ስንክሳር ነሐሴ 7
=>+”+ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +”+
+”+ ቁጽረታ (#ጽንሰታ) ለማርያም +”+
=>ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት “ጥንተ መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን” ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ::
“ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ::”
“#ድንግል_ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው::” (#መጽሐፈ_ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
+ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
“#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
#ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ #እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው #እናታችን_ጽዮን ይላል:: +”+ (መዝ. 86:1-6) ስንክሳር ነሐሴ 7
=>+”+ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +”+
+”+ ቁጽረታ (#ጽንሰታ) ለማርያም +”+
=>ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት “ጥንተ መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን” ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ::
“ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ::”
“#ድንግል_ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው::” (#መጽሐፈ_ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
+ይሕች ዕለት
=>+”+ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +”+
+”+ ቁጽረታ (#ጽንሰታ) ለማርያም +”+
=>ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት “ጥንተ መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን” ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ::
“ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ::”
“#ድንግል_ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው::” (#መጽሐፈ_ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
+ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
“#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
#ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ #እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው #እናታችን_ጽዮን ይላል:: +”+ (መዝ. 86:1-6) ስንክሳር ነሐሴ 7
=>+”+ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +”+
+”+ ቁጽረታ (#ጽንሰታ) ለማርያም +”+
=>ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት “ጥንተ መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን” ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ::
“ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ::”
“#ድንግል_ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው::” (#መጽሐፈ_ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
+ይሕች ዕለት
ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
“#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
=>ነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ "፤ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፤" መዝ 86÷1
"፤ ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል።"
(መዝሙረ ዳዊት 87: 2)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር
>>>
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
“#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
=>ነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ "፤ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፤" መዝ 86÷1
"፤ ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል።"
(መዝሙረ ዳዊት 87: 2)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር
>>>
Audio
መዝሙር #ኦ_ማርያም
በዘማሪ #ክብሮም_ግደይ
ኦ ማርያም ተመላለሺ ሌሊት በህልሜ
ንገሪኝ ቀርበሽ ቀርበሽ ከአጠገቤ ቆመሽ
ብርቱ ጉዳይ አለኝ ላንቺ ምነግርሽ
አንድ ጊዜ ስሚኝ እባክሽ
ኦ ማርያም ኧረ ዐይኖቼ ጥቅስቅሱ
ነገ መቃብር የምትፈሱ
ኦ ማርያም ኧረ አፍንጫዬ…
ነገ ትሆናለች የምስጥ ዋሻ
ግራ ቀኝ እጄ…
ከሄደ ወዲያ ሰው አይመጣም…
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
በዘማሪ #ክብሮም_ግደይ
ኦ ማርያም ተመላለሺ ሌሊት በህልሜ
ንገሪኝ ቀርበሽ ቀርበሽ ከአጠገቤ ቆመሽ
ብርቱ ጉዳይ አለኝ ላንቺ ምነግርሽ
አንድ ጊዜ ስሚኝ እባክሽ
ኦ ማርያም ኧረ ዐይኖቼ ጥቅስቅሱ
ነገ መቃብር የምትፈሱ
ኦ ማርያም ኧረ አፍንጫዬ…
ነገ ትሆናለች የምስጥ ዋሻ
ግራ ቀኝ እጄ…
ከሄደ ወዲያ ሰው አይመጣም…
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ
#ሉቃ ፬ ÷ ፲ ፮
ምኩራብ የአይሁድ የጸሎት ሥፍራ መጠሪያ ነው። የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም ባለ ቤተ መቅደስ ሥርዓት የሚፈጸም ነበር ናቡ ከደነጹር ቤተ መቅደሱን ካፈረሰ እና ሕዝቡንም ካፈለሰ በኃላ ግን አይሁድ በየደረሱበት " #ምኩራብ" እየሰሩ ጸሎትና ትምህርት እንዲሁም ሌሎች የአምልኮ ሥርዓቶችን ያስቀጥሉ ጀምረዋል። አሥር የጎለመሱ ወንዶች ሲገኙ ምኩራብ መሥራት ይፈቀድላቸዋል ቤቱም ወይም ምኩራቡም ትንሽ ወይም ትልቅ ሊሆን ይችላል።/የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃል ገጽ ፷ /
#ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው ሲያስተምር፥ ሁሉም ያመሰግኑት ነበር።
ይህ ምኩራብ እየተባለ የሚጠራው የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደ ነገራቸው ይዘከርበታል፦
ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ #እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና
ተቀመጠ፤ በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር። እርሱም። ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ይላቸው ጀመር።
#ሁሉም_ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው ቃል የተነሣ እየተደነቁም ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? ይሉ ነበር። እርሱም፦ ያለ ጥርጥር ይህን ምሳሌ። ባለ መድኃኒት ሆይ፥ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ አድርግ ትሉኛላችሁ አላቸው። #ሉቃ.፬÷፲ ፬ -፳ ፫
ሳምንቱ ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ሌላው ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት « #ቦአ_ኢየሱስ_ምኩራበ_አይሁድ » «ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ጅራፍ ጀርፎ አንድም ከሐዋርያቱም ተቀብሎ ይላል ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የወንበዴዎች መናህሪያ አደረጋችኋት" ብሎ እየገረፈ ከመቅደስ እዳባረራቸው ገበቴያቸውምን እንደ ገለበጠ ገብያቸውንም እንደፈታባቸው የሚሰበክበት የሚተረክበት ሳምንት ጭምር በመሆኑ ነው ፡፡ #ማቴ ፳ ፩ ፥ ፲ ፪-፲ ፫ ተጠቅሷል፡፡ “ሰንበታቴን ጠብቁ፥ መቅደሴንም ፍሩ፤ #እኔ_እግዚአብሔር ነኝ።” እንዳለ መጻሕፍ #ኦ.ዘሌ ፳ ፮ ፥ ፪.
#ጌታችን_መድኃኔታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በምድር ሲመላለስ ከዚህ ቀደም በምኩራቦቻቸው ተሰምቶ የማይታወቅ የወንጌል ትምህርት እንዳስተማራቸውና ዕውራን እንዲያዩ፤ ደንቆሮዎች እንዲሰሙ፤ ዲዳዎች እንዲናገሩ በማድረግ እንዲሁም ደግሞ ሙታንን በማሥነሳት የተለያዩ ድንቅ ተአምራቶችን በማድረግ የወንጌልን ኃይል ስለማሳየቱ ይተረክበታል።
"እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ (የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና) #መዝ ፷ ፰ ( ፷ ፱ )፥ ፱ ተብሎ እንደተጻፈ ሕገ እግዚአብሔር እንዲፈጸም፤ ሕገ ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ፤ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዳይበላሽ በአይሁድ ምኩራብ በመግባትእንዳስተማረ ሁሉ ዛሬም እያንዳንዳችን የቤተ ክርስቲያንን ነገር ለቤተ ክርስቲያን በማድረግ በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ነገርን ብቻ በመሥራት ለቤተክርስቲያ የሚገባትን ቦታ መስጠት እንደሚገባ ይስበክበታል። ይልቁኑ በአርያ ሥላሴ የተፈጠረ ሰውነታችን ምኩራብ እየተባለ ይጠራል በዚህ ሰውነት ኃጢያትን መሸጥ መለውጥ ማርከስ እንደማይገባም ልብ ሊባል ይገባል። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ፦ ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን?አሉት። #እርሱ_ግን_ስለ_ሰውነቱ_ቤተ_መቅደስ ይል ነበር። #ዮሐ ፪÷፲ ፱-፳ ፩ “ #የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ #የእግዚአብሔርም_መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ” ማንም #የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ #እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ #የእግዚአብሔር_ቤተ_መቅደስ_ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።” #፩ኛ_ቆሮንቶስ ፫ ፥ ፲ ፯
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፲ ፩/ ፳ ፻ ፲ ፫.ዓ.ም
#ሉቃ ፬ ÷ ፲ ፮
ምኩራብ የአይሁድ የጸሎት ሥፍራ መጠሪያ ነው። የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም ባለ ቤተ መቅደስ ሥርዓት የሚፈጸም ነበር ናቡ ከደነጹር ቤተ መቅደሱን ካፈረሰ እና ሕዝቡንም ካፈለሰ በኃላ ግን አይሁድ በየደረሱበት " #ምኩራብ" እየሰሩ ጸሎትና ትምህርት እንዲሁም ሌሎች የአምልኮ ሥርዓቶችን ያስቀጥሉ ጀምረዋል። አሥር የጎለመሱ ወንዶች ሲገኙ ምኩራብ መሥራት ይፈቀድላቸዋል ቤቱም ወይም ምኩራቡም ትንሽ ወይም ትልቅ ሊሆን ይችላል።/የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃል ገጽ ፷ /
#ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው ሲያስተምር፥ ሁሉም ያመሰግኑት ነበር።
ይህ ምኩራብ እየተባለ የሚጠራው የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደ ነገራቸው ይዘከርበታል፦
ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ #እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና
ተቀመጠ፤ በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር። እርሱም። ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ይላቸው ጀመር።
#ሁሉም_ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው ቃል የተነሣ እየተደነቁም ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? ይሉ ነበር። እርሱም፦ ያለ ጥርጥር ይህን ምሳሌ። ባለ መድኃኒት ሆይ፥ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ አድርግ ትሉኛላችሁ አላቸው። #ሉቃ.፬÷፲ ፬ -፳ ፫
ሳምንቱ ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ሌላው ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት « #ቦአ_ኢየሱስ_ምኩራበ_አይሁድ » «ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ጅራፍ ጀርፎ አንድም ከሐዋርያቱም ተቀብሎ ይላል ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የወንበዴዎች መናህሪያ አደረጋችኋት" ብሎ እየገረፈ ከመቅደስ እዳባረራቸው ገበቴያቸውምን እንደ ገለበጠ ገብያቸውንም እንደፈታባቸው የሚሰበክበት የሚተረክበት ሳምንት ጭምር በመሆኑ ነው ፡፡ #ማቴ ፳ ፩ ፥ ፲ ፪-፲ ፫ ተጠቅሷል፡፡ “ሰንበታቴን ጠብቁ፥ መቅደሴንም ፍሩ፤ #እኔ_እግዚአብሔር ነኝ።” እንዳለ መጻሕፍ #ኦ.ዘሌ ፳ ፮ ፥ ፪.
#ጌታችን_መድኃኔታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በምድር ሲመላለስ ከዚህ ቀደም በምኩራቦቻቸው ተሰምቶ የማይታወቅ የወንጌል ትምህርት እንዳስተማራቸውና ዕውራን እንዲያዩ፤ ደንቆሮዎች እንዲሰሙ፤ ዲዳዎች እንዲናገሩ በማድረግ እንዲሁም ደግሞ ሙታንን በማሥነሳት የተለያዩ ድንቅ ተአምራቶችን በማድረግ የወንጌልን ኃይል ስለማሳየቱ ይተረክበታል።
"እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ (የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና) #መዝ ፷ ፰ ( ፷ ፱ )፥ ፱ ተብሎ እንደተጻፈ ሕገ እግዚአብሔር እንዲፈጸም፤ ሕገ ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ፤ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዳይበላሽ በአይሁድ ምኩራብ በመግባትእንዳስተማረ ሁሉ ዛሬም እያንዳንዳችን የቤተ ክርስቲያንን ነገር ለቤተ ክርስቲያን በማድረግ በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ነገርን ብቻ በመሥራት ለቤተክርስቲያ የሚገባትን ቦታ መስጠት እንደሚገባ ይስበክበታል። ይልቁኑ በአርያ ሥላሴ የተፈጠረ ሰውነታችን ምኩራብ እየተባለ ይጠራል በዚህ ሰውነት ኃጢያትን መሸጥ መለውጥ ማርከስ እንደማይገባም ልብ ሊባል ይገባል። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ፦ ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን?አሉት። #እርሱ_ግን_ስለ_ሰውነቱ_ቤተ_መቅደስ ይል ነበር። #ዮሐ ፪÷፲ ፱-፳ ፩ “ #የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ #የእግዚአብሔርም_መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ” ማንም #የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ #እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ #የእግዚአብሔር_ቤተ_መቅደስ_ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።” #፩ኛ_ቆሮንቶስ ፫ ፥ ፲ ፯
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፲ ፩/ ፳ ፻ ፲ ፫.ዓ.ም