ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ እነዚህ #አለባበሶች ግን አሁን #በቤተ መቅደስ ውስጥ እንዲያገለግሉ አድርጋ #የኢትዮጵያ ኦ.ተ.ቤተ ክርስቲያን ከመደበቻቸው #የካህናት አለባበስ #በቁጥርም#በመልክም #በዲዛይንም እጅግ #የተራራቀ ነው። በብሉይ ኪዳን የነበሩት #የሊቀ ካህናት አለባበስ አንድ በአንድ መግለጽ አጀንዳችን ስላልሆነ እኛም እንደ #ጳውሎስ <<ስለእነዚህ እንዳንተርክ አሁን አንችልም>> {ዕብ 9፥5}። ይሁን እንጂ #በቤተ መቅደሱ (ቅድስተ ቅዱሳን) ውስጥ #ሴቶች ፈጽሞው የሚገቡበት ሁኔታ አልነበረም።

ይኸው #ካህን እንኳ በተገቢ ሁኔታ አለባበሱን አስተካክሎና ስለራሱ #ኃጢአት #መስዋዕትን በቅድሚያ አቅርቦ የህዝቡን #ኃጢአት የሚያስተሰርይበትን #መስዋዕት ይዞ በብዙ #ፍርሃት #መጋረጃውን ገልጦ ቢገባ #በታቦቱ #መክደኛ ላይ በወረደው #ደመና #ዓምድ መሰረት #እግዚአብሔር ያናግረዋል። ነገር ግን #ሊቀ ካህኑ #ባይቀደስና በተገቢው ሁኔታ #አለባበሱን #ሳያስተካክል ቢቀርና የመሳሰሉት ነገሮች ባያሟላ እዚያው #ይቀሰፍና #ይሞታል። በውጭ #በአደባባይ የተሰበሰበው #ምህረት ጠባቂ ህዝብ #ካህኑ ቢዘገይባቸውም #እንደተቀሰፈና #እንደሞተ ስለሚገባቸው #በወገቡ ላይ እስከውጨኛው ድረስ በታሰረው #ሰንሰለት ጎትተው ያወጡታል እንጂ እንኳንስ #ሴቶች #ወንዶች እንኳ ገብተው በፍጹም #ሬሳውን አያወጡም።
እንግዲህ ይኸው #ስርዓት በተሟላ መልኩ #ከድንኳንነት ወደ #ህንጻ ቤት ተቀይሮ #የዳዊት ልጅ #ሰለሞን #በኢየሩሳሌም እጅግ ውብ አድርጎ ሰራው። #የሰለሞን #ቤተመቅደስ #ሴቶች #ከአደባባዩ ውጭ ባለው #ዓምድ እንደ #ሃና #ይፀልያሉ እንጂ {1ኛ ሳሙ 1፥9} በጭራሽ #በቅድስተ ቅዱሳኑ (በቤተመቅደሱ) ውስጥ #ሴቶች አይገቡም ነበር።
▶️ ሌላው መጽሀፍ ደግሞ <<ማሪሃም የተባልሽ የተመረጥሽ እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ አንቺን ደግሞ በጠላቶች አንገት #የብረት #ዛንጁር አግቢባቸው የመለከታቸውን ድምጽ #አክብጅው #ደንቆሮም አድርጊው እርሳቸውንም #በቀፎ #በቅርጫት በእግር ብረት #እሰሪያቸው በእግራቸው #ወጥመድ በከንፈራቸውም #ልጓም በአፍንጫቸው #ጉንፋን ላኪባቸው ሊሄዱበትም ወዳልፈቀዱበት መንገድ #መልሻቸው በልቦናቸውም #ፍርሃትን #መንቀጥቀጥን አሳድሪባቸው #መሸበርንና መንቀጥቀጥን ጨምሪባቸው #እንደሴቶች ይሁኑ። ከጽኑ ነፋስ ኃይል የተነሳ ዛፍ ሲንቀሳቀስ ቅጠሉ እንረዲረግፍ እንዲበተን እንዲሁ #ይሁኑ#በርሃብ #በቸነፈር #እህልን #በማጣት ቅሰፊያቸው፣ በሜዳ ሰይፍ ልጆቻቸውን #ያጥፋቸው በቤታቸውም ውስጥ #ፍርሃት ያስጨንቃቸው። #እሳት#በረዶ #ረሀብ፣ ቸነፈር ይፍጃቸው ይህ ሁሉ የእግዚአብሄር #የምጽአቱ #ጽዋ በጠላቶቼ ላይ ይውረድ እድል ፈንታቸው #ጽዋ ትርታቸው ይሁን[1]>>

▶️ እንግዲህ ይህ አይነቱ #ጸሎት #ክርስቶስና #ሐዋሪያቱ #ለገዳዮቻቸው እንኳ <<አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው>> ብለው ከጸለዩት ጋር ይጻረራል። ስለሆነም ይህ አይነት #ጸሎት #የበልዓም ትምህርት {የሰይጣን ትምህርት} እንጂ #የክርስቶስ #ትምህርትና #ጸሎት አይደለም [ዘኃ 22፥17 ፣ ራዕ 2፥14]። አንዳንዶች ለማስተባበል እንደሚሞክሩት <<ይሄ እርግማን ለሰይጣን ነው>> እንዳል እንኳን #አንደኛ <<የሚጠላኝን፣ የሚቃወመኝን ሰው..>> በማለት #ለሰውም ጭምር እንደሆነ ተጽፏል ሁለተኛ #ለሰይጣንም ቢሆን እንኳን እርሱ #መንፈስ ስለሆነ <<የሚለጎም አፍ፣ #ዲዳ የሚሆን #አንደበት፣ የሚዘጋ #ጉሮሮ#የሚደነቁር #ጆሮ፣ የሚቆረጥ #አንገት፣ የሚሰበር #ክንፍ የሉትም። ጌታ ኢየሱስም #አጋንንትን ከሰዎች ሲያስወጣ < #ውጡ!> ብሎ #ከመገሰጽና #ከማስወጣት በስተቀር [ማር 1፤ 25-27] #ዲዳ ሁኑ!፣ #ተቆረጡ!፣ #ተሰበሩ! አላለም። #ደቀመዛሙርቱም ቢሆኑ #አጋንንትን አውጡ ባላቸው መሰረት #በኢየሱስ ስም አስወጡ እንጂ [ማቴ 10፥8] #ቆራርጧቸው#ሰባብሯቸው#አደንቁሯቸው#ሽባ አርጓቸው አላለቸውም። እነርሱም #እርግማንና ሌላ #ቃላትን አልተጠቀሙም። ምክንያቱም ደሞ #አጋንንት #መንፈስ እንጂ #ሥጋዊ #አካላት የላቸውምና [ሐዋ 16፤ 16-18፣ ሉቃ 10፥17፣ ኤፌ 6፥12]። ጌታ በነገር ሁሉ #ማስተዋልን ያድለን [2ጢሞ 2፥7]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
______________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አርጋኖን ፤የእመቤታችን ምስጋና ዘሰኑይ፡ ገጽ 33-37፥ ተስፋ ገብረ ስላሴ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።

@gedlatnadersanat
(8.6.4▶️) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat