ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.82K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
393 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ በቅዱስ ገብርኤል #ሰላምታ #ሰላም እልሻለሁ የሚለውን #ቃል ራሱ ብናየው #የተሳሳተ #አባባልና #ያልተለመደ #ንግግር ነው። በሌላ አገላለጽ #ዩሐንስ #ለጋይዮስ #ሰላም ለአንተ ይሁን ባለው #ሰላምታ [3ኛ ዩሀ 1፥15] #ጋይዮስ ሆይ #በዩሐንስ ሰላምታ #ሰላም እልሃለው እንደማለት ነው። ነገሩን #ግልጽ ለማድረግ አቶ #አበበ አቶ #ከበደ ቤት ገብቶ <<አቶ #ከበደ በአቶ #አበበ #ሰላምታ #ሰላም #እልሀለው>> ብሎ #ሰላምታ እንደመስጠት ያክል ነው። ይህም በማንኛውም #ህብረተሰብና #ክፍለዘመን ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው #ከጤናማው #የሰላምታ ሥነ-ሥርዓት የወጣ #አባባል ነው።

▶️ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል #ከእግዚአብሔር ዘንድ #መልዕክት አድርስ ተብሎ ወደ #ድንግል ማርያም በመምጣት ያደረገውን #ሰላምታ ተንተርሶ #አጼ #ዘረዓ #ያዕቆብ <<ይወድስዋ መላእክት - {መላዕክት ማርያምን ያመሰግኗታል}>> የሚል #ድርሰት ሲያዘጋጅ #የቦረናው #አባ #ጊዮርጊስ #ዘጋስጫ ደግሞ <<ተፈሥሒ ኦ ሙኃዘፍስሐ፤ የተድላና የደስታ መፍሰሻ ሆይ ደስ ይበልሽ መላእክት ብለዋታል[1]>> ብሏል። ነገር ግን ወደ #ማርያም ተልከው የመጡት #መላእክት ሳይሆኑ አንድ #መለአክ ነው። እርሱም ቅዱስ #ገብርኤል ሲሆን ንግግሩም #ከእግዚአብሄር ዘንድ እንደተላከ ማሳወቅና #ክርስቶስን ያለ #ወንድ #ዘር #በድንግልና እንደምትወልድ የሚገልጽ እንጂ የተለየ #ምስጋና ለመስጠትና #የተድላና #የደስታ #መፍሰሻ እንደነበረች ያሳሰበበት #ክፍል አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን #መልአኩ እርሱ ከመምጣቱ በፊት #ማርያምን #የሚያመሰግንበትም የተለየ #የሰራችው አንዳች ነገር የለም። ያም ሆኖ አንዳንዶች እንደሚያደርጉት #መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤልም ሆነ #ድንግል #ማርያም በነበራቸው የአጭር ጊዜ የመረዳዳት #ውይይትን እንደመደበኛ #የግል #ጸሎታቸው አድርገው #መጽሀፍ አዘጋጅተው የሚደግሙ አሉ። ነገር ግን እነርሱ ራሳቸው መልአኩ #ገብርኤልም ሆነ #ድንግል #ማርያም #ውይይት አደረጉ እንጂ #አንዱ #ለአንዱ ያቀረቡት #ጸሎት የለም። ንግግራቸውም #የዘውትር #ጸሎት እንዲሆንላቸው ያሳሰቡት ነገርም የለም።

▶️ ጌታ #ኢየሱስ ክርስቶስ የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደ #ሰማይ ሲያርግ #ድንግል #ማርያም ባለችበት #በማርቆስ #እናት ቤት ሐዋሪያት #በአንድነት #በጸሎት ሲተጉ አጠገባቸው ያለችውን #ማርያምን <<በገብርኤል #ሰላምታ ሰላም እንልሻለን #በነፍስሽም #በስጋሽም ድንግል ነሽ ከተወደደው #ልጅሽ #ይቅርታ #ለምኚልን #ኃጢአታችንን ያስተሰረይልን ዘንድ>> አሏሏትም፤ #የጸሎት #ማዕከላቸውም አልነበረችም። እርሷም እነርሱም በአንድነት << #የሁሉንም #ልብ የምታውቅ #ጌታ ሆይ>> እያሉ #ጌታን እያከበሩ ወደ #ጌታ ሲጸልዩ ነበር። በድንገት #መንፈስ ቅዱስም ለእሷም ለእነሱም #እኩል ያለልዩነት ወረደባቸው። [ሐዋ 1፤ 12-14፣ ሐዋ 2፤ 1-4]።

በተለይ ደግሞ << #ይቅርታን #ለምኚልን>> የሚለው #ቃል ጠቅላላውን #የክርስቶስን #ይቅርታ #ለሰው ልጆች እንዴት እንደተሰጠ አለማወቅና #የክርስቶስን #የደኅንነት #መስዋዕት #ከንቱ የሚያደርግ ነው። በመሆኑም ይህን #ጸሎት ማቅረብ #የጸሎትን #ትርጉም አለማወቅ ብቻ ሳይሆን በግልጽ #የክርስቶስ #ተቃዋሚ መሆን ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_____________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ "መጽሐፈ ሰዓታት" ገጽ 29።
▶️ የሰውነት #አካላትን እየዘረዘረ #የሚያስመሰግነው ባለ ብዙ #አርኬ ግጥም #መልክእን #አለቃ #ኪዳነ ወልድ ክፍሌ <<መልክእ ከራስ ጸጉር እስከ እግር ጥፍሩ የሚቆጠር መጽሀፍ ነው ብለውታል[1]።>> የሚገርመው #የሰውነት #አካል የሌላቸው እንኳ #መልክዕ ከተጻፈላቸው ውስጥ #መልክዓ #መስቀል(ለእንጨቱ) ፣ #መልክዓ #ሰንበት(ለቀኑ)፣ #መልክዓ #አንቀጸ #ብርሃን(ለመጽሀፍ ስም)፣ #መልክዓ #ስዕል(ለስዕሉ)፣ #መልክዓ #ቁስቋም(ለቦታ) ይጠቀሳሉ። ሌላው ደግሞ #ማንም ሊቀርበው በማይችል #ብርሃን ውስጥ ለሚኖረው #መልክዓ እና #ገጽ የሌለው #መንፈስ ለሆነው #ለእግዚአብሄር እንኳን #በሰው #አካል(ብልቶች) እየቆጠረ ባለ ብዙ #አርኪ #ግጥም #መልክ ተዘጋጅቶለታል። #ለመላእክትም#ቅዱሳን ለተባሉ #ሰዎችም#በኢትዮጵያ ነግሰው ለነበሩ #አጼዎችም ሁሉ "መልክእ" አላቸው። ይህ <መልክእ> የተባለው #የስነ ጽሁፍ #አይነት መጻፍ የተጀመረው #ፕሮፌሰር #ኃይሌ #በ17ኛው ክፍለ ዘመን #ፌሬንክ በተባለ #እንግሊዛዊ እንደሆነ ሲናገሩ #አለማየሁ #ሞገስ የተባሉት ደራሲ ደግሞ #በ14ኛው ክፍለ ዘመን #በአጼ #ዘረዓ ዕቆብ #ዘመነ መንግስት ነው ይላሉ። ሌላው ዜግነቱ ያልታወቀው "ቤደርሰን" የተባለ ጸሀፊ ደግሞ #በ17ኛው ክፍለ ዘመን ባልታወቀ #የዜማ #አቀንቃኝ ነው ይላል። ሁሉም #በጀማሪውና #በጅማሬው #ዘመን ባይስማሙም #የቤተክርስቲያኒቷ ጅማሬ ላይ ያልነበረ #አበው ያላስተማሩት #መጤ እንደሆነ ይስማማሉ።

▶️ መነሻ ሀሳባችን ስለማርያም ነውና በ"መልክእ" ይዘት ድንግል ማርያም የምትመለክበትን ከ"ጸሎት መጽሀፍ" አንዱ የሆነውን < #መልክዓ #ማርያምን> እንመልከት፦
▶️ በኢትዮጽያ #የማርያም #ስዕል አመጣጥ #የረጅም ጊዜ #ታሪክ ባይኖረውም #በአጼ #ዳዊት #ዘመነ #መንግስት [በ1365-1395 ዓ.ም] <<ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጽያ ወንጌላዊ ሉቃስ የሳላት የማርያም ስዕል መጣች>> በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ #የሥዕል #በር ተከፈተ[8]።

▶️ በ14ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ #የአፄ ዘርዓ ያቆብ ቤተሰቦች #የፊተኛው ልጃቸው ስለሞተባቸው ገና #ሳይወለድ እያለ <<ተወልዶ በጤና ካደገ ለቅድስት ድንግል ማርያም እሰጠዋለው>> ብለው #በስእሉ ፊት ያልተለመደ #ጸሎትና #ስለት አቀረቡ[9]። ይህንንም #ስለት አይነት በተደጋጋሚ ሲሰማ ያደገው #ዘረዓ ያዕቆብ #ስልጣኑን {አፄነቱን} ሲረከብ #ስእሎችን #በከፍተኛ ሁኔታ #እንዲስፋፉና #እንዲሰገድላቸው #የማርያም #ስእልም [ስእለ አድህኖ] ተብሎ እንዲሰየም አደረገ። በዚህም 2ተኛው #ቆስጠንጢኖስ እንዲባል አስችሎታል[10]።

▶️ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #በሙዚየም በኢትዮጵያ ስላሉ #ስነ ስዕላት አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል።

<<በሰሌዳ ላይ (በእንጨት በጨርቅ በብራናና በመሳሰሉት) የመሳል ጥበብ በኢትዮጵያ የተጀመረው በ15ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ እንደሆነ ይገመታል ከዚህ ዘመን በፊት የተሳሉ አንዳንድ የሰሌዳ ላይ ስዕሎች እስካሁን ድረስ አልተገኙም። የታሪክ ተመራማሪዎች እንደሚሉት {ስዕላተ አስህኖ} ድንገት ብቅ ያሉት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ [1434 እ.አ.አ] ዘመን እንደሆነና ይህም የሆነበት ምክንያት ንጉሱ ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ከነበረው ልዩ እምነትና ፍቅር ጋር የተያያዘ ነው ይላሉ። ከዚህም የተነሳ በኢትዮጵያ ውስጥ "የስእላተ አድህኖ" ምስሎችን ማክበር በእርሱ መታመንና የስዕላቱ ተፈላጊነት እያደገ የመጣው ከእሱ ዘመነ መንግስት ወዲህ ነው። . . . የዘመኑ ዝነኛና ታዋቂ ሰዓሊ አባ ፍሬ ፅዮን የሚባል መነኩሴ ነበር። የእሱ ልዩና ፈር ቀዳጅ ስልት በዘመኑ የኢትዮጵያ የስነ ስዕል ጥበብ ላይ በእጅጉ ተጽኖ አድርጓል። በ15ኛው ክፍለ ዘመን 2ኛ አጋማሽ በአማራው ሃገር እና በሸዋ የተሳሉ ብዙ የሰሌዳ ስዕሎች ላይ እና በዚያ ዘመን በተሰሩ መስቀሎች ላይ የእሱ ስልት በእጅጉ ተንጻባርቆ ይገኛል።>>

▶️ ሥዕላት የተስፋፉት #ከውጪ ዓለም በተለይም #ከኢየሩሳሌምና #ከካይሮ እንዲሁም #በጣሊያን ሃገር ከምትገኘው #ከቪኒስ እና ከሌሎች #ከተሞች ጋር በተመሰረቱት ግንኙነቶች አማካኝነት ነው። ከእነዚህም በተጨማሪ #የኢትዮጽያ #ሰዓሊዎች #የቤዛንታይን #አሳሳል #ስልትንም በማጥናት የራሳቸውን #አዳዲስ #ስልቶች አዳበሩ።

<<ኢታሎ-ክሬታን>> የሚባለው #ስልተ አሳሳል ደግሞ #የእሬታ #ሰዓሊዎች #የቢዛንታይን #ስልት በመጠቀም #የኢጣልያንም #የስዕላተ #አድህኖ ይዘት #በስዕል የገለጹበት ነው። #ብራንካሎዮን የተባለው ታዋቂው #የቪኒስ #ሰዓሊ ኢትዮጵያ ውስጥ #ለ40 ዓመት በኖረበት ጊዜ #የ15ኛው ክፍለ ዘመን #የኢትዮጵያ አሳሳል #ሂደት እና #እድገት ላይ #ታላቅ #አስተዋጽኦ አድርጓል። በኢትዮጵያም ውስጥ #የጣሊያን #የአሳሳልን #ስልት ያስገባው ይኸው #ሰዓሊ ነው። በዚህ #ጣሊያናዊ #ሰዓሊ የተከናወኑት #ስዕሎች #የካትሮችንቶ አሳሳል ጥበቡን #ባህሪያት #ያንፀባርቃሉ

. . . በኢትዮጵያ #የስዕል ጥበብ ላይ ሌላኛው #የውጭ #አስተዋጽኦ የመጣው #በ17ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ 30 #ዓመታት ወደ #ኢትዮጵያ ከገቡት #ኢየሱሳውያን {ጆስዊታስ}[11] አማካኝነት ነው።

▶️ በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበረው #ባህላዊ #የእመቤታችን #ስዕለ #አድህኖ አሳሳል በተጨማሪ <<የማጆ ወሬ ማርያም>> {በሮማ ከተማ ውስጥ የምትገኝ ቤተክርስቲያን} #አሳሳል #ስልት ገባ። ዋነኛው #የጣሊያን #ስዕል ለብዙ #ምዕተ አመታት #ሮማ #ከተማ ይቀመጥ ነበር። #በ1596 እ.ኤ.አ #ኢየሱሳውያን #የሮማውን #ሊቀጳጳሳት በማስፈቀድ #የዋንኛውን #ቅጅ #ስዕሎች በመላው #ዓለም ሊሰብኩ ወደሄዱባቸው #አገሮች ሁሉ ወሰዱ። በዚህ መሰረት #ኢትዮጵያ ውስጥ #ገባ። ከዚያን ጊዜ ወዲህ #የማጆሬዋ #ማርያም #ስዕል <<ምስለ ፍቅር ወልዳ>> ተሰኝቶና #በማርያም ተሰይሞ #በኢትዮጵያ #ጥናትና #ምርምር #ተቋም ከሚገኙት #ስዕላተ #አድህኖ ውስጥ አብዛኛውን ይኸው <<ምስለ ፍቅር ወልዳ>> የተባለው ነው።
@gedlatnadersanat