#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ
ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡
እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::
«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።
ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::
ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::
የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!
«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»
ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::
አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።
«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።
«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::
«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::
አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡
አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::
ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡
የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ
ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡
እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::
«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።
ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::
ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::
የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!
«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»
ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::
አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።
«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።
«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::
«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::
አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡
አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::
ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡
የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
👍16❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ዣቬር ምልክት ሲሰጣቸው ብዙ መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ከክፍሉ
ውስጥ ገቡ፡፡ ሽፍቶቹን ያዝዋቸው: ክፍሉ ውስጥ በርቶ የነበረው ሻማ
አንድ ብቻ ስለነበር ክፍሉ ውስጥ ሰው ሲበዛ ጊዜ ብዙ ጥላ በማጥለሉ እየጨለመ ሄደ።
«ሁሉንም በብረት ሰንሰለት እጆቻቸውን እሰሩ» በማለት ዣቬር አዘዘ
«በሉ ወደዚህ ኑ» የሚል ቀጭን የሴት ድምፅ ተሰማ፡፡ ሚስስ
ቴናድዬ ነበረች፡፡ ባልዋ ከለበሰችው ሰፊ ካባ ስር ተሸሽጓል፡፡
ጠንቀቅ በሉ!» ስትል በመጮህ ተናገረች::
ሽፍቶቹ በሙሉ ያለማንገራገር እጆቻቸውን ሰጥተው ሲጠፈሩ
በማየትዋ «ፈሪ ሁሉ!» ስትል አጉረመረመች፡፡
ዣቬር ፈገግ አለ፡፡ ሚስስ ቴናድዬ ወደነበረችበት አመራ፡፡
«አይጠጉኝ፧ ከዚህ ቶሎ ቢወጡ ይሻላል» ስትል በማንጓጠጥ
ተናገረች::«እምቢ ካሉ ዋጋዎን ነው የምሰጥዎት::»
«ደፋር» አለ ዣቬር፡፡ «እመቤቴ እንደ ወንድ ጢም አብቅለዋል፤ እኔ
ደግሞ እንደ ሴት ጥፍር አሳድጌአለሁ» ሲል አሾፈባት።
ዣቬር እየተጠጋት መጣ፡፡ አጠገብዋ አንዳንዴ ልጆችዋ አንዳንዴም ራስዋ የምትቀመጥበት ድንጋይ ነበር፡፡ ዘልላ ሄዳ ያንን ድንጋይ አነሳችና
ዣቬርን ለመምታት ወረወረችው:: ዣቬር ጎንበስ በማለት ራሱን አዳነ፡፡ድንጋዩ ከግድግዳ ጋር ሄዶ ተላተመ:: የግድግዳው ቀለም ፈራርሶ ወለሉን ሞላው:: ድንጋዩ ሲመለስ እየተንከባለለ ከዣቬር እግር ስር ደረሰ።
ዣቬር ወደ ባልና ሚስቱ ሄደ:: በአንድ እጁ የሴትዮዋን፤ በሌላ እጁ የወንዱን ትከሻ ጨምድዶ ያዘ፡፡
«መሣሪያ አምጡ» ሲል ጮኸ፡፡
ወዲያው የብረት ማሠሪያ መጥቶ ሁለቱ ሰዎች ተቀፈደዱ። የራስዋና
የባልዋ እጆች መቀፍደዳቸውን ባየች ጊዜ «ወይኔ ልጆቼ» በማለት ከጮኸች ኋላ ከመሬት ላይ ተዘረረች፡፡
«በእድላቸው ያድጋሉ» ሲል አፌዘባት::
ሦስቱ ፊታቸውን በከሰል ያጠቆሩና ሦስቱ ፊታቸውን በጨርቅ የሸፈኑ ሽፍቶች እጃቸው ታስሮ ቆመዋል::
«ፊታችሁን እንደሽፈናችሁ ቆዩ» አለ ዣቬር፡-
እያንዳንዳቸውን በስም እየጠራ አንዱን «እንደምን አመሸህ»፣ ሌላውን ጤና ይስጥልኝ»፤ ሌላውን ደግሞ «ብርቱም አልሰነበትክ» በማለት
ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ገና ከክፍሉ ሲገባ አንገቱን ደፍቶ ቆሞ
የነበረው እስረኛ ታወሰው::
«እስረኛውን ፍቱት» ሲል አዘዘ፡፡ «ከዚህ ቤት ደግሞ አንድ ሰው .
እንዳይወጣ?»
ይህን እንደተናገረ ከወንበሩ ላይ ሄዶ ቁጭ አለ፡፡ ከኪሱ ወረቀትና
ብዕር አውጥቶ ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠ፡፡ ቀና ብሉ «እያየ እስረኛውን ወደዚህ አምጡት» አለ፡፡
ፖሊሶቹ በዓይን ፈለጉት::
«ምነው፤ ምን ያንቀረፍፋችኋል? የት አለ ሰውዬው?» ሲል
ጮኸባቸው::
እስረኛው አባባ ሸበቶ ከዚያ አልነበረም፧ ወጥቶ ሄዷል፡፡
በሩ ላይ ፖሊስ ቆሞአል፡፡ የነበሩበት ክፍል ፎቅ ቤት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? መስኮቱ አጠገብ ፖሊስ አልነበረም:: ትርምሱ ሲበዛ ቀደም ሲል እነቴናድዬ ለማምለጫ ባዘጋጁት የገመድ መሰላል አድርጎ ሾልኮአል። የፖሊሶቹ ዓይን አርፎ የነበረው ሽፍቶቹ ላይ ነበር፡፡
«ጋኔላም!» አለ ዣቬር በጥርሶቹ መሀል፤ «ጥሩ ምስክር ይሆነን
ነበር፡፡»
በሚቀጥለው ቀን ማታ አንድ ልጅ በኃይል እያፏጨና እየዘመረ
በመንገድ ላይ ሲጓዝ ከአንድ ነገር ጋር ይጋጫል፡፡ የተጋጨው ከሴት ጋር ነበር፡፡ ለመውደቅ እንደ መንገዳገድ ይልና ወደኋላ ዞር ብሎ ይመለከታል::
«ምነው! ትልቅ ውሻ መስሎኝ ነበር፡፡»
አሮጊትዋ ገንፍላ ከተኛችበት ብድግ አለች፡፡
«የተረገምክ» አለች ፤ «ከድካም ብዛት ሰውነቴ ባይከዳኝ ምን
እንደማደርግህ አውቅ ነበር፡፡»
ልጁ ኣሁን ትንሽ ራቅ ብሎ ነበር የቆመው፡፡
«ፕስ... ፕስ...» በማለት ካሽሟጠጣት በኋላ «በካልቾ ማቅመሴ አልተሳሳትኩም ፤ አበጀሁ፤ አበጀሁ» ሲል ተናገራት፡፡
ሴትየዋ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች፡፡ ልጁ ሮጦ ሸሽ፡፡ እርሱን ለመያዝ ስትሮጥ መብራት ከነበረበት ደረሰች፡፡ የፊትዋ መሸብሸብና የወገብዋ መጉበጥ በግልጽ ታየ:: ልጁ ራቅ ብሎ ቆሞ አጤናት።
«እኔ የምወደው መልክ የለሽም» ብሎአት እያዜመ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የቤት ቁጥር 50-52 ስለደረሰ ቆመ፡፡ በሩ መቆለፉን ሲያይ በእርግጫ መታው
አመታቱ የልጅ ሳይሆን የአዋቂ ነበር፡፡ ለካስ መንገድ ተኝታ
ያያት ሴት ትከተለው ኖሮ ከነበረበት ደረሰች::
ምንድነው ነገሩ እባካችሁ? ያ ከበሩ ላይ የቆመው ማነው? የእግዜር ያለህ በሩን እየሰበሩት ነው፤ ሌቦች ከቤቴ ሊገቡ ነው» ስትል ጮኸች፡፡
ልጁ በር መደብደቡን ቀጠለ፡፡ ሴትዬዋ ትንፋሽ አጥሮአት መተንፈስዋ በግድ ሆነ፡፡
«የአሁነስ ዘረፋ ዓይን በዓይን ሆነ እንዴ?» ብላ ከጠየቀች በኋላ ልጁን አተኩራ ስትመለከተው ማን እንደሆነ አወቀችው፡፡
«እንዴ! ያ ርኩስ፤ ያ ሰይጣን ነው እንዴ!»
«ጉድ ፈላ! አሮጊትዋ ናትና» አለ ልጁ ወደኋላ እየሸሸ፡፡ «ዘመዶቼን
መጠየቅ መጥቼ እኮ ነው::»
«ከዚህ ማንም የለም፤ አንተ ጋኔል» አለች ሴትዬዋ ጥላቻዋን ከፊትዋ ላይ ለማሳየት እየሞከረች::
«አይ ምን ይላሉ እርስዎ ደግሞ፤ ታዲያ አባቴ የት ሄደ?»
«ላ ፎርስ ከተባለ ሥፍራ፡፡»
«እናቴስ?»
«ሳን ላዛር፡፡»
«እሺ፧ እህቶቼስ?»
«ሌ ማደለኔ ሄደዋል፡፡»
ልጁ ጆሮውን አከክ እያደረገ ሴትዮዋን ቀና ብሎ አያት:: ሴትዮዋ እነቴናድዬ ይኖሩበት የነበረው ቤት ጠባቂ ነበረች፡፡
«እንዴት ይሆናል?» ሲል ራሱን ጠየቀ።
ከዚያም ፊቱን አዙሮ ቀደም ሲል ያዜመው የነበረውን ዜማ እያዜመ
መንገዱን ቀጠለ፡
ቅዱስ ዴኒስና ከፕሎሜ
ጎዳና ያስ ቤት
ኢፓኒን
ማሪየስ ባጠመደው ወጥመድ ፍርድ ሲገለባበጥ አየ:: የፖሊሱ
አዛዥ እስረኞቹን ይዞ ወጣ፡፡ ማሪየስም ከነበረበት ክፍል ወዲያው ሄደ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ ወደ ጓደኛው ቤት አመራ፡፡ ከጓደኛ
ው ከኩርፌይራክ ቤት እንደደረሰም ከእርሱ ጋር ለማደር እንደመጣ ገለጸለት፡፡ ኩርፌይራክም ከመሬት ላይ ፍራሽ አነጠፈለት::
በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ከቤቱ ተመልሶ ያለበትን ቤት ኪራይ
ክፍሎ ቤቱን ለቀቀ፡፡ እቃውን በጋሪ አስጭኖ ከኩርፌይራክ ሰፈር ሄደ፡፡
ዣቬር የልጁን ስም ረስቶ ከቤቱ አገኘው እንደሆነ ብሉ ቢመጣ
አጣው:: ማሪየስን ለማግኘት ብዙ ሞከረ ፤ ግን አልተሳካለትም:: ምናልባትም ልጁ የሚደርሰውን አደጋ ላለማየት ብሎ በመፍራት ከአገር የጠፋ መሰለው::
ማሪየስ ግን ባየውና በተሰጠው ፍርድ እጅግ ተረብሾ ነበር፡፡ ሁሉም
ነገር ጨለመበት:: የሚያየው የወደፊት ተስፋ ከፊቱ ራቀ፡፡ ልቡ የተሰቀለላት ልጅና አባትዋ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ብቅ ብለው እንደገና ተሰወሩበት:: የእርሱ የወደፊት ተስፋ እነዚህ የማይታወቁ ፍጡሮች ነበሩ፡፡
ልቡ በልጅትዋ ፍቅር ታውሮአል፡፡ «ሂድና ፈልጋት» ብሎ ስሜቱን
ቢገፋፋውም ዓይኑ ማየት ስላልቻለ እንዲያው ዝም ብሎ መረበሽ፤ መጠበብ፤
መጨነቅ ሆነ፡፡ ቀቢጸ ተስፋ ተጠናወተው:: ተስፋ የተለየው ሕይወት ጨለማ ስለሆነ ፀሐይ ወጥቶ ሳለ ምድር ጨለመችበት:: ዓይኖቹ የፍቅር ረሃብተኞች ቢሆኑም ለማየት የፈለጉትን ባለማግኘታቸው ከማየት ተቆጠቡ::ጀሮዎቹ ለመስማት የፈለጉትን ድምፅ ባለመስማታቸው ሌላ ነገር ከመስማት አፈገፈጉ፡፡ ልቡ የፈለገውን ሳያገኝ ሲቀር የፍላጎቱ መጠንና ግለት እየጎላ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ዣቬር ምልክት ሲሰጣቸው ብዙ መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ከክፍሉ
ውስጥ ገቡ፡፡ ሽፍቶቹን ያዝዋቸው: ክፍሉ ውስጥ በርቶ የነበረው ሻማ
አንድ ብቻ ስለነበር ክፍሉ ውስጥ ሰው ሲበዛ ጊዜ ብዙ ጥላ በማጥለሉ እየጨለመ ሄደ።
«ሁሉንም በብረት ሰንሰለት እጆቻቸውን እሰሩ» በማለት ዣቬር አዘዘ
«በሉ ወደዚህ ኑ» የሚል ቀጭን የሴት ድምፅ ተሰማ፡፡ ሚስስ
ቴናድዬ ነበረች፡፡ ባልዋ ከለበሰችው ሰፊ ካባ ስር ተሸሽጓል፡፡
ጠንቀቅ በሉ!» ስትል በመጮህ ተናገረች::
ሽፍቶቹ በሙሉ ያለማንገራገር እጆቻቸውን ሰጥተው ሲጠፈሩ
በማየትዋ «ፈሪ ሁሉ!» ስትል አጉረመረመች፡፡
ዣቬር ፈገግ አለ፡፡ ሚስስ ቴናድዬ ወደነበረችበት አመራ፡፡
«አይጠጉኝ፧ ከዚህ ቶሎ ቢወጡ ይሻላል» ስትል በማንጓጠጥ
ተናገረች::«እምቢ ካሉ ዋጋዎን ነው የምሰጥዎት::»
«ደፋር» አለ ዣቬር፡፡ «እመቤቴ እንደ ወንድ ጢም አብቅለዋል፤ እኔ
ደግሞ እንደ ሴት ጥፍር አሳድጌአለሁ» ሲል አሾፈባት።
ዣቬር እየተጠጋት መጣ፡፡ አጠገብዋ አንዳንዴ ልጆችዋ አንዳንዴም ራስዋ የምትቀመጥበት ድንጋይ ነበር፡፡ ዘልላ ሄዳ ያንን ድንጋይ አነሳችና
ዣቬርን ለመምታት ወረወረችው:: ዣቬር ጎንበስ በማለት ራሱን አዳነ፡፡ድንጋዩ ከግድግዳ ጋር ሄዶ ተላተመ:: የግድግዳው ቀለም ፈራርሶ ወለሉን ሞላው:: ድንጋዩ ሲመለስ እየተንከባለለ ከዣቬር እግር ስር ደረሰ።
ዣቬር ወደ ባልና ሚስቱ ሄደ:: በአንድ እጁ የሴትዮዋን፤ በሌላ እጁ የወንዱን ትከሻ ጨምድዶ ያዘ፡፡
«መሣሪያ አምጡ» ሲል ጮኸ፡፡
ወዲያው የብረት ማሠሪያ መጥቶ ሁለቱ ሰዎች ተቀፈደዱ። የራስዋና
የባልዋ እጆች መቀፍደዳቸውን ባየች ጊዜ «ወይኔ ልጆቼ» በማለት ከጮኸች ኋላ ከመሬት ላይ ተዘረረች፡፡
«በእድላቸው ያድጋሉ» ሲል አፌዘባት::
ሦስቱ ፊታቸውን በከሰል ያጠቆሩና ሦስቱ ፊታቸውን በጨርቅ የሸፈኑ ሽፍቶች እጃቸው ታስሮ ቆመዋል::
«ፊታችሁን እንደሽፈናችሁ ቆዩ» አለ ዣቬር፡-
እያንዳንዳቸውን በስም እየጠራ አንዱን «እንደምን አመሸህ»፣ ሌላውን ጤና ይስጥልኝ»፤ ሌላውን ደግሞ «ብርቱም አልሰነበትክ» በማለት
ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ገና ከክፍሉ ሲገባ አንገቱን ደፍቶ ቆሞ
የነበረው እስረኛ ታወሰው::
«እስረኛውን ፍቱት» ሲል አዘዘ፡፡ «ከዚህ ቤት ደግሞ አንድ ሰው .
እንዳይወጣ?»
ይህን እንደተናገረ ከወንበሩ ላይ ሄዶ ቁጭ አለ፡፡ ከኪሱ ወረቀትና
ብዕር አውጥቶ ከጠረጴዛው ላይ አስቀመጠ፡፡ ቀና ብሉ «እያየ እስረኛውን ወደዚህ አምጡት» አለ፡፡
ፖሊሶቹ በዓይን ፈለጉት::
«ምነው፤ ምን ያንቀረፍፋችኋል? የት አለ ሰውዬው?» ሲል
ጮኸባቸው::
እስረኛው አባባ ሸበቶ ከዚያ አልነበረም፧ ወጥቶ ሄዷል፡፡
በሩ ላይ ፖሊስ ቆሞአል፡፡ የነበሩበት ክፍል ፎቅ ቤት ነው:: ታዲያ የት ሄደ? መስኮቱ አጠገብ ፖሊስ አልነበረም:: ትርምሱ ሲበዛ ቀደም ሲል እነቴናድዬ ለማምለጫ ባዘጋጁት የገመድ መሰላል አድርጎ ሾልኮአል። የፖሊሶቹ ዓይን አርፎ የነበረው ሽፍቶቹ ላይ ነበር፡፡
«ጋኔላም!» አለ ዣቬር በጥርሶቹ መሀል፤ «ጥሩ ምስክር ይሆነን
ነበር፡፡»
በሚቀጥለው ቀን ማታ አንድ ልጅ በኃይል እያፏጨና እየዘመረ
በመንገድ ላይ ሲጓዝ ከአንድ ነገር ጋር ይጋጫል፡፡ የተጋጨው ከሴት ጋር ነበር፡፡ ለመውደቅ እንደ መንገዳገድ ይልና ወደኋላ ዞር ብሎ ይመለከታል::
«ምነው! ትልቅ ውሻ መስሎኝ ነበር፡፡»
አሮጊትዋ ገንፍላ ከተኛችበት ብድግ አለች፡፡
«የተረገምክ» አለች ፤ «ከድካም ብዛት ሰውነቴ ባይከዳኝ ምን
እንደማደርግህ አውቅ ነበር፡፡»
ልጁ ኣሁን ትንሽ ራቅ ብሎ ነበር የቆመው፡፡
«ፕስ... ፕስ...» በማለት ካሽሟጠጣት በኋላ «በካልቾ ማቅመሴ አልተሳሳትኩም ፤ አበጀሁ፤ አበጀሁ» ሲል ተናገራት፡፡
ሴትየዋ ከተቀመጠችበት ብድግ አለች፡፡ ልጁ ሮጦ ሸሽ፡፡ እርሱን ለመያዝ ስትሮጥ መብራት ከነበረበት ደረሰች፡፡ የፊትዋ መሸብሸብና የወገብዋ መጉበጥ በግልጽ ታየ:: ልጁ ራቅ ብሎ ቆሞ አጤናት።
«እኔ የምወደው መልክ የለሽም» ብሎአት እያዜመ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የቤት ቁጥር 50-52 ስለደረሰ ቆመ፡፡ በሩ መቆለፉን ሲያይ በእርግጫ መታው
አመታቱ የልጅ ሳይሆን የአዋቂ ነበር፡፡ ለካስ መንገድ ተኝታ
ያያት ሴት ትከተለው ኖሮ ከነበረበት ደረሰች::
ምንድነው ነገሩ እባካችሁ? ያ ከበሩ ላይ የቆመው ማነው? የእግዜር ያለህ በሩን እየሰበሩት ነው፤ ሌቦች ከቤቴ ሊገቡ ነው» ስትል ጮኸች፡፡
ልጁ በር መደብደቡን ቀጠለ፡፡ ሴትዬዋ ትንፋሽ አጥሮአት መተንፈስዋ በግድ ሆነ፡፡
«የአሁነስ ዘረፋ ዓይን በዓይን ሆነ እንዴ?» ብላ ከጠየቀች በኋላ ልጁን አተኩራ ስትመለከተው ማን እንደሆነ አወቀችው፡፡
«እንዴ! ያ ርኩስ፤ ያ ሰይጣን ነው እንዴ!»
«ጉድ ፈላ! አሮጊትዋ ናትና» አለ ልጁ ወደኋላ እየሸሸ፡፡ «ዘመዶቼን
መጠየቅ መጥቼ እኮ ነው::»
«ከዚህ ማንም የለም፤ አንተ ጋኔል» አለች ሴትዬዋ ጥላቻዋን ከፊትዋ ላይ ለማሳየት እየሞከረች::
«አይ ምን ይላሉ እርስዎ ደግሞ፤ ታዲያ አባቴ የት ሄደ?»
«ላ ፎርስ ከተባለ ሥፍራ፡፡»
«እናቴስ?»
«ሳን ላዛር፡፡»
«እሺ፧ እህቶቼስ?»
«ሌ ማደለኔ ሄደዋል፡፡»
ልጁ ጆሮውን አከክ እያደረገ ሴትዮዋን ቀና ብሎ አያት:: ሴትዮዋ እነቴናድዬ ይኖሩበት የነበረው ቤት ጠባቂ ነበረች፡፡
«እንዴት ይሆናል?» ሲል ራሱን ጠየቀ።
ከዚያም ፊቱን አዙሮ ቀደም ሲል ያዜመው የነበረውን ዜማ እያዜመ
መንገዱን ቀጠለ፡
ቅዱስ ዴኒስና ከፕሎሜ
ጎዳና ያስ ቤት
ኢፓኒን
ማሪየስ ባጠመደው ወጥመድ ፍርድ ሲገለባበጥ አየ:: የፖሊሱ
አዛዥ እስረኞቹን ይዞ ወጣ፡፡ ማሪየስም ከነበረበት ክፍል ወዲያው ሄደ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ገደማ ሆኖአል፡፡ ወደ ጓደኛው ቤት አመራ፡፡ ከጓደኛ
ው ከኩርፌይራክ ቤት እንደደረሰም ከእርሱ ጋር ለማደር እንደመጣ ገለጸለት፡፡ ኩርፌይራክም ከመሬት ላይ ፍራሽ አነጠፈለት::
በሚቀጥለው ቀን በጠዋት ከቤቱ ተመልሶ ያለበትን ቤት ኪራይ
ክፍሎ ቤቱን ለቀቀ፡፡ እቃውን በጋሪ አስጭኖ ከኩርፌይራክ ሰፈር ሄደ፡፡
ዣቬር የልጁን ስም ረስቶ ከቤቱ አገኘው እንደሆነ ብሉ ቢመጣ
አጣው:: ማሪየስን ለማግኘት ብዙ ሞከረ ፤ ግን አልተሳካለትም:: ምናልባትም ልጁ የሚደርሰውን አደጋ ላለማየት ብሎ በመፍራት ከአገር የጠፋ መሰለው::
ማሪየስ ግን ባየውና በተሰጠው ፍርድ እጅግ ተረብሾ ነበር፡፡ ሁሉም
ነገር ጨለመበት:: የሚያየው የወደፊት ተስፋ ከፊቱ ራቀ፡፡ ልቡ የተሰቀለላት ልጅና አባትዋ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ብቅ ብለው እንደገና ተሰወሩበት:: የእርሱ የወደፊት ተስፋ እነዚህ የማይታወቁ ፍጡሮች ነበሩ፡፡
ልቡ በልጅትዋ ፍቅር ታውሮአል፡፡ «ሂድና ፈልጋት» ብሎ ስሜቱን
ቢገፋፋውም ዓይኑ ማየት ስላልቻለ እንዲያው ዝም ብሎ መረበሽ፤ መጠበብ፤
መጨነቅ ሆነ፡፡ ቀቢጸ ተስፋ ተጠናወተው:: ተስፋ የተለየው ሕይወት ጨለማ ስለሆነ ፀሐይ ወጥቶ ሳለ ምድር ጨለመችበት:: ዓይኖቹ የፍቅር ረሃብተኞች ቢሆኑም ለማየት የፈለጉትን ባለማግኘታቸው ከማየት ተቆጠቡ::ጀሮዎቹ ለመስማት የፈለጉትን ድምፅ ባለመስማታቸው ሌላ ነገር ከመስማት አፈገፈጉ፡፡ ልቡ የፈለገውን ሳያገኝ ሲቀር የፍላጎቱ መጠንና ግለት እየጎላ
👍20
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ከፕሎሜ ጎዳና ላይ ያለ ቤት
ፕሎሜ ከተባለ ጎዳና ላይ ንብረትነቱ የመንግሥት ባለሥልጣን የሆነ ባለአንድ ፎቅ ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሁለት ክፍል ቤት ከፎቁ ላይ፣ ሁለት ክፍል
ደግሞ ከምድር ቤት ነበረው፡፡ በተጨማሪ እንደ ወጥ ቤት የሚያገለግል ተጨማሪ ክፍል ፎቁ ላይ ነበረው:: ከዋናው ጎዳና ጋር የተያያዘ ትልቅ የውጭ በር ሲኖረው በአበባ ያጌጠ ሰፊ ግቢ አለው:: ከበስተጓሮው እንደ
እቃና ማድቤቶች ሊጠቅሙ የሚችሉ ሌሎች ሦስት ክፍሎች ነበሩ:: በጓሮ በኩል ደግሞ የምሥጢር በር አለው::
ምስጢሩን ለሚያውቅ እንጂ ይህ
በር፣ በር መሆኑ በቀላሉ አይታይም:: ቤቱ ብዙ ጊዜ ሰው አይከራየውም::
በ1829 ዓ.ም አንድ በእድሜ በሰል ያለ ሰው መጥቶ ይህን ቤት
ይከራየዋል፡፡ ሰውዬው ብቻውን አልነበረም:: አንዲት ወጣት አብራው ነበረች፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ወጣትዋ ልጅ ደግሞ ኮዜት ናት፡፡ ቀደም ሲል ዣን ቫልዣ ይረዳት የነበረችው አሮጊት ደግሞ አብራቸው ናት:: ስምዋ ቱሴይ ይባላል:: ዣን ቫልዣ ቤቱን የተከራየው መሴይ ፎሽለማ በሚል ስም ነው::
ዣን ቫልዣ ለረጅም ጊዜ የኖረበትን ገዳም ለቅቆ ከወጣ በኋላ ምን
ተፈጸመ ቢባል ምንም የሆነ ነገር የለም:: እንደሚታወሰው ዣን ቫልዣ ገዳሙ ውስጥ ደስ ብሎት ነበር የሚኖረው:: በየቀኑ፡ ኮዜትን ያገኛታል።በተገናኙ ቁጥር ፍቅራቸው እየጠናና የአባትነት ስሜቱ እየዳበረ ይሄዳል፡፡
ልጅትዋን ፈጣሪ የሰጠው ፀጋ እንደሆነች ከማነ ባሻገር ይህችን ልጅ ከእርሱ ማንም ሊለያት እንደማይችል ገምቷል:: እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ከእርሱ የማትለይ ፍጡር ለመሆንዋ አልተጠራጠረም:: ይህም ደስታውን እጥፍ አደረገለት፡፡ ነገር ግን ልጅትዋን የግሉ ሀብት አድርጎ በመቀበልና የደስታው ምንጭ እንድትሆን በማድረጉ በመጠኑም ቢሆን የሕሊና ወቀሣ
ነበረበት::
ይህቺ ልጅ ገና እምቡጥ ናት:: ምንም ነገር አታውቅም:: ሕይወትዋን እንደፈቀደ የሚመራው ዣን ቫልዣ ነው:: ይህንንም ያደረገው ከክፉ ነገር
ላይ እንዳትወድቅ በማሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን ዓይነቱ አስተዳደግ የዓለምን ምንነት ለማወቅ እድል አልሰጣትም:: የራስዋን እድል ራስዋ ልትወስን አልቻለችም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሰውዬው ይህቺን ልጅ እንደ ቦይ ውሃ የመራት ከእርሱ እንዳትሄድ እንጂ ሙሉ በመሉ ለእርስዋ ብሎ አልነበረም፡፡
ይህ ነው የሕሊና ወቀሣ ያስከተለበት::
ከመነኩሴ ትምህርት ቤት ያስገባት እርሱ ነው:: መነኩሲት እንድትሆን የወሰነው እርሱ በመሆኑ ምናልባት ስታድግ በዚህ የተነሣ ልትጠላው ትችላለትች፡ ይህንና ይህን የመሳሰለ አሳቦች ናቸው ገዳሙን ለቅቆ እንዲወጣ
ያደረጉት:: ከዚህ ለመውጣት ከውሳኔ አሳብ ከደረሰ በኋላ አልቆየም::ግቢውን ለቅቆ ለመውጣት ጥሩ አጋጣሚ እየጠበቀ ሳለ ሽማግሌው ፎሽለማ መሞታቸው በዚሁ ሳቢያ ግቢውን ለቅቆ ወጣ፡፡
ከገዳሙ ሲወጣ ለገዳሙ አለቃ የነገራቸው ወንድሙ በመሞታቸውና እንደ እርሳቸውም መሞት የተነሣ መጠነኛ ሀብት ስለወረሰ ሌላ ቦታ ሄዶ መኖር የሚችል መሆኑን ነበር፡፡ ስለዚህ ልጁን ይዞ ያለ ብዙ ድካም ከሌላ
ቦታ ለመኖር የወሰነ መሆኑን ሲነግራቸው አልተቃወሙትም:: ልጅትዋን በማስተማር ገዳሙ ላበረከተው አስተዋጽኦ ለገዳሙ አምስት ሺህ ፍራንክ በስጦታ መልክ ሰጥቶ ነው የወጣው::
ከገዳሙ ሲወጣ የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅና ማንንም ሳያስቸግር
ያቺን ትንሽ ሳጥን እርሱ ራሱ በእጁ ይዞ ነው የወጣው:: የሳጥንዋን ቁልፍ ዘወትር ከእርሱ አይለያትም:: ስለሳጥንዋ ኮዜት ሁልጊዜም ትገረማለች፡፡አንድ ዓይነት የተለየ ጠረን አላት:: ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሳጥንዋን ከራሱ አይለያትም:: ሁልጊዜም የሚያስቀምጣት ከራሱ ክፍል ውስጥ ነው:: ከቦታ ወደ ቦታ በተዘዋወሩ ቀጥር እርስዋን ብቻ ነው አንጠልጥሉ የሚሄደው::
ኮዜት «ይህቺን ሣጥን ቀናሁባት» እያለች አንዳንዴ ብቻዋን ትስቃለች::
ከጊዜ በኋላ ዣን ቫልዣ ወደ ከተማ በወጣ ቁጥር እየተጨነቀ እንጂ
መዝናናትን ከተወ ሰንበት ብሉአል:: ፕሎሜ ጎዳና ላይ ካለው ቤት ውስጥ ከገባ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ከቤት አይወጣም:: ከዚያ ቤት ውስጥ እያለ ስሙ የሚታወቀው ኧልቲስ ፎሽለማ በሚል ስያሜ ነው::
እዚያው ቤት ውስጥ እያለ ሌሉች ሁለት አነስተኛ ቤቶች ከተለያዩ
ሰፈር ተከራይቶ በስሙ ይይዛል:: አልፎ አልፎ ወደ እነዚህ ቤቶች ተራ በተራ አንድ ጊዜ ከአንደኛው በሌላ ጊዜ ደግሞ ከሁለተኛው እየሄደ ወርም ሁለት ወርም ኮዜትን ይዞ ይቀመጣል:: አሮጊትዋን ግን ይዟት አይሄድም፡፡ይህንንም ያደረገው ከፖሊሶች ለመሰወር ነበር፡፡
ከቤት ውስጥ ሲሆኑ ቤቱን የምትመራው ኮዜት ናት ገዳም ውስጥ እያለች ስለቤት አያያዝ ትምህርት ቀስማለች:: ብዙውን ጊዜ ዣን ቫልዣ በጓሮ በኩል ከነበሩት ቤቶች ውስጥ ሲቀመጥ ኮዜት ከትልቁ ቤት ውስጥ
ፎቅ ላይ ነው የምትቀመጠው:: በየቀኑ ዣን ቫልዣ የኮዜትን እጅ እየያዘ ከዚያ ከተንጣለለውና ስአበባ ከአጌጠው ግቢያቸው ውስጥ ይንሸራሽራሉ፡፡
ወደ ከተማ የሚወጠበት ቀን
ውሰን ነው:: እሑድ እሑድ ግን
ወደ ውጭ ወጣ ብለው ይንሸራሸራሉ በዚህ ጊዜ የኮዜትን ቁንጅና ተመልካች እየበዛ መጣ በርግጥ እርሷም ሁሌ የምታስበው ነው ለሽርሽር በወጡ ቁጥር ወንዶች ሰብሰብ ብለው አንዱን አፍጥጣ ስታይ አንድ ሰው ‹‹በእርግጥም ቆንጆ ነሽ የሚላት መሰላት::ትንሽ ተሽኮረመመች:: ያን እለት ማታ ጥሩ እንቅልፍ አልተኛችም፡፡ ከተኛች በኋላ «እውነትም ቆንጆ ነኝ፤ የወንዶች ልብ አሁን እኔን ይመኛል?»
ስትል ብዙ አሰበች:: ገዳም ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የምታውቃቸውን ጓደኞችዋን በማስታወስ መልክዋን ከእነርሱ መልክ ጋር ማነፃፀር ጀመረች::
«እኔ እኮ ከእገሊት አላንስም፡፡ እገሊትም ብትሆን እስከዚህም የምትደነቅ ልጅ አይደለችም፡፡ ውይ እገሊት ግን በጣም ቆንጆ ናት:: እኔን ትበልጠኛለች ብቻ ምንዋ ነው ከእኔ የሚበልጠው?» እያለች ስለውበትዋ ታሰላስል
ጀመር::
አንድ ቀን ከግቢው ውስጥ እየተንሸራሸረች ሳለ አሮጊትዋ ቱሴይ
«ጌታዬ ይህቺ ልጅ እንዴት እየቆነጀች እንደሄደች ልብ ብለዋል?» ብላ ስትናገር ትሰማለች:: አባትዋ ምን መልስ እንደሰጠ ግን አልሰማችም::
የቱሴይ ንግግር ግን ስሜትዋን ነካው:: እየሮጠች ወደ ክፍልዋ ሄደች::
ከመስታወት ፊት ቆማ መልክዋን አየችው:: መስታወት በማየት መልክዋ ካስደነገጣት አንድ ሦስት ወር ያህል አልፎአል፡፡ የመጀመሪያው ቀን ሰው
ሳያያት ትንሽ አልቅሳለች:: የምታየው ራስዋን ሳይሆን የሌላ ሰው መስሎአት ነበር።
በጣም ቆንጆ ለመሆንዋ ለሁለተኛ ጊዜ አረጋገጠች:: መስታወቱና
ቱሴይ ያሉት ነገር ትክክል እንደሆነ አልተጠራጠረችም:: ቅርጽዋ፣ የቆዳዋ ቀለም፣ ፀጉርዋ፣ ዓይንዋ፣ ጥርስዋ፣ አፍንጫዋ ይህ ቀረሽ የምትባል ልጅ አልነበረችም:: ውበትዋ እንደጠዋት ፀሐይ ፊትዋ ላይ በራ፤ ተንጸባረቀ፣ ደመቀ፡፡ ወደ አበባው ቦታ ተመለሰች:፡ ወፎች ስለእርስዋ የሚዘምሩ መሰላት።
ራስዋንም እንደ ንግሥት ለመቁጠር ቃጣች::
ተመልሳ ስትመጣ ዣን ቫልዣ በአያት ጊዜ ልቡ ደነገጠ፡፡ የኮዚት
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ከፕሎሜ ጎዳና ላይ ያለ ቤት
ፕሎሜ ከተባለ ጎዳና ላይ ንብረትነቱ የመንግሥት ባለሥልጣን የሆነ ባለአንድ ፎቅ ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሁለት ክፍል ቤት ከፎቁ ላይ፣ ሁለት ክፍል
ደግሞ ከምድር ቤት ነበረው፡፡ በተጨማሪ እንደ ወጥ ቤት የሚያገለግል ተጨማሪ ክፍል ፎቁ ላይ ነበረው:: ከዋናው ጎዳና ጋር የተያያዘ ትልቅ የውጭ በር ሲኖረው በአበባ ያጌጠ ሰፊ ግቢ አለው:: ከበስተጓሮው እንደ
እቃና ማድቤቶች ሊጠቅሙ የሚችሉ ሌሎች ሦስት ክፍሎች ነበሩ:: በጓሮ በኩል ደግሞ የምሥጢር በር አለው::
ምስጢሩን ለሚያውቅ እንጂ ይህ
በር፣ በር መሆኑ በቀላሉ አይታይም:: ቤቱ ብዙ ጊዜ ሰው አይከራየውም::
በ1829 ዓ.ም አንድ በእድሜ በሰል ያለ ሰው መጥቶ ይህን ቤት
ይከራየዋል፡፡ ሰውዬው ብቻውን አልነበረም:: አንዲት ወጣት አብራው ነበረች፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ወጣትዋ ልጅ ደግሞ ኮዜት ናት፡፡ ቀደም ሲል ዣን ቫልዣ ይረዳት የነበረችው አሮጊት ደግሞ አብራቸው ናት:: ስምዋ ቱሴይ ይባላል:: ዣን ቫልዣ ቤቱን የተከራየው መሴይ ፎሽለማ በሚል ስም ነው::
ዣን ቫልዣ ለረጅም ጊዜ የኖረበትን ገዳም ለቅቆ ከወጣ በኋላ ምን
ተፈጸመ ቢባል ምንም የሆነ ነገር የለም:: እንደሚታወሰው ዣን ቫልዣ ገዳሙ ውስጥ ደስ ብሎት ነበር የሚኖረው:: በየቀኑ፡ ኮዜትን ያገኛታል።በተገናኙ ቁጥር ፍቅራቸው እየጠናና የአባትነት ስሜቱ እየዳበረ ይሄዳል፡፡
ልጅትዋን ፈጣሪ የሰጠው ፀጋ እንደሆነች ከማነ ባሻገር ይህችን ልጅ ከእርሱ ማንም ሊለያት እንደማይችል ገምቷል:: እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ከእርሱ የማትለይ ፍጡር ለመሆንዋ አልተጠራጠረም:: ይህም ደስታውን እጥፍ አደረገለት፡፡ ነገር ግን ልጅትዋን የግሉ ሀብት አድርጎ በመቀበልና የደስታው ምንጭ እንድትሆን በማድረጉ በመጠኑም ቢሆን የሕሊና ወቀሣ
ነበረበት::
ይህቺ ልጅ ገና እምቡጥ ናት:: ምንም ነገር አታውቅም:: ሕይወትዋን እንደፈቀደ የሚመራው ዣን ቫልዣ ነው:: ይህንንም ያደረገው ከክፉ ነገር
ላይ እንዳትወድቅ በማሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን ዓይነቱ አስተዳደግ የዓለምን ምንነት ለማወቅ እድል አልሰጣትም:: የራስዋን እድል ራስዋ ልትወስን አልቻለችም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሰውዬው ይህቺን ልጅ እንደ ቦይ ውሃ የመራት ከእርሱ እንዳትሄድ እንጂ ሙሉ በመሉ ለእርስዋ ብሎ አልነበረም፡፡
ይህ ነው የሕሊና ወቀሣ ያስከተለበት::
ከመነኩሴ ትምህርት ቤት ያስገባት እርሱ ነው:: መነኩሲት እንድትሆን የወሰነው እርሱ በመሆኑ ምናልባት ስታድግ በዚህ የተነሣ ልትጠላው ትችላለትች፡ ይህንና ይህን የመሳሰለ አሳቦች ናቸው ገዳሙን ለቅቆ እንዲወጣ
ያደረጉት:: ከዚህ ለመውጣት ከውሳኔ አሳብ ከደረሰ በኋላ አልቆየም::ግቢውን ለቅቆ ለመውጣት ጥሩ አጋጣሚ እየጠበቀ ሳለ ሽማግሌው ፎሽለማ መሞታቸው በዚሁ ሳቢያ ግቢውን ለቅቆ ወጣ፡፡
ከገዳሙ ሲወጣ ለገዳሙ አለቃ የነገራቸው ወንድሙ በመሞታቸውና እንደ እርሳቸውም መሞት የተነሣ መጠነኛ ሀብት ስለወረሰ ሌላ ቦታ ሄዶ መኖር የሚችል መሆኑን ነበር፡፡ ስለዚህ ልጁን ይዞ ያለ ብዙ ድካም ከሌላ
ቦታ ለመኖር የወሰነ መሆኑን ሲነግራቸው አልተቃወሙትም:: ልጅትዋን በማስተማር ገዳሙ ላበረከተው አስተዋጽኦ ለገዳሙ አምስት ሺህ ፍራንክ በስጦታ መልክ ሰጥቶ ነው የወጣው::
ከገዳሙ ሲወጣ የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅና ማንንም ሳያስቸግር
ያቺን ትንሽ ሳጥን እርሱ ራሱ በእጁ ይዞ ነው የወጣው:: የሳጥንዋን ቁልፍ ዘወትር ከእርሱ አይለያትም:: ስለሳጥንዋ ኮዜት ሁልጊዜም ትገረማለች፡፡አንድ ዓይነት የተለየ ጠረን አላት:: ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሳጥንዋን ከራሱ አይለያትም:: ሁልጊዜም የሚያስቀምጣት ከራሱ ክፍል ውስጥ ነው:: ከቦታ ወደ ቦታ በተዘዋወሩ ቀጥር እርስዋን ብቻ ነው አንጠልጥሉ የሚሄደው::
ኮዜት «ይህቺን ሣጥን ቀናሁባት» እያለች አንዳንዴ ብቻዋን ትስቃለች::
ከጊዜ በኋላ ዣን ቫልዣ ወደ ከተማ በወጣ ቁጥር እየተጨነቀ እንጂ
መዝናናትን ከተወ ሰንበት ብሉአል:: ፕሎሜ ጎዳና ላይ ካለው ቤት ውስጥ ከገባ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ከቤት አይወጣም:: ከዚያ ቤት ውስጥ እያለ ስሙ የሚታወቀው ኧልቲስ ፎሽለማ በሚል ስያሜ ነው::
እዚያው ቤት ውስጥ እያለ ሌሉች ሁለት አነስተኛ ቤቶች ከተለያዩ
ሰፈር ተከራይቶ በስሙ ይይዛል:: አልፎ አልፎ ወደ እነዚህ ቤቶች ተራ በተራ አንድ ጊዜ ከአንደኛው በሌላ ጊዜ ደግሞ ከሁለተኛው እየሄደ ወርም ሁለት ወርም ኮዜትን ይዞ ይቀመጣል:: አሮጊትዋን ግን ይዟት አይሄድም፡፡ይህንንም ያደረገው ከፖሊሶች ለመሰወር ነበር፡፡
ከቤት ውስጥ ሲሆኑ ቤቱን የምትመራው ኮዜት ናት ገዳም ውስጥ እያለች ስለቤት አያያዝ ትምህርት ቀስማለች:: ብዙውን ጊዜ ዣን ቫልዣ በጓሮ በኩል ከነበሩት ቤቶች ውስጥ ሲቀመጥ ኮዜት ከትልቁ ቤት ውስጥ
ፎቅ ላይ ነው የምትቀመጠው:: በየቀኑ ዣን ቫልዣ የኮዜትን እጅ እየያዘ ከዚያ ከተንጣለለውና ስአበባ ከአጌጠው ግቢያቸው ውስጥ ይንሸራሽራሉ፡፡
ወደ ከተማ የሚወጠበት ቀን
ውሰን ነው:: እሑድ እሑድ ግን
ወደ ውጭ ወጣ ብለው ይንሸራሸራሉ በዚህ ጊዜ የኮዜትን ቁንጅና ተመልካች እየበዛ መጣ በርግጥ እርሷም ሁሌ የምታስበው ነው ለሽርሽር በወጡ ቁጥር ወንዶች ሰብሰብ ብለው አንዱን አፍጥጣ ስታይ አንድ ሰው ‹‹በእርግጥም ቆንጆ ነሽ የሚላት መሰላት::ትንሽ ተሽኮረመመች:: ያን እለት ማታ ጥሩ እንቅልፍ አልተኛችም፡፡ ከተኛች በኋላ «እውነትም ቆንጆ ነኝ፤ የወንዶች ልብ አሁን እኔን ይመኛል?»
ስትል ብዙ አሰበች:: ገዳም ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የምታውቃቸውን ጓደኞችዋን በማስታወስ መልክዋን ከእነርሱ መልክ ጋር ማነፃፀር ጀመረች::
«እኔ እኮ ከእገሊት አላንስም፡፡ እገሊትም ብትሆን እስከዚህም የምትደነቅ ልጅ አይደለችም፡፡ ውይ እገሊት ግን በጣም ቆንጆ ናት:: እኔን ትበልጠኛለች ብቻ ምንዋ ነው ከእኔ የሚበልጠው?» እያለች ስለውበትዋ ታሰላስል
ጀመር::
አንድ ቀን ከግቢው ውስጥ እየተንሸራሸረች ሳለ አሮጊትዋ ቱሴይ
«ጌታዬ ይህቺ ልጅ እንዴት እየቆነጀች እንደሄደች ልብ ብለዋል?» ብላ ስትናገር ትሰማለች:: አባትዋ ምን መልስ እንደሰጠ ግን አልሰማችም::
የቱሴይ ንግግር ግን ስሜትዋን ነካው:: እየሮጠች ወደ ክፍልዋ ሄደች::
ከመስታወት ፊት ቆማ መልክዋን አየችው:: መስታወት በማየት መልክዋ ካስደነገጣት አንድ ሦስት ወር ያህል አልፎአል፡፡ የመጀመሪያው ቀን ሰው
ሳያያት ትንሽ አልቅሳለች:: የምታየው ራስዋን ሳይሆን የሌላ ሰው መስሎአት ነበር።
በጣም ቆንጆ ለመሆንዋ ለሁለተኛ ጊዜ አረጋገጠች:: መስታወቱና
ቱሴይ ያሉት ነገር ትክክል እንደሆነ አልተጠራጠረችም:: ቅርጽዋ፣ የቆዳዋ ቀለም፣ ፀጉርዋ፣ ዓይንዋ፣ ጥርስዋ፣ አፍንጫዋ ይህ ቀረሽ የምትባል ልጅ አልነበረችም:: ውበትዋ እንደጠዋት ፀሐይ ፊትዋ ላይ በራ፤ ተንጸባረቀ፣ ደመቀ፡፡ ወደ አበባው ቦታ ተመለሰች:፡ ወፎች ስለእርስዋ የሚዘምሩ መሰላት።
ራስዋንም እንደ ንግሥት ለመቁጠር ቃጣች::
ተመልሳ ስትመጣ ዣን ቫልዣ በአያት ጊዜ ልቡ ደነገጠ፡፡ የኮዚት
👍19❤4
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::
አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡
የማን ጥፋት ነው? የማንም::
አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።
አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡
አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::
ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::
ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::
«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::
ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::
ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::
ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡
«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::
አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::
ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::
«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡
«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!
«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡
«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::
«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::
«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!
በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::
አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡
የማን ጥፋት ነው? የማንም::
አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።
አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡
አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::
ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::
ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::
«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::
ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::
ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::
ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡
«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::
አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::
ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::
«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡
«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!
«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡
«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::
«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::
«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!
በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
👍17😱1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::
ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::
ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::
«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?
«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡
ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡
እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::
«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::
«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»
በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::
ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::
የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡
ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::
አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡
ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡
ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::
«ስምህ ማነው?»
«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::
«የአንቺስ?»
«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማምለጥ
ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::
በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል
መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::
ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::
ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::
ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::
«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?
«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡
ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡
እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::
«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::
«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»
በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::
ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::
የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡
ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::
አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡
ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡
ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::
«ስምህ ማነው?»
«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::
«የአንቺስ?»
«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማምለጥ
ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::
በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል
መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::
ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
👍21👏2❤1😁1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መማረክና መረሳሳት
ብረት በማግኔት እንደሚሳብ ፍቅረኛም ባፈቀረው ጠዋት ማታ
ይሳባል፤ ይጉተታል፡፡ ሮሚዮ በዡልየት ፍቅር ተጎትቶ በአትክልት ቦታ እንደ ተንሸራሸረ ሁሉ ማሪየስም ከኮዜት የአትክልት ሥፍራ ለመንሸራሸር ተመላለሰ፡፡ ሆኖም ማሪየስ የሮሚዮን ያህል አልተቸገረም:: ሮሚዮ ከዡልዬት
ግቢ ለመግባት ረጅም ግምብ መዝለል ነበረበት:: ማሪየስ ግን ይህ አላስፈለገውም:: የሽቦ አጥርን በቀላሉ ፈልቅቆ ነበር የሚገባው:: ቀጭን
ስለነበር ሰፊ ክፍት ቦታ አላስፈለገውም::
አካባቢውም ጭር ያለ ስለነበር ሰው ሳያየው በቀላሉ ሊገባ ቻለ፡፡
የሚመጣው ደግሞ ማታ ማታ ነው:: በዚያች በተባረከች ምሽት ከንፈር ለከንፈር ከተገናኙ ወዲህ በእየለቱ ነው የሚመጣው::
በ1832 ዓ.ም የግንቦት ወርን በሙሉ አንድ ቀን እንኳን ሳይጓደል
ማታ ማታ ተመላልሶ ከፍቅረኛው ጋር ተገናኘ:: እነዚህ ሁለት የዋህ
ፍጡሮች እንዳይገናኙ ጨለማ፣ ብርድ፣ ነፋስ አላገዳቸውም::
በየዕለቱ ሲገናኙ ምን ይሠራሉ? ምንም:: አንዱ ሌላውን በማድነቅ
ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ:: የሚረግጡትን መሬት እንደ ተቀደሰ ቦታ ነው የሚቆጥሩት:: ብዙ ጊዜ የሚያወሩት ስለፍቅር ነው:: ማሪየስ የሙት ልጅ
መሆኑን! ስሙ ማሪየስ ፓንትመርሲ እንደሚባልና የሕግ ባለሙያ እንደሆነ ገልጾላታል፡፡ ኑሮውን የሚያሸንፈው ለአሳታሚ ድርጅቶች አንዳንድ ጽሑፍ
እየጻፈ እንደሆነና አባቱ በአገሩ የታወቀ ጀግና እንደነበር ነገራት፡ እንዲሁም ከዲታው አያቱ ጋር መጣላቱንና የአባቱን ሹመት በመውረስ ባሮን እንደሆነም
ገልጾለታል። ባለማዕረግ ስለሆነ ኮዜት ላይ የተለየ ስሜት አላሳደረባትም::ለእርስዋ ምንም ይሁን ምን ማሪየስ ማሪየስ ነው:: በእርስዋም በኩል ገዳም ውስጥ ማደግዋን፣ እናትና አባትዋ መሞታቸውን፣ የእንጀራ አባትዋ ስም። መሴይ ፎሽለማ መሆኑን፣ ይህም ሰው ድሃን የሚወድ እጅግ ደግና ራሱም ምስኪን እንደሆነና እርስዋን ለማስደሰት ሲል ራሱን ረስቶ ያላደረገው ነገር
እንደሌላ ነገረችው፡፡ የእንጀራ አባትዋ ለእርስዋ ሲል ምቾቱን ሁሉ መሰዋቱንም አስረዳችው::
የሚገርመው ማሪየስ ኮዜትን ስላገኘና በምትነግረው ነገር ሁሉ
ስለረካ ሌላው ቀርቶ አንድ ቀን ሌሊት በቀዳዳ ከነቴናድዬ ቤት ውስጥ ያየውን እንኳን ረስቶ አባትዋ ላይ ደርሶ ስለነበረው ትርኢት አልነገራትም::
ሚስተርና ሚስስ ቴናድዬ በአባትዋ ላይ ስላደረሱት በደልና አባትዋ እንዴት አድርጎ ከዚያ ወጥመድ እንዳመለጠ ለጊዜው አልታወሰውም:: ሌላው ቀርቶ ማታ ያደረገውን ጠዋት፣ ጠዋት የሠራውን ማታ ይረሳል፡፡ አንድ
ሰው ቀን ላይ ተገናኝቶ «ቁርስህን ምንድነው የበላኸው?» ብሎ ቢጠይቀው አያስታውስም፡፡ ጆሮውና ሕሊናው በኮዜት ትዝታ ስለተደፈነ የማስታወስ
ችሎታውን ቀንሶበታል፡፡ ከዚህም በላይ ከኮዜት ተለይቶ የሚያሳልፈው ጊዜ ዝም ብሎ የሚያልፍ እንጂ ኑሮን እየኖረ የሚያልፍ ስላልመሰለው በሌላ
ጊዜ የሚፈጽመው ተግባር ሁሉ እርባነቢስ በመሆነ ይረሳዋል:: ለማሪየስ ኑሮ ወይም ሕይወት ማለት ከኮዜት ጋር የሚያሳልፈው ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ ይህም የእውነተኛ ፍቅር ባሕርይ ነው::
ኮዜት በጣም የተዋበች ልጅ ስትሆን ማሪየስ ነፍስዋንም ጭምር ለማየት ነው የሚፈልገው:: የአንድን ነገር ሁለንተና በጉልህ ለማየት
የሚቻለው ዓይን ሲጨፈን ስለሆነ ማሪየስ ዓይኑን ብዙ ጊዜ ይጨፍናል፡፡ ማሪየስና ኮዜት መጨረሻቸው ምን እንደሚሆን አንስተውና ተነጋግረውበት
አያውቁም፡፡ ማንኛውም ነገር እንደአመጣጡ ነው የሚቀበሉት፡-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣን ቫልዣ ምንም አልጠረጠረም፡ኮዜት ዘወትር ደስ ብሉአት ስላየ
ከዚያ ወዲያ የሚፈልገው ነገር አልነበረምና ደስ እያለው ይኖራል፡፡ ኮዜትም ማሪየስን በማግኘትዋ መንፈስዋ ስለረካ ዘወትር የደስታ ምልክት ግንባርዋ ላይ ይነበባል:: በሁለት ፍቅረኞች መካከል መግባባት ካለ አብረው መኖር
ይችላሉ:: በመካከላቸው ሰላም እስካለ ድሬስ የተለየ ጠባይ ስለማይታይባቸው ሦስተኛ ሰው አዲስ ነገር ሊያይባቸው አይችልም:: ጥቂት ጥንቃቄ በማድረግ ከፍቅረኛቸው ጋር መኖር ይችላሉ::
አባትዋ የፈለገውን ለማድረግ ሲፈልግ ተቃውሞ አላሳየችውም፡፡ ዞርዞር ብዬ ልምጣ? እሺ አባዬ:: ዛሬ ከቤት ልዋል መሰለኝ? እንደፈለግህ፡፡
አብረን እናምሽ፡፡ ደስታውን አልችለውም::አባትዋ ዘወትር አራት ሰዓት አካባቢ ይተኛል፡፡
ማሪየስ እንደሆነ ከኮዚት ጋር ለመጫወት የሚመጣው ከአራት ሰዓት በኋላ ነው:: ቀን ቀን
ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ዣን ቫልዣ እንደሆነ የማሪየስ በሕይወት መኖር እንኳን ረስቷል፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ግን «ምነው ኮዜት፤ ከኋላሽ ኖራ ነክቶሻል ፤ ከየት መጣ?» ብሎ ይጠይቃታል፡፡ ያን እለት ማታ ከማሪየስ
ጋር ግድግዳ ተደግፋ ቆማ ኖሮ ልብስዋን ኖራ ነክቶባታል፡፡
አሮጊትዋ ቱሴይ በጊዜ ስለምትተኛ እርስዋም እንደ ዣን ቫልዣ ምንም ነገር አልጠረጠረችም:: ማሪየስ ደፍሮ ከቤትዋ ውስጥ ገብቶ
አያውቅም፡፡ አትክልቱ ውስጥ እንኳን ቢሆን አሳቻ ቦታ ይቀመጣሉ እንጂ ራሳቸውን አያጋልጡም:: ከአንድ ቦታ ከተቀመጡ አይነሱም:: ሁለቱም
አብረው በመሆናቸው ብቻ ረክተው ወሬም ባያወሩ ደንታ የላቸውም::ሌላው ቀርቶ በመንገድ የሚያልፍ እንኳን እንዳያያቸው ይጠነቀቃሉ፡፡
አብረው ተቀምጠው ሳለ ዓይን ለዓይን መተያየት፤ በየደቂቃው እጅ ለእጅ ተያይዞ ሃያ ጊዜ መጨማመቅ ደስታ ይሰጣቸዋል፡፡ በዚያች ሰዓት መብረቅ
ካጠገባቸወ: ቢወርድ እንኳን አይሰሙትም:: ይህን ያህል ነበር
ተመስጦአቸው::
ሆኖም ሁለቱ ፍቅረኞች በዚህ ሁኔታ እንዳሉ አንዳንድ ችግሮች
ደግሞ ፈር ቀድደው እየገቡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ማታ እንደ ለመደው ማሪየስ ወደ ቀጠሮው ቦታ ለመሄድ አቀርቅሮ ይጓዛል:: ከአንድ ኩርባ መንገድ ላይ
ደርሶ ሊጠመዘዝ ሲል ድምፅ ይሰማል::
‹‹ሚስተር ማሪየስ እንደምን አመሸህ!››
ቀና ብሎ ሲያይ ኢፓኒን ናት:: ደንገጥ አለ፡፡ የኮዜት ቤት ካሳየችው እለት ወዲህ ትዝ ብላው ወይም ተያይተው አያውቁም:: አሁን ላገኘው ደስታ ምክንያት ብትሆንም ጨርሶ ረስቷታል:: መርሳት ብቻ ሳይሆን እንደገና መገናኘታቸው አናደደው::
የተደላደለ ፍቅር አንድን ሰው ፍጹም ያደርገዋል ብንል ተሳስተናል:: በስሜት መዋጥ ዝንጉ እንደሚያደርግም መርሳት የለብንም:: በስሜት የተዋጠ ሰው ክፋትንና ደግነትን መለየት ይሳነዋል፡፡ ውለታን፣ የሥራ
ኃላፊነትንና፡ መቃወስ ያለባቸውን ጉዳዮች ሁሉ ሊያስረሳው ይችላል::
ምን! አንቺ ነሽ እንዴ ኢፓኒን?» ሲል ለሰጠችው ሰላምታ በጥያቄ
መልክ መለሰላት::
«ምነው፣ በጣም ተኮሳትረህ ነው የምታነጋግረኝ? የአጠፋሁት ነገር
አለ?»
«የለም» ሲል መለሰላት::
በእርግጥም የያዘባት ቂም አልነበረም:: ደግሞም የሚቀየምበትም ምክንያት አልነበረውም፡፡ ኮዜትን በሚያነጋግርበት አንደበት ኢፓኒንን በጥሞና ማነጋገሩ ስለከበደው ብቻ ነው እንደዚያ የሆነው:: እርሱ ዝም ሲላት
እርስዋ ጮክ ብላ ተናገረች::
«ንገረኝ እስቲ አሁን» ብላ የሚናገረው ነገር እንደጠፋው ሰው ዝም አለች:: ፈገግታ ለማሳየት ሞከረች፡፡ ግን አቃታት፤ እንደገና ለመናገር ሞከረች::
«እና….» ብላ ንግግርዋን እንደገና አቋርጣ አቀርቅራ ቀረች::
«ደህና አምሽ ማሪየስ» ብላ መንገድዋን ቀጠለች::
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መማረክና መረሳሳት
ብረት በማግኔት እንደሚሳብ ፍቅረኛም ባፈቀረው ጠዋት ማታ
ይሳባል፤ ይጉተታል፡፡ ሮሚዮ በዡልየት ፍቅር ተጎትቶ በአትክልት ቦታ እንደ ተንሸራሸረ ሁሉ ማሪየስም ከኮዜት የአትክልት ሥፍራ ለመንሸራሸር ተመላለሰ፡፡ ሆኖም ማሪየስ የሮሚዮን ያህል አልተቸገረም:: ሮሚዮ ከዡልዬት
ግቢ ለመግባት ረጅም ግምብ መዝለል ነበረበት:: ማሪየስ ግን ይህ አላስፈለገውም:: የሽቦ አጥርን በቀላሉ ፈልቅቆ ነበር የሚገባው:: ቀጭን
ስለነበር ሰፊ ክፍት ቦታ አላስፈለገውም::
አካባቢውም ጭር ያለ ስለነበር ሰው ሳያየው በቀላሉ ሊገባ ቻለ፡፡
የሚመጣው ደግሞ ማታ ማታ ነው:: በዚያች በተባረከች ምሽት ከንፈር ለከንፈር ከተገናኙ ወዲህ በእየለቱ ነው የሚመጣው::
በ1832 ዓ.ም የግንቦት ወርን በሙሉ አንድ ቀን እንኳን ሳይጓደል
ማታ ማታ ተመላልሶ ከፍቅረኛው ጋር ተገናኘ:: እነዚህ ሁለት የዋህ
ፍጡሮች እንዳይገናኙ ጨለማ፣ ብርድ፣ ነፋስ አላገዳቸውም::
በየዕለቱ ሲገናኙ ምን ይሠራሉ? ምንም:: አንዱ ሌላውን በማድነቅ
ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ:: የሚረግጡትን መሬት እንደ ተቀደሰ ቦታ ነው የሚቆጥሩት:: ብዙ ጊዜ የሚያወሩት ስለፍቅር ነው:: ማሪየስ የሙት ልጅ
መሆኑን! ስሙ ማሪየስ ፓንትመርሲ እንደሚባልና የሕግ ባለሙያ እንደሆነ ገልጾላታል፡፡ ኑሮውን የሚያሸንፈው ለአሳታሚ ድርጅቶች አንዳንድ ጽሑፍ
እየጻፈ እንደሆነና አባቱ በአገሩ የታወቀ ጀግና እንደነበር ነገራት፡ እንዲሁም ከዲታው አያቱ ጋር መጣላቱንና የአባቱን ሹመት በመውረስ ባሮን እንደሆነም
ገልጾለታል። ባለማዕረግ ስለሆነ ኮዜት ላይ የተለየ ስሜት አላሳደረባትም::ለእርስዋ ምንም ይሁን ምን ማሪየስ ማሪየስ ነው:: በእርስዋም በኩል ገዳም ውስጥ ማደግዋን፣ እናትና አባትዋ መሞታቸውን፣ የእንጀራ አባትዋ ስም። መሴይ ፎሽለማ መሆኑን፣ ይህም ሰው ድሃን የሚወድ እጅግ ደግና ራሱም ምስኪን እንደሆነና እርስዋን ለማስደሰት ሲል ራሱን ረስቶ ያላደረገው ነገር
እንደሌላ ነገረችው፡፡ የእንጀራ አባትዋ ለእርስዋ ሲል ምቾቱን ሁሉ መሰዋቱንም አስረዳችው::
የሚገርመው ማሪየስ ኮዜትን ስላገኘና በምትነግረው ነገር ሁሉ
ስለረካ ሌላው ቀርቶ አንድ ቀን ሌሊት በቀዳዳ ከነቴናድዬ ቤት ውስጥ ያየውን እንኳን ረስቶ አባትዋ ላይ ደርሶ ስለነበረው ትርኢት አልነገራትም::
ሚስተርና ሚስስ ቴናድዬ በአባትዋ ላይ ስላደረሱት በደልና አባትዋ እንዴት አድርጎ ከዚያ ወጥመድ እንዳመለጠ ለጊዜው አልታወሰውም:: ሌላው ቀርቶ ማታ ያደረገውን ጠዋት፣ ጠዋት የሠራውን ማታ ይረሳል፡፡ አንድ
ሰው ቀን ላይ ተገናኝቶ «ቁርስህን ምንድነው የበላኸው?» ብሎ ቢጠይቀው አያስታውስም፡፡ ጆሮውና ሕሊናው በኮዜት ትዝታ ስለተደፈነ የማስታወስ
ችሎታውን ቀንሶበታል፡፡ ከዚህም በላይ ከኮዜት ተለይቶ የሚያሳልፈው ጊዜ ዝም ብሎ የሚያልፍ እንጂ ኑሮን እየኖረ የሚያልፍ ስላልመሰለው በሌላ
ጊዜ የሚፈጽመው ተግባር ሁሉ እርባነቢስ በመሆነ ይረሳዋል:: ለማሪየስ ኑሮ ወይም ሕይወት ማለት ከኮዜት ጋር የሚያሳልፈው ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ ይህም የእውነተኛ ፍቅር ባሕርይ ነው::
ኮዜት በጣም የተዋበች ልጅ ስትሆን ማሪየስ ነፍስዋንም ጭምር ለማየት ነው የሚፈልገው:: የአንድን ነገር ሁለንተና በጉልህ ለማየት
የሚቻለው ዓይን ሲጨፈን ስለሆነ ማሪየስ ዓይኑን ብዙ ጊዜ ይጨፍናል፡፡ ማሪየስና ኮዜት መጨረሻቸው ምን እንደሚሆን አንስተውና ተነጋግረውበት
አያውቁም፡፡ ማንኛውም ነገር እንደአመጣጡ ነው የሚቀበሉት፡-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣን ቫልዣ ምንም አልጠረጠረም፡ኮዜት ዘወትር ደስ ብሉአት ስላየ
ከዚያ ወዲያ የሚፈልገው ነገር አልነበረምና ደስ እያለው ይኖራል፡፡ ኮዜትም ማሪየስን በማግኘትዋ መንፈስዋ ስለረካ ዘወትር የደስታ ምልክት ግንባርዋ ላይ ይነበባል:: በሁለት ፍቅረኞች መካከል መግባባት ካለ አብረው መኖር
ይችላሉ:: በመካከላቸው ሰላም እስካለ ድሬስ የተለየ ጠባይ ስለማይታይባቸው ሦስተኛ ሰው አዲስ ነገር ሊያይባቸው አይችልም:: ጥቂት ጥንቃቄ በማድረግ ከፍቅረኛቸው ጋር መኖር ይችላሉ::
አባትዋ የፈለገውን ለማድረግ ሲፈልግ ተቃውሞ አላሳየችውም፡፡ ዞርዞር ብዬ ልምጣ? እሺ አባዬ:: ዛሬ ከቤት ልዋል መሰለኝ? እንደፈለግህ፡፡
አብረን እናምሽ፡፡ ደስታውን አልችለውም::አባትዋ ዘወትር አራት ሰዓት አካባቢ ይተኛል፡፡
ማሪየስ እንደሆነ ከኮዚት ጋር ለመጫወት የሚመጣው ከአራት ሰዓት በኋላ ነው:: ቀን ቀን
ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ዣን ቫልዣ እንደሆነ የማሪየስ በሕይወት መኖር እንኳን ረስቷል፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ግን «ምነው ኮዜት፤ ከኋላሽ ኖራ ነክቶሻል ፤ ከየት መጣ?» ብሎ ይጠይቃታል፡፡ ያን እለት ማታ ከማሪየስ
ጋር ግድግዳ ተደግፋ ቆማ ኖሮ ልብስዋን ኖራ ነክቶባታል፡፡
አሮጊትዋ ቱሴይ በጊዜ ስለምትተኛ እርስዋም እንደ ዣን ቫልዣ ምንም ነገር አልጠረጠረችም:: ማሪየስ ደፍሮ ከቤትዋ ውስጥ ገብቶ
አያውቅም፡፡ አትክልቱ ውስጥ እንኳን ቢሆን አሳቻ ቦታ ይቀመጣሉ እንጂ ራሳቸውን አያጋልጡም:: ከአንድ ቦታ ከተቀመጡ አይነሱም:: ሁለቱም
አብረው በመሆናቸው ብቻ ረክተው ወሬም ባያወሩ ደንታ የላቸውም::ሌላው ቀርቶ በመንገድ የሚያልፍ እንኳን እንዳያያቸው ይጠነቀቃሉ፡፡
አብረው ተቀምጠው ሳለ ዓይን ለዓይን መተያየት፤ በየደቂቃው እጅ ለእጅ ተያይዞ ሃያ ጊዜ መጨማመቅ ደስታ ይሰጣቸዋል፡፡ በዚያች ሰዓት መብረቅ
ካጠገባቸወ: ቢወርድ እንኳን አይሰሙትም:: ይህን ያህል ነበር
ተመስጦአቸው::
ሆኖም ሁለቱ ፍቅረኞች በዚህ ሁኔታ እንዳሉ አንዳንድ ችግሮች
ደግሞ ፈር ቀድደው እየገቡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ማታ እንደ ለመደው ማሪየስ ወደ ቀጠሮው ቦታ ለመሄድ አቀርቅሮ ይጓዛል:: ከአንድ ኩርባ መንገድ ላይ
ደርሶ ሊጠመዘዝ ሲል ድምፅ ይሰማል::
‹‹ሚስተር ማሪየስ እንደምን አመሸህ!››
ቀና ብሎ ሲያይ ኢፓኒን ናት:: ደንገጥ አለ፡፡ የኮዜት ቤት ካሳየችው እለት ወዲህ ትዝ ብላው ወይም ተያይተው አያውቁም:: አሁን ላገኘው ደስታ ምክንያት ብትሆንም ጨርሶ ረስቷታል:: መርሳት ብቻ ሳይሆን እንደገና መገናኘታቸው አናደደው::
የተደላደለ ፍቅር አንድን ሰው ፍጹም ያደርገዋል ብንል ተሳስተናል:: በስሜት መዋጥ ዝንጉ እንደሚያደርግም መርሳት የለብንም:: በስሜት የተዋጠ ሰው ክፋትንና ደግነትን መለየት ይሳነዋል፡፡ ውለታን፣ የሥራ
ኃላፊነትንና፡ መቃወስ ያለባቸውን ጉዳዮች ሁሉ ሊያስረሳው ይችላል::
ምን! አንቺ ነሽ እንዴ ኢፓኒን?» ሲል ለሰጠችው ሰላምታ በጥያቄ
መልክ መለሰላት::
«ምነው፣ በጣም ተኮሳትረህ ነው የምታነጋግረኝ? የአጠፋሁት ነገር
አለ?»
«የለም» ሲል መለሰላት::
በእርግጥም የያዘባት ቂም አልነበረም:: ደግሞም የሚቀየምበትም ምክንያት አልነበረውም፡፡ ኮዜትን በሚያነጋግርበት አንደበት ኢፓኒንን በጥሞና ማነጋገሩ ስለከበደው ብቻ ነው እንደዚያ የሆነው:: እርሱ ዝም ሲላት
እርስዋ ጮክ ብላ ተናገረች::
«ንገረኝ እስቲ አሁን» ብላ የሚናገረው ነገር እንደጠፋው ሰው ዝም አለች:: ፈገግታ ለማሳየት ሞከረች፡፡ ግን አቃታት፤ እንደገና ለመናገር ሞከረች::
«እና….» ብላ ንግግርዋን እንደገና አቋርጣ አቀርቅራ ቀረች::
«ደህና አምሽ ማሪየስ» ብላ መንገድዋን ቀጠለች::
👍21
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ምን እንደሚያደርጉ ሳይታወቃቸው ከንፈር ለከንፈር ይገናኛሉ፡፡ ዓይናቸው እምባ አቅርሮ አንዱ ሌላው ላይ ማፍጠጥ ሆነ፡፡ ማሪየስና ኮዜትም የፈጸሙት ተግባር ይኸው ነበር፡፡
የማሪየስ አያት በዚህ ጊዜ ዘጠና አንድ ዓመት ሆኖአቸዋል፡፡ አሁንም
ከዚያ ትልቅ ቤታቸው ውስጥ ከሴት ልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት:: በዚህ እድሜያቸው ወገባቸው ሳይጎብጥና ሀዘን ፊታቸውን ሳይሰባብር ቀጥ ብለው
የሚጓዙና ለምሳሌነት ሊቀርቡ የሚችሉ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው::
ሽማግሌው ሠራተኞችን መደብደብና ምርኩዛቸውን ሳይዞ መንቀሳቀስ በተው ጊዜ ልጃቸው «አሁንስ አባቴ በእርግጥ አርጅቷል» እያለች ታስብ
ጀመር፡፡ በሐምሌ ወር የተጀመረው የፈረንሣይ አብዮት መጥፎ ስሜት
አሳድሮባቸዋል፡፡ ቢሆንም ሞራላቸው ብርቱ ስለነበር ለማንኛውም ነገር በቀላሉ አልተበገሩም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን መጎዳታቸው ሳይሰማቸው አልቀረም:: ከአራት ዓመት በኋላ እንኳን አንድ ቀን ማሪየስ ከቤታቸው ተመልሶ ከጫማዬ ሥር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቀኛል የሚል እምነት
ነበራቸው:: ማሪየስ ተመልሶ ከቤት ሳይወጣ እሞታለሁ የሚል ሀሳብ
ከሕሊናቸው ውስጥ ገብቶ አያውቅም:: እንዲያውም በቅርበ ማሪየስ ይመለሳል የሚለው እምነታቸው እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ ይህም ለውለታቢሱ የልጅ ልጃቸው የነበራቸው ፍቅር አጠነከረባቸው::
ይህ ልጅ ሰማይና ምድር ቀሚጨልምበት በክረምት ወራት ነበር ጥሎአቸው የሄደው:: ሽማግሌው በእርሳቸው በኩል ምንም ጥፋት እንደሌለና
ጥፋቱ የማሪየስ እንደሆነ በፍጹም ልቦናቸው ቢያምኑም ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ግን አልተቀነሰም፡፡ በመጨረሻ ወደ ሞት መቃረባቸው ሲታወሳቸው
ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ያይላል፡፡ ጥርሳቸው መርገፍ ጀምሯል:: ይህም ሀዘናቸውን ከፍ አደረገው::
አንድ ቀን ጉልበታቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን በከፊል ጨፍነው ቁጭ ይላሉ፡፡ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ከፊታቸው ላይ ይነበባል:: ሴት ልጃቸው ጥያቄ ጠየቀቻቸው:
"አባባ፣ አሁንም ልጁን እንደተቀየሙት ነው?»
ይህን ካለች በኋላ ለመቀጠል ስላልደፈረች ዝም አለች::
"ማንን ነው የምትዪው?» ሲሉ ጠየቅዋት::
«ያንን ምስኪን ማሪየስ፡፡»
የሽማግሌ ጭንቅላታቸውን ቀና አደረጉ:: ያንን የተሸበሸበወን
ክርናቸውን ከጠረጴዛ ላይ በማሳረፍ አገጫቸውን ደግፈው ያዙ፡፡ በጣም በተናደደና በተቆጣ አንደበት ተናገሩ፡፡
«ምስኪን ማሪየስ አልሽ? የማይረባ! እርሱ ብሎ ምስኪን፤ አጉራሹን የሚነክስ! የእኛ እልኸኛ! ልስቢስ፣ እንኳን ልብ ነፍስ የለውም::»
እምባ ያቀረረውን ዓይናቸው ልጃቸው እንዳታይ ከነበሩበት ፊታቸውን በማዞር ተነስተው ሄዱ:: ከሦስት ቀን በኋላ በዝምታ አራት ሰዓት ሙሉ ከአንድ ሥፍራ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሽማግሌ ልጃቸውን በመገሰጽ ይናገራሉ::
«ስለዚያ ልጅ ሁለተኛ እንዳታነሽብኝ ብዬ አልነበረም?»
በዚያው ሰሞን መሴይ ጊልኖርማንድ እሳት እየሞቁ አምሽተው ስለደከማቸው በጊዜ ልጃቸውን ደህና እደሪ ብለው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሄዱ:: ልጃቸው ከሚቀጥለው ክፍል ውስጥ በሩን ክፍት አድርጋ ልብስ እየሰፋች ነበር:: ሽማግሌው እሳት ይሞቁ የነበረው ብቻቸውን ሲሆን
መጽሐፍ ለስሙ በእጃቸው ይዘው ነበር እንጂ አያነቡትም::
እሳት እየሞቀ ሳለ የልጅ ልጃቸው ማሪየስን አስታወሱት:: አሁንም
ቢሆን ውስጥ ውስጡን ይናፍቃቸዋል:: ሊታረቁት ፈለጉ፡፡ ግን ልባቸው ውስጥ የገነነው ኩራትና እልህ መንገዱን ዘጋባቸው:: እንዲያውም ከነአካቴው የመታረቅ አሳብ ኅሊናቸው ውስጥ ስለገባ መላ ሰውነታቸውን አንገሸገሸው::
«ምን?» ሲሉ ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ ከአንገታቸው ቀና አሉ:: ከቤት
ውስጥ የገባ ስለመሰላቸው ተንገሸገሹ:: «ከዚህ ቤት ውስጥ ተመልሶ አይገባም» ሲሉ ለራሳቸው ቃል ገቡ:: ያ መላጣ ጭንቅላታቸው ነገር ስለከበደው ከደረታቸው ላይ ዘንበል ብሎ የወደቁ መሰላቸው:: ቀና ብለው
ከግድግዳ ላይ ከተሰቀለው ስእል ላይ አፈጠጡ:: በአሳብ ተውጠው ሳለ ባስክ የተባለ የቤት አሽከራቸው ይገባል፡፡
«ጌታዬ ማሪየስን ያነጋግሩታል?» ሲል ጠየቃቸው:: ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ:: ከአሳባቸው ባንነው ሲነቁ በጣም
ካመደንገጣቸው የተነሳ ጀርባቻው ቀዘቀዛቸው::
‹‹ምን አልክ?» ማሪየስን ነው ያልከው?
«እኔ እንጃ» ሲል ባስክ እየፈራ መልስ ሰጠ፡፡ «እኔ እንኳን በዓይኔ
አላየሁትም:: ሠራተኛዋ ናት የነገረችኝ፡፡ ውጭ ግን አንድ ወጣት መቆሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ማሪየስ ሊሆን ይችላል፡፡»
«ግባ ግባ ግባ በለው» አሉ እየተንተባተቡ፡፡ ልባቸው እንደከበሮ እየመታ ዓይናቸውን በር ላይ ተክለው ቀሩ፡፡ በሩ ተከፈተ:: አንድ ወጣት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ማሪየስ ነበር፡፡
«ገባ በል እንጂ» በማለት እንዲጋበዝ የሚጠብቅ ይመስል ማሪየስ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ ጊዜው ጨልሞ ስለነበር የለበሰው አዳፋ ልብስ መቆሸሹ ብዙም አያስታውቅም፡፡ በሀዘን የተጨማለቀው ፊቱ ምንም እንኳን
ፀጥታ ቢሰፍንበትም መከፋቱን በግልጽ ያሳያል::
መሴይ ጊልኖርማንድ በደስታና በአድናቆት ልቡ እንደተነካ ሰው
ለጥቂት ጊዜ ዝም በማለት ሰማይ ሰማዩን አዩ፡፡ ማሪየስ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሠርቀው አዩት::
በመጨረሻ! ከአራት ዓመት በኋላ! ደስታ አንደበታቸውን ዘግቶ ሽባ
አደረጋቸው:: ባለፉት አራት ዓመታት እንዲያው ሲያስቡት ቆንጆ፣ ረጋ ያለና ምራቁን የዋጠ የጨዋ ልጅ እንደሚሆን ገምተዋል:: ቢመለስ ልባቸው |
በደስታ ፈክቶና ስሜታቸው በሕሊና ዕረፍት ረክቶ እጆቻቸውን ዘርግተው እንደሚቀበሉት ልቦናቸው ተመኝቶ እንደነበር ልቦናቸው ቢያውቁም ያ ሰዓት ሊመጣ ሳያወቁት የማይሆን ቃል አንደበታቸው ውስጥ ይገባል።
«ለምንድነው የመጣኸው?»
ማሪየስ ሀፍረት እየተሰማው መለሰ፡፡
«ጌቶች...»
መሴይ ጊልኖርማንድ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ቢያቅፉት ደስ ባላቸው፤ ግን ማሪየስ አስቀይሞአቸዋል፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውም ቢሆኑ
በወሰዱት እርምጃ ቅር መሰኘታቸው አልቀረም:: ማሪየስ ቢያስቀይማቸውም መታገስ እንደነበረባቸው ያውቃሉ፡፡ ደግና እልኸኛ ሰው የልቡን ደግነት
በእልህና በኃይለ ቃል እየሸፈነ ወስጥ ውስጡን ይሰቃያል:: ምሬቱ ትዝ ብሉአቸው እንዲናገር እድል ሳይሰጡት ጣልቃ ገቡበት::
‹‹ንገረኝ እኮ፣ ለምንድነው የመጣኸው?»
ጉልበቴን ለመሳም ወይም አቅፈህ ጉንጩን በመሳም ይቅርታ ለመጠየቅ ካልሆነ ለምንድነው የመጣኸው ማለታቸው ነበር፡፡ ማሪየስ አያቱን አተኩር
ሲመለከታቸው ሀሞታቸው መፍሰሱን ተገነዘበ፡፡
ሽማግሌው አሁንም በኃይለ ቃል አቋረጡት::
«ይቅርታ ለመጠየቅ ነው የመጣኸው? ተጸጽተህ ነው?»
ወደ እርሳቸው እንዲመለስ በር መክፈታቸው ነበር፡፡ እጁን የሚሰጥና የሚርበተበት መሰላቸው:: እውነትም ማሪየስ በድንጋጤ ሰውነቱ ተርበተበተ፡፡
ዓይኑን ወደ መሬት ሰበረ፡፡ ቢሆንም በድፍረት መልስ ሰጠ፡፡
«የለም ጌቶች::»
«እና ምንድነው የምትፈልገው?» ሲሉ ሽማግሌው ንዴትና ምሬት
እየተናነቃቸው ተናገሩ፡፡ «አሁን ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው?»
ማሪየስ ሁለት እጆቹን በኃይል በመጨበጥ አጋጫቸው አንድ
እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡
እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አባባ ይዘኑልኝ::»
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ምን እንደሚያደርጉ ሳይታወቃቸው ከንፈር ለከንፈር ይገናኛሉ፡፡ ዓይናቸው እምባ አቅርሮ አንዱ ሌላው ላይ ማፍጠጥ ሆነ፡፡ ማሪየስና ኮዜትም የፈጸሙት ተግባር ይኸው ነበር፡፡
የማሪየስ አያት በዚህ ጊዜ ዘጠና አንድ ዓመት ሆኖአቸዋል፡፡ አሁንም
ከዚያ ትልቅ ቤታቸው ውስጥ ከሴት ልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት:: በዚህ እድሜያቸው ወገባቸው ሳይጎብጥና ሀዘን ፊታቸውን ሳይሰባብር ቀጥ ብለው
የሚጓዙና ለምሳሌነት ሊቀርቡ የሚችሉ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው::
ሽማግሌው ሠራተኞችን መደብደብና ምርኩዛቸውን ሳይዞ መንቀሳቀስ በተው ጊዜ ልጃቸው «አሁንስ አባቴ በእርግጥ አርጅቷል» እያለች ታስብ
ጀመር፡፡ በሐምሌ ወር የተጀመረው የፈረንሣይ አብዮት መጥፎ ስሜት
አሳድሮባቸዋል፡፡ ቢሆንም ሞራላቸው ብርቱ ስለነበር ለማንኛውም ነገር በቀላሉ አልተበገሩም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን መጎዳታቸው ሳይሰማቸው አልቀረም:: ከአራት ዓመት በኋላ እንኳን አንድ ቀን ማሪየስ ከቤታቸው ተመልሶ ከጫማዬ ሥር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቀኛል የሚል እምነት
ነበራቸው:: ማሪየስ ተመልሶ ከቤት ሳይወጣ እሞታለሁ የሚል ሀሳብ
ከሕሊናቸው ውስጥ ገብቶ አያውቅም:: እንዲያውም በቅርበ ማሪየስ ይመለሳል የሚለው እምነታቸው እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ ይህም ለውለታቢሱ የልጅ ልጃቸው የነበራቸው ፍቅር አጠነከረባቸው::
ይህ ልጅ ሰማይና ምድር ቀሚጨልምበት በክረምት ወራት ነበር ጥሎአቸው የሄደው:: ሽማግሌው በእርሳቸው በኩል ምንም ጥፋት እንደሌለና
ጥፋቱ የማሪየስ እንደሆነ በፍጹም ልቦናቸው ቢያምኑም ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ግን አልተቀነሰም፡፡ በመጨረሻ ወደ ሞት መቃረባቸው ሲታወሳቸው
ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ያይላል፡፡ ጥርሳቸው መርገፍ ጀምሯል:: ይህም ሀዘናቸውን ከፍ አደረገው::
አንድ ቀን ጉልበታቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን በከፊል ጨፍነው ቁጭ ይላሉ፡፡ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ከፊታቸው ላይ ይነበባል:: ሴት ልጃቸው ጥያቄ ጠየቀቻቸው:
"አባባ፣ አሁንም ልጁን እንደተቀየሙት ነው?»
ይህን ካለች በኋላ ለመቀጠል ስላልደፈረች ዝም አለች::
"ማንን ነው የምትዪው?» ሲሉ ጠየቅዋት::
«ያንን ምስኪን ማሪየስ፡፡»
የሽማግሌ ጭንቅላታቸውን ቀና አደረጉ:: ያንን የተሸበሸበወን
ክርናቸውን ከጠረጴዛ ላይ በማሳረፍ አገጫቸውን ደግፈው ያዙ፡፡ በጣም በተናደደና በተቆጣ አንደበት ተናገሩ፡፡
«ምስኪን ማሪየስ አልሽ? የማይረባ! እርሱ ብሎ ምስኪን፤ አጉራሹን የሚነክስ! የእኛ እልኸኛ! ልስቢስ፣ እንኳን ልብ ነፍስ የለውም::»
እምባ ያቀረረውን ዓይናቸው ልጃቸው እንዳታይ ከነበሩበት ፊታቸውን በማዞር ተነስተው ሄዱ:: ከሦስት ቀን በኋላ በዝምታ አራት ሰዓት ሙሉ ከአንድ ሥፍራ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሽማግሌ ልጃቸውን በመገሰጽ ይናገራሉ::
«ስለዚያ ልጅ ሁለተኛ እንዳታነሽብኝ ብዬ አልነበረም?»
በዚያው ሰሞን መሴይ ጊልኖርማንድ እሳት እየሞቁ አምሽተው ስለደከማቸው በጊዜ ልጃቸውን ደህና እደሪ ብለው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሄዱ:: ልጃቸው ከሚቀጥለው ክፍል ውስጥ በሩን ክፍት አድርጋ ልብስ እየሰፋች ነበር:: ሽማግሌው እሳት ይሞቁ የነበረው ብቻቸውን ሲሆን
መጽሐፍ ለስሙ በእጃቸው ይዘው ነበር እንጂ አያነቡትም::
እሳት እየሞቀ ሳለ የልጅ ልጃቸው ማሪየስን አስታወሱት:: አሁንም
ቢሆን ውስጥ ውስጡን ይናፍቃቸዋል:: ሊታረቁት ፈለጉ፡፡ ግን ልባቸው ውስጥ የገነነው ኩራትና እልህ መንገዱን ዘጋባቸው:: እንዲያውም ከነአካቴው የመታረቅ አሳብ ኅሊናቸው ውስጥ ስለገባ መላ ሰውነታቸውን አንገሸገሸው::
«ምን?» ሲሉ ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ ከአንገታቸው ቀና አሉ:: ከቤት
ውስጥ የገባ ስለመሰላቸው ተንገሸገሹ:: «ከዚህ ቤት ውስጥ ተመልሶ አይገባም» ሲሉ ለራሳቸው ቃል ገቡ:: ያ መላጣ ጭንቅላታቸው ነገር ስለከበደው ከደረታቸው ላይ ዘንበል ብሎ የወደቁ መሰላቸው:: ቀና ብለው
ከግድግዳ ላይ ከተሰቀለው ስእል ላይ አፈጠጡ:: በአሳብ ተውጠው ሳለ ባስክ የተባለ የቤት አሽከራቸው ይገባል፡፡
«ጌታዬ ማሪየስን ያነጋግሩታል?» ሲል ጠየቃቸው:: ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ:: ከአሳባቸው ባንነው ሲነቁ በጣም
ካመደንገጣቸው የተነሳ ጀርባቻው ቀዘቀዛቸው::
‹‹ምን አልክ?» ማሪየስን ነው ያልከው?
«እኔ እንጃ» ሲል ባስክ እየፈራ መልስ ሰጠ፡፡ «እኔ እንኳን በዓይኔ
አላየሁትም:: ሠራተኛዋ ናት የነገረችኝ፡፡ ውጭ ግን አንድ ወጣት መቆሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ማሪየስ ሊሆን ይችላል፡፡»
«ግባ ግባ ግባ በለው» አሉ እየተንተባተቡ፡፡ ልባቸው እንደከበሮ እየመታ ዓይናቸውን በር ላይ ተክለው ቀሩ፡፡ በሩ ተከፈተ:: አንድ ወጣት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ማሪየስ ነበር፡፡
«ገባ በል እንጂ» በማለት እንዲጋበዝ የሚጠብቅ ይመስል ማሪየስ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ ጊዜው ጨልሞ ስለነበር የለበሰው አዳፋ ልብስ መቆሸሹ ብዙም አያስታውቅም፡፡ በሀዘን የተጨማለቀው ፊቱ ምንም እንኳን
ፀጥታ ቢሰፍንበትም መከፋቱን በግልጽ ያሳያል::
መሴይ ጊልኖርማንድ በደስታና በአድናቆት ልቡ እንደተነካ ሰው
ለጥቂት ጊዜ ዝም በማለት ሰማይ ሰማዩን አዩ፡፡ ማሪየስ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሠርቀው አዩት::
በመጨረሻ! ከአራት ዓመት በኋላ! ደስታ አንደበታቸውን ዘግቶ ሽባ
አደረጋቸው:: ባለፉት አራት ዓመታት እንዲያው ሲያስቡት ቆንጆ፣ ረጋ ያለና ምራቁን የዋጠ የጨዋ ልጅ እንደሚሆን ገምተዋል:: ቢመለስ ልባቸው |
በደስታ ፈክቶና ስሜታቸው በሕሊና ዕረፍት ረክቶ እጆቻቸውን ዘርግተው እንደሚቀበሉት ልቦናቸው ተመኝቶ እንደነበር ልቦናቸው ቢያውቁም ያ ሰዓት ሊመጣ ሳያወቁት የማይሆን ቃል አንደበታቸው ውስጥ ይገባል።
«ለምንድነው የመጣኸው?»
ማሪየስ ሀፍረት እየተሰማው መለሰ፡፡
«ጌቶች...»
መሴይ ጊልኖርማንድ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ቢያቅፉት ደስ ባላቸው፤ ግን ማሪየስ አስቀይሞአቸዋል፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውም ቢሆኑ
በወሰዱት እርምጃ ቅር መሰኘታቸው አልቀረም:: ማሪየስ ቢያስቀይማቸውም መታገስ እንደነበረባቸው ያውቃሉ፡፡ ደግና እልኸኛ ሰው የልቡን ደግነት
በእልህና በኃይለ ቃል እየሸፈነ ወስጥ ውስጡን ይሰቃያል:: ምሬቱ ትዝ ብሉአቸው እንዲናገር እድል ሳይሰጡት ጣልቃ ገቡበት::
‹‹ንገረኝ እኮ፣ ለምንድነው የመጣኸው?»
ጉልበቴን ለመሳም ወይም አቅፈህ ጉንጩን በመሳም ይቅርታ ለመጠየቅ ካልሆነ ለምንድነው የመጣኸው ማለታቸው ነበር፡፡ ማሪየስ አያቱን አተኩር
ሲመለከታቸው ሀሞታቸው መፍሰሱን ተገነዘበ፡፡
ሽማግሌው አሁንም በኃይለ ቃል አቋረጡት::
«ይቅርታ ለመጠየቅ ነው የመጣኸው? ተጸጽተህ ነው?»
ወደ እርሳቸው እንዲመለስ በር መክፈታቸው ነበር፡፡ እጁን የሚሰጥና የሚርበተበት መሰላቸው:: እውነትም ማሪየስ በድንጋጤ ሰውነቱ ተርበተበተ፡፡
ዓይኑን ወደ መሬት ሰበረ፡፡ ቢሆንም በድፍረት መልስ ሰጠ፡፡
«የለም ጌቶች::»
«እና ምንድነው የምትፈልገው?» ሲሉ ሽማግሌው ንዴትና ምሬት
እየተናነቃቸው ተናገሩ፡፡ «አሁን ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው?»
ማሪየስ ሁለት እጆቹን በኃይል በመጨበጥ አጋጫቸው አንድ
እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡
እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አባባ ይዘኑልኝ::»
👍18🥰1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ወዴት ነው የሚሄዱት?
ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::
እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::
ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡
ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::
ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።
ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።
ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::
ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡
«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::
በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡
ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡
ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡
ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»
ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ወዴት ነው የሚሄዱት?
ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::
እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::
ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡
ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::
ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።
ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።
ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::
ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡
«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::
በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡
ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡
ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡
ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»
ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
👍18👎1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ከየቤቱ መስኮት እየተንጠላጠለ ይሳሳቃሉ፣ ወጣቶች የነገሩን ምንነት ሳያጤኑ ጥልቅ ይላሉ፡፡ «ተነስ ተንቀሳቀስ» እያሉ ጩኸት ያስተጋባሉ፡ ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፓሪስ ከተማ ላይ የሆነውን ላውጋችሁ።
በየአውራ ጎዳናው፣ በየገበያ ቦታ፣ በየመንደሩ ትንፋሽ ያጠራቸው ሰዎች፣ሠራተኞችና ተማሪዎች፣ «ተነስ፣ ተንቀሳቀስ፣ ክንድህን አንሳ» እያለ በአንድ ቋንቋ ይጮሃሉ፡፡ የመንገድ መብራት፣ መስተዋት፣ የመጓጓዣ ጋሪዎችንና
ሠረገላዎችን ይበረብራሉ፣ ድንጋይ ይወረውራሉ፣ ቤት ውስጥ እየገቡ የቤት እቃ ያንኮታከታሉ፣ ሰሌዳ ይዘው በየመንገዱ ይዞራሉ፡፡ ማን
አስተባበራቸው? ማን አነሳሳቸው? ማን ያውቃል!
የአድመኞቹ ወላፈን እንደ ጭድ እሳት ተቀጣጠለ፡፡ በሦስት ሰዓት
ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ቁልፍ የሆኑትን ስፍራዎች ከቁጥጥራቸው ሥር አደረጉ፡፡ ከሰዓት በኋላ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ የፓሪስ ከተማን |
ሦስት አራተኛ የሚሆነውን ክፍል ያዘ:: ይህም ከድንጋይ ውርወራ ወደ ጦር መሣሪያ መጨበጥ አሸጋገራቸው:: አድመኞቹ የመሣሪያ መጋዘን ስለማረኩ የጦር መሣሪያ ከዚያ ዘረፉ:: በአሥራ ሁለት ሰዓት ቅልጥ ያለ ዝርፊያ
ተጀመረ።
በአንድ ፊት አድመኞቹ በሌላ አቅጣጫ የመንግሥት ወታደሮች
ሥፍራ ሥፍራቸውን ያዙ፡፡ ተኩሰ ተጧጧፈ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ያለ፣
ወደፊት በሚሆነው እጠቀማለሁ ብሎ ያለመ፤ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ
ጭምር ሁኔታውን ለማየት እየተሽሎከሎከ ወደ ጦር ሜዳው አመሩ፡፡እንደ እነቪክተር ህዩጎ ያለ አልጠግብ ባይ ከእሳተ ገሞራ ውስጥ ገብቶ መውጫ በማጣት ተቅበዘበዘ፡፡ ከጦርነቱ፡ መካከል በመግባታቸው ጥግ ይዘው
አውጣን» ከማለት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፡፡ ቅልጥ ያለ ጥይት እሩምታ ግማሽ ሰዓት ወሰደ:: የጦሩ ክፍል በያለበት መሯሯጥ፣መንቀሳቀስ ሆነ፡፡ ከጦር ሜዳው በብዛት የጦር ኃይል ጎረፈ:: ውጊያው ፓሪስ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡
የጦር ኃይሉ እንዳላ መንቀሳቀሱን የተመለከተ ሕዝብ ወደኋላ መሸሽ
ጀመረ፡፡ በየአቅጣጫው ተንሰራፍቶ የነበረው ሰልፈኛ እንደመበተን አለ::ትርምስምሱ ወጣ:: አንዳንዱማ ፈሪ በሩጫ እግሬ አውጪኝ አለ፡፡
ዝናብ በሀይል ይጥላል:: ከዚህ ትርምስ ውስጥ አንድ ልጅ ውራጅ
እቃ ከሚሽጥበት ሱቅ አካባቢ ብቅ አለ፡፡ አንዲት አሮጊት ሽጉጥ ይዘው መቀመጣቸውን ስለተመለከተ ልጁ ወደ ሴትዮዋ ሮጠ
«እማማ፣ አንድ ጊዜ ሽጉጥዎን ያውሱኛል?» ሲል ጠየቃቸው:::
ሽጉጡን ለማግኘት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ወዲያው መሣሪያውን ከእጁ አስገብቶ ወደ መጣበት ተመልሶ ሮጠ፡፡
ልጁ ከአሁን ቀደም ያነሳነው ሚስተር ቴናድዩ ከእስር ቤት እንዲያመልጥ የረዳውና ጋቭሮች የሚባለው ነበር፡፡ መንገድ ከጀመረ በኋላ ነበር ሽጉጡ
ጥይት እንደሌለው የተገነዘበው:: ቢሆንም መንገዱን ቀጠለ፡፡
እነ ኩርፌይራክና ኤንጆልሪስ ከቁጥጥራቸው ስር ካደረጉት ሰፈር ደረሰ:: ከሌላ አቅጣጫ ሌሎች በድኖች የሚመሩት የአድመኞች ቡድን መጥቶ ሲደባለቅ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮችም አብሮ ከሰልፈኞቹ ጋር ተደባለቀ::
««ወዴት ነው የምንሄደው?» ሲል ጠየቀ::
‹‹ተከተለን» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት::
የረብሻው ቀንደኛ መሪዎች ከአፍ እስከ ገደፍ ታጥቀዋል:: ከኋላ
የተከተላቸው ጀሌ አንዳንዱ የጦር መሣሪያ ሲይዝ አንዳንዱ ዱላ ብቻ ነው የያዘውን ፡፡ ከሠራዊቱ መካከል አንድ በእድሜ የገፉ ሽማግሌዎም ነበሩ::
ሽማግሌው ምንም ዓይነት የጦር መሣሪያ አልያዘም:: ግን በጣም እየተቻኮለ ነበር የሚሄዱት፡፡ ፊታቸውን ሲያዩት ከአሳብ ባህር የሰመጠ ይመስላል፡፡
ጋቭሮች ከሩቁ አያቸው::
«ያ ማነው?» ሲል ኩርፌይራክን ጠየቀው::
«አንድ ሽማግሌ ነዋ!» ሲል መለሰለት::
ከአሁን ቀደም ያየናቸው መሴይ ማብዩፍ ነበሩ::
ሽማግሌው ፊት ለፊት ከሚሄደው መስመር ሊደርሱ ምንም ያህል
አልቀራቸውም::
«ምን ዓይነት ቆራጥ ሽማግሌ ናቸው!» ሲሉ ተማሪዎቹ አጉረመረሙ። ማን እንደሆኑ ለማወቅ ተማሪዎቹ ጊዜ አልወሰደባቸውም ገዳም ውስጥ
ይኖሩ እንደነበር የሚያውቋቸው ሰዎች በሹክሹክታ ስማቸውን አስተጋቡ ሠራዊቱ አንዱን ጎዳና ጨርሶ ወደ ሌላው ተሸጋገረ፡፡ ጋቭሮችም መጓዙን ቀጠለ።
ብዙ በተጓዘ ቁጥር የሠራዊቱ ቁጥር እየጨመረ ሄደ፡፡ አንድ ግዙፍ ሰውነት ያለው ረጅም ሰው መጥቶ ተደባለቀ፡፡ ሽበት ጣል ጣል አድርጎበታል ፡መሪዎቹ ይህ ሰው ማን እንደሆነ አላወቁትም፡፡ ግን ወደ እነርሱ ለመጠጋት
በጣም ይፈልጋል፡፡ ጋቭሮች በሚያዜመው መዝሙር ተመስጦ ስለነበረ ሰውዬውን ልብ አላለውም፡፡ ልጁ መዝሙር ሲሰለቸው ያፏጫል፤ አንዳንዴ
ያንን ጥይት የሌለውን ሽጉጡን ያሻሻል፡፡
ሰልፈኛው መንገዱን ቀጥሎ እንደአጋጣሚ ሆኖ በኩርፌይራክ መኖሪያ ቤት ደጃፍ ያልፋል፡፡
«ጥሩ አጋጣሚ ነው» ይላል ኩርፌይራክ፡፡ «ቆቤ ጠፍቷል፤ ጠዋት ደግሞ ቦርሳዬን ረስቼ ነው የመጣሁት፡፡»
ከሰልፈኛው ተገንጥሎ ደረጃዎቹን በእጥፍ እየዘለለ ወደ ቤቱ ገባ
አንድ አሮጌ ቆብና የኪስ ቦርሳውን አነሳ፡፡ ከቆሻሻ ልብስ ውስጥ
የነበረ ሌላ አነስተኛ የእጅ ቦርሳም ወሰደ:: ደረጃውን በችኮላ ሲወርድ በጨለማ ውስጥ አንድ ሰው «ሊያነጋግርህ የሚፈልግ ሰው አለ» ሲል ነገረው፡፡
በዚህ ጊዜ አንድ የተቦጫጨቀ የሴት ቀሚስ ከላይ ያጠለቀ ወንድ
ከወደ ውስጥ ብቅ ብሎ አነጋገረው:: ድምፁ የሴት እንጂ የወንድ አይመስልም:: በጣም ቀጭን ነው::
«ማሪየስን አይተውታል?»
«የለም፤ ከቤት አልመጣም::»
«ማታ ይመጣ ይሆን?»
«እኔ እንጃ፡፡ እኔ ግን ዛሬ ወደቤት አልመለስም::»
አለባበሱና ድምፁ ሴት ያስመስለው ወጣት ኩርፌይራክን አፍጥጦ አየው
ለምን አይመለሱም?» ሲል በድፍረት ጠየቀው::
«ምክንያቱም...»
«እንግዲያው አንተ ወዴት ነው የምትሄደው?» በማለት ጣልቃ ገባ፡፡
«ምን ያደርግልሃል?»
«ቦርሳህን ልያዝልህ?»
«ወደ ጦርነቱ ቦታ ነው የምሄደው?»
«አብሬህ ብሄድ ትፈቅድልኛለህ?»
«ከፈለግህ፣ እኔ ምን ቸገረኝ» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት:: «መንገዱ
ነጻ፣ ጎዳናው የጋራ!»
ኩርፌይራክ ይህን እንደተናገረ ከጓደኞቹ ለመድረስ በሩጫ ወጣ፡፡
እንደደረሰም የእጅ ቦርሳውን እንዲይዝለት ለአንዱ ጓደኛው ሰጠው:: ከሩብ ሰዓት ጉዞ በኋላ መለስ ቢል ወጣቱ እንደተከተለው ተገነዘበ፡፡
ለአመዕ የተነሳሳ ሰልፈኛ ብዙውን ጊዜ የሚመራው በነፋስ ስለሆነ
አንዳንዴ ወደፈለገበት ሳይሆን ወደ አልፈለገበት አቅጣጫ ነው የሚጓዘው::ይህም በመሆኑ ይህ ሰልፈኛ ሴንትሜሪ ከተባለ ሥፍራ ለመሄድ ፈልጎ ሳይታወቀው ይህን ቦታ አልፎ ከሴንት ዴኒስ ይደርሳል፡፡
ከሰላሳ ዓመታት በፊት አንድ መንገደኛ ሴንት ዴኒስ ከተባለ ሥፍራ ቢያልፍ መንገዱ እየጠበበ ሄዶ በመጨረሻ እንደ አቁማዳ ጫፍ መደፈኑን ይገነዘብ ነበር፡፡ አካባቢውን አጥርቶ የማያውቅ ከሆነማ በግራና በቀኝ በኩል
የጨለማ መንገድ መኖሩን ስለማይረዳ መድረሻ ያጣል:: ውስጥ አዋቂ ግን በእነዚህ ጠባብ የጨለማ መንገዶች ተሹለክልኮ ሊያልፍ ይችላል፡፡ በስተቀኝ
በኩል ያለውን የቀኝ መንገድ ይዞ ሲጓዝ ከአንድ መሸታና ምግብ ቤት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ከየቤቱ መስኮት እየተንጠላጠለ ይሳሳቃሉ፣ ወጣቶች የነገሩን ምንነት ሳያጤኑ ጥልቅ ይላሉ፡፡ «ተነስ ተንቀሳቀስ» እያሉ ጩኸት ያስተጋባሉ፡ ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፓሪስ ከተማ ላይ የሆነውን ላውጋችሁ።
በየአውራ ጎዳናው፣ በየገበያ ቦታ፣ በየመንደሩ ትንፋሽ ያጠራቸው ሰዎች፣ሠራተኞችና ተማሪዎች፣ «ተነስ፣ ተንቀሳቀስ፣ ክንድህን አንሳ» እያለ በአንድ ቋንቋ ይጮሃሉ፡፡ የመንገድ መብራት፣ መስተዋት፣ የመጓጓዣ ጋሪዎችንና
ሠረገላዎችን ይበረብራሉ፣ ድንጋይ ይወረውራሉ፣ ቤት ውስጥ እየገቡ የቤት እቃ ያንኮታከታሉ፣ ሰሌዳ ይዘው በየመንገዱ ይዞራሉ፡፡ ማን
አስተባበራቸው? ማን አነሳሳቸው? ማን ያውቃል!
የአድመኞቹ ወላፈን እንደ ጭድ እሳት ተቀጣጠለ፡፡ በሦስት ሰዓት
ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ቁልፍ የሆኑትን ስፍራዎች ከቁጥጥራቸው ሥር አደረጉ፡፡ ከሰዓት በኋላ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ የፓሪስ ከተማን |
ሦስት አራተኛ የሚሆነውን ክፍል ያዘ:: ይህም ከድንጋይ ውርወራ ወደ ጦር መሣሪያ መጨበጥ አሸጋገራቸው:: አድመኞቹ የመሣሪያ መጋዘን ስለማረኩ የጦር መሣሪያ ከዚያ ዘረፉ:: በአሥራ ሁለት ሰዓት ቅልጥ ያለ ዝርፊያ
ተጀመረ።
በአንድ ፊት አድመኞቹ በሌላ አቅጣጫ የመንግሥት ወታደሮች
ሥፍራ ሥፍራቸውን ያዙ፡፡ ተኩሰ ተጧጧፈ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ያለ፣
ወደፊት በሚሆነው እጠቀማለሁ ብሎ ያለመ፤ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ
ጭምር ሁኔታውን ለማየት እየተሽሎከሎከ ወደ ጦር ሜዳው አመሩ፡፡እንደ እነቪክተር ህዩጎ ያለ አልጠግብ ባይ ከእሳተ ገሞራ ውስጥ ገብቶ መውጫ በማጣት ተቅበዘበዘ፡፡ ከጦርነቱ፡ መካከል በመግባታቸው ጥግ ይዘው
አውጣን» ከማለት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፡፡ ቅልጥ ያለ ጥይት እሩምታ ግማሽ ሰዓት ወሰደ:: የጦሩ ክፍል በያለበት መሯሯጥ፣መንቀሳቀስ ሆነ፡፡ ከጦር ሜዳው በብዛት የጦር ኃይል ጎረፈ:: ውጊያው ፓሪስ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡
የጦር ኃይሉ እንዳላ መንቀሳቀሱን የተመለከተ ሕዝብ ወደኋላ መሸሽ
ጀመረ፡፡ በየአቅጣጫው ተንሰራፍቶ የነበረው ሰልፈኛ እንደመበተን አለ::ትርምስምሱ ወጣ:: አንዳንዱማ ፈሪ በሩጫ እግሬ አውጪኝ አለ፡፡
ዝናብ በሀይል ይጥላል:: ከዚህ ትርምስ ውስጥ አንድ ልጅ ውራጅ
እቃ ከሚሽጥበት ሱቅ አካባቢ ብቅ አለ፡፡ አንዲት አሮጊት ሽጉጥ ይዘው መቀመጣቸውን ስለተመለከተ ልጁ ወደ ሴትዮዋ ሮጠ
«እማማ፣ አንድ ጊዜ ሽጉጥዎን ያውሱኛል?» ሲል ጠየቃቸው:::
ሽጉጡን ለማግኘት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ወዲያው መሣሪያውን ከእጁ አስገብቶ ወደ መጣበት ተመልሶ ሮጠ፡፡
ልጁ ከአሁን ቀደም ያነሳነው ሚስተር ቴናድዩ ከእስር ቤት እንዲያመልጥ የረዳውና ጋቭሮች የሚባለው ነበር፡፡ መንገድ ከጀመረ በኋላ ነበር ሽጉጡ
ጥይት እንደሌለው የተገነዘበው:: ቢሆንም መንገዱን ቀጠለ፡፡
እነ ኩርፌይራክና ኤንጆልሪስ ከቁጥጥራቸው ስር ካደረጉት ሰፈር ደረሰ:: ከሌላ አቅጣጫ ሌሎች በድኖች የሚመሩት የአድመኞች ቡድን መጥቶ ሲደባለቅ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮችም አብሮ ከሰልፈኞቹ ጋር ተደባለቀ::
««ወዴት ነው የምንሄደው?» ሲል ጠየቀ::
‹‹ተከተለን» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት::
የረብሻው ቀንደኛ መሪዎች ከአፍ እስከ ገደፍ ታጥቀዋል:: ከኋላ
የተከተላቸው ጀሌ አንዳንዱ የጦር መሣሪያ ሲይዝ አንዳንዱ ዱላ ብቻ ነው የያዘውን ፡፡ ከሠራዊቱ መካከል አንድ በእድሜ የገፉ ሽማግሌዎም ነበሩ::
ሽማግሌው ምንም ዓይነት የጦር መሣሪያ አልያዘም:: ግን በጣም እየተቻኮለ ነበር የሚሄዱት፡፡ ፊታቸውን ሲያዩት ከአሳብ ባህር የሰመጠ ይመስላል፡፡
ጋቭሮች ከሩቁ አያቸው::
«ያ ማነው?» ሲል ኩርፌይራክን ጠየቀው::
«አንድ ሽማግሌ ነዋ!» ሲል መለሰለት::
ከአሁን ቀደም ያየናቸው መሴይ ማብዩፍ ነበሩ::
ሽማግሌው ፊት ለፊት ከሚሄደው መስመር ሊደርሱ ምንም ያህል
አልቀራቸውም::
«ምን ዓይነት ቆራጥ ሽማግሌ ናቸው!» ሲሉ ተማሪዎቹ አጉረመረሙ። ማን እንደሆኑ ለማወቅ ተማሪዎቹ ጊዜ አልወሰደባቸውም ገዳም ውስጥ
ይኖሩ እንደነበር የሚያውቋቸው ሰዎች በሹክሹክታ ስማቸውን አስተጋቡ ሠራዊቱ አንዱን ጎዳና ጨርሶ ወደ ሌላው ተሸጋገረ፡፡ ጋቭሮችም መጓዙን ቀጠለ።
ብዙ በተጓዘ ቁጥር የሠራዊቱ ቁጥር እየጨመረ ሄደ፡፡ አንድ ግዙፍ ሰውነት ያለው ረጅም ሰው መጥቶ ተደባለቀ፡፡ ሽበት ጣል ጣል አድርጎበታል ፡መሪዎቹ ይህ ሰው ማን እንደሆነ አላወቁትም፡፡ ግን ወደ እነርሱ ለመጠጋት
በጣም ይፈልጋል፡፡ ጋቭሮች በሚያዜመው መዝሙር ተመስጦ ስለነበረ ሰውዬውን ልብ አላለውም፡፡ ልጁ መዝሙር ሲሰለቸው ያፏጫል፤ አንዳንዴ
ያንን ጥይት የሌለውን ሽጉጡን ያሻሻል፡፡
ሰልፈኛው መንገዱን ቀጥሎ እንደአጋጣሚ ሆኖ በኩርፌይራክ መኖሪያ ቤት ደጃፍ ያልፋል፡፡
«ጥሩ አጋጣሚ ነው» ይላል ኩርፌይራክ፡፡ «ቆቤ ጠፍቷል፤ ጠዋት ደግሞ ቦርሳዬን ረስቼ ነው የመጣሁት፡፡»
ከሰልፈኛው ተገንጥሎ ደረጃዎቹን በእጥፍ እየዘለለ ወደ ቤቱ ገባ
አንድ አሮጌ ቆብና የኪስ ቦርሳውን አነሳ፡፡ ከቆሻሻ ልብስ ውስጥ
የነበረ ሌላ አነስተኛ የእጅ ቦርሳም ወሰደ:: ደረጃውን በችኮላ ሲወርድ በጨለማ ውስጥ አንድ ሰው «ሊያነጋግርህ የሚፈልግ ሰው አለ» ሲል ነገረው፡፡
በዚህ ጊዜ አንድ የተቦጫጨቀ የሴት ቀሚስ ከላይ ያጠለቀ ወንድ
ከወደ ውስጥ ብቅ ብሎ አነጋገረው:: ድምፁ የሴት እንጂ የወንድ አይመስልም:: በጣም ቀጭን ነው::
«ማሪየስን አይተውታል?»
«የለም፤ ከቤት አልመጣም::»
«ማታ ይመጣ ይሆን?»
«እኔ እንጃ፡፡ እኔ ግን ዛሬ ወደቤት አልመለስም::»
አለባበሱና ድምፁ ሴት ያስመስለው ወጣት ኩርፌይራክን አፍጥጦ አየው
ለምን አይመለሱም?» ሲል በድፍረት ጠየቀው::
«ምክንያቱም...»
«እንግዲያው አንተ ወዴት ነው የምትሄደው?» በማለት ጣልቃ ገባ፡፡
«ምን ያደርግልሃል?»
«ቦርሳህን ልያዝልህ?»
«ወደ ጦርነቱ ቦታ ነው የምሄደው?»
«አብሬህ ብሄድ ትፈቅድልኛለህ?»
«ከፈለግህ፣ እኔ ምን ቸገረኝ» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት:: «መንገዱ
ነጻ፣ ጎዳናው የጋራ!»
ኩርፌይራክ ይህን እንደተናገረ ከጓደኞቹ ለመድረስ በሩጫ ወጣ፡፡
እንደደረሰም የእጅ ቦርሳውን እንዲይዝለት ለአንዱ ጓደኛው ሰጠው:: ከሩብ ሰዓት ጉዞ በኋላ መለስ ቢል ወጣቱ እንደተከተለው ተገነዘበ፡፡
ለአመዕ የተነሳሳ ሰልፈኛ ብዙውን ጊዜ የሚመራው በነፋስ ስለሆነ
አንዳንዴ ወደፈለገበት ሳይሆን ወደ አልፈለገበት አቅጣጫ ነው የሚጓዘው::ይህም በመሆኑ ይህ ሰልፈኛ ሴንትሜሪ ከተባለ ሥፍራ ለመሄድ ፈልጎ ሳይታወቀው ይህን ቦታ አልፎ ከሴንት ዴኒስ ይደርሳል፡፡
ከሰላሳ ዓመታት በፊት አንድ መንገደኛ ሴንት ዴኒስ ከተባለ ሥፍራ ቢያልፍ መንገዱ እየጠበበ ሄዶ በመጨረሻ እንደ አቁማዳ ጫፍ መደፈኑን ይገነዘብ ነበር፡፡ አካባቢውን አጥርቶ የማያውቅ ከሆነማ በግራና በቀኝ በኩል
የጨለማ መንገድ መኖሩን ስለማይረዳ መድረሻ ያጣል:: ውስጥ አዋቂ ግን በእነዚህ ጠባብ የጨለማ መንገዶች ተሹለክልኮ ሊያልፍ ይችላል፡፡ በስተቀኝ
በኩል ያለውን የቀኝ መንገድ ይዞ ሲጓዝ ከአንድ መሸታና ምግብ ቤት
👍14😁2❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...እውነትም ቦታው እስትራቴጂካዊ ነበር በአንድ በኩል ወደቤቱ ሚያስገባው መንገድ ሰፊ ነው:: በጓሮ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ቀጭን የጨለማ መንገድ አለው:: ማንኛውም አጥቂ ጦር በሴንት ዴኒስ
ጎዳና በኩል ባለው ሰፊ ጎዳና እንጂ በጓሮ በኩል ደፍሮ ሊገባ አይችልም::ስለዚህ የፊት ለፊቱን አጥብቀው ከያዙ የኋላውን በቀላሉ መመከት ይቻላል።
ድንገት ማፈግፈግም ቢመጣ በጓሮ በኩል የማምለጥ እድል አለ::
ያ ሁሉ ሕዝብ ሆ እያለ መለስ ሲል መንገዱ ሁሉ ጨነቀው::
ባለሱቅ ቶሎ ብሎ ሱቁን ዘጋ:: ከግራና ከቀኝ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የውጭ በር ካላቸው የውጭ በራቸውን፣ አለዚያም የየቤታቸውን በርና መስኮት ቀረቀሩ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ባይ መስኮቱን ከፍቶ በትንሹ ያያል፡፡ አላስችል
ያለውና «ምን ይቀርብኛል ብሎ ተስፋ የቆረጠው ከሰልፈኛው ጋር
ይደባለቃል፡፡
አንዲት በጣም የተደናገጠች አርጊት ምን አደረገች? ቶሎ ብላ አሮጌ ፍራሽ ከውጭ በኩል በገመድ በማንጠልጠል መስኮትዋን ሸፈነችው:: ሌላ
ፍራሽ ደግሞ ከውስጥ በኩል በማቆም ጋረደችው፡፡ ከዚያም ከመስኮቱ በር ወለል ላይ ለጥ ብላ ተኛች:: ጥይት ሲተኮስ እንዳይመታት ነበር፡፡
በዚያ አካባቢ በርና መስኮቱ የተከፈተ ቤት ሲኖር ያ መሸታ ቤትና ምግብ ቤት ብቻ ነበር:: ይሄ ደግሞ ያለ ምክንያት አልነበረም:: ትርምሱ፣ ጩኸቱ፣ ስድቡና
መዝሙሩ ድብልቅል ያለ ስለነበር የምጽዓት ቀን የመጣ
ስላስመሰለው ነው::
“ወያኔ ፣ ወይኔ፣ አምላኬ የዛሬን! ከዛሬው ብቻ ሰውረኝ» አሉ ማዳም ኻሽሉፕ ፡
ወዲያው በሃያ ደቂቃ ውስጥ ከሴትዮዋ መጠጥና ምግብ ቤት ምሽግ ተሠራ፡፡ በርሜሎች ተለቃቅመው በአሸዋና ጠጠር ተሞሉ፡፡ ጋብሮች በርሜል በማንከባለል ረዳ፡፡ በርሜል ሊሸፍነው ያልቻለውን ቦታ በአፈርና
በድንጋይ ቁልል ታጠረ፡፡ ኤንጂልራስ በጓሮው በኩል ወዳለው ጨለማ መንገድ የሚወስደውን በር ወለል አድርጎ ከፈተው:: ከዚያም ከቤቱ በር
ወደሚገኘው እቃ ማስቀመጫ ክፍል ወረደ:: ከምድር ቤቱ ውስጥ ወደሚገኘው ጥቂት በርሜሎችን አገኘ፡፡ እነርሱንም ለምሽግ ሥራ ተጠቀሙባቸው::መቼም እጅ ከተባበረ የማይሠራው ሥራ የለምና «ብዙ ቀናት ፈጅቷል
ተብሎ ሊገመት የሚችል ምሽግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡ በዚያች አጭር ሰዓት ያ ቤት ከቡናና ምግብ ቤትነት ወደ ጦር ካምፕ ተሸጋገረ::
አንድ ጋሪ ሴቶችን ጭኖ በዚያ በኩል ለማለፍ ይመጣል፡፡ ከሰልፈኞቹ መሪ አንደኛው ሮጦ ሄዶ ባለጋሪውንና ሴቶችን ካስወረደ በኋላ ሴቶቹን
ከይቅርታ ጋር አሰናበታቸው:: የፈረሱን ልጓም ይዞ በመጐተት ጋሪውን ወደ ምሽጉ ወሰደው::
«ጋሪ ደግሞ በዚህ ሰዓት፣ በዚህ መንገድ ምን ያደርጋል?» ሲል
ጠየቀ፡፡ «ከአሁን ቀደም በዚህ መንገድ ጋሪ አልፎ አያውቅም» ብሎ ከተናገረ በኋላ ፈረሱን ከጋሪው አላቅቆ አባረረው:: ፈረሱ ከሄደ በኋላ ጋሪውን በጎን
በማጋደም ያንን መንገድ ለመዝጋት ተጠቀመበት::
ማዳም ኸሽሉፕ ተናደዱ፣ የሚያደርጉትን ስላጡ ከአንደኛው ፎቅ ቁጭ ብለው ቀሩ፡፡ ዓይናቸው ከወዲያ ወዲህ ይቅበዘበዛል፡፡ፀ ሳይታወቃቸው እንባቸው በጉንጫቸው እንደ ጎርፍ ይወርዳል፡፡ ድምፅ አሰምተው ለማልቀስ ተሰብረዋል
አልደፈሩም::
«ምፅዓት ነው ይሄ» ሲሉ አጉረመረሙ::
ከሰካራሙ አንደኛው መጥቶ ጉንጫቸውን ከሳመ በኋላ «መቼም
እንደ ሴት ጉንጭ የሚለሰልስ ነገር የለም» ይላል፡፡
ቫውደር የተባለች ሠራተኛ እነርሱ ከነበሩበት ክፍል ገባች:: ከሰካራሞች ሌላው በሳቅ እየተፍነከነከ የሴትዮዋን ጨርቅ በመጎተት ወደ መስኮት
ወሰዳቸው:: ወደ ጆሮአቸው ተጠግቶ አናገራቸው::
«ቫውደር እኮ በጣም ፉንጋ ናት:: መቼስ ለፉንጋዎች ምሳሌ ሆና |
ልትቀርብ የምትችል ናት:: »
ወዲያው ኤንጆልራስ ጮክ እያለ ተናገረ፡፡
«እናንተ ሰካራሞች የምሽጉን ስም አታጉድፉ:: ቶሎ እንዲበርድላቸው
ከዚህ ሂዱና ከምትተኙበት ተኙ፡፡ ይህ ሥፍራ በአገር ፍቅር ለነደዱ እንጂ ለሰካራሞቹ አይደለም
ከሰካራሞቹ ማለትም ብዙም ያልጠነበዘው በዚህ ስድብ
ከተሞላበት ንግግር ስሜቱ በጣም ስለተነካ ውሃ በጣሳ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለበሰ፡፡ የውሃው ቅዝቃዜ እውነትም ስካሩን ትንሽ አበረደለት:: ወደ መስኮቱ ሄዶ ኢንጆልራስን ጥያቄ ጠየቀው::
«ከዚሁ ልተኛ?»
የለም፣ ከምትተኛበት ሂድና ተኛ እንጂ ከዚህ መተኛት አይቻልም::»
«እባካችሁ ነፍሴ እስክትወጣ ከዚሁ ልተኛ» ሲል ሰካራሙ በለዘበ አነጋገር ተናገረ፡፡
ኢንጆልራስ በንቀት ዓይን አየው:: ሰካራሙም የሚባለውን ሳይሰማ
ጥቂት ከተንተባተበ በኋላ አጠገቡ ከነበረው ጠረጴዛ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ብዙም ሳይቆይ እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ቸ
ዝናቡ ቆሞአል፡፡ ተጨማሪ ሰልፈኛ የተለያየ መሳርሪያ እየያዘ መጣ፡፡
በሩቁ የምትታይ አንዲት የመንገድ መብራት ብቻ ነበረች:: እስዋም ብዙ አልቆየችም፤ ሰልፈኞቹ ሰበርዋት:: የተቀሩት መብራቶች ቀደም ሲል
ተሰብረዋል፡፡
ኢንጆልራስ፣ ካምብፌራና ከርፌይራክ ለሰልፈኛው አመራር መስጠት ጀመሩ፡፡ መንገዱ በሁለቱም አቅጣጫ በምሽግ ተዘጋ:: የጦር መሣሪያ የያዙ
ሁሉ ቦታ ቦታቸውን ያዙ:: አንዳንዶቹ ቆብ መሳይ ነገር አጥልቀዋል::አንዳንዱ በአጭር ታጥቆ ጎራዴ ሲይዝ ሌላው ጠብመንጃ አንግቷል።
መሣሪያ ይዞ ፈረስ ላይ የተቀመጠም አለ፡፡ አንዳንዱ የመጨረሻው ሰው እስከቀረ ድረስ እንዋጋለን» እያለ ይፎክራል፡፡ ሌላው ጥይት ሲያልቅ
በድንጋይ እንማታለን» ይላል:: አንዱ ያቅራራል፣ ሌላው ይሸልላል::አንዳንዱም እነርሱ ሲጠቁ የከተማው ሰው እንደሚደርስላቻው እርስ በእርስ
ይወያያል፡፡ ሁሉም በየፊናው ይነጋገራል፤ ይቻኮላል፤ ሥራ ለመሥራትና ቦታ ለመያዝ ይጣደፋል፡፡ ሰካራሞቹና የቡና ቤቱ ባለቤት የሚያደርጉትን
አጥተው ከአንድ ክፍል ውስጥ ተፋጥጠው ቁጭ ብለዋል::
ከቁመቱ፡ ዘለግ ያለውና የሰልፈኛው መሪ የሆነው ሰው ከሰልፈኛው መካከል ገብቶ ምሽግ ይሠራል:: ጋብሮችም ከምሽጉ ጫፍ ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል:: ማሪየስን የጠየቀውና ኩርፊያሪክን ጠብቀኝ
ያለው የሴት መልክ ያለው ግለሰብ ግን ከዚያ አልነበረም፡፡ ጋብሮትች
ከደስታው ብዛት ከወዲህ ወዲያ የሚለው እየዘፈነ ስለነበር አብዛኛው ሰልፈኛ ለይቶታል:: እንዲያውም ከነአካቴው ሰው ሁሉ የእርሱን ንቃትና ሞራል እያየ በጣም ተደፋፈረ፣ ሰነፉንና ዳተኛውን አነቃቃ:: ለፈሪውም
ልብ ዋጀለት። ለተደነባበረውም መንገድ ከፈተለት።
ጋብሮች ከአሮጊትዋ በነጠቀው ሽጉጥ ስላልረካ «ጠብመንጃ
እፈልጋለሁ፣ ምነው ብትሰጡኝ» እያለ ይጠይቃል::
«ጠብመንጃ ለአንተ ነው ወይስ ለማነው?» ሲል ካምብፌሪ ጠየቀው
«ምነው?» ሲል ጋብሮች ጥያቄን በጥያቄ ይመልሳል፡፡ «ምን ይጉድለኛል? ድሮ እኮ እንዴት ያለ ጠብመንጃ ነበረኝ» ሲል ይሸልላል::
ኢንጆልራስ ይስቃል፡፡
«አዋቂዎቹ ሲዳረሳቸው ለልጆች ይሰጣል::»
ጋብሮች በቁጣ ዞር ብሎ ይመልሳል፡፡
«አንተን ከእኔ በፊት ከገደሉህ እኔ እኮ ነኝ አንተን የምተካው:: ላከወ
«ጉረኛ» ሲል በቀልድ መልክ ኢንጆልሪስ መለሰለት::
«ጉረኛ አልከኝ?» ሲል ጋቭሮች ቃሉን ደገመ:: ይህን እንደጠየቀ
አንድ ሰው ከሰልፉ ወጥቶ ያያል:: ሮጦ ሄዶ «ከሰልፈኛው ተለይተው
አይሄዱ፤ ለዚህች ምስኪን አገር የሚውሉት ውለታ ቢኖር አሁን ነው፤ ስለዚህ አይሂዱ» ሲል ይማጠናቸዋል፡፡ ሰውየው ግን ፈጠን ብለው በመራመድ
ይሄዳሉ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...እውነትም ቦታው እስትራቴጂካዊ ነበር በአንድ በኩል ወደቤቱ ሚያስገባው መንገድ ሰፊ ነው:: በጓሮ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ቀጭን የጨለማ መንገድ አለው:: ማንኛውም አጥቂ ጦር በሴንት ዴኒስ
ጎዳና በኩል ባለው ሰፊ ጎዳና እንጂ በጓሮ በኩል ደፍሮ ሊገባ አይችልም::ስለዚህ የፊት ለፊቱን አጥብቀው ከያዙ የኋላውን በቀላሉ መመከት ይቻላል።
ድንገት ማፈግፈግም ቢመጣ በጓሮ በኩል የማምለጥ እድል አለ::
ያ ሁሉ ሕዝብ ሆ እያለ መለስ ሲል መንገዱ ሁሉ ጨነቀው::
ባለሱቅ ቶሎ ብሎ ሱቁን ዘጋ:: ከግራና ከቀኝ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የውጭ በር ካላቸው የውጭ በራቸውን፣ አለዚያም የየቤታቸውን በርና መስኮት ቀረቀሩ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ባይ መስኮቱን ከፍቶ በትንሹ ያያል፡፡ አላስችል
ያለውና «ምን ይቀርብኛል ብሎ ተስፋ የቆረጠው ከሰልፈኛው ጋር
ይደባለቃል፡፡
አንዲት በጣም የተደናገጠች አርጊት ምን አደረገች? ቶሎ ብላ አሮጌ ፍራሽ ከውጭ በኩል በገመድ በማንጠልጠል መስኮትዋን ሸፈነችው:: ሌላ
ፍራሽ ደግሞ ከውስጥ በኩል በማቆም ጋረደችው፡፡ ከዚያም ከመስኮቱ በር ወለል ላይ ለጥ ብላ ተኛች:: ጥይት ሲተኮስ እንዳይመታት ነበር፡፡
በዚያ አካባቢ በርና መስኮቱ የተከፈተ ቤት ሲኖር ያ መሸታ ቤትና ምግብ ቤት ብቻ ነበር:: ይሄ ደግሞ ያለ ምክንያት አልነበረም:: ትርምሱ፣ ጩኸቱ፣ ስድቡና
መዝሙሩ ድብልቅል ያለ ስለነበር የምጽዓት ቀን የመጣ
ስላስመሰለው ነው::
“ወያኔ ፣ ወይኔ፣ አምላኬ የዛሬን! ከዛሬው ብቻ ሰውረኝ» አሉ ማዳም ኻሽሉፕ ፡
ወዲያው በሃያ ደቂቃ ውስጥ ከሴትዮዋ መጠጥና ምግብ ቤት ምሽግ ተሠራ፡፡ በርሜሎች ተለቃቅመው በአሸዋና ጠጠር ተሞሉ፡፡ ጋብሮች በርሜል በማንከባለል ረዳ፡፡ በርሜል ሊሸፍነው ያልቻለውን ቦታ በአፈርና
በድንጋይ ቁልል ታጠረ፡፡ ኤንጂልራስ በጓሮው በኩል ወዳለው ጨለማ መንገድ የሚወስደውን በር ወለል አድርጎ ከፈተው:: ከዚያም ከቤቱ በር
ወደሚገኘው እቃ ማስቀመጫ ክፍል ወረደ:: ከምድር ቤቱ ውስጥ ወደሚገኘው ጥቂት በርሜሎችን አገኘ፡፡ እነርሱንም ለምሽግ ሥራ ተጠቀሙባቸው::መቼም እጅ ከተባበረ የማይሠራው ሥራ የለምና «ብዙ ቀናት ፈጅቷል
ተብሎ ሊገመት የሚችል ምሽግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡ በዚያች አጭር ሰዓት ያ ቤት ከቡናና ምግብ ቤትነት ወደ ጦር ካምፕ ተሸጋገረ::
አንድ ጋሪ ሴቶችን ጭኖ በዚያ በኩል ለማለፍ ይመጣል፡፡ ከሰልፈኞቹ መሪ አንደኛው ሮጦ ሄዶ ባለጋሪውንና ሴቶችን ካስወረደ በኋላ ሴቶቹን
ከይቅርታ ጋር አሰናበታቸው:: የፈረሱን ልጓም ይዞ በመጐተት ጋሪውን ወደ ምሽጉ ወሰደው::
«ጋሪ ደግሞ በዚህ ሰዓት፣ በዚህ መንገድ ምን ያደርጋል?» ሲል
ጠየቀ፡፡ «ከአሁን ቀደም በዚህ መንገድ ጋሪ አልፎ አያውቅም» ብሎ ከተናገረ በኋላ ፈረሱን ከጋሪው አላቅቆ አባረረው:: ፈረሱ ከሄደ በኋላ ጋሪውን በጎን
በማጋደም ያንን መንገድ ለመዝጋት ተጠቀመበት::
ማዳም ኸሽሉፕ ተናደዱ፣ የሚያደርጉትን ስላጡ ከአንደኛው ፎቅ ቁጭ ብለው ቀሩ፡፡ ዓይናቸው ከወዲያ ወዲህ ይቅበዘበዛል፡፡ፀ ሳይታወቃቸው እንባቸው በጉንጫቸው እንደ ጎርፍ ይወርዳል፡፡ ድምፅ አሰምተው ለማልቀስ ተሰብረዋል
አልደፈሩም::
«ምፅዓት ነው ይሄ» ሲሉ አጉረመረሙ::
ከሰካራሙ አንደኛው መጥቶ ጉንጫቸውን ከሳመ በኋላ «መቼም
እንደ ሴት ጉንጭ የሚለሰልስ ነገር የለም» ይላል፡፡
ቫውደር የተባለች ሠራተኛ እነርሱ ከነበሩበት ክፍል ገባች:: ከሰካራሞች ሌላው በሳቅ እየተፍነከነከ የሴትዮዋን ጨርቅ በመጎተት ወደ መስኮት
ወሰዳቸው:: ወደ ጆሮአቸው ተጠግቶ አናገራቸው::
«ቫውደር እኮ በጣም ፉንጋ ናት:: መቼስ ለፉንጋዎች ምሳሌ ሆና |
ልትቀርብ የምትችል ናት:: »
ወዲያው ኤንጆልራስ ጮክ እያለ ተናገረ፡፡
«እናንተ ሰካራሞች የምሽጉን ስም አታጉድፉ:: ቶሎ እንዲበርድላቸው
ከዚህ ሂዱና ከምትተኙበት ተኙ፡፡ ይህ ሥፍራ በአገር ፍቅር ለነደዱ እንጂ ለሰካራሞቹ አይደለም
ከሰካራሞቹ ማለትም ብዙም ያልጠነበዘው በዚህ ስድብ
ከተሞላበት ንግግር ስሜቱ በጣም ስለተነካ ውሃ በጣሳ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለበሰ፡፡ የውሃው ቅዝቃዜ እውነትም ስካሩን ትንሽ አበረደለት:: ወደ መስኮቱ ሄዶ ኢንጆልራስን ጥያቄ ጠየቀው::
«ከዚሁ ልተኛ?»
የለም፣ ከምትተኛበት ሂድና ተኛ እንጂ ከዚህ መተኛት አይቻልም::»
«እባካችሁ ነፍሴ እስክትወጣ ከዚሁ ልተኛ» ሲል ሰካራሙ በለዘበ አነጋገር ተናገረ፡፡
ኢንጆልራስ በንቀት ዓይን አየው:: ሰካራሙም የሚባለውን ሳይሰማ
ጥቂት ከተንተባተበ በኋላ አጠገቡ ከነበረው ጠረጴዛ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ብዙም ሳይቆይ እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ቸ
ዝናቡ ቆሞአል፡፡ ተጨማሪ ሰልፈኛ የተለያየ መሳርሪያ እየያዘ መጣ፡፡
በሩቁ የምትታይ አንዲት የመንገድ መብራት ብቻ ነበረች:: እስዋም ብዙ አልቆየችም፤ ሰልፈኞቹ ሰበርዋት:: የተቀሩት መብራቶች ቀደም ሲል
ተሰብረዋል፡፡
ኢንጆልራስ፣ ካምብፌራና ከርፌይራክ ለሰልፈኛው አመራር መስጠት ጀመሩ፡፡ መንገዱ በሁለቱም አቅጣጫ በምሽግ ተዘጋ:: የጦር መሣሪያ የያዙ
ሁሉ ቦታ ቦታቸውን ያዙ:: አንዳንዶቹ ቆብ መሳይ ነገር አጥልቀዋል::አንዳንዱ በአጭር ታጥቆ ጎራዴ ሲይዝ ሌላው ጠብመንጃ አንግቷል።
መሣሪያ ይዞ ፈረስ ላይ የተቀመጠም አለ፡፡ አንዳንዱ የመጨረሻው ሰው እስከቀረ ድረስ እንዋጋለን» እያለ ይፎክራል፡፡ ሌላው ጥይት ሲያልቅ
በድንጋይ እንማታለን» ይላል:: አንዱ ያቅራራል፣ ሌላው ይሸልላል::አንዳንዱም እነርሱ ሲጠቁ የከተማው ሰው እንደሚደርስላቻው እርስ በእርስ
ይወያያል፡፡ ሁሉም በየፊናው ይነጋገራል፤ ይቻኮላል፤ ሥራ ለመሥራትና ቦታ ለመያዝ ይጣደፋል፡፡ ሰካራሞቹና የቡና ቤቱ ባለቤት የሚያደርጉትን
አጥተው ከአንድ ክፍል ውስጥ ተፋጥጠው ቁጭ ብለዋል::
ከቁመቱ፡ ዘለግ ያለውና የሰልፈኛው መሪ የሆነው ሰው ከሰልፈኛው መካከል ገብቶ ምሽግ ይሠራል:: ጋብሮችም ከምሽጉ ጫፍ ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል:: ማሪየስን የጠየቀውና ኩርፊያሪክን ጠብቀኝ
ያለው የሴት መልክ ያለው ግለሰብ ግን ከዚያ አልነበረም፡፡ ጋብሮትች
ከደስታው ብዛት ከወዲህ ወዲያ የሚለው እየዘፈነ ስለነበር አብዛኛው ሰልፈኛ ለይቶታል:: እንዲያውም ከነአካቴው ሰው ሁሉ የእርሱን ንቃትና ሞራል እያየ በጣም ተደፋፈረ፣ ሰነፉንና ዳተኛውን አነቃቃ:: ለፈሪውም
ልብ ዋጀለት። ለተደነባበረውም መንገድ ከፈተለት።
ጋብሮች ከአሮጊትዋ በነጠቀው ሽጉጥ ስላልረካ «ጠብመንጃ
እፈልጋለሁ፣ ምነው ብትሰጡኝ» እያለ ይጠይቃል::
«ጠብመንጃ ለአንተ ነው ወይስ ለማነው?» ሲል ካምብፌሪ ጠየቀው
«ምነው?» ሲል ጋብሮች ጥያቄን በጥያቄ ይመልሳል፡፡ «ምን ይጉድለኛል? ድሮ እኮ እንዴት ያለ ጠብመንጃ ነበረኝ» ሲል ይሸልላል::
ኢንጆልራስ ይስቃል፡፡
«አዋቂዎቹ ሲዳረሳቸው ለልጆች ይሰጣል::»
ጋብሮች በቁጣ ዞር ብሎ ይመልሳል፡፡
«አንተን ከእኔ በፊት ከገደሉህ እኔ እኮ ነኝ አንተን የምተካው:: ላከወ
«ጉረኛ» ሲል በቀልድ መልክ ኢንጆልሪስ መለሰለት::
«ጉረኛ አልከኝ?» ሲል ጋቭሮች ቃሉን ደገመ:: ይህን እንደጠየቀ
አንድ ሰው ከሰልፉ ወጥቶ ያያል:: ሮጦ ሄዶ «ከሰልፈኛው ተለይተው
አይሄዱ፤ ለዚህች ምስኪን አገር የሚውሉት ውለታ ቢኖር አሁን ነው፤ ስለዚህ አይሂዱ» ሲል ይማጠናቸዋል፡፡ ሰውየው ግን ፈጠን ብለው በመራመድ
ይሄዳሉ፡፡
👍12
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡
ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)
ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡
ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::
«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»
« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»
«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»
«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡
«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።
በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::
“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»
«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::
«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::
«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»
«አልችልም ጌታው::»
ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::
«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው
«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::
ሸ
«እምቢ አልክ?»
«አዎን የእኔ ጀግ…»
የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::
«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::
«እጅ ወደ ላይ!» አለው::
ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡
«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡
የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።
ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡
«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»
ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::
ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡
«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»
ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::
ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡
«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::
የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡
«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::
«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡
ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)
ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡
ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::
«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»
« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»
«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»
«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡
«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።
በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::
“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»
«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::
«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::
«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»
«አልችልም ጌታው::»
ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::
«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው
«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::
ሸ
«እምቢ አልክ?»
«አዎን የእኔ ጀግ…»
የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::
«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::
«እጅ ወደ ላይ!» አለው::
ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡
«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡
የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።
ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡
«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»
ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::
ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡
«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»
ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::
ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡
«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::
የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡
«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::
«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
👍9
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ኢንጆልራስ ጎንበስ ብሎ የራሣውን ጭንቅላት ቀና ካደረገ በኋላ ግምባሩን ሳመው፡፡
መሞቱን በመርሳት በጥንቃቄ ያልያዘው እንደሆነ የሚያምመው ይመስል ቀስ ብሎ በክርኑ ደግፎ ቀና አደረገው፡፡ የሟቹን
ኮት ካወለቀ በኋላ የሚደሙትን ቀዳዳዎች ለተመልካች አሳየ።
«ይሄ ነው ባንዲራችን!»
ነጭ አንሶላ አምጥተው የመሴይ ማብዩፍን አስከሬን ሸፈኑት:: ስድስት ሰዎች ጠብመንጃዎቻቸውን ከስር አጋድመው ሬሣውን ከዚያ ላይ ካሳረፉ በኋላ ወደ ምድር ቤት በዝግታ ወስደው ከትልቅ ጠረጴዛ ላይ አጋደሙት፡፡ ሰዎቹ በሚፈጽሙት ተግባር ቅዱስነት በመዋጥ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ
መሆናቸውን ጨርሰው ረሱ::
አስከሬኑ ከዣቬር ከታሰረበት ግንድ አጠገብ ሲያልፍ ኢንጆልራስ
ሰላዩን አናገረው::
«የምትቀጥለው አንተ ነህ::»
በዚህ ጊዜ ብቻውን የጥበቃውን ተግባር ያከናውን የነበረው ጋብሮች ሰዎች ከምሽጉ ውስጥ ሲገቡ ውልብ አለው:: በድንገት ጩኸት ተሰማ::
‹‹ተጠንቀቁ!»
የአድማው መሪዎች በሙሉ ዘልለው ወደ ውጭ ወጡ:: የሚያባክኑት ጊዜ አልነበራቸውም:: ወታደሮች ሳንጃቸውን ወድረው ከምሽጉ ሲገቡ ተመለከቱ፡፡
ያቺ ሰዓት ወሳኝ ነበረች:: ምሽጉ በንጉሡ ወታደሮች ተወረረ::
በመጀመሪያ ዘልሎ የገባው ወታደር ከውስጥ የነበረ አንድ ሰው ግምባሩን ብሎ ጣለው:: ገዳዩ ወዲያው በጠላት ወገን ወታደር ተገደለ:: አሁንም ሌላ
ወታደር ከርፌይራክን ከመሬት ስለዘረረው እንደወደቀ «እርዱኝ» እያለ ጮኸ፡፡ በዚያው ወቅት እጅግ በጣም ግዙፍ የሆነ ወታደር ጋቭሮች ከነበረበት ክፍል ገባ፡፡ ጋቭሮች ጠብመንጃዋን ከዣቬር ወደ ወታደሩ አዙራ ለመተኮስ
ቶሎ ብላ ቃታውን ሳብ አደረገች:: ግን ምን ይሆናል ዣቬር ጠብመንጃውን ሲሰጥ ለካስ ጥይት አላጎረሰው ኖር ፀጥ አለ፡፡ ወታደሩ ከት ብሎ ሳቀ፡፡
ሳንጃውን ወድሮ ወደ ልጁ ሄደ::
ወታደሩ ልጁ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ከኋላው ስለተመታ በአፍጢሙ ተደፋ:: ወዲያው ከርፌይራክን የመታው ወታደር ሲወድቅ ታየ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የገደላቸወ ማሪየስ ነበር፡፡
ማሪየስ የመጀመሪያውን ውጊያ በሩቁ ሆኖ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ
ነበር ያየው:: በሁለተኛው ግን የጋብሮችን ሕይወት በመጀመሪያ ሲያድን ጓደኛውን ቀጥሎ ነው ነፃ ያወጣው፡፡ ኩርፌይራክ ከመሬት ወደቀ እንጂ አልተመታም ነበር፡፡
ወታደሮቹ ከምሽጉ ሁለት ሦስተኛ የሚሆነውን ክፍል ከቁጥጥራቸው
ሥር አውለዋል፡፡ በጣም ወደ ውስጥ ዘልቀው ለመግባት ግን አልደፈሩም:: ምናልባት አንድ ዓይነት ወጥመድ ቢኖር ብለው ተጠራጥረዋል። በዚያ !
አካባቢ ይበራ የነበረው መብራት እስከ ውስጥ ዘልቆ አያሳይም::
አንድ ወታደር ማሪየስን ለመጣል ሲያነጣጥር ድንገት ከመሀል አንድ ሰው በመግባቱ የእርሱን እጣ ሰውዬው ወሰደ:: ወዲያው በድንገት አንድ በጣም የሚጮህ ድምፅ ተሰማ::
«እጃችሁን ስጡ ፤ አለበለዚያ ምሽጉን እንዳለ እናቃጥለዋለን፡፡»
አድምኞቹ ሁሉ ድምፁ ወደ ተሰማበት አቅጣጫ ፊታቸውን አዞሩ፡፡ ማሪየስ ከየት መጣ ሳይባል ይህን ያለውን የሃምሣ አለቃ ስለጣለው ምሽጉ ከመጥፋት ዳነ፡፡
አድመኞቹ በሙሉ ማሪየስን ከበቡት:: ኩርፌይራክ ከወደቀበት ተነስቶ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመ
«እንዴት ያለ አጋጣሚ ነው» አለ ኮምብፌሬ::
«ጥሩ ጊዜ ደረስክ» አለ ቦስዩ ቀጠለና::
«አንተ ባትደርስ ይህን ጊዜ በሕይወት የለሁም» አለ ከርፌይራክ።
«እኔ ደግሞ ይህን ጊዜ በአፍጢሜ ተደፍቼ ነበር» አለ ጋቭሮች ቀጥሎ፡፡
ወዲያው አንድ ድርጊት በመፈጸሙ ደስታቸው በሀዘን ተለወጠ። ከመካከላቸው በጣም የሚወዱትና የሚያደንቁት አንዱ ጓደኛቸው ተሰወረ። ከቁስለኛ መካከል ፈለጉት:: ከዚያ አልነበረም:: ከሞቱት መካከል አዩት ከዚያም አልነበረም፡፡ ተማርኳል ማለት ነበር፡፡
«ወንድማችንን ወሰዱት፤ እኛ የእነርሱን መኮንን እንደያዝን ሁሉ
እነርሱም ጓደኛችንን ያዙት ማለት ነው:: በሰላዩ ላይ ስለምንወስደው
እርምጃ ወስነናል?» ሲል ኮምብፌሬ ኢንጆልራስን ጠየቀው፡፡
«አዎን» አለ ኢንጆልራስ የኮምብፌሬን ትከሻ እየነካካ፡፡ «ሆኖም የሰላዩ ደም የጓደኛችንን የዣን ጥሩቬርንን ደም አያህልም፡፡»
«እንግዲያውማ» አለ ኮምብፌራ «መሐረቤን ከጠመንጃዬ ጫፍ
አስሬ ልውጣና ሰላዩን በጓደኛችን እንዲለወጡን ልጠይቅ::»
«ስማ» ብሎ ኢንጆልራስ ሲናገር ከውጭ አንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
የወንድ ድምፅ ነበር::
«ፈረንሣይ ለዘላለም ትኑር!»
የጓደኛቸው ድምዕ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጥይት ተተኩሰ፡፡ ከዚያም ሁሉም ነገር እርጭ አለ::
«ጓደኛችንን ገደሉት!» አለ ኮምብፌሬ:: ኢንጆልራስ ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ጓደኞችህ አሁን አንተን ነው የገደሉት» አለው::
አድመኞቹ ሁሉ አሁን ከቤት ወስጥ ገብቷል:: ማሪየስም
ተከትሉኣቸው ሊገባ ሲል «መሴይ ማሪየስ» ተብሎ ስሙ ሲጠራ ሰምቶ በመደንገጥ ዞር አለ፡፡ ከሁለት ሰዓት በፊት ኮዜትን እየጠበቀ ሳለ ከአጥር ውጭ ሆኖ የጠራው ድምፅ እንደሆነ አውቋል፡፡ ማን እንደሆነ ለማወቅ
ፊቱን ቢያዞርም መለየት አልቻለም:: «እዚህ ነኝ» አለ ያው ድምፅ በጣም የደከመ በመምሰል፡፡
መሬት ለመሬት እየተንፏቀቀ የሚመጣ ሰው በሩቁ ተመለከተ፡፡
መብራት ካለበት ሲደርስ የሴት ሸሚዝ የለበሰ ሰው መሆኑን አየ:: ከስር የተቀዳደደ ሱሪ ታጥቋል፡፡ ጫማ አላጠለቀም፡፡ ይህ ፍጡር ማሪየስ ከነበረበት ሲደርስ የገረጣ ፊቱን ቀና አደረገ፡፡
«አታውቀኝም?»
«የለም»
«ኢፓኒን፡፡»
ማሪየስ ቶሎ ብሎ ወደ መሬት አጎነበሰ፡፡ እውነትም ያቺ እድለቢስ
ኢፖኒን ነበረች፡፡ እንደ ወንድ ነው የለበሰችው::
«እንዴት መጣሽ?» ከዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?
‹‹መሞቴ ነው» ስትል መለሰችለት::
ማሪየስ ደንግጦ «ተመትተሻል እንዴ?» ሲል ጠየቃት::
ከመሬት ብድግ ሊያደርጋት ቀኝ እጁን ከወገብዋ ስር አስገባ፡፡ ብድግ ሲያደርጋት እጅዋ ተዝለፈለፈ:: የማቃሰት ድምፅ አሰማች፡፡
«አሳመምኩሽ?»
«ትንሽ»
«ምነው እጅሽ ዛለ?» ብሎ" ሲያየው በጥይት ተመትቷል፡፡
«ቆስሎአል፧ አይደለም?»
«አዎን፡፡»
«ማን መታሽ?»
«ከጥቂት ጊዜ በፊት ጠብመንጃ ተደቅኖብህ ልትመታ ስትል አንድ
ሰው ከመሀል መግባቱ ትዝ ይልሃል?»
«አዎን፣ አስታውሳለሁ::»
የእኔ እጅ ነው ጣልቃ የገባው::
የማሪየስ ልብ ከሁለት የተሰነጠቀ መሰለው:: ነገሩ አልገባውም::
ምነው እንደዚያ አደረግሽ! ምስኪን! ብቻ ቁስሉ ለክፉ አይሰጥሽም።
ለማንኛውም ከውስጥ አስገብቼ ላስተኛሽ፡፡»
እጄ ብቻ እኮ አይደለም የተመታው:: ጥይቱ በእጄ አልፎ ከብብቴ ጥቂት ዝቅ ብሉ ወደ ወገቤ በመግባቱ ቀስፎ ይዞኛል» አለች በኃይል ለመተንፈስ እየታገለች::
«ስለዚህ ወደ ውስጥ መግባቱ ዋጋ የለውም:: አሁን ብቻ ከአጠገቤ ቁጭ ብለህ አጫውተኝ፡፡ ጨዋታህ ከሐኪም እርዳታ ይበልጥብኛል፡፡»
ትእዛዝዋን ተቀብሎ እግሩን በመዘርጋት ከአጠገብዋ ቁጭ አለ።
ጭንቅላትዋን ከጉልበቱ ላይ አሳረፈች:: ቀና ብላ ሳታየው «እፎይ ተመስገን እንዴት ይመቻል? ምን ዓይነት ደግ ሰው ነህ! በቃ! ሕመሙ ተቀነሰልኝ
ስትል ቀባጠረች፣::
ከዚያም ለጥቂት ጊዜ ፀጥ አለች:: ቀስ ብላ ፊትዋን ወደ ማሪየስ
አዙራ ቀና ብላ አየችው::
«አስቀያሚ ናት ነው ያልከው፤ አይደል? » ንግግርዋን በማቆም ጥቂት ዝም ካለች በኋላ እንደገና ቀጠለች::
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ኢንጆልራስ ጎንበስ ብሎ የራሣውን ጭንቅላት ቀና ካደረገ በኋላ ግምባሩን ሳመው፡፡
መሞቱን በመርሳት በጥንቃቄ ያልያዘው እንደሆነ የሚያምመው ይመስል ቀስ ብሎ በክርኑ ደግፎ ቀና አደረገው፡፡ የሟቹን
ኮት ካወለቀ በኋላ የሚደሙትን ቀዳዳዎች ለተመልካች አሳየ።
«ይሄ ነው ባንዲራችን!»
ነጭ አንሶላ አምጥተው የመሴይ ማብዩፍን አስከሬን ሸፈኑት:: ስድስት ሰዎች ጠብመንጃዎቻቸውን ከስር አጋድመው ሬሣውን ከዚያ ላይ ካሳረፉ በኋላ ወደ ምድር ቤት በዝግታ ወስደው ከትልቅ ጠረጴዛ ላይ አጋደሙት፡፡ ሰዎቹ በሚፈጽሙት ተግባር ቅዱስነት በመዋጥ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ
መሆናቸውን ጨርሰው ረሱ::
አስከሬኑ ከዣቬር ከታሰረበት ግንድ አጠገብ ሲያልፍ ኢንጆልራስ
ሰላዩን አናገረው::
«የምትቀጥለው አንተ ነህ::»
በዚህ ጊዜ ብቻውን የጥበቃውን ተግባር ያከናውን የነበረው ጋብሮች ሰዎች ከምሽጉ ውስጥ ሲገቡ ውልብ አለው:: በድንገት ጩኸት ተሰማ::
‹‹ተጠንቀቁ!»
የአድማው መሪዎች በሙሉ ዘልለው ወደ ውጭ ወጡ:: የሚያባክኑት ጊዜ አልነበራቸውም:: ወታደሮች ሳንጃቸውን ወድረው ከምሽጉ ሲገቡ ተመለከቱ፡፡
ያቺ ሰዓት ወሳኝ ነበረች:: ምሽጉ በንጉሡ ወታደሮች ተወረረ::
በመጀመሪያ ዘልሎ የገባው ወታደር ከውስጥ የነበረ አንድ ሰው ግምባሩን ብሎ ጣለው:: ገዳዩ ወዲያው በጠላት ወገን ወታደር ተገደለ:: አሁንም ሌላ
ወታደር ከርፌይራክን ከመሬት ስለዘረረው እንደወደቀ «እርዱኝ» እያለ ጮኸ፡፡ በዚያው ወቅት እጅግ በጣም ግዙፍ የሆነ ወታደር ጋቭሮች ከነበረበት ክፍል ገባ፡፡ ጋቭሮች ጠብመንጃዋን ከዣቬር ወደ ወታደሩ አዙራ ለመተኮስ
ቶሎ ብላ ቃታውን ሳብ አደረገች:: ግን ምን ይሆናል ዣቬር ጠብመንጃውን ሲሰጥ ለካስ ጥይት አላጎረሰው ኖር ፀጥ አለ፡፡ ወታደሩ ከት ብሎ ሳቀ፡፡
ሳንጃውን ወድሮ ወደ ልጁ ሄደ::
ወታደሩ ልጁ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ከኋላው ስለተመታ በአፍጢሙ ተደፋ:: ወዲያው ከርፌይራክን የመታው ወታደር ሲወድቅ ታየ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የገደላቸወ ማሪየስ ነበር፡፡
ማሪየስ የመጀመሪያውን ውጊያ በሩቁ ሆኖ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ
ነበር ያየው:: በሁለተኛው ግን የጋብሮችን ሕይወት በመጀመሪያ ሲያድን ጓደኛውን ቀጥሎ ነው ነፃ ያወጣው፡፡ ኩርፌይራክ ከመሬት ወደቀ እንጂ አልተመታም ነበር፡፡
ወታደሮቹ ከምሽጉ ሁለት ሦስተኛ የሚሆነውን ክፍል ከቁጥጥራቸው
ሥር አውለዋል፡፡ በጣም ወደ ውስጥ ዘልቀው ለመግባት ግን አልደፈሩም:: ምናልባት አንድ ዓይነት ወጥመድ ቢኖር ብለው ተጠራጥረዋል። በዚያ !
አካባቢ ይበራ የነበረው መብራት እስከ ውስጥ ዘልቆ አያሳይም::
አንድ ወታደር ማሪየስን ለመጣል ሲያነጣጥር ድንገት ከመሀል አንድ ሰው በመግባቱ የእርሱን እጣ ሰውዬው ወሰደ:: ወዲያው በድንገት አንድ በጣም የሚጮህ ድምፅ ተሰማ::
«እጃችሁን ስጡ ፤ አለበለዚያ ምሽጉን እንዳለ እናቃጥለዋለን፡፡»
አድምኞቹ ሁሉ ድምፁ ወደ ተሰማበት አቅጣጫ ፊታቸውን አዞሩ፡፡ ማሪየስ ከየት መጣ ሳይባል ይህን ያለውን የሃምሣ አለቃ ስለጣለው ምሽጉ ከመጥፋት ዳነ፡፡
አድመኞቹ በሙሉ ማሪየስን ከበቡት:: ኩርፌይራክ ከወደቀበት ተነስቶ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመ
«እንዴት ያለ አጋጣሚ ነው» አለ ኮምብፌሬ::
«ጥሩ ጊዜ ደረስክ» አለ ቦስዩ ቀጠለና::
«አንተ ባትደርስ ይህን ጊዜ በሕይወት የለሁም» አለ ከርፌይራክ።
«እኔ ደግሞ ይህን ጊዜ በአፍጢሜ ተደፍቼ ነበር» አለ ጋቭሮች ቀጥሎ፡፡
ወዲያው አንድ ድርጊት በመፈጸሙ ደስታቸው በሀዘን ተለወጠ። ከመካከላቸው በጣም የሚወዱትና የሚያደንቁት አንዱ ጓደኛቸው ተሰወረ። ከቁስለኛ መካከል ፈለጉት:: ከዚያ አልነበረም:: ከሞቱት መካከል አዩት ከዚያም አልነበረም፡፡ ተማርኳል ማለት ነበር፡፡
«ወንድማችንን ወሰዱት፤ እኛ የእነርሱን መኮንን እንደያዝን ሁሉ
እነርሱም ጓደኛችንን ያዙት ማለት ነው:: በሰላዩ ላይ ስለምንወስደው
እርምጃ ወስነናል?» ሲል ኮምብፌሬ ኢንጆልራስን ጠየቀው፡፡
«አዎን» አለ ኢንጆልራስ የኮምብፌሬን ትከሻ እየነካካ፡፡ «ሆኖም የሰላዩ ደም የጓደኛችንን የዣን ጥሩቬርንን ደም አያህልም፡፡»
«እንግዲያውማ» አለ ኮምብፌራ «መሐረቤን ከጠመንጃዬ ጫፍ
አስሬ ልውጣና ሰላዩን በጓደኛችን እንዲለወጡን ልጠይቅ::»
«ስማ» ብሎ ኢንጆልራስ ሲናገር ከውጭ አንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
የወንድ ድምፅ ነበር::
«ፈረንሣይ ለዘላለም ትኑር!»
የጓደኛቸው ድምዕ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጥይት ተተኩሰ፡፡ ከዚያም ሁሉም ነገር እርጭ አለ::
«ጓደኛችንን ገደሉት!» አለ ኮምብፌሬ:: ኢንጆልራስ ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ጓደኞችህ አሁን አንተን ነው የገደሉት» አለው::
አድመኞቹ ሁሉ አሁን ከቤት ወስጥ ገብቷል:: ማሪየስም
ተከትሉኣቸው ሊገባ ሲል «መሴይ ማሪየስ» ተብሎ ስሙ ሲጠራ ሰምቶ በመደንገጥ ዞር አለ፡፡ ከሁለት ሰዓት በፊት ኮዜትን እየጠበቀ ሳለ ከአጥር ውጭ ሆኖ የጠራው ድምፅ እንደሆነ አውቋል፡፡ ማን እንደሆነ ለማወቅ
ፊቱን ቢያዞርም መለየት አልቻለም:: «እዚህ ነኝ» አለ ያው ድምፅ በጣም የደከመ በመምሰል፡፡
መሬት ለመሬት እየተንፏቀቀ የሚመጣ ሰው በሩቁ ተመለከተ፡፡
መብራት ካለበት ሲደርስ የሴት ሸሚዝ የለበሰ ሰው መሆኑን አየ:: ከስር የተቀዳደደ ሱሪ ታጥቋል፡፡ ጫማ አላጠለቀም፡፡ ይህ ፍጡር ማሪየስ ከነበረበት ሲደርስ የገረጣ ፊቱን ቀና አደረገ፡፡
«አታውቀኝም?»
«የለም»
«ኢፓኒን፡፡»
ማሪየስ ቶሎ ብሎ ወደ መሬት አጎነበሰ፡፡ እውነትም ያቺ እድለቢስ
ኢፖኒን ነበረች፡፡ እንደ ወንድ ነው የለበሰችው::
«እንዴት መጣሽ?» ከዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?
‹‹መሞቴ ነው» ስትል መለሰችለት::
ማሪየስ ደንግጦ «ተመትተሻል እንዴ?» ሲል ጠየቃት::
ከመሬት ብድግ ሊያደርጋት ቀኝ እጁን ከወገብዋ ስር አስገባ፡፡ ብድግ ሲያደርጋት እጅዋ ተዝለፈለፈ:: የማቃሰት ድምፅ አሰማች፡፡
«አሳመምኩሽ?»
«ትንሽ»
«ምነው እጅሽ ዛለ?» ብሎ" ሲያየው በጥይት ተመትቷል፡፡
«ቆስሎአል፧ አይደለም?»
«አዎን፡፡»
«ማን መታሽ?»
«ከጥቂት ጊዜ በፊት ጠብመንጃ ተደቅኖብህ ልትመታ ስትል አንድ
ሰው ከመሀል መግባቱ ትዝ ይልሃል?»
«አዎን፣ አስታውሳለሁ::»
የእኔ እጅ ነው ጣልቃ የገባው::
የማሪየስ ልብ ከሁለት የተሰነጠቀ መሰለው:: ነገሩ አልገባውም::
ምነው እንደዚያ አደረግሽ! ምስኪን! ብቻ ቁስሉ ለክፉ አይሰጥሽም።
ለማንኛውም ከውስጥ አስገብቼ ላስተኛሽ፡፡»
እጄ ብቻ እኮ አይደለም የተመታው:: ጥይቱ በእጄ አልፎ ከብብቴ ጥቂት ዝቅ ብሉ ወደ ወገቤ በመግባቱ ቀስፎ ይዞኛል» አለች በኃይል ለመተንፈስ እየታገለች::
«ስለዚህ ወደ ውስጥ መግባቱ ዋጋ የለውም:: አሁን ብቻ ከአጠገቤ ቁጭ ብለህ አጫውተኝ፡፡ ጨዋታህ ከሐኪም እርዳታ ይበልጥብኛል፡፡»
ትእዛዝዋን ተቀብሎ እግሩን በመዘርጋት ከአጠገብዋ ቁጭ አለ።
ጭንቅላትዋን ከጉልበቱ ላይ አሳረፈች:: ቀና ብላ ሳታየው «እፎይ ተመስገን እንዴት ይመቻል? ምን ዓይነት ደግ ሰው ነህ! በቃ! ሕመሙ ተቀነሰልኝ
ስትል ቀባጠረች፣::
ከዚያም ለጥቂት ጊዜ ፀጥ አለች:: ቀስ ብላ ፊትዋን ወደ ማሪየስ
አዙራ ቀና ብላ አየችው::
«አስቀያሚ ናት ነው ያልከው፤ አይደል? » ንግግርዋን በማቆም ጥቂት ዝም ካለች በኋላ እንደገና ቀጠለች::
👍19