#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ጥናት ጥያቄዎች ትክክለኛ ምላሾች
እውነት ወይም ሐሰት በሉ
1 #_መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በአንድ ጊዜ ነው።
ሀ) እውነት ለ)✅ ሐሰት
2 #_መዝሙረ ዳዊት በከተማ ስም ከተሰየሙ መጻሕፍት መካከል አንዱ ነው።
ሀ ) እውነት ለ )✅ ሐሰት
3 #_የመጽሐፈ ሶስና እናት መጽሐፍ ትንቢተ ዳንኤል ነው።
ሀ ) ✅እውነት ለ ) ሐሰት
4 #_መጽሐፈ አስቴርን የጻፈችው አስቴር ነች።
ሀ ) እውነት ለ)✅ ሐሰት
5 #_የሐዋርያት ሥራን የጻፈው ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ነው።
ሀ ) ✅እውነት ለ ) ሐሰት
#ይዘት ምርጫ
6 #_ከሚከተሉት መካከል የታሪክ መጽሐፍ የሆነው የቱ ነው❓
ሀ) ✅ግብረ ሐዋርያት
ለ )የማቴዎስ ወንጌል
ሐ )ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች
መ) ሀ እና ለ
7) #ከተዘረዙት መጻሕፍት መካከል #_ሊቀ _ነቢያት ቅዱስ ሙሴ #ያልጻፈው መጽሐፍ የቱ ነው❓
ሀ ) መጽሐፈ ኩፋሌ
ለ ) ኦሪት ዘፍጥረት
ሐ ) ኦሪት ዘዳግም
መ )✅ መጽሐፈ አክሲማሮስ
8) #_የኦ/ተ ቤተ ክርስቲያናችን ምትቀበላቸው የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ቁጥራቸው ስንት ነው❓
ሀ ) 46
ለ ) 27
ሐ ) ✅ 35
መ ) 81
9 #_መጽሐፈ ምሥጢር ከየትኛው የአዋልድ መጽሐፍ ጋር ይመደባል❓
ሀ )ድርሳን
ለ )✅ነገረ ሃይማኖት
ሐ )የሥርዓት
መ )የታሪክ
10 #_"ገና እንደተወለዱ ልጆች የቃሉን ወተት ተመኙ።" 1ጴጥ 2:3 ይህ ኃይለ ቃል ምንን ያመለክታል❓
ሀ )መጽሐፍ ቅዱስ ዳኛ መሆኑን
ለ ) መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ጽድቅ የሚመራ መሆኑን
ሐ) ✅መጽሐፍ ቅዱስ ምግበ ነፍስ መሆኑን
መ)መጽሐፍ ቅዱስ የሕግ እና የአስተዳደር ምንጭ መሆኑን
#በአጭሩ መልስ ስጡ
11 #መጽሐፍ_ቅዱስን_ቅዱስ ካሰኙት ነገሮች መካከል ቢያንስ ሦስት ጥረሱ::❓
#በእግዚአብሔር መንፈስ የተነሱ ቅዱሳን ሰዎች ስለጻፉት
#ወደ ቅድስና ስለሚመራ
#በቅዱሱ በእግዚአብሔር ፈቃድ ስለተጻፈ
#ዘመን የማይሽረው መሆኑ
#መጻኤዉንና አላፊውን በትክክልና በእርግጠኛነት የሚናገር ሰለሆነ
#የሌሉሎች መጻሕፍት ዋኘና ምንጭ በመሆኑ
12 #ከመጻሕፍ_ቅዱስ ባህል መካከል ቢያንስ 2ቱ ጠቅሰህ(ሺ)ከሀገራችን ተመሳሳይ ባህል ጋር አንድነቱንና ልዮነቱን አነጻጽር(ሪ)::❓
እረኝነት:-
ሰርግ:-
ጫማ ማውለቅ:-
13 #አዋልድ_መጻሕፍት ከሚባሉት መካከል 3ቱን ጥቀስና ጥቅማቸውን በአጭሩ አብራራ(ሪ)❓
#መልስ
#አዋልድ መጻሕፍ የሚባሉ
#ገድል :-
#ተአምር :-
#ድርሳን :-
#መልክዕ :-
#ጥቅማቸው
ከአባታቸው ከመጻሕፍ ቅዱስ ጠባይ ሳይወጡ የቅዱሳንን ተጋሎ ድንቅ ድንቅ ተአምራት እና ተራዳይነት እንዲሁም ክብርን የሚገልጡ በመሆን መጻሕፍ ቅዱስ በጥቂቱ እና በመጠኑ በፍንጭ መልክ የገለጠውን አነርሱ አምልተውና አስፍተው ይተነትኑታይ ማለት ነው::#በአጠቃላይ በደረቁ በንባብ የተጻፈውን ወንጌል በሕይወት ተተግብሮ እያሳዮ ሃይማኖት ያጸናሉ ምግባር ያቀናሉ ይሕወት ይሆናሉ::
14 #የመጻሕፍ_ቅዱስ ዕድሜ ሰንት ነው? መጀመሪያ የተጻፈውስ የመጻሕፍ ቅዱስ ክፍል የትኛው ነው?በምንስ ቋንቋ ተጻፈ?
#መልስ
ዘመኑ በትክክል በውል አይታወቅም መጀመሪያ የተጻፈውም መጽሐፈ ሄኖክ ሲሆን የተጻፈበት ቋንቋም እንደ ኢትዮጲያዊያን ሊቃውንት ገለጻ #በግዕዝ_ቋንቋ ነው
15 #መጻሕፍ_ቅዱስን እንደ ምንኖርበት ሀገር ባህል ፣ እንደ ደረስንበት የዕውቀት ደረጃ ፣ በሥጋዊ ሀሳብና ፍልስፍ ማንበብእና መተርጎምና የሚያስከትለውን ጥፋት በራስህ(ሺ) አገላለጽ አስረዳ(አስረጂ)❓
#መልስ
*ወደ ክህደትና ምንፍቅና ይከታል #በአጠቃላይ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ይለያል የሚል መሰል ምላሾችን የሰጣችሁ ሁሉ ትክክል ናችሁ!::
#ለበለጠ_መረጃ የተላለፉ ኮርሶችን ያድምጡ
#በመልሶቻችሁን ዙሪያ ላላችሁ ማንኛውም አሳብ ጥያቄና ጥቆማ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::
#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እውነት ወይም ሐሰት በሉ
1 #_መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በአንድ ጊዜ ነው።
ሀ) እውነት ለ)✅ ሐሰት
2 #_መዝሙረ ዳዊት በከተማ ስም ከተሰየሙ መጻሕፍት መካከል አንዱ ነው።
ሀ ) እውነት ለ )✅ ሐሰት
3 #_የመጽሐፈ ሶስና እናት መጽሐፍ ትንቢተ ዳንኤል ነው።
ሀ ) ✅እውነት ለ ) ሐሰት
4 #_መጽሐፈ አስቴርን የጻፈችው አስቴር ነች።
ሀ ) እውነት ለ)✅ ሐሰት
5 #_የሐዋርያት ሥራን የጻፈው ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ነው።
ሀ ) ✅እውነት ለ ) ሐሰት
#ይዘት ምርጫ
6 #_ከሚከተሉት መካከል የታሪክ መጽሐፍ የሆነው የቱ ነው❓
ሀ) ✅ግብረ ሐዋርያት
ለ )የማቴዎስ ወንጌል
ሐ )ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች
መ) ሀ እና ለ
7) #ከተዘረዙት መጻሕፍት መካከል #_ሊቀ _ነቢያት ቅዱስ ሙሴ #ያልጻፈው መጽሐፍ የቱ ነው❓
ሀ ) መጽሐፈ ኩፋሌ
ለ ) ኦሪት ዘፍጥረት
ሐ ) ኦሪት ዘዳግም
መ )✅ መጽሐፈ አክሲማሮስ
8) #_የኦ/ተ ቤተ ክርስቲያናችን ምትቀበላቸው የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ቁጥራቸው ስንት ነው❓
ሀ ) 46
ለ ) 27
ሐ ) ✅ 35
መ ) 81
9 #_መጽሐፈ ምሥጢር ከየትኛው የአዋልድ መጽሐፍ ጋር ይመደባል❓
ሀ )ድርሳን
ለ )✅ነገረ ሃይማኖት
ሐ )የሥርዓት
መ )የታሪክ
10 #_"ገና እንደተወለዱ ልጆች የቃሉን ወተት ተመኙ።" 1ጴጥ 2:3 ይህ ኃይለ ቃል ምንን ያመለክታል❓
ሀ )መጽሐፍ ቅዱስ ዳኛ መሆኑን
ለ ) መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ጽድቅ የሚመራ መሆኑን
ሐ) ✅መጽሐፍ ቅዱስ ምግበ ነፍስ መሆኑን
መ)መጽሐፍ ቅዱስ የሕግ እና የአስተዳደር ምንጭ መሆኑን
#በአጭሩ መልስ ስጡ
11 #መጽሐፍ_ቅዱስን_ቅዱስ ካሰኙት ነገሮች መካከል ቢያንስ ሦስት ጥረሱ::❓
#በእግዚአብሔር መንፈስ የተነሱ ቅዱሳን ሰዎች ስለጻፉት
#ወደ ቅድስና ስለሚመራ
#በቅዱሱ በእግዚአብሔር ፈቃድ ስለተጻፈ
#ዘመን የማይሽረው መሆኑ
#መጻኤዉንና አላፊውን በትክክልና በእርግጠኛነት የሚናገር ሰለሆነ
#የሌሉሎች መጻሕፍት ዋኘና ምንጭ በመሆኑ
12 #ከመጻሕፍ_ቅዱስ ባህል መካከል ቢያንስ 2ቱ ጠቅሰህ(ሺ)ከሀገራችን ተመሳሳይ ባህል ጋር አንድነቱንና ልዮነቱን አነጻጽር(ሪ)::❓
እረኝነት:-
ሰርግ:-
ጫማ ማውለቅ:-
13 #አዋልድ_መጻሕፍት ከሚባሉት መካከል 3ቱን ጥቀስና ጥቅማቸውን በአጭሩ አብራራ(ሪ)❓
#መልስ
#አዋልድ መጻሕፍ የሚባሉ
#ገድል :-
#ተአምር :-
#ድርሳን :-
#መልክዕ :-
#ጥቅማቸው
ከአባታቸው ከመጻሕፍ ቅዱስ ጠባይ ሳይወጡ የቅዱሳንን ተጋሎ ድንቅ ድንቅ ተአምራት እና ተራዳይነት እንዲሁም ክብርን የሚገልጡ በመሆን መጻሕፍ ቅዱስ በጥቂቱ እና በመጠኑ በፍንጭ መልክ የገለጠውን አነርሱ አምልተውና አስፍተው ይተነትኑታይ ማለት ነው::#በአጠቃላይ በደረቁ በንባብ የተጻፈውን ወንጌል በሕይወት ተተግብሮ እያሳዮ ሃይማኖት ያጸናሉ ምግባር ያቀናሉ ይሕወት ይሆናሉ::
14 #የመጻሕፍ_ቅዱስ ዕድሜ ሰንት ነው? መጀመሪያ የተጻፈውስ የመጻሕፍ ቅዱስ ክፍል የትኛው ነው?በምንስ ቋንቋ ተጻፈ?
#መልስ
ዘመኑ በትክክል በውል አይታወቅም መጀመሪያ የተጻፈውም መጽሐፈ ሄኖክ ሲሆን የተጻፈበት ቋንቋም እንደ ኢትዮጲያዊያን ሊቃውንት ገለጻ #በግዕዝ_ቋንቋ ነው
15 #መጻሕፍ_ቅዱስን እንደ ምንኖርበት ሀገር ባህል ፣ እንደ ደረስንበት የዕውቀት ደረጃ ፣ በሥጋዊ ሀሳብና ፍልስፍ ማንበብእና መተርጎምና የሚያስከትለውን ጥፋት በራስህ(ሺ) አገላለጽ አስረዳ(አስረጂ)❓
#መልስ
*ወደ ክህደትና ምንፍቅና ይከታል #በአጠቃላይ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ይለያል የሚል መሰል ምላሾችን የሰጣችሁ ሁሉ ትክክል ናችሁ!::
#ለበለጠ_መረጃ የተላለፉ ኮርሶችን ያድምጡ
#በመልሶቻችሁን ዙሪያ ላላችሁ ማንኛውም አሳብ ጥያቄና ጥቆማ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::
#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
የሚከላከሉትና ጥቃት የሚያደርሱት በቀንዶቻቸው አማካኝነት ነው ስለዚህ ቀንዳቸው ኃይላቸው ሥልጣናቸው ነው :: ታዲያ ይህ ለአብርሃም በይስሐቅ ፈንታ ይሰዋው ዘንድ የተሰጠው በግ እንደማንኛውም የቀንድ ከብት እራሱን ከአራጁ የሚከላከልበት ኃይልና ሥልጣን ያለው ቀንዳም በግ ቢሆንም ቀንዱ ግን በ አፀ ሳቤቅ ስለተያዘ ያን ያደርግ ዘንድ አላስቻለውም ። በሕልውና ፣በሥልጣን ፣በኃይል ከባሕሪ አባቱ ከአብ እና ከባሕሪ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ትክክል (እኩል ፣የተተካከለ) ቢሆንም ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስም በሰው ልጆች የፍቅር እጸ ሳቤቅ ተይዟልና ከልዕልና ወደ ትዕትና ዝቅ አለ ባሕሪውንም ሰውሮ እንደኛ የተገዢ የሰውን አራዐያ ነሳ። ፍቅር ሰአቡ ኃያል ወልድ እም መንበሩ ወአብጽዮ እስከ እለ ሞት / #ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው"/ የበጉ ቀንድ በእጸ ሳቤቅ ስለተያዘ ከመታረድ እንዳልሸሸ ና በቀንዴም ተዋግቼ ላምልጥ ብሎ የቀንዱን ሥልጣን እንዳልተጠቀመ ሁሉ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስም በፍቃዱ በሰው ፍቅር ተይዟልና ሥልጣን ሁሉ የእርሱ ሆኖ ሳለ ሥልጣኑን ሳይሆን ፍቅሩን ተጠቅሞ ለኛ ተሰውቶ አዳነን:: "ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?" ኢሳ 53፥7-8
#የአሮን በትር ዘኁልቁ 17÷8
ሙሴም ለእስራኤል ልጆች ተናገራቸው፤ አለቆቻቸው ሁሉ አሥራ ሁለት በትሮች፥ እያንዳንዱም አለቃ በየአባቱ ቤት አንድ አንድ በትር፥ ሰጡት፤ የአሮንም በትር በበትሮቻቸው መካከል ነበረች። ሙሴም በትሮቹን በእግዚአብሔር ፊት በምስክሩ ድንኳን ውስጥ አኖራቸው። እንዲህም ሆነ፤ በነጋው ሙሴ ወደ ምስክሩ ድንኳን ውስጥ ገባ፤ እነሆም፥ ለሌዊ ቤት የሆነች #የአሮን_በትር_አቈጠቈጠች_ለመለመችም_አበባም_አወጣች የበሰለ ለውዝም አፈራች። ሙሴም በትሮችን ሁሉ ከእግዚአብሔር ፊት ወደ እስራኤል ልጆች ሁሉ አወጣቸው፤ እነርሱም አዩ፥ እያንዳንዱም በትሩን ወሰደ። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ የአሮንን በትር ወደ ምስክሩ ፊት መልስ፤ ማጕረምረማቸው ከእኔ ዘንድ እንዲጠፋ እነርሱም እንዳይሞቱ ለሚያምፁብኝ ልጆች ምልክት ሆና ትጠበቅ አለው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የማክሰኞ እርሻ ትባላለች የማክሰኞ እርሻ ገበሬ ሳይኮተኩታት ውኃም ሳያጠጣት አብባ አፍርታ ተገኝታለች ይህች የማክሰኞ ዕለት እርሻ የመጀመሪያይቱ ምድር ወይም ጥንተ ምድርም እየተባለች ትጠራለች የሶሪያው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊም አክሎ በውዳሴው እንዲ ብሏታል #ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበር እንቺ እንደርሷ ነሽ" #አባ ኤፍሬም ሶሪያዊ #ውዳሴ_ማርያም ዘ እሁድ
#የኖህ መርከብ ዘፍ 6፥14
በኖህ መርከብ ፍጥረት ከጥፋት እንደተረፈ በእመቤታችንም ከጥፋት ድኗል ። የኖህ መርከብ ሦስት ክፍሎች ነበሯት እመቤታችንም በሦስት ነገሯ ንጽሕት ነች በሥጋዋ ፣በነፍሷ፣ በሕሊናዋ የጋስጫ ፍሬ አባ ጊዮርጊስ "በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " ድንግል ሆይ በምንና በምን እንመስልሻለን ምሳሌን የለሽም" እንዳለ ምሳሌዎች ሁሉ እመቤታችንን አይመስሏትም(አይመጥኗትም)
#የኖህ መርከብ ስምንት ሰዎችና ብዙ ዐይነት እንሰሳት ገብተውባታል ወጥተውባታል
#በእመቤታች ግን ከኃያላ ከጌታ በቀር ወደ እርሷ ገብቶ የወጣ የለም
#በኖህ መርከብ ሲገባም ሲወጣም በሮቹአን ከፍተው ዘግተው ነው
#እመቤታችን ግን ማንም ለዘላለሙ የተዘጋች ገነት የታተመች ፈሳሽ ነችና ዘላለም እትዕምት ፣ዝግ ፣ድንግል ነች ። ጌታችንንም የጸነሰችው እንዲሁ ዝግ ሆና ነው ስትወልደውም እንዲሁ ዝግ ሆና ነው። " ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም፦ ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።" ሕዝ 44÷1-2
#ወደ ኖህ መርከብ የገቡት እንሰሳት እንሰሳዊ ጠባያቸውን ሳይለቁ ነው የወጡት ለምሳሌ ወደ ኖህ መርከብ የገባ አንበሳ ሲወጣም የአንበሳነቱን ሥጋ ቦጫቂነቱን ሳይለቅ ወጣ ፣ነብሩም ደም መጣጭነቱን ሳይተው ወጣ ፣በግም ውኃም መጎንጨቱን ሳር ጋጪነቱን ሰይለውጥ ወጣ ::
#በእመቤታችን ምልጃ አምኖና ተማምኖ አማልጂኝ ብሎ በሥሯ የተጠለለባት ሰው ግን እንዲሁ እንደ ኖህ መርከብ በቀደመ ግብሩ አይቆይም ንፉጉ ለጋሽ፣ጨካኙ እሩሩ ፣ ዘማዊው ድንግል ሆኖ ተለወጦ ይገኛል ስለዚህ እመቤታችን ከኖህ መርከብ በእጅጉ ትልቃለች ትበልጥማለች :: ዝም ብለን እንደ ሊቁ
......በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ........ እንበላት።
.............ይቆየን..............
እረድኤትና ቃልኪዳኗ አማላጅነቷም ለዘለዓለሙ ከኛ አይራቅ ...አሜን!
ኃ/ማርያም
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👇
#የአሮን በትር ዘኁልቁ 17÷8
ሙሴም ለእስራኤል ልጆች ተናገራቸው፤ አለቆቻቸው ሁሉ አሥራ ሁለት በትሮች፥ እያንዳንዱም አለቃ በየአባቱ ቤት አንድ አንድ በትር፥ ሰጡት፤ የአሮንም በትር በበትሮቻቸው መካከል ነበረች። ሙሴም በትሮቹን በእግዚአብሔር ፊት በምስክሩ ድንኳን ውስጥ አኖራቸው። እንዲህም ሆነ፤ በነጋው ሙሴ ወደ ምስክሩ ድንኳን ውስጥ ገባ፤ እነሆም፥ ለሌዊ ቤት የሆነች #የአሮን_በትር_አቈጠቈጠች_ለመለመችም_አበባም_አወጣች የበሰለ ለውዝም አፈራች። ሙሴም በትሮችን ሁሉ ከእግዚአብሔር ፊት ወደ እስራኤል ልጆች ሁሉ አወጣቸው፤ እነርሱም አዩ፥ እያንዳንዱም በትሩን ወሰደ። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ የአሮንን በትር ወደ ምስክሩ ፊት መልስ፤ ማጕረምረማቸው ከእኔ ዘንድ እንዲጠፋ እነርሱም እንዳይሞቱ ለሚያምፁብኝ ልጆች ምልክት ሆና ትጠበቅ አለው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የማክሰኞ እርሻ ትባላለች የማክሰኞ እርሻ ገበሬ ሳይኮተኩታት ውኃም ሳያጠጣት አብባ አፍርታ ተገኝታለች ይህች የማክሰኞ ዕለት እርሻ የመጀመሪያይቱ ምድር ወይም ጥንተ ምድርም እየተባለች ትጠራለች የሶሪያው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊም አክሎ በውዳሴው እንዲ ብሏታል #ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበር እንቺ እንደርሷ ነሽ" #አባ ኤፍሬም ሶሪያዊ #ውዳሴ_ማርያም ዘ እሁድ
#የኖህ መርከብ ዘፍ 6፥14
በኖህ መርከብ ፍጥረት ከጥፋት እንደተረፈ በእመቤታችንም ከጥፋት ድኗል ። የኖህ መርከብ ሦስት ክፍሎች ነበሯት እመቤታችንም በሦስት ነገሯ ንጽሕት ነች በሥጋዋ ፣በነፍሷ፣ በሕሊናዋ የጋስጫ ፍሬ አባ ጊዮርጊስ "በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " ድንግል ሆይ በምንና በምን እንመስልሻለን ምሳሌን የለሽም" እንዳለ ምሳሌዎች ሁሉ እመቤታችንን አይመስሏትም(አይመጥኗትም)
#የኖህ መርከብ ስምንት ሰዎችና ብዙ ዐይነት እንሰሳት ገብተውባታል ወጥተውባታል
#በእመቤታች ግን ከኃያላ ከጌታ በቀር ወደ እርሷ ገብቶ የወጣ የለም
#በኖህ መርከብ ሲገባም ሲወጣም በሮቹአን ከፍተው ዘግተው ነው
#እመቤታችን ግን ማንም ለዘላለሙ የተዘጋች ገነት የታተመች ፈሳሽ ነችና ዘላለም እትዕምት ፣ዝግ ፣ድንግል ነች ። ጌታችንንም የጸነሰችው እንዲሁ ዝግ ሆና ነው ስትወልደውም እንዲሁ ዝግ ሆና ነው። " ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም፦ ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።" ሕዝ 44÷1-2
#ወደ ኖህ መርከብ የገቡት እንሰሳት እንሰሳዊ ጠባያቸውን ሳይለቁ ነው የወጡት ለምሳሌ ወደ ኖህ መርከብ የገባ አንበሳ ሲወጣም የአንበሳነቱን ሥጋ ቦጫቂነቱን ሳይለቅ ወጣ ፣ነብሩም ደም መጣጭነቱን ሳይተው ወጣ ፣በግም ውኃም መጎንጨቱን ሳር ጋጪነቱን ሰይለውጥ ወጣ ::
#በእመቤታችን ምልጃ አምኖና ተማምኖ አማልጂኝ ብሎ በሥሯ የተጠለለባት ሰው ግን እንዲሁ እንደ ኖህ መርከብ በቀደመ ግብሩ አይቆይም ንፉጉ ለጋሽ፣ጨካኙ እሩሩ ፣ ዘማዊው ድንግል ሆኖ ተለወጦ ይገኛል ስለዚህ እመቤታችን ከኖህ መርከብ በእጅጉ ትልቃለች ትበልጥማለች :: ዝም ብለን እንደ ሊቁ
......በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ........ እንበላት።
.............ይቆየን..............
እረድኤትና ቃልኪዳኗ አማላጅነቷም ለዘለዓለሙ ከኛ አይራቅ ...አሜን!
ኃ/ማርያም
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
👆👆👆👆👆👇
ስለ ጥያቄዎ እናመሰግናለን ቃለ ሕይወት ያሰማልን
#ወደ መልሱ ስናመራ በኦርቶዶክስ ተዋህዶና በካቶሊክ መካከል የሰማይና የምድር ያክል ብዙ ልዮነት አለ ልዮነት የለውም የሚሉ አካላትን በሦስት ከፍሎ መመልከት ይቻላል የመጀመሪያዎች ባለማወቅ ና በለመረዳት በየዋህነት አንድ ነን የሚሉ የዋሐን ሲሆኑ እነዚኞችን በማሳወቅ በመንገርና በማስተማር በቀናች ሃይማኖት ማጽናት ይጠበቅብናል ሁለተኞቹ ሆን ብለው ልዮነቱን እያወቁ ምዕመናንን በማደናገር በአንድነን ሽፋን ለማስኮብለል በማሰብ የሚናገሩት ሲሆን እነዚኞቹን ደግሞ በአፍ የሚያስተምሩትን በአፍ በመጽአፍ የሚያስተምሩትን በመጽሐፍ እንደ አመጣጣቸው መመለስ ይገባል “ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥14 ሦስተኞቹ ደግሞ ለመኮብለል በራሳቸው ተነሳሽነት ካመጡት ዝንባሌ የተነሳ ልዮነት የለም ወደ ሚል ዝንባሌያቸውን ትክክል ለማሰመሰል የሚጥሩ ወይም ለመሄድ ያኮበኮቡ ናቸውና ከእነዚኞቹ ነፍስ ይማር ብለን እንርቃቸዋለን
“ወንድሞች ሆይ፥ ከእኛ እንደ ተቀበለው ወግ ሳይሆን ያለ ሥርዓት ከሚሄድ ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዛችኋለን።”
— 2ኛ ተሰሎንቄ 3፥6
ከዚህ አንጻር ጥቂት ልዮነቶቻችንን እንመልከት
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ
1) መንፈስ ቅዱስ የሰረጸው ከአብ ብቻ ነው ።
2) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋህዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆኗል።
3)ንሰሐ መግባት በአጸደ ሥጋ እንጂ በአጸደ ነፍስ ሆና ንስሐ መግባት የለም ወይም አይቻልም ይህም ማለት በሰማይ መካነ ንስሐ የለም ።ያለውም የጽድቅ እና የኩነኔ ቦታ ነው። ለዚህም የአላዛርና የነዌ ታሪክ አስረጂ ነው። ሉቃ 16÷19
4) ሾማምንት የሚወስኑት ውሳኔ አይሳሳቱም ብለን አናምንም።
5) ህጻናትን ቃጠመቅን በኃላ ወዲያው 36 ዕዋሳቶቻቸውን ሜሮን እንቀባለን።
6) የምንሰዋው የክርስቶስን ክቡር ሥጋና ቅዱስ ደም ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሕደው ነው ብለን እናምናለን።
7 )ሕጻናት ከተጠመቁ በኃላ ሜሮን እንደተቀቡ ወዲያው ይቆርባሉ።
8)ከጳጳሳት በቀር ቀሳውስትና ዲያቆናት ማግባት ከፈለጉ አንዳንድ ሚስት አግብተው ክህነትን ተቀብለው ሊያገለግሉ ይችላሉ ።
9) ሥዕል እንስላለን እንጂ ሐውልት አንቀርጽም አንዳንድ የተሰሩ ሃውልቶች ቢኖሩም የኛ ትውፊት አይደለም ። ከ10ቱ ትዕዛዛት መእንዱና ግንባር ቀደሙ በፊትህ ማናቸውንም ምስል አትቅረጽ አትስገድላቸውም የሚል ነውና። ዘጸ20
10)ካህናት ጽሕማቸውን ያሳድጉታል እንጂ አይላጩትም እንኳን ካህናት ሥልጣነ ክህነት የሌላቸው ወንዶች እንኳ ከከንፈሮቻቸው ጽሕማቸውን እዳያራግፉ (እንዳይላጩ)ፍትሐ ነገሥት ያዛዛል።
11) ከጥንት እስከዛሬ በካህናትና በምዕመናን መካከል ያለ ልዮነት በእኩል ሥጋ ወደሙን እናቀብላለን ።
12)የሥጋውና ደሙ መንበር የሆነ የፈጣሪያችን ኅቡዕ ሥሞች የተቀረጹበት የምህረት መሰዊያ በሜሮን የከበረ ታቦት አለን።
#ካቶሊክ
1) መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ይሰርጻል ይላሉ።
2) ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት በሕርይ ነው ይላሉ።
3) ሰውች ስለሰሩት ኃጢያት ንስሐ ገብተው የንሰሐ ሥርዓትን እየፈጸሙ(ቀኖናቸውን)ሳይፈጽሙ ቢሞቱ በመንግሥተ ሰማያትና በገሃነም እሳት መካከል ልዮ የሆነ መካነ ንስሐ/Pergatory/ስላለ ወደዚያ በመሄድ መከራ ተቀብለው በኃላ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ ብለው ያምናሉ።
4) ፖፑ የክርስቶስ እንደራሴና የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በላይ ስለሆነ የሚወስነው ውሳኔ አይሳሳትም ብለው ያምናሉ።
5) ሕጻናትን አቁርበው ሜሮን የሚቀቡት አድገው ነፍስ ካወቁ በኃላ ነው።
6) የሚሰውት መሥዋዕት/የክርስቶስ ሥጋና ደም /ነፍስ ያለው መለኮት የተዋሐደው ነው ብለው ያምናሉ ።
7) ካህቶቻቸው በሙሉ ሚስት አያገቡም።
8) ከሥዕል በተጨማሪ ለጌታችን እና ለእመቤታች የድንጋይ ሃውልት ያቆማሉ።
9) ካህናቶቻቸው ጽሕማቸውን ይላጫሉ ::
10) ለቀዳስያን ካህናት ሥጋ ወደሙን ሲሰጡ ለምዕመናን ግን ሥጋውን ብቻ ያቀብላሉ በኃላ ከቫቲካን(ሀለት) 2 ጉባኤ ወዲህ ግን አሻሽለው ለምዕመናንም ሥጋና ደሙን እንዲሰጣቸው ወስነዋል። ሆኖም ሥጋውን በደሙ ውስጥ ነክረው ሥጋውን ብቻ ነው የሚያቀብሏቸው ። ይህንንም የሚያደርጉት ደም በሥጋ ያድራል ስለዚህ ደሙን ከሥጋው ያገኙታል የሚል ፍልስፍና ስላነገቡ ነው። ይህ ግን ዳቦን በሻይ ነክሮ እንደ ማውጣት ያለ ነውና ያስቅፋል ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በምሴተ አሙስ ለቅዱሳን ሐዋርያቶቹ ይህ ሥጋዬ ነው ብሎ ይህም ደሜ ነው ጠጡ አላቸው እንጂ ነክራችሁ ብሎ አላላቸውም። #ማቴ 26÷26
11) ታቦት የላቸውም
..........ይቆየን......
@YEAWEDIMERITE
ሕዳር 05/2013ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ወደ መልሱ ስናመራ በኦርቶዶክስ ተዋህዶና በካቶሊክ መካከል የሰማይና የምድር ያክል ብዙ ልዮነት አለ ልዮነት የለውም የሚሉ አካላትን በሦስት ከፍሎ መመልከት ይቻላል የመጀመሪያዎች ባለማወቅ ና በለመረዳት በየዋህነት አንድ ነን የሚሉ የዋሐን ሲሆኑ እነዚኞችን በማሳወቅ በመንገርና በማስተማር በቀናች ሃይማኖት ማጽናት ይጠበቅብናል ሁለተኞቹ ሆን ብለው ልዮነቱን እያወቁ ምዕመናንን በማደናገር በአንድነን ሽፋን ለማስኮብለል በማሰብ የሚናገሩት ሲሆን እነዚኞቹን ደግሞ በአፍ የሚያስተምሩትን በአፍ በመጽአፍ የሚያስተምሩትን በመጽሐፍ እንደ አመጣጣቸው መመለስ ይገባል “ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥14 ሦስተኞቹ ደግሞ ለመኮብለል በራሳቸው ተነሳሽነት ካመጡት ዝንባሌ የተነሳ ልዮነት የለም ወደ ሚል ዝንባሌያቸውን ትክክል ለማሰመሰል የሚጥሩ ወይም ለመሄድ ያኮበኮቡ ናቸውና ከእነዚኞቹ ነፍስ ይማር ብለን እንርቃቸዋለን
“ወንድሞች ሆይ፥ ከእኛ እንደ ተቀበለው ወግ ሳይሆን ያለ ሥርዓት ከሚሄድ ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዛችኋለን።”
— 2ኛ ተሰሎንቄ 3፥6
ከዚህ አንጻር ጥቂት ልዮነቶቻችንን እንመልከት
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ
1) መንፈስ ቅዱስ የሰረጸው ከአብ ብቻ ነው ።
2) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋህዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆኗል።
3)ንሰሐ መግባት በአጸደ ሥጋ እንጂ በአጸደ ነፍስ ሆና ንስሐ መግባት የለም ወይም አይቻልም ይህም ማለት በሰማይ መካነ ንስሐ የለም ።ያለውም የጽድቅ እና የኩነኔ ቦታ ነው። ለዚህም የአላዛርና የነዌ ታሪክ አስረጂ ነው። ሉቃ 16÷19
4) ሾማምንት የሚወስኑት ውሳኔ አይሳሳቱም ብለን አናምንም።
5) ህጻናትን ቃጠመቅን በኃላ ወዲያው 36 ዕዋሳቶቻቸውን ሜሮን እንቀባለን።
6) የምንሰዋው የክርስቶስን ክቡር ሥጋና ቅዱስ ደም ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሕደው ነው ብለን እናምናለን።
7 )ሕጻናት ከተጠመቁ በኃላ ሜሮን እንደተቀቡ ወዲያው ይቆርባሉ።
8)ከጳጳሳት በቀር ቀሳውስትና ዲያቆናት ማግባት ከፈለጉ አንዳንድ ሚስት አግብተው ክህነትን ተቀብለው ሊያገለግሉ ይችላሉ ።
9) ሥዕል እንስላለን እንጂ ሐውልት አንቀርጽም አንዳንድ የተሰሩ ሃውልቶች ቢኖሩም የኛ ትውፊት አይደለም ። ከ10ቱ ትዕዛዛት መእንዱና ግንባር ቀደሙ በፊትህ ማናቸውንም ምስል አትቅረጽ አትስገድላቸውም የሚል ነውና። ዘጸ20
10)ካህናት ጽሕማቸውን ያሳድጉታል እንጂ አይላጩትም እንኳን ካህናት ሥልጣነ ክህነት የሌላቸው ወንዶች እንኳ ከከንፈሮቻቸው ጽሕማቸውን እዳያራግፉ (እንዳይላጩ)ፍትሐ ነገሥት ያዛዛል።
11) ከጥንት እስከዛሬ በካህናትና በምዕመናን መካከል ያለ ልዮነት በእኩል ሥጋ ወደሙን እናቀብላለን ።
12)የሥጋውና ደሙ መንበር የሆነ የፈጣሪያችን ኅቡዕ ሥሞች የተቀረጹበት የምህረት መሰዊያ በሜሮን የከበረ ታቦት አለን።
#ካቶሊክ
1) መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ይሰርጻል ይላሉ።
2) ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት በሕርይ ነው ይላሉ።
3) ሰውች ስለሰሩት ኃጢያት ንስሐ ገብተው የንሰሐ ሥርዓትን እየፈጸሙ(ቀኖናቸውን)ሳይፈጽሙ ቢሞቱ በመንግሥተ ሰማያትና በገሃነም እሳት መካከል ልዮ የሆነ መካነ ንስሐ/Pergatory/ስላለ ወደዚያ በመሄድ መከራ ተቀብለው በኃላ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ ብለው ያምናሉ።
4) ፖፑ የክርስቶስ እንደራሴና የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በላይ ስለሆነ የሚወስነው ውሳኔ አይሳሳትም ብለው ያምናሉ።
5) ሕጻናትን አቁርበው ሜሮን የሚቀቡት አድገው ነፍስ ካወቁ በኃላ ነው።
6) የሚሰውት መሥዋዕት/የክርስቶስ ሥጋና ደም /ነፍስ ያለው መለኮት የተዋሐደው ነው ብለው ያምናሉ ።
7) ካህቶቻቸው በሙሉ ሚስት አያገቡም።
8) ከሥዕል በተጨማሪ ለጌታችን እና ለእመቤታች የድንጋይ ሃውልት ያቆማሉ።
9) ካህናቶቻቸው ጽሕማቸውን ይላጫሉ ::
10) ለቀዳስያን ካህናት ሥጋ ወደሙን ሲሰጡ ለምዕመናን ግን ሥጋውን ብቻ ያቀብላሉ በኃላ ከቫቲካን(ሀለት) 2 ጉባኤ ወዲህ ግን አሻሽለው ለምዕመናንም ሥጋና ደሙን እንዲሰጣቸው ወስነዋል። ሆኖም ሥጋውን በደሙ ውስጥ ነክረው ሥጋውን ብቻ ነው የሚያቀብሏቸው ። ይህንንም የሚያደርጉት ደም በሥጋ ያድራል ስለዚህ ደሙን ከሥጋው ያገኙታል የሚል ፍልስፍና ስላነገቡ ነው። ይህ ግን ዳቦን በሻይ ነክሮ እንደ ማውጣት ያለ ነውና ያስቅፋል ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በምሴተ አሙስ ለቅዱሳን ሐዋርያቶቹ ይህ ሥጋዬ ነው ብሎ ይህም ደሜ ነው ጠጡ አላቸው እንጂ ነክራችሁ ብሎ አላላቸውም። #ማቴ 26÷26
11) ታቦት የላቸውም
..........ይቆየን......
@YEAWEDIMERITE
ሕዳር 05/2013ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ዐውደ ምሕረት
Photo
ከወደቁ አይቀር .....#ለጽዮን
____________________
አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::
#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::
ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::
#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ
በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::
#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።
“ #የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14
አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
ኅዳር 21/2013ዓ.ም የተከተበ
____________________
አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::
#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::
ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::
#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ
በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::
#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።
“ #የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14
አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
ኅዳር 21/2013ዓ.ም የተከተበ
#እቡዘ_ልብ ለምን ሆንክ ?
_______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ግንቦት 11/2014ዓ.ም
_______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ግንቦት 11/2014ዓ.ም
ከወደቁ አይቀር .....#ለጽዮን
____________________
አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::
#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::
ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::
#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ
በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::
#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።
“ #የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14
አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
ኅዳር 21/2013ዓ.ም የተከተበ
____________________
አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::
#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::
ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::
#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ
በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::
#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።
“ #የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14
አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
ኅዳር 21/2013ዓ.ም የተከተበ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዕርገተ ክርስቶስ"
#ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ፤ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ፤ዘምሩ ለንጉሣችን ዘምሩ"(መዝ46:5) በማለት ጌታው ሲሆን ልጁ ልጁ ሲሆን ጌታው ስለሚሆን ስለ ኢየሱስ ክርሰቶስ ትንቢት ተናግሯል።
#በዚህ ኃይለ ቃል ያለው ምሥጢረ ተዋሕዶ ምንድን ነው? ቢሉ "አምላክ" ብሎ አምላክነቱን "ዐረገ" ብሎ ሰውነቱን ያስረዳል።ማረግ (ከፍ ከፍ ማለት፣ወደ ሰማይ መውጣት) የሚስማማው ሥጋ ነውና በተዋሕደው "ሥጋ ማርያም" በሁሉ ላለ "ቃል ለሚባል እግዚአብሔር" ዕርገት ተነገረለት።
#ነገሩን ትንሽ ለመግለጥ ያህል፦አምላክ በሁሉ ቦታ (በምልዐት) የሚገኝ ስለሆነ ከዚህ ተነሥቶ እዚያ ደረሰ አይባልም።አምላክ በተዋሕዶ ሰው ሲሆን ግን ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር ለእኛ የሚነገረው ሁሉ ለእርሱም ተነገረለት።ተፀነሰ፣ተወለደ፣ተሰደደ፣ተጠመቀ፣ተሰቀለ፣ሞተ፣ተቀበረ፣ተነሣ፣ዐረገ ተባለለት።ይህ ሁሉ ግን በበጎ ፈቃዱ የተከናወነ ነው ፤ እንደኛ ግዳጅ ያለበት አይደለም።
#ክርስትና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን የእግር አሻራ የመከተል ሕይወት ነውና እርሱ ስለኛ የፈጸማቸውን ሁሉ እንፈጽማለን።ኋላም እርሱ በኃይሉና በሥልጣኑ ተነሥቶ እንዳረገ እንዲሁ እኛንም አስነሥቶ ያሳርገናል።ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ "እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ" ማለቱም ለዚህ ነው።
#ወደ እኔ እወስዳችኋለሁ ብሎ ጌታችን የነገረን ቃል እኔን በመመሰል እንድታድጉ (Theosis:ሱታፌ አምላክ) አደርጋችኋለሁ ሲል ነው።ይኸውም በመንግሥተ ሰማያት የምንኖረው ኑሮ "ዕርገታዊ" (ከፍ ከፍ የማለት) እንደሆነ ያስረዳል።ከቅዱሳን መላእክቱ ጋር "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" በማለት ውስጥ እየተቀደስን በጸጋ ላይ ጸጋ በክብር ላይ ክብር በጣዕም ላይ ጣዕም እየተጨመረልን እግዚአብሔርን እየመሰልን ከፍ እንላለን።
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን!!!
#ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ፤ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ፤ዘምሩ ለንጉሣችን ዘምሩ"(መዝ46:5) በማለት ጌታው ሲሆን ልጁ ልጁ ሲሆን ጌታው ስለሚሆን ስለ ኢየሱስ ክርሰቶስ ትንቢት ተናግሯል።
#በዚህ ኃይለ ቃል ያለው ምሥጢረ ተዋሕዶ ምንድን ነው? ቢሉ "አምላክ" ብሎ አምላክነቱን "ዐረገ" ብሎ ሰውነቱን ያስረዳል።ማረግ (ከፍ ከፍ ማለት፣ወደ ሰማይ መውጣት) የሚስማማው ሥጋ ነውና በተዋሕደው "ሥጋ ማርያም" በሁሉ ላለ "ቃል ለሚባል እግዚአብሔር" ዕርገት ተነገረለት።
#ነገሩን ትንሽ ለመግለጥ ያህል፦አምላክ በሁሉ ቦታ (በምልዐት) የሚገኝ ስለሆነ ከዚህ ተነሥቶ እዚያ ደረሰ አይባልም።አምላክ በተዋሕዶ ሰው ሲሆን ግን ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር ለእኛ የሚነገረው ሁሉ ለእርሱም ተነገረለት።ተፀነሰ፣ተወለደ፣ተሰደደ፣ተጠመቀ፣ተሰቀለ፣ሞተ፣ተቀበረ፣ተነሣ፣ዐረገ ተባለለት።ይህ ሁሉ ግን በበጎ ፈቃዱ የተከናወነ ነው ፤ እንደኛ ግዳጅ ያለበት አይደለም።
#ክርስትና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን የእግር አሻራ የመከተል ሕይወት ነውና እርሱ ስለኛ የፈጸማቸውን ሁሉ እንፈጽማለን።ኋላም እርሱ በኃይሉና በሥልጣኑ ተነሥቶ እንዳረገ እንዲሁ እኛንም አስነሥቶ ያሳርገናል።ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ "እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ" ማለቱም ለዚህ ነው።
#ወደ እኔ እወስዳችኋለሁ ብሎ ጌታችን የነገረን ቃል እኔን በመመሰል እንድታድጉ (Theosis:ሱታፌ አምላክ) አደርጋችኋለሁ ሲል ነው።ይኸውም በመንግሥተ ሰማያት የምንኖረው ኑሮ "ዕርገታዊ" (ከፍ ከፍ የማለት) እንደሆነ ያስረዳል።ከቅዱሳን መላእክቱ ጋር "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" በማለት ውስጥ እየተቀደስን በጸጋ ላይ ጸጋ በክብር ላይ ክብር በጣዕም ላይ ጣዕም እየተጨመረልን እግዚአብሔርን እየመሰልን ከፍ እንላለን።
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን!!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
Ethiopia : #ዲያቆን ዘላለም ታዬ #ወደ ድኅነት የሚያመራ ድንቅ ስብከት #የኃጢኣትን በር ጥልቀት አሳየን #eotc #Dn Zelalem Taye #sibket
Ethiopia : #ዲያቆን ዘላለም ታዬ #ወደ ድኅነት የሚያመራ ድንቅ ስብከት #የኃጢኣትን በር ጥልቀት አሳየን #eotc #Dn Zelalem Taye #sibket
#sibket
#Mezmur
#ኆኅተ ብርሃን
#habesha
#eotcmk
#ኃጢአት
|ንስሐ
Sibket 2024, Ethiopia News, Habesha, Dr Abiy, Jawar Mohamed, Amharic Movie, Ethiopia music, Abel…
#sibket
#Mezmur
#ኆኅተ ብርሃን
#habesha
#eotcmk
#ኃጢአት
|ንስሐ
Sibket 2024, Ethiopia News, Habesha, Dr Abiy, Jawar Mohamed, Amharic Movie, Ethiopia music, Abel…
#አባቴ_ነውና_አዎን አውቀዋለሁ !
______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ግንቦት 11/2014ዓ.ም
______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ግንቦት 11/2014ዓ.ም