አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#አኮረፈች_መሰል...?

አኮረፈች መሰል . . . ?
ተፈጥሮ ንክ ኾነች
ቀኙን ግራ አረገች።

አኮረፈች መሰል . . .?
ሰማይ ደም መሰለ፤
ነጸብራቅ ተሞልቶ በጥቀረት ተሣለ።
ፍም መሳይ ደመና፣ እንባውን እረጨ
ዑደቱን ሳይጨርስ፣ ዘመንም ተቋጨ።
ጀንበር ተሸሸገች፤ ቀትር ተጠልላ
ከዋክብት አንድ ኾኑ፣ ፀሓይ ተጠቅልላ።
ፀሓይ እኩለሌት፣
ጨረቃም ታስያት፣
ኾኑ ተቀያይረ፤
ምድር ቀን ብታግድ፣ ጸዳልን ረስተው።

አኮረፈች መሰል . . . ?
የምድር ዘልማድ፣
ታሪክ ተረተረት ፣ በ'ውን ተሳከረ
እሳተ ጎመራ በረዶ ጋገረ።

( ሐሩር ቆፈን ኾነ! )
ዛፎች ፣ ዕለት ኾኑ . .
ዕለት ፣ ዛፍ አፈራ
ደርቆ ታየ ፤ ወይራ።
ቅጠልም ያለ ግንድ፣ ያለውም ከሰመ
ግንድም ሥር ሳይኖረው፣ ደርቆ ለመለመ።

አኮረፈች መሰል . . . ?
ባሕሮች ፣
ባ'ርምሞ ተዋጡ
ቅን ፋታን መረጡ።
ከጽሞና ዕብረዉ ፣ ጎርፎችም ዝም አሉ!
ጅረት ሽቅብ ወጣ . . .
ውቅያኖስ ጠብታ ፣ ወንዞች ጤዛ አከሉ።

አኮረፈች መሰል . . .?
አዎ . . . !
አኩርፋ ነው እንጂ፣
የሚኾነው ቀርቶ የማይኾን የኾነው
'ያቺ 'ምወዳት ሴት . . .
ምን ነገር ፈልጋ ፣ ምን ነገር አጥታ ነው ?!

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የመልስ_ጥያቄ

በዚች ምድር ዓለም.....
የመምጣትን ትርጉም
ዘልቆ ያለማወቅ፤
ወይም እንደጅረት ......
በውድም በግድም
ፈስሶ ያለማለቅ።
ወይ እንደ አውሎ ንፋስ.....
የሚንሳፈን ኃይል
በዱር ፣ በገደሉ
ምንድን ነው ያልገባኝ....
ወዳንቺ ሚመራኝ
የተፈጥሮ ውሉ።
#የእሳት_እራት

በፍቅርሽ ነበልባል ነፍሴ ተቃጠለ
እቶኑ ውበትሽ ገጹን አከሰለ።
ቀልቤ ብትንትኑ ትርምስምሱ ወጣ
የልጅነት ወዜ በመውደድ ገረው።
ከዕልቆ ሥፍር ራቀ ፤ ባ'ንቺው ተመሽገ
ጕያሽ ሥር ተቀብሮ ፣ ካ'ለም ተሸሽገ።

አቤት ይኼ ልቤ . . .
ስትኼጂ ሲሟሽሽ ፣ ጠውልጎ ሲወድቅ
ስትመጪ ሲፈካ ፣ አብቦ ሲጸድቅ።
መከነ ንዳዱ ጠረንሽ አራሰው፤
ለምልሞ ጸደቀ ፤ ዙሪያሽን ሲያስሰው።

እናም ይኼ ልቤ . . .
ወጋገን ኾነችው ጸዳል እንዳለመ፣
ብርሃን ገላሽ ላይ ሲያርፍልሽ ከሰመ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_አንድ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

“ተነሱ ወታደሮች” አለ አስር አለቃ፡፡ የደንብ ልብሱን ለብሶ ሙሉ ትጥቁን ታጥቆ ነበር የመጣው። በተጠንቀቅ ተሰልፈን ነበር። አረንጓዴ ከረባት ሰጠን እና “ይሄን ከረባት ያላደረገ ወይም እንደ እኔ አይነት ባርኔጣ ያላደረገ ካያችሀ ተኩሳችሁ ምቱት” አለ በጩኸት። አሁን ለስልጠና እንደማንሄድ ለሁሉም
ግልጸ ነው። “አሁን ዘና በሉ፤ ከተወሰኑ ከደቂቃዎች በኋላ ጉዞ እንጀምራለን።”

አስር አለቃ ትቶን ሄደ፡፡ መሬት ላይ ተቀመጥን፤ ሁላችንም በየግል ሃሳባችን ተውጠን ነበር፡፡ሼኩ እና ጆሲያህ ከጎኔ
ተቀምጠዋል ፤ አይናቸው ውሃማ ነበር የተከፉ ይመስላሉ።ማድረግ የምችለው ራሳቸውን እያሻሽሁ አይዙዋችሁ ማለት ብቻ ነበር። ተነስቼ ወደ አል ሃጂ እና ሌሎች ጓደኞቼ ሄድኩ። ምንም
ቢፈጠር አንድ ላይ ለመሆን ተስማማን።

ወጣት ወታደር የፕላስቲክ ቦርሳ ይዞ ወደ እኛ መጣና ክኒን የሚመስል ነጭ ነገር ስጠን፡፡ “አስር አለቃ ተጨማሪ ሃይል
ይሰጣችኋል ፦ያበረታችኋል” ብሏል አለ። ክኒኖቹን ከወሰድን በኋላ መንቀሳቀስ ጀመርን። መሳሪያችንን ይዘን አዋቂ
ወታደሮችን ተከትለን መራመድ ጀመርን። ምሽት ላይ እንመለሳለን ተብሎ ስለታሰበ ምግብ እና መጠጥ አልያዝንም፡፡
ጫካው ውስጥ ብዙ ኩሬዎች አሉ።” አለ መቶ አለቃ:: ብዙ ምግብ እና ውሃ ይዞ ከመምጣት ጥይት እና መሳሪያ መሸከም
ይሻላል ለማለት ይመስላል :: “በብዙ ጥይቶች ውሃ እና ምግብ ማግኘት እንችላለን። ምግብ እና ውሃ ብንዝ ግን እስከ ማታ እንኳ አያቆየንም::” አለ አስር አለቃ መቶ አለቃ ጃባቲ የጀመረውን
ሃሳብ ሲያስረዳ፡፡

ሴቶች እና ትልልቅ ሰዎች ቤታቸው ደጃፍ ሁነው ስንሄድ ይመለከቱ ነበር። አንድ ህጻን የት እንደምንሄድ ምን እንደሚገጥመን ያወቀ ይመስል ስቅ ስቅ ብሎ አለቀሰ።ፀሐይዋ አንፀባራቂ ከመሆኗ የተነሳ ጥላችን መሬት ላይ ይታይ ነበር።

በህይወቴ እንደዛን ቀን መንቀሳቀስ ወደ ማንኛውም ቦታ ለመሄድ ፈርቼ አላውቅም። አይኖቼ እንባ ሲያቀርሩ ለመዋጥ እታገል ነበር። መሳሪያየም አጥብቄ ያዝኩ።

ወደ ጫካው አንድ ክፍል ስንገባ መሳሪያችንን እንደብቸኛ የጥንካሬ ምንጭ ይዘን ነበር። በጥንቃቄ በቀስታ ነበር የምንተነፍሰው። መቶ አለቃ በሚመራው ረድፍ ነበርኩ። እጁን
ወደ ሰማይ ሲያነሳ ጉዟችንን ገተን ቆምን። ቀስ አድርጎ እጁን ሲያወርድ በአንድ እግራችን ሸብረክ ብለን ከተቀመጥን በኋላ አካባቢን ቃኘን። ወዲያው ተነስተን ረግረጋ ጥግ እስክንደርስ ድረስ በፍጥነት መንቀሳቀስ ጀመርን። ረግረጉ ላይ መሳሪያችንን አስተካክለን ጠላት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ለመሰንዘር ተዘጋጀን።
በዝምታ እንደ አዳኝ አድፍጠን ጣታችንን ቃታ ላይ አሳርፈን ጠበቅን፡፡ ፀጥታው ግን አስጨነቀኝ።

አማጺዎች በረግረጉ በኩል ሲያልፉ በአካባቢው የነበሩ ትናንሽ ዛፎች ተንቀሳቀሱ። ገና አይታዩም መቶ አለቃ ግን “ሳዛችሁ ተኩሱ” አለ። ከደቂቃዎች በኋላ የተወሰነ ቡድን ሲመጣ
አየን። እጃቸውን አንስተው ተጨማሪ ታጣቂዎችን ጠሩ።አንዳንዶቹ እንደ እኛ ታዳጊዎች ነበሩ። መቶ አለቃ RPG
እንዲተኮስ አዘዘ፡፡ የአማጺዎች አዛዥ ግን ለመተኮስ ስንዘጋጅ ድምፅ ስምቶ ስለነበር ወታደሮቹን “በማፈግፈግ!” “ሸሹ”
“አምልጡ” አለ። ስለዚህ ፈንጁ የተወሰኑትን ብቻ ነበር ያገኘው።
ከፍንዳታው በኋላ በሁለቱም በኩል የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ።

መሳሪያየን ፊት ለ ፊት ደቅኜ ደርቄ ቀረሁ፡፡ መተኮስ አልቻልኩም። ጠቋሚ ጣቴ ደነዘዘ፡፡ ጫካው ይዞርብኝ ጀመር።
የምወድቅ ስለመሰለኝ ከጎኔ የነበረውን የዛፍ ግንድ በአንድ እጄ ያዝኩ። ማስብ አልቻልኩም ግን ከሩቅ ተኩስ ይሰማኛል ፤ ሰዎች በስቃይ እየጮሁ ይሰማኛል። ቅዥት በሚመስል ስሜት ውስጥ
እያለሁ የደም ርጭት ፊቴን መታኝ፡፡ ደሙን ከፊቴ ላይ እያበስኩ አንድ ወታደር ወደ እኔ ሲመጣ አየሁ::

ፀሐዮዋ የመሳሪያ ጫፍ እና ወደ እኛ የሚመጡ ጥይቶችን ታሳይ ነበር። ጆሲያህን መፈለግ ጀመርኩ፡፡ ጆሲያህን ግን መድፉ አግንቶት ነበር፡፡ ዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ ሰውነቱ በደም ተጨማልቆ አገኘሁት። እጆቹን ትክሻየ ላይ እንዳደረገ
መንቀሳቀስ አቆመ። አይኖቹን ዘግቼ መሬት ላይ አሳረፍኩት።ከጎኔ የሆነ ሰው እንደቆመ ይሰማኝ ነበር። አስር አለቃ ነበር።
“ዝቅ በል” “ተኩስ” አለኝ። ፊት ለ ፊት ሙሳን አየሁት ጭንቅላቱ በደም ተሸፍኗል እጆቹ ግን ዘና ያሉ ይመስላሉ።ወደ ረግረጉ ስዞር አማጺዎች እየሮጡ ነበር። ድንገት መሳሪያየን አንስቼ ተኮስኩ።
አንድ ሰው ገደልኩ፡፡ ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ ያየሁት እልቂት በጨረፍታ በአዕምሮየ ይመላለስ ጀመር። የሁለት ጓደኞቼ ሞት ውስጤን እየረበሸኝ ነበር የምተኩሰው። ብዙ ሰው ገደልኩ።
እንድናፈገፍግ ትዕዛዝ እስከሚሰጠን ድረስ መተኮሴን አላቆም ኩም ነበር።
የተሰው ጓደኞቻችንን መሳሪያ እና ጥይት ከወሰድን በኋላ ከዛው ጫካ ትተናቸው መጓዝ ጀመርን፡፡በዱር መሃል ቀስ ብለን
አድብተን ለተወሰነ ሜትሮች ከተጓዝን በኋላ ለሌላ የደፈጣ ውጊያ ተዘጋጀን። አሁንም አድፍጠን ጠበቅን፡፡ ጊዜው በምሽት እና ለሊት መሃል ነበር። አንድ ድንቢጥ ወፍ መዘመር ብትጀምርም
ሌሎች ሊከተሉዋት አልቻሉም:: እሱዋም አቆመች፤ ለሊቱ በፀጥታ ተዋጠ፡፡ ከአስር አለቃ ጎን ነበርኩ፡፡ አይኖቹ ከተለመደው
በላይ ቀልተዋል። የሚመጡ ሰዎችን ኮቴ ስንሰማ በተጠንቀቅ መጠበቅ ጀመርን። የተወሰኑ ታጣቂዎች ከቁጥቋጦ በመውጣት በዛፎች መሃል ራሳቸውን ከለሉ። ወደ እኛ ሲቀርቡ መተኮስ
ጀመርን። ፊት ለ ፊት የነበሩት ተኩሰን ከጣልነው በኋላ ሌሎቹን በረግረጉ በኩል ከተከተልናቸው በኋላ ጠፉን። ብዙ
አማጺዎችን ገደልን። ደማቸው የረግረጉን ውሃ ወደ ደም ለወጠው። አስክሬናቸውን
መሳሪያዎችን ወሰድን፡፡

አስክሬናቸውን አልፈራሁም ነገር ግን ተፀየፍኳቸው።በእግሬ አገላብጬ G3 መሳሪያ፣ ጥይቶች እና ሽጉጥ አገኘሁ::
ሽጉጡን አስር አለቃ ለራሱ አደረገ።ሟቾቹ አንገታቸው እና እጃቸው ላይ ጌጣ ጌጦች አድርገው ነበር። አንዳንዶቹ ከአምስት
በላይ የወርቅ ስዓቶችን እጃቸው ላይ አስረው ነበር። አንድ ፀጉሩ ያልተበጠረ ታዳጊ ደግሞ 'All eyes on me “ሁሉም አይኖች ወደ እኔ( ይመለከታሉ)” የሚል Tupac Shakur ቱፓክ ሻኩር ቲሸርት ለብሶ ነበር፡፡ የተወሰኑ አዋቂ ወታደሮች እና ጓደኞቼን ሙሳ እና ጆስያህን አጥተናል። ተረት አዋቂው ሙሳ አልፏል።
አጫዋቻችንን፥ ቀልድ አዋቂ እና ተረት ነጋሪው አሁን በምንፈልገው ጊዜ የለም! ተነጥቀናል። ጆስያህቱ ያኔ ከእንቅልፉ ባልቀስቅሰው እና የመጀመሪያው ስልጠና ቢያልፈው ዛሬ ባልዘመተ ነበር።

አመሻሽ ላይ መንደራችን ደርሰን የጦር መጋዝኑን ግድግዳ ተደግፈን ተቀመጥን፡ መንደሩ ጸጥታ ወርሶት ነበር። ጸጥታው
ያስፈራን ይመስል መሳሪያዎቻችንን ማፅዳት ዘይት መቀባት እና መገጣጥም ጀመርን። አዳዲስ መሳሪያዎችንን ወደ ሰማይ በመተኮስ ስንሞክርም ነበር። መክሰስ መብላት ብፈልግም አልቻልኩም ውሃ ጠጣሁ ግን ምንም አልተሰማኝም። ወደ ድንኳኔ ስገባ ከስሚንቶ ግድግዳ ጋር ተጋጪቼ ጉልበቴ ደማ።
አሁንም ምንም አልተሰማኝም ደንዝዥ ነበር፡፡ መሳሪያየን ድንኳኔ መውጫ ላይ አድርጌ በጀርባየ ተንጋልየ ተኛሁ።
አዕምሮየ ባዶ ሆነ፤ ምንም አይነት ሃሳብ ስሜት አልነበረኝም፡፡
በተዓምር እስክተኛ ድረስ የድንኳኑን ጣራ አንጋጥጬ ለደቂቃዎች አየሁ። በህልሜ ጆስያህን ከዛፍ ጉቶ ላይ ላነሳው ስሞክር አንድ ሰው ከበላየ ላይ ወጣብኝ። ግንባሬ ላይ መሳሪያ ሽጉጥ ደቀነ። ወዲያው
👍2
ከእንቅልፌ ባንኜ ነቃሁ እና ድንኳኔ
ውስጥ እንዳለሁ መተኮስ ጀመርኩ ጥይቶቼን እስከምጨርስ ለስላሳ ዙር ተኮስኩ። መቶ አለቃ እና አስር አለቃ መጥተው ወደ ውጭ ወሰዱኝ። አልቦኝ ነበር፤ ፊቴ ላይ ውሃ ከደፉብኝ በኋላ
ክኒን ስጡኝ። ሙሉ ለሊቱን ቁሜ አደርኩ። ለሳምንት ያህል መተኛት አልቻልኩም። ለተጨማሪ ሁለት ቀናት ለውጊያ
ወጥተን ነበር፤ መሳሪያየን ለመተኮስ አልተቸገርኩም::

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
😱1
#ዐዲስ_ገጽ

ያላለምኩት
ያልጠየኩት ኾነ !
ልቤ ጥበብ ገባው . . ፤
ምስጢርን ዐወቀ
ዐውቆ ተራቀቀ
ተራቆም ራቀ።

ሐሳቡን አፍታታ ፤ ሐሳቡን አናኘው
ጥያቄው ምሶ ፣ ምላሹን አገኘው።
በሐሳብ ተሞልቶ
በሐሳብ ተመርቶ
መጠየቅ ጀመረ ፤
ያልተፈቀደውን
የተደበቀውን
እየመረመረ።
እየመረመረ፤

በከፍታ ጕዞ . . .
ሽቅብ ተምዘግዝጎ ከኅዋው ላይ ዋለ
ከእርሱ ተገናኘ ከዚያም ይኼን አለ።
ጠቢቡ ሠለሞን . . .
“ከፀሓይዋ በታች ዐዲስ ነገር የለም ! "
ብሎ በመናገር .
የተሰጠው ኹሉ በከንቱ ከኾነ ፣
ከታችኛው ሳይኾን . . .
ከከፍታው ላይ ነው ፤ ሕልሙ የመከነ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍1
#ውሉድ_ወወላድ

የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ!ምግባሩን ካለየ።

ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መኾን ክብር በከንቱ አይሰጥም!
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም!

እፍኝትን እይዋት .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣በፍትወት መቃጠል።
አንበሳም ደቦሉን .
በጊዜው ካልቀጣ ንግሥናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል።

አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ፣
ካልተነጻጸረ፣
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የመኖር_ልኬ

ሰይጣን ከፈጣሪ እንዴት ይፏከራል?
እግዜርስ ከሰው ጋር እንዴት ይማከራል?

ድንቢጥ ሐሳብ ይዞ ከሰማይ ጋር መዋጋት
ደመና ላይ ምሎ ነፋስን መዘንጋት።

መርከብ ሳያበጁ መልሕቅ መወርወር
ከውቅያኖስ ጠልቆ ከውሃ መሰወር።

ጭላንጭሏ ኩራዝ ፀሓይን ረስታ
ጣራ አልባ ጎጆዋ ዝናብ ተመኝታ
ከማይችሉት መግጠም ከማይደርሱት ቦታ።

ውስጤ እንደዚህ ነው! የሚያግደረድረው
ሐሳቤ እንደዚህ ነው! የሚወዳደረው።
ስሜቴ ከልቤ እየተደበቀ
ነፍሴ ከምኞቴ እየተሳበቀ ፣

(ልቤ ትቢያ ቀረ . . .!)

ሚዛኑን ረስቶ እየተመዘነ
መመዘኛ ስቶ እየተተመነ ፣
ከማያሸንፈው እየተጋጠመ
የሽንፈቱን ጕዞ እየደጋገመ ፣
እየደጋገመ እየደጋገመ . . .
እያልጎመጎመ . . .!
ይኸው አለኹ አለ. .!

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሁለት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


ቀኖቼን በወታደራዊ ስራዎች ተጠምጄ ባሳለፍኩ ቁጥር የራስ ምታቴ እየተሻለኝ መጣ፡፡ ቀን ቀን ኳስ መጫወት ትቼ ጥበቃ
ላይ እሰማራለሁ። ነጩን ክኒን በብዛት አዘውትሬ እወስድ ነበር።
ክኒኖቹ ሱስ ሁነውብኛል። ብዙ ኃይል ይሰጡኛል። መጀመሪያ አብዝቼ የወሰድኩ ቀን በጣም አልቦኝ ሁሉንም ልብሶቼን አውልቄ ነበር። ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል፤ ዕይታየ ደበዘዘ ብዥታ
ለደቂቃዎች ያህል መስማትም አልቻልኩም። ያለ ምንም ስራ
መንደሩን እዞረዋለሁ፤ እረፍት የለኝም ብዙ ኃይል ይሰማኛል ነገር ግን ደንዝዣለሁ ስሜት አይሰማኝም፡፡ ክኒኑን አብዝቼ
መውሰዴን ቀጠልኩ።ምንም ነገር አይሰማኝም ብዙ ኃይል ከማግኘት እና ለሳምንት እንቅልፍ ካለመተኛት በስተቀር። ማታ ማታ ፊልም እናያለን። የጦርነት ፊልሞች፥ራምቦ፣ ፈርስት ብለድ፣ ራምቦ ሁለት፣ ኮማንዶ እና ሌሎች በጄነሬተር ወይም በመኪና ባትሪ በመታገዘ እንመለከት ነበር። ሁላችንም እንደ
ራምቦ መሆን እንፈልግ ነበር። እሱ ያደረጋቸውን እንቅስቃሴዎች ለመተግበር እንጓጓ ነበር።

ምግብ፣ መድሃኒት፣ ጥይቶች እና ጋዝ እያለቀብን ሲመጣ በከተማ፣ በገጠር መንደሮች እና በጫካ ውስጥ የሚገኙ
በር የአማጺዎችን ካምፖችን መውረር ጀመርን። ያልታጠቁ ሰዎች የሚገኝባቸውን ሌሎች መንደሮችን በማጥቃት ወታደሮችን መለመልን፡፡

“መልካም ዜና ደርሶናል ከመልዕክተኞቻችን የተወሰኑ አማጺዎችን ለመግደል እና በመጀመሪያም የእኛ የሆነውን ቁሳቁሳቸውን ለመውሰድ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ከዚህ እንቀሳቀሳለን” አለ መቶ አለቃ አዋጁን ሲነግር። ፊቱ ላይ ልበ ሙሉነት ይነበባል። ግንባራችን ላይ አረንጓዴ ጨርቅ አስረን
ነበር ታዳጊዎች ይመሩ ነበር። ምንም አይነት ካርታ ምንም አይነት ጥያቄም አልተነሳም:: ቀጣይ ትዕዛዝ እስከሚሰጠን ድረስ እንዲሁ መንገድ እንድንከተል ነበር የተነጋገርነው ሰርዲን ለመብላት እና ነጩን ክኒን ለመውሰድ ከቆምንበት ውጭ ለብዙ ሰአታት
ያለማቋረጥ ተጓዝን፡፡ ክኒኖቹ ብዙ ኃይል
ከመስጠታቸውም በላይ ደፋር አደረጉን፡፡ የሞት ሃሳብ በጭራሽ ወደ አዕምሮዬ አልመጣም፡፡ መግደል ግን ውሃ እንደመጠጣት ቀላል ሆነ። የመጀመሪያውን ሰው ስገድል ብቻ ልቤ ተነክቶ ነበር። ከዛ በኋላ ግን ምንም አይነት ሃዘን ፀፀት አልተሰማኝም::
ከበላን በኋላ መድሃኒቱን ወስደን አዋቂዎች ለተወሰነ ደቂቃ እረፍት እስኪወስዱ ዙሪያውን ለጥበቃ እንሰማራለን። ከ አልሃጂ ጋር ነበርኩ፡፡ የጥይት መያዣውን በፍጥነት መቀየርን
እየተወዳደርን ነበር።

“ቆይ አንድ ቀን ልክ እንደ ራምቦ ብቻየን አንድ ሙሉ መንደር እቆጣጠራለሁ” አል ሃጂ ፈገግ እያለ እቅዱን ነገረኝ።

ልክ እንደ ኮማንዶ ፊልም የራሴ ባዙቃ እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ። ያምራል።” አልኩ እና አንድ ላይ ሳቅን፡፡

ወደ አማጺዎች ካምፕ ከመግባታችን በፊት መንገዳችን ቀይረን በጫካው ውስጥ በመጓዝ አሰሳ አናደርጋለን፡፡ ካምፑ ዕይታችን ውስጥ ከገባ በኋላሸ ከበባ እናደርግ እና የመቶ አለቃን ትዕዛዝ
እንጠብቃለን። አማጺዎች ከአንዱ ወደ አንዱ ይንቀሳቀሳሉ ፣ሌሎቹ ግድግዳ ተገድፈው ሲቀመጡ እንደእኛ ያሉ ታዳጊዎች ደግሞ ይጠብቃሉ:: አማጺዎችን ባየኋቸው ቁጥር ደሜ
ይፈላል፤ እናደዳለሁ። አማጺዎቹ ቤተሰቤን ያጣሁበትን መንደር አውድመው ካርታ የተጫወቱት ይመስሉኛል። ስለዚህ መቶ አለቃ ትዕዛዝ ሲሰጥ የቻልኩትን ያህል እተኩሳለሁ። ንዴቴ አይወጣልኝም! ከተኩስ በኋላ ወደ ካምፑ እንገባለን፡፡ የቆሰሉትን
እንገድላለን ፤ ቤት ውስጥ ገብተን ጋዝ፣ አደንዛዥ እፆች፣ ጫማ፣የእጅ ስዓቶች፣ ሩዝ፣ ዓሳ፣ ጨው እና ሌሎች ነገሮችን
እንሰበስባለን።ያልታጠቁ ሰዎችን (ሲቪል) ሰብስበን የዘረፍነውንእንዲሸከሙ እናደርጋለን።

“እኛ” መቶ አለቃ ወደ እኛ እየጠቆመ ” ልንጠብቃችሁ ነው እዚህ ያለነው። ምንም አይነት ጉዳት እንዳይደርስባችሁ የምንችለውን እናደርጋለን።” አለ ወደ ያልታጠቁት ሰዎች እየጠቆመ።
“የእኛ ስራ ጥብቅ ነው፤ ሃገራቸውን ለመጠበቅ ምንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ጎበዝ ወታደሮችም
አሉን። እኛ እንደ አማጺዎች አይደለንም። እነዛ ነፍስ ገዳዮች ያለ ምንም ምክንያት ሰው ይገድላሉ፤ ሁሉንም ሰው በጅምላ
ይጨፈጭፋሉ። እኛ ግን የሃገራችንን ለመጠበቅ፤ አገራችን ከእነሱ ክፋት እና ጥፋት ለማዳን ስንል ብቻ እንገድላቸዋለን።ስለዚህ ለእነዚህ የሃገራችሁ ጠባቂዎች ክብር ስጡ” ብሎ መቶ አለቃ ረጂም ንግግር አደረገ። ንግግሩ ሁለት ዓላማ ነበረው።
አንዱ በሲቪሎች ስለ እኛ ጥሩ አመለካከት እንዲኖራቸው ማድረግ ሲሆን ሌላው ደግሞ የእኛን ሞራል መገንባት ነበር።ጠበንጃየን ይዤ ቁሜለሁ። ልዩ የመሆን ስሜት ተሰማኝ፣የተፈላጊነት ፤ አንድ ትልቅ እና ጥብቅ ነገር ተሳታፊ መሆን እና ከአሁን በኋላ ደግሞ ከማንም አልሸሽም።ሽጉጤ አለኝ አስር አለቃ ሁልጊዜ እንደሚለው “ ይሄ መሳሪያ በዚህ ጊዜ የሃይላችሁ ምንጭ ነው:: ይጠብቃችኋል! እንዴት መጠቀም እንዳለባችሁ ካወቃችሁ ደግሞ የምትፈልጉትን ሁሉ ይሰጣችኋል።
መቶ አለቃ ንግግሩን ለማድረግ ምን እንደገፋፋው አላስታውስም። ብዙ ነገሮች ያለ ምንም ምክንያት ወይም ማብራሪይ ይሰሩ ነበር። አንዳንዴ ፊልም እያየን መሐል ላይ ድንገት ለጦርነት እንድንቀሳቀስ እንጠየቃለን። ከስዓታት በኋላ እንዳልተፈጠረ ከማስታወቂያ በኋላ እንደተመለስ ፊልሙን ካቆምንበት
እንቀጥላለን። ሁሌም ውጊያ ላይ ነን ወይ የጦርነት ፊልም እየተመለክትን ነው ወይ ደግሞ አደንዛዥ ዕፅ እየወሰድን ነው።
ብቻችን የምንሆንበት የምናስብበት ምንም አይነት ጊዜ የለም::እርስበርሳችን ስናወራ የምናወራው ስለተመለከትነው የጦርነት ፊልሞች እና መቶ አለቃ፣ አስር አለቃ ወይም ከእኛ አንዳችን ስለፈፅምነው ጀብድ ብቻ ነበር። ከዛ ውጭ ሌላ አለም ያለ አይመስለንም ነበር።

ከመቶ አለቃ ንግግር በኋላ ተራ በተራ ምርኮኞችን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደልን። አማጺዎችን ስንገድል የቤተሰቦቻችን ገዳዮች የተበቀልን ይመስለን ነበር። በፍጥነት የመግደልም ውድድር
ነበር፡፡እኔ አንዱን ምርኮኛ በፍጥነት ስለገደልኩ ተጨበጨበልኝ።ትልቅ ገድል እንደፈፀምኩ ተሰማኝ ። ለእኔ እና ኬን ታናሽ መቶ አለቃ እና ታናሽ ሐምሳ አለቃ የሚል ማዕረግ በቅደም ተከተል
ተሰጠን። ደስታችንን አደንዛዥ ዕፅ እና የጦርነት ፊልም በማየት ገለፅን፡፡

የግሌ ድንኳን ነበረኝ እንቅልፍ ስሌለኝ ተኝቼበት አላውቅም።አንዳንድ ቀን በውድቅት ለሊት ለስለስ ያለው ንፋስ ላንሳ የሚባል ጓደኛየን ዝማሬ ያስታውሰኛል። ዛፎቹ የእሱን ዝማሬ
ሚያንሾሻሽኩ ይመስላሉ:: ትንሽ ካዳመጥኩ በኋላ ደጋግሜ
እተኩስ እና ድምጹን አስወግዳለሁ ።

በምርኮ ይዘን ወደ ዋና ማዕከላችን የቀየርነው መንደር እና በጉዞችን የምናድርባቸው ጫካዎች ቤቴ ሆኑ፡፡ የጦር ጓዶቼ ቤተሰቤ ! መሳሪያዬ የፈለኩትን ማገኝበት እና ጠባቂየ ሲሆን
መግደል ወይም መገደል ደግሞ የምኖርበት ህግ ወይም ደንብ ሆነ። ሃሳቤ ከዚህ በላይ አይሻገርም። ከሁለት አመታት በላይ ተዋጋን መግደል የሌተ ቀን ተግባራችን ሆነ፡፡ ለማንም አላዝንም:: እንደልጅ ሳልኖር ልጅነቴን ሳላውቀው ሳላጣጥመውም ነጎደ። የቀን እና ለሊቱን መፈራረቅ ማውቀው በፀሐይ እና
ጨረቃ መውጣት ወይም መጥለቅ ብቻ ነው። እሁድ ይሁን አርብ ግን አላውቅም::

ህይወቴ ጤናማ ይመስለኝ ነበር። ጥር 1996 አስራ አምስት አመት ሲሞላኝ ግን ይሄ መቀየር ጀመረ

አንድ ቀን ሃያ የሚሆኑ የጦር ጓዶቼን ይዤ ጥይት ለማግኘት ባውያ ወደ ምትባል
👍1
ትንሽ ከተማ ሄድኩ፡፡ በደቡብ በኩል የአንድ ቀን የእግር ጉዞ ነበረ። ጓደኞቼ አል ሃጂ እና ኬን ም ከእኔ ጋር ነበሩ።ከዛ የተመደበውን ጁማህን ለማየት ጓጉተን ነበር። የውጊያ ገጠመኞቹን እና ስንት ሰው እንደገደለ መስማት ፈልገናል። መቶ
አለቃንም ማግኘት ፈልጌ ነበር። ስለ ሼክስፔየር ለማውራት ጊዜ ይኖረናል የሚልም ተስፋ ነበረኝ፡፡

በአቧራማው መንገድ ዳር እና ዳር ሁለት ረድፍ ሰርተን ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ደም በለበሱ አይኖቻችንን እያየን መጓዝ
ጀመርን። ጀንበሯ ስትዘቀዝቅ ወደ ባውያ ከተማ ዳርቻ ተቃረብን። እኛ እዛው ስንቆይ አዛዣችን ወደፊት ሄደ። ከተወሰኑ
ደቂቃዎች በኋላ ወደ ከተማው እንድንገባ ምልክት ሰጠን፡፡


ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሶስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን
ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን ሰላምታ ከተሰጣጣን በኋላ ጁማህን መፈለግ
ጀመርን። ፊቱን ወደ ጫካው ያዞረ ጡብ ቤት ደጃፍ ላይ ዥዋዥዌ ላይ ተቀምጦ ነበር። ከጎኑ መሳሪያ ነበር። ቀስ ብለን ወደ እሱ ስንጠጋ ፊቱን አዞሮ አየን።

ከባድ መሳሪያ ይዘህ ነው ምትዞረው ማለት ነው?” ብሎ አል ሃጂ ቀለደ።

“እንግዲህ ምን ታረገዋለህ! ከ AK ከፍ እያልኩ ነው” ብሎ መለሰ።ሁላችንም ሳቅን።

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እንደምንመለስ ነግረነው ጥይት እና ምግብ ልንጭን ወደ መጋዝን ሄድን።መጋዝን እያለን አዛዣችን፥ መቶ አለቃ “ዛሬን ከዚህ እደሩ፤ እራት ተዘጋጅቷል” እንዳለ ነገረን፡፡ አልራበኝም፡ ስለዚህ ኬን እና አል ሃጂ ወደ እራት
ሲሄድ እኔ ተለይቼ ወደ ጁማህ ተመልሼ ሄድኩ። ማውራት ከመጀመሩ በፊት ለደቂቃዎች ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡

ነገ በጥዋት ለውጊያ ስለምወጣ ከመሄዳችሁ በፊት አላይህም” ብሎ ዝም አለ እና መሳሪያውን እየነካካ ቀጠለ:
የዚህን መሳሪያ ባለቤት ገደልኩት።
ብዙዎቻችንን ከገደለ በኋላ ነበር የደረስኩበት። ከዛ በኋላ ነበር እኔ የያዝኩት ”ብሎ ፈገግ አለ፡፡ እጃችንን አጋጨንና ሳቅን።ወዲያውኑ እንድንሰበሰብ ተጠራን:: ተሰባስቦ መጫወቻ እና
የአዛዦችን መተዋወቂያ ማህበራዊ ፕሮግራም ነበር። ጁማህ መሳሪያውን በአንድ እጁ ከያዘ በኋላ በሌላ እጁ ጫንቃየ ላይ አድርጎ አቅፎኝ ወደ መሰብሰቢያው ሜዳ ሄድን።ኬን እና አል
ሃጂ ከዛው እያጨሱ ነበሩ። መቶ አለቃም በቦታው ነበር። ትንሽ ፈንጠዝያ ነበር። የመቶ አለቃ ጓደኞች አብዛኞቹ ማለትም ሃምሳ አለቃ ማንሳራይ እና አስር አለቃ ጋዳፊ ሙተዋል። እሱ እንዴት
እንደተረፈ አይታወቅም። በተዕምር ምኑም ሳይነካ የለአንዳች ጠባሳ ተርፎ ሌሎች ሃይለኛ እና ታዛዥ ጓዶችን በሞቱ ጓደኞቹ ምትክ ለማፍራት በቅቷል።መቶ አለቃ ጋር ስለ ሼክስፔየር ማውራት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን እሱ በማስተባበር ፤ ሰላም በመስጠት ተጠምዶ ነበር። በመጨረሻ እኔ ፊት ለ ፊት ሲደርስ
እጄን ጥብቅ አርጎ ያዘና “ማክቤዝ አይበገርም፧ ታላቁ የብሪያም ጫካ ዶንከን ኮረብታ እስኪደርስ ድረስ ማክቤዝ እጅ አይሰጥም አለ።

ጮክ ብሎ ”ልለያችሁ ነው ጓዶች” አለ። እጅ ከነሳን በኋላ እጁን እያውለለበ ሄደ። እኛም መሳሪያችን ከፍ አድርገን በጩኸት
ሰላምታችን ገለጸን። መቶ አለቃ ከሄደ በኋላ የሴራሊዮንን ብሄራዊ መዝሙር መዘመር ጀመርን። “ከፍ አድርገን
እናከብርሻለን፤ የነጻ ህዝቦች ሃገር፤ ጥልቅ ነው ለአንቺ ያለን ፍቅር” ለሊቱን ሙሉ ስንጫወት ስናወራ አሳለፍን።
ከመንጋቱ በፊት ጁማህ እና የተወሰኑ ወታደሮች ለውጊያ ሄዱ። አል ሃጂ፣ ኬን እና እኔ በሚቀጥለው ጥየቃ ብዙ
እንደምንጫወት ቃል ገብተን ተሰናበትነው:: ጁማህ ፈገግታ ካሳየን በኋላ መሳሪያውን ጠበቅ አድርጎ ከያዘ በኋላ ወደ ጫካው ገባ፡፡

ከትንሽ ስዓታት በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ወደ መንደር መጣ፡፡ ዩኒሴፍ UNICEF የሚል ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ የለበሱ
አራት ሰዎች ከመኪናው ወርደው ወደ እኛ መጡ። አንድ ነጭ እና ቆዳዋ ነጣ ያለ ምንአልባት የሊባኖስ ሰው እና ሌሎቹ የሃገሩ ሰዎች ሴራሊዎናውያን ናቸው:: ጦርነቱን ያዩ አይመስሉም የተመቻቸው ነበሩ። ወደ መቶ አለቃ ተልከው የመጡ ይመስላሉ። እሱም ሲጠብቃቸው ነበር፡፡ ቤት ደጃፍ ተቀምጠው ሲያወሩ ከማንጎ ዛፍ ስር ተቀምጠን መሳሪያችንን
እየወለወልን እናያቸው ነበር። በኋላ መቶ አለቃ ከሁለቱ የውጭ ሃገር ሰዎች ጋር እጅ ተጨባበጠ፡፡ ጠባቂው ወደ እኛ መጣ እና እንድንሰለፍ ነገረን። ሰፈሩን እየዞረ ከ “ መቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው!” ትዕዛዝ መቀበል እና የታዘዝ ነውን መፈፀም ለምደናል። ወደ ጎን መስመር ሰርተን መጠበቅ ጀመርን።

መቶ አለቃ ከፊታችን ቁሞ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠን፡፡ ሌላ ግዳጅ እየጠበቅን ነበር፡፡ “አሳርፍ” ብሎ ቀስ ብሎ መራመድ
መቃኘት ጀመረ፡፡ እንግዶቹ ከጀርባ ነበሩ።
“ስጠቁም ወደ ጠባቂየ በመሄድ ትሰለፋላችሁ ገብቷችሃል።”ሲል “አዎ! አለቃ” ብለን ጮህን፡፡

“አንተ፣ አንተ.....” መቶ አለቃ እየመረጠ እስከ ሰልፉ መጨረሻ ደረሰ፡፡ መቶ አለቃ እኔን ሲመርጠኝ አትኩሬ ተመለከትኩት።
እሱ ግን አላየኝም:: አል ሃጂም ተመረጠ። ኬን ግን ትልቅ ስለሆነ አልተመረጠም:: “መሳሪያችሁን የጥይት ካዝና አወላልቃችሁ መሬት ላይ አስቀምጡ” የሚል ትዕዛዝ ከመቶ አለቃ ሰጠ፡፡ መሳሪያችንን አወላልቀን መሬት ላይ አስቀመጥን።መቶ አለቃን ተከትለን እንግዶች ወደ የመጡበት ገልባጭ መኪና ሄድን። መቶ አለቃ ፊቱን ወደ እኛ ሲያዞር ቆምን “ ጎበዝ ጀግና
ወታደር ነበራችሁ! ታውቃላችሁ የዚህ ወንድማማችነት እና ሃገርን የማዳን ጥሪ አካል እንደነበራችሁ። ከእናንተ ጋር ሃገሬን
በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል። ኮርቼባችዋለሁ። አሁን ስራችሁ
እዚህ ጋ ያበቃል። ልለቃችሁ ይገባል። እነዚህ ሰዎች ትምህርት ቤት ያስገቧችኋል፤ ሌላ መልካም ህይወት እንዲኖሩዋችሁ ይረድዋችኋል።” ይሄን ብቻ ነበር ተናግሮ ትቶን ሄደ:: ቀጥሎ
ፍተሻ ነበር። ሰንጢ እና ቦምብ ይዤ ስለነበር መፈተሽ አልፈለኩም፡ ፈታሹን ብትነካኝ እገልሃለሁ ብየ ዛትኩበት። ከእኔ
ጎን ወደ አለው ቀጠለ።

ምን እየሆነ እንዳለ አልገባኝም? መቶ አለቃ ለእነዚህ ሰዎች ለምን አሳልፎ ሊሰጠን እንደወሰነ አልገባኝም። ጦርነቱ እስኪበቃ ድረስ የምንቀጥል መስሎን ነበር፡፡ ግን ያለምንም ማብራሪያ
ተወሰድን፡፡

መኪና ውስጥ የደንብ ልብሳቸው ንጹህ እና መሳሪያቸው አዲስ የሆነ ሶስት ፖሊሶች ነበሩ። ፖሊሶቹ ከገልባጩ ወርደው እኛ እንድንወጣ ጠቆሙን። ወጥተን ሁለት አግድም ወንበሮች
ላይ ፊት ለ ፊት ተቀመጥን። ፖሊሶች መውረጃው ላይ ተቀመጥን።

አል ሃጂ እና እኔ በመገረም በብስጭት ተያየን። የት እንደሚወስዱን እንኳ አናውቅም። ለስዓታት ተጓዝን። ያለምንም ስራ ቁጭ ብሎ መጓዙ አድካሚም
አሰልቺም ነበር፡፡ መኪናውን ጠልፎ ወደ ባውያ ለመመለስ አሰብኩ። መሳሪያውን ለመንጠቅ ስዘጋጅ መኪናው ለፍተሻ
ፍጥነቱን ቀንሶ ፖሊሶቹ ወረዱ።
መቀመጥ ስላልቻልኩ በጉዞ በሙሉ እረፍት አልነበረኝም ያቁነጠንጠኝ ነበር። የፍተሻ ጣቢያዎች ስንደርስ ትንሽ ፈታ እል ነበር። በመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያ ያገኘናቸው ወታደሮች የሚያምር ደንብ ልብስ የለበሱ መሳርያቸው አዲስ ነበር።

በኮሮኮንች መንገድ የመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያውን አልፈን እንደሄድን የተጨናነቀ የአስፓልት መንገድ ደረስን። ዙሪያውን
መኪኖች በተለያየ አቅጣጫ ሲጓዙ አየሁ፡፡ በህይወቴ የዚህን ያህል ብዙ መኪኖች አይቼ አላውቅም፡፡ መርሰዲሶች፣ቶዮታዎች፣ማዝዳዎች፣ቼርቮያለ ትዕግስት ሲያጮሁ ሙዚቃ ሲያጫውቱ ነበር፡፡ የት እንደምንሄድ አሁንም አላውቅም ነገር ግን Freetown ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ እንዳለን
አውቂያለሁ።ለምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም፡፡

ውጩ እየጨለመ ነው። መኪናችን በዝግታ ወደ ተጨናነቀው መንገድ ሲገባ የመንገድ መብራቶች ተራ በተራ
እንደፍንጣቂ ነገር ቦግ ቦግ እያሉ መብራት ጀመሩ። የሱቆች እና
የመጠጥ ቤት መብራቶች ሳይቆጠር ብዙ መንገድ መብራቶች ከተማዋን አንቆጥቁጠዋታል። የከተማዋ ፎቆቹም በብዙ ብርሃን የተንቆጠቆጡ ናቸው። ለተወሰኑ ደቂቃዎች በፍጥነት
👍1
ከተጓዝን በኋላ መኪናዋ ቆመች፡፡ ከመኪና ወርደን አራት የ ዩኒሴፍ UNICEF ሰራተኞችን ተከትለን አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ገባን።
ግቢው ብዙ ቤቶች አሉት:: በእኛ እድሜ የሚገኙ ታዳጊ ወንዶችን ደጃፍ ላይ ራሳቸውን አጉብጠው ተቀምጠዋል። ሊያዩን አልፈለጉም፧ ለምን ከዚህ እንደመጡ አላወቁም፥ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሊባኖሳዊ የሚመሰለው ሰውየ ወደ አንዱ ቤት በመውሰድ ከዛ እንደምንቆይ እና የምንተኛበትን አልጋ አሳየን።
በየኣንዳንዳችን ቁም ሳጥን ውስጥ ሳሙና፣ የጥርስ ሳሙና፣ የጥርስ ቡርሽ፣ ፎጣ እና ንጹህ ቲ ሸርት እንደተቀመጠ በደስታ ነገረን፡፡ ነገ ደግሞ ጫማ ትውስዳላችሁ አለ። ምንም አይነት
ስሜት አላሳየንም፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አትሮኖስ pinned «#ለኀጥአን_የመጣ #ክፍል_አስራ_ሶስት #የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ #በኢስማኤል_ቤህ #ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን…»
#እስኪምን_አለበት !?

ፈገግታሽ . . .
እንደ በጋ መብረቅ
አንዴ ብልጭ ብሎ ፣ ዓመት የሚቀድስ
ዘመን የሚያስቀድስ ፤

ሣቅሽ . . .
ደራሽ አውሎ ነፋስ ፤
ሐዘን ግብስብሱን ባ'ንደዜ የሚያድስ።

እንባሽ . . .
የጤዛ ጠብታ ፣
ካ'ስፈሪው ዝናብ ላይ እፍታን ጨልፎ
እምቡጥ ጉንጮችሽ ላይ በጨረፍታ አርፎ
( ዕፎይታ የሚሰጥ ፤ ገጸ ውበት ኾነ ! )

ዝምታሽ . . .
ልክ እንደ ደመና ፤
የፀሓዩን ንዳድ ፣ የጨረቃን ጮራ
ሰማይና አድማሱን . . .
በግርዶሽ ያስረዋል አንዳች ሳያወራ።

ታዲያ ምን አለበት . . .?!
አንድ ጊዜ ብቻ ፣
አንድ'ዜ ብቅ ብለሽ
ከጎጄዬ መጥተሽ
ከ'ልፍኜ ተገኝተሽ
ቤቴን ብታደምቂው ፤

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ሕገ_ደንብ

ከጥቁሩ ሰሌዳ . . .
ከጨቅሎች ፊትለፊት ፤
እንደ'ዚኽ ተጻፈ .
ከጨዋታ በፊት።

"በተሰጣችኹ መብት
እዉነትን መስክሩ
ሐቃችኹን አውሩ ! "
ብሎ እንዳ'ሠመረ ፤
"ሕጉ ለእኔ አይሠራም!"
ብሎ ተናገረ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የፈጣሪ_ልሳን

እጆቼን ዘርግቼ . . .
ልጸልይ፣ ልማልድ ፣ ከደጅኽ ተገኘኹ፤
አንጋጥጬ ሽቅብ በሐሳቤ ዋኘኹ።
ተንበርክኬ ለምሕላ በግንባሬ ተደፍቼ
ቀና ማለት ተዘነጋኝ ፤ የቃል ጸሎት ረስቼ።

ያ'ንደበትኽ ልሳን ከየት ተሠወረ?
ቃል ከምላሴ ላይ እንደምን ታወረ ?
ዝም ...!
ዝም ዝም . . .!
እንደው ዝም! ዝምታዬ ቀረ ፤
ሰምተኸኛል አንተ ፤
በዝምታ ልሳን ጸሎቴም ሰመረ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_አራት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


“ኑ ወደ ማዕድ ቤት ትንሽ ምግብ ያስፈልጋችኋል።” አለ ሴራሊዮናዊው የዩኒሴፍ ሰራተኛ፡፡ ተከተልነው።

በማዕድ ቤቱ ውስጥ አግድም ወንበርአ ላይ ከሌሎች ልጆች ጋር ተቀመጥን። ሩዝ በጎድጓዳ ስሃን ቀረበልን፡፡ እሱን ያለምንም
ፋታ መብላት ጀመርን። አል ሃጂ ከየት ናችሁ ብሎ እስከሚጠይቅ ድረስ ምንም አላወራንም: አል ሃጂ ሲጠይቃቸው
ደስተኛ አልነበሩም:: ማነህ አንተ? ያንተን ጥያቄ ልንመልስ ነው የመጣነው?” ሲል አል ሃጂ ተነስቶ ገፈተረው። ልጁ ተነስቶ
ሊደባደብ ሲል አንድ ሰው ተዉ ልጆች!” አለ።

ቦምብ አውጥቼ ይሄ የመጨረሻችሁ እንዲሆን ነው የምትፈልጉት ወይስ ጥያቄውን ትመልሳላችሁ?” አልኩ፡፡

ከኬኖ ወረዳ ነው የመጣነው”
“አልማዝ ከሚገኝበት አካባቢ?” አለ አል ሃጂ።
“ከጦሩ ጋር ነው ወይስ ለአማጺዎች ነው የተዋጋችሁት?”
ምኔ አማጺ ይመስላል? ለጦሩ ወግኜ ነው የተዋጋሁት።
አማጺዎች መንደሬን አቃጥለው ወላጆቼን ገለዋል፤ አንተ ግን እነሱን ትመስላለህ።”

በአንድ ወገን ነዋ የተዋጋነው” አለ አል ሃጂ። ተቀመጥን።ቦምቡን እንደያዝኩት ነበር። ፊቴን ወደ ማዕድ ቤቱ ያመጣን
ሰውየ አዙሬ “ መቶ አለቃ ለምን ለእነዚህ ያልታጠቁ ሴታ ሴት ሰዎች አሳልፈው እንደሰጡን ታውቃለህ?” ብየ ጠየቅኩት።
በፍርሃት ርዶ፣ በላብ ተጠምቆ ሊመልስ ሲል አንዱ ልጅ “ እሱ ያልታጠቀ ነው ሌሎች ልጆችን እንጠይቃቸው”አለ። ማቡ ይባል ነበር በኋላ ጓደኛሞች ሁነናል፡፡ ተነስተን ቤት ደጃፍ ላይ ወደ ተቀመጡት ታዳጊዎች ሄድን፡፡

“ጓዶች አዛጋችሁ ለምን ለእነዚህ ሰዎች እንደሰጡዋችሁ ታውቃላችሁ?” ብሎ አል ሃጂ ጠየቀ። ዝም አሉ፡፡ “ኣትሰሙም
እንዴ?

“ማንም እንዲያስቸግረን አንፈልግም” አለ በሸካራ ድምጸ።በዛ ላይ ላልታጠቀ ተራ ሰው ጥያቄ መልስ መስጠት አንፈል
ግም።”

“ተራ ሰው ሲቪል አይደለንም! አለ ማቡ በቁጣ።” ተራ ያልታጠቀ ሰው ካለ እናንተ ናችሁ። መለዮ እንኳን ያልለበሳ
ችሁ። ምን አይነት ወታደር ነው መለዮ ማይለብሰው ባካችሁ?!”

“ለአማጺዎች ነው የተዋጋ ነው፤ ጦሩ ጠላታችን ነው።ለነጻነት ነው የተዋጋነው! ጦሩ ቤተሰቤን ገድሏል መንደሬንም
አፍርሷል፡፡የጦሩን አባላት ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ እገላለሁ”ብሎ ተነሳ።

“አማጺዎች” ብሎ ማቡ ጮኸ። ሰንጢዎቻችን አውጥተን ተፋጠጥን፡፡ እንደገና ጦርነት! ፈረንጆቹ ቦታ ስለቀየርን ከጦር ቀጠና ስለተገለልን ብቻ ደህና የምንሆን መስሏቸዋል።አዕምሮችን የተበረዘ አደገኛ ነፍሰ ገዳይ መሆናችንን አላወቁም! አሁን በቀላሉ እንደማናገግም ይገባቸዋል።

ቦምብ ወረወርኩ ግን ዘገየ፡፡ ድብድቡ ቀጠለ አንዳንዶቻችን ሰንጢ ይዘን ሌሎች በባዶ እጅ መታገል ጀመርን። አንዱን እግሩን ወጋሁት ሌላው እኔን ሊወጋ ሲል አል ሃጂ ቀድሞ ከጀርባ ወጋው፡፡ የጮኸ ወይም ያለቀስ የለም ሁላችንም ለምደነዋል በዛ ላይ አደገኛ ዕፅ ወስደን ነበር፡፡ ፖሊሶቹ “አቁሙ አቁሙ” እያሉ
ወደ እኛ መጡ፡፡ከአገላገሉን በኋላ የወደቀውን ሊያነሱ ሲጎነበሱ ገፍትረን ጥለን መሳሪያቸውን ቀማን። ማቡ ተኩሶ የተወሰኑትን ገደለ ሌሎችን ደግሞ አቆሰለ፡፡ አማጺዎች ከእኛ ወገን ሁለት
ታዳጊዎችን ገደሉ፡፡ ፖሊስ ወደ ሰማይ ቢተኩስም መታገል አላቆምንም:: ስለዚህ በጉልበት ለያዩን መሳሪያ ድቅነው
አቆሙን። አምቡላንስ እየጮኸ መጥቶ የተጎዱትን ወሰደ።ስድስት ታዳጊዎች ሲሞቱ ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ ብዙዎች
ቆሰሉ።

በማቡ ጀብድ ተገረምን፤ማዕድ ቤት ተመልሰን ስለእሱ ነበር የምናወራው። አንዱን ልጅ አይኑን መትቶት ልጁ ቡጢ ሊመልስ ቢፈልግም ማቡን ማየት አልቻለም። ድብድብ ረብሻው ለእኛ
ጨዋታ ነበር። ከማዕድ ቤት አውጥተው ወሰዱን። የጦር መኪና እየጠበቀን ነበር፡፡ “ወደ ጦርነቱ ሊመልሱን መሆን አለበት::” አለ አል ሃጂ። ዝም ብለን ብሔራዊ መዝሙሩን መዘመር ጀመርን::ወደ ጦርነቱ አልመለሱንም ነገር ግን ቤኒን ቤት ወደ ሚባል ሌላ የማገገሚያ ማዕከል ነበር የወስዱን፡፡ ለምን ወደ እዚህ ቦታ
እንደመጣን አሁንም አላወቅኩም፡፡ G3 ሽጉጤ፣ የጦርነት ፊልም እና የምወስደው ክኒን ትዝ ይለኛል። ከሁሉም በላይ መቶ
አለቃ “ከአሁን በኋላ ያገኘነውን አማጺ እንገላለን፧ ምህረት ምርኮኛ የሚባል ነገር የለም”የሚለው ንግግር ወደ አዕምሮየ
ይመላለስ ነበር።

ባልታጠቀ በሲቪል መታዘዝ ያበሳጫል፡፡ ድምጻቸውን መስማት እንኳ አልፈልግም:: ለቁርስ እንኳ ሲጠሩን ሳጥን ያገኘሁትን ነገር በቡጢ እመታለሁ። ከመመገብ ውጭ የታዘዝነውን አንፈፅምም ነበር።
እንቢተኛ ነበርን! ቁርስ ሻይ እና ዳቦ፣ ምሳ እና እራት ደግሞ ሩዝ እና ሾርባ እንበላ ነበር። መሳሪያችን እና አደገኛ ዕፅ ከእኛ
ጋር ስላልነበር ደስተኞች አልነበርንም።

ተደጋጋሚ የጤና ምርመራ እና የምክር አገልግሎት በነርሶቹ እና ሌሎች ሰራተኞች ይደረግልን ነበር፡፡ አንወደውም ነበር፡፡ ገና
ሲጀምሩ ያገኘነውን እቃ እንወረውራለን እንደበድባቸዋለን።ከምግብ በኋላ ያለምንም ምክንያት እንደባደብ ነበር። ሰራተኞቹ ምንም ብናደርግ እነሱን እንኳ ብንደበድባቸው አያዝኑብንም።
“የእናንተ ጥፋት አይደለም እንደዚህ ልታደርጉ የቻላችሁት”ብለው ፈገግታ ያሳዩናል።በእኛ ተስፋ ላለመቁረጥ የተስማሙ ይመስላሉ።

የራስ ምታት ማይግሬን እንደገና ተንስቶ ያሰቃየኝ ጀምሯል። አንጥረኛ በመዶሻ ራሴን የሚቀጠቅጥ ይመስለኛል።
አንዳንድ ቀን ራሴን መቆጣጠር ከብዶኝ መሬት ላይ እንከባለላሁ:: አል ሃጂ ደግሞ የቤቱን ምሰሶ በመደብደብ ሆስፒታል ገብቶ ነበር፡፡ ቆይቼ እኔም ራሴን ስቼ ሆስፒታል ገባሁ:: ሰውነቴን ሙሉ ያመኝ ነበር፤ ጉሮሮየ ደርቆ የማጥወልወል ስሜት ይሰማኝ ነበር። ነርሷ ፈገግታ እያሳየች ወደ እኔ አልጋ መጥታ መርፌ ወጋችኝ። አካሌ ተዳክሞ ተኛሁ።
በሚቀጥለው ቀን ከሆስፒታል ወጣሁ። ነርሷ ውሃ በደንብ ጠጣ አለች::

አንዳንዴ ከማጥወልወል ስሜት እና ድንገት እራስን ስቶ ከመውደቅ ባለፈ ከሁለት ወር በኋላ በአብዛኛው እየተሻለን
መጣ፡ የጦርነቱ መጥፎ ትዝታዎች ትርፍ ጊዜ ስለነበረን ወደ አዕምሮዋችን እየመጣ ያስጨንቀን ነበር። ይሄን ለማስረሳት ይመስላል ትምህርት ትጀምራላችሁ ተብለን የትምህርት
መሳሪያዎች ተሰጠን። ደብተር፣ እስክርቢቶ እና እርሳስ ከተሰጠን በኋላ ከሰኞ እስከ አርብ ከአራት ስዓት እስከ አስራ ሁለት ስዓት ትምህርቱ እንደሚሰጥ ተነገረን።ወዲያው ግን የተሰጠንን የትምህርት መሳሪያዎች አቃጠልን።
እንደገና ተሰጠን። እንደገና አቃጠልነው፡፡

አንድ ቀን ቀትር ላይ የማገገሚያው ሰራተኛች የተወሰነ የትምህርት መሳሪያዎች ደጃፍ አስቀምጠው ሂዱ። ማቡ የትምህርት መሳሪያዎችን አየና ለምን አንሸጠውም የሚል ሃሳብ
አመጣ። “ማን ይገዛናል? ሰዎች ይፈሩናል? አለ አንድ ታዳጊ ልጅ፡፡ “የሚረከበን ነጋዴ እንፈልጋለን” አለ ማቡ። በፕላስቲክ ቦርሳ ተሸክመን ቅርብ ወደ ሚገኝ ገቢያ ወስደን ለአከፋፋይ
ሸጥነው:: “ብዙ ገንዘብ ነው ያገኘነው” አለ ማቡ። ምሳ እንዳያመልጠን ወደ ማዕከሉ ቶሎ ተመልሰን። ከምሳ በኋላ ማቡ ድርሻችንን አከፋፈለ። ግማሾቹ ኮካ ኮላ፣ ከረሜላ እና ሌሎች ነገሮች ሲገዙ ማቡ፣ አል ሃጂ እና እኔ ደግሞ ለሽርሽር ወደ ፍሪ ታውን ለመሄድ አቀድን።

ጥዋት ቶሎ ቶሎ በላይ በላይ ቁርሳችንን ከበላን በኋላ አንድ በ አንድ ሾልከን ከመመገቢያ አዳራሹ ወጣን። ከውጭ ከተገናኘን በኋላ አውቶብስ መጠበቅ ጀመርን።

“ከተማውን ታውቁታላችሁ? ከዚህ በፊት ወደ ከተማው

ሂዳችሁ ታውቃላችሁ?”
አልሃጂ ጠየቀን።
አይ ሂጄ አላውቅም” አልኩ::

' ለትምህርት ወደ ፍሪ ታውን ልመጣ ነበር ግን ጦርነቱ ቀድሞ ተከሰተ። ውብ ከተማ እንደሆነ ግን ሰምቻለሁ” አለ አል
ሃጂ።

“እንግዲህ ታውቁታላችሃ! አውቶብሱ መጥቷል” አለ ማቡ። እስከ አንቃሩ የተከፈተው ሙዚቃ ከሰው ጫጫታ ጋር
ተዳምሮ አውቶብሱ ገበያ መስሏል። የሚዳንሱ ሰዎችም ነበሩ።ከጀርባ ተቀምጠን የሚያልፉትን ቤቶች አና ሱቆች አየን።

መሃል ከተማው አካባቢ ኪሲ መንገድ ወረድን። ሰዎች ለዕለት ተዕለት ኑሮቸው ከዚያ ወደዚህ ይጣደፋሉ፡፡ ትላልቅ
ሱቆች በሁለቱም የመንገድ አቅጣጫ ሲገኙ የመንገድ አዟሪዎች መንገዱን አጣበው ይሸጣሉ። የአይን አዋጅ ሆነብን በቀላሉ ተማረክን”::

“ጥሩ እንደሚሆን ነግሬችሁ ነበር” አለ ማቡ በደስታ እየዘለለ።ይሄን ረዥም ፎቅ ተመልከት” ወደ አንድ በእጄ እያመለከትኩ።
“ ያን ተመልከት በጣም ረዥም ነው” ብሎ አል ሃጂ ጮኸ።
“ሰዎች እንዴት ነዉ እዛ ላይ የሚወጡት?” ብሎ ማቡ ጠየቀ።
ቀስ ብለን ሁሉን እየቃኘን ፤የመኪናውን ብዛት እና ሁሉም አይነት ምግቦች ባላቸው የሊባኖስ ሱቆች እየተደነቅን መራመድ ጀመርን፡፡ ስንዞር ከቆየን በኋላ የሃገሪቱ ብሔራዊ ምልክት ወደ
ሆነው የጥጥ ዛፍ ደረስን። አፋችንን ከፍተን አትኩረን ተመለከትነው:: ከዚህ በፊት ከገንዘብ ጀርባ ላይ ነበር ያየነው።


ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#መንገድ

የመኼድ ርዝመት በዕርምጃ ስኬት
የሕይወትም ዳና በመሥመሩ ልኬት

ከተነጻጸረ . . .!
ይመተራል ዕድሜ ፣ ይሰበዛል ታሪክ
ይፍታታል ትርጓሜ ፣ በተጓዙበት ልክ።

ዕርምጃ - ፩
ዕንቅፋት በበዛው በጠባብ ጎዳና
ዐይነ ስውር ተጓዥ በእዝነ ልቦና ፣
ያለ መሪ ጒዞ በሐሳብ በትሩ
ያለመደናቀፍ ፣ መድረስ ከመንበሩ።

ዕርምጃ – ፪
በፍሥሓ ጕዝጓዝ ፣ በተደላደለ
የሚደነቃቀፍ ፣ ማየት ያልታደለ
ትላንቱን የረሳ ፣ በነግ አልባ ጕዘት
በለኮሰው እሳት ፣ ያልወጣ ከፍዘት።

እንግዲኽ . . .
በመንገድ ርቀት በ'ርምጃችን ዕድሜ
ከምንም መጀመር . . .
ያልጀመሩት ጉዞ የለም ፍጻሜ።

ለቅጽበት አይተሺኝ
በድኔን ዳብሰሺኝ
ያንቀላፋው ልቤን
ነክተሽ ብታነቂው።

እስኪ አኹን ምን ነበር . . . ?!
በምኞት ሠቀቀን ያ'ላንቺ ከምኖር
አንድ'ዜ ዳብሰሽኝ ዘላ'ለም ብቀበር።

እስኪ ምን አለበት . . . ?!
ፍቅርሽን ሰጥተሺኝ ፣
ሞትን ብንቅበት
ትንሣኤን ባውቅበት።

እስኪ ምን አለበት . . . ?!
ዘመኑን በሙሉ ባክኖ እንደኖረ
የመናፈቅ ዕድሜው በፍቅር ተሻረ።
( . . . የሚል ገድል ታሪክ . . . )
(. . . ተጽፎ ቢተረክ . . .)
እስኪ ምን አለበት . . .?!

ድንገት ተከስተሽ ፣
ፍካት ባጣው ቤቴ ፣ ሣቅሽን ብትዘሪበት
ብለሽ ብትነግሪያቸው ሕያውነት ቅጽበት።
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_አምስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

...ቅጠሎቹ አረንጓዴ ሲሆኑ ግንዱ ግን በጣም አርጅቷል። “ይሄን ስንነግራቸው ማንም አያምነንም” አለ አል ሃጂ።

የእራት ስዓት እየደረሰ ስለነበር ወደ ማዕከል መመለስ ነበረብን፡፡ ያን ምሽት ጓደኞቻችን ስለ ረጃጂም ህንጻዎች :
መኪናዎች እና ገበያው ነገርናቸው፡፡ ሁሉም ደስ ብሏቸው ማየት ፈለጉ። ማዕከሉም ይሄን በመረዳት በሳምንት አንድ ቀን የሽርሽር ፕሮግራም ተያዘልን፡፡

ቀስ በቀስ ወደ ትምህርት ተመለስን። ቀለል ያለ የትምህርት ስርዓት ነበር፡፡ ለሂሳብ መደመር፣ማባዛት እና ማካፈል ስንማር እንግሊዝኛ ደግሞ ምንባብ ማንበብ፣ ቃላቶችን ትርጉም ማወቅ
እና የእጅ ጽሁፍ እንማራለን። ብዙም አንከታተልም ; ትኩረታችን በትንሽ ነገር ይሰረቃል። በእርሳስ እንወጋጋላን
እንደባደባለን። “የናንተ ጥፋት አይደለም
ወደፊት ትስተካከላላችሁ' ይለናል መምህሩ።

ከምሳ በኋላ የጠረጴዛ ቴንስ ወይም እግር ኳስ እንጫወት ነበር። ለሊት ግን አስጨናቂ ነበር። በቅዥት እንባንናለን፣ በላብ እንጠመቃለን፣ ጩኸት እና ግድግዳ መደብደብ ነበር። ሰራተኞቹ
ይህን ስለሚያውቁ ጥበቃ ያደርጉልን ነበር።

የሴራሊዮን ዝናባማ ወቅት ከግንቦት እስከ ጥቅምት ሲሆን ሐምሌ፣ ነሐሴ እና መስከረም ደግሞ ከባድ ዝናብ ይኖራል።
ዝናቡ አንዳንዴ የጦርነቱን መጥፎ ትዝታዎች ይቀሰቅስብኛል።
የሰለጠንኩበት ቦታ እና የሞሪባ ሞት ትዝ ይለኛል። ሞሪባ በተኩስ እሩምታ ሲገደል መቅበር ቀርቶ ማልቀስ እንኳ አልቻልንም። አንድ ዛፍ ላይ አስጠግተነው በአፉ ደም እየደፈቀ ትተነው ሄድን።

ሲነጋ ሰራተኛዋ ብርድ ልብሱን መልሳ እያለበሰችኝ “ያንተ ጥፋት አይደለም በፍጹም! አይዞህ ትረሳዋለህ ይሻልሃል”
ትለኛለች፡፡

አንድ ቀን ረፋድ ላይ ቴንስ ስንጫወት የግቢው ሰራተኞች በሙሉ ይመለከቱን ነበር። አንድ ሰው ከኋላ ትከሻዬ ላይ ሲነካኝ ተሰማኝ ። ነርሷ ነበረች ። ነጭ ደምብ ልብስ እና ነጭ ኮፍያ ለብሳለች። ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር ፊት ለ ፊት ሳያት። ነጭ ጥርሷ ከጥቁር እና አንጸባራቂ ቆዳዋ ጋር ተጣምሮ ልዩ ውበት
ሰጥቷታል። ስትስቅ ደግሞ የበለጠ ውበቷ ይፈካል። ረዥም ናት፤ ትልልቅ አይኖች አሏት፡፡ ጠርሙስ ኮካ ኮላ ሰጥታኝ በሚያስፈልግህ ጊዜ ና እና እየኝ” ብላ ፈገግታ ሰጥታኝ ሄደች::
ከአል ሃጂ ጋር ጨዋታውን ትተን ወደ ውጭ ወጣን እና ኮካውን መጠጣት ጀመርን። “ወዳሃለች” እያለ አል ሃጂ ሊቀልድብኝ ሞከረ። ምንም አላልኩም::

እህ ትወዳታለህ እንዴ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡
“ እኔ አላውቅም:: ትልቅ ናት በዛ ላይ ነርሳችን ናት” አልኩ።
ማለት ሴቶችን ትፈራለህ?” አለ
“አንተ እንደምታስበው ወዳኝ አይመስለኝም” ብየ አል ሃጂን
ተመለከትኩት። የምለውን ነገር እያዳመጠ ይስቃል።

ኮካውን ጠጥተን እንደጨረስን አል ሃጂ ሄደ እኔ ግን ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ በሩ ስደርስ ነርሷ ስልክ እያወራች አየኋት። እንድገባ እና እንድቀመጥ በእጇ ምልክት አሳየችኝ።
ወዲያው ስልኳን አቁማ ፈገግታ እያሳየችኝ ወንበሯን ወደ እኔ
አቀረበች፡፡ ስለ ጦርነቱ ጥያቄ ልትጠይቀኝ እንደሆነ ገመትኩ።
እሷ ግን በተረጋጋ መንፈስ “ ስምህ ማነው” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ገረመኝ! ስሜን እንደምታውቀው እርግጠኛ ነበርኩ። “ስሜን ታውቂዋለሽ” ብየ በቁጣ መለስኩ።
“ ምን አልባት ላውቀው እችላለሁ ግን ስምህን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ?” አለች አይኗን እያፈጠጠች::

እሺ እሺ እስማይል” አልኩ፡፡

“ጥሩ ስም” አለች እራሷን እየነቀነቀች፡፡ “ የእኔ ስም አስቴር ነው። ጓደኛሞች እንሁን።”

“እርግጠኛ ነሽ ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ትፈልጊያለሽ” አልኳት::ለተወሰነ ጊዜ ካሰበች በኋላ “እርግጠኛ ላልሆን እችላለሁ” አለች።

ምን ማለት እንዳለብኝ ስላላወቅኩ እና ማንንም ስለማመን ለተወሰነ ጊዜ ዝም አልኩ። እንዴት መትረፍ እና እራሴን
መንከባከብ እንዳለብኝ ብቻ ነው ነበር የተማርኩት። እንደ መቶ አለቃ ጃባቲ ያሉ ያመንኳቸው የታዘዝኳቸው ሰዎች እንኳ
ሰዎችን በተለይ አዋቂዎችን እንድጠራጠር አድርገውኛል::
የሰዎችን ሃሳብ መጠራጠር ከጀመርኩ ቆይቻለሁ። ሰዎች ጓደኛ የሚሆኑት አንዱ ሌላው ላይ ጥቅም ለማግኘት ነው ብየ አስብ ነበር፡፡ ስለዚህ ለነርሷ ምንም መልስ አልሰጠኋትም።

“ያንተ ነርስ ነኝ በቃ ይሄ ነው። ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ከፈለክ ልትጠይቀኝ እና ላምንህ ይገባል” አለች። ተመሳሳይ ሃሳብ
ስለነበረን ፈገግ አልኩ። ፈገግታህ ያምራል” አለች። አፍሬ ቁጥብ ሆንኩ።
“ከከተማ እንዳመጣልህ የምትፈልገው ነገር አለ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ መልስ አልሰጠሁም::

“ለዛሬ ይበቃናል” አለች፡፡

ከተወሰነ ቀን በኋላ ነርሷ ስጦታ ሰጠችኝ። የተጠቀለለ ነገር ነበር ምን ይሆን እያልኩ መክፈት ጀመርኩ። ልክ እንዳየሁት በደስታ ተነስቼ አቀፍኳት። “ጓደኛ ካልሆን ለምን ይሄን ማዳመጫ እና ካሴት አመጣሽልኝ? ራፕ ሙዚቃ እንደምወድ እንዴት አወቅሽ?”

“እባክህ ተቀመጥ” አለች። የጆሮ ማዳመጫውን አደረኩ
D.M.C የዲ.ኤም.ሲ ሙዚቃ ነበር የምሰማው “It's like that and that the Way it is...” እንደዛ ነው እንደነገሩ” ራሴን ማንቀሳቀስ ጀመርኩ።አስቴር የጆሮ ማዳመጫውን ከጆሮዬ አውጥታ “አንተ ሙዚቃ ስታዳምጥ እኔ ልመረምርህ ነው”
አለች። ተስማማሁ። ምላሴን ፣ አይኔን አየች ከዛ እግሬን ስታይ ጠባሳ ነበረኝ። “ይሄ ጠባሳ እንዴት ወጣብህ?”

“በጥይት ተመትቼ ቆስየ ነው” እላለሁ በቀላሉ።

ፊቷ በሃዘን ተሞላ “ምን እንደሆንክ ምን እንደሚሰማህ ከነገርከኝ መድሃኒት ላዝልህ እችላለሁ” አለች። ሁሉንም
ነገርኳት፡፡ እንዴት በጥይት እንደተመታሁ፣
ስንት ጊዜ እንደተመታሁ እና ከዛ ምን እንዳደረኩ ነገርኳት። ልነግራት ግን
ፈልጌ አልነበረም፡፡ አስቃቂውን የጦርነቱን ክስተት ስነግራት መጠየቅ ታቆማለች ብዬ እንጂ። እሷ ግን በጥንቃቄ ታዳምጣለች። የትናንቱን ታሪኬን ማስታወስ ስጀምር አንገቴን ደፋሁ።

በበጋ ወቅት ስለነበረው ጦርነት ነገርኳት። ምግብ እና ጥይት ያጠረን አስቸጋሪ ወቅት ነበር። ሌላ መንደር ማጥቃት ነበረብን።ከትንሽ ስለላ በኋላ የሶስት ቀን ጉዞ ወደ ሚጠይቅ አንድ ሰፈር ሄድን። እቅዳችን ምግብ እና ጥይት ይዞ መምጣት ሳይሆን የምናጠቃውን ሰፈር ወደ ዋና ማዕከል መቀየር ነበር። ያለን
መሳሪያ እና ምግብ ይዘን ወጣን። ቦታው ደርሰን ለደፈጣ ውጊያ ስንዘጋጅ መንደሩ ባዶ መሆኑን ተገነዘብን። ከስዓት በኋላ
አምስት ታጣቂዎች መጥተው ባልዲ ይዘው ወደ ወንዙ ወረዱ..ገና መጠርጠር ስንጀምር ከኋላ ተኩስ ተከፈተብን። ለሊቱን ሙሉ ተታኮስን፡፡ አምስት ሰዎች ሞቱብን፣ የተረፍነውንም ተከተሉን። መቶ አለቃ ጠንክሮ ከመዋጋት ሌላ አማራጭ
እንደለለን ነገረን። ሌላ መንደር ለመሄድ በቂ ምግብ ወይም ጥይት የለንም፡፡ይሄን ጦርነት ካላሸነፍን ጫካው ውስጥ
መንከራተት ከዛም ማለቃችን ነው:: ስለዚህ ወደ ማጥቃት ገብተን መጀመሪያ ከሞቱት መሳሪያ አገኘን እና ተበተን::
በሁለተኛው ዙር እንደገና ተሰባስበን ማጥቃት ጀመርን::በመጨረሻ ከጠላቶቻችን በላይ ሐይል አግኝተን መበተን ቻልን:: የተኩስ እሩምታው በረደ፡፡ መንደሩ በእኛ ቁጥጥር ውስጥ ሆነ::
በድንገት ጥይቶችን በምሰበስብበት ወቅት የጥይት ዝናብ ወረደብን።

ሶስት ጊዜ እግሬ ላይ ተመትቼ ራሴን ስቼ ወደቅኩ። ሁለቱ ጥይቶች ገብተው ወጥተዋል አንዱ ግን እግሬ ውስጥ ቀረ::
በሚቀጥለው ቀን ስነቃ እግሮቼ ላይ ምስማር የተተከለ ይመስላል።