YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#ደቡብ_አፍሪካ የዜጎቻችን ጉዳይ ⤵️

በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የዜጎችን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገለጸ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስቸኳይ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎችን ለመደገፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡

ኤምባሲው ከስራ ቦታቸው የተፈናቀሉ የኢትዮጵያውያ ማህበረሰብ አባላትን ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ለማድረግም ጥረት ላይ መሆኑን ገልጿል፡፡

ትናንት የተፈፀመውን ክስተት ተከትሎም ጉዳዩ ላይ ውይይት ማድረጉን ጠቅሷል፡፡

በዚህም ከደቡብ አፍሪካና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ለችግሩ እልባት ለመስጠት የሚያግዝ እቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም አስታውቋል፡፡

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬም በሶዌቶ እና በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በድጋሚ ጥሪውን አቅርቧል፡፡
©FBC
@YeneTube @Fikerassefa
ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ሲያስተምራቸው የነበሩ 5 ሺህ 161 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመረቀ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በስድስተኛ ዙር ካስተማራቸው ተማሪዎች መካከል $የኤርትራ፣ #ሶማልያ#ደቡብ ሱዳን እንዲሁም #ሳውዲ_ዓረብያ ዜጎች ይገኙበታል፡፡ 
@YeneTube @FikerAssefa
#ደቡብ_አፍሪካ በሌሎች ሀገር ዜጎች ላይ ያነጣጠረው ጥቃት በኢትዮጵያውያን ላይ ብቻ ያነጣጠረ ባይሆንም በዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሰረት ከሀገሪቱ መንግስት ጋር ተወያይተው መፍትሄ እንደሚፈልጉ ኘሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተናገሩ::

ፕሬዘዳንቷ በደቡብ አፍሪካከሚኖሩ የዲያስፖራ አባላት ጋር ተወያይተዋል:: አባላቱ በስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እንዳሰጋቸው እና መንግስት ከመንግስት ጋር ውይይት አድርገው መፍትሄ እንዲፈልጉላቸው ጠይቀዋል። በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን በ28ኛው የዓለም አቀፍ ምጣኔ ሀብት ጉባኤ ላይ በመሳተፍ ላይ ያሉት ፕሬዘዳንቷ ከዚህ ጎን ለጎን ነው ከኢትዮዽያውያኑ ጋር የተወያዩት።ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በጉባኤው ላይም በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ እና በሰላም ዙሪያ ባተኮረው ውይይት ላይ ተሳትፈዋል።

ፕሬዝደንቷ የስራ እድል ፈጠራን ለማሳደግ ከፖሊሲ ማውጣት እና ከአዳራሽ ውስጥ ውይይት ባለፈ እታች ድረስ ወደ ህዝቡ ወርዶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።ወጣቶች በስደት ለሚኖሩበት ሀገር እንደ ስጋት ብቻ ሳይሆን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦም እንዳላቸው መታየት እንዳለበት ገልጸዋል።በሰላም መፍትሄ አመንጪነት ዙሪያ ሴቶችም በሀላፊነት ደረጃ ሊሳተፉ እንደሚገባ ፕሬዝደንቷ ጠቁመዋል።እንደ ፕሬዝደንቷ አገላለጽ የልማት ጉዳይ እና የሰላም አጀንዳዎች ተነጣጥለው የሚታዩ መሆን የለባቸውም።

ምንጭ:የፕሬዘዳንት ፅ/ቤት
@YeneTube @FikerAssefa
#Update

በኮሮና ቫይረስ ሳይያዙ አይቀሩም የተባሉ 4 ሰዎች በአዲስ አበባ ተገኙ!!

የጤና ጥበቃ ሚንስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ በኮሮና ቫይረስ ሳይያዙ አይቀሩም የተባሉ አራት ሰዎች በኢትዮጵያ መገኘታቸውን አሳውቋል።

አራቱም ኢትዮጵያዊያን መሆናቸው የተነገረ ሲሆን፤ #ሦስቱ_ቫይረሱ ከተከሰተበት ዉሃን ግዛት ተማሪ የነበሩ ናቸው ተብሏል።

ጤና ጥበቃ አሁን እየሰጠ ባለው መግለጫ የደም ናሙናው ወደ #ደቡብ_አፍሪካ መላኩን አስታውቋል።

ምንጭ:- BBC አማርኛ
@YeneTube @Fikerassefa
#በዓለማችን በኮሮና ከተጠቁ ሰዎች ውስጥ ከ723 ሺህ በላይ ዜጎች ድነዋል፡፡

በአለም ዙርያ ይሄንን ዜና እስካጠናቀርንበት ሰአት ድረስ 2 ሚሊዮን 646 ሺህ 428 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ 723 ሺህ 713 ያህሉ ሲያገግሙ 184 ሺህ 353 ያህሉ ደግሞ ህይወታቸው አልፏል፡፡

በህመሙ ከተጠቁት ውስጥ 1 ሚሊዮን 600 ሺህ 140 ያህሉ በደህና ሁኔታ ውስጥ ሲሆኑ 58 ሺህ 222 ሰዎች ህመሙ ፀንቶባቸው በፅኑ ህሙማን ማቆያ ውስጥ ናቸው፡፡

- በኮሮና ተጠቂ ብዛት #አሜሪካ አንደኛ ስትሆን ከሁለተኛ እስከ ሰባተኛ ያሉት የአውሮፓ ሀገራት ናቸው፡፡

- #አሜሪካ በኮሮና ከተጠቁባት 849 ሺህ 92 ሰዎች መካከል 84 ሺህ 50 ያህሉ ሲድኑ 47 ሺህ 681 ደግሞ ሞቶባታል፡፡

- #ስፔን_ጣልያንና_ኢራን በቅደም ተከተል ብዙ ዜጎቻቸውን በሞት ያጡ አገራት ናቸው።
የወረርሽኙ መነሻ የሆነችው ቻይና 82 ሺህ 798 ተጠቂ አስመዝግባ 77 ሺህ 207 ሰዎች ሲድኑ ከ4 ሺህ በላይ ያህሉ ደግሞ ሞተዋል፡፡

- ወደ ደበቡ አሜሪካ ስናቀና በኮሮና ተጠቂ ብዛት #ብራዚል ትቀድማለች፤ 46 ሺህ 182 ተጠቅተው 25 ሺህ 318 አገግመው 2 ሺህ 924 ሞተውባታል፡፡

- የመካከለኛው ምስራቅ ሀያል ሀገር እስራኤል 14 ሺህ 592 ተጠቂ አስመዝግባ 5 ሺህ 334 አገግመው 2 ሰው ብቻ ሞተውባታል።

- #ሳውዲ_አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ከ20 ሺህ በላይ ዜጎች በቫይረሱ ሲጠቁ ከ150 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

- #በአውስትራሊያ 6 ሺህ 660 ሰው በኮሮና ተይዞ 75 ሰዎች ሞተዋል፡፡

- #ከአፍሪቃ በተጠቂዎች ብዛት ቀዳሚ የሆነችው አገር ደግሞ #ግብፅ ነች፤3 ሺህ 659 ተጠቂ አስመዝግባ 935 ያህሉ ሲያገግሙ 276 ያህል ሰዎች ሞተውባታል፡፡

- #ደቡብ_አፍሪካም ከግብፅ ጋር ተቀራራቢ ያህል ሰው ነው በኮሮና የተጠቃባት፤ 3 ሺህ 635 ሰው ተጠቅቷል፡፡ 1 ሺህ 55 ሰው ሲያገግም 65 ሰው ደግሞ ሞቷል፡፡

- ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት #ጅቡቲ ብዙ ሰው በኮሮና የተያዘባት ሀገር ነች፡፡ 974 ሰው ተይዞ 183 አገግሞ 2 ደግሞ ሞቷል፡፡

- #ኬንያ 303 ተጠቂ አስመዝግባ 83 አገግመውላታል 14 ሰዎች ደግሞ ሞተውባታል፡፡ #ሶማሊያ 286 ሰዎች ተጠቅተው 4 አገግመው 8 ደግሞ ሞተዋል፡፡

- #ኤርትራ 39 ሰው ተጠቅቶ 6ቱ ሲያገግሙ እስካሁን የሞተ ሰው የለም፡፡

- ሀገራችን #ኢትዮጵያ 116 የኮሮና ተጠቂ ስታስመዘግብ 21 ሰዎች አገግመው 3 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፡፡


Via:- Ethio FM // ጆንሆፕኪንስ ዩንቨርሲቲ ድረገጽ
@Yenetube @Fikerassef
በኢትዮጵያ እና በጎረቤት ሀገሮች የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ -19) ወቅታዊ ሁኔታ

#ኢትዮጵያ

በበሽታው የተያዙ - 26,204
ህይወታቸው ያለፈ - 479

#ሱዳን
በበሽታው የተያዙ - 12,115
ህይወታቸው ያለፈ - 792

#ደቡብ ሱዳን

በበሽታው የተያዙ - 2,478
ህይወታቸው ያለፈ - 47

ኤርትራ
በበሽታው የተያዙ - 285
ህይወታቸው ያለፈ - 0

#ሶማሊያ

በበሽታው የተያዙ - 3,227
ህይወታቸው ያለፈ - 93

#ኬንያ

በበሽታው የተያዙ - 28,753
ህይወታቸው ያለፈ - 460
@Yenetube @Fikerassefa
#ጅማ ዞን በድረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ

#ኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ ሚርጋኖ በሶ ቀበሌ ባሳለፍነው ሳምንት መገባደጃ በጣለው ከባድ ዝናብ በድረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ።

አደጋው እሁድ ሚያዚያ 26 ቀን 2017 በሚርጋኖ ባሶ ቀበሌ ልዩ ስሙ ገሬ ኦጎደማ በተባለ ቦታ ላይ ለሌት 6 ሰዓት በጣለው ዝናብ መከሰቱን የሸቤ ሶምቦ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

ከባድ ዝናብ እና ኃይለኛ ንፋስ በቀላቀለ ዝናብ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን እና በተለያዩ ንብረቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የሸቤ ሶምቦ ቡሳ ጎኖፋ ጽህፈት ቤቱ አክሎ ገልጿል።

የወረዳው ቡሳ ጎኖፋ ጽህፈት ቤት ኃላፊ፤ ዩሱፍ አባ ማጫ እና የሚርጋኖ በሶ ቀበሌ የብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ ምስጋና ለታ ተጎጂዎችን በመጎብኘት ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ገልጸዋል ተብሏል።

ባሳለፍነው አመት ሀምሌ 15 ቀን በ #ደቡብ_ኢትዮጵያ ክልል #ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ250 በላይ ሰዎች ህይወት መለፉም አይዘነጋም።

በተመሳሳይ ወቅት በ #ሲዳማ ክልል በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የ 11 ሰዎች ህይወት አልፏል።

ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ቤንች ሽኮ ዞንም የአራት ሶዎች ህይወት በመሬት መንሸራተት አደጋ ማለፉም ይታወሳል።

@Yenetube @Fikerassefa
👍12😭64