ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
" #እምዬ_ምኒልክ የታሪክ #ፈርጥ "
______________________
አፄ ምኒልክ ከአፄ ልብነድንግል ልጅ ከአቤቶ ያዕቆብ ትውልድ ሲያያዝ የመጣ የስመ ጥሩ ንጉሥ የሣህለ ሥላሴ የልጅ ልጅ የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ናቸው።
#ትውልዱም_ከአቤቶ ያዕቆብ ዠምሮ ቢቆጠር አፄ ምኒልክ ፲ ፫ ተኛ ይሆናሉ፤ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴ ና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም ቅዳሜ ነሐሴ ፲ ፪ ቀን ፲ ፰ ፻ ፴ ፮ ዓ.ም. ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደዋል፤ ከዚያም በ አንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ።
አያታቸው ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የልጁን መወለድ ሲሰሙ “ምን ይልህ ሸዋ” በሉት ብለው ስም አወጡ። እሳቸው “…ምኒልክ በሚል ስም የሚነግሥ ንጉሥ ኢትዮጵያ ን ታላቅ ያደርጋታል” የሚል ትንቢት ስለነበር ‘ምኒልክ’ የኔ ስም ነው ብለው ነበር። ሆኖም፣ በህልማቸው ከልጁ ጋር አብረው ቆመው ከሳቸው ጥላ የልጁ ጥላ በልጦ፤ በእግር የረገጡትን መሬት ሲያለካኩ እሳቸው ከረገጡት ልጁ የረገጠው ረዝሞ አዩ።
#ከዚህ በኋላ “ምኒልክ የኔ ስም አይደለም። የሱ ነው። ስሙን ምኒልክ በሉት” ብለው አዘዙ ። ይላል ( ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፉ /ገጽ ፲፪)
አፄ ምኒልክ በተወለዱ በ፲ ፩ ዓመት በ፫ ወር በሺ ፰ ፻ ፵ ፰ ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ወደ ሸዋ በመጡ ጊዜ ይዘዋቸው ወደ ጎንደር ሄዱ ፤ በዚያም አፄ ቴዎድሮስ ብልዕነታቸውንና አስተዋይነታቸውን ተመልክተው አብረው በማዕረግ ይዘዋቸው ሲኖሩ ቆዮ በመጨረሻም ሴት ልጃቸውን ወይዘው አልጣሽ ቴዎድሮስን ዳሩላቸው።

#በዓመት_በዓል የፈረስ ጉግስ ከምኒልክ በቀር ሌላ ሰው አይታይም ነበር ይባላል። በመጨረሻ ግን አፄ ቴዎድሮስ ኢትዮጵያን አንድ አደርጋለሁ በማለት ያቀዱትን ዕቅድ ፣ በያሉበት መኳንቱና ሕዝቡ እየሸፈቱ ስላበላሹባቸው ከብስጭት የተነሳ ሰውን ሁሉ ያለ ሕግ በገደሉና ባሰሩ ጊዜ እንደዚሁ አቤቶ ምኒልክን አስረው ወደ መቅደላ ላኩዋቸው ፤ በዚያም ከታመኑ አሽከሮቻቸውና ከእናታቸው ከወይዘሮ እጅጋየሁ ጋር ሆነው ከሸዋ ባለ አባቶች ጋር ውስጥ ውስጡን እየተላላኩ ምቹ የማምለጫ ጊዜ ሲፈልጉ ወዲያው አፄ ቴዎድርስ የትግሬና የጎንደር፣ የበጌምድርም ሕዝብ ሸፍቶባቸው ወደ ላይና ወደ ታች ሲሮጡ አቤቶ ምኒልክ ከወሎዎች ጋር ውስጥ ውስጡን ተስማምተው ከመቅደላ ፲ ፰ ፻ ፶ ፯ ዓ.ም ሰኔ ፳ ፬ ቀን ሌሊት አምልጠው ወሎ ገብተው አደሩ ።
በዚህ ጊዜ አቶ በዛብህ እንደ ንጉሥ ሆነው ሸዋን ሲገዙ ይህንኑ ሰምተው ነበርና እሰሪልኝ ብለው ለወሎ ገዢ ለወዘሮ ወርቂት ገጸ በረከት ጨምረው ላኩላቸው ወይዘሮ ወርቂትም ስለ አቶ በዛብህ ሳይሆን መቅደላ ለታሰረው ልጃቸው ለውጥ አድርገው ለአፄ ቴዎድርስ ለመመለስ ምኒልክ የቁም እስረኛ አድርገው ወደ አፄ ቴዎድሮስ መልክተኛ ላኩ ።
#መልክተኞቹም ወደ መቅደላ በደረሱ ጊዜ አፄ ምኒልክ አምልጠው ስለነበር አፄ ቴዎድሮስ ተበሳጭተው እስረኛውን ሁሉ እጅና እግሩን እየቆረጡ ገደል ሲጥሉ እንዲ ተብሎ ተገጠመላቸው።

" #አፄ_ቴዎድሮስ_እጅግ_ተዋረዱ
#የሸዋን_ሰው_ሁሉ_እጅ_ነስተው_ሄዱ "

#የወይዘሮ ወርቂትም ልጅ አብሮ መጣሉን ሰሙ ስለዚህ መልክተኞቹ ተመልሰው ይህንኑ ለወዘሮ ወርቂት ነገሩ ወይዘሮ ወርቂትም በእግዚአብሔር ሥራ ተደንቀው ቦሩ ሜዳ ላይ ምኒልክን ተቀብለው፣ “ #የሸዋ_ሰው_አውራህ_መጥቷልና_ደስ_ይበልህ_ተቀበል ” ብለው አዋጅ አስነግረው፣ አጃቢ አድርገው በመለከትና እምቢልታ አሳጅበው ከሸዋ ድንበር ድረስ ላኳቸው። ሸዋን ‘ንጉሥ ነኝ’ እያሉ ይገዙ የነበሩት አቶ በዛብህ የምኒልክን ወደመሀል ሸዋ መግፋት ሲሰሙ ለመውጋት ጋዲሎ ከተባለ ሥፍራ ተሠልፈው ሲጠባበቁ፣ አንዲት ሴት እንዲህ ስትል ገጠመች።

«ማነው ብላችሁ ነው ጋሻው መወልወሉ፣
ማነው ብላችሁ ነው ጦራችሁ መሾሉ
ማነው ብላችሁ ነው ካራችሁ መሳሉ፣
የጌታችሁ ልጅ ነው ኧረ በስመ አብ በሉ»

በኃላ ግን አቶ በዛብህ ስለተሸነፈ ከዛ ሸሽተው አፍቀራ ገቡ ከዚህ በኃላ አቤቶ ምኒልክ ከሸዋ በመጡ በ፲ ዓመት ንጉሥ ተብለው ሲገዙ አቶ በዛብህ አፍቀራ ሆነው ታርቀው ለመግባት ወደ ንጉሥ አማላጅ ላኩ።
በዚህ ጊዜ ንጉሡ ሊታረቋቸው ሲያስቡ የአቶ በዛብህን ሀሳብ አውቃለው ባይ ቀርቦ " አቶ በዛብህ አሁን ታርቄ ልግባ የሚለው ከገባ በኃላ መኳንንቶን እየሰበከ ለማስከዳት ነው እንጂ በእውነት እርቅ ፈልጎ አይደለም በእውነት እርቅ ፈልጎ ከሆነ የአፈቀራን ምሽግ አስረክበኝ ይበሉትና እስቲ ያስረክብሆ?! " ብሎ ተናገረ። ንጉሥ ምኒልክም አቶ በዛብህን የአፍቀራን ምሽግ እንዲያስረክብ ጠየቁት አቶ በዛብህም እኔስ ፈቅጄ ነበር አሽከሮቼ ግን ተው አታስረክብ ይሉኛል ስላሉ ይህም በቂ ምክንያት ሆኖ ስላልተቀበሏቸው ወዲያው ተያዙና ፍርድ ተጀመረ ።
#በፍርዱም_መጀመሪያ ጋዲሎ ላይ አላስገባም ብለው መዋጋታቸውንና ሁለተኛም የአፍቀራን ምሽግ አላስረክብም ማለታቸው እየተጠቀሰ ይሙት በቃ ተብሎ ተፈርዶባቸው በጥይት ተደበደቡ በጥይትም ሲመቱ ባሩዱ ከልብሳቸው ላይ ተያይዞ ገላቸው ስለነደደ አንዲት ሴት ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ገጠመች፤

" #አንተም_ጨካኝ_ነበርክ_ጨካኝ_አዘዘብህ
#እንደ_ገና_ዳቦ_ከላይም_ከታችም_እሳት_ነደደብህ "

አፄ ምኒልክ በአባታቸው ዙፋን ተቀምጠው ንጉሥ ምኒልክ እየተባሉ ይገዙ ዠመር። እንዲህም አድርገው እስከ ፲ ፰ ፻ ፸ ዓ.ም ድረስ ለ፲ ፪ ዓመት በሙሉ የበላይነት ሸዋን ሲገዙ ኖሩ።

የጽሁፉ ግብቶች፦
- ተክለ ጻድቅ መኩሪያ " የኢትዮጵያ ታሪክ"
- ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ”

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት ፲ ፰ /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ሰኞ
#መርገመ_በለስ እና #አንጾሖተ_ቤተ መቅደስ

‹‹ያቺ በለስ ጌታ ወደርሷ ከመምጣቱ በፊት ለምልማ ቅጠል አውጥታ ነበር››
#ቅ/ዮሐንስ_አፈወርቅ

#በማለዳ(ሲነጋ) ወደ ከተማ(ሀገር) መጣ ሲል:- ጌታችን አዳም ወደ ወደቀበት ስፍራ ወደዚያ ሀገር መጣ፤ያን ጊዜም ተራበ መራቡም እንጀራና ሕብስትን ሳይሆን ስለ ሰው ድኅነት ተራበ ራሱ በወንጌልም ሲናገር ‹‹የእኔስ መብል የላከኝን የአባቴን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ነው እናንተም በላከኝ በአባቴ ታምኑ ዘንድ ነው ››ዮሐ4፤34 ፤ክርስቶስ ወደ ዓለም ሲመጣ እንደ ማለዳ ጸሐይ ነው (የቀትርም የአመሻሽም ያይደለ) የማለዳ ጸሐይ ጨለማውን ገፎ ነው የሚመጣው ክርስቶስም ጨለማ የተባለ ክፉ ከይሲ ዲያብሎስን በጽንሰቱ ድል እየነሳው ተገለጠ፤የማለዳ ጸሐይ እንደ ቀትር ፀሐይ አይፋጅም አይለበልብም ክርስቶስም ለዓለሙ ተመጥኖ የሕይወት ብርሃን ሆኖ ከመዓቱ ምሕረቱ የቀረበ ሆኖ የተገለጠ ነው፡፡ጌታችን በወንጌሉም “የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ የሚከተሉኝ የሕይወት ብርሃንን ያገኛል እንጂ በጨለማ ውስጥ አይመላለስም “ዮሐ8፤12 ሲል በቃሉትምህርት በተአምራቱ በደሙ ፈሳሽነት በብዙ ወገን ድኅነተ-ብርሃኑን ሊሰጠን በመምጣቱ ነው፡፡ ፀሐይ ለሁለቱም እኩል ታበራለች ስለርሷ ብርሃንነት ራሷም ትመሰክራለች ሆኖም ግን ጸሐይን ማየት የተሳነው ሕልውናዋን አይረዳም እንዲሁ ክርስቶስም ጸሐይ ሆኖ ለእስራኤል ቢመጣ ፀሐይነቱን ተረድተው ለሞቁት ለሰውነታቸው ኃይልን ለልብ ዓይናቸው ማየትን የሰጠ ነው፡፡
#የበለስ_ፍሬ ፡- የተባሉ ጉባኤ አይሁድ (ቤተ አይሁድ) ናቸው፤ጌታችንም የሃይማኖት ፍሬ ፈልጎባቸው ቢመጣ ከመጽሐፍተ ኦሪት ከነቢያት በቀር አላገኘም ፤የተጻፈውን በተግባር ፍሬ አልተመለከተባቸውም፡፡ ያንጊዜም ረገማት ቤተ አይሁድም ክርስቶስን ባለማመናቸው በኋላም እንደ ወንበዴ በመስቀላቸው ርግማንን አትርፈዋል፡፡ነገር ግን አይሁዳውያን ቢረገሙም እነርሱን ያልመሰሉትን ቀትቷቸዋል ማለት አይደለም፡፡ምክንያቱም ከቤተ አይሁድ እስጢፋኖስን የመሰለ ሰማዕት ተገኝቷል፤እነ ቅዱስ ጳውሎስን የመሰለ ሐዋርያም ተገኝቷል ‹‹ በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ ከእስራኤል ትውልድ ከብንያም ወገን ከዕብራውያን ዕብራዊ ኝ ስለ ሕግ ብትጠይቁ ፈሪሳዊ ነበርሁ›› #ፊል3፤5

#የበለስ_ፍሬ :- ጌታችን የረገማት በለስ አዳምና ሔዋንን የጣለች ዕጸ በለስ ናት፤ጌታም ለዘላለም ፍሬ አይገኝብሽ ማለት በሰው ላይ አትሰልጥኚ ብሎ ፍዳ መርገምን እንዳጠፋት አስረዳን፡፡ በርግጥ ፍዳ መርገሙን የፈጸመው በጽንሰት ጀምሮ በስቅለት ነው፡፡ በለስ ፍሬ የተባለ በሰው ላይ ሰልጥኖ የነበረ ምልዓተ ኃጢአት ነው መጽሐፍት ኃጢአትን በለስ ይሏታል፤ምክንያቱም የበለስ ቅጠል ሰፊ ደስ የምታሰኝ ናት እንዲሁም የኃጢአት መንገድ ወደ ጥፋት የምትወስድ ሰፊ በር ናት፤የበለስ ፍሬ በመብላትና በማላመጥ ጊዜ ጣፋጭ ናት እንዲሁ ኃጢአት ሲሠርዋት ደስ ታሰኛለች ከሠርዋት በኋላ ግን መከራ ታመጣለች በሚሠርዋት ጊዜ ጣፋጭ ከሠርዋት በኋላ ግን መራራ ናት፡፡ አዳምና ሔዋንም ለጊዜው በለሷ ጣፋጭና ውብ ሆና ታየቻቸው በውሃላ ግን መራራ ሞት አመጣችባቸው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹ከአመንዝራ ሴት ከንፈር ማር ይንጠባጠባልና አፍዋም ከቅ የለሰለሰ ነውና ፍጻሜዋ ግን እንደ እሬት የመረረ ነው ሁለት አፍ እንዳው ሰይም የተሳለ ነው እግሮችዋ ወደ ሞት ይወርዳሉ አረማመድዋም ወደ ሲዖል ነው›› #ምሳ5፤3-5 ማርን በቀመስናት ጊጊ ለአፍና ለጉሮሮ ጣፋጭ ናት ከዚያ በውሃላ ግን የሚጎዳ መራራ ሆኖ እናገኘዋለን፤አመንዝራም ሴት አንደበተ ለስላሳ ናት ከማር ከስኳር የሚጣፍጥ ነገርን ትናገርሃለች ወዲያውኑ መራራ ሞትም ከእርሷ ያገኝሃል ሲል ነው፡፡ አርዌ ምድር እባብም(ሰይጣን ተዋሕዷት) ሔዋንን ስትናገራት አንደበቷ የጣፈጠ ነበር፤በሽንገላዋ ግን መራራ ነበረች፡፡

#የበለስ ፍሬ:- የተባለ አዳም የበለስ ፍሬ ከበላ በውሃላ ፈርቶ የተሸሸገባት የበለስ ቅጠል ናት፡፡ ‹‹የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድ አደረጉ›› ዘፍ3፤7 አዳምና ሔዋን ፈርተው የተሸሸጉበት በለስ አስቀድሞ ዕጸ በለስን የቀጠፉባስ ዛፍ ቅጠል ነው፡፡

ነገር ግን በዚህ ቅጠል ይሸፈን ዘንድ የቁርበት ልብስ አለበሳቸው ፡፡ ጌታችን ያደረቃት በለስ ይህቺ አዳምና ሔዋን ተሸሽገውባት የነበረችውን ምክንያተ ፍዳ ወመርገም የሆነችውን ነው፡፡ ሊቁ አፈወርቅ ዕደ ወርቅ ዮሐንስ ‹‹አዳም በገነት ዕርቃኑን ሆኖ ሳለ በየትኛው ቅጠል ነበር መሸፈኛ ሰፍቶ ዕርቃኑን የሸፈነ ይህች ቅጠል እንዴት እንደደረቀች አየህን አዳም የለበሳት ዕርቃኑን የሸፈነባት አይደለችምን ጌታ ኢየሱስ ወደ ለመለመችው ዛፍ መጥቶ አዳም ዕርቃን የሸፈነባትን ቅጠል በቃ አደረቃት አዳምን ድኃ ሁኖ ስለዘገኘው ንጹሕ የሆነ የብርሃንንም
ልብስ ሰጠው ይኸውም ብርሃን ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ የተሰራ ነው ፤የበለስን ቅጠል አድርቆ የነፍስን ድኅነት ሰጠው ተድላ ደስታ ባለባት ገነት ፍጹም የሆነ የተድላ ደስታ ልብስ ተጎናጽፎ እንደ መላእክት ሕያው ሁኖ ሲኖር ከይሲ ያሳተችው አዳምን እንዴት እንደዳነ አስባለሁ›› #ግብረ_ሕማማት ገጽ 163/164 ቁ.ጀ50-54
#ፍሬ_ግን_አላገኘባትም
________________
ወንጌሉ እንዳስቀመጠው ጊዜው የፍሬ ወር አልነበረም;ለምስጢሩ ግን ወዲያውኑም ደረቀች ሲል ደግሞ ለዘመናት የሰለጠነ ፍዳ መርገም ሞት ዲያብሎስ ጠፋ ተሸረ ሲል ነው፡፡ #ኛ_ቆሮ 15÷55 ‹‹ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ፤ሲዖል ሆይ ድል መንሳትህ የት አለ››የሚለው ተፈጸመ፤ምክንያቱም አስቀድሞ በትንቢት ተነግሮ ነበርና ‹‹ከሲዖል እጅ እታደጋቸዋለሁ ከሞትም እቤዣቸዋለሁ ሞት ሆይ ቸነፈርህ ወዴት አለ ሲዖል ሆይ ማጥፋትህ ወዴት አለ ርኅራኄ ከዓይኔ ተሰወረች›› #ት.ሆሴዕ 13፤14 ክርስቶስ በሰው ላይ የሰለጠኑ ክፉ በለሶችን አድርቆ አጥፍቶልናል ይህንንም ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹‹መጥቶም ፍትወታት እያትን ኃጣውዕ ርኩሳንን አጠፋ ሁከቱን ጸጥ አደረገ ዕጸ በለስንም አድርቆ
ብሩህ በሆነ ሕይወት በሃይማኖት የበቀለውን ዕጸ መስቀል ተከለልን ›› #ግብረ_ሕማማት ገጽ 167 ቁ.104 በበለስ የመጣውንም ርግማን በዕጸ መስቀሉ ድል ነሳው ፤በለሷን ሲረግም በአንጻሩ በለስ ዕጸ መስቀልን ተከለልን፡፡
#ይህ_የከበረ የተዘረጋ መስቀል ሥሩ በምድር ጫፉ በሰማይ ያለ ቅጠሉ የማይረግፍ አበባው ለጥፋት ፍሬው ለሞት ያልሆነ ነው፡፡ባለ በገናው ነቢዩ ዳዊትም ‹‹ወይከውን ከመዕጽ እንተ ትክልት ኅበ ሙሐዘ ማይ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ ወቁጽላኒ ኢይትነገፍ -በውኃ ዳር የተተከለ በየጊዜው ፍሬውን የሚሰጥ ቅጠሉም የማይረግፍ ›› #መዝ1÷3 ክርስቶስ በዕጸ መስቀሉ ክፉ በለስ የተባሉ ዲያብሎስና ሠራዊቱን የቀጣበት ፤ዛሬም ለሚያምኑበት ወደ ሰማይ የሚያወጣ መሰላል ነው፡፡ይቺ ዕለትም መርገመ በለስ ተብላለች

#ከዚህ ቀጥሎ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደ፤ ቤተ መቅደስ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምሥያጥ /የንግድ ቤት/ ሆኖ ቢያገኘው፤ «ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች… እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት» ማቴ. 21፤13 ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸዉ፣ ገርፎም አስወጣቸዉ፣ ይህም የሚያሳየዉ ማደሪያው ቤቱ የነበርን እኛ የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታ ችንን ሁሉ እንዳራቀልን
............ #ይቆየን ..........
ግብሐት :- ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት ቤት ሰሌዳ መጽሔት