#የእግዜር እጅ /The hand of God/
እግር ኳስ ከዓለማችን ስፖርቶች ሁሉ እጅግ ተወዳጅ የሆነ ስፖርት ነው። የስፖርት ዓይነቶች ብዙና አያሌ ቢሆኑም እንደ እግር ኳስ ስፖርት ግን የገነነ የለም ።
#የስፖርት ዜና እንይ ስንል እንኳ የእግር ኳስ ዘገባዎችን እንከታተል ማለታችን እንደሆነ ተደርጎ ብቻ ይታሰባል ። ይህም እግር ኳስ ሌሎች ስፖርቶች እንዳልተፈጠሩ አድርጎ በማስረሳት በብዝዎቻችን ልቡናና አእምሮ ላይ እንደነገሰ ያመላክታል።
እግር ኳስ ተወዳጅ ከመሆኑ አልፎ ተወዳጂና ታዋቂ ያደረጋቸው ሰዎችም አያሌ ናቸው። ከነዚህ ሰዎች መካከል አርጄንቲናዊው ማራዶና አንዱ ነው።
#እንደ_ግሪጎሪያን የዘመን ቀመር ጥቅምት 30 ቀን 1960 ዓ.ም ከዛሬ 60ዓመት በፊት ላኑስ ፣ ቦነስ አይረስ ፣ አርጀንቲና ከተማ ውስጥ የተወለደው ማራዶና ወይም በሙሉ ስሙ (Diego Armando Maradona) /ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና/ ዓለም የምታውቀው በእግር ኳስ ነው።
ይልቁኑ የእግዚአብሔር እጅ /Hand of God/ በመባል በምትታወቀው ግቡ በስፖርቱ ወዳጆች ልብ ውስጥ አይረሴ አድርጋ አትማዋለች ።
#ዲያጎ አርማዶ ማራዶና በ1986 በሜክሲኮ የተካሄደውን ውድድርን በበላይነት መቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ እንግሊዝን በተሸነፈበት የ1-1 የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በዓለም ዋንጫው ውስጥ በጣም የማይረሱ ሁለት ግቦችን አስቆጠረ።
ከነዚህም አንዷ በጭንቅላቱ መግጨት እንደማይሆንለት ሲረዳ እስከሚችለው ከዘለለ በኋላ በቴክኒክ እጁን በመጠቀም ኳሷን ወደ ግብነት ቀየራት ዳኛው በጭንቅላቱን ገጭቶ እንዳገባው አስበው አጸደቁለት። በኃላ ግን በጭንቅላት ሳይሆን በእጅ እንደተቆጠረች የዓለም ሕዝብ ዐወቀ ግቧም “የእግዚአብሔር እጅ ግብ” በመባል የምትታወስ ግብ ሆነችለች፡፡ ዛሬ ድረስ ማራዶና ሲነሳ ይህች ግብ አብራው ትነሳለች።
#በሁላችንም የሕይወት እግር ኳስ ውስጥ አናስተውላትም እንጂ የእግዚአብሔር እጅ አለች ከጅምሩ አጥንት ሰክቶ ጅማት ወጥሮ ደም አሰራጭቶ ያበጃጀን ይህው የእግዚአብሔር እጅ ነው በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ የሌለችበት ጊዜና ቦታ የለም "ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ #እጅህ_ትመራኛለች_ቀኝህም_ትይዘኛለች " እንዲል ነቢዩ መዝ138(139)÷8-10
እነ_ቫር እና ጎል ላይን ቴክኖሎጂ ሳይመጡ በፊት እግር ኳስ ከነ ወዙ መቆየት ችሎ ነበር አሁን አሁን ግን ጨዋታ ሁሉ ቆሞ በቴክኖሎጂ እገዛ ፍርድ የሚቀለበስበት ሁኔታ ተፈጥሯል ይህም የተወዳጁን የእግር ኳስ እስፖርት አዝናኝ ኩነቶች በእጅጉ አደብዝዘውታል ።
#በእግር ኳስ ጨዋታ ውስጥ ከበረኛና የእጅ ከሚወረውር ተጫዋች በቀር ኳስን ሆን ብሎ በእጅ መንካት አይፈቀድም ወይም እጅን ወደ ኳስ ማምጣትና መንኳት ክልክል ነው። ካልሆነ ግን "ማኖ" ብሎም የቅጣት ምቶችን ያስከትላል ከፍ ሲልም በቢጫና በቀይ ካርዶች ከጨዋታው ሊያስወጣ ይችላል። ታዲያ ይህች የማራዶና ግብ እንዴት ከግብ ተቆጠረች? ብለክ ታስብ ይሆናል መልሱ ቀላል ነው "የእግዚአብሔር እጅ" ስለሆነች ነው። የእግዚአብሔር እጅ ማኖ የላትም
ምድራዊ ሕግ በእጅህ እዳትነካ ቢያስጠነቅቅህም የእግዚአብሔር እጅ ካንተ ጋር ካለች እግር ኳሱን ቅርጫት ኳስ ብታደርገው እንኳ ዓላማህ ግብን ይመታል ። ባርም ጎል ላይን ቴክኖሎጂም አይቃወሙህም።
#ይህ_ሲባል ግን ወዳጄ የእግዚአብሔር እጅ አጭበርባሪውንና አታላዮን ትወዳለች ከእርሱ ጋርም ታብራለች ማለት አይደለም። የቤቱ ሁለተኛ ልጅ ብትሆንና ብኩርናን አጥብቀህ ብትሻት መሻትህን አውቆ እንደ ያዕቆብ ፊተኛ ያለው ቀዳማዊ ፣ተከታይ የሆነ መሪ ፣ታላቅ ያለው በኩር ያደርግሃል ማለቴ ነው። እንደ ዔሳው ካቃለልካት፣ በኩርናህን ካልጠበካት ፣ በምስር ወጥም ከሸጥካት ግን የመጀመሪያው መጨረሻ አንተ ትሆናለህ በእግር ብታገባው እንኳን ግብ የተሻረ ይሆናል ፊተኞች ዋለኞች ዋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ የሚለው ቃል የሚከወነው በሰው መሻትና በእግዚአብሔር እጅ እንደሆነ ዕወቅ። #ዘፍ25÷34
#የእግዚአብሔር እጅ ተንጠራርተው ከግባቸው ላልደረሱ ብቻ ትቀጠላለች እንጂ ባሉበት ቆመው ያለ ጥረት ተአምር ለሚጠብቁት አትቀጠልም ሞክረህ ባቃተ ጊዜ ብቻ እርዳታ ጠይቅ አቤቱ ከአርያም ክድህን ስደድልኝ በለው።
በባለጋራዬ በሥጋ ፍቃድ፣በሰይጣን ፈተና ፣ በዓለም መውጊ ተውግቼ መሸነፍ አልፈልግም አድነኝ ብለ ጥራው እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ፈጥና ታድንለች በጠላቶችህ ላይም ድልን ታቀዳጅሃለች። “ #እነሆ_የእግዚአብሔር_እጅ ከማዳን አላጠረችም ፤ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም "
#ኢሳ 59፥1
#እኔም_እንደ_ፔሌ አንድ ቀን በሰማይ ኳስ እንገፋለን ባልለውም ይህን የዓለማችን የእግር ኳስ ፈርጥ ግን ነብስህን ይማራት ሳልል ማለፍ አልፈልግም 🙏!
#Thank_you Armando
ኃ/ማርያም
አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር 3/2013 ዓ.ም
እግር ኳስ ከዓለማችን ስፖርቶች ሁሉ እጅግ ተወዳጅ የሆነ ስፖርት ነው። የስፖርት ዓይነቶች ብዙና አያሌ ቢሆኑም እንደ እግር ኳስ ስፖርት ግን የገነነ የለም ።
#የስፖርት ዜና እንይ ስንል እንኳ የእግር ኳስ ዘገባዎችን እንከታተል ማለታችን እንደሆነ ተደርጎ ብቻ ይታሰባል ። ይህም እግር ኳስ ሌሎች ስፖርቶች እንዳልተፈጠሩ አድርጎ በማስረሳት በብዝዎቻችን ልቡናና አእምሮ ላይ እንደነገሰ ያመላክታል።
እግር ኳስ ተወዳጅ ከመሆኑ አልፎ ተወዳጂና ታዋቂ ያደረጋቸው ሰዎችም አያሌ ናቸው። ከነዚህ ሰዎች መካከል አርጄንቲናዊው ማራዶና አንዱ ነው።
#እንደ_ግሪጎሪያን የዘመን ቀመር ጥቅምት 30 ቀን 1960 ዓ.ም ከዛሬ 60ዓመት በፊት ላኑስ ፣ ቦነስ አይረስ ፣ አርጀንቲና ከተማ ውስጥ የተወለደው ማራዶና ወይም በሙሉ ስሙ (Diego Armando Maradona) /ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና/ ዓለም የምታውቀው በእግር ኳስ ነው።
ይልቁኑ የእግዚአብሔር እጅ /Hand of God/ በመባል በምትታወቀው ግቡ በስፖርቱ ወዳጆች ልብ ውስጥ አይረሴ አድርጋ አትማዋለች ።
#ዲያጎ አርማዶ ማራዶና በ1986 በሜክሲኮ የተካሄደውን ውድድርን በበላይነት መቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ እንግሊዝን በተሸነፈበት የ1-1 የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ በዓለም ዋንጫው ውስጥ በጣም የማይረሱ ሁለት ግቦችን አስቆጠረ።
ከነዚህም አንዷ በጭንቅላቱ መግጨት እንደማይሆንለት ሲረዳ እስከሚችለው ከዘለለ በኋላ በቴክኒክ እጁን በመጠቀም ኳሷን ወደ ግብነት ቀየራት ዳኛው በጭንቅላቱን ገጭቶ እንዳገባው አስበው አጸደቁለት። በኃላ ግን በጭንቅላት ሳይሆን በእጅ እንደተቆጠረች የዓለም ሕዝብ ዐወቀ ግቧም “የእግዚአብሔር እጅ ግብ” በመባል የምትታወስ ግብ ሆነችለች፡፡ ዛሬ ድረስ ማራዶና ሲነሳ ይህች ግብ አብራው ትነሳለች።
#በሁላችንም የሕይወት እግር ኳስ ውስጥ አናስተውላትም እንጂ የእግዚአብሔር እጅ አለች ከጅምሩ አጥንት ሰክቶ ጅማት ወጥሮ ደም አሰራጭቶ ያበጃጀን ይህው የእግዚአብሔር እጅ ነው በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ የሌለችበት ጊዜና ቦታ የለም "ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ #እጅህ_ትመራኛለች_ቀኝህም_ትይዘኛለች " እንዲል ነቢዩ መዝ138(139)÷8-10
እነ_ቫር እና ጎል ላይን ቴክኖሎጂ ሳይመጡ በፊት እግር ኳስ ከነ ወዙ መቆየት ችሎ ነበር አሁን አሁን ግን ጨዋታ ሁሉ ቆሞ በቴክኖሎጂ እገዛ ፍርድ የሚቀለበስበት ሁኔታ ተፈጥሯል ይህም የተወዳጁን የእግር ኳስ እስፖርት አዝናኝ ኩነቶች በእጅጉ አደብዝዘውታል ።
#በእግር ኳስ ጨዋታ ውስጥ ከበረኛና የእጅ ከሚወረውር ተጫዋች በቀር ኳስን ሆን ብሎ በእጅ መንካት አይፈቀድም ወይም እጅን ወደ ኳስ ማምጣትና መንኳት ክልክል ነው። ካልሆነ ግን "ማኖ" ብሎም የቅጣት ምቶችን ያስከትላል ከፍ ሲልም በቢጫና በቀይ ካርዶች ከጨዋታው ሊያስወጣ ይችላል። ታዲያ ይህች የማራዶና ግብ እንዴት ከግብ ተቆጠረች? ብለክ ታስብ ይሆናል መልሱ ቀላል ነው "የእግዚአብሔር እጅ" ስለሆነች ነው። የእግዚአብሔር እጅ ማኖ የላትም
ምድራዊ ሕግ በእጅህ እዳትነካ ቢያስጠነቅቅህም የእግዚአብሔር እጅ ካንተ ጋር ካለች እግር ኳሱን ቅርጫት ኳስ ብታደርገው እንኳ ዓላማህ ግብን ይመታል ። ባርም ጎል ላይን ቴክኖሎጂም አይቃወሙህም።
#ይህ_ሲባል ግን ወዳጄ የእግዚአብሔር እጅ አጭበርባሪውንና አታላዮን ትወዳለች ከእርሱ ጋርም ታብራለች ማለት አይደለም። የቤቱ ሁለተኛ ልጅ ብትሆንና ብኩርናን አጥብቀህ ብትሻት መሻትህን አውቆ እንደ ያዕቆብ ፊተኛ ያለው ቀዳማዊ ፣ተከታይ የሆነ መሪ ፣ታላቅ ያለው በኩር ያደርግሃል ማለቴ ነው። እንደ ዔሳው ካቃለልካት፣ በኩርናህን ካልጠበካት ፣ በምስር ወጥም ከሸጥካት ግን የመጀመሪያው መጨረሻ አንተ ትሆናለህ በእግር ብታገባው እንኳን ግብ የተሻረ ይሆናል ፊተኞች ዋለኞች ዋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ የሚለው ቃል የሚከወነው በሰው መሻትና በእግዚአብሔር እጅ እንደሆነ ዕወቅ። #ዘፍ25÷34
#የእግዚአብሔር እጅ ተንጠራርተው ከግባቸው ላልደረሱ ብቻ ትቀጠላለች እንጂ ባሉበት ቆመው ያለ ጥረት ተአምር ለሚጠብቁት አትቀጠልም ሞክረህ ባቃተ ጊዜ ብቻ እርዳታ ጠይቅ አቤቱ ከአርያም ክድህን ስደድልኝ በለው።
በባለጋራዬ በሥጋ ፍቃድ፣በሰይጣን ፈተና ፣ በዓለም መውጊ ተውግቼ መሸነፍ አልፈልግም አድነኝ ብለ ጥራው እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ፈጥና ታድንለች በጠላቶችህ ላይም ድልን ታቀዳጅሃለች። “ #እነሆ_የእግዚአብሔር_እጅ ከማዳን አላጠረችም ፤ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም "
#ኢሳ 59፥1
#እኔም_እንደ_ፔሌ አንድ ቀን በሰማይ ኳስ እንገፋለን ባልለውም ይህን የዓለማችን የእግር ኳስ ፈርጥ ግን ነብስህን ይማራት ሳልል ማለፍ አልፈልግም 🙏!
#Thank_you Armando
ኃ/ማርያም
አ.አ ኢትዮጵያ
ጥር 3/2013 ዓ.ም