡ #መስዋዕትን ይዞ #በእግዚአብሄር ፊት ይቆማል {ዘጸ 28}። #የሊቀ ካህኑ ልብሰ #ተክህኖ #በ4 #ቀለማት ማለትም #ከነጭ#ከሰማያዊ#ከሐምራዊና #ከቀይ #በፍታ #በወርቅ የተለጠፈ ነበር {ዘጸ 28}። የላይኛው አላባሽ #ኤፉድ ሲባል {ዘጸ 39፥2} #በቀኝና #በግራ ትከሻው ላይ ሁለት የመረግድ #ድንጋዮች ነበሩት። በእነዚህ #ሁለት የከበሩ #ድንጋዮች በእያንዳንዱ ላይ #የ6 ነገድ #ስም በሁለቱም ላይ #የ12ቱ ነገደ #እስራኤል ስም #ተቀርጾባቸዋል {ዘጸ 28፥9 እና 12}። በእነርሱም አማካኝነት #ሊቀ ካህኑ #የህዝቡን #ስም በአጠቃላይ በትከሻው ይሸከማል። #የደረት ኪሱ #አራት ማዕዘን ያለው ሆኖ #በወርቅ ጥልፍ የተሰራ #የ12 ነገድ #ስም የተቀረጸባቸው #የሚያንጸባርቁ #የከበሩ #ድንጋዮች እንደ #ፈርጥ ሆነው የተሰሩ ናቸው {ዘጸ 28፥29}። #የደረት ኪሱ ታጥፎ የተደረበ ነው በውስጣቸው #ኡሪምና #ቱሚም ይይዛሉ {ዘጸ 28፥30}። #ቀሚሱ ሙሉ በሙሉ #ሰማያዊ ሲሆን በታችኛውም ዘርፍ ዙሪያ #በ3 #ቀለም የተሰራ #የሮማን ፍሬ #ቅርጽ #ከወርቅ #ሻኩራ ጋር ተሰባጥሮ ይደረግበታል። የሻኩራዎቹ #ድምጽ #ለቀሚሱ ውበትን ይሰጠዋል። #ጥምጥሙ ደግሞ #ካህኑ በራሱ ላይ የሚጠመጥመው ሲሆን ከጥሩ #በፍታ የተሰራ ነው <<ቅድስና ለእግዚአብሔር>> የሚል ጽሑፍ #ከወርቅ በተሰራ #ዝርግ #ጌጥ ላይ ተቀርጾ በዚህ #ጥምጥም ላይ #ይንጠለጠልበታል {ዘጸ 28፥36}።
▶️ በቅዱስ ገብርኤል #ሰላምታ #ሰላም እልሻለሁ የሚለውን #ቃል ራሱ ብናየው #የተሳሳተ #አባባልና #ያልተለመደ #ንግግር ነው። በሌላ አገላለጽ #ዩሐንስ #ለጋይዮስ #ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው #ሰላምታ [3ኛ ዩሀ 1፥15] #ጋይዮስ ሆይ #በዩሐንስ ሰላምታ #ሰላም እልሃለው እንደማለት ነው። ነገሩን #ግልጽ ለማድረግ አቶ #አበበ አቶ #ከበደ ቤት ገብቶ <<አቶ #ከበደ በአቶ #አበበ #ሰላምታ #ሰላም #እልሀለው>> ብሎ #ሰላምታ እንደመስጠት ያክል ነው። ይህም በማንኛውም #ህብረተሰብና #ክፍለዘመን ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው #ከጤናማው #የሰላምታ ሥነ-ሥርዓት የወጣ #አባባል ነው።

▶️ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል #ከእግዚአብሔር ዘንድ #መልዕክት አድርስ ተብሎ ወደ #ድንግል ማርያም በመምጣት ያደረገውን #ሰላምታ ተንተርሶ #አጼ #ዘረዓ #ያዕቆብ <<ይወድስዋ መላእክት - {መላዕክት ማርያምን ያመሰግኗታል}>> የሚል #ድርሰት ሲያዘጋጅ #የቦረናው #አባ #ጊዮርጊስ #ዘጋስጫ ደግሞ <<ተፈሥሒ ኦ ሙኃዘፍስሐ፤ የተድላና የደስታ መፍሰሻ ሆይ ደስ ይበልሽ መላእክት ብለዋታል[1]>> ብሏል። ነገር ግን ወደ #ማርያም ተልከው የመጡት #መላእክት ሳይሆኑ አንድ #መለአክ ነው። እርሱም ቅዱስ #ገብርኤል ሲሆን ንግግሩም #ከእግዚአብሄር ዘንድ እንደተላከ ማሳወቅና #ክርስቶስን ያለ #ወንድ #ዘር #በድንግልና እንደምትወልድ የሚገልጽ እንጂ የተለየ #ምስጋና ለመስጠትና #የተድላና #የደስታ #መፍሰሻ እንደነበረች ያሳሰበበት #ክፍል አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን #መልአኩ እርሱ ከመምጣቱ በፊት #ማርያምን #የሚያመሰግንበትም የተለየ #የሰራችው አንዳች ነገር የለም። ያም ሆኖ አንዳንዶች እንደሚያደርጉት #መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤልም ሆነ #ድንግል #ማርያም በነበራቸው የአጭር ጊዜ የመረዳዳት #ውይይትን እንደመደበኛ #የግል #ጸሎታቸው አድርገው #መጽሀፍ አዘጋጅተው የሚደግሙ አሉ። ነገር ግን እነርሱ ራሳቸው መልአኩ #ገብርኤልም ሆነ #ድንግል #ማርያም #ውይይት አደረጉ እንጂ #አንዱ #ለአንዱ ያቀረቡት #ጸሎት የለም። ንግግራቸውም #የዘውትር #ጸሎት እንዲሆንላቸው ያሳሰቡት ነገርም የለም።

▶️ ጌታ #ኢየሱስ ክርስቶስ የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደ #ሰማይ ሲያርግ #ድንግል #ማርያም ባለችበት #በማርቆስ #እናት ቤት ሐዋሪያት #በአንድነት #በጸሎት ሲተጉ አጠገባቸው ያለችውን #ማርያምን <<በገብርኤል #ሰላምታ ሰላም እንልሻለን #በነፍስሽም #በስጋሽም ድንግል ነሽ ከተወደደው #ልጅሽ #ይቅርታ #ለምኚልን #ኃጢአታችንን ያስተሰረይልን ዘንድ>> አሏሏትም፤ #የጸሎት #ማዕከላቸውም አልነበረችም። እርሷም እነርሱም በአንድነት << #የሁሉንም #ልብ የምታውቅ #ጌታ ሆይ>> እያሉ #ጌታን እያከበሩ ወደ #ጌታ ሲጸልዩ ነበር። በድንገት #መንፈስ ቅዱስም ለእሷም ለእነሱም #እኩል ያለልዩነት ወረደባቸው። [ሐዋ 1፤ 12-14፣ ሐዋ 2፤ 1-4]።

በተለይ ደግሞ << #ይቅርታን #ለምኚልን>> የሚለው #ቃል ጠቅላላውን #የክርስቶስን #ይቅርታ #ለሰው ልጆች እንዴት እንደተሰጠ አለማወቅና #የክርስቶስን #የደኅንነት #መስዋዕት #ከንቱ የሚያደርግ ነው። በመሆኑም ይህን #ጸሎት ማቅረብ #የጸሎትን #ትርጉም አለማወቅ ብቻ ሳይሆን በግልጽ #የክርስቶስ #ተቃዋሚ መሆን ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_____________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ "መጽሐፈ ሰዓታት" ገጽ 29።