አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ገረገራ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በታደለ_አያሌው

...ለአንዳፍታም ቢሆን እንኳን ቱናትን መለየት ያሸብራል፡ መቼስ እንዲህ የሚያደርገኝ ልጅነቷ ወይም መላመዳችን ወይ ደግሞ ገዳሜ ስለሆነች ብቻ አይመስለኝም፡ ታዲያ ምንድነዉ?
ብቻ ክብድ ብሎኛል፡

ደረስሁ።

ከጨዋታ ይልቅ ለዝምታ የሚያመቸዉን በትላልቅ ሀገር በቀል ዛፎች የተሞላዉን ግቢ፣ በተለያየ ዕድሜ የሚገኙት ሕጻናት ይቦርቁበታል። አንዳንዶች ክብ ሠርተዉ፣ አንዳንዶች በመስመር ሆነዉ፣ ሌሎች ዝብርቅርቅ ብለዉ የልባቸዉን ይጫወቱበታል፡ አለፍ ብሎ ባለዉ ሜዳ ላይ ሰፊ ምንጣፍ ተነጥፎላቸዉ ጨቅላዎች ይንከባለላሉ ከእነሱ በወራት
ዕድሜ ከፍ ያሉት ደግሞ ራሳቸዉን ችለዉ ለመቆም ይዉተረተራሉ
የሕጻናቱ ተንከባካቢዎች እንደየምድባቸዉ የሚቆሙት ቆመዉ፣ ያቀፉት ደግሞ ተቀምጠዉ በየትዕይንቱ ይደሰታሉ።

መሥራትስ እንደ እነሱ ነዉ› አልሁኝ፣ በቅናት።

ሆኖም ሥጋቴ ሊያልፍልኝ አልቻለም: እንዲሁ ከመኪናዬ ወረድሁና ቱናትን ከአልጋዋ አንስቼ አቀፍኋትና፣ የግቢዉ አማካይ የሚሆን ሥፍራ ላይ ቆምሁ፡፡ በየትኛዉ ቢሮ የትኛዉን ሰዉ ማናገር እንዳለብኝ በዓይኖቼ
ወዲያ ወዲህ ስል አንዲት በልተት ያሉ ሴትዮ ቀረቡኝ፡

“እንኳን በደህና መጣችሁ” አሉ፣ ልብ በሚሞላ ፈገግታ እኔንም
ቱናትንም አይተዉ ይበልጥ እየቀረቡን፡፡

“እንኳን ደህና አገኘኋችሁ” አልሁ፣ አንገቴን ወደ ጉልበታቸዉ
በመስበር ለትሕትናቸዉ ጭምር አክብሮት እየሰጠሁት፡
እዉነትም እነ እመዋ ነገሮችን ጨራርሰዉልኝ ኖሮ፣ ማነሽ የሚለኝ ሰዉ ቀርቶ ቅጽ እንድሞላ እንኳን የጠየቀኝ ሰዉ የለም፡ ቀድሜ ያገኘኋቸዉ ሴትዮ ለቱናት የተመደበላትን ማደሪያ ክፍል፣ ክፍሉን የሚጋሯትን
ሕጻናት፣ ያለማስታጎል እንዲከታተላት የተመደበላትን ነርስ፣ የምግቦቿን ዝርዝር መርሐ ግብር፣ልብሶቿን እና ሌሎች ነገሮችን በዚያዉ በማይለዋወጥ ትሕትናቸዉ ከገለጹልኝ በኋላ፣ ሥጋት ወይም አስታያየት
ይኖረኝ እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡

“እንግዲያዉ መዋእለ ሕጻናት ብቻ አይደለማ ይኼማ?” አልኋቸዉ:
“ትክክል። ያዉ እንደምታዉቂዉ” አሉ፣ ደጋገሜ አንቺ እንዲሉኝ
የለመንኋቸዉን እንደ ምንም ተስማምተዉልኝ፡ “ያዉ እንደምታዉቂዉ አብዛኛዉ የማኅበራች አገልጋዮች ሌት ከቀ ሥራ ላይ ናቸዉ። በዚህም
የተነሳ ለልጆቻቸዉ በቂ እክብካቤ ለማድረግ ይቸገራሉ። ይኼ የሕጻናት መዋያ ከተከፈተ ወዲህ ግን እንደየአገልግሎት ጸባያቸዉ፣ ሙሉ ኃላፊነቱን ለእኛ ለመተዉ የተፈቀደላቸዉ አገልጋዮች አሉ: ሥራቸዉ ፋታ የሚሰጣቸዉ ያሉ እንደሆነ ግን ኃላፊነት የም ወስድላቸዉ ወይ ቀኑን ወይ ማታዉን ብቻ ይሆናል ማለት ነዉ” አሉኝ፣ ቱናትን ባዘጋጁላት
አልጋዋ ላይ እያሳረፏት፡
“ታዲያ” አልሁኝ፣ ከሁሉም ቅድሚያ ለቱናት የሚበላ እንዲሰጡልኝ ለመጠየቅ እንደገና እየዳዳሁ የአንገት ሰላምታ በርቀት ሰጥተዉኝ ከነበሩት ሴቶች አንደኛዋ፣ የልቤን አዉቃልኝ ይሁን የቱናትን ቡዝዝ ማለት አይታ እንደሆነ እንጃ፣ ትኩስ የሥጋ ፍትፍት አመጣችላት። ደቀቅ
ያለዉን የሥጋ አመታሮ በቀይ እንጀራ ፈትፍታ አምጥታ ስታጎርሳት እኔ ምራቄን ብዉጥም፣ቱናት ግን እምቢ አለች: ለማጫወት ብትሞክራት ሁሉ ለማልቀስ ተነፋነፈች።

“ግድ የለም” አሉ፣ ባልቴቷ። “ግድየለም፤ እንግድነት ተሰምቷት ነዉ። ትንሽ ትፋሽ ትዉሰድና እኔ አጫዉቼ አበላታለሁ”

“አይ አልሁኝ፣ ሥጋቴን መደበቅ እያቃተኝ፡

“ግድ የለሽም”

“እንዲያዉ ዛሬ እምብዛም ሳትበላ ነዉ የዋለችዉ”

“ሐሳብ አይግባሽ፤ አጫዉቼ አበላታለሁ”

“እንግዲህ ምን እላለሁ፣ እግዚአብሔር ይስጥልኝ ከማለት በቀር አልኋቸዉ ኹለቱንም፣ ስለ በጎ አድራጎታቸዉ፡
"ተዪ ተዪ: እኛ ነን ማመስገን ያለብን: እንኳንም እግዚአብሔር ልዩ አድርጎ የሰጠሽ ልጅሽ እንድናገለግላት ዕድሉን ሰጠሸን”

“አይ… እንዲያዉ ወድጄ እንኳን አይደለም ያመጣኋት: ልጄ ከብዳኝ ወይ ደግሞ ከእሷ የሚበልጥብኝ ሥራ ኖሮብኝም አይደለም”

“ይገባኛል”

“የሆነዉ ሆኖ እንግዲህ ከኹለት ወይ ከሦስት ሰዓት በላይ
አላስቸግራችሁም”

“ማስቸገር? የለም የለም: ለእሷ ከምናደርግላት ይልቅ፣ እሷ ለእኛ
የምታደርግልን ይበልጥብናል። ከባሪዎቹ እኛዉ ነን''

“ይሁን” ብዬ፣ ወጣሁ።

ለቅሶዋን ከኋላዬ እየሰማሁ፣ እንደ ምንም ጨክኜ ወጣሁ ወደ ጦር ሜዳ እየኼድሁ እንደሆነ ነዉ የሚሰማኝ፡ ከወንድሞቼ እና
ከእህቶቼ፣ በተለይም ከጃሪም ጋር ፊት ለፊት እስከምገጥም ቸኩያለሁ።እሱም ቢሆን ሌላ ምንም ምርጫ አልተዉልኝም፡፡

‹ምን ይሉት ፍርጃ ነዉ ግን? ኧረ እንደ ዋዛ የት ነዉ የደረስነዉ
በማርያም? እያልሁ እንዲችዉ እንደ ተብሰለሰልሁ፣ በአዲስ አበባ
ዩኒቨርስቲ ዋናዉ ግቢ በኩል ባለዉ ቁልቁለት ወረድሁ።

ለነገሩ ለምን በእነሱ ብቻ እፈርዳለሁ? ጥፋቱ የራሴም ጭምር አይደል?እነሱ ሆኑብኝና ተለማመጥኋቸዉ፡ የእኔ በሕይወት መኖር በእነሱ ፈቃድ እስኪመስል ድረስ ግፊያቸዉን ሁሉ ቻልሁላቸዉ᎓ የጃሪም ወንድምነት
ቢቀርብኝ እሞት ይመስል፣ ያለ ጥፋቴ ጭምር ማረኝ ማረኝ አልሁት።

ቆይ፤ እዉነት ግን አልሞትም? ያለ ጃሪም ወንድምነት፣ ያለ እህቶቼ
እህትነት ምንድን ነኝ እኔ?

ወደ ማኅበራችን ሕንጻ የሚያደርሰኝን መንገድ እንደ ተያያዝሁት፣ የዛፍ እና የንብ ሽርክና በልቡናዬ ክችች አለብኝ፡፡
ሠራተኛዋ ንብ ለማኅበረ ንቧ የሚሆነዉን ምግብ ለመቅሰም አበባ ወዳለው ዛፍ ታርፋለች:: ከአበባዉ ላይ የምታገኘዉን ዕጩ ማር ከቀሰመች በኋላ ተጨማሪ ፍለጋ ወደ ሌላ ባለ አበባ ዛፍ ትሄዳለች: ነገር ግን ከዛፋ
በምትነሳበት ጊዜ፣ የአበባዉ ወንዴ ዘር በጸጉራም አካሏ ላይ ተሳፍሮ ይከተላታል። ወደ ቀጣዩ የአበባ ዛፍ በምታርፍ ጊዜም፣ ያ ከዚያኛዉ ዛፍ ያመጣችዉ ወንዴ ዘር፣ እዚህኛዉ ዘንድ ካለዉ የአበባዉ ሴቴ ዘር ጋር ይገናኛል፡ በዚህም ምክንያት፣ ንቧ ምግቧን ፍለጋ ከዛፍ ዛፍ ባረፈች
ቁጥር፣ የአበባ ዛፎች እንዲራቡ ታደርጋለች ማለት ነዉ ንብ ያለ አበባ ማለት እንግዲህ ያለ ምግብ፤ አበባም ያለ ንብ ማለት ደግሞ ያለ መራባት ስለሆነ ተከላክለዉ አያዉቁም:: እርስ በእርስ ቢከላከሉ፣ አንዳቸዉም መኖር እንደማይችሉ ኹለቱም ጠንቅቀዉ ያዉቁታል።

ስለዚህ ንብ እና አበባ አይለማመኑም:: አለመለማመን ብቻም ሳይሆን፣ ነፍሳቸዉ እስኪገባ ድረስ ይዋደዳሉ
እንደ እዉነቱ፣ እኔና ጃሪምም ሆንን ከሌሎች እህትና ወንድሞቻችንም
ጋር ግን፣ አበባና ንብ ብቻ አይደለንም፡፡ ወይ ንብ እና ንብ፣ ወይ አበባና አበባ ነን፡ ያዉም ወይ የአንድ እናት ንብ እናት አበቦች ነን፡፡ እንዲያዉ እሱም አጉል ሆኖ ቢፈርስ ግን፣ ቢያንስ ንቦች፣ ወይ ደግሞ የአንድ እንደ አበባና ንብ እንኳን መሆን እንዴት ያቅተናል?

የእኔም እጅ አለበት፡፡

አዎ፣ አለበት!

እኔ ያለ እነሱ መኖር እንደማልችል ብቻ እንጂ፣ እነሱም ያለ እኔ መኖር
እንደማይችሉ ነግሪያቸዉ አላዉቅም አበባ የንብን ጥቅም ባያዉቅ ኖሮ አያከብረዉም: የማያከብረዉን ደግሞ የሚወድ የለም፡ መናቅን እንጂ፣በእጄ ነሽ፣ ብለቅሽ ያልቅልሻል፣ ተሸከምሁሽ፣ በደልሽኝ ማለትን እንጂ
እንደ'ኔ ማለትን ያስተዋል፡፡ እህትነቴ እንዲተናነቃቸዉ፣ እነ ጃሪም እዚህ እንዲደርሱ የእኔም ሚና አለበት፡፡

“የት ናት?” አልሁት ባልቻን፣ ከራሴ ጋር እንዲህ እየተዋቀስሁ ወደ
ሲራክ ፯ ማዕከል ደርሼ ቢሮዉ ዉስጥ ያገኘሁት ከኹለት ሰዎች ጋር እየተነጋገረ ቢሆንም፣ ምንም ሳይመስለኝ፡
👍31👏2
“ከእንግዶች ጋር እኮ ነኝ” አለኝ፣ በቁጣ ጥርሱን ነክሶብኝ፡፡
ይኼን እንዳወቅሁ ድንግጥ ብዬ መመለስ ቢኖርብኝም፣ ምንም ግድ ሳይሰጠኝ፣ እንዲያዉም እኔን አስቀድሞ እንዲያናግረኝ አፍጥጬ ቀረሁበት፡ እሱም፣ ምርር ማለቴን ሲያይ እንግዶቹን ለአንድ አፍታ ይቅርታ ጠይቆ፣ እኔ ወደ ቆምሁበት ወደ በሩ አቅራቢያ መጣልኝ፡

“እመዋስ?”

“እቤቷ”

“በማርያም! እንዳትቀልድብኝ። ልጄን ጥዬ ነዉ የመጣሁት። እመዋ የት ናት?”

“እየነገርሁሽ?”

“እቤቷ?” አልሁት፣ ለማመን እየተቸገርሁ፡ አላመንሁትም ግን ደግሞ ከማመን ዉጪ ምንም ምርጫ የለኝም እየተጠራጠርሁ ቢሆንም በቆመበት ትቼዉ ወደ ቤት ለመሄድ፣ ስጠቀምበት የቆየሁትን የራሱን የባልቻን መኪና ካቆምሁበት አስነስቼ
አሽከረከርሁ፡ እዉነት ባልቻ እንዳለዉ እመዋ በዚህ ጊዜ በቤቷ ከሆነች፣ ቅድም ጃሪም በሯን ዘግቶ ፈጥሮት የነበረዉ አምባጓሮ ላይ አዲስ ነገር ተፈጥሯል ማለት ነዉ።

እስከምደርስ ቸኮልሁ።

እንዳይደርሱት የለም ፍርሃት እንደ ሞላብኝ፣ እልህ እንደ ቀላቀለብኝ ወደ ሰፈር ደረስሁ ቅድም እየተገፋፉ ግርግሩን ታድመዉ ያየኋቸዉን ሰዎች አሁን አላገኘኋቸዉም: ይኼ በራሱ በጎ ነገር ቢሆንም፣ ለእኔ ግን
ጭንቀቴን ነዉ የጨመረብኝ፡፡ በዚያ ላይ የግቢዉ አጥር ወደ ዉጪ ዘመም ያለ መሰለኝ፡፡
ምንድነዉ የተፈጠረዉ?
መኪናዬን ወደ በሩ ጠጋ አድርጌ አቆምኋትና በድቅድቅ ጨለማ ወንዝ እንደሚሻገር ሰዉ እየተንቀጠቀጥሁ በሩን ቀስ አድርጌ ገፋሁት᎓ በዉስጥ
በኩል ስላልተሸነጎረ፣ ስገፋዉ በቀላሉ ተገፍቶ ተከፈተልኝ፡ ወደ ግቢዉ
ዉስጥ ዘልቄ ዋናዉን የእመዋ ቤት ስመለከት እረጭ ብሏል፡ ከራሴ
የእርምጃ ድምፅ እና የልብ ምት በቀር ምንም አይሰማኝም:

ወደ ሳሎን የሚያስገባዉን በር ቀስ አድርጌ ስከረፍደዉ፣ እመዋን በሳሎኑ
በኩል ባለዉ የጃሪም ክፍል መግቢያ አጠገብ ተቀምጣ አገኘኋት᎓
ምንጊዜም ከትከሻዋ ወርዶ አይቼዉ የማላዉቀዉ ነጠላዋ፣ እንደ መቀደድ
ብሎ ከወገቧ አልፎ ወርዷል።

እጥፍ ብላ ሳያት፣ ሁኔታዋ ነፍሴን ነዉ ያሳጣኝ፡፡ ብቻ እንዲሁ “እመዋ”
ብዬ ተብረክርኬ እግሯ ሥር ወደቅሁ ምኗን ልዳብሳት? እንባዋን
እንዳላብስላት ዓይኖቿ ድርቅ እንዳሉ ናቸዉ፡፡ ጠብታ እንኳን
አልፈሰሰባቸዉም፡ ወደ ዉስጧ ነዉ ያለቀሰችዉ: ጃሪም እናትነቷን
ከተጠራጠራት ጀምሮ ሐሜቱን እና ወሬዉን ሁሉ በሆዷ ይዛዉ እንደ
ኖረች፣ አሁንም ወደ ሆዷ ነዉ የምታለቅሰዉ፡

“እመዋ” አልኋት፣ አቤት ብትለኝ የምላት ምንም ሳይኖረኝ፡፡

ዝም አለችኝ፡፡ ዘወር ስል በሳሎኑ የግራ ጠርዝ በኩል አንደኛዋ እህቴ
እና ሌሎች ኹለት ወንድሞቼ ፈንጠር ፈንጠር ብለዉ ተቀምጠዋል።
ምንም እንዳልተፈጠረ ቆጥረዉ ሞባይል ይነካካሉ፣ እርስበእርስ ይተያያሉ፣ አልፎ አልፎ ደግሞ ወደ እኛ ሰረቅ እያደረጉ አይተዉ ፈገግ ይላሉ፡ ኧረ ምን ያለዉን ልብ ነዉ ያገኙት? እሺ፣ የቀሩት እህትና
ወንድሞቼስ የት ይሆኑ?

“እምዬ”

ዘወር እንኳን ሳትልልኝ ዝም ብላ መሬት መሬቱን እያየች ቆየችብኝ፡
እኔም የሆነዉን እንድትነግረኝ ዓይን ዓይኗን እያየሁ በመጠባበቅ ላይ
ሳለሁ፣ በሳሎኑ በኩል ያለዉ የጃሪም ክፍል በር ሲጢጥ ሲል ሰማሁት።
ዓይኔን ለበስ አድርጌ ቀና አልሁ
ዓይኔን እንደ ነገሩ ብገልጠዉም ጭልምልም ብሎብኛል፡ ብቻ እንደ
ተቀመጥሁ፣ ይኼንኑ ቡዝዝ ያለ ዓይኔን በተከፈተዉ በር ትክክል አየ ወዲያዉ ነዉ ዓይኖቼ ቦግ ያሉት፡ በጃሪም ጉልበቶች መካከል ዓይኔ ስወረዉረዉ፣ በሩን በከፈተዉ ሰዉ እግሮች መሀል አልፎ አንድ ልጅ አየ ወዲያው ነው አይኖቼ ቦግ ያሉት። በጃሪም ጉልበቶች መካከል ዐይኔ
ዉስጥ የገባዉ ሰዉ፣ እንደ ራሴ የማምነዉ ቢራራ ነዉ፡ የሲራክ ፯ቱ
ቢራራ! ዓይኔን ልመነዉ? ስለ ሲራክ ፯ መረጃ እያሾለከ ለጃሪም ያቀብለዉ
የነበረዉ ሰዉ ቢራራ ነዉ?

ሰአሊ ለነ ማርያም!

ሽንፈትም፣ መከዳትም፣ ወንድምን ያህል ሰዉ ጨርሶ ማጣትም፣ መተንፈሻ ሳይቀር መቀማትም በየነበልባሉ ለመጠጠኝ፡ በላኝ፡ በጣም በላኝ፡፡ እንዲህ ነዉ፣ እዚህ ጋ ነዉ የማልለዉን አካሌን እከኪዉ እከኪዉ የሚል ስሜት ዕረፍት ነሳኝ፡ በኃይል መከፋት፣ አሟጦ ተስፋ ማጣት፣
የእናትን የተሰበረ አንገት ማየት እና ከእናት ልጅ ጋር አንገት ለአንገት ለመተናነቅ የሚያጣድፍ ስሜትን መግለጽ እንደሚከብድ ያለ መከራ
መኖሩን አላዉቅም፡

እንደ ጃሪም ሁኔታ፣ ከእንግዲህ እሱን ከተለማመጥሁም የምለማመጠዉ
ወንድምነቱን ብቻ ላይሆን ነዉ ማለት ነዉ፡ የገዛ ትንፋሼን ጭምር ነዉ፡
አየሩን ሁሉ! እመዋን አየኋት ፤ እንደዚያዉ ናት፡ በስሕተት እንኳን ዓይኗን
አታርገበግበዉም: በሳሎን የተቀመጡትን እህትና ወንድሞቼንም አየቸዉ፣ እነሱም እንደ ነበሩት ናቸዉ፡፡

“እመዋ?” አልኋት፣ ሳግ ይሁን እልህ ጉሮሮዬ ላይ እንደ ያዘኝ፡

ዝም፡፡

“እመዋ፣ አናግሪኝ''

ዝም:

“አናግሪኝ!” አልኋት፣ በገዛ እናቴ ላይ እጄን ለማንሳት ጭምር እየቃጣኝ፡ “ንገሪኝ!” አልኋት እንደገና፣ ጮኼ፡ የምትሰማኝ መሆኗን ሁሉ እንጃ፣ አሁንም ዝም እንዳለችብኝ ቀረች:

ስቅስቅ ብዬ አለቀስሁ፡ እንባዬ እንዴት እንደሚያቃጥል! እየለመጠጠኝ
በአካላቴ ፈሰሰ፡ ያም ሆኖ ግን ሊወጣልኝ አልቻለም፡

“እመዋ በማር ያም!” አልኋት፣ አልቅሼ አልቅሼ ባይበርድልኝም::
“ንገሪኛ! ጃሪም ነዉ ልክ ወይስ እኔ? ምንም እዉነት የለኝም እኔ? በል
በል ብለዉ እዚህ ያደረሱት መካሪዎቹ ናቸዉ እዉነት ያላቸዉ? እዉነት
ወንድም አለኝ? የለኝም? እህትስ? በእዉነትም ከእኛ መሀል አንቺ እናት
ያልሆንሽው ልጅ አለሽ?

ዝም።

“ጃሪም የሆነ ጊዜ ጥሩ ጥያቄ ጠይቆኝ ነበር፤ የእኔና የእሱ ልደት በእኩል ቀን ይከበርልን የነበረዉ ለምን እንደሆነ: (መንታ ነን ወይ ሲለኝ አይደለንም አልሁት። እንግዲያዉ ታላቅና ታናሽ ሆነን በተለያየ ዓመት ግን በአንድ ዓይነት ቀን ተወልደ ነወይ> ሲለኝም አይደለም አልሁት:አሁን ሳስበዉ ግን የማላዉቀዉን ነበር የመለስሁለት ያኔ። ንገሪኝ፣
ለምንድነዉ ልደታችን በአንድ ቀ ይከበርል የነበረዉ? ቢያንስ ይቺን ብቻ ንገሪኝ''

ክስል ያለ ጥርሷን ለአንድ አፍታ አሳየችኝ፡፡

ቁርጤን ልትነግረኝ ነዉ ብዬ ለማዳመጥ ትንፋሼን ስዉጥ፣ ቀስ ብላ
እግሮቿን ዘረጋች: ከዚያ ግራና ቀኝ በእጆቿ ተመርኩዛ ከመቀመጫዋ
ሸርተት ብላ ተንጋለለች ቀጥላ፣ ወደ ቀኝ ጎኗ ገልበጥ አለችና፣ በጃሪም
ክፍል ትይዩ ጋደም አለች::

“እመዋ!”

ወይ ፍንክች! ዝም፡

መለስ እያደረጉ ፈንጠር ፈንጠር ብለዉ ምኑም እንደማይመለከታቸዉ
“እሺ እናንተስ?” አልኋቸዉ፣ ልክ እንደ ሌላ ሰዉ ትኩረታቸዉን ወሰድ
መስለዉ ወደሚመለከቱን ወንድም እና እህቶቼ ቀረብ ብዬ፡ “በቃ?
እንዲህ ይሁን እንኳን አትሉም?''

ዝም።

“በቃ?”

ጭጭ፡

እነሱ ከጃሪም የሚለዩት ምናልባትም የሚወላዉል እንጥፍጣፊ ልብ
ያላቸዉ እንደሆነ ብቻ ነዉ፡ ምናልባት ነዉ ያዉም ምናልባት ወደ ዉስጤ ብቻ ተነፈስሁ ከዚያ ዓይኔን ጨፈንሁና ወደ ልቤ አዳራሽ ዘለቅሁ፡ ጨከን ያለ ዉሳኔ ለመወሰን ከራሴ ጋር ተሰበሰብሁ፡ በልቤ
አዳራሽ ዉስጥ ራሴን ከራሴ ጋር ስበሰባ አስቀመጥሁበት፡፡
👍30
‹ብቻ አትቀደሚ! አንዴ አይቅደሙሽ እንጂ፣
ከተቀደምሽ አንቺን ለመድፈቅ የማይበረታ የለም ሳር
ቅጠሉ ይነሳብሻል፡ ምናምንቴዉ ሁሉ ጎሮሮሽ ላይ ይቆማል፡ እንኳንስ የኔ ነዉ የምትዪዉ ይቅርና፣
ራሳቸዉ ያንቺ ነዉ ያሉሽን እንኳን ይወስዱብሻል።
ጭራሽ ባዶሽን ማስቀረታቸዉም አልበቃ ብሏቸዉ፣
ወሰደችብን ብለዉ ያዋክቡሻል፡ መልሰዉ ደግሞ ይዘባበቱብሻል። ይሸልሉብሻል ግድየለም እነሱን ራሳቸዉን እንኳን አጥቻቸዉ የለ ብለሽ እንኳን
ትንፋሽ የሚባል እንዳትጽናኝ፣ የመጽናኛ
አያስቀሩልሽም አንቺን በፍህም ያዉም በሹል ሚስማር ላይ አቁመዉሽ፣ ያሽኩብሻል። ልንገርሽ?
በፍጹም እንዳትቀደሚ፡ ወደ አንቺ የተዘረጋዉ እጅ ለፍቅርም ይሁን ለጸብ፣ እንዳመጣጡ አፈፍ አድርጊዉ
እንጂ አትቀደሚ ለምንም ነገር፣ ማንም አይቅደምሽ! የፈለገ ብትሸሸጊዉ ዉጊያዉ እንደሆነ አይቀርልሽም እንግዲህ! ይልቁንስ ምረጪ። መዋጋት
ያለብሽ ራስሽን ለማዳን ነዉ ወይስ ራሱን የሚዋጋሽን ቤተሰብ ለማትረፍ? ወጣ ወረደ፣ እንዳትቀደሚ!

አመጽሁ: በራሴ ላይ ራሴ ተነሳሁ፡ ይኼን የራሴን ከራሴ ጋር ያደረግሁትን ስብሰባ ጨርሼዉ ተነሳሁና፣ ጃሪም ወደ ክፍሌ ገባሁ ከዚያ፣ ሲራክ ፯ን በዋና አባልነት የተቀላቀልሁ ጊዜ ለማዕከሉ ተልእኮ
ብቻ እንድጠቀምበት የተሰጠኝን ሽጉጥ ከደበቅሁበት አወጣሁት ሽጉጡን ይዤ በጎኗ ወደተኛችዋ እመዋ ተመለስሁና፣ ዘርፈፍ ብሎ የተረፈዉ የቀሚሷ ጥለት ላይ ተቀመጥሁ እያንጎራጎርሁ፡ ያዉም፣ አንድ ጊዜ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የሩስያዉን የሐኪም ልዑክ እራት የጋበዘ ዕለት
አንጎራጉሬዉ፣ ትንቢቱ ገብቶት ይሁን ሳይገባዉ እንጃ፣ ብቻ አምባሳደሩ ሳይቀር አጀብ አጀብ ካለልኝ እንጉርጉሮ መካከል፡፡ አሁን እንደ ልማዴ ክራር ሳይሆን ሽጉጥ ቢሆንም በእጄ የጨበጥሁት፣ የዚያን ጊዜዉን ስሜት ግን ጨርሼ አላጣሁትም፡

የማታ መንገድ የሚያልቅ መስሎት
የፀሐይን ዓይን እፍ እፍ አለበት።
እፍ ፍታዉ ላይ ባልኖርበትም፣
የመጣዉ ይምጣ
ዓይኔን አልከድንም፣
አ ል ቀ ደ ም ም!


አልቋል


ቀጣዩን ክፍል በቅርብ ያደርስንላን ብለን ተስፋ እናደርጋለን
👍49🥰5😁1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አንድ


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


ደሃና ሁን አባዬ

የእኛ ህይወት የተጀመረው ደስ በሚል አይነት ስለነበረ፣ በጣም ትንሽ ልጅ ሳለሁ ጀምሮ ህይወት ሁሉ እንደ አንድ ደስ የሚል ረጅም ብሩህ ቀን እንደሆነ አድርጌ አምን ነበር። የልጅነታችንን ጊዜ በተመለከተ በጣም ጥሩ
ጊዜ ነበር ከማለት በስተቀር ልለው የምችለው እምብዛም የሆነ ነገር የለም በኑሯችን ሀብታምም፣ ደሀም አልነበርንም፧ እኛ ያሉንን ነገሮች ሌሎች ካሏቸው ጋር ሳወዳድር፣ አስፈልጎን ያጣነውንም ሆነ በቅንጦት ያገኘነውን ነገር አላስታውስም:: በዚያ ላይ በመካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎች በሚኖሩበት በእኛ አካባቢ ማንም ሰው ብዙም ሆነ ትንሽ አልነበረውም በሌላ አነጋገር፣ ተራና የተለየ ነገር ያልነበረን ልጆች ነበርን።

አባታችን በፔንሲልቫንያ፣ ግላድስተን ውስጥ በሚገኝ 12,602 ሰዎች ባሉበት
ግዙፍ የኮምፒውተር ማምረቻ ውስጥ የህዝብ ግንኙነት ሰራተኛ ሆኖ ይሰራ ነበር የአባታችን አለቃ አብዛኛውን ጊዜ ከእኛ ጋር እራት ይበላ ስለነበርና አባታችንን “ክሪስ በዚህ ማራኪ ባህርይህና በመልከ መልካም ፊትህ ማን አስተዋይ ሰው ሊቋቋምህ ይችላል?” እያለ ያደንቀው ስለነበር በአባታችን
ደስተኞች ነበርን።

በዚህ አባባሉ እኔም ከልቤ እስማማለሁ አባታችን እንከን የለሽ ነው: ዘንካታ ቁመና ያለው ሲሆን ከቁመቱ ጋርም ተመጣጣኝ ውፍረት ታድሏል። ፀጉሩ
ጥቅጥቅ ያለና ወርቃማ ነው፡ ሰማያዊ አይኖቹ ለመኖርና ለመደሰት ያለውን ትልቅ ፍቅር የሚያንፀባርቁ ናቸው። አፍንጫው ቀጥ ያለና ረጅምም አጭርም
ያልሆነ… ተመጥኖ የተሰጠው ነው። ቴኒስና ጎልፍ መጫወትና መዋኘት ይወዳል፡ ሁልጊዜ እኛን ከእናታችን ጋር ትቶን ለስራ ጉዳይ ከካሊፎርኒያ ወደ ፍሎሪዳ ወይም ወደ ሌላ ውጪ ሀገር ይሄድና በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ይመለሳል ዘወትር አርብ ከሰዓት በኋላ ወደ ቤት መጥቶ በፊት ለፊቱ በር በመግባት ደስ የሚል ትልቅ ፈገግታውን ፈገግ ሲልልን ስናይ፣ ዝናብ ቢጥልም ሆነ በረዶ ቢዘንብ ለእኛ ግን ፀሀይ ይሆንልን ነበር ሻንጣውን ወለሉ ላይ ጣል አድርጎ ሰላምታ ይጀምራል። “የሚወደኝ መጥቶ ይሳመኝ::
ይለናል።

ልክ ይህንን ሲናገር እኔና ወንድሜ ከተደበቅንበት ወንበር ወይም ሶፋ ስር እየሮጥን ወጥተን እቅፉ ውስጥ እንወድቃለን፡ እሱም አጥብቆ ያቅፈንና ጉንጮቻችንን ጥብቅ አድርጎ በመሳም ያሞቀናል። አርብ ሁልጊዜ አባታችንን መልሶ ወደ እኛ ስለሚያመጣልን ከሁሉም ቀናት የበለጠ ምርጥ ቀናችን
ነበር፡

አባታችን በመጣ ቁጥር በኪሱ ውስጥ ይዞልን የሚመጣውን ትንንሽ ስጦታዎች ከሰጠን በኋላ ሻንጣው ውስጥ ያሉትን ትልልቆቹን ስጦታዎች ለመቀበል
ደግሞ እኛ ሰላምታችንን እስክንጨርስ ድረስ በትዕግስት የምትጠብቀውን እናታችንን ሰላም ብሎ እስኪጨርስ እንጠብቃለን
እኔና ክሪስቶፈር ኪሱ ውስጥ የያዛቸውን ትንንሽ ስጦታዎች ካገኘን በኋላ፣እናታችን የአባታችንን አይኖች እንዲያበሩ የሚያደርገውን የእንኳን ደህና
መጣህ ፈገግታዋን ተላብሳ ወደ እሱ በቀስታ ስትራመድ እንመለከታታለን፡

አባታችንም እጆቹን ዘርግቶ ያቅፋትና ቢያንስ ለዓመት ያህል ያላያት በሚመስል ሁኔታ ፍዝዝ ብሎ ቁልቁል በናፍቆት ይመለከታታል።

እናታችን ዘወትር አርብ ሽቶ ባለው የመታጠቢያ ዘይት በተቀላቀለበት ውሀ ገላዋን ስትታጠብ፣ ጸጉሯን ስትሰራና ጥፍሮቿን ስታሳምር ነው ግማሹን ቀን የምታሳልፈው። እኔም እስክትጨርስ ድረስ በመልበሻ ክፍሏ ውስጥ ቁጭ ብዬ በጉጉት እጠብቃለሁ። ራሷን ከቆንጆ ሴት እጅግ ውብና እውን ወደማትመስል ሴት ስትቀይር የምታደርገውን እያንዳንዷን ነገር በጉጉት አስተውላለሁ።

የሚገርመኝ ነገር አባታችን በተፈጥሮ አስደናቂ ውበት እንዳላትና ፊቷን ምንም እንደማትቀባባ ማሰቡ ነው።

እኛ ቤት ከመጠን በላይ የሚደመጥ ቃል ቢኖር ፍቅር የሚለው ቃል ነው።
“እኔ በጣም አፈቅርሻለሁ አንቺስ ታፈቅሪኛለሽ? ናፍቄሽ ነበር? ቤት
በመምጣቴ ደስ ብሎሻል? እዚህ የሌለሁ ጊዜ ስለእኔ ታስቢ ነበር? በየምሽቱ እየተገላበጥሽ አጠገብሽ ሆኜ እንዳቅፍሽ ተመኝተሸ ነበር? እንደዚያ ካልሆነ
ካሪን… የእውነት ብሞት ይሻለኛል።” ይላታል። እናታችን ለእንደዚህ አይነት ጥያቄዎች እንዴት በአይኖቿ በለስላሳ
ሹክሹክታዋና በመሳም መመለስ እንዳለባት በትክክል ታውቅ ነበር።

በአንድ ክረምት ላይ እኔና ክሪስቶፈር ከትምህርት ቤት ወደ ቤት ተመልሰን እየተቻኮልን በፊት ለፊቱ በር ገባን፡ እናታችን ሳሎን ውስጥ ከምድጃው ፊት ለፊት ተቀምጣ ለአሻንጉሊት የሚሆን ነጭ ሹራብ እየሰፋች ነበር።
ከአሻንጉሊቶቼ ለአንዷ የሚሆን የገና ስጦታ እንደሆነ አስቤ ደስ አለኝ በተቀመጠችበት ሆና “ወደዚህ ከመግባታችሁ በፊት ጫማችሁን በሩ ጋ አውልቁና አስቀምጡት!” አለችን፡

ቦት ጫማዎቻችንና ወፍራም ኮቶቻችንን እንዲሁም ኮፍያችንን አስቀምጠን በካልሲ ብቻ በመሆን ነጭ ምንጣፍ ወደተነጠፈበት ክፍል አመራን አብዛኛውን ጊዜ ነጭ ምንጣፍ በተነጠፈበት ክፍል በሚያማምሩት ሶፋዎችና
ወንበሮች ላይ እንደልባችን ለመሆን ስለማይፈቀድልን የተዋበው የእናታችን ክፍል ለእኛ ምርጫችን አይደለም የአባታችን ክፍል ግን ጠቆር ያለ ቀለም
ያለው በመሆኑና ምንም ነገር እናበላሻለን ብለን ስለማንሳቀቅ ጠንካራው ሶፋ ላይ እንደልባችን መላፋትና መታገል ስለምንችል ክፍሉን በጣም እንወደው
ነበር።

እግሯ ስር ተቀምጬ እንዲሞቀኝ እግሮቼን ወደ እሳቱ እየዘረጋሁ “እማዬ… ሳይክሎቻችንን እየነዳን ወደ ቤት ስንመጣ ዛፎቹ ሁሉ በበረዶ ተሸፍነው ሲታዩ እንዴት ደስ እንደሚሉ ብታይ። ደሞ እማዬ ውጪውን ብታይው ተረት ተረት ላይ ያለውን ቦታ ነው የሚመስለው: ግን ብርዱ አይቻልም ያም ሆኖ ደስ ይላል እኔ በበኩሌ መቼም ቢሆን በረዶ የማይጥልበት ደቡብ አካባቢ መኖር አልፈልግም” አልኳት።

ክሪስቶፈር ሁለት ዓመት ከአምስት ወር ስለሚበልጠኝና ሁልጊዜ ከእኔ የተሻለ ብልህ መሆኑን ማሳየት ስለሚፈልግ ስለ አየር ሁኔታውና በረዶው ስለፈጠረው
ውበት ምንም አልተናገረም ልክ እንደኔ የቀዘቀዘውን እግሩን በእሳት እያሞቀ በጭንቀት ተኮሳትሮ የእናታችንን ፊት አፍጥጦ እየተመለከተ ነበር እንደዚያ አይነት ጭንቀት እንዲሰማው ያደረገው ምን አይቶ እንደሆነ ለማወቅ ፈልጌ እኔም ቀና ብዬ አየኋት᎓

“እማዬ ደህና ነሽ?” ሲል ጠየቃት።

ስስና ደስ የሚል ፈገግታ እያሳየችው “አዎ በጣም ደህና ነኝ” ብላ መለሰችለት።

“የደከመሽ ትመስይኛለሽ” አላት።

የምትሰራውን ትንሽ ሹራብ ወደጎን አስቀመጠችና የክሪስቶፈርን ፅጌረዳ
የሚመስሉ ቀዝቃዛ ጉንጮች ለመዳበስ ወደፊት ዘንበል ብላ “ዛሬ ሀኪም ቤት
ሄጄ ነበር” አለች:

“አሞሻል እንዴ እማዬ?” ሲል በድንጋጤ ጮኸ፡

በስሱ ሳቅ አለችና ጥቅጥቅ ያለውን ወርቃማ ጸጉሩን ቀጫጭንና ረጃጅም
በሆኑ ጣቶቿ እያሻሸች “ክሪስቶፈር ዶላንጋንገር፣ የሆነ ነገር ጠርጥረህ
እያሰብክ ነው አይደል? መቼም ምን ሆኜ እንደሆነ ሳትገምት አትቀርም አለችው ከዚያ እጁን ያዘችና የእኔንም አንዱን እጄን ጎትታ ሁለቱንም ሆዷ ላይ አስቀመጠቻቸው

ሚስጥራዊና ደስ የሚል አስተያየት ፊቷ ላይ እየተነበበ “የሆነ ነገር
አልተሰማችሁም?” ስትል ጠየቀችን፡
ክሪስቶፈር በፍጥነት እጁን መነጨቃት እኔ ግን ምን እንደሆነ በመጠበቅ
እጄን እዚያው ላይ ተውኩት።

“ምን ተሰማሽ ካቲ?”
👍62🥰21
በመዳፌ ስር ሆዷ ውስጥ በትንሹ የሚሰማ እንቅስቃሴ አለ እጅግ ተገርሜ
ጭንቅላቴን ቀና አድርጌ ፊቷን አየሁት ምን ያህል ተአምር ሆኖብኝ
እንደነበር ዛሬም አስታውሰዋለሁ።
“እማዬ የበላሽው ምሳ ሆድሽ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ነው” አልኳት።
ሰማያዊ አይኖቿ በሳቅ እያንፀባረቁ እንደገና እንድገምት ነገረችኝ።
ከዚያ ዜናውን ስትነግረን ድምጿ ጣፋጭ ሆኖ ነበር። “ውዶቼ፣ ግንቦት መጀመሪያ ላይ አዲስ ልጅ ይኖረኛል። በእርግጥ ዛሬ ሀኪሙ ሁለት የልብ ትርታዎች መስማቱን ነግሮኛል ይህ ማለት ልጆቹ መንታ ናቸው ማለት ነው እግዚአብሔር አያድርገውና ምናልባት ሶስትም ሊሆኑ ይችላሉ። ይህንን ዜና አባታችሁ ገና ስላልሰማ ከእኔ ቀድማችሁ እንዳትነግሩት” አለችን፡፡

በሰማሁት ነገር ደንግጬ ክሪስቶፈር ምን እንደተሰማው ለማወቅ አይኖቼን
ወደሱ ወረወርኩ። ያፈረ ግን ደግሞ የተደሰተ ይመስላል እንደገና በእሳቱ
ብርሃን የሚያበራውን የእናቴን ቆንጆ ፊት ተመለከትኩ። ከዚያ ፍንጥር ብዬ
ተነሳሁና እየሮጥኩ ወደ ክፍሌ ሄድኩ
አልጋዬ ላይ በደረቴ ተወረወርኩና ፊቴን ትራሱ ውስጥ ቀብሬ አለቀስኩ።
ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ህፃናት ሊመጡ! ህፃኗ እኔ ነኝ! የሆኑ ነጭናጫና
አልቃሻ ፍጡራን መጥተው የእኔን ቦታ እንዲወስዱ አልፈልግም ስቅስቅ
ብዬ እያለቀስኩ የሆነ ሰው መጉዳት ባልችል እንኳን የሆነ ነገር መጉዳት
ስለፈለግኩ እጆቼን ጨብጬ ትራሱን በቡጢ ቀጠቀጥኩት አልቅሼ ሲወጣልኝ
ቀና ብዬ ተቀመጥኩና ጠፍቶ ስለመሄድ ማሰብ ጀመርኩ።

እናቴ የተቆለፈው በሬ ላይ ሆኖ እየጠራችኝ ነው። "ካቲ” አለች እናቴ: “አንድ ጊዜ ገብቼ መነጋገር እንችላለን?” ስትል ጠየቀችኝ።

“ሂጂልኝ!” ስል ጮህኩ። “ልጆችሽን ገና ከአሁኑ ጠልቻቸዋለሁ።"

መካከለኛ ለሆንኩት ለእኔ በግዴለሽ ወላጆቼ ምን እንደተደገሰልኝ አውቄያለሁ።
በቃ ከዚህ በኋላ ልረሳ ነው የአርብ ስጦታዎች የሚባሉ ነገሮች አይኖሩም
አባቴም ቢሆን ከአሁን በኋላ ስለ እናቴ፣ ስለ ክሪስቶፈርና ከቦታዬ ስላስነሱኝ
የሚያስጠሉ ህፃናት ብቻ ነው የሚያስበው።

የዚያን ቀን ምሽት አባቴ ቤት እንደገባ ብዙም ሳይቆይ ወደኔ ክፍል መጣ።
ሊያየኝ ከመጣ ብዬ በሩን ከፍቼው ነበር፡ በጣም ስለምወደው ቀስ ብዬ ፊቱን
አየት አደረግኩት ያዘነ ይመስላል፡ በዛ ላይ ተለቅ ያለ ብራማ ቀለም ባለው
ካርቶን ውስጥ የታሸገ ነገር ይዟል።
“የኔ ካቲ እንዴት ናት?” ሲል በለሆሳስ ጠየቀ፡፡ በደረቴ ተኝቼ በክንዴ ስር
አጮልቄ እያየሁት ነው፡ “ቤት ስገባ ሰላም ልትይኝ ሮጠሽ አልመጣሽም !
አሁንም እዚህ ስመጣ ሰላም አላልሽኝም ሌላው ቀርቶ ቀና ብለሽ እንኳን
አላየሽኝም: ካቲ፣ እየሮጥሽ ወደ እቅፌ ስላልመጣሽና ስላልሳምሽኝ አዝኛለሁ”
ምንም አልመለስኩለትም ግን አልጋው ላይ እንዳለሁ በጀርባዬ ሆንኩና
አፈጠጥኩበት፡ እሱና እናቴ ለምን ሌሎች ልጆች ፈለጉ? ሁለት አይበቃም
ነበር? በህይወቱ ሙሉ ተወዳጅ መሆን ያለብኝ ሴት ልጁ እኔ ብቻ መሆን
እንዳለብኝ አያውቅም እንዴ?
በረጀሙ ተነፈሰ፡ ከዚያ ቀረብ ብሎ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ፡ “አንድ
ነገር ታውቂያለሽ? በእንደዚህ አይነት አስተያየት ስታይኝ ለመጀመሪያ ጊዜ
ነው እየሮጥሽ እቅፌ ውስጥ ያልገባሽበት የመጀመሪያ አርብ ነው: ላታምኒኝ
ትችያለሽ ግን አርብ ደርሶ ቤት እስክመጣና አንቺን እስካይሽ ድረስ ህያውነት አይሰማኝም መሸነፍ አልፈለግኩም ከአሁን በኋላ አይፈልገኝም ትልቁ ልጁ አለ አሁን ደግሞ ሌሎች አልቃሻ ልጆች እየመጡለት ነው። በመሃሉ እረሳለሁ:

“ሌላም ነገር ልንገርሸ?” ሲል ጀመረ። ...

ይቀጥላል
👍54🤩16🥰1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሁለት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ

..."ሌላም ነገር ልንገርሽ?" ሲል ጀመረ።በቅርበት እየተመለከተኝ ነው፡ “አርብ አርብ ወደ ቤት ስመጣ ላንቺም ሆነ ለወንድምሽም ምንም ስጦታዎች
ባላመጣላችሁ እንኳን… ሁለታችሁም በመምጣቴ ብቻ ተደስታችሁ እንደ እብድ እየሮጣችሁ እንደምታቅፉኝና እኔን እንጂ ስጦታዎቹን እንደማታስበልጡ አምን ነበር እናታችሁና እኔ በደርዘን የሚቆጠሩ ልጆች ቢኖሩንም እንኳን ሁልጊዜም በልቤ ውስጥ ትልቅ ቦታ እንዳለሽ የምታውቂና ጥሩ አባት በመሆኔ ትወጂኛለሽ ብዬ አስብ ነበር ለካ ተሳስቻለሁ አለ: ከዚያ መናገሩን ቆም አደረገና እንደገና በረጅሙ ተነፈሰ: ሰማያዊ አይኖቹ ደፈረሱ፡ “የእኔ
ካቲ የመጀመሪያ ሴት ልጄ በመሆኗ አሁንም ለእኔ የተለየች እንደሆነች የምታውቅ ይመስለኝ ነበር :"

በተቆጣና በተጎዳ አስተያት አየሁት ከዚያ ሳግ አነቀኝ “ግን እማዬ ሌላ ሴት ልጅ ሲኖራት ለሷም ተመሳሳይ ነገር ትላታለህ” አልኩት።

“እላታለሁ?”

“አዎና” ከመቅናቴ የተነሳ ተንሰቅስቄ ጮህኩ፡ “ትንሽና ቆንጅዬ ስለምትሆን እኔን ከምትወደኝ የበለጠ ትወዳታለህ”
“በጣም ልወዳት እችላለሁ ግን hአንቺ የበለጠ አይሆንም” አለና ክንዶቹን ዘረጋ ከዚህ የበለጠ መቋቋም አልቻልኩም: ከተጋደምኩበት ብድግ ብዬ ደረቱ
ላይ ልጥፍ አልኩና አጥብቄ አቀፍኩት። እቅፉ ውስጥ እንዳለሁ ማልቀሴን እንዳቆም አባበለኝ “አታልቅሺ ካቲ… ቅናት አይሰማሽ፡ የምወድሽ በፍጹም ከእነርሱ ባነሰ አይሆንም: ደግሞ ካቲ፣ እውነተኛ ህፃናት ከአሻንጉሊቶች
የበለጠ ደስ ይላሉ ታያለሽ ትወጃቸዋለሽ፡ እናትሽ ልትይዛቸው ከምትችላቸው በላይ ልጆች ስለሚኖሯት የአንቺን እርዳታ መፈለጓ የማይቀር ነው እኔ ቤት
በማልኖርባቸው ጊዜያት እናትሽ የሁላችንንም ህይወት ቀላል የምታደርግ ውድ ልጅ እንዳለቻት ማወቄ በራሱ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ያደርገኛል” አለኝና
ሞቃት ከንፈሮቹ በእንባ የራሰ ጉንጬ ላይ አረፉ። “ነይ አሁን ስጦታሽን ክፈቺና ውስጡ ስላለው ነገር ምን እንደምታስቢ ንገሪኝ አለ።

ስጦታውን ከመክፈቴ በፊት አይኖቹ ውስጥ ላስቀመጥኩት ሀዘን ማካካሻ ፊቱን በሙሉ በመሳም አዳረስኩትና የበለጠ ጥብቅ አድርጌ አቀፍኩት።
በሚያምረው ካርቶን ውስጥ ኢንግላንድ ውስጥ የተሰራ ብርማ ቀለም ያለው ቀ የሙዚቃ ሳጥን ነበረበት። ሙዚቃው ሲጫወት ሮዝ ቀለም ያለው ቀሚስ
የለበሰች አሻንጉሊት መስታወት ፊት እየተሸከረከረች ትደንሳለች።

“የሙዚቃ ሳጥን ብቻ ሳይሆን የጌጥ መያዣም ነው” አለና ካርቶኑ ውስጥ ከነበረች ማስቀመጫ ውስጥ ቀይ ፈርጥ ያለባት የወርቅ ቀለበት አውጥቶ
ጣቴ ላይ አጠለቀልኝ። “ገና ካርቶኑን ሳየው ልገዛልሽ እንደሚገባኝ አወቅኩ።እና በዚህ ቀለበት የኔዋን ካቲ ለዘለዓለም እንደምወዳት ቃል እገባለሁ" አለ።

አባታችን ህፃናቱ እስኪወለዱ ለመጠበቅ ለሁለት ሳምንት ያህል ቤት ነበር።ሁልጊዜ እናትና አባታችን ከባልና ሚስትነት ይልቅ ወንድምና እህት ይመስላሉ
ብላ የምትናገረው ጎረቤት የምትኖረው ወይዘሮ ቤርታ ሲምሰን ወጥ ቤት ውስጥ ሆና ምግብ እያዘጋጀችልን ነበር።

አራት ሰዓት አካባቢ አባታችን ወደምንመገብበት ክፍል እየተጣደፈ ገባና ለእኔና ለክሪስቶፈር እናታችንን ሆስፒታል ይዟት ሊሄድ እንደሆነ ነገረን
“አትጨነቁ፣ ሁሉም ነገር ጥሩ ይሆናል፡ ወይዘሮ ሲምሰንን እንዳታስቸግሯት የቤት ስራዎቻችሁን ስሩ። በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ወንድሞች፣ እህቶች ወይም ደግሞ ወንድምና እህት ማግኘታችሁን ታውቃላችሁ።” አለን በማግስቱ ጠዋት አባታችን ከሆስፒታል ሲመለስ ፂሙን ሳይላጨው ልብሱም ተጨማድዶ በጣም የደከመው ቢመስልም በደስታ እየሳቀ “ገምቱ! ወንዶች
ወይስ ሴቶች?” አለን። “ወንዶች!” አለ ኳስ መጫወት የሚያስተምራቸው ወንድሞች የሚፈልገው ክሪስቶፈር፡ እኔም የምፈልገው ወንዶች እንዲሆኑ
ነው የአባቴን ፍቅር የሚነጥቁን ሴቶች ልጆች አልፈልግም:

“ወንድና ሴት ናቸው:: አለ አባታችን በኩራት: “እስከዛሬ አይቻቸው የማላውቃቸው አይነት የሚያማምሩ ፍጥረታት ናቸው: ራሳችሁ እንድታዩዋቸው ኑ ልብሶቻችሁን ልበሱና ልውሰዳችሁ ”

እንዳኮረፍኩ ነው አባታችን ህጻናቱ የተኙበት ክፍል ውስጥ እንዳሉ ማየት እንድችል ወደ መስኮቱ ከፍ አድርጎ ሲያቅፈኝ እንኳን ነርሷ ያቀፈቻቸውን ሁለት ሚጢጢ ህፃናት ለመመልከት እያመነታሁ ነበር በጣም ትንንሾች
ናቸው! ጭንቅላታቸው ከአፕል አይበልጥም: ትንንሽ እጆቻቸው በአየር ላይ ይወናጨፋሉ፤ አንደኛው ደግሞ ልክ በመርፌ እንደተወጋ አይነት ይጮሃል።
አባታችን ጉንጬን እየሳመና ጥብቅ አድርጎ እያቀፈኝ “እፎይ… እግዚአብሔር እንዴት መልካም ነው! ልክ እንደመጀመሪያዎቹ ልጆቼ እንከን የለሽ የሆኑ
ሌላ ወንድና ሌላ ሴት ልጅ ሰጠኝ።” አለ። ሁለቱንም እንደምጠላቸው አስቤ ነበር። በተለይ ኮሪ ተብሎ ከተሰየመ
ዝምተኛ ልጅ በአስር እጥፍ ጯሂ የሆነችውን ኬሪ ተብሎ ስም የወጣላትዐልወዳት እንደማልችል አስብ ነበር። ሁለቱ ከእኔ ክፍል ባሻገር ያለው ክፍብ ውስጥ ከሆኑ ፀጥ ያለ መኝታ የማይታሰብ ነው: ሆኖም ከፍ ብለው ፈገግ ማለት ሲጀምሩና እኔ ስመጣ ወይም ሳቅፋቸው አይኖቻቸው ላይ ያለውን ደስታ ስመለከት የቅናት ስሜቴን ሞቃትና ደስ የሚል የእናትነት ስሜት ሲተካው ታወቀኝ፡ የትምህርት ሰዓት እንዳለቀ እነሱን ለማየት፣ ከእነሱ ጋር ለመጫወት፣ የሽንት ጨርቃቸውን ለመቀየር፣ ጡጧቸውን ለመያዝና እነሱን
ለማቀፍ ወደቤት እጣደፍ ጀመር። እውነትም ለካ ከአሻንጉሊቶች የበለጠ ደስታ የሚሰጡ ናቸው።

እኔ ሁለቱንም ለመውደድ ልቤ ውስጥ ቦታ እንዳለኝ ሲገባኝ፣ ወላጆችም ልባቸው ውስጥ ቁጥራቸው ከሁለት በላይ ለሆኑ ልጆች የሚሆን በቂ ቦታ
እንዳላቸው ተረዳሁ

ትንሽ ጠየም ከሚለው ከአባታችን በስተቀር ሁላችንም ተመሳሳይ የሚያምር የቆዳ ቀለምና ወርቃማ ፀጉር ስላለን፣ የአባታችን የልብ ጓደኛ ጂም ጆንስተን
“የድሬስደን አሻንጉሊቶች” በሚል ቅጽል ስም ይጠራን ነበር እሱን የሰሙ ጎረቤቶቻችንም የሚጠሩን በዚህ ስም ነበር።

መንትዮቹ አራት አመት ሲሆናቸው ክሪስቶፈር አስራ አራት አመት ሞላው"እኔም አስራ ሁለተኛዬን ይዣለሁ። ለየት ያለው አርብ መጣ የአባታችን ሰላሳ ስድስተኛ አመት የልደት ቀን ነው: ድንገት ልናስገርመው ግብዣ አዘጋጅተናል። እናታችን ተጣጥባና ተቆነጃጅታ ተረት ተረት ላይ ያለችውን ልዕልት መስላለች የምግብ ቤቱ ጠረጴዛ በምግቦች ተሞልቶ አሸብርቋል።
ስጦታዎቹ ሁሉ ተደርድረዋል ለቅርብ ወዳጆቻችንና ለቤተሰብ ብቻ የተዘጋጀ ግብዣ ነበር፡

ሁላችንም አምሮብንና ተውበን አባታችን እስኪመጣ መጠበቅ ጀመርን፡አስራ አንድ ሰዓት አለፈ እየጠበቅነው ነው:: የአባታችን አረንጓዴ ካዲላክ መኪና ግን እስካሁን አልመጣም: እናታችን በጭንቀት ክፍሉ ውስጥ
እየተንጎራደደች ነው: የተጠሩት እንግዶች እያወሩ ነው አባታችን በተለምዶ አስር ሰዓት ላይ ይመጣ ነበር፡ አረ እንዲያውም አንዳንዴ ከዚያም ሁሉ ቀደም ይላል። ዛሬ ግን ያለወትሮው በጣም ዘግይቷል።

አንድ ሰዓት ሆነ፤ አባታችን እስካሁን ብቅ አላለም።

እናታችን ረጅም ሰዓት ወስዶባት ያዘጋጀቻቸው ምግቦች ማሞቂያው ውስጥ ብዙ በመቆየታቸው ምክንያት ደረቁ አንድ ሰዓት የመንትዮቹ የመኝታ ሰዓት በመሆኑ እንቅልፋችው መጥቶ እንኳን ሳያዩት ላለመተኛት አስር ጊዜ “አባባ የሚመጣው መቼ ነው?” እያሉ መጠየቅ ጀምረዋል።

እናታችን ወዲያ ወዲህ እየተመላለሰች ደጋግማ በሰፊው መስኮት ወደ ውጪ
ትመለከታለች።

ድንገት የሆነ መኪና ወደ እኛ ግቢ ሲታጠፍ ተመለከትኩና “አባታችን መጣ!” ብዬ ጮህኩ።
👍591
በራፋችን ላይ መጥቶ የቆመው ግን የአባታችን አረንጓዴ ካዲላክ ሳይሆን ፖሊስ የሚል የተጻፈበት ነጭ መኪና ነበር።

ሁለት የደንብ ልብስ የለበሱ ፖሊሶች ወደ በሩ ቀርበው የበሩን ደወል ሲጫኑ እናታችን በድንጋጤ ደርቃ ቀረች። እጇን አንገቷ ላይ አድርጋ፣ የደነዘዘች መስላና አይኖቿ ጠቁረው ስመለከታት ልቤ ውስጥ የሆነ የሚስፈራ ነገር
ሲራወጥ ተሰማኝ።

በሩን የከፈተው የአባታችን ጓደኛ ጂም ጆንስተን ነበር።በእድሜ ጠና ያለው ፖሊስ እይታውን ከአንደኛዋ ሴት ወደ ሌላኛዋ እያንከራተተ “ወይዘሮ ክሪስቶፈር ዶላንጋንገር?” ሲል ጠየቀ
እናታችን በዝግታ ጭንቅላቷን ነቀነቀች። ወደሷ ጠጋ አልኩ፤ ከሪስቶፈርም እንደዚያው አደረገ፡ መንትዮቹ ግን የፖሊሶቹ መምጣት ምንም ግድ ሳይሰጣቸው ወለሉ ላይ ተቀምጠው በትናንሽ መኪኖቻቸው እየተጫወቱ ነው
ሌላኛው ፖሊስ ወደ እናታችን ጠጋ አለና “ወይዘሮ ዶላንጋንገር፣ በጣም እናዝናለን፡ በግሪንፊልድ አውራጎዳና ላይ አደጋ ደርሶ ነበር አደጋው ውስጥ ባለቤትሽም ነበረበት” አለ

ከእናታችን የታፈነ ጉሮሮ ድንገተኛ ሳግ ተሰምቶ ተንገዳገደች: እኔና ክሪስ አጠገቧ ሆነን ባንደግፋት ኖሮ ትወድቅ ነበር።

“አደጋውን በተመለከተ የአይን ምስክር አነጋግረን ነበር፤ የባለቤትሽ ጥፋት አልነበረም::” ሲል ያለምንም ስሜት ቀጠለ፡፡ “እንደ መረጃው ከሆነ ሰማያዊ
ፎርድ መኪና ይነዳ የነበረ የሰከረ ሰው የባለቤትሽን መኪና ለመግጨት እየተጠጋ ነበር። ባለቤትሽ አደጋ እየመጣ መሆኑን በማወቁ ላለመጋጨት
መንገዱን ሲለቅ ሌላ መኪና ላይ የነበረ ማሽን መኪናው ላይ ወደቀበትና የባለቤትሽ መኪና ተገለባበጠ፡ ያም ሆኖ ሊተርፍ ይችል ነበር. ነገር ግን እየመጣ ያለ ሌላ የጭነት መኪና መቆም ባለመቻሉ የባለቤትሽን መኪና
በሃይል ሲገጨው የባለቤትሽ መኪና እንደገና ተገለባበጠና ... በእሳት ተያያዘ

"የኔ ባለቤት?” እናታችን በሹክሹክታ ተናገረች: ድምጿ በጣም የደከመና ለመስማት የሚያስቸግር ነበር፡ “አልሞተም… አይ…ሞትም” አለች:

“እመቤቴ፣” አለ ፖሊሱ በፊኛዎችና በመብራት የደመቀውን ክፍል እየተመለከተ። “በዚህ ልዩ በሚመስል ቀን እንደዚህ አይነት መጥፎ ዜና ይዤ
በመምጣቴ ይቅርታ: አዝናለሁ እመቤቴ ሁሉም ሰው እሱን ለማትረፍ የሚችለውን ሁሉ አድርጓል: ግን ዶክተሩ እንደነገረን ህይወቱ ያለፈው ወዲያውኑ ነበር”

ሶፋ ላይ ከተቀመጡት መሀል የሆነ ሰው ጩኸቱን አቀለጠው
እናታችን አልጮኸችም: አይኗ ላይ ግን ከባድ ሀዘን ይታያል። ፊቷ ላይ
የነበረው የሚያምር ቀለም የሞት ጭንብል መሰለ ይህ ሁሉ ነገር እውነት ሊሆን እንደማይችል በአይኖቼ ልነግራት በመሞhር አይነት ቀና ብዬ አተኩሬ
ተመለከትኳት።

አባቴ አይሆንም! የእኔ አባት አይሆንም! እሱ ሊሞት አይችልም... ሊሆን አይችልም! የሚሞቱት ያረጁና የታመሙ ሰዎች እንጂ የሚፈለግ፣ የሚወደድና ወጣት የሆነ ሰው አይደለም።

ሆኖም እናቴ ፊቷ ገርጥቶ፣ አይኗ ፈዞና እጆቿ እርጥብ መሀረብ እያፍተለተሉ ቆማለች፡ በምመለከታት በእያንዳንዱ ሰከንድ አይኖቿ ወደ ውስጥ እየጎደጎዱ የሚሄዱ ይመስሉ ነበር።

ማልቀስ ጀመርኩ። ፖሊሱ “እመቤት፣ በመጀመሪያው ግጭት ወቅት ከመኪናው ውስጥ የወደቁ
የተወሰኑ እቃዎቹን አግኝተናል: ለማትረፍ የቻልነውን ያህልም ሞከረናል አለ።

“ሂድ ከዚህ! ውጣ! የኔ አባት አልሞተም: እሱ አልሞተም! መንገድ ላይ አይስክሬም ለመግዛት ቆሞ ነው አውቃለሁ በየትኛውም ደቂቃ ይመጣል!
ውጣ ከዚህ!” እያልኩ ፖሊሱ ላይ ጮህኩበት: ፖሊሱን ለመምታት ወደፊት ተንደረድሬ ያዝኩት ሊያላቅቀኝ እየሞከረ ሳለ ክሪስቶፈር መጣና ጎትቶ
ወሰደኝ።

“እባካችሁ አንዳችሁ ይህችን ልጅ እርዷት” አለ።

የእናቴ እጆች ትከሻዬን ይዘው ወደ እሷ አስጠጉኝ፡ ቤት ውስጥ ያሉት ሰዎች በደነገጠ ድምፅና በሹክሹክታ ያልጎመጉማሉ። በሞቀው መጋገሪያ ውስጥ
የነበረው ምግብ ተቃጥሎ መሽተት ጀመረ።

የሆነ ሰው መጥቶ እጄን ይዞኝ እግዚአብሔር እንደ አባቴ ያለ ሰው ህይወት በጭራሽ እንደማይወስድ እንዲነግረኝ ጠበቅኩ። ግን ማንም አልመጣም።

ክሪስቶፈር ብቻ እጁን ወገቤ ላይ አደረገ፡ ሶስታችንም ተቃቀፍን-ዘ እኔ፣ እናቴና ክሪስቶፈር።

በመጨረሻ እንግዳ በሆነ ሻካራ ድምፅ መናገር የመጀረው ክሪስቶፈር ነበር።
“አባታችን ለመሆኑ እርግጠኞች ናችሁ? በእሳት የተያያዘው አረንጓዴ ካዲላክ ።መኪና ውስጥ የነበረው ሰው የደረሰበት ከባድ ቃጠሎ ከነበረ ማንነቱን እንዴት
ታውቃላችሁ? የእኛ አባት አይሆንም ምናልባት ሌላ ሰው ሊሆን ይችላል አለ።

እናታችን ከአይኖቿ እምባ ባይወርድም ከጉሮሮዋ ውስጥ የተቆራረጠ ጥልቅ መንሰቅሰቅ ይሰማ ነበር አምናለች እነዚያ ሁለት ሰዎች እውነቱን እየተናገሩ
እንደሚሆን አምናለች!
ልደት ለማክበር ዘንጠው የመጡት እንግዶች ሁሉ አሁን በዙሪያችን ተሰብስበው ለተፈጠረው ነገር ማጽናኛ የሚሉትን ቃል እየነገሩን ነው።

“በጣም እናዝናለን ኮሪን፣ እውነት በጣም አስደንጋጭ ...አሳዛኝ ... "

“ምስኪን ክሪስ ... ምን አይነት ከባድ መከራ ደረሰበት”

“ቀናችን የተቆጠረ ነው
ሁልጊዜም እንዲህ ነው፣ ከተወለድንበት ጊዜ ጀምሮ ቀናችን የተቆጠረ ነው።"

ቀጠለ ቀጠለ እናም ልክ ውሀ ኮንክሪት ውስጥ እንደሚሰርግ አይነት ነገሩ በውስጣችን በቀስታ ሰረገ: አባታችን ሞቷል። ከዚያ በኋላ መቼም በህይወት
አናየውም ልናየው የምንችለው በሳጥን ውስጥ ሆኖ ከዚያ መሬት ውስጥ ሲገባና ስሙ፣ የተወለደበትና የሞተበት ቀን የተፃፈበት ድንጋይ ላይ ነው።
እኔ እንደተሰማኝ ሊሰማቸው የማይገባ ስለሆነ መንትዮቹ እንዴት እንደሆኑ ለማወቅ ዞሬ ተመለከትኩ።

ይቀጥላል
👍31😢174🎉1
አትሮኖስ pinned «#የጣሪያ_ስር_አበቦች ፡ ፡ #ክፍል_ሁለት ፡ ፡ #ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ ..."ሌላም ነገር ልንገርሽ?" ሲል ጀመረ።በቅርበት እየተመለከተኝ ነው፡ “አርብ አርብ ወደ ቤት ስመጣ ላንቺም ሆነ ለወንድምሽም ምንም ስጦታዎች ባላመጣላችሁ እንኳን… ሁለታችሁም በመምጣቴ ብቻ ተደስታችሁ እንደ እብድ እየሮጣችሁ እንደምታቅፉኝና እኔን እንጂ ስጦታዎቹን እንደማታስበልጡ አምን ነበር እናታችሁና እኔ በደርዘን የሚቆጠሩ…»
#ሳቤላ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


...«ደኅና እኔ እጠራታለሁ » አለና ሚስተር ካርላይል በዚያ ግጥም ብሎ በሞላው ሕዝብ መኻል ዐልፎ ሔደ " በዚያ ሰዓት አንዲቷ የለንደን ተጫዋች አሳዛኝ
ዘፈን ስትዘፍን ስለነበር ተመልካቹ ሁሉም ሚስተር ካርላይልን በክፉ ዐይን ዐየው የሰውን መከፋት ችላ ብሎ አለፈና ከሳቤላ ፊት ቆመ።

"እኔ ደሞ ዛሬ ማታ ወደኔ ትመጣለህ ብዬ አላሰብኰም - በጣም ግሩም ዝግጅት አይዶለም ? እኔን መቸም እንዴት አስደሰተኝ መሰለህ » አለችው .

« እዎን በጣም ደስ የሚል ነው » አላት ፊቱን ጥቁርቁር እያደረገ
« አሁን ግን ስቤላ ( ሎርድ ማውንት እስቨርን እምብዛም ደኅንነት የተሰማቸው አልመሰለኝም " ስለዚህ ሠረገላውን ልከውልሻል »

« ምን ! አባባ ደኅና አይዶለም !! » አለች ከመናገሩ ቀጠል አድርጋ።

«ሳያማቸው አልቀረም ግን እስከዚሀም አይመስለኝም " ሆኖም ወደቤት እንድትመጭ ይፈልጉሻል : እየመራሁ ላሳልፍሽ ? »

«አየ አባባ ... ሁልጊዜ እንዳሰበልኝ አሁንኮ እንዳይሰለቸኝ ስለሠጋ ቀደም ብሎ ሊያላቅቀኝ ፈልጎ ነው " አመሰግናለሁ ... ሚስተር ካርላይል " እስከ ዝግጅቱ መጨረሻ እቆያለሁ »

« የለም የለም ሳቤላ ... እሱማ ስለ ባሰባቸው ነው የላኩብሽ» መልኳ ልውጥ ግንባሯ ቁጥር አለ ግን አልደነገጠችም « እሺ ጥሩ አሁን አዳራሹን አንዳንረብሽ ይህ የተጀመረው ዘፈን ያብቃና እወጣለሁ »

« ጊዜ ባታባክኝ ይሻላል ስለ አዳራሹና ስለ ሕዝቡ ምንም አታስቢ»

ወዲያው ተነሥታ ክንዷን ከሚስተር ካርላይል ክንድ ጣል አደረገች » እሱም ነገሩን ለሚስዝ ዲሊ ገጸላትና ሳቤላን እየመራ ይዟት ወጣ ተመልካቹ በግድ
በመጨነቅ መንገድ እየሰጠ አሳለፋቸው " ብዙ ሕዝብም በዐይኑ ተከተላቸው ከሁሉ የበለጠ የተቅበጠበጠችውና ለማወቅ የጓጓችው ግን ባርባራ ነበረች "
የት ሊወስዳት ነው ? » አለች ሳታስበው
« እኔ ምን ዐውቃለሁ ? » አለቻት ኮርነሊያ « ባርባራ ... ዛሬ ማታ መቁነጥነጥ አበዛሽሳ? ምን ነካሽ? ሰዎችወደዚህ የሚመጡት እኮ ሊያዳምጡ ሊመለከቱ
እንጂ እንደዚህ ሊቅበጠበጡ አይደለም »

የሳቤላ ካባ ከተቀለበት ወርዶ ተደረበላትና ደረጃውን ከሚስተር ካርላይል ጋር ወረደች " ሠረገላው እስከ በሩ ተጠጋላት ። ሠረገላ ነጂው መንገድ ለመጀመር
ልጓሙን ሳብ አድርጎ ተዘጋጅቶ ጠበቃት አንድ ሌላ አሽከር እመቤቲቱን ገና ሲያያት የሠረገላውን በር ከፈተላት ሰውየው ገና ሥነ ሥርዓት ያልተማረ አዲስ ገብ ገጠሬ ብጤ ነበር " ክንዷን ከሚስተር ካርላይል ክንድ አስለቅቃ ወዶ ሠረገላው ልትገባ ስትል ሰውየውን እያየች ትንሽ ቆም አለችና « አባባ በጣም አሞታል እንዴ ? » አለችው "

« አዎን እመቤቴ ሲያቃስቱ ለሰማቸው ያሳዝናሉ " አዩ አንጀት ሲበሉ ! ሰዎችማ ምናልባት ዛሬን ቢያድሩ ነው እንጂ አይተርፉም ይላሉ » አላት።

ምርር ብላ ጮኸችና ከመደንገጧ የተነሣ ልትወድቅ ስትል የካርላይልን ክንድ ግጥም አድርጋ በመያዝ ተረፈች ሚስተር ካርላይል ሰውየውን በቁጣ ገፈተረው ።ከዚያ ድንጋይ ንጥፍ መሬት ላይ በቁመቱ ቢዘርረውም አይረካም ነበር " በጣም
ተናድዶበታል "

«ምነው ሚስተር ካርላይል ለምን አልነገርከኝም ? » አለችው እየተንቀጠቀጠች "

« እኔስ አሁን በመናገርሽም በጣም አዝኛለሁ አሁንም አትደንግጪ ! ሁል ጊዜም እንዴት እንደሚነሣባቸው ታውቂያለሽ " የተለመደው በሽታ ተነሣባቸው
እንጂ ሌላ ምን ይሆናሉ ብለሽ ነው » በይ ይልቅ አሁን ግቢና እንሒድ ምንም ክፉ ነገር እንደማይጠብቀን አምናለሁ»

« አንተም አብረኸኝ ልትመጣ ነው ? »

«አዎን ብቻሽን እንዴት እሰድሻለሁ?» አላት እንዲቀመጥ ፈቀቅ አለችለት "

« ግድ የለም ተይው እኔ ከውጭ እቀመጣለሁ » አላትና በሩ ከተዘጋ በኋላ ከነጂው ጐን ተቀመጠ አሽከሮቼ ከኋላ ተቀመጡ " ሠረገላው ገሠገሠ " ሳቤላ
ከአንድ ጥግ ሽብልል ብላ ተቀምጣ ትንሠቀሠቅ ጀመር "

« ለፈረሶቹ አትዘንላቸው ቶሎ ቶሎ ንዳ አለበለዚያ ሳቤላ በሐሳብ ብቻ ትታመማለች » አለ ሚስተር ካርላይል

« ምስኪን ልጅ መከራዋ አላለቀላትም " ሌሊቱ ከመንጋቱ በፊት ከዚህ የከፋ ነገር ይጠብቃታል " እኔ ከዚህ ቤት ዐሥራ አምስት ዓመቴ ነው ። እሷን ገና ሕፃን ሳለች ጀምሬ ነው የማውቃት »

« ግን ኧርሉን በጣም የሚያሠጋቸው ነው ? »

« አዎን በጣም ታመዋል ሚስተር ዌይን ራይት በሽታው ወደ ልባቸው ተሸጋግሯል ሲሉ ሰምቻለሁ »
« ወትሮምኮ በሺታው ሲነሣባቸው እንዶዚህ ኃይለኛ ነው »

« ዐውቃለሁ የዛሬው ግን የተለየ ነው » ከዚህ ሌላ ዶግሞ » አለ ሠረግላ ነጅው በምስጢር አነጋገር « የሌሊት ወፎቹም በከንቱ አይዶለም የመጡት »

« የሌሊት ወፎቹ ? » አለ ሚስተር ካርላይል "

« አዎን " የነሱ መምጣት ሞት ሰተት ብሎ ወዶቤት መግባት መሆኑን የማያወላውል ምልክት ነው»
« ስለ ምንድን ነው የምታወራው ሚስተር ዌልስ?» አለው ሚስተር ካርላይል
« ዛሬ ቤቱን የሌሊት ወፎች ሲዞሩት አመሹ የት አባታቸው አስቀያሚዎች ናቸው " እኔማ አልወዳቸውም "

« የሌሊት ወፎች ኮ ሌሊት የትም መብረር ይወዳሉ ተፈጥሯአቸው ነው . . .

« ተፈጥሮአቸው ቢሆንም በመንጋ ሁነው እየበረሩ በመስኮት አይገቡም ዛሩ ማታ እመቤቴን ከሙዚቃው ትርዒት አድርሼ ተመለስኩ " ከዚያ ሚስዝ ሜሰን
እንደምትፈልገኝ ነገሩኝና እሷ ወደ ነበረችበት ወደ ቤተ መጻሕፍቱ ስገባ ከተከፈተው መስኮት ቁማ አገኘኋት » ብርድ ስለነበር ለምን መስኮት ከፍታ እንደ ቆመች ጠየቅኳት እሷም ቀረብ ብዬ
እንድመለከት ጠራችኝ እኔም ወደ መስኳቱ ጠጋ ብዬ ብመለከት
ብመለከት በሕይወቴ አይቸው የማላውቀው ጉድ አየሁ" በብዙ መቶ የሚቆጠሩ የሌሊት ወፎች ዳመና መስለው ክንፎቻቸውን እያማቱ መጡብን ወደ ኋላችን ሸሸት ባንል ኖሮ ፊታችንን ይመቱን ነበር " ከየት እንደ ተጠራቀሙ አላውቅም ከአንድ ደቂቃ በፊት ከደጅ ሳለሁ ለምልክት እንኳን አልነበሩም "

እነዚህ የለሊት ወፎች ምን ነካችው ይህን የሚያህል ክምችት ባንድ ላይ ሆነው አይተህ ታውቃለህ ... ዌልስ ? አለችኝ ሚስዝ ሜሰን “ እኔም ኧረ የለም ደግሞ እንደዚህ ከሰው ሲጠጉም አይቸ አላውቅም እንደዚህ ሆነው ባያቸውም ደስ አይለኝም " ገዱ ደግ አይደለም የክፉ ነገር ምልክት ነው አልኳት ለካስ እሷም በምልክቶችና በሕልመች ከሚስቁት አንዷ ሆናለች በሳቅ ልትፈርስ
እርሶዎም እንደሚያውቁት እሷ እመቤት ሳቤላን ከድሮ ጀምራ ስታስተምር የኖረች ናት እነዚህ የተማሩ ሰዎች በምልክት በሕልም በቀላሉ አያምኑም »

ሚስተር ካርላይል አንገቱን ነቀነቀ

« እንዶዚህ በብዛት መምጣታቸው የምን ምልክት ነው ትላለሀ ... ዌልስ አለችኝ ሚስዝ ሚዞን እያሾፈችብኝ „ “ እኔ እንደዚህ ግጥም ብለው በብዛት ሲመጡ
አይቻለሁ አላልኩም ግን የሌሊት ወፎች እንደዚህ በብዛት ሆነው ወደ ቤት ሲገቡ ብዙ ጊዜ መታየታቸውንና ከገቡበት ቤትም ሰው እንደሚሞት የማያብል
የታወቀ ምልክት መሆኑን ሲነገር ሰምቻለሁ ' አልኳት “ ኧረ ሞትስ በዚህ ቤት አይምጣ” እያለች መስኮቱን ዘጋችው የጌቶች ነገር በሐሳቧ መጣባት መስኮቱ እንደ
ተዘጋ እነዚያ አስቀያሚ ፍጡሮች መስኮቱን በክንፋቸው ይጠፈጥፉት ጀመር ከዚያ ሚስዝ ሜሰን ለአንድ ሦስት ደቂቃ ያህል ስለሌላ ጉዳይ ስታነጋግረኝ ቆየችና ስታበቃ ወደ መስኮቱ ዞር ብዬ ብመለከት አንድም የሌሊት ወፍ አልነበረም“

« ደግሞ ካንዱ ቤት መስኮት ክንፎቻቸውን ሊያርገበግቡ ሔደው ይሆናላ» አለ ሚስተር ካርላይል በነግሩ ባለማመን ።
👍27
« ከዚያ ከትንሽ ጊዜ በኋላ ቤቱ ተበጠበጠ ጌቶች በጣረ ሞት መያዛቸው ተሰማ " በሽታው ከሆዳቸው መግባቱን ወደ
ልባቸውም ሊሸጋገር ይችላል ብሎ ሚስተር ዌይን ራይት መናሩን ወሬው በአንድ ጊዜ በመላ ቤተሰቡ ዘንድ ተዳራሰ“ ዶኔስ ሐኪሞችን ፍለጋ ወደ ሊንበራ ተላከ እኔም እመቤት ሳቤላን ለማምጣት ወደ ሙዚቃው አዳራሽ መጣሁ " »

«መቸም በሽታው ቢጠናባቸውም የሌት ወፎቹም በረው ቢመጡም መልስው በጎ እንደሚሆኑ ተስፋ አለኝ » አለ ሚስተር ካርላይል "
ሠረገላ ነጂው ( ራሱን በአሉታ ነቀነቀና ፈረሶቹን ገረፋቸው እየጋለቡ መጥተው በሩን ዐልፈው ከቤት ደረሱ "

የቤቱ ጠባቂ የሆነችው ሚስዝ ሜዞን ከበራፉ ቁማ ስትጠብቃት ነበር " ሚስተር ካርላይል ደግፎ ከሠረገላው አወረዳት ሳቤላ ስላባቷ ለመጠየቅ ፈራች " ዝም
ለማለትም አልቻለችም " ተጨነቀች ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ እያለ « በጎ ነው ? ከክፍሉ ገብቼ ላየው እችላለሁ ? » አለች።

በርግጥ መሻል ይባል እንደሆነ እንጃ እንጂ አባቷ ነፍሱን ስለሳተ ከዚያ ሁሉ ማቃሰትና መጓጐር ዐርፎ ጸጥ ብሎ ነበር ሳቤላ ወደ እሱ ክፍል ስትግባ ካርላይል
ቤት ጠባቂዋን ወደኋላ ሳብ አደረጋት "

« የመትረፍ ተስፋ አላቸው ? » አላት "
« ምንም ተስፋ የላቸውም መሞታቸው ነው " »

ኧርሉ ማንንም አይለይም" ሥቃዩ ለጊዜው ተግ ብሎለት አልጋው ላይ ጸጥ ብሎ ተኝቶ ነበር ፊቱ ግን የሞት ጥላ ነበረበት " ሳቤላም ፊቱን አይታ ደነገጠች ቢሆንም ምንም ሳትጮህ ከመንቀጥቀጧ ጸጥ ብላ ቆች " « ቶሎ የሚሻለው ነው?»አለችው አጠገቧ ቆሞ ለነበረው ለሚስተር ዌይንራይት

« መቸም ... ተስፋ አለመቁረጥ ነው » አለ።

« ግን ፊቱ ግርጥት ብሎ ጢስ የመሰለው ለምንድነው ? እንደዚህ ሲሆን አይቸው አላውቅም " »

« በጣም ከባድ ሥቃይ ላይ ነበሩ . . እመቤት ሥቃይ ደግሞ ምልክቱን መልክ ላይ ይተዋል »

ሚስተር ካርላይልም ገብቶ ከሐኪሙ ጐን ቆመና እሱም የኧርሎን ፊት አይቶ ደነገጠ ሐኪሙን ለብቻው ሊያነጋግረው ፈልጎ በእጁ ነካ አድርጐት ሲወጣ ሳቤላ ደግሞ ካርላይልን ሲወጣ አይታ በእጅዋ ጠቀሰችው "

« ወጥተህ እንዳትሔድ . . . ሚስተር ካርላይል ሲነቃ ካጠገቡ ያየህ እንደሆነ ደስ ይለዋል አባባ አንተን ሲወድህ ለብቻው ነው " »

« የለም አልሔድም " የመሔድ አሳብም የለኝም " »

ከሊንበራ ሦስት ሐኪሞች ደረሱ - እነሱ ሲገቡ ኧርሎ ጣሩ እንደና ተነሥቶበት ከምትተናነቀው ነፍሱ ጋር ሲጠራሞት በበዓል ልብስና በሚያንጸባርቁ ጌጦች ያሸበረቀችው ቆንጆ ከጐኑ ቆማ ስትመለከተው አገኛት » ከአንድ ድግስ ላይ በድንገት ተጠርታ እንደ መጣች እነሱም ገምተው ነበር "
ሐኪሞቹ ቀረብ ብለው አዩት ትርታውን አዳመጡት ልቡን ዳስሱት " ለራሳቸው እንጂ ለሌላ የማይሰሙ ቃላት ተለዋጡ " እነሱ ልብ ያላሏት ቢመስሉም እስከ መጨረሻ ያደርጉት የነበረውን ሁሉ ስትከታተል የነበረች ሳቤላ ወዶ
ነሱ ጠጋ ብላ' « የምትረዱት ነገር ይኖራል ? ይድናል ? እባካችሁ እውነቱን ንገሩኝ » አላወቃችሁኝም እኔ እኮ አንዲት ልጁ ነኝ " ማንም የሌለኝ ብቸኛ ነኝ " »

ታላቁ ለውጥ ስለታቀረበ ነፍስና ሥጋ ሲለያዩ የሚኖረውን ከባድ መወራጨትና መጠራሞት እንዳታይ ከክፍሉ ሊያስወጧት ፈለጉ " እሷ ግን ከአባቷ ትራስ
ተደፍታ ተስፋ በመቁረጥ እየተንሰቀሰቀች አልወጣም ብላ አስቸገረች "

« አንዴ መውጣት አለባት » አለ አንዱ ሐኪም ቆጣ ብሎ « ስሙ እሜቴ » አላት ወዶ ሚስዝ ሚዞን እያየ «ምነው ይህችን ልጅ ነግሮ የሚያሰማ ዘመድ ከቤት
ውስጥ የለም? »
«ማን አላት?አሁን ያለነዉ ብቻችን ነን " ከነጭራሹም የቅርብ ዘመድ የላትም የኧርሎ ሁኔታ በየደቂቃው እየከፋ መወራጨቱም አየጨመረ መምጣቭን የተመለከተው ሚስተር ካርላይል የነገሩን አሳሳቢነት ተገንዝቦ ወደሷ ጠጋ ብሎ ሁላችንም ላባትሽ ደህንነት እየተጨነቅን ነው ። ግን ካንቺ መጨነቅ ጋር ልናወዳድረው አንችልም ። ኢምንት ነው " »

«አዎን ! ኢምት ነው ! አረ እንዴት ልሁነው እናን† ! ኧረ የት ልድረስ!ልቤ ፈሰሰ » አለች

« ስለዚህ የሐኪሞችን ትአዛዝ መቀበል አለብሽ በሽተኛውን ብቻቸውን ሆነው ሊያክሟቸው ይፈልጋሉ ጊዜ ዶግሞ በከንቱ እየባከነ ነው . .

« እና የኔ መውጣት አስፈላጊ ነው?ለአባቴ ይጠቅመዋል ? »

« አስፈላጊ ነው አመቤት ፍጹም አስፈላጊ ነው » »

ምንም ቃል ሳትጨምር ቀደም ብለው የሌሊት ወፎች ሲንጋጉበት ወደ ነበረው መጻሕፍት ቤት ገባች ከመሞቂያው ምድጃ እሳቱ ይንቀለቀል ነበር " ወደዚያው
ተጠጋችና ከምድጃው ላይኛ ጠርዝ ሔዳ በእጅዋና በራሷ ተደገፈች "

« ሚስተር ካርላይል » አለችው ቀና ሳትል "
« አለሁ ምን ላድርግልሽ ? » አላት ተከትሎ መጥቶ ነበርና ።

« ይኸውልህ ወጣሁ ተመልሸ አስክገባ ድረስ ሁኔታውን ቶሎ ቶሎ ትነግረኛለህ ? »

« አምን እነግርሻለሁ » ብሏት እንደ ወጣ ደንገጡሯ ማርቨል እየሰፈፈች ገባች

« እሜቴ ልብስሽን ብትለውጭውስ ? » አለቻት "

« አይ ተይኝ... አውልቄ እንዳበቃሁ ወደ አባቴ ቢጠሩኝስ ? »

« ግን እኮ እሜቴ እንዳሁኑ በመሰለ የመከራ ሰዓት እንዶዚህ ያለ ልብስ አይለበስም »
ሚስዝ ሜሰን አልማዟን አወለቀችላትና ገና ትንቀጠቀጥ ስለ ነበር አንድ ወፍራም መደረቢያ ትከሻዋ ላይ ጣል አዶረገችላት "

ሚስተር ዌይን ራይት ሲቀር ሌሎች ሐኪሞች ሔዱ " ለሎርድ ማውንት እስቨርን አንድም ነገር ሊደረግለት አልተቻለም " ጣሩ ረጅምና አስፈሪ ሆነ " የሞት
ጣሩ ጠናበት " መጓጐሩ • ማቃሰቱ መፈራገጡ መወራጮቱ የሚስቀጥጥ ነበር "

ሊነጋጋ ሲል ሳቤላ ትዕግሥቷ አለቀ " ሚስተር ካርላይል ያባቷን እውነተኛ ሁኔታ እያለሳለሰ ቶሎ ቶሎ ይነግራት ነበር ። እሷ ግን እንዳታየው የተደሪገበት ምክንያት ሊገባት ስላልቻለ ካርላይል አስቆጥቷት ነበር ሚስተር ካርላይል ጀርባውን ለበሩ ስጥቶ ከፊቷ ቆመና'«ይቅርታ አድርጊልኝ ሳቤሳ ... አላስገባሽም » አላት
እሱም ሁኔታዋን አይቶ አንጀቱ በኀዘን እንዶ ተላወሰ በፊቱ ላይ ያስታውቅ ነበር።

አምቃ ይዛው የነበረችው ለቅሶ ጥሶ መጣ ጦሽ ብላ አለቀሰች ወደ እሳቱ ይዟት ተመለሰና አብሯት ቆመ ።

« የምወዴው አባቴኮ ነው " በዚህ ዓለም ያለኝ እሱ ብቻ ነው»

« ዐውቃለሁ ብሶትሽ ስሜትሽ ሁሉ ለኔም ይሰማኛል »

«በል እስቲ ለምን እንዳላየው ተከለከልኩ ? በቂ ምክንያት ከሰጠኸኝ እቀበላለሁ እታዛለሁ ግን አባቴ እንዳይረበሽ ነው አትበለኝ አላምንህም" ውሸት
ነው። »

« በጣም ከባድ በሆነ ጣር ላይ ነው ያሉት « አሁን ያሉበትን ሥቃይ ያንቺዐአንጀት አይችለውም " አሁን እምቢ ብለሽ ብትገቢ የምታይው አስቃቂ ሁኔታ ዘለዓለም አዲስ እንዶ ሆነብሽ ይኖራል " ስለዚህ ምክሬን ተቀ0ዪ » »

« መሞቱ ነው ? »

ሚስተር ካርላይል እመነታ " እንደ ሐኪሞቹ ገልጾ ለመናገር ቢያስብ ልቡ አልቻለም መናገር እንዴሌለበት የሚገፋፋ ከባድ ስሜት ተናነቀው "

« እንደማታታልለኝ አምንሃለሁ » አለችው "

« ወዶዚያው ናቸው ብዬ እሠጋለሁ " የሚተርፉ አይመስሎም»

ብድግ አለች » በመጣባት ድንገተኛ ፍራት ተወርውራ ክንዱን ጭምድድ አድርጋ ያዘችውና ዐውቀህ ነው ሙቷል » አለችው "

« የለም አላታለልኩሽም ሳቤላ ገና አልሞቱም » ግን ብዙ ላይቆዩ ይችላሉ »

ከሶፋው መከዳ ድፍት አለች » «አባቴ ... እስከ ዘለዓለሙ ከኔ ጋር ልንለያይ ላንተያይ ! ለዘለዓለም !

ሚስተር ካርላይል... ለአንድ ደቂቃ ልየው! ልሰናበተው
እባክህን አንድ ጊዜ ልየው»
👍24
« እስኪ ፊት እኔ ልያቸው " አንቺ ግን ከዚህ ዝም ብለሽ ቆይ ! እንዳትመጪ»ብሏት ነገሩ ተስፋ እንደሌለው እያወቀ ወጣና ወደ በሽተኛው ክፍል ገብቶ ወዲያው
ተመለሰ "

« አበቃ » አላት ለሚስዝ ሜሰን በሹክታ ከኮሪደሩ አገኛትና ሚስተር ዌይን ራይት ይፈልግሻል

« ቶሎ ተመለስክሳ ? » አለችው ሳቤላ « ልግባ ? »

ተቀመጠና እጅዋን ያዛት » «አንቺን ማጽናናት ብችል ደስ ይለኝ ነበር» አላት ጥልቅ በሆነ ስሜት ሲቃ እየተናነቀው
« ንገረኝ » አለችው እየቃተተች » «ኧረ ጉዴን ንገረኝ »

« እኔም ከመራራው መርዶ በቀር የምነግርሽ የለኝም » የተወደድሽ እመቤት ሳቤላ ... ብርታቱን ይስጥሽ » አላት "

ጢስ የመሰለው ንጋት ተመልሶ በዓለም ላይ ወግግ አለ " በሕይወት ጉዞ ላይ አዲስ ውጣ ውረድ አዲስ ሸብ ረብ ተጀመረ የዊልያም ቬን ነፍስ ግን ከዓለም ለዘለዓለም ተለየች - ወደ ሰማይ መጠቀች።"....

💫ይቀጥላል💫
👍10😱1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሶስት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


....እኔ እንደተሰማኝ ሊሰማቸው የማይገባ ስለሆነ መንትዮቹ እንዴት እንደሆኑ ለማወቅ ዞሬ ተመለከትኩ።አንድ መልካም ሰው ወደ ወጥ ቤት ወስዷቸው
ከመተኛታቸው በፊት ቀለል ያለ ምግብ እያዘጋጀላቸው ነበር። አይኔ ከክሪስቶፈር አይን ጋር ተጋጨ ልክ እንደኔ በዚህ ቅዠት ውስጥ እንደተያዘ ያስታውቃል። ፊቱ የገረጣና የደነገጠ ይመስላል። አይኖቹ ሀዘን አጥልቶባቸው ጠቁረዋል።

አንደኛው ፖሊስ ወደ መኪናው ተመልሶ የታሰሩ ነገሮች ይዞ መጣና በጥንቃቄ ጠረጴዛ ላይ ዘረገፋቸው አባቴ ኪሱ ውስጥ የሚያስቀምጣቸው ነገሮች
ነበሩ እናታችን ለገና በስጦታ የሰጠችው የኪስ ቦርሳ፣ የማስታወሻ ደብተሩ፣ የእጁን ሰዓትና የጋብቻ ቀለበቱን ስመለከት በቆምኩበት ደረቅኩ። ሁሉም ነገር ጠቁሯል። በጭስና በእሳት አርሯል።

በመጨረሻ የመጡት የመኪናው የእቃ ማስቀመጫ ሲመታ ከሻንጣው ውስጥ የተበተኑት የአባቴ ልብሶችና ለኮሪና ኬሪ የተገዙላቸው ባለቀለም አሻንጉሊቶች ነበሩ። ባለ ቀይ ፊቱ ፖሊስ ሲናገር ሁሉም የተገኙት መንገዱ ላይ ተበትነው ነበር።

እነዚያን ልብሶች አውቃቸዋለሁ: እነዚያን ሸሚዞች፣ ከረባቶችና ካልሲዎች...ሁሉንም አውቃቸዋለሁ ከልብሶቹ መሀል ላለፈው ልደቱ ሰጥቼው የነበረው ከረባት ነበረበት።

“አስከሬኑ የእሱ መሆኑን የሚለይልን አንድ ሰው እንፈልጋለን፡” አለ ፖሊሱ።

አሁን በእርግጠኝነት አወቅኩ እውነት ነው: አባታችን… በራሱ የልደት ቀን እንኳን ሳይቀር ስጦታ ይዞልን የሚመጣው አባታችን ሞቷል!!

ከዚያ ክፍል ሮጬ ወጣሁ! ልቤን ከሚያደሙትና እስከዛሬ ከተሰሙኝ ህመሞች ሁሉ በከፋ ሁኔታ ካሳመሙኝ ከተዘረገፉት ዕቃዎች ሸሽቼ ሮጥኩ። ከቤት
ወጥቼ ከጀርባ ያለው የአትክልት ቦታ ሄድኩና አሮጌውን የማፕል ዛፍ በጡጫ ቀጠቀጥኩት እስኪያመኝና እጄ ደም በደም እስኪሆን ድረስ ቀጠቀጥኩት።
ከዚያ ሳሩ ላይ ዘጭ ብዬ ወድቄ አምርሬ አነባሁ በህይወት መቆየት ይገባው ስለነበረው አባቴ አለቀስኩ። ያለ እርሱ ህይወታችንን ለምንገፋው ለእኛ አነባሁ እናም ምን ያህል መልካም አባት እንደሆነና እንደነበረ የማወቅ
እድል ላላገኙት መንታ እህትና ወንድሜ አለቀስኩ። እምባዬ አልቆ አይኖቼ አብጠው ደም መስለው እየቆጠቆጡኝ ባለሁበት ቅፅበት የእግር ኮቴ ወደኔ ሲመጣ ሰማሁ። እናቴ ነበረች:

ሳሩ ላይ አጠገቤ ተቀመጠችና እጄን በእጆቿ ያዘች ሰማዩ ላይ ግማሽ ጨረቃ በሚሊየን በሚቆጠሩ ከዋክብት ታጅባ ወጥታለች አዲስ ከተወለደው ከፀደዩ ሽታ ጋር ንፋሱ ደስ የሚል ነበር። በመካከላችን የነበረው ዝምታ ማብቂያ የሌለው በሚመስል ሁኔታ ለረጅም ደቂቃዎች ቀጠለ፡ በመጨረሻ እናቴ “ካቲ አባትሽ ከላይ ከሰማይ ሆኖ እያየሽ ነው፡ ጎበዝ እንድትሆኚ እንደሚፈልግ
ታውቂያለሽ አይደል?” አለችኝ።

“አልሞተም እማዬ!” ላለማመን ፈለግኩ።

“እዚህ ቦታ ብዙ ቆይተሻል። ምናልባት አላስተዋልሽ ይሆናል እንጂ አራት ሰዓት ሆኗል። አንድ ሰው የአባትሽን አስከሬን መለየት ነበረበት ለዚህ ደግሞ
ጂም ጆንስተን እንደሚሄድ ነገሮኝ ነበር። እኔ ግን ራሴ ማየት ስፈለግኩ ሄጄ አየሁት። አየሽ እኔም ለማመን ከብዶኝ ነበር አባትሽ ሞቷል ካቲ። ክሪስቶፈር አልጋው ላይ ሆኖ እያለቀሰ ነው፡ መንትዮቹ ተኝተዋል። መሞት
ምን እንደሆነ ገና በደንብ አልገባቸውም:”

አቅፋኝ ጭንቅላቴን ትከሻዋ ላይ አሳረፈችው።

ከዚያ ተነሳችና ከእሷ ጋር እንድነሳ ክንዷን ወገቤ ላይ አድርጋ እየጎተተችኝ “ነይ… እንደዚህ አዝነሽ ብቻሽን መሆንሽ ጥሩ አይደለም: ሀዘንሽን ውስጥሽ
ከምትቀብሪው ይልቅ ሀዘንሽን ከሚጋሩሽ ሰዎች ጋር መሆን የተሻለ ነው:"

ይህንን ስትነግረኝ አንዲት ዘለላ እምባ እንኳን አይኖቿ ላይ አልነበረም ነገር ግን በውስጧ እያለቀሰችና እየጮኸች እንደሆነ ከድምጽዋና አይኖቿ ላይ
ከሚታየው ጥልቅ ሀዘን መናገር ይቻላል።

ከአባታችን ሞት ጋር ተያይዞ ቀኖቻችንን ቅዠት ያጠላባቸው ጀመር᎓ እናቴን ያለማቋረጥ አተኩሬ እያየኋት ለእንደዚህ አይነት ነገር አስቀድማ ልታዘጋጀን
ይገባ እንደነበር አሰብኩ የሆነ ነገር በሞት ማጣት ምን እንደሚመስል
እንድናውቅ የራሳችን የሆነ ውሻ ወይም ድመት እንዲኖረን ፈቅዳልን
አታውቅም ያንን ብታደርግ ኖሮ ድንገት ሲሞቱብን ሞት ምን ማለት
እንደሆነ በጥቂቱም ቢሆን ማወቅ እንችል የነበረ ይመስለኛል የሆነ ሰው፣ትልቅ ስው፣ መልከ መልካሞችም፣ ወጣቶችም፣ በጣም አስፈላጊ ሰዎችም
ሊሞቱ እንደሚችሉ ሊያስጠነቅቀን ይገባ ነበር።

ዕጣ ፋንታ በሆነ ቀዳዳ ውስጥ እየጎተታት ቀጭንና ስስ ላደረጋት እናት እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር ሊባል ይችላል? መናገር ወይም መብላት ወይም ፀጉሯን ማበጠር ወይም ሳጥኗን የሞሉትን የሚያማምሩ ልብሶች መልበስ ለማትፈልግ ሴት እንዴት እንዲህ አይነት ነገር በግልፅ መናገር
ይቻላል? ሌላው ቀርቶ እኛ የሚያስፈልገንን ነገር እንኳ ማየት አትችልም ነበር። ደጋግ የጎረቤቶቻችን ሴቶች መጥተው የሚወስዱን መሆናቸው
ቤታቸው ያዘጋጁትን ምግብ የሚያመጡልን መሆኑ መልካም ሆኖልን ነበር ቤታችንም በአበቦችና ጎረቤቶች ሰርተው በሚያመጡት ምግብ የተሞላ ነበር።

አባታችንን የሚወዱት፣ የሚያደንቁትና የሚያከብሩት ብዙ ሰዎች ሁለ ይመጡ ስለነበር አባታችን ይህን ያህል ታዋቂ በመሆኑ ተገረምኩ። ሆኖም
የሆነ ሰው እንዴት እንደሞተ ጠይቆ ስንት ጥቅም የሌለው መሞት ያለበት ለማህበረሰቡ ሸክም የሆነ ሰው እያለ እንደሱ አይነት ወጣት መሞቱ አሳዛኝ
ነገር እንደሆነ በተናገረ ቁጥር ሞቱ ይበልጥ ያሳምመኝ ነበር።

ከሰማኋቸው ነገሮች የተነሳ ዕጣ ፋንታ የሚባለው ነገር ክፉና ለሚወደድና ለሚፈለግ ሰው እንኳን ክብር የሌለው አሰቃቂ ነገር እንደሆነ አወቅኩ።

የፀደይ ቀናት እያለፉ ወደ በጋ ተጠጋ። ምንም ያህል ለቅሶውን ለማስተናገድ ቢሞhርም ሀዘን እየደበዘዘ የሚመጣበት የራሱ መንገድ አለው። እናም
በህይወት ውስጥ በጣም ተወዳጅ የነበረ ሰው ሳይቀር የደበዘዘና ከትኩረታችን ወጣ ያለ ጥላ እየሆነ ይመጣል።

አንድ ቀን እናታችን ፈገግ ማለት እንዴት እንደሆነ የረሳች በሚመስል ሁኔታ ፊቷ ተከፍቶ ተቀምጣ ነበር ሀዘኗን ላስረሳት በመጣር “እማዬ… አባታችን
በህይወት እንዳለ ቁጠሪውና ለሌላ የስራ ጉዞ እንደሄደና እንደሚመለስ፣ ከዚያ "
በበሩ ገብቶ ልክ ድሮ እንደሚያደርገው ተጣርቶ “የሚወደኝ መጥቶ ይሳመኝ
ሲል አይታይሽም? እማዬ ለሁላችንም እንደዚህ ብናስብ ይሻለናል ሁላችንም የሆነ እኛ የማናየው ቦታ እየኖረ እንደሆነና ድንገት እንደሚመጣ መጠበቅ እንችላለን" አልኳት።

“አይሆንም ካቲ፣ እውነቱን መቀበል አለብሽ፡ በማስመሰል ውስጥ መደበቂያ መፈለግ የለብሽም ሰምተሸኛል? አባትሽ ሞቷል። ነፍሱ ወደ መንግስተሰማይ ሄዳለች እናም በአንቺ እድሜ ማንም ሰው ከሰማይ ተመልሶ እንደማይመጣ
መረዳት አለብሽ፡ እኛ ካለእሱ የምንችለውን እናደርጋለን፡ ያ ማለት ግን እውነታን ባለመጋፈጥ ማምለጥ ማለት አይደለም” አለችኝ በቁጣ።

ከዚያ ከተቀመጠችበት ወንበር ላይ ተነስታ ቁርስ ለመስራት ከማቀዝቀዣው ውስጥ የሆኑ ነገሮች ስታወጣ አየኋት።
እንደገና እንዳትቆጣኝ እየተጠነቀቅኩ “እማዬ ካለሱ የምትችይ ይመስልሻል?
አልኳት።

“በህይወት እንድንቆይ የቻልኩትን ሁሉ አደርጋለሁ” አለች ስሜት በማይሰጥ ድምፅ።

“አሁን እንደ ወይዘሮ ጆንስተን ስራ መሄድ አለብሽ ማለት ነው?”
👍345👏3👎1
“ምናልባት አዎ። ካቲ… ህይወት ብዙ አስገራሚ ነገሮች አሏት አንዳንዶቹ ደስ አይሉም፤ ዋናው ነገር ግን ለአስራ ሁለት አመታት አካባቢ ሁልጊዜ አንቺ እጅግ ልዩ እንደሆንሽ የሚያስብ አባት ስለነበረሽ የተባረክሽ ልጅ እንደሆንሽ አስታውሺ።”

ከፍሪጁ እቃ እያወጣች ዞር ብላ ተመለከተችኝ። “ካቲ ከዚህ በፊት ነግሬሽ የማላውቀውን አንድ ነገር አሁን እነግርሻለሁ። በመልክ እኔ አንቺ እድሜ ላይ እያለሁ የምመስለውን ነው የምትመስይው! በባህሪሽ ግን እኔን አትመስይም፡ አንቺ በጣም ቁጡና ቆራጥ ነሽ፤ አባትሽ እናቱን እንደምትመስይ ይናገር
ነበር። እሱም እናቱን በጣም ይወድ ነበር:”

“ሁሉም ሰው እናቱን ይወድ የለ እንዴ?”

“አይ እንድትወጃቸው ስለማይፈልጉ ልትወጃቸው የማትችይ አንዳንድ እናቶች
አሉ።” አለች በሚያስገርም አገላለጽ። ከዚያ ወደኔ ዞራ አቀፈችኝና “የምወድሽ ካቲ አንቺና አባትሽ በጣም ልዩና የቀረበ ግንኙነት ነበራችሁ: በዚያ ምክንያት ከክሪስቶፈርና ከመንትዮቹ በተለየ በጣም ናፍቀሽዋል ብዬ እገምታለሁ:”

ትከሻዋን ተደግፌ አነባሁ። እሱን ስለወሰደብኝ እግዚአብሔርን እጠላዋለሁ! እስኪያረጅ መኖር ነበረበት። እኔ ዳንሰኛ፣ ክሪስቶፈር ደግሞ ዶክተር ሲሆን እሱ አይኖርም። እሱ ስለሄደ አሁን ሁሉም ነገር ምንም ስሜት አይሰጥም ስል ተነፋረቅኩ።

“አንዳንድ ጊዜ ሞት እንደምታስቢው መጥፎ አይደለም በጭንቅላትሸ ውስጥ አባትሽ አያረጅም ሁልጊዜም ወጣት ሆኖ ይቆያል። አንቺም ሁልጊዜ
የምታስታውሺው ወጣት፣ መልከመልካምና ጠንካራ እንደሆነ ነው። ከዚህ በላይ አታልቅሺ ካቲ። አባትሽ ሁልጊዜ ይለው እንደነበረ ለሁሉም ነገር ምክንያት፣ ለሁሉም ችግር መፍትሄ አለው ከዚህ በመነሳት እኔም ጥሩ ነው
ብዬ የማስበውን ለማድረግ በጣም እየሞከርኩ ነው" አለች:

በሀዘንና በማጣት ውስጥ የተሰበሰብን አራት ልጆች ነበርን። ጓሮ ያለው አትክልት ቦታ ውስጥ እንጫወታለን፡፡ ህይወት ድንገት በአስከፊና ድንገተኛ ሁኔታ እንደሚለወጥና “ጓሮ” እና “የአትክልት ቦታ" የሚባሉት ነገሮች
አንድ ቀን ለእኛ የመንግስተ ሰማይ ስያሜ እንደሚሆኑ ባለማወቃችን ከፀሀዩዋ ብርሀን ውስጥ መፅናናትን ለማግኘት እየሞከርን ነበር።

ከአባታችን ቀብር በኋላ ባለ አንድ ከሰዓት በኋላ እኔ፣ ክሪስቶፈርና መንታዎቹ ጓሮ እየተጫወትን ነው ኮሪና ኬሪ መልካቸው የማይመሳሰል መንትዮች
ቢሆኑም ልክ እንደ አንድ ሆነው እየተጫወቱ ነው አንዳቸው በሌላኛቸ ይረካሉ አንዳቸው ለአንዳቸው እስካሉ ድረስ በቂ ነበር።

እናታችን ሳትጠራን የእራት ሰዓት አለፈ ቀስ እያለ ምግብ ከቤታችን ሊጠፋ እንደሚችል ሁሉ መፍራት ጀምረናል። ስለዚህ ለእራት ባንጠራም እንኳን የመንትዮቹን እጆች ይዘን ወደ ቤት ገባን እናታችን የአባታችን ትልቅ ጠረጴዛ
ኋላ ተቀምጣ አስቸጋሪ የሆነባት የሚመስለውን ደብዳቤ እየፃፈች አገኘናት::ኮስተር እንዳለች ለረጅም ደቂቃዎች ትፅፍና ቆም አድርጋ ጭንቅላቷን ቀና በማድረግ ባዶ ግድግዳ ላይ ታፈጣለች።

“እማዬ አስራ ሁለት ሰዓት ሊሆን ነው: መንትዮቹ እርቧቸዋል” አልኳት።

“መጣሁ… መጣሁ” አለች እናቴ ለመምጣት በተዘጋጀ አይነት። “ቨርጂኒያ ለሚኖሩት አያቶቻችሁ ደብዳቤ እየፃፍኩ ነው፡ ጎረቤቶቻችን ለሳምንት
የሚበቃ ምግብ አምጥተውልናል። አንደኛውን ወደ ማሞቂያው ማስገባት ትችያለሽ ካቲ።" አለችኝ
ማዘጋጀቱ ላይ የተሳተፍኩበት የመጀመሪያ ምግብ ነበር እናቴ ልታግዘኝ ስትመጣ ጠረጴዛው ተስተካክሎ፣ ምግቡ ሞቆና ወተቱ ተቀድቶ ነበር።

አባታችን ከሞተ ጀምሮ እናታችን ብዙ ጊዜ ደብዳቤ ትፅፋለች። በዚያ ላይ አብዝታ የምትሄድበት ቦታ ስለሚኖራት እኛን ጎረቤት ትተወን ነበር። ሲመሽ ደግሞ የአባታችን ጠረጴዛ ጋር ትቀመጥና አረንጓዴ የማስታወሻ ደብተር
አውጥታ የተከመሩ ደረሰኞች ታገላብጣለች ሁሉም ነገር ምንም ደስ የሚል ስሜት አይሰጥም: አሁን አሁን አብዛኛውን ጊዜ መንትዮቹን የምናጥበው፣
የሌሊት ልብሶቻቸውን የምናለብሰውና ወደመኝታቸው የምንወስደው እኔና ወንድሜ ነን፡ ከዚያ ክሪስቶፈር ወደ ክፍሉ ሄዶ ለማጥናት ሲጣደፍ ደግሞ እንደገና ደስታ ወደ አይኖቼ የመመለሻ መንገድ ለመፈለግ ወደ እናቴ እሄዳለሁ።

ከጥቂት ሳምንታት በኋላ እናቴ ለወላጆቿ ለፃፈቻቸው ደብዳቤዎች ምላሽ መጣላት። ፖስታውን እንዳገኘች ሁላችንንም ጓሮ ከምንጫወትበት ጠራችንና
ሳሎን ሶፋ ላይ እንድንቀመጥ አደረገች። እናቴ ወፍራሙን ፖስታ ሳትከፍተው ገና ማልቀስ ጀመረች....

ይቀጥላል
👍331👎1
#ሳቤላ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


በማውንት እስቨርን ኧርል ዕረፍትና ቀብር መካከል የነበረው ጋዜ ውስጥ ሁኔታዎች ቶሎ ቶሎ ተከታተሉ " አንባቢ ከነዚህ ሁኔታዎች አንዱን ከእውነተኛ
ሕይወት ጋር የማይዛመድና መሠረት የሌለው ነገር ነው ይል ይሆናል ካለ ስሕተት ነው " ሁኔታዎቹ ደርሰው ታይተዋል "

ዊልያም ቬን ዓርብ ጥዋት ንጋት ላይ ዐረፈ " ወሬው ወዲያው ተዛመተ ትልቅ ሰው ሲሞት ምን ጊዜም ይኸው ነው የዚያኑለት ለንደን ላይ ተሰማ " ስለዚ ሟቹ በሕይወት ቢኖር ኖሮ «መንቻኮች» ይላቸው የነበሩት ብዙ ሰዎች ኢስት ሊንን ለመክበብ ቅዳሜ ማለዳ ደረሱ የጥቂት ገንዘብ ባለዕዳዎችም የብዙ ገንዘብ ባለዕዳዎችም ነበሩባቸው " ከአምስት እስከ ዐሥር ፓውንድ የሚጠይቁ ' ከአምስት እስከ አሥር ሺ የሚፈልጉም ሁሉ ነበሩባቸው አንዳንዶቹ ሰላማዊ ሰዎች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ትዕግሥት የሌላቸው አንዳንዶቹ ለፍላፊዎች ሥነ ሥርዓት
የሌላቸውና ቁጡዎች ሌሎች ደግሞ እዚያው ላይ እርምጃ ለመውሰድ አንዳንዶቹ አስከሬኑን በቁጥጥራቸው ሥር ለማድረግ የመጡ ነበሩ።

የመጨረሻው ድርጊት በዘዴ ነበር የተፈጸመው " ሁለት አፍንጫ ቈልማማ ሰዎች ከግርግሩና ከሽብሩ ሹልክ ብለው በጓሮ በር አለፉና ሲደውሉ አንዲት የማድ ቤት ሠራተኛ ከፈተችላቸው።

« የሬሳው ሳጥን ገና አልመጣም እንዴ ? » አሉ
« የሬሳ ሳጥን ? የለም ሚስተር ጆንስ ከሦስት በፊት እመጣለሁ አላለም "አሁን ገና ሁለት ሰዓት እንኳን አልሞላም » አለቻቸው።

« እሱስ አሁን ይዶርሳል እመንገድ ላይ ነው " ስለዚህ ወደ ክቡርነታቸው ክፍል አቅንተን አስከሬኑን እያዘጋጀን እንቆያለን » አሏት ሠራተኛዋ የቢት አዛዡን ጠርታ « ከቀብር አስፈጻሚው ከጆንስ ዘንድ የመጡ ሁለት ሰዎች ሳጥኑ እስኪደርስ ከላይ ወጥው ሬሳውን አሰናድተው ለመቆየት ይፈልጋሉ » አለችው ።

አዛዡም ሰዎቹን እየመራ ወስዶ አስከሬኑ ከነበረበት ክፍል ካስገባቸው በኋላ
« ይበቃሃል » አሉት አብሮ ለመግባት ሲል «እዚህ በመቆየት አናስቸግርህም » ሲሉት ምንም ሳይጠረጥር ወጣላቸው ። እነሱም ክፍሉን ዘግተው ከሬሳው ግራና
ቀኝ ተቀምጠው ሲያበቁ ጥያቄያቸው ካልተሟላ በቀር ሬሳውን እንዶማይለቁ አስ
ታወቁ ከአንድ ሰዓት በኋላ ( ሳቤላ ከክፍሏ ወጥታ ምንም ድምፅ ሳታሰማ ያባቷ ሬሳ ካረፈበት ክፍል ስትገባ ሁለት የማይታወቁና የሚቀፉ ሰዎች ባጠገቡ ተቀምጠው ስታገኛቸው ጊዜ ክው ብላ ደነገጠች "

መጀመሪያ ነገሩ ተገቢ ባይሆንም እንኳን'ለወሬ የቸኮሉና ሁኔታውን ለማየት የጓጉ የመንደር ሰዎች መስለዋት ነበር " ቢሆንም ትክክለኛውን ነገር ከነሱ አግኝታ ለማረጋገጥ ፈለገችና « እዚህ የምትፈልጉት ነገር አላችሁ ? » አለቻቸው "

« ስለ ጠየቅሺን እናመሰግናለን " እመቤት ) ደኅና ነን ምንም አትቸገሪ » አሏት " ሥራቸውም አነጋገራቸውም ፍጹም ያልተለመደና ያልተጠበቀ ሆነባት
ጨነቃት » ይህን ተናግረው ቢደነግጡም የወግ ነበር ከዚያ ገብተው ቁጭ ለማለት መብትና ሥልጣን ያገኙ ይመስል ተደላድለው እንደ ተቀመጡ ዝም አሉ።

« እዚሀ ምን አመጣችሁ ? ምን እያደረጋችሁ ነው ? » አለቻቸው።

« እንደ መሰለን አንች ልጃቸው ነሽ ብንነግርሺም ግድ የለንም » አላት
አንደኛው በግራ አውራ ጣቱ በስተኋላው ወደነበረው አስከሬን የኋሊት እያመለከተ"
« ባጠገባቸው ሌላ የቅርብ ዘመድ እንዶሌላቸው ስምተናል አሁን እኛ እዚህ የመጣነው በጣም ብዙ ዕዳ ስለ ነበረባቸው ገንዘባቸውን ያላገኙ አበዳሪዎቻቸው መሞታቸውን ሲሰሙ ሬሳውን በዕዳ መያዣ እንድናስከብር ቀጥረው ልከውን ነው » አላት

ድንጋጤና ፍርሃት በአስጨናቂው መከራዋ ላይ ተደምረው የምትለውን አስጠፋት » እንደዚያ ያለ ጉድ ሰምታ አታውቅም » ብታውቅም አታምንም ነበር "
ሬሳን በእስረኝነት መያዝ ? ምን ለማድረግ » ቁና ቁና እየተነፈሰች ከክፍሉ ወጥታ ስትወርድ ሚሲዝ ሜዞንን ከደረጃው ስታልፍ አኘቻትና በሁለት እጆቿ ጥምጥም
አድርጋ ይዛ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች ራሷን መቈጣጠር አልቻለችም አስተካክላ መናገርም አልሆነላትም።

« እነዚያ ሰዎች እዚያ ! » አለች እየቃተተች "
« የምን ሰዎች ናቸው . . . የኔ እመቤት ? »
« ኧረ እኔስ እንጃ ! ኧረ እኔስ እንጃ ! ከዚያ የሚወጡም አልመሰሉኝም አባባን በዕዳ ይዘነዋል ይላሉ። የቤት ጠባቂዋም ነገሩ አስገርሟት ዝም ብላ ከቆየች በኋላ ሁኔታውን በዐይኗ ለማየት ሔደች " ሳቤላ ግን ከዚያ ለመነቃነቅ ፈራች ሰውነቷ ዛለባት ከደረጃው መደገፊያዎች ላይ ተደግፋ ብቻዋን ቀረች ሁኔታው ደስ
የማይል ሌላ ብጥብጥ በምድር ቤት በኩል ሰማች » ማንነታቸው ያልታወቁ እንዲያውም ከማያገባቸው ገብተው ነገር የሚያዳንቁ ሰዎች ከምድር ቤቱ አዳራሽ ዘልቀው ሲያማርሩ ' ሲፎክሩ ሲደነፉ ተሰማት ፍራቷ እየጨመረ መጣ " በደንብ ለማዳመጥ ትንፋሿን ያዝ አደረገች።

« ይህች ልጅ ከናንተ ፊት ብትቀርብ ጥቅማችሁ ምንድነው ? እሷ ስለ አባቷ
ጉዳዮች ምን ታውቃለች ? አሁን ለራሷ በከባድ ኀዘን ላይ እያለች በተጨማሪ ባታስጨንቋት ምናለበት ? » እያለ የቤት አዛዡ ሲያነጋግራቸው ከጆሮዋ ገባ "

« የፈለገው ይምጣ እሷን ማየት አለብኝ » ይላል አንድ ችክ ያለ ድምፅ «እዚሀ ድረስ ወርዳ አንድ ሁለት ጥያቄዎች ለመመለስ ክብሯ የሚዋረድ ከሆነ
ካለችበት ድረስ በግድ እገባለሁ " ገንዘባችን የተጭበረበረብን ምስኪኖች ከዚች ልጅ በቀር ልናነጋግረው የምንችል ማንም እንደሌለ እየተነገረን ከነሷው ደግሞ አታስቸግሯት ለምን ትሉናላችሁ ? ገንዘባችንን ለማጫረስ አባቷን ስትረዳ ግን አልተቸገረችም " እዚህ ድረስ መጥታ ልታነጋግረን ካልፈቀደች የሴት ወይዘሮ ስሜትም
ክብርም የላትም »

ስሜቷን አምቃ ይዛ ደረጃዎቹን ወረዶችና የቤቱን አዛዥ ወደሷ ጠራችው "

« ምንድነው ይህ ሁሉ ሽብር ? ማወቅ እፈልጋለሁ " »

« ተይ እመቤቴ አትሒጂ " ሥነ ሥርዓት የላቸውም ያንቺ ከመኻከላቸው መገኘት የሚያስታግሣቸው አይደሉም ። እኔ ለሚስተር ካርላይል ስለ ላክሁባቸው አሁን ይመጣሉ ስለዚህ አንቺ እነዚህ ሰዎች ሳያዩሽ ግቢ » አላት።

« ግን አባባ ከነዚህ ሁሉ ገንዘብ ወስዷል ማለት ነው? »

« አዎን ሳይወስዱ የቀሩ አይመስለኝም » አላት።

ሳቤላ ቀጥታ ወደነሱ ሔዴች ከመተላለፊያው ተበታትነው የነበሩትን 0ልፋ ብዙዎቹ ተሰብስበው ከቆሙበት ጩኸትና ጫጫታ ከበዛበት ከምግብ ቤት
ገባች " ሁሉም ሲያዩዋት ጸጥ አሉ የሚያምር የጧት ልብስ ለብሳ፡ ቆንጆው ፊቷ በተዘናፈለው ጸጉሯ ተጋርዶ ሲያዩዋት በዚያ ሁኔታቸው ከነሱ ጋር መልስ ልትለዋወጥ
ቀርቶ ጕዳዬም ሊገባት የማይችል ምንም ነግር የማታውቅ ገና ልጅ አድርገው ገመቷት " በደላቸውን የብሶታቸውን ያሀል በመዘርዘር ፋንታ ሁሉም ጸጥ አሉ።

« አንድ ሰው እኔን ለማየት እንደሚፈልግ ሲናገር ስምቸ ነበር» አለች ንግግሯ እየተቆራረጠ « ከኔ ምን ትፈልጋላችሁ? » ሁሉም ረጋ ባለ አነጋግር የየራሱን ጉዳይ ሰነዘረ ። እስኪያጥወለሡላት ድረስ በጥምና አዳመጠቻቸው " ብዙ የከፍተኛ ገንዘብ ጥያቄዎች ቀረቡ ። በተወሰነ ጊዜ
የሚመለስ የብድር ሰነዶች ባለዕዳነት መተማመኛዎች የጊዜ ገደባቸው ያለፈና ያልደረሰ ሒሳቦች ፡ በጠቅላላው ለቤት ጣጣ ለአሽከች የደንብ ልብስ ለውጭ ከትልቅ እስከ ትንሽ ይህ ነው የማይባል ብዙ ብዙ ዕዳ
አሽከሮች ደሞዝ ተዘረዘረ ።
👍21🔥1👏1😁1
ሳቤላ የምትሰጣቸው ተስፋ የምትጠይቃቸው ይቅርታ : የምትመልስላቸው አልነበራትም ዐይኖቿን ከአንዱ ወደሌላው አመልካች እያንከራተተች
በኀዘን እንደ ተሸማቀቀች ዝም አለች።

« ሰማሽ እመቤት . ... » አለ አንድ ሲያዬት ከበድ ያለ ሰው ፡ « እኛ እዚህ ድረስ መጥተንም ባላስቸገርንሽ ነበር ዕረፍታቸውን እንደ ሰማን ብዙዎቻችን
ወደ ወኪሎቻቸው ወደ ዋርበርተንና ዌር ብንሔድ ምናልት ከቤት ዕቃ ካልሆነ በቀር አንዲት ሺልንግ እንኳን እንደማናገኝ ነገሩን እኔም ቀድሞ የመጣ ቀድሞ
ያግኛል ነውና ጎህ ሲቀድ መጥቼ ዕቃውን ያዝኩ … »

« አልሰሜ ካንተ በፊት የተያዘውን» አለ በአፍንጫው ቆልማማነት የነዚያ አስከሬኑን የያዙት ሰዎች ወንድም የመስለ አንድ ስውዬ
« ግን ያስ ቢሆን ይህ ዕቃ እኛ ከምንጠይቀው ገንዘብ ጋር ብናስተያየው ከምናችን ይደርሳል ? በውነቱ አንድ ቅምጫና ውሃ ከቴምዝ ወንዝ ቢቀዳ ወይ ቢጨመር ምን ያህል ይለውጠዋል ?የኛም እንደዚሁ ነው » አለ።

« አሁን ምን ማድረግ እችላለሁ?» አለች ሳቤላ እየተንቀጠቀጠች » « ምን እንዳደርግላችሁ ትፈልጋላችሁ ? የምሰጣችሁ ገንዘብ የለኝም " እኔ . . . »

« የለም እመቤት » አለ አንድ ግርጥት ያለና የረጋ ሰውዬ
« የሚባለው እውነት ከሆነ አንቺም ከኛ የበለጠ ጉዳት ደርሶብሻል ያንገት ማስገቢያ ጣራና የኔ ነው
የምትይው አንድ ቤት እንኳን እንደሌለሽ ይነገራል »

«ሰውየው ወሮበላ ነበር » አለ አንድ የተናደደ ድምፅ« ብዙ ሺ ሕዝብ አቀለጠ።

በዚህ መኻከል ሚስተር ካርላይል ደረሰ በጭንቀት የተለዋወጠው ፊቷንና ሲንቀጠቀጡ የነበሩት እጆን ዐይቶ የመጨረሻውን ተናጋሪ አቋረጠው።

« ምንድነው ይኸ ሁሎ ? ምን ፈልጋችሁ ነው ? » አላቸው በሥልጣን አነጋገር "
«ጌታዬ . . . የሟቹ ወዳጅ ከሆንክ የምንፈልገውን ማወቅ ነበረብህ " እኛ ገንዘባችን እንዲከፈለን ብቻ ነው የምንፈልገው »

« ታድያ ወደ ዋርበርተንና ዌር ሒዱ እንጂ እዚህ ብትንጋጉ ምን ታግኛላችሁ?»
« እነሱማ ማናችንም ምንም ገንዘብ እንደማናገኝ ነግረውናል»

« እንግዲያውስ ከዚህም ምንም ስለማታገኙ ፡ አሁኑኑ ትወጡ ዘንድ በፍቅር እለምናችኋለሁ »

እነሱ ግን ጥያቄውን እንደማይቀበሉት ነገሩት "

« ይህ ቤት የሎርድ ማውንት እስቨርን ንብረት አይዶለም ። ከሸጡት ሰንብቷል ስለዚህ እናንተም የሌላ ሰው ንብረት በመድፈር ላይ ነው ያላችሁትና እምቢታችሁ ሌላ መዘዝ እንዳያመጣ ላስጠነቅቃችሁ እፈልጋለሁ »

እነሱ ግን እሱ ከሚነግራቸው የበለጠ እንደሚያውቁ በማመን የሱን ንግግር ጊዜ ያለፈበት ማታለያ በመሆኑ እንደማይቀበሉት ነገሩት "

« ስሙኝ ወንድሞቼ. . . ንብረቱ ሲመረመር በግልጽ የሚታወቀውን ነገር ለማለባበስ መሞከር የዋህነት ነው " ይህ ቤትና በውስጡ ያለውንም ንብረት ከሎርድ ማውንት ስቨርን እጅ በሕግ ወደሌላ የተዛወረው ከብዙ ወሮች በፊት ነው እሳቸው ከዚህ የሰነበቱት በባለቤቱ ፈቃድና ስምምነት እንጂ በባለቤትነታቸው
አልነበረም ። ከተጠራጠራችሁ ከወኪሎቻቸው ዘንድ ሔዳችሁ ማረጋገጥ ትችላላችሁ »

« ማን ገዛው ? »

« የዌስት ሊኑ ካርላይል ገዝቶታል " ያም ሰው እኔ ነኝ " ኢስት ሊንን በሕግ ተዋውዬ ገዝቼ ገንዘቡን ባለፌው ሰኔ ወር ነው ጨርሽ የከፈልኩ ” እኔ ራሴ የሕግ ሰው እንደ መሆኔ መጠን ገንዘቤን ያለውል የምበትን አልምሰላችሁ " እሳቸው ከኔ ጋር ተስማምተን ጥቂት ቀኖች ሰንብተው ሊሔዱ ሲሉ በሽታቸው እየተነሣባቸው እስከዛሬ ሰነበቱ” ሰሞኑንም ለመሔድ ሲዘጋጁ ሰንብተው እነሆ ዛሬ ሊነሡ በቀጠሩበት ቀን እንደዚህ ሆኑ " አሁን ይህ ቤት ከፈረሶቹና ከሠረገላው በቀር ከነ
ዕቃው የኔ ነው »

« ወይ ማውንት እስቨርን ! እንዴት ያለው ወሮበላ ኖሯል ? »

« እሳቸው የፈለጋቸውን ዐይነት ሰው ቢሆኑም'እናንተ ልጃቸውን የማስቸገር መብት የላችሁም በተለይ በእንግሊዛዊነቱ የሚኮራ ሰው እንደዚህ ያለውን አስፈሪ
ድርጊት አይፈጽምም ነይ ሳቤላ » አላት እጅዋን ይዞ ሊያስወጣት በማሰብ "

« ጉዳዩን እኔ እከታተለዋለሁ » ሲላት አመነታች » አባቷ የሠራው በደል ተሰማትና ስሜቷን ልትገልጽላቸው ፈለገች " በአካልም በመንፈስም ተጨነቀች ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ እያለ አስቸገራት "

« በጣም አዝናለሁ » አለች በግድ እየተንተባተበችና ዕንባዋም ከቁጥጥሯ ውጭ ዝርግፍግፍ እያለ " « እኔ ይኸን ሁሉ አላውቅም አባቴ የሚሠራውን ሁሉ ነግሮኝ አያውቅም አሁን እንደምስማው ከሆነ ምንም ሀብት የለኝም " ቢኖረኝም በምችለው መጠን እያመጣጠንኩ እከፍላችሁ ነበር " አሁንም ወደፊት ንዘብ ማግኘትከቻልኩ ገንዘባችሁን አከፍላችኋለሁ »

እሷ « ሁሉ » ብላ ስትናገር አባቷ ከነበረበት ዕዳ መጠን ጋር አገናዝባ አልተረዳችውም " ሚስተር ካርላይል ከዚያ ክፍል ይዟት ወጣ " በሩን በሰዎቹ ላይ ዘጋባቸው በኋላ ዕንባዋ ገንፍሎ መጣ " ሕሊናዋን እስክትስት ድሬስ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች »

« በጣም አዝናለሁ እኔ አንደዚህ ያለ ጭቅጭቅ እንደሚደርስብሽ ባውቅ ኖሮ መቸ በቀላሉ ትገኝላቸው ነበር " አሁን ብቻሽን ወደ ፎቅ መውጣት ትችያለሽ ወይስ ሚሲሲስ ሜዞንን ልጥራት?"

« ብቻዬን እወጣለሁ ፍራትና የሆድ ብሶት እንጂ ሕወም የለብኝም ደሞም ጉዱ በዚህ አላበቃም » አለችው እየተንቀጠጠች " " ከላይ ከፎቅ ደግሞ ከአባባ ጋር ሁለት ሰዎች አሉ »

« እላይ አባባ ጋር » ሚስተር ካርይል ግራ ገባው " እሷ ከፌቱ እንደቆመች ከእግር እስከ ራሷ ስትንዘፈዘፍ አያት "

« እኔ ነገሩ ሊገባኝ አልቻለም እንዲያውም አስደነገጠኝ ካባባ አስከሬን አጠገብ ተቀምጠው በቁጥጥራቸው ሥር እንዳደረጉት ይናገራሉ "

« እነዚህን ካስወጣሁ በኋላ» አላት ወደ ምግብ ቤቴ እያመለከተ
« ወደፎቁ እመጣለሁ "

« ሁለት ወመኔዎች » አለች ሳቤላ « ከቀብር አስፈጻሚው የተላኩ በመምሰል አታለው ከገቡ በኋላ አስከሬኑን ይዘው ወርም ቢሆን ይቀመጣል እንጂ የጠየቁትን ገንዘብ እስካላገኙ ድረስ ሬሳውን እንደማይለቁና እንደማያስቀብሩት ተናግረዋል »

ሚስተር ካርላይል በመጀመሪያ ወደ ምግብ ቤት ተመልሶ እነዚያ የተበደሉና የተናደዱ ሰዎች በሟቹ ላይ ያወረዱትን የምሬትና የቁጭት ንግግር በትዕግስት አዳመጠ " ሆኖም ከነገራቸው መልስ የተለየ ተስፋ እንደማያኙ በማወቅና
እንዳላቸውም ንብረቱ በሕጋዊ መንገድ ለሌላ ተዛውሮ ከተገኘ ዕዳው ከማይመከተው ሰው ጋር መጣላት ምንም ፋይዳ እንዴሌለው በመገንዘብ አንድ ባንድ እየወጡ ሔዱ።

እነዚያ አስከሬን አጋችዎች ግን ሊወጡ አልቻሉም " ሚስተር ካርላይል አስከሬኑ ወዶ ነበረበት ክፍል ገብቶ ማንነታቸውንና በምን መብታቸው እንደዚያ ማድረግ እንደቻሉ ጠየቀ መረመረ እንደዚህ ያለ ድፍረት በሕይወቱ ዘመን አይቶ አያውቅም " ብቻ ዱሮ አንድ የቤተ ክህነት ባለሥልጣን የሆነ ሰው እንደዚሁ በከባድ ዕዳ እንደ ተዘፈቀ ሞተና አስከሬኑ ሊቀበር ቤተ ክርስቲያን እንዶ ደረሰ እንደዚሁ ባለዕዳዎች ይዘውት እንደነበር አባቱ ያጫወተውን ያስታውሳል " አሁንም እነዚህ ሰዎች የጠየቁትን ከባድ ገንዘብ ካልተከፈላቸው ሚስተር ቬን ተተኪው የማውንት እስቨርን ኧርል ከካስል ማርሊንግ እስኪደርስ ድረስ ሬሳውን መልቀቅ
እንዶማይችሉ አስታወቁ "....

💫ይቀጥላል💫
👍251😁1
Forwarded from Yared😊 buttons

📌 በሀዘን😔
በደስታ😀
💻 በስራ ቦታ
💺 የእረፍት ጊዜ ለይ

የሚደመጡ ዝማሬዎችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇
👍12
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አራት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


...ሳሎን ሶፋ ላይ እንድንቀመጥ አደረገች። እናቴ ወፍራሙን ፖስታ ሳትከፍተው ገና ማልቀስ ጀመረች ከዚያ በዝግታ የደብዳቤ መክፈቻ አመጣችና በሚንቀጠቀጡ እጆቿ ሦስት ወረቀቶችን ከፖስታ ውስጥ አውጥታ ደጋግማ አነበበቻቸው: እያነበበች እያለ እምባዋ የተቀባችውን ሜካፕ እያበለሻሸ ቀስ እያለ በጉንጮቿ ይወርድ ነበር።

እያየኋት ለስላሳና ማራኪ ገፅታዋ ወዲያው ወደሚያስፈራ ኮስታራነት
እየተቀየረ አፈጠጠችብን፡ ያኔም ቀዝቃዛ ብርድ ታች አከርካሪዬ ድረስ ደርሶ አንቀጠቀጠኝ ከዚያ ልክ ደብዳቤው ላይ ለተፃፈ የሆነ ጥያቄ መልስ የምትሰጥ ይመስል በሚንቀጠቀጡ እጆቿ ወደያዘቻቸው ወረቀቶች እንደገና
ደግሞ ወደ መስኮቱ ተመለከተች

እናታችን እንግዳ የሆነ ፀባይ እያሳየችን በመሆኑ ስለተደናገርን ባልተለመደ ሁኔታ ዝም አልን፡ የእናታችንን ምላስ የቆለፈና አይኖቿን ያደነደነው ባለሶስት ገፅ ደብዳቤ ሳይጨመር እንኳን አባት የሌለበት ቤታችን በበቂ ሁኔታ
አስፈራርቶን ነበር ለምን ይሆን እንደዚህ እንግዳ በሆነ አይን የምትመለከተን?

በመጨረሻ ጉሮሮዋን አፀዳችና በተለመደው ለስላሳና ሞቃት ድምፅ ሳይሆን የእሷ በማይመስል ቀዝቃዛ ድምፅ መናገር ጀመረች: “አያታችሁ በመጨረሻ
ለደብዳቤዬ መልስ ፅፋልኛለች: የፃፍኩላት እነዚያ ሁሉ ደብዳቤዎች ላይ...በቃ ተስማምታለች: ሄደን ከእሷ ጋር እንድንኖር ተስማምታለች” አለች።

መልካሙን ዜና ለመስማት ስንጠብቀው የነበረ በመሆኑ ልንደሰት ይገባን ነበር ግን አልተደሰትንም: እናታችን በድጋሚ ወደዚያ ዝምታዋ ተመለሰችና
እዚያው እንደተቀመጠች እኛ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለች ምን ሆና ነው? የልብስ ማስጫ ገመድ ላይ የተቀመጡ ወፎች የምንመስል አራት እንግዳ ፍጥረታት
አይደለንም፧ የእሷ ልጆች እንደሆንን አታውቅም?
“ክሪስቶፈር፣ ካቲ፣ አስራ አራትና አስራ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ስለሆናችሁ የምለውን ለመረዳት፣ ለመተባበርና እናታችሁን ካለችበት ተስፋ መቁረጥ ለማውጣት በቂ እድሜ ላይ ናችሁ።” መናገሯን ቆም አድርጋ ጣቷን ጉሮሮዋ
ላይ አድረገችና በጭንቀት በከባዱ ተነፈሰች: ለማልቀስ የደረሰች ትመስላለች
ባል የሌላት ምስኪኗ እናቴ በጣም፣ እጅግ በጣም አሳዘነችኝ፡፡

“እማዬ ሁሉም መልካም ነው? አልኳት።

“አዎ ውዴ ሁሉ መልካም” ብላ ፈገግ ለማለት ሞከረች: “ነፍሱን ይማረውና አባትሽ ረጅም እድሜ እንደሚኖርና በቂ የሆነ ንብረት እንደሚያጠራቅም ያስብ ነበር፡ ገንዘብ እንዴት መስራት እንደሚቻል ከሚያውቁ ሰዎች መሀል ስለመጣ እድሜ ቢሰጠው ኖሮ ያቀደውን በትክክል እንደሚፈፅም ምንም
ጥርጣሬ አልነበረኝም ሰዎች ሁልጊዜ መጥፎ ነገሮች ሌሎች ሰዎች ላይ እንጂ እነርሱ ላይ እንደማይደርስ አድርገው የሚያምኑበት መንገድ አላቸው
አደጋዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አንገምትም። በወጣትነት መሞት እንዳለ አንጠብቅም አባታችሁና እኔ አብረን እንደምናረጅ እናስብ ነበር። በአንድ ቀን አብረን ከመሞታችን በፊትም የልጅ ልጆቻችንን እንደምናይ ተስፋ ነበረን::አንደኛችንም፣ ብቻችንን ቀርተን በሌላኛችን ሞት እናዝናለን ብለን አስበን አናውቅም ነበር።

እንደገና በጭንቀት ተነፈሰች “ከዛሬ ቀድመን እየኖርን እንደነበር መናገርh እፈልጋለሁ። ማለቴ ከወደፊታችን ላይ እንኳን ገንዘብ እንበደር ነበር፧ ከማግኘታችን በፊት እናጠፋ ነበር። በዚህ ጉዳይ ላይ እሱን እንዳትወቅሱት: ስለ ድህነት በደንብ ያውቅ ነበር። እኔ ግን ስለ ድህነት ብዙም ስለማላውቅ
ጥፋቱ የኔ ነበር። እንዴት ያሞላቅቀኝ እንደነበር ታውቃላችሁ። ይህንን ቤት
ስንገዛ እንኳን የሚያስፈልጉን ሶስት መኝታ ክፍሎች ያሉት ቤት ነው ብሎኝ ነበር። እኔ ግን አራት ካልሆኑ አልኩት። አራትም በቂ አይመስለኝም ነበር።

“ተመልከቱ፣ ይህ ቤት የሰላሳ ዓመት የባንክ ዕዳ አለበት። ውስጡ ያሉት የትኞቹም ዕቃዎች የእኛ አይደሉም መኪኖቹም፣ ወጥቤት ያሉት ዕቃዎችም
ሆኑ የልብስ ማጠቢያው ክፍል ውስጥ ያሉት የትኞቹም ነገሮች ሙሉ ዋጋ የተከፈለባቸው አይደሉም”

ፈራን… ደነገጥን፡ ፊቷ ቀልቶ መናገሯን ቆም አደረገችና አይኖቿ የእሷ ውበት አምሳያ የሆነውን የሚያምረውን ክፍል መቃኘት ጀመሩ የሚያምሩት ቅንድቦቿ በመጓጓት አይነት ተኮሳተሩ። “አባታችሁ ተይ እንዳይለኝ ይወደኝ
ነበር ስለሚወደኝም ያሞላቅቀኝ ነበር። እኔም እንዴት ላሳምነው እንደምችል አውቅ ነበር። በመጨረሻ እነዚያ የቅንጦት ነገሮች አስፈላጊዎቻችን እየሆኑ
መጡና እጅ ሰጠ፡ ሁለታችንም ፍላጎቶቻችንን ለማሳካት መንገዶች ነበሩን።

እንግዳ በሆነ ድምጿ የምትናገረውን ከመቀጠሏ በፊት ፊቷ ከባዶ ትዝታዎቿ በአንዱ የተዋጠ መሰለ፡ “አሁን ሁሉም ውብ ነገሮቻችን ተወስደዋል። በህግ ቋንቋ ሁኔታው መውረስ ይባላል የገዛችሁትን ነገር ዋጋውን ከፍላችሁ ለመጨረስ በቂ ገንዘብ ከሌላችሁ እነሱ እንደዚያ ነው የሚደረጉት። ለምሳሌ ያንን ሶፋ ውሰዱ፤ ከሶስት ዓመት በፊት ዋጋው ስምንት መቶ ዶላር ነበር።
ሁሉንም ከፍለን የቀረን አንድ መቶ ዶላር ብቻ ነው: ግን በቃ ይወስዱታል።

ሁሉም ነገር ላይ የከፈልነውን ጭምር እናጣለን ይሄ ደግሞ ህጋዊ አሰራር ነው። የምናጣው እቃዎቹንና ቤቱን ብቻ አይደለም መኪናቹንም ጭምር ነው። ከልብሶቻችንና ከአሻንጉሊቶቻችሁ በስተቀር ሁሉንም እናጣለን ማለት
ነው። የጋብቻ ቀለበቴን እንድወሰደው ፈቅደውልኛል። እኔ ደግሞ ስንተጫጭ የሰጠኝን የአልማዝ ቀለበት ደብቄዋለሁ ስለዚህ እነሱ ለማረጋገጥ ሲመጡ
ለአንደኛቸውም እንኳን የቃልኪዳን ቀለበት እንዳለኝ እንዳትናገሩ፡"

“እነሱ” ማን እንደሆኑ ማናችንም አልጠየቅንም መጠየቅም አልመጣልኝም። ካለፈ በኋላ ደግሞ አስፈላጊ አልነበረም።

ከክሪስቶፈር ጋር ተያየን: ለመረዳት በመፈለግ ውስጥ እንዳልሰምጥ
እየታገልኩ ነበር። እውነታው ግን በትልልቅ ሰዎች የሞትና የዕዳ አለም ውስጥ እየሰመጥኩ መሆኑ ነው። ወንድሜ እጁን ዘርግቶ ያዘኝና ባልተለመደ ወንድማዊ የማረጋገጫ ምልክት ጣቶቼን ጨመቅ አደረጋቸው።

ለማንበብ ቀላል የሆንኩ የንፋስ መጥረጊያ ነኝ አንዴ ዋና አጥቂዬ የሆነው ወንድሜ እንኳን ሊያፅናናኝ የሚፈልገው? ምን ያህል ትልቅ ሰው እንደሆንኩ
ለማረጋገጥና እነሱ ሁሉንም ነገር በመውሰዳቸው ምክንያት የተሰማኝን ፍርሀትና ደካማነት ላለማሳየት ፈገግ ለማለት ሞከርኩ። የትኛዋም ትንሽ
ልጅ በእኔ ክፍል ውስጥ እንድትኖርም ሆነ እኔ አልጋ ላይ እንድትተኛና እኔ በምወዳቸው ነገሮች እንድትጫወት፣ አሻንጉሊቶቼን እንድትነካም ሆነ
በሙዚቃ ሳጥኔ እንድትጫወት አልፈልግም እነዚያንም ይወስዱብኝ ይሆን?

እናቴ የእኔንና የወንድሜን ሁኔታ በቅርበት እየተመለከተች ነበር። ከዚያ እንደገና በቀድሞው ጣፋጭ አነጋገሯ “ልባችሁ አይሰበር፤ እኔ ስነግራችሁ
እንደሚመስለው ያህል መጥፎ አይደለም: አሁንም ገና ትንንሽ ልጆች መሆናችሁን ረስቼ ሀሳብ የለሽ በመሆኔ ይቅር በሉኝ። መጥፎውን ዜና በመጀመሪያ የነገርኳችሁ ጥሩውን ወደ ኋላ አስቀርቼ ነው አሁን ትንፋሻችሁን
ያዙ! ወላጆቼ እጅግ ሀብታሞች እንደሆኑ ስነግራችሁ አታምኑኝም: መካከለኛ ኑሮ የሚኖሩ ሀብታሞች እንዳይመስሏችሁ፤ በማይታመን አይነት በጣም በጣም ሀብታሞች ናቸው! ቨርጂኒያ ውስጥ በሚገኝ ግዙፍ ቤት ውስጥ ነው የሚኖሩት። እንደዚያ አይነት ቤት ከዚህ በፊት አይታችሁ አታውቁም
የተወለድኩትና ያደግኩት እዚያ ነው ያንን ቤ ትዚህ ጋር ስታነፃፅሩት ይሄኛው እንደ ትንሽ ጎጆ ነው
👍391🥰1
እዚያ ልንኖር ነው: ከእናቴና ከአባቴ ጋር ልንኖር ነው ብዬ አልነገርኳችሁም አይደል?”
ይህንን ዜና በደካማና በአታላይ ፈገግታ አስውባ ብታቀርበውም እኔን ግን እሷ በነገረችን ነገር ከገባሁበት ጥርጣሬና ግራ መጋባት ሊያስወጣኝ አልቻለም
አይኖቿን ለማየት ስሞክር በጥፋተኝነት ስሜት እኔን ላለማየት የሚያደርጉት ሽሽት አልወደድኩትም: የሆነ ነገር የደበቀችን መስሎኛል።

ግን እናቴ ናት።

አባቴ ደግሞ ሞቷል!

ኬሪን አንስቼ ጭኔ ላይ አስቀመጥኳትና የሚሞቅ ሰውነቷን ወደእኔ አስጠግቼ
ግንባሯ ላይ ድፍት ያለውን ወርቃማ ፀጉሯን ሳም አደረግኩት። የአይኔ ቅንድቦች ተከድነዋል ከንፈሯ በመጠኑ ከፈት ብሏል። ወደ ኮሪ ስመለከት
ክሪስቶፈር ላይ ጋደም ብሏል፡ “መንትዮቹ ደክሟቸዋል፡ ራታቸውን ይፈልጋሉ፡”

“ለእራት የሚሆን በቂ ጊዜ አለን:" ስትል ትዕግስት በማጣት ተነፈሰች “እቅድ ማውጣት አለብን፡ ልብሶቻችንን ማዘጋጀት አለብን፡ ዛሬ ማታ በባቡር
መሳፈር አለብን፡ ልጆቹ እኛ ዕቃ በምናሽግበት ጊዜ ራታቸውን ሊበሉ ይችላሉ::አራታችሁም የምትለብሷቸው ልብሶች በሁለት ሻንጣዎች ውስጥ ብቻ መሆን "
አለባቸው አራት የምትመርጧቸውን ልብሶችና ልትተዋቸው የማትችሏውን ትንንሽ አሻንጉሊቶች ብቻ መያዝ አለባችሁ: ሌላ አያስፈልግም፤ እዚያ ከደረስን በኋላ እኔ ብዙ መጫወቻዎች እገዛላችኋለሁ: ካቲ፣ አንቺ መንትዮቹ በጣም ይወዷቸዋል ብለሽ የምታስቢያቸውን ጥቂት ልብሶችና አሻንጉሊቶች ምረጪላቸው: በአጠቃላይ ከአራት ሻንጣ በላይ መያዝ አንችልም። እኔ የራሴን ዕቃዎች ለመያዝ ሁለት ሻንጣዎች ያስፈልጉኛል” አለች።

የአምላክ ያለህ! እውነት ነው! ሁሉንም ነገር ትተን መሄድ ሊኖርብን ነው፡ ወንድሞቼና እህቴ በሚጋሩኝ ሁለት ሻንጣዎች ውስጥ ሁሉንም ነገር መክተት
አለብኝ፡ የምወዳት አንዷ አሻንጉሊቴ ራሷ የአንዱን ሻንጣ ግማሽ ትይዛለች።ታዲያ አባቴ ገና የሶስት ዓመት ልጅ ሳለሁ የሰጠኝን በጣም የምወዳትን ምርጥ አሻንጉሊቴን እንዴት ነው የምተዋት? ተንሰቀሰቅኩ
በደነገጠ ፊት እናታችን ላይ እንዳፈጠጥን ተቀምጠናል ለሷም ቀላል አላደረግንላትምና ከተቀመጠችበት ዘላ ተነስታ ክፍሉ ውስጥ መንጎራደድ ጀመረች:

“አስቀድሜ እንደነገርኳችሁ ወላጆቼ ሀብታሞች ናቸው" እኔንና ክሪስቶፈርን አየት አድርጋን ወዲያውኑ ፊቷን ለመደበቅ ዞረች።
“እማዬ ችግር አለ?” አለ ክሪስቶፈር።

ሁሉም ነገር የሆነ ችግር እንዳለበት ግልፅ ሆኖ ሳለ እንዲህ አይነት ጥያቄ መጠየቁ አስደነቀኝ። ስትራመድ የሚያምሩት እግሮቿ በለበሰችው ጥቁር ስስ ገዋን የፊት ለፊት ተካፋች ውስጥ ይታዩ ነበር በሀዘን ውስጥ ሆና ጥቁር ለብሳና አይኖቿ ችግር እየተንፀባረቀባቸው እንኳን በጣም ቆንጆ ነች: በጣም
ደስ የምትል ናት እና እወዳታለሁ። እንዴት እንደምወዳት!

የዚያን ጊዜ ሁላችንም እንዴት እንደምንወዳት!

“ውዶቼ… በሚያምረው በወላጆቼ ቤት ውስጥ መኖር ምን ችግር ሊኖረው ይችላል? ወደ ትምህርት ቤት ከተላኩባቸው አመታት በስተቀር የተወለድኩትና
ያደግኩት እዚያው ነው ትልቅና የሚያምር ቤት ነው፡: በዚያ ላይ በየጊዜው አዳዲስ ክፍሎች ይጨምሩበታል። ስለዚህ በቂ ክፍሎች እንደሚኖሩት የታወቀ
ነው።"

ፈገግ አለች። ነገር ግን ፈገግታዋ የሆነ ነገሩ የውሸት ይመስላል: “ግን ከአባቴ ማለትም ከአያታችሁ ጋር ከመገናኘታችሁ በፊት ልነግራችሁ የሚያስፈልግ
አንድ ትንሽ ነገር አለ” አለችና እንደገና ያንን ፈገግታዋን አሳየችን፡ “ከአመታት በፊት ገና የአስራ ስምንት ዓመት ልጅ ሳለሁ፣ አባቴ የተቃወመው እናቴም ያልደገፈችውን አንድ ከባድ ነገር አደረግኩ። ባደረግኩት ነገር ምክንያት አባቴ ከውርስ እንድሰረዝ አደረገኝ ስለዚህ አሁን ከውርስ ውጪ ነኝ።

“ሁልጊዜ ከሁሉም ነገሮች ውስጥ መልካም ነገር የሚያወጣው አባታችሁ ይህንን ጉዳይ ከፀጋ መውደቅ ብሎ ይጠራውና ምንም ችግር እንደሌለው ይነግረኝ ነበር”
“ከፀጋ መውደቅ" ትርጉሙ ምንም ይሁን ምን እናቴ ምን አይነት መጥፎ ነገር ብትሰራ እንደሆነ አባቷ ሊጣላትና የሚገባትን ነገር ሁሉ ሊወስድባት የቻለው
ማሰብ አልቻልኩም።

“እሺ እማዬ ምን ማለትሽ እንደሆነ በትክክል ገብቶኛል።" አለ ክሪስቶፈር “በኑዛዜው ውስጥ ተካተትሽ የነበረ ቢሆንም፣ አባትሽ ያልፈቀደውን ነገር በማድረግሽ እሱ ደግሞ ነገሩን በደንብ ከማሰብ ይልቅ ጠበቃውን አንቺን ከውርስ ውጪ አድርጎ እንዲፅፍ ስላደረገው፣ አሁን የትኛውንም ንብረቱን አትወርሺም ማለት ነው።” ከእኔ የበለጠ የሚያውቅ በመሆኑ በራሱ በመኩራራት ፈገግ
አለ: ሁልጊዜ ስለሁሉም ነገር መልስ ነበረው። ቤት ውስጥ ካለ አፍንጫው መፅሀፍ ውስጥ ነው። ከቤት ውጪ ከጓደኞቹ ጋር ሲሆን ደግሞ አካባቢው ላይ እንደሚኖሩት እንደሌሎች እኩዮቹ ነው። ቤት ውስጥ ግን ከቴሌቪዥን የራቀ መፅሀፍ አንባቢ ነው ትልቁ ወንድሜ!

ትክክል ነበር።

“አዎ ክሪስቶፈር፣ አያታችሁ በሞተ ጊዜ ወደኔ የሚመጣ ከእኔም ወደናንተ የሚያልፍ ምንም ውርስ የለም፡ ለዚያ ነው እናቴ መልስ አልሰጥ ስትለኝ እነዚያን ሁሉ ደብዳቤዎች መፃፍ የቀጠልኩት: እንደገና ፈገግ አለች የአሁኑ ደግሞ መራራ ነበር።

“አሁን ያለሁት ወራሽ እኔ ብቻ ስለሆንኩ፣ የእሱን ስምምነት እንደማገኝ ተስፋ አለኝ አያችሁ ሁለት ወንድሞች ነበሩኝ: አሁን ግን ሁለቱም በአደጋ ምክንያት ሞተዋል፡ እና አሁን ለመውረስ የቀረሁት ብቸኛ ልጅ እኔ ነኝ: "
የመወራጨት ፍጥነቷ ቀነሰ። እጇ አፏን ለመሸፈን ከፍ አለ ጭንቅላቷን ነቀነቀችና በአዲስ በቀቀን መሳይ ድምፅ “ሌላም ነገር ብነግራችሁ የተሻለ
ነው እውነተኛ የአባታችሁ ስም ዶላንጋንገር ሳይሆን ፎክስወርዝ ነው። ፎክስወርዝ ደግሞ ቨርጂኒያ ውስጥ በጣም አስፈላጊ ስም ነው።

በድንጋጤ ውስጥ እንዳለሁ “እማዬ ያንን የውሸት ስም የልደት ሰርተፊኬት ላይ ማፃፍ ህጋዊ ነው?” ስል ጠየቅኳት።

ድምጽዋ ትዕግስት አልባ ነበር። “ስለ እግዚአብሔር ካቲ ሰዎች ስማችውን በህጋዊ መንገድ መቀየር ይችላሉ'ኮ እና ዶላንጋንገር አነሰም በዛ የኛ ስም ነው: አባታችሁ ያንን ስም ከድሮ ዝርያዎቹ ተውሶት ነው አስቂኝ የቀልድ ስም እንደሆነ ያስብ ነበር። እናም በበቂ ሁኔታ ተገልግሎበታል።"

“በምን ዓይነት በቂ ሁኔታ? ለምንድነው አባዬ ፎክስወርዝ የሚለውን ለመፃፍ ቀላል የሆነ ስሙን በህጋዊ መንገድ ዶላንጋንገር ወደሚል ረጅምና አስቸጋሪ ስም የለወጠው?” ብዬ ጠየቅኩ።

“ካቲ ደክሞኛል” አለችና አጠገቧ ያለ ወንበር ላይ ተቀመጠች። “ገና የምሰራው ብዙ ነገር አለ፤ ብዙ የህግ ዝርዝሮች አሉ። ሁሉንም ነገር በቅርቡ ስለምናውቅ
እነግራችኋለሁ: እውነቱን ብቻ እንደምነግራችሁ እምላለሁ። ግን እባካችሁ " አሁን ትንፋሼን ልሰብስብ:” አለች።

ምን አይነት ቀን ነው: መጀመሪያ ሚስጥራዊዎቹ “እነሱ” መጥተው ሁሉንም ነገራችንን ቤታችንን ሳይቀር እንደሚወስዱብን ሰማን ከዚያ ደሞ የአባታችን
ስም እንኳን ሳይቀር የእኛ እንዳልሆነ አወቅን።
መንትዮቹ በጭኖቻችን ላይ ጋደም ብለው እያንቀላፉ ነው: የሆነውን ሁሉ ለመረዳት ገና ትንንሾች ናቸው። እኔም የአስራ ሁለት ዓመት ትልቅ ሴት ሆኜ እንኳን እናቴ ለአስራ አምስት ዓመታት አይታቸው የማታውቃቸውን
ወላጆቿን እንደገና የማየቷ ነገር ለምን እንዳላስደሰታት መረዳት አልቻልኩም። ሚስጥራዊ አያቶቻችንን እስከ አባታችን ቀብር ማለፍ ድረስ እንደሞቱ
እያሰብን ነበር። በአደጋ የሞቱ ሁለት አጎቶች እንዳሉን የሰማነው ገና ዛሬ ነው። ወላጆቻችን ልጆች ከመውለዳቸው በፊት እንኳን የተሟላ ህይወት
እንዳልነበራቸውና እኛም ያን ያህል አስፈላጊ እንዳልሆንን በማሰብ ቅሬታ ተሰማኝ።
👍38🤔21
ክሪስቶፈር “እማዬ ቨርጂኒያ ያለው ትልቁ ቤትሽ አሪፍ ይመስላል፤ ግን
ለእኛ እዚህ ይሻለናል። ጓደኞቻችን ሁሉ ያሉት እዚህ ነው፡ ሁሉም ሰዎች ይወዱናል፣ ያውቁናል። እኔ ከዚህ መሄድ እንደማልፈልግ አውቃለሁ። የአባዬን ጠበቃ አግኝተሽ እዚህ መቆየት እንድንችል የሚረዳንን መንገድ
እንዲፈልግ ማድረግ አትችይም?” አለ በቀስታ።

“አዎ እማዬ እባክሽ እዚሁ እንሁን” ብዬ ለመንኳት።

ወዲያውኑ እናቴ ከወንበሯ ላይ ተነስታ ወደኛ መጣች። ከዚያ ፊት ለፊታችን በጉልበቷ ተንበረከከችና አይኖቿን ከእኛ አይኖች ትይዩ አደረገች። የእኔንና የወንድሜን እጆች ይዛ በጣቶቿ ላይ አደረገችና “አሁን አዳምጡኝ. እዚህ መቆየት እንዴት እንደምንችል ብዙ ጊዜ አስቤ ነበር። ግን ምንም መንገድ
የለም: ምንም! ምክንያቱም በየወሩ የሚጠበቁብንን ክፍያዎች ለመክፈል በቂ ገንዘብ የለንም አራት ልጆችና ራሴን ለመደገፍ የሚያስችል በቂ ደሞዝ
የሚያስገኝ ስራ ለመስራትም እውቀት የለኝም:"

እጆቿን ወደጎን ዘረጋችና “ተመልከቱኝ እስቲ…. እኔ ምን እንደሆንኩ ታውቃላችሁ? ቆንጆ ነኝ ግን ሁልጊዜም የሚንከባከባት ባል እንዳላት የምታምን
ጥቅም አልባ ጌጥ ነኝ፡ ምንም ነገር እንዴት እንደሚሰራ አላውቅም የፅህፈት መኪና ተጠቅሜ መፃፍ እንኳን አልችልም: በሂሳብ ጥሩ አይደለሁም: ጥሩ
ግን እንደዚህ የሆነ በመርፌ የሚሰራ ጥልፍ መጥለፍ ብቻ እችላለሁ ግን እንደዚህ
አይነት ስራ በቂ ገንዘብ አያስገኝም: ያለ ገንዘብ ደግሞ መኖር አትችሉም።አለምን የሚያሽከረክራት ፍቅር አይደለም ገንዘብ ነው: አባቴ ስልሳ ስድስት
ዓመቱ ነው! በዚያ ላይ በልብ በሽታ ምክንያት ተዳክሟል እናቴ በፃፈችው ደብዳቤ ላይ አያታችሁ ግፋ ቢል ከሁለት ወይም ከሶስት ወር በላይ በህይወት አይቆይም ግን ምን እንደሚሰራበት ከሚያውቀው በላይ ብዙ ገንዘብ አለው።በህይወት ያለች አንዲት ወራሽ ልጁ እኔ ብቻ ነኝ: በዚህ ሁኔታ ላይ የእሱን ፍቅር መልሶ ማግኘት ከባድ አይሆንብኝም ከዚያ ጠበቃውን በአዲ
ኑዛዜ ውስጥ እንዲያካትተኝ ይነግረውና ሁሉንም እወርሳለሁ: ከዚያ ሲሞት ንብረቱ ሁሉ የእኔ፣ የእኛ ይሆናል፡ ከገንዘብ ማጣት ጭንቀት ለዘለዓለም ነፃ
እንሆናለን፡፡ የፈለግንበት ለመሄድም ሆነ የምንፈልገውን ለማድረግ እንዲሁም ልባችን የተመኘውን ለመግዛት ጭምር ነፃ እንሆናለን፡ የምነግራችሁ ስለ
አንድ ወይም ሁለት ሚሊየን ሳይሆን ስለ ብዙ… በጣም ብዙ ሚሊየኖች ምናልባትም ቢሊየኖች ነው: አያታችሁ አሁን ለመሞት ጫፍ ደርሶ እንኳን ገንዘብ መስራት ላይ ጎበዝ ነው: የነካው ሁሉ ወደ ወርቅ ይቀየራል:"

ሰማያዊ አይኖቿ አንፀባረቁ:: በዋጋ ከሚተመን በላይ ሀብታም መሰለች::እማዬ አባታችን ከሞተ በኋላ ይህ ሁሉ እንዴት መጣ?

“ክሪስቶፈር፣ ካቲ... እየሰማችሁኝ ነው? እያሰባችሁ ነው? ብዙ መጠን ያለው ገንዘብ ምን መስራት እንደሚችል አስተዋላችሁ? ዓለምና በውስጧ ያለው ሁሉ የእናንተ ይሆናል! ኃይል፣ ተፅዕኖና ክብር ይኖራችኋል። እመኑኝ በፍጥነት የአባቴን ልብ መልሼ አሸንፋለሁ። ገና ሲያየኝ ወዲያውኑ ተለያይተን
የቆየንባቸው እነዚያ አስራ አምስት አመታት የባከኑ እንደነበሩ ያስተውላል አሁን እሱ ነርሶች ቀንና ሌሊት እየተንከባከቡት ከቤተ መፃህፍቱ ባሻገር ባለች
ትንሽ ክፍል ውስጥ ነው ያለው አርጅቷል፣ ታሟል... ሊሞት ነው" አለች።....

ይቀጥላል
👍4414🥰2😢1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አምስት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


ወደ ሀብታምነት ጉዞ

እናታችን እቃዎቿን ስታሽግ እኔና ክሪስቶፈር ደግሞ ልብሶቻችንን ከጥቂት አሻንጉሊቶችና ከአንድ መጫወቻ ጋር በሁለት ሻንጣዎች ውስጥ ማጨቅ ጀመርን: በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ጓደኛችንን እንኳን ሳንሰናበት ታክሲ መጥቶ ወደ ባቡር ጣቢያ ወሰደን፡ እናታችን ማንንም ሳንሰናበት
በሚስጥር ሹልክ ብለን እንድንሄድ የግድ ያለችን ለምን እንደሆነ አልገባኝም።

ባቡሩ ብዙ ከተሞችና መንደሮች እንዲሁም እርሻ ቦታ ላይ ያሉ ቤቶችን እያቆራረጠ ወደ ቨርጂኒያ ግዛት ሲያመራ እኔና ወንድሜ አንድም ነገር እንዳያመልጠን ብለን መተኛት አልፈለግንም በዚያ ላይ ብዙ የምናወራችው
ነገሮች ነበሩን፡ ወሬያችን በአብዛኛው ስለዛ ትልቅ የሀብታም ቤት፣ ተንደላቀን ስለመኖር፣በወርቅ ሳህን ስለመመገብና የሚያምር ልብስ በለበሰ ሰራተኛ
ስለመስተናገድ ነበር ልብሶቼን የምታጣጥፍ፣ የገላ ውሀ የምታዘጋጅ፣ ፀጉሬን
የምታበጥርልኝና ባዘዝኳት ቁጥር ከች የምትል የግል ሠራተኛ እንደምትኖረኝ አሰብኩ ግን በጣም ክፉ አልሆንባትም በጣም የምወደውን ዕቃ ካልሰበረችብኝ
በስተቀር ሠራተኞች ሁሉ የሚመኟት አይነት ደግ እመቤት ነው የምሆንላት መቼም የማልወዳቸውንና የማልፈልጋቸውን ነገሮች መጣሌ ስለማይቀር በደንብ ነው የምከፍላት፡

በዚያ ምሽት ባቡሩ ውስጥ እያለን ጨለማውን ወደ ኋላ ስመለከት ምሽቱ ማደግና መፈላሰፍ የጀመርኩበት የመጀመሪያ ምሽት እንደሆነ አስተዋልኩ ሁሉንም ለማግኘት የሆነ ነገር ማጣት ስላለ እኔም የሚመጣውን ልለምደው
እና በጣም ጥሩ ላደርገው ያስፈልጋል እኔና ወንድሜ ገንዘቡ እጃችን ውስጥ ሲገባ በምን እንደምናጠፋው እየተነጋገርን
እያለ ፀጉሩ በመመለጥ ላይ ያለ የባቡሩ ሠራተኛ ወዳለንበት መጣ። የመጣበት ከመናገሩ በፊት እናታችንን በአድናቆት ከእግር እስከራሷ ተመለከታት። ከዚ
“ወ/ሮ ፓተርስን፣ በአስራ አምስት ደቂቃ ውስጥ መውረጃሽ ጋር እንደርሳለን አላት።

አሁን ደግሞ ለምንድነው “ወ/ሮ ፓተርሰን” ብሎ የጠራት? ግራ ገባኝ፡ ክሪስቶፈርን በጥያቄ አይን ተመለከትኩት እሱም ግራ የተጋባ ይመስላል።

ድንገት ስትነቃ የት እንዳለች ግር በመሰኘቷ የእናታችን አይኖች በሀይል ተከፈቱና ትኩረቷ ወደ ባቡሩ ሠራተኛ፣ ቀጥሎ ወደ እኔና ክሪስቶፈር ከዚያ ደግሞ ተስፋ በመቁረጥ እንቅልፍ ውስጥ ወዳሉት መንትዮች ተሻገረ። ወዲያው እምባዋ መጣና ከቦርሳዋ ውስጥ መሀረብ አውጥታ አይኖቿን ጠረገች። ሀዘን
በተሞላበት አይነት በከባዱ ስትተነፍስ ልቤ በሽብር መምታት ጀመረ።

አሁንም ቆሞ በአድናቆት እየተመለከታት ላለው የባቡሩ ሠራተኛ እሺ አመሰግናለሁ አትስጋ፣ ለመውረድ ተዘጋጅተናል” አለችው: የኪስ ስዓቱን ተመለከተና የጭንቀት እይታውን ወደ እኔና ክሪስቶፈር ከዚያ ደግሞ ወደ የተኙት መንትዮች አደረገ። ከዚያ “እመቤቴ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ነው ስትወርዱ የሚጠብቃችሁ ሰው አለ?” አላት።

“ችግር የለም” ስትል እናቴ አረጋገጠችለት።

“እመቤቴ በጣም ጨለማ እኮ ነው”

“የቤቴን መንገድ በእንቅልፍ ልቤ እንኳን አውቀዋለሁ።”

የአያት አይነት ባህርይ ያለው የባቡሩ ሠራተኛ የተናገረችው ነገር አላረካውም። “እመቤት፣ ቻርለትስቪል ከመውረጃችሁ የአንድ ሰዓት መንገድ ነው: አንቺንና ልጆቹን የምናወርዳችሁ ቤት የሚባል ነገር በማይታይበት ቦታ ላይ ነው አላት።

እናቴ ተጨማሪ ጥያቄዎችን ላለመፍቀድ በጣም ትዕቢት በተሞላበት አነጋገር
“የሆነ ሰው ይጠብቀናል” አለችው ባንድ ጊዜ እንዴት እንደዚህ ያለ ባህርይ ልታመጣና ወዲያው ደግሞ ልክ እንደ ኮፍያ በቀላሉ ልታወልቀው እንደቻለች ማየት ያስገርማል።

እውነትም ምንም ነገር በሌለበት ቦታ ደረስን ከባቡሩ ወረድን፡ ከባቡር ስንወርድ ሙሉ በሙሉ ጨለማ ቢሆንም ማንም የጠበቀን አልነበረም: የባቡሩ ሠራተኛ እንዳስጠነቀቀን አንድም የሚታይ ቤት የለም። በጨለማ ብቻችንን
የሰው ፍጥረት በማይታይበት ቆም ብለን የባቡሩ ደረጃ ላይ ለቆመው የባቡሩ ሠራተኛ የስንብት እጃችንን አውለበለብንለት ከገፅታው እንደተረዳሁት “ወ/ሮ ፓተርሰንን” ፦ሤከአራት እያንቀላፉ ካሉ ልጆቿ ጋር ትቶ መሄዱ ደስ አላሰኘውም።
ዙሪያውን ስመለከት ማየት የቻልኩት በአራት የእንጨት ምሰሶዎች የተደገፈ የዛገ የቆርቆሮ ጣራና አረንጓዴ አግዳሚ ወንበር ብቻ ነው፡ የባቡር ጣቢያው
መሆኑ ነው። ባቡሩ በጨለማው ውስጥ እስኪሰወርና መልካም ዕድል እየተመኘልን የሚመስል አንድ አሳዛኝ የጥሩምባ ድምፁን እስክንሰማ ድረስ ቆመን እያየነው ነበር።

በሜዳና በመስኮች ተከበናል ከባቡር መውረጃው ጀርባ ካለው ጫካ ውስጥ የሆነ የተለየ ድምፅ ስሰማ በድንጋጤ ዘለልኩና ምንነቱን ለማወቅ ዙሪያውን
ረስመለከት ክሪስቶፈር ሳቀብኝ።“ጉጉት እኮ ናት! ጣረሞት መስሎሽ ነበር?”
አለኝ።
እናታችን “አሁን ማንም የለም: በሹክሹክታ መናገር የለባችሁም: ይህ የእርሻ ሀገር ነው በአብዛኛው ያሉት የወተት ላሞች ናቸው። ዙሪያውን ተመልከቱ። የስንዴና የአጃ እንዲሁም የገብስ መሬቶች ናቸው። እዚህ ያሉት ገበሬዎች ናቸው ኮረብታው ላይ ለሚኖሩት ሀብታሞች ምርቶቻቸውን በትኩሱ
የሚያቀርቡት”

ተቀጣጥለው የቆሙ በጣም ብዙ ኮረብታዎች ሲኖሩ ኮረብቶቹ ላይ በንፋስ ላይና ታች የሚሉ በርካታ ዛፎችም ተደርድረዋል። የምሽት ዘበኞች ብዬ ጠራኋቸው። እናታችን ግን ተደርድረው የተተከሉት በርካታ ዛፎች ከባዱን
ነፋስ ለመከላከልና ከባድ በረዶ ሲመጣ እንዲይዙ መሆኑን ነገረችን። ንፋስና በረዶ ክሪስቶፈርን የማረኩት ትክክለኛ ቃላት ነበሩ። ምክንያቱም በበረዶ
የሚደረጉ ሁሉንም አይነት የክረምት ስፖርቶች ይወዳል። እና እንደ ቨርጂያ ያለ የደቡብ ክፍል ከባድ በረዶ ይኖረዋል ብሎ አላሰበም።

“እዚህም በረዶ ይጥላል” አለች እናቴ: “ያለነውኮ ከብሉሪች ተራራዎች ስር ነው: ልክ እንደ ግላድስተን እዚህም ብርድ አለ። በበጋ ቀኑ በጣም ይሞቃል፤
ምሽቱ ግን ሁልጊዜም ቢያንስ አንድ ብርድ ልብስ ብቻ የሚያስለብስ ቅዝቃዜ አለው አሁን ፀሀዩዋ ብትወጣ ኖሮ ውብ የሆነውን ገጠር ማየት ትችሉ ነበር።በዓለም ላይ የዚህን ያህል የሚያምር ቦታ የለም አሁን በጣም መፍጠን አለብን ቤት ለመድረስ በጣም ረጅም መንገድ ይጠብቀናል። ከመንጋቱና
ሠራተኞቹ ከመነሳታቸው በፊት መድረስ አለብን፡” አለችን፡።
በጣም ይገርማል፡ “ሰራተኞቹ ከመነሳታቸው በፊት? ለምን? የባቡሩ ሠራተኛ ወ/ሮ ፓተርሰን ብሎ የጠራሽ ለምንድነው?” ብዬ ጠየቅኳት፡፡

"ካቲ አሁን ለአንቺ የማብራራበት ጊዜ የለኝም:: እየፈጠንን መራመድ አለብን አለችና ሁለቱን ከባባድ ሻንጣዎች አንስታ ጠንhር ባለ ድምፅ እንድንከተላት
አዘዘችን፡ እኔና ክሪስቶፈር እንቅልፋቸው ከመምጣቱ የተነሳ ለመራመድ ሙከራ ማድረግ ያልቻሉትን መንትዮቹን ለመሸከም ተገደድን።

ትንሽ እንደተራመድን “እማዬ የባቡሩ ሠራተኛ የአንቺን ሁለት ሻንጣዎጆ ሳይሰጠን ረስቶታል” አልኳት።

“ምንም አይደል ካቲ፤ ሻንጣዎቹን ወስዶ ሻንጣ ክፍል ውስጥ እንዲያደርግልኝ ነገ እንደምወስደው ነግሬዋለሁ” አለችኝ: የያዘቻቸው ሁለት ሻንጣዎች ጥንካሬዋን እንደቀነሱት ሁሉ ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ነበር

“ለምንድነው እንደዚያ ያደረግሽው?” ሲል ጠየቃት ክሪስቶፈር።
👍33🥰41