ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የነገረ_ድኅነት ጥያቄ #መልሶች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ሐሰት
#ምክንያቱም :-ሰው ለመዳን ከማመን ያለፈ የተግባር ሰው (ምግባራትን እና ምሥጢራትን የሚፈጽም) መሆን አለበት:: ምግባራት የሚባሉትም በዋናነት #ጾም #ጸሎት #ስግደት #ምጽዋት ሲሆኑ ምሥጢራቱም #ምሥጢረ_ሜሮን #ቅዱስ_ጥምቀት እና #ቅዱስ_ቁርባን ይጠቀሳሉ #ሃይማኖት ያለ #ምግባራት ጥቅም አልባ የሞተ ነው::
"፤ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ #ከሥራ (ከምግባራት )የተለየ እምነት የሞተ ነው።" (የያዕቆብ መልእክት 2: 26)


#ኛ ሐሰት

#ምክንያቱም :-በተለየ አካሉ #ከእመቤታችን ከቅድስት #ድንግል_ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሶ ነፍስን ተስቶ በፍጽም ተዋህዶ #ተወልዶ ያዳነን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና:: #በምስጢረ ሥላሴ ትምህርታችን #አብ አባት #ወልድ ልጅ #መንፈስ ቅዱስ ሰራፂ ብለን ተምረናል እንዲህም እናምናለን:: ቅዱሳት መጻሕፍትም በተዋህዶ ተወልዶ ያዳነን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በስፋት ይነግሩናል:: ለምሳሌ "እግዚአብሔር አንድያ #ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶልና" ዮሐ3÷16

#ኛ ሐሰት

#ምክንያቱም :- ምንም እንኳን ድኅነት በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ አንድ ጊዜ ተፈጽሞ ለሰው ልጆች የተሰጠ ቢሆንም ከዚህ ከተሰጠው ድኅነት ግን ለመካፈል ሰው የራሱን ጥረት ማድረግ ይገባዋል። ድኅነት በእግዚአብሔር ዘንድ የተፈጸመ ስለሆነ ብቻ ሰው ሁሉ ያመነውም ያላመነውም በግዴታ ይድናል ማለት አይደለም:: ለመዳን የወደደ ብቻ ከተፈፀመለት የድኅነት ሥራ በምግባራት ተሳትፎ ድኅነትን ያገኛል:: ስለዚህ በድኅነት ውስጥ ሰውም ሊፈጽመው የሚገባ ሂደት ነው::
"፤ ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ #እንደ_ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ #የራሳችሁን_መዳን_ፈጽሙ፤"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2: 12)

ልናስተውለው የሚገባን #የታዘዛችሁትን_በመፈጸም የምትለዋ እና #የራሳችሁን_መዳን_ፈጽሙ የምትለዋን ነው

በመሆኑም የእራሳችንን መዳን መፈጸም የምንችለው እና ከተሰራልን የድኅነት ሥራ የምንካፈለው የታዘዝነውን በመፈፀም ነው:: #የታዘዝነውም 10ቱ ትዕዛዛት 6ቱ ቃላተ ወንጌል ናቸው እነዚህን ለመፈፀም ደግሞ ጊዜ ዘመን ያስፈልገናል:: ይህ ደግሞ ድኅነት በሂደት የሚፈፀም እንጂ በአንድ ቀን በአንድ ቦታ በሰዓት ጌታን በመቀበል ብቻ አለመሆኑን ያስገነዝበናል:: በጥቅሉ ለመዳን ሰው የራሱ ድርሻን መወጣት ይገባዋል።

#ኛ እውነት

#ኛ ሐሰት
ምክንያቱም:-ያልተመለሰለት ጸጋ የለምና::
ፀጋ:-
ልጅነትን:- ከእንግዲ ወዲ ባሮች አትባሉም
ወራሽነትን:-
ገዢነትን(ሥልጣንን):- ግዛ ንዳ የተባለሁ ዓለምና በዓለም ያሉትን ነገሮች ሁሉ ዛሬም ሰው ከትዕዛዙ ካልራቀ ሕጉን ከጠበቀ ከተፈጥሮ ሁሉ በላይ መግዛት መንዳት የሚችልና ሥልጣኑ ያለው መሆኑን በቅዱሳን ሕይወት መመልከት ይቻላል::


#በአጭሩ መልሱ

#ኛ #ስለ_ፍጽም_ፍቅሩ
#ለካሳ ለቤዛ
#የዲያብሎስ ጥበብ #በጥበቡ #ለመሻር
#ለምሳሌነት_ለአራያነት
#ድኅነት ሥርዓት ስላለው…

#ኛ #ማመን
#ሥራ (ምግባራት)
#ምሥጢራትን መፈጸም ማር 16:16 ዮሐ 6:54


#ኛ "፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ #በእርሱም ቍስል #እኛ ተፈወስን።"

(ትንቢተ ኢሳይያስ 53: 5)
"፤ #እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ #ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም #የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53: 6)

ነብዩ ስለ እኔ ብቻ አላለም #እኛ ብሎ አብዝቶ ተናገረ እንጂ:: እኛ ብሎ አብዝቶ መናገሩ የዓለምን ኃጢያት የተሸከመ የዓለም መድኀን መሆኑን ሲገልጥ ነው::

"እነሆ #የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ #የእግዚአብሔር_በግ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1: 29)


#ኛ #መንግስቱን_ሲወርስ_ስሙን_ሲቀድስ


#ኛ ማዳን የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው ማለት እንጂ ቅዱሳን አያድኑም ወይም መድኀኒት አይባሉም ለማለት አይደለም:: በቅዱስ መጽሐፍ ሰዎች ሆነው አዳኝ ተብለው የተጠሩ አሉ #ለምሳሌ "፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ #እግዚአብሔርም_የሚያድናቸውን_አዳኝ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ #ጎቶንያልን_አስነሣላቸው።"
(መጽሐፈ መሳፍንት 3: 9) ይህ የሚያሳየው እግዚአብሔር ቅዱሳን ሰዎችን አዳኝ መድኀኒት አድርጎ እንደሚያስነሳ ነው:: መዳን በሌላ በማንም የለም ማለቱ የቅዱሳን አዳኝነት (መድኀኒትነት) ጠፍቶት አይደለም:: ቅዱሳን የጸጋ አዳኝ ናቸው:: ጸጋ ደግሞ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ፣የተቸረ ፣የተለገሰ ስጦታ ማለት ነው:: ስለዚህ ቅዱሳን መድኀኒት ቢባሉ በስጦታ ያገኙት ነው። "#እድንበት ዘንድ ከሰማይ በታች የተሰጠን #ሌላ ስም የለም" ማለቱ ደግሞ ቅዱሳን ሲያድኑም በእራሳቸው ኃይል ሳይሆን ማዳንን በሰጣቸው በፈጣሪያቸው ስም ነው ማለቱ ነው:: ቅዱሳን መላእክት አዳኝ (መድኅኒት )ናቸው። ስማቸው ስመ እግዚአብሔር ተሸክሞልና:: ስለሆነም ቅዱስ ሚካኤል አዳነ ማለት እግዚአብሔር አደነ ማለት ነው ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ (ቅዱሳን ሰዎችም) ቢያድኑ የፈጣሪን ስሙን ጠርተው ነው "፤ ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ #በናዝሬቱ_በኢየሱስ_ክርስቶስ_ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።"
(የሐዋርያት ሥራ 3: 6)
ከዚህም ባሻገር ቅዱሳን ወደ ቅድስና ሲጠሩ ስማቸው ይለወጣል ስመ እግዚአብሔርም ይሆናል:: በመሆኑ እነርሱም በስማቸው ማዳን ይቻላቸዋል "፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ #በእኔ_የሚያምን_እኔ_የማደርገውን_ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ #ከዚህም_የሚበልጥ_ያደርጋል፥" (የዮሐንስ ወንጌል 14: 12)
ከእርሱ አብልጦ የሚሰራ የለም ነገር ግን በስሙ ላመኑ እርሱ ያደረገውን ሁሉ የማድረግ ሥልጣን አላቸው ማለቱ ነው።

ይቆየን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ #እንደ_ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ18፥3

"ቃል ይቀትል ትርጓሜ ያድን"
"ቃል ይገላል ትርጓሜ ግን ያድናል"

#መታሰቢያነቱ :- ትርጓሜ ለምኔ ለሚሉ ወንድሞች ይሁን !
" #እምዬ_ምኒልክ የታሪክ #ፈርጥ "
______________________
አፄ ምኒልክ ከአፄ ልብነድንግል ልጅ ከአቤቶ ያዕቆብ ትውልድ ሲያያዝ የመጣ የስመ ጥሩ ንጉሥ የሣህለ ሥላሴ የልጅ ልጅ የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ናቸው።
#ትውልዱም_ከአቤቶ ያዕቆብ ዠምሮ ቢቆጠር አፄ ምኒልክ ፲ ፫ ተኛ ይሆናሉ፤ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴ ና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም ቅዳሜ ነሐሴ ፲ ፪ ቀን ፲ ፰ ፻ ፴ ፮ ዓ.ም. ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደዋል፤ ከዚያም በ አንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ።
አያታቸው ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የልጁን መወለድ ሲሰሙ “ምን ይልህ ሸዋ” በሉት ብለው ስም አወጡ። እሳቸው “…ምኒልክ በሚል ስም የሚነግሥ ንጉሥ ኢትዮጵያ ን ታላቅ ያደርጋታል” የሚል ትንቢት ስለነበር ‘ምኒልክ’ የኔ ስም ነው ብለው ነበር። ሆኖም፣ በህልማቸው ከልጁ ጋር አብረው ቆመው ከሳቸው ጥላ የልጁ ጥላ በልጦ፤ በእግር የረገጡትን መሬት ሲያለካኩ እሳቸው ከረገጡት ልጁ የረገጠው ረዝሞ አዩ።
#ከዚህ በኋላ “ምኒልክ የኔ ስም አይደለም። የሱ ነው። ስሙን ምኒልክ በሉት” ብለው አዘዙ ። ይላል ( ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፉ /ገጽ ፲፪)
አፄ ምኒልክ በተወለዱ በ፲ ፩ ዓመት በ፫ ወር በሺ ፰ ፻ ፵ ፰ ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ወደ ሸዋ በመጡ ጊዜ ይዘዋቸው ወደ ጎንደር ሄዱ ፤ በዚያም አፄ ቴዎድሮስ ብልዕነታቸውንና አስተዋይነታቸውን ተመልክተው አብረው በማዕረግ ይዘዋቸው ሲኖሩ ቆዮ በመጨረሻም ሴት ልጃቸውን ወይዘው አልጣሽ ቴዎድሮስን ዳሩላቸው።

#በዓመት_በዓል የፈረስ ጉግስ ከምኒልክ በቀር ሌላ ሰው አይታይም ነበር ይባላል። በመጨረሻ ግን አፄ ቴዎድሮስ ኢትዮጵያን አንድ አደርጋለሁ በማለት ያቀዱትን ዕቅድ ፣ በያሉበት መኳንቱና ሕዝቡ እየሸፈቱ ስላበላሹባቸው ከብስጭት የተነሳ ሰውን ሁሉ ያለ ሕግ በገደሉና ባሰሩ ጊዜ እንደዚሁ አቤቶ ምኒልክን አስረው ወደ መቅደላ ላኩዋቸው ፤ በዚያም ከታመኑ አሽከሮቻቸውና ከእናታቸው ከወይዘሮ እጅጋየሁ ጋር ሆነው ከሸዋ ባለ አባቶች ጋር ውስጥ ውስጡን እየተላላኩ ምቹ የማምለጫ ጊዜ ሲፈልጉ ወዲያው አፄ ቴዎድርስ የትግሬና የጎንደር፣ የበጌምድርም ሕዝብ ሸፍቶባቸው ወደ ላይና ወደ ታች ሲሮጡ አቤቶ ምኒልክ ከወሎዎች ጋር ውስጥ ውስጡን ተስማምተው ከመቅደላ ፲ ፰ ፻ ፶ ፯ ዓ.ም ሰኔ ፳ ፬ ቀን ሌሊት አምልጠው ወሎ ገብተው አደሩ ።
በዚህ ጊዜ አቶ በዛብህ እንደ ንጉሥ ሆነው ሸዋን ሲገዙ ይህንኑ ሰምተው ነበርና እሰሪልኝ ብለው ለወሎ ገዢ ለወዘሮ ወርቂት ገጸ በረከት ጨምረው ላኩላቸው ወይዘሮ ወርቂትም ስለ አቶ በዛብህ ሳይሆን መቅደላ ለታሰረው ልጃቸው ለውጥ አድርገው ለአፄ ቴዎድርስ ለመመለስ ምኒልክ የቁም እስረኛ አድርገው ወደ አፄ ቴዎድሮስ መልክተኛ ላኩ ።
#መልክተኞቹም ወደ መቅደላ በደረሱ ጊዜ አፄ ምኒልክ አምልጠው ስለነበር አፄ ቴዎድሮስ ተበሳጭተው እስረኛውን ሁሉ እጅና እግሩን እየቆረጡ ገደል ሲጥሉ እንዲ ተብሎ ተገጠመላቸው።

" #አፄ_ቴዎድሮስ_እጅግ_ተዋረዱ
#የሸዋን_ሰው_ሁሉ_እጅ_ነስተው_ሄዱ "

#የወይዘሮ ወርቂትም ልጅ አብሮ መጣሉን ሰሙ ስለዚህ መልክተኞቹ ተመልሰው ይህንኑ ለወዘሮ ወርቂት ነገሩ ወይዘሮ ወርቂትም በእግዚአብሔር ሥራ ተደንቀው ቦሩ ሜዳ ላይ ምኒልክን ተቀብለው፣ “ #የሸዋ_ሰው_አውራህ_መጥቷልና_ደስ_ይበልህ_ተቀበል ” ብለው አዋጅ አስነግረው፣ አጃቢ አድርገው በመለከትና እምቢልታ አሳጅበው ከሸዋ ድንበር ድረስ ላኳቸው። ሸዋን ‘ንጉሥ ነኝ’ እያሉ ይገዙ የነበሩት አቶ በዛብህ የምኒልክን ወደመሀል ሸዋ መግፋት ሲሰሙ ለመውጋት ጋዲሎ ከተባለ ሥፍራ ተሠልፈው ሲጠባበቁ፣ አንዲት ሴት እንዲህ ስትል ገጠመች።

«ማነው ብላችሁ ነው ጋሻው መወልወሉ፣
ማነው ብላችሁ ነው ጦራችሁ መሾሉ
ማነው ብላችሁ ነው ካራችሁ መሳሉ፣
የጌታችሁ ልጅ ነው ኧረ በስመ አብ በሉ»

በኃላ ግን አቶ በዛብህ ስለተሸነፈ ከዛ ሸሽተው አፍቀራ ገቡ ከዚህ በኃላ አቤቶ ምኒልክ ከሸዋ በመጡ በ፲ ዓመት ንጉሥ ተብለው ሲገዙ አቶ በዛብህ አፍቀራ ሆነው ታርቀው ለመግባት ወደ ንጉሥ አማላጅ ላኩ።
በዚህ ጊዜ ንጉሡ ሊታረቋቸው ሲያስቡ የአቶ በዛብህን ሀሳብ አውቃለው ባይ ቀርቦ " አቶ በዛብህ አሁን ታርቄ ልግባ የሚለው ከገባ በኃላ መኳንንቶን እየሰበከ ለማስከዳት ነው እንጂ በእውነት እርቅ ፈልጎ አይደለም በእውነት እርቅ ፈልጎ ከሆነ የአፈቀራን ምሽግ አስረክበኝ ይበሉትና እስቲ ያስረክብሆ?! " ብሎ ተናገረ። ንጉሥ ምኒልክም አቶ በዛብህን የአፍቀራን ምሽግ እንዲያስረክብ ጠየቁት አቶ በዛብህም እኔስ ፈቅጄ ነበር አሽከሮቼ ግን ተው አታስረክብ ይሉኛል ስላሉ ይህም በቂ ምክንያት ሆኖ ስላልተቀበሏቸው ወዲያው ተያዙና ፍርድ ተጀመረ ።
#በፍርዱም_መጀመሪያ ጋዲሎ ላይ አላስገባም ብለው መዋጋታቸውንና ሁለተኛም የአፍቀራን ምሽግ አላስረክብም ማለታቸው እየተጠቀሰ ይሙት በቃ ተብሎ ተፈርዶባቸው በጥይት ተደበደቡ በጥይትም ሲመቱ ባሩዱ ከልብሳቸው ላይ ተያይዞ ገላቸው ስለነደደ አንዲት ሴት ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ገጠመች፤

" #አንተም_ጨካኝ_ነበርክ_ጨካኝ_አዘዘብህ
#እንደ_ገና_ዳቦ_ከላይም_ከታችም_እሳት_ነደደብህ "

አፄ ምኒልክ በአባታቸው ዙፋን ተቀምጠው ንጉሥ ምኒልክ እየተባሉ ይገዙ ዠመር። እንዲህም አድርገው እስከ ፲ ፰ ፻ ፸ ዓ.ም ድረስ ለ፲ ፪ ዓመት በሙሉ የበላይነት ሸዋን ሲገዙ ኖሩ።

የጽሁፉ ግብቶች፦
- ተክለ ጻድቅ መኩሪያ " የኢትዮጵያ ታሪክ"
- ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ”

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት ፲ ፰ /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ
#ሉቃ ፬ ÷ ፲ ፮

ምኩራብ የአይሁድ የጸሎት ሥፍራ መጠሪያ ነው። የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም ባለ ቤተ መቅደስ ሥርዓት የሚፈጸም ነበር ናቡ ከደነጹር ቤተ መቅደሱን ካፈረሰ እና ሕዝቡንም ካፈለሰ በኃላ ግን አይሁድ በየደረሱበት " #ምኩራብ" እየሰሩ ጸሎትና ትምህርት እንዲሁም ሌሎች የአምልኮ ሥርዓቶችን ያስቀጥሉ ጀምረዋል። አሥር የጎለመሱ ወንዶች ሲገኙ ምኩራብ መሥራት ይፈቀድላቸዋል ቤቱም ወይም ምኩራቡም ትንሽ ወይም ትልቅ ሊሆን ይችላል።/የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃል ገጽ ፷ /

#ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው ሲያስተምር፥ ሁሉም ያመሰግኑት ነበር።

ይህ ምኩራብ እየተባለ የሚጠራው የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደ ነገራቸው ይዘከርበታል፦

ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ #እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና
ተቀመጠ፤ በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር። እርሱም። ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ይላቸው ጀመር።

#ሁሉም_ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው ቃል የተነሣ እየተደነቁም ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? ይሉ ነበር። እርሱም፦ ያለ ጥርጥር ይህን ምሳሌ። ባለ መድኃኒት ሆይ፥ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ አድርግ ትሉኛላችሁ አላቸው። #ሉቃ.፬÷፲ ፬ -፳ ፫

ሳምንቱ ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ሌላው ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት « #ቦአ_ኢየሱስ_ምኩራበ_አይሁድ » «ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ጅራፍ ጀርፎ አንድም ከሐዋርያቱም ተቀብሎ ይላል ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የወንበዴዎች መናህሪያ አደረጋችኋት" ብሎ እየገረፈ ከመቅደስ እዳባረራቸው ገበቴያቸውምን እንደ ገለበጠ ገብያቸውንም እንደፈታባቸው የሚሰበክበት የሚተረክበት ሳምንት ጭምር በመሆኑ ነው ፡፡ #ማቴ ፳ ፩ ፥ ፲ ፪-፲ ፫ ተጠቅሷል፡፡ “ሰንበታቴን ጠብቁ፥ መቅደሴንም ፍሩ፤ #እኔ_እግዚአብሔር ነኝ።” እንዳለ መጻሕፍ #ኦ.ዘሌ ፳ ፮ ፥ ፪.
#ጌታችን_መድኃኔታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በምድር ሲመላለስ ከዚህ ቀደም በምኩራቦቻቸው ተሰምቶ የማይታወቅ የወንጌል ትምህርት እንዳስተማራቸውና ዕውራን እንዲያዩ፤ ደንቆሮዎች እንዲሰሙ፤ ዲዳዎች እንዲናገሩ በማድረግ እንዲሁም ደግሞ ሙታንን በማሥነሳት የተለያዩ ድንቅ ተአምራቶችን በማድረግ የወንጌልን ኃይል ስለማሳየቱ ይተረክበታል።

"እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ (የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና) #መዝ ፷ ፰ ( ፷ ፱ )፥ ፱ ተብሎ እንደተጻፈ ሕገ እግዚአብሔር እንዲፈጸም፤ ሕገ ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ፤ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዳይበላሽ በአይሁድ ምኩራብ በመግባትእንዳስተማረ ሁሉ ዛሬም እያንዳንዳችን የቤተ ክርስቲያንን ነገር ለቤተ ክርስቲያን በማድረግ በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ነገርን ብቻ በመሥራት ለቤተክርስቲያ የሚገባትን ቦታ መስጠት እንደሚገባ ይስበክበታል። ይልቁኑ በአርያ ሥላሴ የተፈጠረ ሰውነታችን ምኩራብ እየተባለ ይጠራል በዚህ ሰውነት ኃጢያትን መሸጥ መለውጥ ማርከስ እንደማይገባም ልብ ሊባል ይገባል። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ፦ ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን?አሉት። #እርሱ_ግን_ስለ_ሰውነቱ_ቤተ_መቅደስ ይል ነበር። #ዮሐ ፪÷፲ ፱-፳ ፩ “ #የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ #የእግዚአብሔርም_መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ” ማንም #የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ #እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ #የእግዚአብሔር_ቤተ_መቅደስ_ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።” #፩ኛ_ቆሮንቶስ ፫ ፥ ፲ ፯

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፲ ፩/ ፳ ፻ ፲ ፫.ዓ.ም
#በቅዱሳት መጻሕፍት አስተምህሮ " #ራስ " የክብር የበላይነትን የልዕልና መገለጫ ነው። ቤተ ክርስቲያናችንም ርዕሰ ዕሩሳን ክርስቶስ ርዕሳተ ደናግል ድንግል ማርያም ርዕሰ ነቢያት ሙሴ፣ ርዕሰ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ፣ ርዕሰ ባሕታዊያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እያለች ታስተምራለች።
በሀገራች ታሪክም ከሥልጣን ማዕረጋት መካከል የራስነት ማዕረግ የተለመደ ነው። ራስ ተፈሪ፣ ራስ አሊ ፣ራስ መኮንን እንደሚባለው ። ዛሬ ዛሬ ግን ይህ ስም የዘፈን ናዝራዊያን የሆኑ ሰዎች ፀጉራቸውን በማስረዘም ራስ(ራስታ) ተብለው የጨለማው ዓለም ገዢ ኤሮድስን ለማስደሰት የሚዘፍኑ የዘማዊያን መጠሪያ ሆኗል።
#ሄሮድስ የወንድሙ የፊልጶስ ሚስት ሄሮድያዳን ያገባት ዘንድ ፈለገ ዮሐንስ ግን እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም አለው። ሊገድለውም ወዶ ሳለ፥ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስለ አዩት ፈራቸው። አሳስሮት በወህኒ(እስር ቤት) ዘጋበት፤ ነገር ግን ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው፤ ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት።
እርስዋም በእናትዋ ተመክራ፦ የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው። ንጉሡም አዘነ፥ ነገር ግን ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ተቀምጠው ስላሉት ሰዎች እንዲሰጡአት አዘዘ፤ ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።
#ራሱንም በወጭት አምጥተው ለብላቴናይቱ ሰጡአት፥ ወደ እናትዋም ወሰደችው ። እናቷ የሄሮድያዳ የነቢዮን ራስ በወጪት ይዛ ምላሱን ወደ ውጪ አውጥታ አንቺ ነሽ የንጉሥ ሚስት ሆኜ ንግሥት እንዳልባል ያደረግሽኝ እያለች በወስፌ ትወጋው ትጠቀጥቀው ነበር የነቢዩ እራስም ክንፍ አውጥታ በራ ሄዳ ለ15 ዓመታት ዞራ ወንጌልን ሰብካለች #ማቴ 14÷3-12
አንባቢ ሆይ ዘፈንን ዕርም ብለህ ተው። ዘፋኞች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አይገቡምና #ገላ 5÷16 ደግሞ እኔ አልዘፍንም የሚዘፍኑትን እሰማለው፣ዐያለው እንጂ አልክን ? ሄሮድስን ለዘፉኝ ወለታ የነቢይ ራስን እንዲሰጥ ያደረገው ዘፈን መስማትና ማየቱ አይደለምን? ሄሮድስ ቅዱስ ዮሐንስን የመሰለ ርዕሰ ያጣው ዘፈንን በማየቱና በመስማቱ ነው። ዘፉኝ ካየህ ዘፈን ከሰማህ እራስህን ታጣዋለህ ራስ ክርስቶስን ነው ነውና እራስህን ጠብቅ ።
#ራስ የአካል ሁሉ መዲና ናት አካል ያለ ራስ ምንም ነው ወይም በድን ነው እራስ ግን ያለ አካል ሕያው ሆኖ መቆም ይቻለዋል። ለዚህም የነቢዮ ዮሐንስ ራስ ሆነኛ ምስክር ናት ከአካል ከተለየች በኋላ 15 ዓመት ዞራ አስተምራለችና። መጋቢ አዲስ የኔታ እሸቱ እንዳሉት የሰው ዋነኛ መገለጫው ራስ ነው ሰው ለመታወቂያ የሚያገለግል ፎቶግራፍ እንኳን የሚነሳው ከአንገቱ በላይ ያለውን የራሱን አካል ነው እንጂ እግሩን ወይም ደረቱን አይደለም።
ዋና ዋና ስብአዊ ተግባራት የሚፈጸሙትም እራስ ላይ ባሉ ልዮ ልዮ ባለ ድርሻ አካላት ነው። እነማ ቢሉ ዐይን ፣ጀሮ፣ አፍንጫ ፣አፍ /ምላስ። ገድለ ጊዮርጊስ ደግሞ አዳሪ በማኅደሩ ማኅደሩም በአዳሪው የመጥራት የመጻሕፍት ልማድን ተጠቅሞ ዐይን ፣ጀሮ፣ አፍንጫ ፣አፍ /ምላስ በማደሪያቸው በራስ ቅል አማካኝነት ራስ ተብለው ሊጠሩ ይችላሉ ይላል። ግሩም ነው ! ዳዊት የጎልያድን ራስ ቆረጠ ሲባል ዐይን ፣ጀሮ፣ አፍንጫ ፣አፍ /ምላስ ን አልነካም ማለት አይደለም እነርሱም በራስ ያሉ ናቸውና እነርሱም ተቆረጡ ማለት ጭምር ነው።
#እንደ እባብ ልባሞች ሁኑ በማለት የእባብ ልባምነቱ የተገለጠበት ዋነኛ ምክንያትም እባባ ከአካላቱ ሁሉ እራሱን (ጭንቅላቱን) ከምት ከዱላ መጠበቁ ነው። ወገቡ ጢቆረጥ አይሞትም ጭራው ቢበጠስ እስትንፋሱ አይቋረጥም ጭንቅላቱን ከተመታ ግን ሕያውነቱ ያከትማል ስለሆነም ጥንቅላቱን ወይም የራስ ቅሉን በከፍተኛ ጥንቃቄ ከምት ይጠብቃል። እባብን ልባም ካሰኚት ጠባዮቹ አንዱ እራሱን መጠበቁ ነው ።
እራስ የተባለች ሃይማኖት ነች ሃይማኖቱ በምንፍቅና ሀሳብ የተመታ ሰውም ምንም ምግባር ትሩፋት ቢኖረው ዋጋ የለውም የሞተ ነው እራሳችሁ የሆነች ሃይማኖታችሁን ከመናፍቃን ጥርጥር ከአሕዛብ ክሕደት ጠብቋት ሲል ነው።
#ሐዋርያው ሃይማኖቴን ጠብቄያለው ማለቱ እራሴን ጠብቂያለው በክፉዎች ምክር አልሃድኩም በኃጢያተኞችም መንገድ አልቆምኩም በዋዘኞችም ወንበር አልተቀመጥኩም ማለቱ ነው። 2ኛ ጢሞ 4፥7 መዝ1÷1 “በእግራቸው እንዳይረግጡት ተመልሰውም እንዳይነክሱአችሁ፥ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ፥ ዕንቁዎቻችሁንም በእሪያዎች ፊት አትጣሉ።” #ማቴ 7፥6

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መስከረም ፪ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#እንደ_ልቤ ከሆነ ከጻድቁ ልጅ #ከዳዊት ሃብታት አንዱ ሲገለጥ !

#ሃብተ_ዝማሬ
|በስባረ ሐጽምህ በፈሰሰው ደምህ
በፈጸምከው ገድልህ ባማላጅነትህ
ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ እርዳን በጸሎትህ

ሐዲስ ዝማሬ #በዘማሪ ዳዊት ክብሩ
#በቅዱሳት መጻሕፍት አስተምህሮ " #ራስ " የክብር የበላይነትን የልዕልና መገለጫ ነው። ቤተ ክርስቲያናችንም ርዕሰ ዕሩሳን ክርስቶስ ርዕሳተ ደናግል ድንግል ማርያም ርዕሰ ነቢያት ሙሴ፣ ርዕሰ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ፣ ርዕሰ ባሕታዊያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እያለች ታስተምራለች።
በሀገራች ታሪክም ከሥልጣን ማዕረጋት መካከል የራስነት ማዕረግ የተለመደ ነው። ራስ ተፈሪ፣ ራስ አሊ ፣ራስ መኮንን እንደሚባለው ። ዛሬ ዛሬ ግን ይህ ስም የዘፈን ናዝራዊያን የሆኑ ሰዎች ፀጉራቸውን በማስረዘም ራስ(ራስታ) ተብለው የጨለማው ዓለም ገዢ ኤሮድስን ለማስደሰት የሚዘፍኑ የዘማዊያን መጠሪያ ሆኗል።
#ሄሮድስ የወንድሙ የፊልጶስ ሚስት ሄሮድያዳን ያገባት ዘንድ ፈለገ ዮሐንስ ግን እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም አለው። ሊገድለውም ወዶ ሳለ፥ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስለ አዩት ፈራቸው። አሳስሮት በወህኒ(እስር ቤት) ዘጋበት፤ ነገር ግን ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው፤ ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት።
እርስዋም በእናትዋ ተመክራ፦ የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው። ንጉሡም አዘነ፥ ነገር ግን ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ተቀምጠው ስላሉት ሰዎች እንዲሰጡአት አዘዘ፤ ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።
#ራሱንም በወጭት አምጥተው ለብላቴናይቱ ሰጡአት፥ ወደ እናትዋም ወሰደችው ። እናቷ የሄሮድያዳ የነቢዮን ራስ በወጪት ይዛ ምላሱን ወደ ውጪ አውጥታ አንቺ ነሽ የንጉሥ ሚስት ሆኜ ንግሥት እንዳልባል ያደረግሽኝ እያለች በወስፌ ትወጋው ትጠቀጥቀው ነበር የነቢዩ እራስም ክንፍ አውጥታ በራ ሄዳ ለ15 ዓመታት ዞራ ወንጌልን ሰብካለች #ማቴ 14÷3-12
አንባቢ ሆይ ዘፈንን ዕርም ብለህ ተው። ዘፋኞች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አይገቡምና #ገላ 5÷16 ደግሞ እኔ አልዘፍንም የሚዘፍኑትን እሰማለው፣ዐያለው እንጂ አልክን ? ሄሮድስን ለዘፉኝ ወለታ የነቢይ ራስን እንዲሰጥ ያደረገው ዘፈን መስማትና ማየቱ አይደለምን? ሄሮድስ ቅዱስ ዮሐንስን የመሰለ ርዕሰ ያጣው ዘፈንን በማየቱና በመስማቱ ነው። ዘፉኝ ካየህ ዘፈን ከሰማህ እራስህን ታጣዋለህ ራስ ክርስቶስን ነው ነውና እራስህን ጠብቅ ።
#ራስ የአካል ሁሉ መዲና ናት አካል ያለ ራስ ምንም ነው ወይም በድን ነው እራስ ግን ያለ አካል ሕያው ሆኖ መቆም ይቻለዋል። ለዚህም የነቢዮ ዮሐንስ ራስ ሆነኛ ምስክር ናት ከአካል ከተለየች በኋላ 15 ዓመት ዞራ አስተምራለችና። መጋቢ አዲስ የኔታ እሸቱ እንዳሉት የሰው ዋነኛ መገለጫው ራስ ነው ሰው ለመታወቂያ የሚያገለግል ፎቶግራፍ እንኳን የሚነሳው ከአንገቱ በላይ ያለውን የራሱን አካል ነው እንጂ እግሩን ወይም ደረቱን አይደለም።
ዋና ዋና ስብአዊ ተግባራት የሚፈጸሙትም እራስ ላይ ባሉ ልዮ ልዮ ባለ ድርሻ አካላት ነው። እነማ ቢሉ ዐይን ፣ጀሮ፣ አፍንጫ ፣አፍ /ምላስ። ገድለ ጊዮርጊስ ደግሞ አዳሪ በማኅደሩ ማኅደሩም በአዳሪው የመጥራት የመጻሕፍት ልማድን ተጠቅሞ ዐይን ፣ጀሮ፣ አፍንጫ ፣አፍ /ምላስ በማደሪያቸው በራስ ቅል አማካኝነት ራስ ተብለው ሊጠሩ ይችላሉ ይላል። ግሩም ነው ! ዳዊት የጎልያድን ራስ ቆረጠ ሲባል ዐይን ፣ጀሮ፣ አፍንጫ ፣አፍ /ምላስ ን አልነካም ማለት አይደለም እነርሱም በራስ ያሉ ናቸውና እነርሱም ተቆረጡ ማለት ጭምር ነው።
#እንደ እባብ ልባሞች ሁኑ በማለት የእባብ ልባምነቱ የተገለጠበት ዋነኛ ምክንያትም እባባ ከአካላቱ ሁሉ እራሱን (ጭንቅላቱን) ከምት ከዱላ መጠበቁ ነው። ወገቡ ጢቆረጥ አይሞትም ጭራው ቢበጠስ እስትንፋሱ አይቋረጥም ጭንቅላቱን ከተመታ ግን ሕያውነቱ ያከትማል ስለሆነም ጥንቅላቱን ወይም የራስ ቅሉን በከፍተኛ ጥንቃቄ ከምት ይጠብቃል። እባብን ልባም ካሰኚት ጠባዮቹ አንዱ እራሱን መጠበቁ ነው ።
እራስ የተባለች ሃይማኖት ነች ሃይማኖቱ በምንፍቅና ሀሳብ የተመታ ሰውም ምንም ምግባር ትሩፋት ቢኖረው ዋጋ የለውም የሞተ ነው እራሳችሁ የሆነች ሃይማኖታችሁን ከመናፍቃን ጥርጥር ከአሕዛብ ክሕደት ጠብቋት ሲል ነው።
#ሐዋርያው ሃይማኖቴን ጠብቄያለው ማለቱ እራሴን ጠብቂያለው በክፉዎች ምክር አልሃድኩም በኃጢያተኞችም መንገድ አልቆምኩም በዋዘኞችም ወንበር አልተቀመጥኩም ማለቱ ነው። 2ኛ ጢሞ 4፥7 መዝ1÷1 “በእግራቸው እንዳይረግጡት ተመልሰውም እንዳይነክሱአችሁ፥ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ፥ ዕንቁዎቻችሁንም በእሪያዎች ፊት አትጣሉ።” #ማቴ 7፥6

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መስከረም ፪ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#የእግዜር እጅ /The hand of God/

እግር ኳስ ከዓለማችን ስፖርቶች ሁሉ እጅግ ተወዳጅ የሆነ ስፖርት ነው። የስፖርት ዓይነቶች ብዙና አያሌ ቢሆኑም እንደ እግር ኳስ ስፖርት ግን የገነነ የለም ።

#የስፖርት ዜና እንይ ስንል እንኳ የእግር ኳስ ዘገባዎችን እንከታተል ማለታችን እንደሆነ ተደርጎ ብቻ ይታሰባል ። ይህም እግር ኳስ ሌሎች ስፖርቶች እንዳልተፈጠሩ አድርጎ በማስረሳት በብዝዎቻችን ልቡናና አእምሮ ላይ እንደነገሰ ያመላክታል።

እግር ኳስ ተወዳጅ ከመሆኑ አልፎ ተወዳጂና ታዋቂ ያደረጋቸው ሰዎችም አያሌ ናቸው። ከነዚህ ሰዎች መካከል አርጄንቲናዊው ማራዶና አንዱ ነው።

#እንደ_ግሪጎሪያን የዘመን ቀመር ጥቅምት 30 ቀን 1960 ዓ.ም ከዛሬ 60ዓመት በፊት ላኑስ ፣ ቦነስ አይረስ ፣ አርጀንቲና ከተማ ውስጥ የተወለደው ማራዶና ወይም በሙሉ ስሙ (Diego Armando Maradona) /ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና/ ዓለም የምታውቀው በእግር ኳስ ነው።

ይልቁኑ የእግዚአብሔር እጅ /Hand of God/ በመባል በምትታወቀው ግቡ በስፖርቱ ወዳጆች ልብ ውስጥ አይረሴ አድርጋ አትማዋለች ።

#ዲያጎ አርማዶ ማራዶና በ1986 በሜክሲኮ የተካሄደውን ውድድርን በበላይነት መቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ እንግሊዝን በተሸነፈበት የ1-1 የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በዓለም ዋንጫው ውስጥ በጣም የማይረሱ ሁለት ግቦችን አስቆጠረ።

ከነዚህም አንዷ በጭንቅላቱ መግጨት እንደማይሆንለት ሲረዳ እስከሚችለው ከዘለለ በኋላ በቴክኒክ እጁን በመጠቀም ኳሷን ወደ ግብነት ቀየራት ዳኛው በጭንቅላቱን ገጭቶ እንዳገባው አስበው አጸደቁለት። በኃላ ግን በጭንቅላት ሳይሆን በእጅ እንደተቆጠረች የዓለም ሕዝብ ዐወቀ ግቧም “የእግዚአብሔር እጅ ግብ” በመባል የምትታወስ ግብ ሆነችለች፡፡ ዛሬ ድረስ ማራዶና ሲነሳ ይህች ግብ አብራው ትነሳለች።

#በሁላችንም የሕይወት እግር ኳስ ውስጥ አናስተውላትም እንጂ የእግዚአብሔር እጅ አለች ከጅምሩ አጥንት ሰክቶ ጅማት ወጥሮ ደም አሰራጭቶ ያበጃጀን ይህው የእግዚአብሔር እጅ ነው በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ የሌለችበት ጊዜና ቦታ የለም "ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ #እጅህ_ትመራኛለች_ቀኝህም_ትይዘኛለች " እንዲል ነቢዩ መዝ138(139)÷8-10

እነ_ቫር እና ጎል ላይን ቴክኖሎጂ ሳይመጡ በፊት እግር ኳስ ከነ ወዙ መቆየት ችሎ ነበር አሁን አሁን ግን ጨዋታ ሁሉ ቆሞ በቴክኖሎጂ እገዛ ፍርድ የሚቀለበስበት ሁኔታ ተፈጥሯል ይህም የተወዳጁን የእግር ኳስ እስፖርት አዝናኝ ኩነቶች በእጅጉ አደብዝዘውታል ።

#በእግር ኳስ ጨዋታ ውስጥ ከበረኛና የእጅ ከሚወረውር ተጫዋች በቀር ኳስን ሆን ብሎ በእጅ መንካት አይፈቀድም ወይም እጅን ወደ ኳስ ማምጣትና መንኳት ክልክል ነው። ካልሆነ ግን "ማኖ" ብሎም የቅጣት ምቶችን ያስከትላል ከፍ ሲልም በቢጫና በቀይ ካርዶች ከጨዋታው ሊያስወጣ ይችላል። ታዲያ ይህች የማራዶና ግብ እንዴት ከግብ ተቆጠረች? ብለክ ታስብ ይሆናል መልሱ ቀላል ነው "የእግዚአብሔር እጅ" ስለሆነች ነው። የእግዚአብሔር እጅ ማኖ የላትም

ምድራዊ ሕግ በእጅህ እዳትነካ ቢያስጠነቅቅህም የእግዚአብሔር እጅ ካንተ ጋር ካለች እግር ኳሱን ቅርጫት ኳስ ብታደርገው እንኳ ዓላማህ ግብን ይመታል ። ባርም ጎል ላይን ቴክኖሎጂም አይቃወሙህም።

#ይህ_ሲባል ግን ወዳጄ የእግዚአብሔር እጅ አጭበርባሪውንና አታላዮን ትወዳለች ከእርሱ ጋርም ታብራለች ማለት አይደለም። የቤቱ ሁለተኛ ልጅ ብትሆንና ብኩርናን አጥብቀህ ብትሻት መሻትህን አውቆ እንደ ያዕቆብ ፊተኛ ያለው ቀዳማዊ ፣ተከታይ የሆነ መሪ ፣ታላቅ ያለው በኩር ያደርግሃል ማለቴ ነው። እንደ ዔሳው ካቃለልካት፣ በኩርናህን ካልጠበካት ፣ በምስር ወጥም ከሸጥካት ግን የመጀመሪያው መጨረሻ አንተ ትሆናለህ በእግር ብታገባው እንኳን ግብ የተሻረ ይሆናል ፊተኞች ዋለኞች ዋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ የሚለው ቃል የሚከወነው በሰው መሻትና በእግዚአብሔር እጅ እንደሆነ ዕወቅ። #ዘፍ25÷34

#የእግዚአብሔር እጅ ተንጠራርተው ከግባቸው ላልደረሱ ብቻ ትቀጠላለች እንጂ ባሉበት ቆመው ያለ ጥረት ተአምር ለሚጠብቁት አትቀጠልም ሞክረህ ባቃተ ጊዜ ብቻ እርዳታ ጠይቅ አቤቱ ከአርያም ክድህን ስደድልኝ በለው።

በባለጋራዬ በሥጋ ፍቃድ፣በሰይጣን ፈተና ፣ በዓለም መውጊ ተውግቼ መሸነፍ አልፈልግም አድነኝ ብለ ጥራው እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ፈጥና ታድንለች በጠላቶችህ ላይም ድልን ታቀዳጅሃለች። “ #እነሆ_የእግዚአብሔር_እጅ ከማዳን አላጠረችም ፤ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም "
#ኢሳ 59፥1

#እኔም_እንደ_ፔሌ አንድ ቀን በሰማይ ኳስ እንገፋለን ባልለውም ይህን የዓለማችን የእግር ኳስ ፈርጥ ግን ነብስህን ይማራት ሳልል ማለፍ አልፈልግም 🙏!

#Thank_you Armando

ኃ/ማርያም
አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር 3/2013 ዓ.ም
መድኃኔዓለም

#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!? ከእርሱ ሴትን ፈጠረ።የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ።ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ።" (ቅዱስ ኤፍሬም)

#እንደ ክርስቲያን ይህንን ቃል በሐሙስ ውዳሴ ማርያም ላይ ባነበብን ቁጥር የቀራንዮ በግ መድኃኔዓለም በዕፀ መስቀል ላይ ከፍ ብሎ ተሰቅሎ ስለኛ ሲሞሸር እኛንም ሲሞሽረን እንመለከተዋለን።ጌታችን ይህንን ስቅለቱን "ክብር" በማለት ጠርቶታል።"ጌታችን ኢየሱስም መለሰላቸው እንዲህ ሲል የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል።"(ዮሐ 12:23) እሰቀላለሁ እሞታለሁ ማለቱ ነው።ክብሩማ ለእኛ ነው፤ፍቅር ስለሆነ በሥጋ ማርያም ድንግል ስለተዛመድንም የእኛን ክብር የራሱ ክብር አድርጎ ተናገረ።"የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ" የሚለው አነጋገር የሰው ልጅ የተባለ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ሲከብር (ሲሰቀል)፤በእርሱ የባሕርይ አምላክነት (መድኃኒትነት) ያመኑ ሁሉ ከብረው በቀኙ እንደሚቆሙ (እንደሚድኑ) ያሳያል።ለዚህ ነው በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ በመድኃኒትነቱ አምኖ የዳነው።

እንዴት በዚህ ቃል የመድኃኔ ዓለምን የሙሽርነቱን በዓል እንመለከታለን? ቢሉ

#"ከአዳም ጎን አንዲት አፅም መንሣት ምን ይደንቅ!?" እውነት ነው ያለ ተረፈ ደዌ፣ያለ ሕማም፣ያለ ቁስል የሆነ ነውና ይደንቃል።ከዚህ በላይ ደዌአችንን ከመቀበል ጋር ፤ ሕማማችንን ከመሸከም ጋር ፤ ቁስላችንን ከመቁሰል ጋር የሆነ "ከዳግማዊ አዳም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጎን የንጹሕ ውኃና የትኩስ ደም መፍሰስ ምን ይደንቅ!!!?"

#"ከእርሱ ሴትን ፈጠረ" ከቀዳማዊ አዳም ጎን ከተነሣ አፅም ሴትን(ሔዋንን) በጥንተ ተፈጥሮ ፈጠረ።ዳግማዊ አዳም መድኃኒታችን ከጎኑ ባፈሰሰው ውኃና ደምም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በአዲስ ተፈጥሮ ሠራ።ሴትን ራሷ ከሆነው ወንድ እንዳስገኛት፤ቤተክርስቲያንንም ራሷ ከሆነላት ከራሱ አስገኝቷታል። አባታችን አዳም "ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ሥጋዋም ከሥጋዬ ነው ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል" እንዳለ፤ መድኃኔዓለምም "ይህቺ ጥምቀት ከጎኔ ከፈሰሰው ውኃ ፤ ማዕዷም ከእኔ ሥጋና ደም ነው ፤ ከእኔ ከክርስቶስ ተገኝታለችና ቤተክርስቲያን ትባል" ይላል።ሔዋን መባሏ የሕያዋን እናት በመሆኗ ነበር ፤ ቤተክርስቲያንም የሕያዋን (የክርስቲያኖች) እናት ናት።

#"የሰው ፍጥረትንም ሁሉ ፈጠረ" ከአዳምና ከሔዋን "ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት" ባለው አምላካዊ ቡራኬው የሰው ፍጥረትን ሁሉ እንደፈጠረ ፤ "ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ስም አጥምቋቸው።" በሚለው አምላካዊ ትእዛዙ ክርስቲያኖችን ሁሉ ፈጠረ።

#"ጌታ የአብ ቃል ተሰጠ" የጌቶች ጌታ፣ ቃለ አብ ፣የዓለም መድኃኒት በሥጋ ማርያም ተገልጦ ለሕማም ፣ ለመስቀል ፣ ለሞት ተላልፎ ተሰጠልን።"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል" እንዲል።እንዲህ ባለ መልኩ በዙፋኑ ዕፀ መስቀል ላይ ነግሦ አነገሠን፤ተሞሽሮ ሞሸረን፤ተርቦ አጠገበን፤ተጠምቶ አረካን፤ተራቁቶ አለበሰን፤ቆስሎ ፈወሰን፤ሞቶ ሕይወትን ሰጠን!!!

የመድኃኔዓለም ቸርነቱ አይለየን!!!
የመስቀሉን ፍቅር ያሳድርብን!!!

የካቲት 27/2016 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ