+++🙏 የጉጠቱ ፍም 🙏+++
🙏 እግዚአብሔርን በመለኮቱ ልዕልና ያየው ማንም የለም ነገር ግን እርሱን መስለው ለኖሩ ቅዱሳን በአቅማቸው ልክ ይገለጥላቸዋልያናግራቸውማል።
ለአብርሃም በሽማግሌ ፣ ለሙሴ በሃመልማል እንዲሁም ለእነ ዳንኤል ዕዝራ ኢሳይያስ አይቶ በቃላት ድርድር ማስረዳት በማይቻልበት ክብር ተገልጦላቸዋል።
🙏የጉጠቱን ፍም ስናስብ ከክርስቶስ ልደት በፊት ንጉስ ዖዝያን የሞተበትን ዓመት እናስታውሳለን መጽሐፍ እንደሚነግረን የይሁዳ ሕዝብ እስራኤልን እንዲመራ ዖዝያንን ገና የ16 ዓመት ጎልማሣ እያለ ነበር የቀቡት የንግስናን ዘውድ ደፍተው የወርቅ ካባን የደረቡለት።በንግስናውም ዘመን መልካሙንም ክፋውንም አሳልፏል።ከፍልስጥኤማውያን ጋር በነበረው ጦርነት እግዚአብሔር ረድቶት እነርሱን ድል አድርጎል በኋላ ዝናው እና ስሙ በዓለም ሁሉ ተሰማለት በደስታውም ተነሳስቶ ሦስት መቶ ሰባ ሺ አምስት መቶ ለሚሆኑ ጭፍሮቹ ልዩ ልዩ የሆኑ ጋሻና ጦር ቀስቶችን ሰርቶ አስረከባቸው ነገር ግን ይህን ሁሉ የስኬት ጫማ ሲጫመት የረዳውን አምላክ በመዘንጋቱ ልቡ ታበየ አምላኩንም በደለ በዙፋኑ በቀኝ አብሮት የሚቀመጠውን ካህኑን አዛርያስን ለምን በቀኜ ትቀመጣለህ በማለት ሠማያዊ ወምድራዊ ሥልጣን ካለው ጋር ይፎካከር ጀመረ እርሱም መልሶ "ካህን ይነብር በየማንከ(ካህናት በቀኝ ይቀመጣሉ)" ይልብሀል ህጉ ይለውና ደንቡን ነግሮ ዝም የስብለዋል ቀኝ የክብር መገለጫ ነውና።ኋላ ግን ዖዝያን በድፍረት ቤተመቅደስ ገብቶ ያለ ሥልጣኑ በዕጣን መሰዊያ ላይ አጠነ ያኔ እግዚአብሔር አምላክ በለምጽ መታው ከሰው ተለይቶ በተለየ ቤት ለምጻም ሆኗልና ተቀመጠ ጊዜውም ደረሰና የንግስናውን ዘውድ ለልጁ አስረክቦ ከዚች አለም በሞተ ተለየ።
🙏ንጉስ ዖዝያን በሞተበት አመት ልጁ ኢዮአታም በምትኩ በነገሰበት ዘመን ነበር ነብዮ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ከፍ ባለ በሚያስፈራ ዙፋን የልብሱ ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት የተመለከተው። ቅዱሳን የቅድስናቸው ደረጃ ጥግ ሲደረስ እግዚአብሔርን የማያት ክብር ላይ ይደርሳሉ። እንዴት መታደል ነው! እግዚአብሔርን ማየት! ማነው ይህንን ክብር'ስ የማይፈልግ? ነቢዩ በዙፋኑ ላይ ለማመን የሚከብዱ ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የመጠቁ ዕጹብ የሚያስብሉ ድንቆችንም ተመልክቷል፤ሃያ አራቱ ካህናተ ሠማያ ስድት ክንፍ ያላቸው በመቅደሱ ዙሪያ ረበው አንተን ማየት አይቻለንም ሲሉ በሁለቱ ክንፋቸው ፊታቸውን ይሸፍናሉ በአንተ ፊት መቆም አይቻለንም ሲሉ በሁለቱ ክንፋቸው እግራቸውን ሸፍነው በቀሪው ሁለት ክንፋቸው እየበረሩ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ያመሠግናሉ። ምግባቸው መጠጣቸው ህይወታቸው ምስጋና! የእኛስ ህይወት? በምስጋና የተሞላ ወይስ በማማረር? መልሱን ለእራሳችን ። የሚደንቀው ነገር ሱራፌልም እኛም እርሱን ብናመሰግን ለእግዚአብሔር የምንጨምረው የምንቀንሰው ባለመኖሩ ነው ይልቁንስ አመስግነን መንግስቱን እንወርሳለን እንጂ።
🙏በመላእክቱ የምስጋና ቃል ጩኸት የመድረኩ መሠረት ተናወጠ ቤቱም በጢስ ተሞላ ነብዪም ተጨነቀ እጅግም ፈራ “እንዲህም ሲል ተናገረ፦ ከንፈሮቼ የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ! "
ትሁት አነጋገር! እግዚአብሔርን አይቻለሁ በቅቻለሁ ብሎ አልታበየም ነብዩ ኢሳይያስ ዖዚያን ከብርያለው ገንኛለሁ ብሎ እንደታበየ ይልቁን እራሱን ከነፈሮቻቸው በረከሱባቸው ሰዎች ጉባኤ መሀል ወረወረ ራሱን ዝቅ አደረገ የሠራዊት ጌታ ዝቅታውን ፀፀቱን ተመልክቶ አንዱን ሱራፌል ላከለት ያም መልአክ በእጁ ከመሠዊያው በጉጠት ፍም ወስዶ አፋንም ዳሰሰለት ቀጠለና ታላቅ የድኅነት ቃል አሰማው " እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ።” በነብዩ ኤርሚያስ የተነገረው “እግዚአብሔርም እጁን ዘርግቶ አፌን ዳሰሰ፥ እግዚአብሔርም፦ እነሆ፥ ቃሌን በአፍህ ውስጥ አኑሬአለሁ” የሚለው ትንቢት ተፈጸመ።
🙏+ ጌታ ሆይ እንደ ነብዩ የተተረኮሰ አንደበት ስጠን ለእርሱም የላከውን ፍም እሳት ላክና ከአርያም የሚያቃጥለንን በደል ኃጢአት የሚያሰራንን በውስጣችን ያለውን እንክርዳድ አቃጥልልን። +
15/02/2014
ድሬዳዋ ኢትዮጵያ
ተጻፈ በባሮክ ዘ አሚን
🙏 እግዚአብሔርን በመለኮቱ ልዕልና ያየው ማንም የለም ነገር ግን እርሱን መስለው ለኖሩ ቅዱሳን በአቅማቸው ልክ ይገለጥላቸዋልያናግራቸውማል።
ለአብርሃም በሽማግሌ ፣ ለሙሴ በሃመልማል እንዲሁም ለእነ ዳንኤል ዕዝራ ኢሳይያስ አይቶ በቃላት ድርድር ማስረዳት በማይቻልበት ክብር ተገልጦላቸዋል።
🙏የጉጠቱን ፍም ስናስብ ከክርስቶስ ልደት በፊት ንጉስ ዖዝያን የሞተበትን ዓመት እናስታውሳለን መጽሐፍ እንደሚነግረን የይሁዳ ሕዝብ እስራኤልን እንዲመራ ዖዝያንን ገና የ16 ዓመት ጎልማሣ እያለ ነበር የቀቡት የንግስናን ዘውድ ደፍተው የወርቅ ካባን የደረቡለት።በንግስናውም ዘመን መልካሙንም ክፋውንም አሳልፏል።ከፍልስጥኤማውያን ጋር በነበረው ጦርነት እግዚአብሔር ረድቶት እነርሱን ድል አድርጎል በኋላ ዝናው እና ስሙ በዓለም ሁሉ ተሰማለት በደስታውም ተነሳስቶ ሦስት መቶ ሰባ ሺ አምስት መቶ ለሚሆኑ ጭፍሮቹ ልዩ ልዩ የሆኑ ጋሻና ጦር ቀስቶችን ሰርቶ አስረከባቸው ነገር ግን ይህን ሁሉ የስኬት ጫማ ሲጫመት የረዳውን አምላክ በመዘንጋቱ ልቡ ታበየ አምላኩንም በደለ በዙፋኑ በቀኝ አብሮት የሚቀመጠውን ካህኑን አዛርያስን ለምን በቀኜ ትቀመጣለህ በማለት ሠማያዊ ወምድራዊ ሥልጣን ካለው ጋር ይፎካከር ጀመረ እርሱም መልሶ "ካህን ይነብር በየማንከ(ካህናት በቀኝ ይቀመጣሉ)" ይልብሀል ህጉ ይለውና ደንቡን ነግሮ ዝም የስብለዋል ቀኝ የክብር መገለጫ ነውና።ኋላ ግን ዖዝያን በድፍረት ቤተመቅደስ ገብቶ ያለ ሥልጣኑ በዕጣን መሰዊያ ላይ አጠነ ያኔ እግዚአብሔር አምላክ በለምጽ መታው ከሰው ተለይቶ በተለየ ቤት ለምጻም ሆኗልና ተቀመጠ ጊዜውም ደረሰና የንግስናውን ዘውድ ለልጁ አስረክቦ ከዚች አለም በሞተ ተለየ።
🙏ንጉስ ዖዝያን በሞተበት አመት ልጁ ኢዮአታም በምትኩ በነገሰበት ዘመን ነበር ነብዮ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ከፍ ባለ በሚያስፈራ ዙፋን የልብሱ ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት የተመለከተው። ቅዱሳን የቅድስናቸው ደረጃ ጥግ ሲደረስ እግዚአብሔርን የማያት ክብር ላይ ይደርሳሉ። እንዴት መታደል ነው! እግዚአብሔርን ማየት! ማነው ይህንን ክብር'ስ የማይፈልግ? ነቢዩ በዙፋኑ ላይ ለማመን የሚከብዱ ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የመጠቁ ዕጹብ የሚያስብሉ ድንቆችንም ተመልክቷል፤ሃያ አራቱ ካህናተ ሠማያ ስድት ክንፍ ያላቸው በመቅደሱ ዙሪያ ረበው አንተን ማየት አይቻለንም ሲሉ በሁለቱ ክንፋቸው ፊታቸውን ይሸፍናሉ በአንተ ፊት መቆም አይቻለንም ሲሉ በሁለቱ ክንፋቸው እግራቸውን ሸፍነው በቀሪው ሁለት ክንፋቸው እየበረሩ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ያመሠግናሉ። ምግባቸው መጠጣቸው ህይወታቸው ምስጋና! የእኛስ ህይወት? በምስጋና የተሞላ ወይስ በማማረር? መልሱን ለእራሳችን ። የሚደንቀው ነገር ሱራፌልም እኛም እርሱን ብናመሰግን ለእግዚአብሔር የምንጨምረው የምንቀንሰው ባለመኖሩ ነው ይልቁንስ አመስግነን መንግስቱን እንወርሳለን እንጂ።
🙏በመላእክቱ የምስጋና ቃል ጩኸት የመድረኩ መሠረት ተናወጠ ቤቱም በጢስ ተሞላ ነብዪም ተጨነቀ እጅግም ፈራ “እንዲህም ሲል ተናገረ፦ ከንፈሮቼ የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ! "
ትሁት አነጋገር! እግዚአብሔርን አይቻለሁ በቅቻለሁ ብሎ አልታበየም ነብዩ ኢሳይያስ ዖዚያን ከብርያለው ገንኛለሁ ብሎ እንደታበየ ይልቁን እራሱን ከነፈሮቻቸው በረከሱባቸው ሰዎች ጉባኤ መሀል ወረወረ ራሱን ዝቅ አደረገ የሠራዊት ጌታ ዝቅታውን ፀፀቱን ተመልክቶ አንዱን ሱራፌል ላከለት ያም መልአክ በእጁ ከመሠዊያው በጉጠት ፍም ወስዶ አፋንም ዳሰሰለት ቀጠለና ታላቅ የድኅነት ቃል አሰማው " እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ።” በነብዩ ኤርሚያስ የተነገረው “እግዚአብሔርም እጁን ዘርግቶ አፌን ዳሰሰ፥ እግዚአብሔርም፦ እነሆ፥ ቃሌን በአፍህ ውስጥ አኑሬአለሁ” የሚለው ትንቢት ተፈጸመ።
🙏+ ጌታ ሆይ እንደ ነብዩ የተተረኮሰ አንደበት ስጠን ለእርሱም የላከውን ፍም እሳት ላክና ከአርያም የሚያቃጥለንን በደል ኃጢአት የሚያሰራንን በውስጣችን ያለውን እንክርዳድ አቃጥልልን። +
15/02/2014
ድሬዳዋ ኢትዮጵያ
ተጻፈ በባሮክ ዘ አሚን
ኒቆዲሞስ ማነው? ምን ምንስ
አደረገ?
🌕🌖🌗🌒🌑
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር መጥቶ የምስራቹን ቃል ሲያውጅ እስራኤላውያን የተቀበሉት በተደበላለቀ ስሜት ነበር፡፡ በአንድ በኩል ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ሲገዛ ስለነበር ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነጻ የሚያወጣቸው መሲህ ይፈልጋሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ቀንበር ስለደከመ ተስፋ በመቁረጥ ተዳክሞ ነበር፡፡
መሲህ ቢመጣ እንኳ ይመጣል ብለው የሚጠብቁት ጦር ይዞ ሰራዊት አስከትሎ ነው ብለው ያምኑ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው ክርስቶስን መሲህ ነኝ ብሎ ሲመጣ ለመቀበል ፈቃደኞች አልነበሩም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ጦር ሳይዝ ሰራዊት ሳያስከትል እንዲሁ ባዶ እጁን አርነት ላወጣችሁ መጥቻለሁ እያለ ደጋግሞ ተናግሯልና ነው፡፡ ምንም እንኳ አብዛኛው እስራኤላዊ የክርስቶስን መሲህነት ቢጠራጠርና ባይቀበለውም፣ በፍጹም እምነት እስከ መጨረሻው የተከተሉትም ነበሩ፡፡ ለዚህም ትልቅ ማሳያ የሚሆነን ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አይሁዳዊ ነው፡፡ቅድስት ቤተክርስቲያንም ይህን ታላቅ ሰው ለማዘከር የዐቢይን ጾም ሰባተኛ እሁድ በእርሱ ስም ሰይማ ታከብረዋለች ፡፡ ተከታዮቿ ምዕመናንም የእርሱን አሰረ ፍኖት እንዲከተሉ ትመክራለች ታስተምራለችም፡፡
ኒቆዲሞስ ማነው?
፩. ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ነው ዮሐ 3-1
የእስራኤላዊያን ለብዙ ዘመን በባርነት መኖር የሕዝቡን የአኗኗር ሁኔታ ቀይሮታል፡፡በግዞት ጊዜ ከአሕዛብ የቀሰሟቸው አጉል ትምህርቶች በእምነትም በአስተሳሰብም እጅግ እንዲለያዩና እንዲራራቁ ምክንያት ሆኗል፡፡ አይሁዳዊ ሳምራዊ፤ ከአይሁድም ሰዱቃዊ ፣ ፈሪሳዊ ፣ ጸሐፍት ፣ ኤሴያዊ ብለው እንዲከፋፈሉ ከዚህም እጅግ ወርደው ገሊላዊ ናዝራዊ እንዲባባሉ ያበቃቸው ከአህዛብ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ፈር ባለማስያዛቸው ነበር፡፡ ፈሪሳዊያን ደግሞ ሕግን በማጥበቅ ሕዝቡን የሚያስመርሩ ቀሚሳቸውን በማስረዘም እነሱ የማይፈጽሙትን ሕግ በሕዝብ ላይ የሚጭኑ ራሳቸውን ከሌሎች በላይ ከፍ ከፍ የሚያደርጉ አባታችን አብርሐም እያሉ የሚመጻደቁ የአባታቸው የአብርሐምን ስራ ግን የማይሰሩ ክፍሎች ናቸው ዮሐ 8-39፡፡ ታዲያ ኒቆዲሞስ ምንም እንኳ ከፈሪሳዊያን ወገን ቢሆንም ራሱን ከዚህ ሕዝብ ለይቶ ክርስቶስን ፍለጋ በፍጹም ልቡ የመጣ ፈሪሳዊ ነው፡፡ ቀድሞ አባታችን አብርሀምን ከቤተሰብህ ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ ያለው አምላክ ኒቆዲሞስን ከፈሪሳዊያን ለይቶ ጠራው፡፡ ዘፍ 12
፪. ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ነው ዮሐ 3-1
ሮማውያን ሕዝቡን የሚያሥተዳድሩት ከላይ ያለውን ዋና ሥልጣን ተቆናጠው ታች ያለውን ሕዝብ ደግሞ ባህላቸውን በሚያውቅ ቋንቋቸውን በሚጠነቅቅ አይሁዳዊ ምስለኔ ነው፡፡ አውሮፓውያንም አፍሪካን ለመቀራመት የተጠቀሙበት ስልት ይህን ዓይነት ነበር፡፡ ኒቆዲሞስም ምንም እንኳ ፈሪሳዊ ቢሆን አለቃ እንዲሆን በሮማውያን የተሾመ ባለሥልጣን ነው፡፡
፫. ኒቆዲሞስ መምህረ እስራኤል ነው ዮሐ 3-10
ጌታ ምስጢረ ጥምቀትን በገለጸለት ጊዜ ሲደናገር አይቶ «አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን? » ብሎታል፡፡ ይህ የሚጠቁመን ኒቆዲሞስ አለቅነትን ከመምህርነት የያዘ በአይሁዳውያን የታፈረና የተከበረ ሰው እንደነበረ ነው፡፡ መምህር ቢሆንም የሚቀረኝ ያላወቅሁት ያልጠነቀቅሁት ብዙ ነገር አለ በማለት የመምህርነቱን ካባ አውልቆ የተማሪነትን ዳባ ለብሶ ከክርስቶስ ሊማር መጣ፡፡
፬. ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ነው ዮሐ 7-51
አንዳንዴ ሳያውቁ አወቅን ሳይማሩ እናስተምር የሚሉ ደፋር መምህራን አይጠፉም፡፡ ኒቆዲሞስ ግን ከዚህ በተለየ አለቅነትን ከመምህርነት መምህርነትን ከምሁርነት አስተባብሮ የያዘ ዕውቀትን ከትህትና ምሁርነትን ከደፋርነት አንድ አድርጎ የያዘ ሰው ነበር፡፡ የኦሪት ምሁር መሆኑን የሚጠቁመን ደግሞ ከካህናት አለቆች ጋር ያደረገውን ክርክር ባስታወስን ጊዜ ነው፡፡
ኒቆዲሞስ ምን አደረገ?
ለምስጢረ ጥምቀት መገለጥ ምክንያት ሆነ ዮሐ 3 1-21
የአይሁድ የፋሲካ በዓል እየቀረበ ሲመጣ ክርስቶስ ቀኑ እንደደረሰ ለሐዋርያቱ ተናግሮ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፡፡ እንደ ሰውነቱ ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይል ሕዝቡን ቀንና ሌሊት በትምህርትና በተዐምራት ያገለግል ነበር፡፡ በዚህ ሰዐት ነው ኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው፡፡ በፊቱ ቀርቦም «መምህር ሆይ » ብሎ የእርሱን አላዋቂነት የክርስቶስን ማእምረ ኅቡዐትነት (የተሰወረን አዋቂነት) መሰከረ፡፡ ጌታችንም አመጣጡ ከልብ መሆኑን አውቆ ምሥጢረ ጥምቀትን (ዳግም ውልደትን) ገለጸለት፡፡ ምስጢሩ የኦሪት ምሁር ለነበረው ኒቆዲሞስ ለጆሮ የከበደ ለመቀበል የሚቸግር ሆነበት፡፡ የከበደውን የሚያቀል የጠበበውን የሚያሰፋ አምላክ ምሥጢሩ ለኒቆዲሞስ እንደከበደው ስለተረዳ ቀለል አደረገለት፡፡ ዳግም ውልደት ከእናት ማኅፀን ሳይሆን ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ አብራራለት ፡፡
አዋቂ ነን የሚሉትን አሳፈራቸው ዮሐ 7-51
ወቅቱ የአይሁድ የፋሲካ በዓል የቀረበበት ጻፎችና የካህናት አለቆች ጌታን ለመያዝ፣ እንደሙሴም ህግ ሊያስፈርዱበት የቋመጡበት ጊዜ ነበር፡፡ የሙሴ ፈጣሪ መሆኑን መቸ አወቁና? የካህናት አለቆች ተሰብስበው ክርስቶስን ለመያዝ በሚመካከሩ ጊዜ ከሙሴ መጽሐፍ ሕግ ጠቅሶ ሊቃውንተ ኦሪትን አፍ ያስያዛቸው እሱ ነበር፡፡በዚህም የተነሳ ሳይስማሙ ወደየቤታቸው እንዲበታተኑ ምክንያት የሆነ ታላቅ ሰው ነው፡፡
ጌታን ለመገነዝ በቃ ዮሐ 19-38
ጌታችን በቀራንዮ አደባባይ ራሱን ለዓለሙ ቤዛ አድርጎ ሲሰጥ እስከ ሞት ከአንተ አንለይህም ያሉት ደቀ መዛሙርቱ ሲበታተኑ ፣ከዮሐንስ በቀር ፣በዘጠኝ ሰዐት ቀራንዮ የነበረ ኒቆዲሞስ ነበር፡፡ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ሆኖ የክርስቶስን ስጋ ከአለቆች ለምኖ፣ የገነዘ፣የክርስቶስን ክቡር ሥጋ ከርቤና የእሬት ቅልቅል ያርከፈከፈለት ወደ ሐዲስ መቃብር ያወረደውም ኒቆዲሞስ ነበር፡፡
ከኒቆዲሞስ ምን እንማር?
አትኅቶ ርእስ
በቅዱስ ወንጌል ላይ በተደጋጋሚ የምናገኘው የፈሪሳውያንን ግብዝነትና የጌታችንን ተግሳጽ ነው፡፡ ማቴ 9 10፣ ማቴ 23፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነን የፈሪሳዊውና የቀራጩ ጸሎት ምን ይመስል እንደነበር መመልከት ነው ሉቃ 18 9፡፡ ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፣ የአይሁድ አለቃ ፣መምህረ እስራኤል ፣ምሁረ ኦሪት ቢሆንም ራሱን ዝቅ አድርጎ ከጌታ እግር ስር ቁጭ አለ፡፡ ሕዝብን ከመምራትና ከማስተማር ይልቅ ቁጭ ብሎ መማር ምንኛ መታደል ነው! ጌታስ በትምህርቱ «ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርሷም አይወሰድባትም » ያለ ለዚህ አይደል ሉቃ 10 42፡፡ ብዙዎቻችን ባለን የኑሮ ደረጃ የዕውቀት ደረጃ የስልጣን ደረጃ ራሳችን ሰቅለን የመማር አቅም አጥተናል፡፡ ቁጭ ብሎ መማር ደረጃችንን የማይመጥን የሚመስለንስ ስንቶች እንሆን? አንድ ወቅት አባ መቃርስ ከህጻናት እንቆቅልሽ ለመማር ቁጭ እንዳሉ በእንቆቅልሹም ልባቸው ተነክቶ እያነቡ ወደ በዐታቸው መመለሳቸውን እያወቅን የመማር አቅም ያጣን ስንቶች እንሆን? ማን ያውቃል ከአንድ ሰአት ስብከት ውስጥ እግዚአብሔር ሊያስተመረን የፈለገ አንዲት ዐረፍተ ነገር ቢሆንስ? ትሑት የሚያሰኘው ሳያውቁ አላውቅም ማለት ሳይሆን እያወቁ አላውቅም ማለት ነው፡፡ ሳይማሩ ተምሬያለሁ ማለት ሳይሆን ተምረውም ልክ እንደ ኒቆዲሞስ ለመማር ራስን ዝቅ ማድረግ ነው፡፡
ጎደሎን ማወቅ
መምህርም ምሁርም ሆኖ ቁጭ ብሎ መማር ምን ረብ አለው? ይባል ይሆናል፡፡ ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት እንጅ ምሁረ ሐዲስ አይደ
አደረገ?
🌕🌖🌗🌒🌑
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር መጥቶ የምስራቹን ቃል ሲያውጅ እስራኤላውያን የተቀበሉት በተደበላለቀ ስሜት ነበር፡፡ በአንድ በኩል ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ሲገዛ ስለነበር ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነጻ የሚያወጣቸው መሲህ ይፈልጋሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ቀንበር ስለደከመ ተስፋ በመቁረጥ ተዳክሞ ነበር፡፡
መሲህ ቢመጣ እንኳ ይመጣል ብለው የሚጠብቁት ጦር ይዞ ሰራዊት አስከትሎ ነው ብለው ያምኑ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው ክርስቶስን መሲህ ነኝ ብሎ ሲመጣ ለመቀበል ፈቃደኞች አልነበሩም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ጦር ሳይዝ ሰራዊት ሳያስከትል እንዲሁ ባዶ እጁን አርነት ላወጣችሁ መጥቻለሁ እያለ ደጋግሞ ተናግሯልና ነው፡፡ ምንም እንኳ አብዛኛው እስራኤላዊ የክርስቶስን መሲህነት ቢጠራጠርና ባይቀበለውም፣ በፍጹም እምነት እስከ መጨረሻው የተከተሉትም ነበሩ፡፡ ለዚህም ትልቅ ማሳያ የሚሆነን ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አይሁዳዊ ነው፡፡ቅድስት ቤተክርስቲያንም ይህን ታላቅ ሰው ለማዘከር የዐቢይን ጾም ሰባተኛ እሁድ በእርሱ ስም ሰይማ ታከብረዋለች ፡፡ ተከታዮቿ ምዕመናንም የእርሱን አሰረ ፍኖት እንዲከተሉ ትመክራለች ታስተምራለችም፡፡
ኒቆዲሞስ ማነው?
፩. ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ነው ዮሐ 3-1
የእስራኤላዊያን ለብዙ ዘመን በባርነት መኖር የሕዝቡን የአኗኗር ሁኔታ ቀይሮታል፡፡በግዞት ጊዜ ከአሕዛብ የቀሰሟቸው አጉል ትምህርቶች በእምነትም በአስተሳሰብም እጅግ እንዲለያዩና እንዲራራቁ ምክንያት ሆኗል፡፡ አይሁዳዊ ሳምራዊ፤ ከአይሁድም ሰዱቃዊ ፣ ፈሪሳዊ ፣ ጸሐፍት ፣ ኤሴያዊ ብለው እንዲከፋፈሉ ከዚህም እጅግ ወርደው ገሊላዊ ናዝራዊ እንዲባባሉ ያበቃቸው ከአህዛብ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ፈር ባለማስያዛቸው ነበር፡፡ ፈሪሳዊያን ደግሞ ሕግን በማጥበቅ ሕዝቡን የሚያስመርሩ ቀሚሳቸውን በማስረዘም እነሱ የማይፈጽሙትን ሕግ በሕዝብ ላይ የሚጭኑ ራሳቸውን ከሌሎች በላይ ከፍ ከፍ የሚያደርጉ አባታችን አብርሐም እያሉ የሚመጻደቁ የአባታቸው የአብርሐምን ስራ ግን የማይሰሩ ክፍሎች ናቸው ዮሐ 8-39፡፡ ታዲያ ኒቆዲሞስ ምንም እንኳ ከፈሪሳዊያን ወገን ቢሆንም ራሱን ከዚህ ሕዝብ ለይቶ ክርስቶስን ፍለጋ በፍጹም ልቡ የመጣ ፈሪሳዊ ነው፡፡ ቀድሞ አባታችን አብርሀምን ከቤተሰብህ ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ ያለው አምላክ ኒቆዲሞስን ከፈሪሳዊያን ለይቶ ጠራው፡፡ ዘፍ 12
፪. ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ነው ዮሐ 3-1
ሮማውያን ሕዝቡን የሚያሥተዳድሩት ከላይ ያለውን ዋና ሥልጣን ተቆናጠው ታች ያለውን ሕዝብ ደግሞ ባህላቸውን በሚያውቅ ቋንቋቸውን በሚጠነቅቅ አይሁዳዊ ምስለኔ ነው፡፡ አውሮፓውያንም አፍሪካን ለመቀራመት የተጠቀሙበት ስልት ይህን ዓይነት ነበር፡፡ ኒቆዲሞስም ምንም እንኳ ፈሪሳዊ ቢሆን አለቃ እንዲሆን በሮማውያን የተሾመ ባለሥልጣን ነው፡፡
፫. ኒቆዲሞስ መምህረ እስራኤል ነው ዮሐ 3-10
ጌታ ምስጢረ ጥምቀትን በገለጸለት ጊዜ ሲደናገር አይቶ «አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን? » ብሎታል፡፡ ይህ የሚጠቁመን ኒቆዲሞስ አለቅነትን ከመምህርነት የያዘ በአይሁዳውያን የታፈረና የተከበረ ሰው እንደነበረ ነው፡፡ መምህር ቢሆንም የሚቀረኝ ያላወቅሁት ያልጠነቀቅሁት ብዙ ነገር አለ በማለት የመምህርነቱን ካባ አውልቆ የተማሪነትን ዳባ ለብሶ ከክርስቶስ ሊማር መጣ፡፡
፬. ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ነው ዮሐ 7-51
አንዳንዴ ሳያውቁ አወቅን ሳይማሩ እናስተምር የሚሉ ደፋር መምህራን አይጠፉም፡፡ ኒቆዲሞስ ግን ከዚህ በተለየ አለቅነትን ከመምህርነት መምህርነትን ከምሁርነት አስተባብሮ የያዘ ዕውቀትን ከትህትና ምሁርነትን ከደፋርነት አንድ አድርጎ የያዘ ሰው ነበር፡፡ የኦሪት ምሁር መሆኑን የሚጠቁመን ደግሞ ከካህናት አለቆች ጋር ያደረገውን ክርክር ባስታወስን ጊዜ ነው፡፡
ኒቆዲሞስ ምን አደረገ?
ለምስጢረ ጥምቀት መገለጥ ምክንያት ሆነ ዮሐ 3 1-21
የአይሁድ የፋሲካ በዓል እየቀረበ ሲመጣ ክርስቶስ ቀኑ እንደደረሰ ለሐዋርያቱ ተናግሮ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፡፡ እንደ ሰውነቱ ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይል ሕዝቡን ቀንና ሌሊት በትምህርትና በተዐምራት ያገለግል ነበር፡፡ በዚህ ሰዐት ነው ኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው፡፡ በፊቱ ቀርቦም «መምህር ሆይ » ብሎ የእርሱን አላዋቂነት የክርስቶስን ማእምረ ኅቡዐትነት (የተሰወረን አዋቂነት) መሰከረ፡፡ ጌታችንም አመጣጡ ከልብ መሆኑን አውቆ ምሥጢረ ጥምቀትን (ዳግም ውልደትን) ገለጸለት፡፡ ምስጢሩ የኦሪት ምሁር ለነበረው ኒቆዲሞስ ለጆሮ የከበደ ለመቀበል የሚቸግር ሆነበት፡፡ የከበደውን የሚያቀል የጠበበውን የሚያሰፋ አምላክ ምሥጢሩ ለኒቆዲሞስ እንደከበደው ስለተረዳ ቀለል አደረገለት፡፡ ዳግም ውልደት ከእናት ማኅፀን ሳይሆን ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ አብራራለት ፡፡
አዋቂ ነን የሚሉትን አሳፈራቸው ዮሐ 7-51
ወቅቱ የአይሁድ የፋሲካ በዓል የቀረበበት ጻፎችና የካህናት አለቆች ጌታን ለመያዝ፣ እንደሙሴም ህግ ሊያስፈርዱበት የቋመጡበት ጊዜ ነበር፡፡ የሙሴ ፈጣሪ መሆኑን መቸ አወቁና? የካህናት አለቆች ተሰብስበው ክርስቶስን ለመያዝ በሚመካከሩ ጊዜ ከሙሴ መጽሐፍ ሕግ ጠቅሶ ሊቃውንተ ኦሪትን አፍ ያስያዛቸው እሱ ነበር፡፡በዚህም የተነሳ ሳይስማሙ ወደየቤታቸው እንዲበታተኑ ምክንያት የሆነ ታላቅ ሰው ነው፡፡
ጌታን ለመገነዝ በቃ ዮሐ 19-38
ጌታችን በቀራንዮ አደባባይ ራሱን ለዓለሙ ቤዛ አድርጎ ሲሰጥ እስከ ሞት ከአንተ አንለይህም ያሉት ደቀ መዛሙርቱ ሲበታተኑ ፣ከዮሐንስ በቀር ፣በዘጠኝ ሰዐት ቀራንዮ የነበረ ኒቆዲሞስ ነበር፡፡ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ሆኖ የክርስቶስን ስጋ ከአለቆች ለምኖ፣ የገነዘ፣የክርስቶስን ክቡር ሥጋ ከርቤና የእሬት ቅልቅል ያርከፈከፈለት ወደ ሐዲስ መቃብር ያወረደውም ኒቆዲሞስ ነበር፡፡
ከኒቆዲሞስ ምን እንማር?
አትኅቶ ርእስ
በቅዱስ ወንጌል ላይ በተደጋጋሚ የምናገኘው የፈሪሳውያንን ግብዝነትና የጌታችንን ተግሳጽ ነው፡፡ ማቴ 9 10፣ ማቴ 23፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነን የፈሪሳዊውና የቀራጩ ጸሎት ምን ይመስል እንደነበር መመልከት ነው ሉቃ 18 9፡፡ ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፣ የአይሁድ አለቃ ፣መምህረ እስራኤል ፣ምሁረ ኦሪት ቢሆንም ራሱን ዝቅ አድርጎ ከጌታ እግር ስር ቁጭ አለ፡፡ ሕዝብን ከመምራትና ከማስተማር ይልቅ ቁጭ ብሎ መማር ምንኛ መታደል ነው! ጌታስ በትምህርቱ «ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርሷም አይወሰድባትም » ያለ ለዚህ አይደል ሉቃ 10 42፡፡ ብዙዎቻችን ባለን የኑሮ ደረጃ የዕውቀት ደረጃ የስልጣን ደረጃ ራሳችን ሰቅለን የመማር አቅም አጥተናል፡፡ ቁጭ ብሎ መማር ደረጃችንን የማይመጥን የሚመስለንስ ስንቶች እንሆን? አንድ ወቅት አባ መቃርስ ከህጻናት እንቆቅልሽ ለመማር ቁጭ እንዳሉ በእንቆቅልሹም ልባቸው ተነክቶ እያነቡ ወደ በዐታቸው መመለሳቸውን እያወቅን የመማር አቅም ያጣን ስንቶች እንሆን? ማን ያውቃል ከአንድ ሰአት ስብከት ውስጥ እግዚአብሔር ሊያስተመረን የፈለገ አንዲት ዐረፍተ ነገር ቢሆንስ? ትሑት የሚያሰኘው ሳያውቁ አላውቅም ማለት ሳይሆን እያወቁ አላውቅም ማለት ነው፡፡ ሳይማሩ ተምሬያለሁ ማለት ሳይሆን ተምረውም ልክ እንደ ኒቆዲሞስ ለመማር ራስን ዝቅ ማድረግ ነው፡፡
ጎደሎን ማወቅ
መምህርም ምሁርም ሆኖ ቁጭ ብሎ መማር ምን ረብ አለው? ይባል ይሆናል፡፡ ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት እንጅ ምሁረ ሐዲስ አይደ
ለም ኒቆዲሞስ መምህረ እስራኤል ዘስጋ እንጅ መምህረ እስራኤል ዘነፍስ አይደለም፡ ክርስትና አለቃና ባሪያን አንድ እንደምታደርግ አያውቅምና የጎደለውን ፍለጋ መጣ ገላ 3 26፡፡ ያለውን ሳይሆን ያጣውን የሞላለትን ሳይሆን የጎደለውን ፍለጋ መጣ፡፡ዕውቀት ብቻውን ምሉእ አያደርግም፡፡ አለቅነትም ቢሆን ገደብ አለው፡፡የሕይወቱን ክፍተት ሊሞላ የሚችል አንድ ክርስቶስ ብቻ ነውና ጎደሎነቱን አምኖ መጣ፡፡ የሚጎድለኝ ምንድን ነው? ብሎ እንደጠየቀው እንደዚያ ሰው ጎደሎን ማመን ምንኛ ታላቅ ነገር ነው ማቴ 18 21፡፡ በአብዛኞቻችን የሚታየውና ክርስትናችንን አገልግሎታችንን ቤተክርስትያናችንን እየተፈታተነ ያለ ችግር ጎደሎዎቻችንን አለማወቅና ምሉእ ነኝ ብሎ ማሰብ ነው፡፡ ምንም እንዳልሆኑ አውቆ ራስን ለክርስቶስ፣ ራስን ለመርዐተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አሳልፎ መስጠት ምንኛ መታደል ነው!
አልዕሎ ልቡና (ልቡናንን ከፍ ማድረግ)
ኒቆዲሞስ ይዞ የመጣው ስጋዊ ህዋሳቱን ነበር፡፡ጌታችን ግን አመጣጡ ለመልካም እንደሆነ አውቆ ለስጋዊ ዕውቀት እጅግ የሚከብደውን ምስጢረ ጥምቀትን ገለጸለት፡፡ መጀመሪያ ይህን ምስጢር ለመቀበል አልተቻለውም ነበር፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ምስጢሩን ፍንትው አድርጎ ሲያብራራለት ግን ልቡናው ይህን ምስጢር ለመቀበል ከፍ ከፍ አለ፡፡ ምስጢራትን ለመቀበል ልቦናን ከፍ ከፍ ማድረግ ይገባል፡፡የእምነታች መሰረት በስጋ ዓይን ማየት በስጋ ጆሮ መስማት በስጋ እጅ መዳሰስ ብቻ ከሆነ ልክ እንደ እንቦይ ካብ ሆነ ማለት ነው፡፡ ትንሽ ነፋስ ትንሽ ተፅዕኖ ሲያርፍበት መፈራረስ መናድ ይጀምራል፡፡ ኒቆዲሞስም ምስጢሩ መጀመሪያ ቢከብደውም ቅሉ በኋላ ላይ ልቦናውን ወደ ሰማያዊው ምስጢር ከፍ ስላደረገ ምስጢሩ ተገለጸለት፡፡ ቤተክርስቲያንን ሲፈታተኗትና እየተፈታተኗት ያሉ አካላት በሙሉ የስህተታቸው ምንጭ እንደ ግያዝ ከአካባቢያቸውና ከምናየው አካል (ቁሳዊ ዓለም) ውጭ መመልከት አለመቻል ነው 2ነገ 6- 17፡፡ ለዚህም ነው ካህኑ በስርዓተ ቅዳሴ ጊዜ የቁርባኑ ምስጢር እንዲገለጽልን «አልዕሉ አልባቢክሙ (ልቦናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ)» የሚሉን፡፡
የእውነት ምስክር (ስምዐ ጽድቅ) መሆን
ኒቆዲሞስ ያለፍርሐትና ያለ ሃፍረት በካህናቱ ፊት እውነትን መስክሯል፡፡እውነትንና ፀሐይን ፈርቶ የትም መድረስ አይቻልም፡፡ ካህናቱን መጽሐፍ ጠቅሶ እውነትን ተናግሮ አሳፍሯቸዋል፡፡ በመሪዎች ፊት በታላላቅ ሰዎች ፊት እውነትን መመስከር ክርስትናችን የሚያስገድደን ቁም ነገር ነው ሉቃ 12 8፡፡ ቤተክርስቲያን ሰማዕታት እያለች የምትዘክራቸው በሙሉ ለእውነት ብለው ራሳቸውን ለክርስቶስ አሳልፈው የሰጡ ቅዱሳንን ነው፡፡በፍርሐትና በሀፍረት በይሉኝታና በሀዘኔታ እውነትን አለመመስከር በክርስቶስ ፊት ያስጠይቃል እንጅ አያስመሰግንም ማቴ 10 32፡፡ «ለእውነት እንጅ በእውነት ላይ ምንም ማድረግ አንችልም» እንዳለ 2ቆር 13 8፡፡
ትግሃ ሌሊት
እንደ ሌሊት ለመንፈሳዊ ህሊና ለተመስጦ የሚመች ጊዜ የለም ፡፡ ቀን ለስጋ ሲራወጥ የነበረ አካልና መንፈስ ሌሊቱን ለነፍስ በምገዛት ስጋውን መጎሰም አለበት፡፡ ለዚህም ነው ቅድስት ቤተክርስቲያን ቀኑን በቅዳሴ ሌሊቱን ደግሞ በማኅሌት በሰዓታት በኪዳን እግዚአብሔርን ስታምሰግን የምታድረው፡፡ ቅዱስ ማር ይስሐቅ ሌሊትስ ጌታን ለማመስገን የተፈጠረ ድንቅ ጊዜ ነው ያለው፡፡ ጌታችንም ሐዋርያቱን ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ብሏቸዋል ማቴ 26፡፡ አሁንም ቤተክርስቲያን እንደ ኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ ለኪዳን ለማኅሌት ለጸሎት የሚመጣን ምዕመን ትፈልጋለች፡፡
እስከ መጨረሻ መጽናት
ጌታችንን በመዋዕለ ስብከቱ ብዙ ሺህ ሕዝብ ቢከተለውም እስከመስቀሉ አብረውት የነበሩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ የተወሰነው ሕዝብ ቀድሞም የተከተለው ለምግበ ስጋ ነበርና ቀራንዮ ላይ አልተገኘም፡፡ ቀራንዮ ላይ ምግበ ነፍስ እንጅ ምግበ ስጋ የለም፡፡ ሌሎችም በቤተሰብ በሀብት በፍርሀት ምክንያትነት መስቀሉ ስር አልተገኙም፡፡ ምንም እንኳ ኒቆዲሞስ በስድስት ሰዐት ባይገኝም የክርስቶስ ስጋ ከነፍሱ በምትለይበት ሰዐት ክርስቶስን ከመስቀል አውርዶ ለሐዲስ መቃብር ያበቃው እሱ ነበር፡፡ በዚህ የመከራ ሰዐት ከዮሐንስና ከእናቱ ከድንግል ማርያም ውጭ ማንም እንዳልነበረ መጻሕፍት ከገለጹልን በኋላ የምናገኛቸው የቁርጥ ቀን ልጆች ዮሴፍንና ኒቆዲሞስን ነው፡፡ ይህም ፈተናውን ሁሉ ተቋቁሞ እስከ መጨረሻው ለመጽናቱ ምስክር ነው፡፡ በክርስትና ሕይወታችንም የምናያቸው ነገሮች ከዚህ የተለዩ አይደሉም፡፡በምቹ ጊዜ የምናገለግል ፈተና ሲመጣ ጨርቃችን(አገልግሎታችንን) ጥለን የምንሮጥ ማር 14-51 ሰበብ አስባብ ፈልገን የምናፈገፍግ ብዙዎች ነን፡፡ ዕውቀት ጣዖት ሆኖበት መሀል መንገድ የቀረው ሀብት ጣዖት ሆኖበት ሩጫ ያቋረጠውን ጊዜ ጣዖት ሆኖበት ቅዳሴ የሚቀረውን ቆጥረን እንጨርሰው ይሆን? ጌታ በትምህርቱ «ለዘአዝለፈ ትዕግስቶ ውእቱ ይድኅን -እስከ መጨረሻው የሚፀና እርሱ ይድናል » እንዳለ ማቴ 2413፡፡ ክርስትና ለጀመሩት ሳይሆን ለጨረሱት ለወጠኑት ሳይሆን ለፈጸሙት የድል አክሊል የምትሰጥ መንገድ እንጅ የመሮጫ መሙን ጠበበን ሩጫው ረዘመብን ለሚሉ ዴማሶች ቦታ የላትም፡፡2ጢሞ 4-9
በአጠቃላይ ከኒቆዲሞስ ህይወት ብዙ ቁምነገሮችን እንማራለን፡፡ የኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ መምጣት ለምስጢረ ጥምቀት ትምህርት መገለጥ ምክንያት እንደሆነ ሁሉ በቅዳሴው በኪዳኑ በሰዓታቱ በማኅሌቱ መገኘትና መሳተፍ ረቂቅ የሆነው ሰማያዊ ምሥጢር ፍንትው ብሎ አንዲገለጥልን በምሥጢራት በመሳተፍ ራስን ዝቅ በማድረግ ለታላቅ ክብር እንድንበቃ የእርሱ መልካም ፈቃድ ይሁንልን፡፡ አሜን 👉❤️
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ :-ማህበረ ቅዱሳን መካነ ድህር
ዓውደ ምህረት የእናንተ
አስተያየት ጥቆማና የከበረ ሀሳብዎን በዚህ ይስደዱልን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE
አልዕሎ ልቡና (ልቡናንን ከፍ ማድረግ)
ኒቆዲሞስ ይዞ የመጣው ስጋዊ ህዋሳቱን ነበር፡፡ጌታችን ግን አመጣጡ ለመልካም እንደሆነ አውቆ ለስጋዊ ዕውቀት እጅግ የሚከብደውን ምስጢረ ጥምቀትን ገለጸለት፡፡ መጀመሪያ ይህን ምስጢር ለመቀበል አልተቻለውም ነበር፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ምስጢሩን ፍንትው አድርጎ ሲያብራራለት ግን ልቡናው ይህን ምስጢር ለመቀበል ከፍ ከፍ አለ፡፡ ምስጢራትን ለመቀበል ልቦናን ከፍ ከፍ ማድረግ ይገባል፡፡የእምነታች መሰረት በስጋ ዓይን ማየት በስጋ ጆሮ መስማት በስጋ እጅ መዳሰስ ብቻ ከሆነ ልክ እንደ እንቦይ ካብ ሆነ ማለት ነው፡፡ ትንሽ ነፋስ ትንሽ ተፅዕኖ ሲያርፍበት መፈራረስ መናድ ይጀምራል፡፡ ኒቆዲሞስም ምስጢሩ መጀመሪያ ቢከብደውም ቅሉ በኋላ ላይ ልቦናውን ወደ ሰማያዊው ምስጢር ከፍ ስላደረገ ምስጢሩ ተገለጸለት፡፡ ቤተክርስቲያንን ሲፈታተኗትና እየተፈታተኗት ያሉ አካላት በሙሉ የስህተታቸው ምንጭ እንደ ግያዝ ከአካባቢያቸውና ከምናየው አካል (ቁሳዊ ዓለም) ውጭ መመልከት አለመቻል ነው 2ነገ 6- 17፡፡ ለዚህም ነው ካህኑ በስርዓተ ቅዳሴ ጊዜ የቁርባኑ ምስጢር እንዲገለጽልን «አልዕሉ አልባቢክሙ (ልቦናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ)» የሚሉን፡፡
የእውነት ምስክር (ስምዐ ጽድቅ) መሆን
ኒቆዲሞስ ያለፍርሐትና ያለ ሃፍረት በካህናቱ ፊት እውነትን መስክሯል፡፡እውነትንና ፀሐይን ፈርቶ የትም መድረስ አይቻልም፡፡ ካህናቱን መጽሐፍ ጠቅሶ እውነትን ተናግሮ አሳፍሯቸዋል፡፡ በመሪዎች ፊት በታላላቅ ሰዎች ፊት እውነትን መመስከር ክርስትናችን የሚያስገድደን ቁም ነገር ነው ሉቃ 12 8፡፡ ቤተክርስቲያን ሰማዕታት እያለች የምትዘክራቸው በሙሉ ለእውነት ብለው ራሳቸውን ለክርስቶስ አሳልፈው የሰጡ ቅዱሳንን ነው፡፡በፍርሐትና በሀፍረት በይሉኝታና በሀዘኔታ እውነትን አለመመስከር በክርስቶስ ፊት ያስጠይቃል እንጅ አያስመሰግንም ማቴ 10 32፡፡ «ለእውነት እንጅ በእውነት ላይ ምንም ማድረግ አንችልም» እንዳለ 2ቆር 13 8፡፡
ትግሃ ሌሊት
እንደ ሌሊት ለመንፈሳዊ ህሊና ለተመስጦ የሚመች ጊዜ የለም ፡፡ ቀን ለስጋ ሲራወጥ የነበረ አካልና መንፈስ ሌሊቱን ለነፍስ በምገዛት ስጋውን መጎሰም አለበት፡፡ ለዚህም ነው ቅድስት ቤተክርስቲያን ቀኑን በቅዳሴ ሌሊቱን ደግሞ በማኅሌት በሰዓታት በኪዳን እግዚአብሔርን ስታምሰግን የምታድረው፡፡ ቅዱስ ማር ይስሐቅ ሌሊትስ ጌታን ለማመስገን የተፈጠረ ድንቅ ጊዜ ነው ያለው፡፡ ጌታችንም ሐዋርያቱን ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ብሏቸዋል ማቴ 26፡፡ አሁንም ቤተክርስቲያን እንደ ኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ ለኪዳን ለማኅሌት ለጸሎት የሚመጣን ምዕመን ትፈልጋለች፡፡
እስከ መጨረሻ መጽናት
ጌታችንን በመዋዕለ ስብከቱ ብዙ ሺህ ሕዝብ ቢከተለውም እስከመስቀሉ አብረውት የነበሩ ጥቂቶች ናቸው፡፡ የተወሰነው ሕዝብ ቀድሞም የተከተለው ለምግበ ስጋ ነበርና ቀራንዮ ላይ አልተገኘም፡፡ ቀራንዮ ላይ ምግበ ነፍስ እንጅ ምግበ ስጋ የለም፡፡ ሌሎችም በቤተሰብ በሀብት በፍርሀት ምክንያትነት መስቀሉ ስር አልተገኙም፡፡ ምንም እንኳ ኒቆዲሞስ በስድስት ሰዐት ባይገኝም የክርስቶስ ስጋ ከነፍሱ በምትለይበት ሰዐት ክርስቶስን ከመስቀል አውርዶ ለሐዲስ መቃብር ያበቃው እሱ ነበር፡፡ በዚህ የመከራ ሰዐት ከዮሐንስና ከእናቱ ከድንግል ማርያም ውጭ ማንም እንዳልነበረ መጻሕፍት ከገለጹልን በኋላ የምናገኛቸው የቁርጥ ቀን ልጆች ዮሴፍንና ኒቆዲሞስን ነው፡፡ ይህም ፈተናውን ሁሉ ተቋቁሞ እስከ መጨረሻው ለመጽናቱ ምስክር ነው፡፡ በክርስትና ሕይወታችንም የምናያቸው ነገሮች ከዚህ የተለዩ አይደሉም፡፡በምቹ ጊዜ የምናገለግል ፈተና ሲመጣ ጨርቃችን(አገልግሎታችንን) ጥለን የምንሮጥ ማር 14-51 ሰበብ አስባብ ፈልገን የምናፈገፍግ ብዙዎች ነን፡፡ ዕውቀት ጣዖት ሆኖበት መሀል መንገድ የቀረው ሀብት ጣዖት ሆኖበት ሩጫ ያቋረጠውን ጊዜ ጣዖት ሆኖበት ቅዳሴ የሚቀረውን ቆጥረን እንጨርሰው ይሆን? ጌታ በትምህርቱ «ለዘአዝለፈ ትዕግስቶ ውእቱ ይድኅን -እስከ መጨረሻው የሚፀና እርሱ ይድናል » እንዳለ ማቴ 2413፡፡ ክርስትና ለጀመሩት ሳይሆን ለጨረሱት ለወጠኑት ሳይሆን ለፈጸሙት የድል አክሊል የምትሰጥ መንገድ እንጅ የመሮጫ መሙን ጠበበን ሩጫው ረዘመብን ለሚሉ ዴማሶች ቦታ የላትም፡፡2ጢሞ 4-9
በአጠቃላይ ከኒቆዲሞስ ህይወት ብዙ ቁምነገሮችን እንማራለን፡፡ የኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ መምጣት ለምስጢረ ጥምቀት ትምህርት መገለጥ ምክንያት እንደሆነ ሁሉ በቅዳሴው በኪዳኑ በሰዓታቱ በማኅሌቱ መገኘትና መሳተፍ ረቂቅ የሆነው ሰማያዊ ምሥጢር ፍንትው ብሎ አንዲገለጥልን በምሥጢራት በመሳተፍ ራስን ዝቅ በማድረግ ለታላቅ ክብር እንድንበቃ የእርሱ መልካም ፈቃድ ይሁንልን፡፡ አሜን 👉❤️
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ :-ማህበረ ቅዱሳን መካነ ድህር
ዓውደ ምህረት የእናንተ
አስተያየት ጥቆማና የከበረ ሀሳብዎን በዚህ ይስደዱልን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE
#እቡዘ_ልብ ለምን ሆንክ ?
_______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ግንቦት 11/2014ዓ.ም
_______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ግንቦት 11/2014ዓ.ም
#ኦርቶጵያ
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#Ethiopia | ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን ከኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያን ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነጥሎ ማየት ይከብዳል፡፡
ቤተክስርቲያኒቱ ለኢትዮጵያ ህልውና ዋጋ ብትከፍልም ለውለታዋ ጥርስ እንዲነከስባት ሆናለች፡፡
ለመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክስርቲያን በምን ምክንያት ጥርስ ተነከሰባት?
ውለታዋና በደሏስ ምንድነው?
ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጋር የነበራቸው ሙግት በአስደናቂ ሁኔታ በመጽሐፉ ውስጥ ተዳስሷል፡፡
በሙግቱ ማን ረትቶ ይሆን?
ላሊበላ ሦስት ቀናት ሞቶ የተገለጠለት አስገራሚ ምስጢርም ተካትቶበታል፡፡
ብዙም ያልተነገረለት ላሊበላ ሞቶ የተገለጠለት ምስጢር ምን ይሆን?
ታቦተ ፂዮንን በአይናቸው ያዩት አጼ ኢያሱን ጨምሮ የጥቂት ሰዎች ምስክርነት በሚገርም ሁኔታ በመጽሐፉ ላይ ሰፍሯል፡፡
ታቦተ ፂዮንን በአይናቸው ያዩ ሰዎች ምን ተናረው ይሆን?
ኦርቶጵያ መጽሐፍ የሚነግረን ብዙ አስገራሚ ታሪኮች አሉ፡፡
ሁሉም ሰው ሊያነበው፣ ብሎም ቅርስ ሊያደርገው የሚገባ ለትውልድ የሚተላለፍ መጽሐፍ።
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#Ethiopia | ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን ከኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያን ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነጥሎ ማየት ይከብዳል፡፡
ቤተክስርቲያኒቱ ለኢትዮጵያ ህልውና ዋጋ ብትከፍልም ለውለታዋ ጥርስ እንዲነከስባት ሆናለች፡፡
ለመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክስርቲያን በምን ምክንያት ጥርስ ተነከሰባት?
ውለታዋና በደሏስ ምንድነው?
ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጋር የነበራቸው ሙግት በአስደናቂ ሁኔታ በመጽሐፉ ውስጥ ተዳስሷል፡፡
በሙግቱ ማን ረትቶ ይሆን?
ላሊበላ ሦስት ቀናት ሞቶ የተገለጠለት አስገራሚ ምስጢርም ተካትቶበታል፡፡
ብዙም ያልተነገረለት ላሊበላ ሞቶ የተገለጠለት ምስጢር ምን ይሆን?
ታቦተ ፂዮንን በአይናቸው ያዩት አጼ ኢያሱን ጨምሮ የጥቂት ሰዎች ምስክርነት በሚገርም ሁኔታ በመጽሐፉ ላይ ሰፍሯል፡፡
ታቦተ ፂዮንን በአይናቸው ያዩ ሰዎች ምን ተናረው ይሆን?
ኦርቶጵያ መጽሐፍ የሚነግረን ብዙ አስገራሚ ታሪኮች አሉ፡፡
ሁሉም ሰው ሊያነበው፣ ብሎም ቅርስ ሊያደርገው የሚገባ ለትውልድ የሚተላለፍ መጽሐፍ።
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡
#ሱባዔ ነቢያት
እግዚአብሔር ለአዳም የገባውን ቃል ኪዳን መሠረት በማድረግ ቀደምት ነቢያት በተነሡበት ዘመን ቅደም ተከተል ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆንና ዳግም መምጣት ትንቢት ተናግረዋል፡፡ ሱባዔም ቆጥረዋል፡፡ ኢሳ.7.14፡፡ መዝ.49.3፡፡ ዘካ.13.6፤ ዘካ.14.1፡፡ የአንዱ ነቢይ ትንቢታዊ ንግግርና ሱባኤ በአነጋገርና በአቆጣጠር ከሌላኛው ነቢይ ጋር ይለያያል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ትንቢቱን ሲያናግር ምሳሌውን ሲያስመስል ጐዳናው ለየቅል በመሆኑ ነው፡፡ «ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጐዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናገረ፡፡» እንዲል፡፡ ዕብ.1.1፡፡ የአቆጣጠር ስልታ ቸውና የሱባዔ መንገዳቸው ቢለያይም ዓላማና ግባቸው ግን አንድ ነው፡፡
#ሱባዔ አዳም
አዳም ትንቢት በመናገርና ሱባዔ በመቁጠር የመጀመሪያውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ ምክንያቱም በገነት ሰባት ዓመት ከአንድ ወር ከዐሥራ ሰባት ቀን በተድላና በደስታ ከኖረ በኋላ ሕግ በማፍረሱና የፈጣሪውን ቃል በመጣሱ ያለምንም ትካዜና ጉስቁልና ከሚኖርበት ዔደን ገነት ተባርሯል፡፡ ዘፍ.3.24፡፡ እርሱም ፈጣሪው እንዲታረቀው፣ በዐይነ ምሕረት እንዲጐበኘው፣ ቅዝቃዜው ሰውነት ከሚቆራርጥ ባሕር ውስጥ በመቆም ለሠላሳ አምስት ቀን /አምስት ሱባዔ/ ሱባዔ ገብቷል፡፡ በባሕርዩ የሰውን ልጅ እንግልት የማይወድ ቸሩ ፈጣሪ የአዳምን ፈጽሞ መጸጸት ተመልክቶ «በኀሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእድኅክ ውስተ መርህብከ ወእቤዝወከ በመስቀልየ ወበሞትየኸ በአምስት ቀን ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ» ብሎ ተስፋውን ሰጠው፡፡ አዳም የተሰጠውን ተስፋ ይዞ በዓለመ ሥጋ ለዘጠኝ መቶ ሠላሳ አመት ከኖረ በኋላ መከራና ችግር ከበዛበት ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
በወንጀል ተከሶ በወኅኒ የተፈረደበት ሰው ከእስር የሚፈታበትን ዕለት በማውጣት በማውረድ ወራቱንና ዓመታቱን እንደሚቆጥር፣ አዳምም በሞት ቢለይም በሲኦል የነፍስ ቅጣት ካለበት ሥፍራ ይኖር ስለነበር የተሰጠውን ተስፋ በማሰብ ሱባዔውን እየቆጠረ የተናገረውን የማያስቀር የማያደርገውን የማይናገር ጌታየ «እነሆ አድንኀለሁ» ብሎ የገባልኝ ዘመን ተፈጸመ፤ ሰዓቱ አሁን ነው፤ እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ቸር አምላክ ሰው ኾኖ ሥጋ ለብሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ፡- «ተንሥኡ ለጸሎት ለጸሎት ተነሡ፤ ሰላም ለኩልክሙ፤ ሰላም ለእናንተ ይሁን» በማለት አዳምን ከነልጅ ልጆቹ ነጻ አውጥቶታል፡፡ አዳምን በመከተል ልጆቹም አበው ቅዱሳን ነቢያት ሱባዔ በመግባት የተስፋን ዘመን በመቁጠር በመልካም ግብር ተከትለውታል፡፡ በዚህም መሠረት በርካታ ነቢያት በተለያየ ስልት ሱባዔ ቆጥረዋል፤ እኛም ሱባዔ ከቆጠሩ ነቢያት የተወሰኑትን በዚህ ጽሑፍ እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡
#ሱባዔ ሔኖክ
ጻድቁ ሔኖክ፣ የያሬድ ልጅ ሲሆን፣ በትውልድ ከአዳም ሰባተኛ ነው፡፡ እርሱም በሕይወቱ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ቤት ንብረቱን በመተው በሱባዔና በትሕርምት እግዚአብሔርን አገልግሏል፡፡ ፍጹም አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ ሰው በመሆኑ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መልካም ግብር ተመስክ ሮለታል፡፡ «ሔኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡» ዘፍ.5.22፡፡ ይህም በመሆኑ እግዚአብሔር የሱባዔውን ዋጋ ቅዱስ መንፈሱን በረድኤት ስለ አሳደረበት ትንቢት ተናግሯል፤ ሱባዔ ቆጥሯል፡፡ በሰማይ ተሰውሮ ሳለ ስለ ቅዱሳን መላእክት፣ ስለ መሲሕ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ፀሐይና ጨረቃ አመላለስ /ዑደት/ የሚተርክ በስሙ የተሰየመውን መጽሐፍ ጽፏል፡፡ ዘፍ.5 21-24፡፡ ይሁዳ ቁ.14፡፡ ሔኖክ 1.9፡፡
ሱባዔ ሔኖክ የሚባለው ነቢዩ ሔኖክ በመስፈርት የቆጠረው ሱባዔ ነው፡፡ መስፈርቱ /ማባዣ ቁጥር/ 35 ሲሆን 35'19 ሲበዛ በውጤቱ 685 ዓመት ይሆናል፡፡ 685'12 ስናባዛው 7980 ይሆናል፡፡ ይኸውም ሐሳብ የሚያስረዳው ስለክርስቶስ ምጽአት ነው፡፡
ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን የደረስንበት ዘመን 7497 ይሆናል፡፡ ይህን ለማረጋገጥ በ5500 ዓመት ላይ 1997 ዓመትን መደመር ነው፡፡ በዚህን ጊዜ ከላይ ያስቀመጥነውን 7497 ዓመት ይሰጠናል፡፡ በነቢዩ ሔኖክ አቆጣጠር መሠረት ምጽአተ ክርስቶስ በ7980 ይሆናል፡፡ ከላይ ሔኖክ የቀመረውን ቁጥር ይዘን ከ7980 ዓመት ላይ አሁን ያለንበትን ዘመን /1997/ ስንቀንስ 483 ዓመት እናገኛለን፡፡ ስለዚህ በሔኖክ ሱባዔ መሠረት ምጽአተ ክርስቶስ ሊሆን 483 ዓመት ይቀራል፡፡
#ሱባዔ ዳዊት
ነቢዩ ዳዊት ከእስራኤል ነገሥታት ሁሉ ታላቅና ተወዳጅ ንጉሥ ነበር፡፡ ዘመነ መንግሥቱ 1011-971 ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደ ነበር ይታመናል፡፡ ነቢዩ ዳዊት ልበ አምላክ እንደ መሆኑ ትንቢት ተናግሯል፡፡ ሱባዔ ቆጥሯል፡፡ ይኽውም ቀመረ ዳዊት በመባል ይታወቃል፡፡ «እስመ ዐሠርቱ ምእት ዓመት በቅድሜከ፤ ከመ ዕለት እንተ ትማልም ኃለፈት፤ ሺ ዓመት በፊትህ እንዳለፈች እንደ ትላንት ቀን»፡፡ /መዝ.89.4/ የሚለውን መምህራን ሲቆጥሩት 1140 ዓመት ይሆናል፡፡ ይኸውም በጌታ ዘንድ 1140 ዓመት እንደ አንድ ቀን እንደሆነ ነቢዩ ዳዊት ተናግሯል፡፡ ይህም ለዳዊት ሱባዔ መቁጠሪያ /መሥፈሪያ/ ሆኖ አገልግሏል፤ 1140’7= 7980 ዓመት ይሆናል፡፡ ይህም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በ7980 ዓመት ክርስቶስ ዳግም እንደ ሚመጣ የሚያመለክት ነው፡፡
#ሱባዔ ዳንኤል
ነቢዩ ዳንኤል ምድቡ ከዐበይት ነቢያት ነው፡፡ እስራኤል ወደ ባቢሎን ሲማረኩ ተማርኮ ወደ ባቢሎን ወርዷል፡፡ እርሱም ስለ ክርስቶስ መምጣት ትንቢት ተናግሯል፤ ሱባዔም ቆጥሯል፡፡ «ሰብአ ሰንበታተ አድሞሙ ለሕዝብከ፤ ሰባ ሰንበት ወገኖችህን ቅጠራቸው፡፡» ይኸውም ክርስቶስ ከ490 ዓመት በኋላ ሰው መሆኑን የሚያመለክት ትንቢት ነው፡፡ እንዲሁም «እስከ ክርስቶስ ንጉሥ ትትሐነፅ መቅደስ ወእምዝ ትትመዘበር፤ እስከ ንጉሥ ክርስቶስ ድረስ መቅደስ ትታነፃለች በኋላም ትፈርሳለች» ሲል ተናግሯል፡፡
የአቆጣጠር ስልቱም በዓመት ሲሆን ይኸውም ሰባቱን ዓመት አንድ እያሉ መቁጠር ነው፡፡ ይኽውም ሱባዔ ሰንበት ይባላል፡፡ ዳንኤል ሱባዔ ከቆጠረበትና ትንቢት ከተናገረበት ጀምሮ ክርስቶስ እስከ ሚወለድ 490 ይሆናል፡፡ መስፈርቱ /ማባዣው/ ሰባት ስለሆነ 7’70 ስናባዛው 490 እናገኛለን፡፡ ይኸውም ነቢዩ ሱባዔ ከቆጠረና ትንቢት ከተናገረ ከ490 ዓመት በኋላ የክርስቶስን መወለድ ያመለክታል፡፡
በአጠቃላይ ከላይ የተመለከትናቸው ቅዱሳን ነቢያት አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረግ ሱባዔ ገብተው በትሕርምት በመኖራቸው ድንቅ የሆነውን የክርስቶስን ልደትና ዳግም ምጽአት ለመተንበይ ችለዋል፡፡ ሱባዔ መግባት የራቀን ለማቅረብ የረቀቀን ለማጉላት ብቃትን ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስገኝ መንፈሳዊ ጥበብ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡
**** ይቀጥላል*****
እግዚአብሔር ለአዳም የገባውን ቃል ኪዳን መሠረት በማድረግ ቀደምት ነቢያት በተነሡበት ዘመን ቅደም ተከተል ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆንና ዳግም መምጣት ትንቢት ተናግረዋል፡፡ ሱባዔም ቆጥረዋል፡፡ ኢሳ.7.14፡፡ መዝ.49.3፡፡ ዘካ.13.6፤ ዘካ.14.1፡፡ የአንዱ ነቢይ ትንቢታዊ ንግግርና ሱባኤ በአነጋገርና በአቆጣጠር ከሌላኛው ነቢይ ጋር ይለያያል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ትንቢቱን ሲያናግር ምሳሌውን ሲያስመስል ጐዳናው ለየቅል በመሆኑ ነው፡፡ «ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጐዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናገረ፡፡» እንዲል፡፡ ዕብ.1.1፡፡ የአቆጣጠር ስልታ ቸውና የሱባዔ መንገዳቸው ቢለያይም ዓላማና ግባቸው ግን አንድ ነው፡፡
#ሱባዔ አዳም
አዳም ትንቢት በመናገርና ሱባዔ በመቁጠር የመጀመሪያውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ ምክንያቱም በገነት ሰባት ዓመት ከአንድ ወር ከዐሥራ ሰባት ቀን በተድላና በደስታ ከኖረ በኋላ ሕግ በማፍረሱና የፈጣሪውን ቃል በመጣሱ ያለምንም ትካዜና ጉስቁልና ከሚኖርበት ዔደን ገነት ተባርሯል፡፡ ዘፍ.3.24፡፡ እርሱም ፈጣሪው እንዲታረቀው፣ በዐይነ ምሕረት እንዲጐበኘው፣ ቅዝቃዜው ሰውነት ከሚቆራርጥ ባሕር ውስጥ በመቆም ለሠላሳ አምስት ቀን /አምስት ሱባዔ/ ሱባዔ ገብቷል፡፡ በባሕርዩ የሰውን ልጅ እንግልት የማይወድ ቸሩ ፈጣሪ የአዳምን ፈጽሞ መጸጸት ተመልክቶ «በኀሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእድኅክ ውስተ መርህብከ ወእቤዝወከ በመስቀልየ ወበሞትየኸ በአምስት ቀን ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ» ብሎ ተስፋውን ሰጠው፡፡ አዳም የተሰጠውን ተስፋ ይዞ በዓለመ ሥጋ ለዘጠኝ መቶ ሠላሳ አመት ከኖረ በኋላ መከራና ችግር ከበዛበት ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
በወንጀል ተከሶ በወኅኒ የተፈረደበት ሰው ከእስር የሚፈታበትን ዕለት በማውጣት በማውረድ ወራቱንና ዓመታቱን እንደሚቆጥር፣ አዳምም በሞት ቢለይም በሲኦል የነፍስ ቅጣት ካለበት ሥፍራ ይኖር ስለነበር የተሰጠውን ተስፋ በማሰብ ሱባዔውን እየቆጠረ የተናገረውን የማያስቀር የማያደርገውን የማይናገር ጌታየ «እነሆ አድንኀለሁ» ብሎ የገባልኝ ዘመን ተፈጸመ፤ ሰዓቱ አሁን ነው፤ እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ቸር አምላክ ሰው ኾኖ ሥጋ ለብሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ፡- «ተንሥኡ ለጸሎት ለጸሎት ተነሡ፤ ሰላም ለኩልክሙ፤ ሰላም ለእናንተ ይሁን» በማለት አዳምን ከነልጅ ልጆቹ ነጻ አውጥቶታል፡፡ አዳምን በመከተል ልጆቹም አበው ቅዱሳን ነቢያት ሱባዔ በመግባት የተስፋን ዘመን በመቁጠር በመልካም ግብር ተከትለውታል፡፡ በዚህም መሠረት በርካታ ነቢያት በተለያየ ስልት ሱባዔ ቆጥረዋል፤ እኛም ሱባዔ ከቆጠሩ ነቢያት የተወሰኑትን በዚህ ጽሑፍ እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡
#ሱባዔ ሔኖክ
ጻድቁ ሔኖክ፣ የያሬድ ልጅ ሲሆን፣ በትውልድ ከአዳም ሰባተኛ ነው፡፡ እርሱም በሕይወቱ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ቤት ንብረቱን በመተው በሱባዔና በትሕርምት እግዚአብሔርን አገልግሏል፡፡ ፍጹም አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ ሰው በመሆኑ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መልካም ግብር ተመስክ ሮለታል፡፡ «ሔኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡» ዘፍ.5.22፡፡ ይህም በመሆኑ እግዚአብሔር የሱባዔውን ዋጋ ቅዱስ መንፈሱን በረድኤት ስለ አሳደረበት ትንቢት ተናግሯል፤ ሱባዔ ቆጥሯል፡፡ በሰማይ ተሰውሮ ሳለ ስለ ቅዱሳን መላእክት፣ ስለ መሲሕ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ፀሐይና ጨረቃ አመላለስ /ዑደት/ የሚተርክ በስሙ የተሰየመውን መጽሐፍ ጽፏል፡፡ ዘፍ.5 21-24፡፡ ይሁዳ ቁ.14፡፡ ሔኖክ 1.9፡፡
ሱባዔ ሔኖክ የሚባለው ነቢዩ ሔኖክ በመስፈርት የቆጠረው ሱባዔ ነው፡፡ መስፈርቱ /ማባዣ ቁጥር/ 35 ሲሆን 35'19 ሲበዛ በውጤቱ 685 ዓመት ይሆናል፡፡ 685'12 ስናባዛው 7980 ይሆናል፡፡ ይኸውም ሐሳብ የሚያስረዳው ስለክርስቶስ ምጽአት ነው፡፡
ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን የደረስንበት ዘመን 7497 ይሆናል፡፡ ይህን ለማረጋገጥ በ5500 ዓመት ላይ 1997 ዓመትን መደመር ነው፡፡ በዚህን ጊዜ ከላይ ያስቀመጥነውን 7497 ዓመት ይሰጠናል፡፡ በነቢዩ ሔኖክ አቆጣጠር መሠረት ምጽአተ ክርስቶስ በ7980 ይሆናል፡፡ ከላይ ሔኖክ የቀመረውን ቁጥር ይዘን ከ7980 ዓመት ላይ አሁን ያለንበትን ዘመን /1997/ ስንቀንስ 483 ዓመት እናገኛለን፡፡ ስለዚህ በሔኖክ ሱባዔ መሠረት ምጽአተ ክርስቶስ ሊሆን 483 ዓመት ይቀራል፡፡
#ሱባዔ ዳዊት
ነቢዩ ዳዊት ከእስራኤል ነገሥታት ሁሉ ታላቅና ተወዳጅ ንጉሥ ነበር፡፡ ዘመነ መንግሥቱ 1011-971 ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደ ነበር ይታመናል፡፡ ነቢዩ ዳዊት ልበ አምላክ እንደ መሆኑ ትንቢት ተናግሯል፡፡ ሱባዔ ቆጥሯል፡፡ ይኽውም ቀመረ ዳዊት በመባል ይታወቃል፡፡ «እስመ ዐሠርቱ ምእት ዓመት በቅድሜከ፤ ከመ ዕለት እንተ ትማልም ኃለፈት፤ ሺ ዓመት በፊትህ እንዳለፈች እንደ ትላንት ቀን»፡፡ /መዝ.89.4/ የሚለውን መምህራን ሲቆጥሩት 1140 ዓመት ይሆናል፡፡ ይኸውም በጌታ ዘንድ 1140 ዓመት እንደ አንድ ቀን እንደሆነ ነቢዩ ዳዊት ተናግሯል፡፡ ይህም ለዳዊት ሱባዔ መቁጠሪያ /መሥፈሪያ/ ሆኖ አገልግሏል፤ 1140’7= 7980 ዓመት ይሆናል፡፡ ይህም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በ7980 ዓመት ክርስቶስ ዳግም እንደ ሚመጣ የሚያመለክት ነው፡፡
#ሱባዔ ዳንኤል
ነቢዩ ዳንኤል ምድቡ ከዐበይት ነቢያት ነው፡፡ እስራኤል ወደ ባቢሎን ሲማረኩ ተማርኮ ወደ ባቢሎን ወርዷል፡፡ እርሱም ስለ ክርስቶስ መምጣት ትንቢት ተናግሯል፤ ሱባዔም ቆጥሯል፡፡ «ሰብአ ሰንበታተ አድሞሙ ለሕዝብከ፤ ሰባ ሰንበት ወገኖችህን ቅጠራቸው፡፡» ይኸውም ክርስቶስ ከ490 ዓመት በኋላ ሰው መሆኑን የሚያመለክት ትንቢት ነው፡፡ እንዲሁም «እስከ ክርስቶስ ንጉሥ ትትሐነፅ መቅደስ ወእምዝ ትትመዘበር፤ እስከ ንጉሥ ክርስቶስ ድረስ መቅደስ ትታነፃለች በኋላም ትፈርሳለች» ሲል ተናግሯል፡፡
የአቆጣጠር ስልቱም በዓመት ሲሆን ይኸውም ሰባቱን ዓመት አንድ እያሉ መቁጠር ነው፡፡ ይኽውም ሱባዔ ሰንበት ይባላል፡፡ ዳንኤል ሱባዔ ከቆጠረበትና ትንቢት ከተናገረበት ጀምሮ ክርስቶስ እስከ ሚወለድ 490 ይሆናል፡፡ መስፈርቱ /ማባዣው/ ሰባት ስለሆነ 7’70 ስናባዛው 490 እናገኛለን፡፡ ይኸውም ነቢዩ ሱባዔ ከቆጠረና ትንቢት ከተናገረ ከ490 ዓመት በኋላ የክርስቶስን መወለድ ያመለክታል፡፡
በአጠቃላይ ከላይ የተመለከትናቸው ቅዱሳን ነቢያት አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረግ ሱባዔ ገብተው በትሕርምት በመኖራቸው ድንቅ የሆነውን የክርስቶስን ልደትና ዳግም ምጽአት ለመተንበይ ችለዋል፡፡ ሱባዔ መግባት የራቀን ለማቅረብ የረቀቀን ለማጉላት ብቃትን ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስገኝ መንፈሳዊ ጥበብ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡
**** ይቀጥላል*****
#በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ ሉቃ ፩÷፲፱
ቅዱስ ገብርኤል በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ዘንድ ከፍ ያለ መወደድ ያለው መልአክ ነው::ኦርቶዶክሳውያን የክርስቶስ የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን አብዝተን የምንወድበት ብዙ ምክንያቶች አሉን
፩. ቤተሰብኡን የሚጠላ ማን አለ ?
ክርስቲያኖች ከቅዱሳን መላእክት ጋር የአንድ ቤተሰብእ ሀገር አባላት አካላት ነን:: በሐዋ ፱÷፲፭ መምህረ አሕዛብ ብርሃነ ዓለም ተብሎ የተመሠከረለት ቅዱስ ጳውሎስ "እናንተ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና (ባለሀገሮችና) ቤተሰቦች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" እንዳለ ኤፌ ፪:፲፱:: ሐዋርያው በዚህ ክፍል ቅዱሳን ከተባሉ መላእክት ጋር ቤተሰብእ እንደሆንን ነገረን ሀገራችንም አንድ መሆኑን ሲመሠክር "ከእነርሱ ጋር ባለሀገሮች ናችሁ " አለን:: ሀገራችን የት ነው ? ብለን ብንጠይቅም ራሱ በፊልጵዩስ መልእክቱ "ሀገራችን በሰማይ ነው" ብሎናል ፊልጵ ፫፥፲፰-፲፱ ::የመላእክት ሀገር መንግሥተ ሰማይ እንደሆነ የእኛም ሀገር በሰማይ ነው::ሐዋርያው "እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" ያለው ቅዱስ ጴጥሮስ "እንግዶችና መጻተኞች ናችሁ" ፩ጴጥ ፪:፲፩ ብሎ በዚህ ኃላፊ ዓለም እንግዶች መሆናችንን የገለጠበትን የዚህ ዓለም እንግዳነታችንንና መጻተኛነታችንን ሳይሆን በሰማይ መንግሥት እንግዶች አለመሆናችንን ለመግለጥ ነው:: ይህ ዓለም ቢበዛ 70 ቢበረታም 80 ዘመን ብቻ የምንኖርበት ጊዜያዊ መኖሪያችን ነው መዝ 89÷10 ::ቅዱሳን መላእክት ቤተሰቦቻችን (እንደ ወንድም አባት እናት እህት) ስለሆኑ በአንዳችን የልብ ንስሐና መመለስ እንኳን ተደስተው በሰማይ ሀሴትን ያደርጋሉ ይዘምራሉ ያሸበሽባሉም :: ይህም የጌታችን በሥጋዌው ወራት ምሥክርነት ነበር ሉቃ ፲፭:፲::ቅዱሳን መላእክት ከምእመናን የማይለዩ እንደ እውነተኛ ወንድም አሳቢ እንደ አባት ጠባቂና ከክፉ የሚያድኑ አገልጋዮችም ናቸው:: መዝ 90÷11 ዳን 4÷12 የሐዋ 12÷5 የሐዋ 27÷23
2. ቅዱስ ገብርኤል መምህራችንም ነው
ቅዱስ ገብርኤል በቅዱሳት መጻሕፍት ከተገለጡልን ሥራዎቹ አንዱ የቅዱሳን ነቢያት እንዲሁም ምእመናን አስተማሪ መካሪ ጥበብ ገላጭ መሆኑ ነው :: እስከ ምጽአተ ክርስቶስ ሊሆን ያለውን ነገር በምልአት በስፋት የተናገረ ነቢዩ ዳንኤል "ገብርኤል ወደ እኔ እየበረረ መጣ በማታም በመሥዋእት ጊዜ ተናገረኝ አስተማረኝም እንዲህም አለኝ ዳንኤል ሆይ ጥበብና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ" ዳን 9:22 እንዳለ :: ቅዱስ ገብርኤል ምሥጢርን ጥበብን የመግለጥ ጸጋ ሀብት እንደተሰጠው ትመለከታላችሁን ? ዛሬ ላለን ምእመናን የክርስቶስ እናቱ እመቤታችንን "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ" እያልን እናመሰግናት ዘንድ ያስተማረን እርሱ አይደለምን ? ሉቃ 1:26-40 :: "በገብርኤል ሰላምታ ሰላም እንልሻለን" ማለታችንም ለዚሁ ነው::
3 . አረጋጊ አጽናኝ ፍርሃትንም የሚያርቅ መልአክ ነው
አንዱ የቅዱስ ገብርኤል ሥራ ፍርሃትን ማራቅ የታወኩትንም ማረጋጋት ነው :: ስለሆነም ወደ ሰዎች በመጣ ጊዜ "አትፍሩ" እያለ ያረጋጋቸዋል :: እንኮዋ በዚህ ዓለም ሀሳብና የሥጋ ነገር የታወክነውን ቀርቶ መንፈሳዊውን ሰው ነቢዩ ዳንኤልን "አትፍራ" ብሎ ፍርሃትን አርቆለታል ዳን 8:15 ; 10:12 :: የአምላክ እናት ድንግል ማርያምንም ሲያበሥራት "ማርያም ሆይ አትፍሪ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋን አግኝተሻልና" ሉቃ 1:29-40 እያለ ነበር ::
4 . ስለ ምእመናን በእግዚአብሔር ፊት በባለሟልነት የሚቆም (የሚለምን የሚማልድ) መልአክ ነው "እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ" እንዳለ ሉቃ 1:19
5 . ደጋግ ሰዎችን ለንስሐ እንዲበቁ ከስህተታቸው እንዲታረሙ እንደ አባት የሚቀጣ መልአክ ነው :: ካህኑ ዘካርያስን ዲዳ እንዲሆን እንደቀጣውና ልጁ በተወለደ ጊዜም አንደበቱ እንደሚፈታለት እንደነገረው መጽሐፍ ይነግረናል ሉቃ 1:19-25 :: "ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት በፊቱም ተጠንቀቁ" ተብሎም ከኃጢአታቸው የማይመለሱትን እንደሚቀጣ ተነግሮናል ዘጸ 23:20
6 . በእባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው ተብሎም ተነግሮናል ሔኖክ 6:7-8 :: እንግዲህ ምን እንላለን ? የመላእክት አለቃ የአብሣሬ ትስብእት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃ አይለየን አሜን!!
#ቢትወደድ ወርቁ
የካቲት 18 ቀን 2011 ዓ ም
ድጋሚ የተለጠፈ
ቅዱስ ገብርኤል በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ዘንድ ከፍ ያለ መወደድ ያለው መልአክ ነው::ኦርቶዶክሳውያን የክርስቶስ የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን አብዝተን የምንወድበት ብዙ ምክንያቶች አሉን
፩. ቤተሰብኡን የሚጠላ ማን አለ ?
ክርስቲያኖች ከቅዱሳን መላእክት ጋር የአንድ ቤተሰብእ ሀገር አባላት አካላት ነን:: በሐዋ ፱÷፲፭ መምህረ አሕዛብ ብርሃነ ዓለም ተብሎ የተመሠከረለት ቅዱስ ጳውሎስ "እናንተ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና (ባለሀገሮችና) ቤተሰቦች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" እንዳለ ኤፌ ፪:፲፱:: ሐዋርያው በዚህ ክፍል ቅዱሳን ከተባሉ መላእክት ጋር ቤተሰብእ እንደሆንን ነገረን ሀገራችንም አንድ መሆኑን ሲመሠክር "ከእነርሱ ጋር ባለሀገሮች ናችሁ " አለን:: ሀገራችን የት ነው ? ብለን ብንጠይቅም ራሱ በፊልጵዩስ መልእክቱ "ሀገራችን በሰማይ ነው" ብሎናል ፊልጵ ፫፥፲፰-፲፱ ::የመላእክት ሀገር መንግሥተ ሰማይ እንደሆነ የእኛም ሀገር በሰማይ ነው::ሐዋርያው "እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" ያለው ቅዱስ ጴጥሮስ "እንግዶችና መጻተኞች ናችሁ" ፩ጴጥ ፪:፲፩ ብሎ በዚህ ኃላፊ ዓለም እንግዶች መሆናችንን የገለጠበትን የዚህ ዓለም እንግዳነታችንንና መጻተኛነታችንን ሳይሆን በሰማይ መንግሥት እንግዶች አለመሆናችንን ለመግለጥ ነው:: ይህ ዓለም ቢበዛ 70 ቢበረታም 80 ዘመን ብቻ የምንኖርበት ጊዜያዊ መኖሪያችን ነው መዝ 89÷10 ::ቅዱሳን መላእክት ቤተሰቦቻችን (እንደ ወንድም አባት እናት እህት) ስለሆኑ በአንዳችን የልብ ንስሐና መመለስ እንኳን ተደስተው በሰማይ ሀሴትን ያደርጋሉ ይዘምራሉ ያሸበሽባሉም :: ይህም የጌታችን በሥጋዌው ወራት ምሥክርነት ነበር ሉቃ ፲፭:፲::ቅዱሳን መላእክት ከምእመናን የማይለዩ እንደ እውነተኛ ወንድም አሳቢ እንደ አባት ጠባቂና ከክፉ የሚያድኑ አገልጋዮችም ናቸው:: መዝ 90÷11 ዳን 4÷12 የሐዋ 12÷5 የሐዋ 27÷23
2. ቅዱስ ገብርኤል መምህራችንም ነው
ቅዱስ ገብርኤል በቅዱሳት መጻሕፍት ከተገለጡልን ሥራዎቹ አንዱ የቅዱሳን ነቢያት እንዲሁም ምእመናን አስተማሪ መካሪ ጥበብ ገላጭ መሆኑ ነው :: እስከ ምጽአተ ክርስቶስ ሊሆን ያለውን ነገር በምልአት በስፋት የተናገረ ነቢዩ ዳንኤል "ገብርኤል ወደ እኔ እየበረረ መጣ በማታም በመሥዋእት ጊዜ ተናገረኝ አስተማረኝም እንዲህም አለኝ ዳንኤል ሆይ ጥበብና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ" ዳን 9:22 እንዳለ :: ቅዱስ ገብርኤል ምሥጢርን ጥበብን የመግለጥ ጸጋ ሀብት እንደተሰጠው ትመለከታላችሁን ? ዛሬ ላለን ምእመናን የክርስቶስ እናቱ እመቤታችንን "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ" እያልን እናመሰግናት ዘንድ ያስተማረን እርሱ አይደለምን ? ሉቃ 1:26-40 :: "በገብርኤል ሰላምታ ሰላም እንልሻለን" ማለታችንም ለዚሁ ነው::
3 . አረጋጊ አጽናኝ ፍርሃትንም የሚያርቅ መልአክ ነው
አንዱ የቅዱስ ገብርኤል ሥራ ፍርሃትን ማራቅ የታወኩትንም ማረጋጋት ነው :: ስለሆነም ወደ ሰዎች በመጣ ጊዜ "አትፍሩ" እያለ ያረጋጋቸዋል :: እንኮዋ በዚህ ዓለም ሀሳብና የሥጋ ነገር የታወክነውን ቀርቶ መንፈሳዊውን ሰው ነቢዩ ዳንኤልን "አትፍራ" ብሎ ፍርሃትን አርቆለታል ዳን 8:15 ; 10:12 :: የአምላክ እናት ድንግል ማርያምንም ሲያበሥራት "ማርያም ሆይ አትፍሪ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋን አግኝተሻልና" ሉቃ 1:29-40 እያለ ነበር ::
4 . ስለ ምእመናን በእግዚአብሔር ፊት በባለሟልነት የሚቆም (የሚለምን የሚማልድ) መልአክ ነው "እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ" እንዳለ ሉቃ 1:19
5 . ደጋግ ሰዎችን ለንስሐ እንዲበቁ ከስህተታቸው እንዲታረሙ እንደ አባት የሚቀጣ መልአክ ነው :: ካህኑ ዘካርያስን ዲዳ እንዲሆን እንደቀጣውና ልጁ በተወለደ ጊዜም አንደበቱ እንደሚፈታለት እንደነገረው መጽሐፍ ይነግረናል ሉቃ 1:19-25 :: "ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት በፊቱም ተጠንቀቁ" ተብሎም ከኃጢአታቸው የማይመለሱትን እንደሚቀጣ ተነግሮናል ዘጸ 23:20
6 . በእባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው ተብሎም ተነግሮናል ሔኖክ 6:7-8 :: እንግዲህ ምን እንላለን ? የመላእክት አለቃ የአብሣሬ ትስብእት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃ አይለየን አሜን!!
#ቢትወደድ ወርቁ
የካቲት 18 ቀን 2011 ዓ ም
ድጋሚ የተለጠፈ
++ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግዶ በዓለም ላይ ያበራ ፀሐይ ++
#በመ/ር ዲ/ን #ቢትወደድ ወርቁ
የመልክዐ ተክለሃይማኖት ደራሲ በመልክዑ አርኬ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን "ቅዱስ አባት ሆይ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግደህ በዓለም የምታበራ ፀሐይ አንተ መዓዛህ የተወደደ ደብረ ከርቤን ነህ? ወይስ መሠወር የማይቻላት ደብረ ጽጌን ነህ? " በማለት ያመሰግናል፡፡ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት እንዲሁም በየዘመኑ የተነሡ መምህራን ዋና ተልዕኮ ጣዖት አምልኰን በቃለ ወንጌል ማስወገድ ነው፡፡ በሰዎች ዘንድ የሚታይ የሚዳሰስ ጣዖት አለ፡፡ እንዲሁም የማይታይ የማይዳሰስ ልብም የማይባል ረቂቅ ጣዖትም አለ፡፡
በኑሯችንና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ልብ ሳንላቸው ከእግዚአብሔር አስቀድመን ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች ሁሉ ሳናውቃቸው ጣዓታት እንደሆኑብን ልናስተውል ይገባናል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን በየዘመናቸው ከሰዎች ልቡና የሚታዩትንም ሆነ የማይታዩትን ጣዖታት በቃለ እግዚአብሔር ሲያጠፉ ኑረዋል፡፡ በዚህም በነቢዩ ዳንኤል የትንቢት መጽሐፍ "ጥበበኞቹ እንደሰማይ ፀዳል ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡" (ዳን 12፡4) ተብሎ ትንቢት ተነግሮላቸዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በገድላቸው እንደተጻፈልን በዘመናቸው ጣዖታትን አጥፍተዋል፡፡ በጣዖታቱ ላይ አድረው ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃቸውን ሰዎች ሲያታልሉ የኖሩትንም እኵያን አጋንንት በወንጌል ትምህርት ሲያሳፍሩና ሲበቀሏቸው ኑረዋል፡፡ በዚህም ለብዙዎች ብርሃን ሆነዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ምን ያህል ጣዖታትን እንዳጠፉ ስንቶችን ከጣዖት አምልኰ እንዳላቀቁና አጋንንትን በወንጌል ትምህርት እንዴት እንዳወጡ ለመረዳት ገድላቸውን በእምነት ሆኖ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ይኽን በሕሊናችን እንያዝና በዚህ ክፍል ጻድቁ የተገለጡበትን የምስጋና ቃል እንመልከት፡፡
+++ ተክለሃይማኖት ፀሐይ +++
በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ብርሃን ፀሐይ ተብሏል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "እግዚአብሔር ብሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው?" (መዝ 26፡1) በማለት ዘምሯል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡፡" (ዮሐ 8፡12) በማለት አስተምሯል፡፡ ጌታችን ጨለማ ያለው እርሱን አለማወቅ እንደፈቃዱ አለመመላለስ በኃጢአትና በክሕደት መኖርን ነው፡፡ (ሮሜ 13፡11-13) ብርሃን የተባለ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በእምነት ጸንተው በምግባር ቀንተው በትሩፋት አጊጠው እንደፈቃዱ የተመላለሱትንና ያገለገሉትን ወዳጆቹችንም ብርሃናት መሆናቸውን "እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ" በማለት መስክሮላቸዋል፡፡ ጌታችን ወዳጆቹ የዓለም ብርሃን የሚባሉት ብርሃን ሲሆኑ መሆኑን ሲናገርም "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ፡፡" (ማቴ 5፡14-16) ብሎዋል፡፡ በመነሻችን እንደተመለከትነው ጻድቁ ጨለማ ጣዖትን በማስወገድ ለዓለም ብርሃን ሆነዋል፡፡ ሰዎች ልቡናቸውን ከጣዖታት መልሰው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩትም ምክንያት ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ደራሲው የጌታችንን ቃል ይዞ ጻድቁን "ብርሃን ፀሐይ" በማለት አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን "መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡"(ያዕ 1፡17-18) በማለት የብርሃናት አባት ብሎ ጠርቶታል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ብርሃናት ብሎ የጠራቸው የብርሃን ክርስቶስ ልጆች ወዳጆቹ ቅዱሳን መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስወግዱ ኑፋቄንና ክሕደትንና እንዲያጠፋ የሰዎች ልጆችን ሕይወት በቅዱስ ቃሉ አማካኝነት እንዲያርሙና እንዲያስተካክሉ ወደ ዓለም የተላኩ ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱሳን ሐዋርያት በኋላ ዘመን የተነሡ ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ "እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ እግዚአብሔር አዞናል፡፡" በማለት በአንድ ቃል ተናግረዋል፡፡ (የሐዋ 13፡47) ቅዱሳን ጨለማ (ኃጢአት) በሞላው በሰው ልቡና ብርሃን ክርስቶስን የሚያበሩ ብርሃናት መሆናቸውን ትመለከታላችሁን? ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የንስሐ ስብከትን እየሰበከ የንስሐ ጥምቀትን እያጠመቀ በመንገድ የተመሰለ የሰውን ልቡና እያስተካከለ የተቀበለውን መጥምቁ ዮሐንስን "የሚነድና የሚያበራ ብርሃን" ብሎ ጠርቶታል፡፡ (ዮሐ 5፡35) መጥምቁ ዮሐንስ በጌታችን አንደበት የሚነድና የሚያበራ መብራት ተብሎ ስለምን ተመሰገነ? ወንጌልን በመስበኵ ጣዖታትን በማጥፋቱ ሰዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን በመመለሱ አይደለምን? ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፍቅር ነድደው ሰይጣንን ድል ነሥተዋል፡፡ በሕይወታቸው ክርስቶስን አብርተው በሰው ልቡና ነግሦ የነበረውን ጨለማ ኃጢአት ደርምሰዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጽድቅ (የእውነት ፀሐይ) እንደሆነ መንገዱን የተከተሉ ወዳጆቹም ፀሐይ ሆነው ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዘሪውን ምሳሌ ባስተማረበት ክፍል "በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡" (ማቴ 13፡44) በማለትም ጭምር አስተምሮዋል፡፡ እርሱ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሐይ ሲሆን ወዳጆቹ ደግሞ ጨረቃ ናቸው፡፡ ጨረቃ ብርሃንን የምታገኘው ከፀሐይ እንደሆነ ቅዱሳንም ጸጋን ክብርን ሥልጣንንም ያገኙት ከክርስቶስ ነውና ጌታችን "እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡" ብሎ አስተማረ፡፡ እንግዲህ በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን ተከትለው ጨለማ ጣዖትን ያጠፉ ደጋግ አባቶችና እናቶች ብርሃናት ፀሐይ ከዋክብት መባላቸውን ስንመለከት ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን ብርሃን ፀሐይ ብለን እንጠራቸዋለን እንጂ በጥርጥር መንፈስ ሆነን እንዴት? ለምን? ብለን አንጠይቅም፡፡
በመ/ር ዲ/ን #ቢትወደድ ወርቁ
ግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ ም
#በመ/ር ዲ/ን #ቢትወደድ ወርቁ
የመልክዐ ተክለሃይማኖት ደራሲ በመልክዑ አርኬ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን "ቅዱስ አባት ሆይ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግደህ በዓለም የምታበራ ፀሐይ አንተ መዓዛህ የተወደደ ደብረ ከርቤን ነህ? ወይስ መሠወር የማይቻላት ደብረ ጽጌን ነህ? " በማለት ያመሰግናል፡፡ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት እንዲሁም በየዘመኑ የተነሡ መምህራን ዋና ተልዕኮ ጣዖት አምልኰን በቃለ ወንጌል ማስወገድ ነው፡፡ በሰዎች ዘንድ የሚታይ የሚዳሰስ ጣዖት አለ፡፡ እንዲሁም የማይታይ የማይዳሰስ ልብም የማይባል ረቂቅ ጣዖትም አለ፡፡
በኑሯችንና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ልብ ሳንላቸው ከእግዚአብሔር አስቀድመን ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች ሁሉ ሳናውቃቸው ጣዓታት እንደሆኑብን ልናስተውል ይገባናል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን በየዘመናቸው ከሰዎች ልቡና የሚታዩትንም ሆነ የማይታዩትን ጣዖታት በቃለ እግዚአብሔር ሲያጠፉ ኑረዋል፡፡ በዚህም በነቢዩ ዳንኤል የትንቢት መጽሐፍ "ጥበበኞቹ እንደሰማይ ፀዳል ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡" (ዳን 12፡4) ተብሎ ትንቢት ተነግሮላቸዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በገድላቸው እንደተጻፈልን በዘመናቸው ጣዖታትን አጥፍተዋል፡፡ በጣዖታቱ ላይ አድረው ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃቸውን ሰዎች ሲያታልሉ የኖሩትንም እኵያን አጋንንት በወንጌል ትምህርት ሲያሳፍሩና ሲበቀሏቸው ኑረዋል፡፡ በዚህም ለብዙዎች ብርሃን ሆነዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ምን ያህል ጣዖታትን እንዳጠፉ ስንቶችን ከጣዖት አምልኰ እንዳላቀቁና አጋንንትን በወንጌል ትምህርት እንዴት እንዳወጡ ለመረዳት ገድላቸውን በእምነት ሆኖ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ይኽን በሕሊናችን እንያዝና በዚህ ክፍል ጻድቁ የተገለጡበትን የምስጋና ቃል እንመልከት፡፡
+++ ተክለሃይማኖት ፀሐይ +++
በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ብርሃን ፀሐይ ተብሏል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "እግዚአብሔር ብሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው?" (መዝ 26፡1) በማለት ዘምሯል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡፡" (ዮሐ 8፡12) በማለት አስተምሯል፡፡ ጌታችን ጨለማ ያለው እርሱን አለማወቅ እንደፈቃዱ አለመመላለስ በኃጢአትና በክሕደት መኖርን ነው፡፡ (ሮሜ 13፡11-13) ብርሃን የተባለ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በእምነት ጸንተው በምግባር ቀንተው በትሩፋት አጊጠው እንደፈቃዱ የተመላለሱትንና ያገለገሉትን ወዳጆቹችንም ብርሃናት መሆናቸውን "እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ" በማለት መስክሮላቸዋል፡፡ ጌታችን ወዳጆቹ የዓለም ብርሃን የሚባሉት ብርሃን ሲሆኑ መሆኑን ሲናገርም "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ፡፡" (ማቴ 5፡14-16) ብሎዋል፡፡ በመነሻችን እንደተመለከትነው ጻድቁ ጨለማ ጣዖትን በማስወገድ ለዓለም ብርሃን ሆነዋል፡፡ ሰዎች ልቡናቸውን ከጣዖታት መልሰው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩትም ምክንያት ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ደራሲው የጌታችንን ቃል ይዞ ጻድቁን "ብርሃን ፀሐይ" በማለት አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን "መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡"(ያዕ 1፡17-18) በማለት የብርሃናት አባት ብሎ ጠርቶታል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ብርሃናት ብሎ የጠራቸው የብርሃን ክርስቶስ ልጆች ወዳጆቹ ቅዱሳን መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስወግዱ ኑፋቄንና ክሕደትንና እንዲያጠፋ የሰዎች ልጆችን ሕይወት በቅዱስ ቃሉ አማካኝነት እንዲያርሙና እንዲያስተካክሉ ወደ ዓለም የተላኩ ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱሳን ሐዋርያት በኋላ ዘመን የተነሡ ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ "እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ እግዚአብሔር አዞናል፡፡" በማለት በአንድ ቃል ተናግረዋል፡፡ (የሐዋ 13፡47) ቅዱሳን ጨለማ (ኃጢአት) በሞላው በሰው ልቡና ብርሃን ክርስቶስን የሚያበሩ ብርሃናት መሆናቸውን ትመለከታላችሁን? ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የንስሐ ስብከትን እየሰበከ የንስሐ ጥምቀትን እያጠመቀ በመንገድ የተመሰለ የሰውን ልቡና እያስተካከለ የተቀበለውን መጥምቁ ዮሐንስን "የሚነድና የሚያበራ ብርሃን" ብሎ ጠርቶታል፡፡ (ዮሐ 5፡35) መጥምቁ ዮሐንስ በጌታችን አንደበት የሚነድና የሚያበራ መብራት ተብሎ ስለምን ተመሰገነ? ወንጌልን በመስበኵ ጣዖታትን በማጥፋቱ ሰዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን በመመለሱ አይደለምን? ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፍቅር ነድደው ሰይጣንን ድል ነሥተዋል፡፡ በሕይወታቸው ክርስቶስን አብርተው በሰው ልቡና ነግሦ የነበረውን ጨለማ ኃጢአት ደርምሰዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጽድቅ (የእውነት ፀሐይ) እንደሆነ መንገዱን የተከተሉ ወዳጆቹም ፀሐይ ሆነው ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዘሪውን ምሳሌ ባስተማረበት ክፍል "በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡" (ማቴ 13፡44) በማለትም ጭምር አስተምሮዋል፡፡ እርሱ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሐይ ሲሆን ወዳጆቹ ደግሞ ጨረቃ ናቸው፡፡ ጨረቃ ብርሃንን የምታገኘው ከፀሐይ እንደሆነ ቅዱሳንም ጸጋን ክብርን ሥልጣንንም ያገኙት ከክርስቶስ ነውና ጌታችን "እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡" ብሎ አስተማረ፡፡ እንግዲህ በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን ተከትለው ጨለማ ጣዖትን ያጠፉ ደጋግ አባቶችና እናቶች ብርሃናት ፀሐይ ከዋክብት መባላቸውን ስንመለከት ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን ብርሃን ፀሐይ ብለን እንጠራቸዋለን እንጂ በጥርጥር መንፈስ ሆነን እንዴት? ለምን? ብለን አንጠይቅም፡፡
በመ/ር ዲ/ን #ቢትወደድ ወርቁ
ግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (ተርቢኖስ ሰብስቤ)
አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል
በሰሙነ ሕማማት ጠቅለል ባለ መልኩ የምናስባቸው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት አሥራ ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል ይባላሉ፡፡ ለክርስቲያኖች እነዚህን ሕማማተ መስቀል ማወቅና ዘወትር ማሰብ ተገቢ በመሆኑ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
1. ተኰርዖተ ርእስ (ራስና በዘንግ መመታት)፤
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን በዘንግ መመታቱንና መቀጥቀጡን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተኰርዖት›› የሚለው ቃል ኩርዐ -
መታ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ርእስ ደግሞ ራስ ማለት ነው፡፡ አገረ ገዥው ጲላጦስ ‹‹እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ›› ብሎ እጁን ከታጠበ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ገርፎ ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች አሳልፎ ሰጥቶት ነበር፡፡ በአይሁድ ሕግ የተገረፈ አይሰቀልም፤ የሚሰቀል ደግሞ አይገረፍም፡፡ እርሱ ጲላጦስ ግን ከገረፈው በኋላ፣ የበደል በደል፣ እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው (ማቴ 27¸24፤ ማር 15¸15፤ ሉቃ 23¸25፤ ዮሐ 18¸39)፡፡
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተላልፎ ከተሰጠ በኋላ የእሾህ አክሊል ጐንጉነው ራሱ ላይ ደፍተውበታል፡፡ ራሱንም በዘንግ መትተውታል (ማር 15¸19)፡፡ የሰው ዘር ከአዳም ጀምሮ በጠላቱ በዲያብሎስ በተጐነጐነ የኃጢአት እሾህ ራሱ ተይዞ ነበርና ይህንኑ ለማስወገድ ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ የሆነ ዳግማዊ አዳም ክርስቶስ በጠላቶቹ በአይሁድ ተንኮል የተጐነጐነ አክሊለ ሦክ እንደ ዘውድ ደፋ፡፡ በሲኦል ወድቆ በዲያብሎስ ተረግጦ ራሱ የሚቀጠቀጠውን የሰውን ልጅ ለማዳን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ራሱን በመቃ ተቀጠቀጠ፡፡ ከራሱ ላይ በሚወርደው ደም ፊቱ ተሸፈነ፡፡
2. ተፀፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)፤
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እጃቸው በደም፣ ጣቶቻቸው በበደል በረከሰ በአይሁድ እጅ በጥፊ መመታቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተፀፍዖ›› የሚለው ቃል ፀፍዐ በጥፊ መታ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡
መልታሕት ደግሞ ፊት ጉንጭ ማለት ነው፡፡
ጌታችን ለሊቀ ካህናት ቀያፋ እውነትን መናገር እንደ ስድብ ተቆጥሮበት መላልሰው ፊቱን በጥፊ መትተውታል፡፡ ፊቱንም በጨርቅ ሸፍነው ‹‹ክርስቶስ ሆይ በጥፊ የመታህ ማነው? ትንቢት ተናገርልን›› እያሉ ዘብተውበታል፡፡ በጠላት ዲያብሎስ እጅ ወድቆ በነፍሱ ይቀለድበትና ይንገላታ የበረውን የሰውን ልጅ ለማዳን ብሎ በጠላቶቹ በአይሁድ እጅ ወድቆ ተጐሰመ፤ ተንገላታ፤ በጥፊም ተመታ (ማቴ 27¸27)፡፡ ጲላጦስ አሳልፎ ከሰጠው በኋላም አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ አኑረው ቀይ ልብስ አልብሰው ‹‹የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን›› እያሉ እየተሳለቁበት በጥፊ መትተውታል (ዮሐ 19¸2-4)፡፡ አላወቁትም እንጂ እርሱ በመንግሥቱ ሽረት፣ በባሕርዩ ሞት የሌለበት የዘለዓለም አምላክ ነው፡፡
3. ወሪቀ ምራቅ (ምራቅ መተፋት)፤
ርኩሳን አይሁድ በብርሃናዊው የክርስቶስ ፊት ላይ በሚያስጸይፍ ሁኔታ ምራቃቸውን እንደተፉበት የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ወሪቅ›› የሚለው ቃል
ወረቀ ካለው ግእዛዊ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ትርጉሙም እንትፍ አለ፣ (ተፋ) ማለት ነው፡፡ በነቢዩ በኢሳይያስ መጽሐፍ (ምዕራፍ 5ዐ¸6) ‹‹ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስኩም›› ተብሎ እንደተነገረ እየዘበቱበት ምራቃቸውን ተፉበት (ማቴ 27¸29-3ዐ፤ ማር 15¸19)፡፡ በኃጢአት የቆሸሸውን የሰውን ሕይወት ለማጥራት የመጣው ንጹሐ ባሕርይ አምላክ ተተፋበት፡፡ በሥራው ከገነት ተተፍቶ፤ ተንቆ፤ ተዋርዶ የነበረውን የሰውን ልጅ ለማዳን ኃጢአትን ይቅር የሚል እርሱ ጌታችን ያለ ኃጢአቱ ተተፋበት፤ ተናቀ፤ ተዋረደ፡፡ እንኳን በአምላክ ፊት በሰው ፊት እንኳን መትፋት እጅግ ያስነውራል፡፡ እርሱ ግን የኃጢአታችንን ነውር ከእኛ ሊያጠፋ ነውር የሆነውን ምራቅ ተቀበለ፡፡
4. ሰትየ ሐሞት ( መራራ ሐሞት መጠጣት)፤
ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል ሳለ ተጠማሁ ባለ ጊዜ መራራ ሐሞት መጠጣቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ሰተየ›› ማለት ጠጣ ማለት ነው፡፡ ሐሞት የሚለውም አሞት ተብሎ በቁሙ ይተረጐማል፡፡ በመዝሙር 68 ቁጥር 21 ላይ ‹‹ለመብሌ ሐሞት ሰጡኝ፣ ለጥማቴም ሆምጣጤ አጠጡኝ›› ብሎ ነቢዩ ዳዊትን ትንቢት ያናገረ የነቢያት አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ ‹‹ተጠማሁ›› ባለ ጊዜ ሆምጣጤ ተሞልቶበት ተቀምጦ ከነበረው ዕቃ ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው ወደ አፉ አቀረቡለት፡፡ ውኃ አጠጡኝ ቢላቸው በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፡፡ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም (ማቴ 27¸34)፡፡ ጌታችንም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ ‹‹ተፈጸመ›› አለ፡፡ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ (ማቴ 27¸48፤ ማር 15¸36፤ ሉቃ 23¸36፤ ዮሐ 19¸29)፡፡
ቢጠጡት ለዘለዓለም የማያስጠማ ውኃ የሚሰጥ አምላክ፤ የተጠማችውን ነፍስ የሚያረካ ጌታ፤ ለዘለዓለም የሚፈልቅ የሕይወት ውኃ ምንጭ የሚያድል ፈጣሪ በተጠማ ጊዜ የፈጠረውን ውኃ እንኳን የሚያጠጣው የሚያቀምሰውም አላገኘም (ኢሳ 55¸1)፡፡ አርባ ዓመት ሙሉ በቃዴስ በረሃ ኳትነው ለነበሩ አባቶቻቸው ከሰማይ መና አውርዶ የመገባቸው፤ ከአለት ላይ ውኃ አመንጭቶ ያጠጣቸው ክርስቶስ በተጠማ ጊዜ ቀዝቃዛ ውኃ ነፈጉት (ዘዳ 16¸1-2ዐ፤ 1ቆሮ 1ዐ¸3)፡፡ የዝናማት፤ የባሕርና የውቅያኖስ ጌታ በውኃ ጥም ተቃጠለ፡፡
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሲኦል በረሃ ወድቀው በሕይወት ውሃ ጥም የተቃጠሉትን ነፍሳት ለማርካት ሲል እርሱ ተጠማ፡፡ በኃጢአት ወድቀው፣ በበደል ረክሰው፣ በነፍሳቸው ተጐሳቁለው፣ መራራ መከራን የሚቀበሉትንና ምረረ ገሃነም አፉን ከፍቶ ሆዱን አስፍቶ የሚጠብቃቸውን ሁሉ ለማዳን መራራ ሐሞትን ቀመሰ፤ ሆምጣጣውንም ጠጣ፡፡ የመረረውን የሰው ልጆችን ሕይወት ለማጣፈጥ የመረረውን መጠጥ ተቀበለ፡፡
5. ተቀሥፎ ዘባን (ጀርባን መገረፍ)፤
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጀርባው እስኪላጥ ያለ ርኅራኄ የመገረፉን ነገር የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ተቀሥፎ›› የሚለው ቃል ቀሠፈ- ገረፈ ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹‹ ዘባን›› ደግሞ ጫንቃ፣ ትከሻ፣ ጀርባ ማለት ነው፡፡ ከላይ እንደተገለጠው የተገረፈ አይሰቀልም፡፡ የሚሰቀል ደግሞ አይገረፍም ነበር፡፡ ጲላጣስ ግን ኢየሱስ ክርስቶስን አስገረፈው፡፡ ከደሙ ንጹሕ ነኝ ብሎ ከታጠበ በኋላ ክርስቶስን ያለ ኃጢአቱ በመግረፍ ለአይሁድም አሳልፎ በመስጠት ‹‹ታጥቦ ጭቃ›› እንዲሉ የታጠበ እጁን መልሶ አቆሸሸው (ማቴ 27¸28፤ ማር 15¸15፤ ዮሐ19¸1)፡፡
መድኃኒታችን መንፀፈ ደይን ወድቆ በእግረ አጋንንት ተጠቅጥቆ በእሳት አለንጋ የሚገረፈውን የሰው ልጅ ለማዳን ሲል ጀርባውን ለግርፋት ሰጠ፡፡ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪቆጠር ተገረፈ፡፡ አይሁድ አገረ ገዥያቸው ጲላጣስ ላቀረበላቸው ምርጫ ይፈታላቸው ዘንድ ነፍሳትን ከሲኦል የሚያወጣውን ክርስቶስን ሳይሆን ራሱን እንኳን ከምድራዊ ወህኒ ማውጣት ያልቻለውን ወንበዴውን በርባንን መረጡ፡፡ መገረፍ ይገባው የነበረ በርባን ተለቀቀ፡፡ በነቢዩ በኢሳይያስ ‹‹ጀርባዬን ለገራፊዎች፣ ጉንጬንም ለጠጉር ነጪዎች ሰጠሁ›› (በኢሳ 5ዐ¸6) ተብሎ እንደተነገረ ጀርባውን ለገራፊዎች አሳልፎ ሰጠ፤ ጽሕሙንም ተነጨ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የሰው ልጅ ከሚያድነው አምላክ ይልቅ የሚገርፈውንና የሚዘርፈውን ወንበዴ መርጦ ስለተገኘ ነው፡፡
6. ተዐርቆተ ልብስ (ከልብስ መራቆት)፤
አምላካችን ኢየሱስ ክርስስቶስ ልብሱን መራቆቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ተዐርቆተ›› ማለት ታረዘ፤ ተራቆተ ማለት ነው፡፡ ፀሐይና ከዋክብትን ብርሃን አልብ
በሰሙነ ሕማማት ጠቅለል ባለ መልኩ የምናስባቸው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት አሥራ ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል ይባላሉ፡፡ ለክርስቲያኖች እነዚህን ሕማማተ መስቀል ማወቅና ዘወትር ማሰብ ተገቢ በመሆኑ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
1. ተኰርዖተ ርእስ (ራስና በዘንግ መመታት)፤
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን በዘንግ መመታቱንና መቀጥቀጡን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተኰርዖት›› የሚለው ቃል ኩርዐ -
መታ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ርእስ ደግሞ ራስ ማለት ነው፡፡ አገረ ገዥው ጲላጦስ ‹‹እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ›› ብሎ እጁን ከታጠበ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ገርፎ ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች አሳልፎ ሰጥቶት ነበር፡፡ በአይሁድ ሕግ የተገረፈ አይሰቀልም፤ የሚሰቀል ደግሞ አይገረፍም፡፡ እርሱ ጲላጦስ ግን ከገረፈው በኋላ፣ የበደል በደል፣ እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው (ማቴ 27¸24፤ ማር 15¸15፤ ሉቃ 23¸25፤ ዮሐ 18¸39)፡፡
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተላልፎ ከተሰጠ በኋላ የእሾህ አክሊል ጐንጉነው ራሱ ላይ ደፍተውበታል፡፡ ራሱንም በዘንግ መትተውታል (ማር 15¸19)፡፡ የሰው ዘር ከአዳም ጀምሮ በጠላቱ በዲያብሎስ በተጐነጐነ የኃጢአት እሾህ ራሱ ተይዞ ነበርና ይህንኑ ለማስወገድ ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ የሆነ ዳግማዊ አዳም ክርስቶስ በጠላቶቹ በአይሁድ ተንኮል የተጐነጐነ አክሊለ ሦክ እንደ ዘውድ ደፋ፡፡ በሲኦል ወድቆ በዲያብሎስ ተረግጦ ራሱ የሚቀጠቀጠውን የሰውን ልጅ ለማዳን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ራሱን በመቃ ተቀጠቀጠ፡፡ ከራሱ ላይ በሚወርደው ደም ፊቱ ተሸፈነ፡፡
2. ተፀፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)፤
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እጃቸው በደም፣ ጣቶቻቸው በበደል በረከሰ በአይሁድ እጅ በጥፊ መመታቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ተፀፍዖ›› የሚለው ቃል ፀፍዐ በጥፊ መታ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡
መልታሕት ደግሞ ፊት ጉንጭ ማለት ነው፡፡
ጌታችን ለሊቀ ካህናት ቀያፋ እውነትን መናገር እንደ ስድብ ተቆጥሮበት መላልሰው ፊቱን በጥፊ መትተውታል፡፡ ፊቱንም በጨርቅ ሸፍነው ‹‹ክርስቶስ ሆይ በጥፊ የመታህ ማነው? ትንቢት ተናገርልን›› እያሉ ዘብተውበታል፡፡ በጠላት ዲያብሎስ እጅ ወድቆ በነፍሱ ይቀለድበትና ይንገላታ የበረውን የሰውን ልጅ ለማዳን ብሎ በጠላቶቹ በአይሁድ እጅ ወድቆ ተጐሰመ፤ ተንገላታ፤ በጥፊም ተመታ (ማቴ 27¸27)፡፡ ጲላጦስ አሳልፎ ከሰጠው በኋላም አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ አኑረው ቀይ ልብስ አልብሰው ‹‹የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፣ ሰላም ለአንተ ይሁን›› እያሉ እየተሳለቁበት በጥፊ መትተውታል (ዮሐ 19¸2-4)፡፡ አላወቁትም እንጂ እርሱ በመንግሥቱ ሽረት፣ በባሕርዩ ሞት የሌለበት የዘለዓለም አምላክ ነው፡፡
3. ወሪቀ ምራቅ (ምራቅ መተፋት)፤
ርኩሳን አይሁድ በብርሃናዊው የክርስቶስ ፊት ላይ በሚያስጸይፍ ሁኔታ ምራቃቸውን እንደተፉበት የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ወሪቅ›› የሚለው ቃል
ወረቀ ካለው ግእዛዊ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ትርጉሙም እንትፍ አለ፣ (ተፋ) ማለት ነው፡፡ በነቢዩ በኢሳይያስ መጽሐፍ (ምዕራፍ 5ዐ¸6) ‹‹ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስኩም›› ተብሎ እንደተነገረ እየዘበቱበት ምራቃቸውን ተፉበት (ማቴ 27¸29-3ዐ፤ ማር 15¸19)፡፡ በኃጢአት የቆሸሸውን የሰውን ሕይወት ለማጥራት የመጣው ንጹሐ ባሕርይ አምላክ ተተፋበት፡፡ በሥራው ከገነት ተተፍቶ፤ ተንቆ፤ ተዋርዶ የነበረውን የሰውን ልጅ ለማዳን ኃጢአትን ይቅር የሚል እርሱ ጌታችን ያለ ኃጢአቱ ተተፋበት፤ ተናቀ፤ ተዋረደ፡፡ እንኳን በአምላክ ፊት በሰው ፊት እንኳን መትፋት እጅግ ያስነውራል፡፡ እርሱ ግን የኃጢአታችንን ነውር ከእኛ ሊያጠፋ ነውር የሆነውን ምራቅ ተቀበለ፡፡
4. ሰትየ ሐሞት ( መራራ ሐሞት መጠጣት)፤
ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል ሳለ ተጠማሁ ባለ ጊዜ መራራ ሐሞት መጠጣቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ሰተየ›› ማለት ጠጣ ማለት ነው፡፡ ሐሞት የሚለውም አሞት ተብሎ በቁሙ ይተረጐማል፡፡ በመዝሙር 68 ቁጥር 21 ላይ ‹‹ለመብሌ ሐሞት ሰጡኝ፣ ለጥማቴም ሆምጣጤ አጠጡኝ›› ብሎ ነቢዩ ዳዊትን ትንቢት ያናገረ የነቢያት አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ ‹‹ተጠማሁ›› ባለ ጊዜ ሆምጣጤ ተሞልቶበት ተቀምጦ ከነበረው ዕቃ ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው ወደ አፉ አቀረቡለት፡፡ ውኃ አጠጡኝ ቢላቸው በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፡፡ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም (ማቴ 27¸34)፡፡ ጌታችንም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ ‹‹ተፈጸመ›› አለ፡፡ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ (ማቴ 27¸48፤ ማር 15¸36፤ ሉቃ 23¸36፤ ዮሐ 19¸29)፡፡
ቢጠጡት ለዘለዓለም የማያስጠማ ውኃ የሚሰጥ አምላክ፤ የተጠማችውን ነፍስ የሚያረካ ጌታ፤ ለዘለዓለም የሚፈልቅ የሕይወት ውኃ ምንጭ የሚያድል ፈጣሪ በተጠማ ጊዜ የፈጠረውን ውኃ እንኳን የሚያጠጣው የሚያቀምሰውም አላገኘም (ኢሳ 55¸1)፡፡ አርባ ዓመት ሙሉ በቃዴስ በረሃ ኳትነው ለነበሩ አባቶቻቸው ከሰማይ መና አውርዶ የመገባቸው፤ ከአለት ላይ ውኃ አመንጭቶ ያጠጣቸው ክርስቶስ በተጠማ ጊዜ ቀዝቃዛ ውኃ ነፈጉት (ዘዳ 16¸1-2ዐ፤ 1ቆሮ 1ዐ¸3)፡፡ የዝናማት፤ የባሕርና የውቅያኖስ ጌታ በውኃ ጥም ተቃጠለ፡፡
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሲኦል በረሃ ወድቀው በሕይወት ውሃ ጥም የተቃጠሉትን ነፍሳት ለማርካት ሲል እርሱ ተጠማ፡፡ በኃጢአት ወድቀው፣ በበደል ረክሰው፣ በነፍሳቸው ተጐሳቁለው፣ መራራ መከራን የሚቀበሉትንና ምረረ ገሃነም አፉን ከፍቶ ሆዱን አስፍቶ የሚጠብቃቸውን ሁሉ ለማዳን መራራ ሐሞትን ቀመሰ፤ ሆምጣጣውንም ጠጣ፡፡ የመረረውን የሰው ልጆችን ሕይወት ለማጣፈጥ የመረረውን መጠጥ ተቀበለ፡፡
5. ተቀሥፎ ዘባን (ጀርባን መገረፍ)፤
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጀርባው እስኪላጥ ያለ ርኅራኄ የመገረፉን ነገር የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ተቀሥፎ›› የሚለው ቃል ቀሠፈ- ገረፈ ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹‹ ዘባን›› ደግሞ ጫንቃ፣ ትከሻ፣ ጀርባ ማለት ነው፡፡ ከላይ እንደተገለጠው የተገረፈ አይሰቀልም፡፡ የሚሰቀል ደግሞ አይገረፍም ነበር፡፡ ጲላጣስ ግን ኢየሱስ ክርስቶስን አስገረፈው፡፡ ከደሙ ንጹሕ ነኝ ብሎ ከታጠበ በኋላ ክርስቶስን ያለ ኃጢአቱ በመግረፍ ለአይሁድም አሳልፎ በመስጠት ‹‹ታጥቦ ጭቃ›› እንዲሉ የታጠበ እጁን መልሶ አቆሸሸው (ማቴ 27¸28፤ ማር 15¸15፤ ዮሐ19¸1)፡፡
መድኃኒታችን መንፀፈ ደይን ወድቆ በእግረ አጋንንት ተጠቅጥቆ በእሳት አለንጋ የሚገረፈውን የሰው ልጅ ለማዳን ሲል ጀርባውን ለግርፋት ሰጠ፡፡ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪቆጠር ተገረፈ፡፡ አይሁድ አገረ ገዥያቸው ጲላጣስ ላቀረበላቸው ምርጫ ይፈታላቸው ዘንድ ነፍሳትን ከሲኦል የሚያወጣውን ክርስቶስን ሳይሆን ራሱን እንኳን ከምድራዊ ወህኒ ማውጣት ያልቻለውን ወንበዴውን በርባንን መረጡ፡፡ መገረፍ ይገባው የነበረ በርባን ተለቀቀ፡፡ በነቢዩ በኢሳይያስ ‹‹ጀርባዬን ለገራፊዎች፣ ጉንጬንም ለጠጉር ነጪዎች ሰጠሁ›› (በኢሳ 5ዐ¸6) ተብሎ እንደተነገረ ጀርባውን ለገራፊዎች አሳልፎ ሰጠ፤ ጽሕሙንም ተነጨ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የሰው ልጅ ከሚያድነው አምላክ ይልቅ የሚገርፈውንና የሚዘርፈውን ወንበዴ መርጦ ስለተገኘ ነው፡፡
6. ተዐርቆተ ልብስ (ከልብስ መራቆት)፤
አምላካችን ኢየሱስ ክርስስቶስ ልብሱን መራቆቱን የሚገልጥ ነው፡፡ ‹‹ ተዐርቆተ›› ማለት ታረዘ፤ ተራቆተ ማለት ነው፡፡ ፀሐይና ከዋክብትን ብርሃን አልብ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝
“ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።” (ቅዱስ ጳውሎስ 2ኛ ቆሮ 9፥14)
--------------------------------
☞ ጻድቃን "አያማልዱም" የሚለውን ክርክር ተወውና የዘፍጥረትን መጽሐፍ ገልጠህ ፈጣሪህን ጠይቅ። ደጋጎች አይደለም ማልደው ለጥፋት በተዘጋጀች ከተማ ቢኖሩ እንኳን በከተማይቱ ስለመኖራቸው ብሎ ምሕረትን ያወርዳል።
☞ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን በኃጢአታቸው ምክንያት በእሳትና በዲን አቃጥሎ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ለወዳጁ ለአብርሃም "እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።" ካለ በኋላ "የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።" በማለት ነገረው። ይህ ነገር በእግዚአብሔር የተነገረው አብርሃም ደጋግሞ ምን ብሎ እንደጸለየ ታስተውላለህን? "አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?"….... ዳግመኛም "ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? "… ሦስተኛም "ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ?… አራተኛም፦ "እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ?" አለ።" ቅዱሱ ሰው አብርሃም በመጨረሻ የጸለየውን ጸሎት ልብ በል "በእነዚህ በሁለት ታላላቅ ከተሞች አሥር ጻድቃንን ብታገኝ አትምርምን?" የሚል ነው። እግዚአብሔር ምን ብሎ የመለሰ ይመስልሃል? "አምሳ ሳይሆን አሥርም ጻድቃን ባገኝ እምራለሁ!!!" (ዘፍ 18:17-25)
☞ እስቲ ልጠይቅህ ዛሬ ግብረ ሰዶማዊነት የት ደርሶዋል? በደጅህ አልደረሰምን? ለቀደሙት ስለገባው ቃልኪዳን ታግሦዋል እንጂ ሰዶማውያኑ በጠፉበት ግብረ ሰዶም ዓለሙ ይጠፋ እንደነበር የታወቀ ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።” (ምሳ 29፥2) ብሎ ለምን ተናገረ? በጻድቃን ብዛት ሀገር እንደምትድን በተረዳ ነገር ስላወቀ አይደለምን?
☞ የጻድቃን ልመና ብቻ ሳይሆን መኖር እንኳን ከጥፋት ይታደግሃል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።” ብሎ በምሥጢረ ምጽዓት ትምህርቱ እንዳስተማረ። (ማቴ 24፥22) እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በሚገባው ቃልኪዳን ቁጣውን በምሕረት በትእግሥት እንደሚለውጥ መከራውን እንደሚያሳጥር ይህ የጌታ ቃል ምስክር ነው። ዓለም አልገባውም እንጂ ሐሳዊ መሲሕ የሚሠለጥንባቸው እነዚያ አስጨናቂ ወራት እንኳን የሚያጥሩት በጽኑ እምነታቸው በቀና ምግባራቸው እርሱን ላስደሰቱት ወዳጆቹ በገባው ቃልኪዳን ነው።
መድኅን ዓለም ክርስቶስ ሕያዋን ቅዱሳኑን "ሙታን" ለሚሉ ሰዱቃውያን “እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።” ብሎ የተናገረውን ቃል ልብ በልና ሙታን እንደሌሉን አውቀህ ወደ ሕይወት የተሻገሩበትን የዕረፍታቸውን ቀን እንደ ዳዊት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” (መዝ116፥15) እያልክ እየዘመርክ አክብር። (ማቴ 22፥31-32)
እባክዎን ቃለ እግዚአብሔርን በማጋራት ለወዳጆችዎ ያድርሱ።
መምህር ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ ም
“ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።” (ቅዱስ ጳውሎስ 2ኛ ቆሮ 9፥14)
--------------------------------
☞ ጻድቃን "አያማልዱም" የሚለውን ክርክር ተወውና የዘፍጥረትን መጽሐፍ ገልጠህ ፈጣሪህን ጠይቅ። ደጋጎች አይደለም ማልደው ለጥፋት በተዘጋጀች ከተማ ቢኖሩ እንኳን በከተማይቱ ስለመኖራቸው ብሎ ምሕረትን ያወርዳል።
☞ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን በኃጢአታቸው ምክንያት በእሳትና በዲን አቃጥሎ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ለወዳጁ ለአብርሃም "እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።" ካለ በኋላ "የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።" በማለት ነገረው። ይህ ነገር በእግዚአብሔር የተነገረው አብርሃም ደጋግሞ ምን ብሎ እንደጸለየ ታስተውላለህን? "አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?"….... ዳግመኛም "ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? "… ሦስተኛም "ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ?… አራተኛም፦ "እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ?" አለ።" ቅዱሱ ሰው አብርሃም በመጨረሻ የጸለየውን ጸሎት ልብ በል "በእነዚህ በሁለት ታላላቅ ከተሞች አሥር ጻድቃንን ብታገኝ አትምርምን?" የሚል ነው። እግዚአብሔር ምን ብሎ የመለሰ ይመስልሃል? "አምሳ ሳይሆን አሥርም ጻድቃን ባገኝ እምራለሁ!!!" (ዘፍ 18:17-25)
☞ እስቲ ልጠይቅህ ዛሬ ግብረ ሰዶማዊነት የት ደርሶዋል? በደጅህ አልደረሰምን? ለቀደሙት ስለገባው ቃልኪዳን ታግሦዋል እንጂ ሰዶማውያኑ በጠፉበት ግብረ ሰዶም ዓለሙ ይጠፋ እንደነበር የታወቀ ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።” (ምሳ 29፥2) ብሎ ለምን ተናገረ? በጻድቃን ብዛት ሀገር እንደምትድን በተረዳ ነገር ስላወቀ አይደለምን?
☞ የጻድቃን ልመና ብቻ ሳይሆን መኖር እንኳን ከጥፋት ይታደግሃል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።” ብሎ በምሥጢረ ምጽዓት ትምህርቱ እንዳስተማረ። (ማቴ 24፥22) እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በሚገባው ቃልኪዳን ቁጣውን በምሕረት በትእግሥት እንደሚለውጥ መከራውን እንደሚያሳጥር ይህ የጌታ ቃል ምስክር ነው። ዓለም አልገባውም እንጂ ሐሳዊ መሲሕ የሚሠለጥንባቸው እነዚያ አስጨናቂ ወራት እንኳን የሚያጥሩት በጽኑ እምነታቸው በቀና ምግባራቸው እርሱን ላስደሰቱት ወዳጆቹ በገባው ቃልኪዳን ነው።
መድኅን ዓለም ክርስቶስ ሕያዋን ቅዱሳኑን "ሙታን" ለሚሉ ሰዱቃውያን “እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።” ብሎ የተናገረውን ቃል ልብ በልና ሙታን እንደሌሉን አውቀህ ወደ ሕይወት የተሻገሩበትን የዕረፍታቸውን ቀን እንደ ዳዊት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” (መዝ116፥15) እያልክ እየዘመርክ አክብር። (ማቴ 22፥31-32)
እባክዎን ቃለ እግዚአብሔርን በማጋራት ለወዳጆችዎ ያድርሱ።
መምህር ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
++ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ! ++ (መዝ 91:13)
☞ ሞተ ሥጋ ሳያገኛቸው እግዚአብሔር የሠወራቸው ብዙ ቅዱሳን አሉ። ከነዚህም መካከል ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱ ሰው ሄኖክ ሞት ሳያገኘው የተሰወረበትን ምክንያት ሲገልጽ “ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና።” ይላል አካሄድን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ እስከምን እንደሚያደርስ ተመልከት። (ዘፍ 5፥24) አካሄዳቸውን ከእርሱ ጋር ባደረጉ ወዳጆቹ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቸርነትና ከኃሊነት ተገልጦአልና ነቢዩ “እግዚአብሔር በጻድቁ እንደ ተገለጠ እወቁ።” በማለት ተናገረ። (መዝ 4፥3) በቅዱስ ሰው ሃይማኖት፣ በጎ ምግባርና መልካምነት ኢየሱስ ክርስቶስ ይገለጣል እንጂ አይሸፈንም።
☞ ከቅዱሱ ሰው ከሄኖክ ሌላ ቀናተኛው ነቢዩ ኤልያስም ሞት ሳያገኘው በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ተነጥቆዋል። ይህንም መጽሐፍ ሲነግረን “ሲሄዱም፦ እያዘገሙም ሲጫወቱ፥ እነሆ፥ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።” ከነቢዩ ጋር የነበረ ይህን የተመለከተና ለእግዚአብሔር የተገዛ ኤልሳዕም የነቢዩ ኤልያስ በረከት አድሮበት ተመሷል። (2ኛ ነገ 2፥11) መጽሐፍ በቅድስናቸው ለዚህ የበቁ እንዳሉ ሲነግርህ ዕፁብ ድንቅ ብለህ ማመን ማሰብም አንተንም ለክብር ያበቃሃል። ክርስቶስን በእነርሱ ሕይወት ትመለከተዋለህ እንጂ አይሠወርብህም። እንዲያም ባይሆን “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።” ባላለህም ነበር። (ዕብ 13፥7)
👇ይቀጥላል 👇
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
☞ ሞተ ሥጋ ሳያገኛቸው እግዚአብሔር የሠወራቸው ብዙ ቅዱሳን አሉ። ከነዚህም መካከል ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱ ሰው ሄኖክ ሞት ሳያገኘው የተሰወረበትን ምክንያት ሲገልጽ “ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና።” ይላል አካሄድን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ እስከምን እንደሚያደርስ ተመልከት። (ዘፍ 5፥24) አካሄዳቸውን ከእርሱ ጋር ባደረጉ ወዳጆቹ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ቸርነትና ከኃሊነት ተገልጦአልና ነቢዩ “እግዚአብሔር በጻድቁ እንደ ተገለጠ እወቁ።” በማለት ተናገረ። (መዝ 4፥3) በቅዱስ ሰው ሃይማኖት፣ በጎ ምግባርና መልካምነት ኢየሱስ ክርስቶስ ይገለጣል እንጂ አይሸፈንም።
☞ ከቅዱሱ ሰው ከሄኖክ ሌላ ቀናተኛው ነቢዩ ኤልያስም ሞት ሳያገኘው በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ተነጥቆዋል። ይህንም መጽሐፍ ሲነግረን “ሲሄዱም፦ እያዘገሙም ሲጫወቱ፥ እነሆ፥ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።” ከነቢዩ ጋር የነበረ ይህን የተመለከተና ለእግዚአብሔር የተገዛ ኤልሳዕም የነቢዩ ኤልያስ በረከት አድሮበት ተመሷል። (2ኛ ነገ 2፥11) መጽሐፍ በቅድስናቸው ለዚህ የበቁ እንዳሉ ሲነግርህ ዕፁብ ድንቅ ብለህ ማመን ማሰብም አንተንም ለክብር ያበቃሃል። ክርስቶስን በእነርሱ ሕይወት ትመለከተዋለህ እንጂ አይሠወርብህም። እንዲያም ባይሆን “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።” ባላለህም ነበር። (ዕብ 13፥7)
👇ይቀጥላል 👇
https://tttttt.me/zdk24_5_21_official
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
+ ጨለማን አስወግዶ በዓለም ላይ ያበራ ፀሐይ +
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።” አለ :- የጽድቅ ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ (ማቴ 13፥43)
የመልክዐ ተክለሃይማኖት ደራሲ በመልክዑ አርኬ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን "ቅዱስ አባት ሆይ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግደህ በዓለም የምታበራ ፀሐይ አንተ መዓዛህ የተወደደ ደብረ ከርቤን ነህ? ወይስ መሠወር የማይቻላት ደብረ ጽጌን ነህ? " በማለት ያመሰግናል፡፡ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት እንዲሁም በየዘመኑ የተነሡ መምህራን ዋና ተልዕኮ ጣዖት አምልኰን በቃለ ወንጌል ማስወገድ ነው፡፡ በሰዎች ዘንድ የሚታይ የሚዳሰስ ጣዖት አለ፡፡ እንዲሁም የማይታይ የማይዳሰስ ልብም የማይባል ረቂቅ ጣዖትም አለ፡፡
በኑሯችንና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ልብ ሳንላቸው ከእግዚአብሔር አስቀድመን ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች ሁሉ ሳናውቃቸው ጣዓታት እንደሆኑብን ልናስተውል ይገባናል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን በየዘመናቸው ከሰዎች ልቡና የሚታዩትንም ሆነ የማይታዩትን ጣዖታት በቃለ እግዚአብሔር ሲያጠፉ ኑረዋል፡፡ በዚህም በነቢዩ ዳንኤል የትንቢት መጽሐፍ "ጥበበኞቹ እንደሰማይ ፀዳል ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡" (ዳን 12፡4) ተብሎ ትንቢት ተነግሮላቸዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በገድላቸው እንደተጻፈልን በዘመናቸው ጣዖታትን አጥፍተዋል፡፡ በጣዖታቱ ላይ አድረው ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃቸውን ሰዎች ሲያታልሉ የኖሩትንም እኵያን አጋንንት በወንጌል ትምህርት ሲያሳፍሩና ሲበቀሏቸው ኑረዋል፡፡ በዚህም ለብዙዎች ብርሃን ሆነዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ምን ያህል ጣዖታትን እንዳጠፉ ስንቶችን ከጣዖት አምልኰ እንዳላቀቁና አጋንንትን በወንጌል ትምህርት እንዴት እንዳወጡ ለመረዳት ገድላቸውን በእምነት ሆኖ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ይኽን በሕሊናችን እንያዝና በዚህ ክፍል ጻድቁ የተገለጡበትን የምስጋና ቃል እንመልከት፡፡
+++ ተክለሃይማኖት ፀሐይ +++
በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ብርሃን ፀሐይ ተብሏል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "እግዚአብሔር ብሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው?" (መዝ 26፡1) በማለት ዘምሯል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡፡" (ዮሐ 8፡12) በማለት አስተምሯል፡፡ ጌታችን ጨለማ ያለው እርሱን አለማወቅ እንደፈቃዱ አለመመላለስ በኃጢአትና በክሕደት መኖርን ነው፡፡ (ሮሜ 13፡11-13) ብርሃን የተባለ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በእምነት ጸንተው በምግባር ቀንተው በትሩፋት አጊጠው እንደፈቃዱ የተመላለሱትንና ያገለገሉትን ወዳጆቹችንም ብርሃናት መሆናቸውን "እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ" በማለት መስክሮላቸዋል፡፡ ጌታችን ወዳጆቹ የዓለም ብርሃን የሚባሉት ብርሃን ሲሆኑ መሆኑን ሲናገርም "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ፡፡" (ማቴ 5፡14-16) ብሎዋል፡፡ በመነሻችን እንደተመለከትነው ጻድቁ ጨለማ ጣዖትን በማስወገድ ለዓለም ብርሃን ሆነዋል፡፡ ሰዎች ልቡናቸውን ከጣዖታት መልሰው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩትም ምክንያት ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ደራሲው የጌታችንን ቃል ይዞ ጻድቁን "ብርሃን ፀሐይ" በማለት አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን "መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡"(ያዕ 1፡17-18) በማለት የብርሃናት አባት ብሎ ጠርቶታል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ብርሃናት ብሎ የጠራቸው የብርሃን ክርስቶስ ልጆች ወዳጆቹ ቅዱሳን መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስወግዱ ኑፋቄንና ክሕደትንና እንዲያጠፋ የሰዎች ልጆችን ሕይወት በቅዱስ ቃሉ አማካኝነት እንዲያርሙና እንዲያስተካክሉ ወደ ዓለም የተላኩ ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱሳን ሐዋርያት በኋላ ዘመን የተነሡ ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ "እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ እግዚአብሔር አዞናል፡፡" በማለት በአንድ ቃል ተናግረዋል፡፡ (የሐዋ 13፡47) ቅዱሳን ጨለማ (ኃጢአት) በሞላው በሰው ልቡና ብርሃን ክርስቶስን የሚያበሩ ብርሃናት መሆናቸውን ትመለከታላችሁን? ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የንስሐ ስብከትን እየሰበከ የንስሐ ጥምቀትን እያጠመቀ በመንገድ የተመሰለ የሰውን ልቡና እያስተካከለ የተቀበለውን መጥምቁ ዮሐንስን "የሚነድና የሚያበራ ብርሃን" ብሎ ጠርቶታል፡፡ (ዮሐ 5፡35) መጥምቁ ዮሐንስ በጌታችን አንደበት የሚነድና የሚያበራ መብራት ተብሎ ስለምን ተመሰገነ? ወንጌልን በመስበኵ ጣዖታትን በማጥፋቱ ሰዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን በመመለሱ አይደለምን? ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፍቅር ነድደው ሰይጣንን ድል ነሥተዋል፡፡ በሕይወታቸው ክርስቶስን አብርተው በሰው ልቡና ነግሦ የነበረውን ጨለማ ኃጢአት ደርምሰዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጽድቅ (የእውነት ፀሐይ) እንደሆነ መንገዱን የተከተሉ ወዳጆቹም ፀሐይ ሆነው ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዘሪውን ምሳሌ ባስተማረበት ክፍል "በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡" (ማቴ 13፡44) በማለትም ጭምር አስተምሮዋል፡፡ እርሱ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሐይ ሲሆን ወዳጆቹ ደግሞ ጨረቃ ናቸው፡፡ ጨረቃ ብርሃንን የምታገኘው ከፀሐይ እንደሆነ ቅዱሳንም ጸጋን ክብርን ሥልጣንንም ያገኙት ከክርስቶስ ነውና ጌታችን "እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡" ብሎ አስተማረ፡፡ እንግዲህ በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን ተከትለው ጨለማ ጣዖትን ያጠፉ ደጋግ አባቶችና እናቶች ብርሃናት ፀሐይ ከዋክብት መባላቸውን ስንመለከት ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን ብርሃን ፀሐይ ብለን እንጠራቸዋለን እንጂ በጥርጥር መንፈስ ሆነን እንዴት? ለምን? ብለን አንጠይቅም፡፡
©️ መምህር ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ ም
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።” አለ :- የጽድቅ ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ (ማቴ 13፥43)
የመልክዐ ተክለሃይማኖት ደራሲ በመልክዑ አርኬ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን "ቅዱስ አባት ሆይ አምልኰተ ጣዖት ጨለማን አስወግደህ በዓለም የምታበራ ፀሐይ አንተ መዓዛህ የተወደደ ደብረ ከርቤን ነህ? ወይስ መሠወር የማይቻላት ደብረ ጽጌን ነህ? " በማለት ያመሰግናል፡፡ ቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት እንዲሁም በየዘመኑ የተነሡ መምህራን ዋና ተልዕኮ ጣዖት አምልኰን በቃለ ወንጌል ማስወገድ ነው፡፡ በሰዎች ዘንድ የሚታይ የሚዳሰስ ጣዖት አለ፡፡ እንዲሁም የማይታይ የማይዳሰስ ልብም የማይባል ረቂቅ ጣዖትም አለ፡፡
በኑሯችንና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ልብ ሳንላቸው ከእግዚአብሔር አስቀድመን ቅድሚያ የምንሰጣቸው ነገሮች ሁሉ ሳናውቃቸው ጣዓታት እንደሆኑብን ልናስተውል ይገባናል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን በየዘመናቸው ከሰዎች ልቡና የሚታዩትንም ሆነ የማይታዩትን ጣዖታት በቃለ እግዚአብሔር ሲያጠፉ ኑረዋል፡፡ በዚህም በነቢዩ ዳንኤል የትንቢት መጽሐፍ "ጥበበኞቹ እንደሰማይ ፀዳል ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡" (ዳን 12፡4) ተብሎ ትንቢት ተነግሮላቸዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት በገድላቸው እንደተጻፈልን በዘመናቸው ጣዖታትን አጥፍተዋል፡፡ በጣዖታቱ ላይ አድረው ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጃቸውን ሰዎች ሲያታልሉ የኖሩትንም እኵያን አጋንንት በወንጌል ትምህርት ሲያሳፍሩና ሲበቀሏቸው ኑረዋል፡፡ በዚህም ለብዙዎች ብርሃን ሆነዋል፡፡ ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ምን ያህል ጣዖታትን እንዳጠፉ ስንቶችን ከጣዖት አምልኰ እንዳላቀቁና አጋንንትን በወንጌል ትምህርት እንዴት እንዳወጡ ለመረዳት ገድላቸውን በእምነት ሆኖ ማንበቡ ተገቢ ይሆናል፡፡ ይኽን በሕሊናችን እንያዝና በዚህ ክፍል ጻድቁ የተገለጡበትን የምስጋና ቃል እንመልከት፡፡
+++ ተክለሃይማኖት ፀሐይ +++
በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ብርሃን ፀሐይ ተብሏል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "እግዚአብሔር ብሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማነው?" (መዝ 26፡1) በማለት ዘምሯል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡፡" (ዮሐ 8፡12) በማለት አስተምሯል፡፡ ጌታችን ጨለማ ያለው እርሱን አለማወቅ እንደፈቃዱ አለመመላለስ በኃጢአትና በክሕደት መኖርን ነው፡፡ (ሮሜ 13፡11-13) ብርሃን የተባለ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በእምነት ጸንተው በምግባር ቀንተው በትሩፋት አጊጠው እንደፈቃዱ የተመላለሱትንና ያገለገሉትን ወዳጆቹችንም ብርሃናት መሆናቸውን "እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ" በማለት መስክሮላቸዋል፡፡ ጌታችን ወዳጆቹ የዓለም ብርሃን የሚባሉት ብርሃን ሲሆኑ መሆኑን ሲናገርም "መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ፡፡" (ማቴ 5፡14-16) ብሎዋል፡፡ በመነሻችን እንደተመለከትነው ጻድቁ ጨለማ ጣዖትን በማስወገድ ለዓለም ብርሃን ሆነዋል፡፡ ሰዎች ልቡናቸውን ከጣዖታት መልሰው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩትም ምክንያት ሆነዋል፡፡ በመሆኑም ደራሲው የጌታችንን ቃል ይዞ ጻድቁን "ብርሃን ፀሐይ" በማለት አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን "መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡"(ያዕ 1፡17-18) በማለት የብርሃናት አባት ብሎ ጠርቶታል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ብርሃናት ብሎ የጠራቸው የብርሃን ክርስቶስ ልጆች ወዳጆቹ ቅዱሳን መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡ አምልኮ ጣዖትን እንዲያስወግዱ ኑፋቄንና ክሕደትንና እንዲያጠፋ የሰዎች ልጆችን ሕይወት በቅዱስ ቃሉ አማካኝነት እንዲያርሙና እንዲያስተካክሉ ወደ ዓለም የተላኩ ቅዱሳን ነቢያት፣ ቅዱሳን ሐዋርያት በኋላ ዘመን የተነሡ ጻድቃን ሰማዕታት ሁሉ "እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ እግዚአብሔር አዞናል፡፡" በማለት በአንድ ቃል ተናግረዋል፡፡ (የሐዋ 13፡47) ቅዱሳን ጨለማ (ኃጢአት) በሞላው በሰው ልቡና ብርሃን ክርስቶስን የሚያበሩ ብርሃናት መሆናቸውን ትመለከታላችሁን? ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የንስሐ ስብከትን እየሰበከ የንስሐ ጥምቀትን እያጠመቀ በመንገድ የተመሰለ የሰውን ልቡና እያስተካከለ የተቀበለውን መጥምቁ ዮሐንስን "የሚነድና የሚያበራ ብርሃን" ብሎ ጠርቶታል፡፡ (ዮሐ 5፡35) መጥምቁ ዮሐንስ በጌታችን አንደበት የሚነድና የሚያበራ መብራት ተብሎ ስለምን ተመሰገነ? ወንጌልን በመስበኵ ጣዖታትን በማጥፋቱ ሰዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን በመመለሱ አይደለምን? ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፍቅር ነድደው ሰይጣንን ድል ነሥተዋል፡፡ በሕይወታቸው ክርስቶስን አብርተው በሰው ልቡና ነግሦ የነበረውን ጨለማ ኃጢአት ደርምሰዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጽድቅ (የእውነት ፀሐይ) እንደሆነ መንገዱን የተከተሉ ወዳጆቹም ፀሐይ ሆነው ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዘሪውን ምሳሌ ባስተማረበት ክፍል "በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡" (ማቴ 13፡44) በማለትም ጭምር አስተምሮዋል፡፡ እርሱ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ፀሐይ ሲሆን ወዳጆቹ ደግሞ ጨረቃ ናቸው፡፡ ጨረቃ ብርሃንን የምታገኘው ከፀሐይ እንደሆነ ቅዱሳንም ጸጋን ክብርን ሥልጣንንም ያገኙት ከክርስቶስ ነውና ጌታችን "እንደ ፀሐይ ይበራሉ፡፡" ብሎ አስተማረ፡፡ እንግዲህ በቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን ተከትለው ጨለማ ጣዖትን ያጠፉ ደጋግ አባቶችና እናቶች ብርሃናት ፀሐይ ከዋክብት መባላቸውን ስንመለከት ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖትን ብርሃን ፀሐይ ብለን እንጠራቸዋለን እንጂ በጥርጥር መንፈስ ሆነን እንዴት? ለምን? ብለን አንጠይቅም፡፡
©️ መምህር ቢትወደድ ወርቁ
ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ ም
#አንዳንድ ልጆች ከወላጆቻቸው የሚበልጡበት ጊዜ አለ አንዳንድ ወላጆች ደግሞ በነገሮች ዕይታ ከልጆቻቸው የሚያንሱበትም ጊዜ አለ ። እናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ይህን በመገንዘቧ ነበር ልጇን ሕፃኑ ቂርቆስን ስለ መልካም ምክሩ ልጇ ሆኖ ሳለ አባቴ ብላ ለመጥራት የተገደደችሁ ።
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
"ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሣራ ተመልከቱ።" (ኢሳ 51:2)
ነቢዩ ይህንን ቃል ቅዱስ አብርሃምንና ቅድስት ሣራን ምሰሏቸው ለማለት ተናግሮታል።
#አብርሃም አበ መናንያን (የመናንያን አባት) ነው።ሁሉን ትቶ እግዚአብሔርን ተከትሎአልና።(ዘፍ 12:1)
#አብርሃም የሙሽሮችም አባት ነው።ሚስቱ ምን መካን ብትሆን አልተዋትምና።
#አብርሃም ለሰብዓ ዓለም (በዓለም ለሚኖሩ ክርስቲያኖች) አባት ነው።በሕገ ልቡና ሁኖ ወንጌልን ፈጽሟልና።አረ ግሩም ነው !!! የእግዚአብሔር እንግዳ ቤቴ ሳይመጣ ግብር አላገባም፤እህል አልቀምስም ማለት እንዴት ያለ ብፅዕና ነው!? ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅረ ቢጽ እንዴት ቢጸኑለት ነው!?ደጉ አባታችን የእግዚአብሔር ሰው አብርሃም ወንጌልን ሲፈጽማት ተመልከቱልኝማ!!!
#"በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና"(ማቴ 5:3) ትሑቱ አብርሃም ባለጠጋ ሆኖ ሳለ ለእኔ የሚስማማ ደህነትነው፤ባለጠግነትማ የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው በማለት መንፈሱን ዝቅ አድርጎ ራሱን እንዳሳላፊ ቆጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ለሌሎች ያካፍል ነበር።በዚህም መንግሥተ ሰማያት (የሰማያት መንግሥት) የሆኑ ሥላሴን አስተናግዷል።መንግሥተ ሰማያት የሚባል ጌታም ከእርሱ ዘር ተወልዷል።"የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።"ማቴ 1:1እንዲል
#“የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።”
(ማቴ 5:4) ርኅሩኁ አብርሃም ለሦስት ቀናት ያህል ሰው ቤቱ ስላልመጣ እጅጉን አዝኗል።ሥላሴን በማግኘት ተጽናንቷል።
#"ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።"(ማቴ 5:6) መፍቀሬ ሰብእ ደጉ አብርሃም ስለ ሰው ፍቅር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ተርቧል።ጽድቅ የሚባል እግዚአብሔርን በድንኳኑ ተቀብሎም ጠግቧል (ነፍሱ ተደስታለች) ።
#"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።"(ማቴ 5:10) የሃይማኖት ሰው አብርሃም እግዚአብሔር "ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"(ዘፍ 12:1) ሲለው በፍጹም እምነት ወጥቷል።መንግሥቱንም ወርሷል።
"አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፤አየም ደስም አለው።" ዮሐ8:56 ማለት እንግዲህ ይህ ነው።በጨለማው ዘመን ሆኖ ብርሃንን ማየት ወንጌልን መኖር!!!ቅድስት ሥላሴን በቤቱ ተቀብሎ"የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተእመለሳለሁ፤ሣራምልጅንታገኛለች።"ዘፍ18፤14 ባለው ቃል መሠረት ለጊዜው ይስሐቅን እንደሚወልድ ለፍጻሜው ክርስቶስ ከእርሱ እንደሚወለድ ኪዳንን ተቀብሏል።
#በሕገ ልቡና ሕገ ኦሪት በሕገ ኦሪት ሕገ ወንጌል በተሰጠን በእኛ ቅዱስ አብርሃም ይፈርዳል፤ከአብርሃም የሚከብር ጌታ በሥጋ አብርሃም ተወልዶ በጥምቀት ልጅነትን፣በልጅነት መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶን የአብርሃምን ሥራ አልሠራንምና።
የአብርሃሙ ሥላሴ በሁላችን ቤት ይደሩ!!!
ሐምሌ ሥላሴ/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
ነቢዩ ይህንን ቃል ቅዱስ አብርሃምንና ቅድስት ሣራን ምሰሏቸው ለማለት ተናግሮታል።
#አብርሃም አበ መናንያን (የመናንያን አባት) ነው።ሁሉን ትቶ እግዚአብሔርን ተከትሎአልና።(ዘፍ 12:1)
#አብርሃም የሙሽሮችም አባት ነው።ሚስቱ ምን መካን ብትሆን አልተዋትምና።
#አብርሃም ለሰብዓ ዓለም (በዓለም ለሚኖሩ ክርስቲያኖች) አባት ነው።በሕገ ልቡና ሁኖ ወንጌልን ፈጽሟልና።አረ ግሩም ነው !!! የእግዚአብሔር እንግዳ ቤቴ ሳይመጣ ግብር አላገባም፤እህል አልቀምስም ማለት እንዴት ያለ ብፅዕና ነው!? ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅረ ቢጽ እንዴት ቢጸኑለት ነው!?ደጉ አባታችን የእግዚአብሔር ሰው አብርሃም ወንጌልን ሲፈጽማት ተመልከቱልኝማ!!!
#"በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና"(ማቴ 5:3) ትሑቱ አብርሃም ባለጠጋ ሆኖ ሳለ ለእኔ የሚስማማ ደህነትነው፤ባለጠግነትማ የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው በማለት መንፈሱን ዝቅ አድርጎ ራሱን እንዳሳላፊ ቆጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ለሌሎች ያካፍል ነበር።በዚህም መንግሥተ ሰማያት (የሰማያት መንግሥት) የሆኑ ሥላሴን አስተናግዷል።መንግሥተ ሰማያት የሚባል ጌታም ከእርሱ ዘር ተወልዷል።"የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።"ማቴ 1:1እንዲል
#“የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።”
(ማቴ 5:4) ርኅሩኁ አብርሃም ለሦስት ቀናት ያህል ሰው ቤቱ ስላልመጣ እጅጉን አዝኗል።ሥላሴን በማግኘት ተጽናንቷል።
#"ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።"(ማቴ 5:6) መፍቀሬ ሰብእ ደጉ አብርሃም ስለ ሰው ፍቅር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ተርቧል።ጽድቅ የሚባል እግዚአብሔርን በድንኳኑ ተቀብሎም ጠግቧል (ነፍሱ ተደስታለች) ።
#"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።"(ማቴ 5:10) የሃይማኖት ሰው አብርሃም እግዚአብሔር "ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"(ዘፍ 12:1) ሲለው በፍጹም እምነት ወጥቷል።መንግሥቱንም ወርሷል።
"አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፤አየም ደስም አለው።" ዮሐ8:56 ማለት እንግዲህ ይህ ነው።በጨለማው ዘመን ሆኖ ብርሃንን ማየት ወንጌልን መኖር!!!ቅድስት ሥላሴን በቤቱ ተቀብሎ"የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተእመለሳለሁ፤ሣራምልጅንታገኛለች።"ዘፍ18፤14 ባለው ቃል መሠረት ለጊዜው ይስሐቅን እንደሚወልድ ለፍጻሜው ክርስቶስ ከእርሱ እንደሚወለድ ኪዳንን ተቀብሏል።
#በሕገ ልቡና ሕገ ኦሪት በሕገ ኦሪት ሕገ ወንጌል በተሰጠን በእኛ ቅዱስ አብርሃም ይፈርዳል፤ከአብርሃም የሚከብር ጌታ በሥጋ አብርሃም ተወልዶ በጥምቀት ልጅነትን፣በልጅነት መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶን የአብርሃምን ሥራ አልሠራንምና።
የአብርሃሙ ሥላሴ በሁላችን ቤት ይደሩ!!!
ሐምሌ ሥላሴ/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናትና!!" +++
ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናት ዓመታዊ በዓል (ብዙኃን ማርያም) እንኳን አደረሰን!!
(በትዕግሥት ሆነው ያንብቡት፣ ለሌላውም በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ)
ላለመማርና ላለማወቅ አእምሯቸውን አሳልፈው የሰጡ ኦርቶዶክሳዊነትንና ኦርቶዶክሳውያንን አምርረው የጠሉ ሰዎች "ድንግል ማርያም ምክንያተ ድኂን እንጂ መድኃኒት አትባልም" ሲሉ ለይቶላቸው የወጡቱ ደግሞ ጥቅሶችን ከዓውድና ከተነገሩበት ዓላማ ውጭ በመጥቀስ "ማርያምን መድኃኒት ቤዛ አድኝን" አትበሏት ብለው በአፍም በመጽሐፍም ይናገራሉ:: ኦርቶዶክሳውያን ድንግል ማርያምን "መድኃኒት፣ ቤዛ" ብለን ስንጠራት በውስጥም በአፋ ያሉ ብዙዎች ባልተረዱት ባላወቁት ባልመረመሩት ነገር እርሷን ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያተካከልናት በእርሱ የማዳን ዙፋን ያስቀመጥናት አድርገው ያስባሉ ይናገራሉም:: ከዚያም አልፈው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ላይ የተንሸዋረረ እውቀትና እምነት እንዳለን አድርገው በሌሎች ዘንድ ያጠለሹናል:: ኦርቶዶክሳውያን ያዳነን ማን እንደሆነ ከምን እንዳዳነን ለምን እንዳዳነንና በማዳኑም ሥራ ውስጥ ማዳኑ የተፈጸመለት የሰው ልጅ ሱታፌና ድርሻ ምን መሆን እንደሚገባው ቤተክርስቲያን ታስተምረናለች:: ድንግል ማርያምና ቅዱሳኑን በመንቀፍና በመጥላት ስለ እነርሱም ላለመናገር ዳተኛ በመሆን ለክርስቶስ ያለኝን "ፍቅር" እገልጻለሁ ብሎ መድከም ምንኛ አለመታደል ነው? ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የ"ፓስተሮቻቸውን የ"መጋቤዎቻቸውን" የ"ነቢያቶቻቸውን" የ"ያድናሉ" መልእክት በፖስተር በብሮሸርና በትላልቅ "ባነሮች" እየለጠፋ ወደ የመስብሰቢያ አዳራሾቻቸው ሰዎችን ይጋብዛሉ : በየጉባኤዎቻቸውም የሚያምኑበትን የራሳቸውን ትምህርት ከማስተማር ይልቅ ኦርቶዶክሳዊነትን እያጨለሙና እያጠለሹ የሌለ ስም እየሰጡ ይሰብካሉ:: ኢየሱስ ክርስቶስ ከምንና ለምን አዳነን? እርሱ ካዳነን ከእኛ ምን ይጠበቃል? የሚሉትን ሀሳቦች ማየቱ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ለጊዜው አቆይተነው ወደ ነጥባችን እንመለስ :-
+++ ድንግል ማርያም መድኃኒት አትባልምን ? +++
መልሱ ግልጽ ነው::መድኃኒት ትባላለች:: እርሷ መድኃኒት ማለታችን ግን ከክርስቶስ ጋር አስተካከልናት ማለት አይደለም ሊሆንም አይችልም::በመጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ብርሃን ተብሏል ቅዱሳንም ብርሃን ተብለዋል:: (ማቴ 5:14 ዮሐ 5:38፣ 8:12) እናስተውል እርሱን ብርሃን ስንለውና እነርሱን ብርሃናት ስንላቸው አንድ አይደለም:: እርሱን ብርሃን ስንለው ቃሉ እንደ አምላክነቱ ይረቃል ይመጥቃል ይረቃልም:: እነርሱን ብርሃናት ስንላቸውም እንደ ማዕረጋቸው እንደ ቅድስና ደረጃቸው ነው። (ማቴ 13: 8 1ቆሮ 15:41) ያ ባይሆን ቅዱስ መጽሐፍ ክርስቶስንም ብርሃን አገልጋዮቹንም ብርሃን በማለቱ እርሱንና ቅዱሳኑን አፎካከረ ያሰኝ ነበር:: ወዳጆቹን ብርሃናት ማለት የእርሱን ብርሃንነት መካድ አይደለም:: እርሱ እንደውም የብርሃናት (የቅዱሳን) አባት ተብሏል:: (ያዕ 1:17) ይህን እንደ መነሻ ካልን እርሷ መድኃኒት መባል እንደሚገባት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርገን በንጽጽር እንመልከት::
+++ ቤዛ እስራኤል ቤዛዊተ ዓለም +++
በብሉይ ኪዳን እስራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ነጻ ያወጣ በጸናች እጅ በተዘረጋችም ክንድ ለሕዝቡ ቤዛ የሆነ ጠላቶቻቸውን የጣለ እርሱ እግዚአብሔር ነው::እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ነፃ ሲያወጣ ነፃ ካወጣቸውም በኋላ የነፃነት ጉዞ ሲያደርጉ መላእክት ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን እንደሚመራቸው ተነግሯቸው ነበር:: (ዘጸ 14:19 ዘጸ 23:20) በዚህ ነጻ የመውጣት ጉዞ ውስጥ ታላቅ ሚናና ድርሻ የነበረው ሰው መስፍኑ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነበር :: ሕዝቡን ይመራና ያስተዳድር ስለእነርሱም ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ነበር:: (ዘጸ 32:32) በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር የሆኑት እስራኤላውያን "የሙሴ ሕዝብ" ሲባሉ ሙሴም በፈጣሪው "የሕዝቡ ነፃ አውጪ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8) እስራኤል እግዚአብሔርን ባሳዘኑት ጊዜ ሙሴ ስለ እነርሱ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ ያጠፋቸው ነበር:: (መዝ 105:23) ከዚህ ሁሉ የተነሳ እግዚአብሔር ሙሴን ምክንያት አድርጎ ሕዝቡን ከባርነት ነጻ ስላወጣቸው ሙሴ "የእስራኤል ነፃ አውጪና ቤዛ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8፣ የሐዋ 7:35) ይህንም መጽሐፍ ሲመሠክር " ይህ ሰው (ሙሴ) በግብጽ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው" ብሏል :: (የሐዋ 7:36)
እስቲ ጥያቄ እናንሣ እስራኤልን ነፃ ያወጣ ማነው? ሙሴ እንዴት ነፃ አውጪ ተባለ? የእስራኤል ቤዛ ማነው? ሙሴ እንዴት የእስራኤል ቤዛ ተባለ? እስራኤል የማን ሕዝብ ናቸው? የእግዚአብሔር የሆኑት ሕዝቡ እንዴት የሙሴ ሕዝብ ተባሉ? ሙሴ በሕዝቡ መካከል ድንቅና ምልክት ካደረገ "ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ድንቅና ምልክቶችን አድርጋለች።" ተብሎ ሲነገር "ይህማ አይሆንም!" ብሎ ሽንጥ ገትሮ መከራከርን ምን አመጣው? (ማር 16:17 ዮሐ 14:15 ::) በሐዲስ ኪዳን ግብጽ የሲኦል እስራኤላውያን የምእመናነ ሐዲስ ጉዟቸው የጉዟችን የገጠሟቸው ፈተናዎች የፈተናዎቻችን ምሳሌዎች እንደሆኑ ተነግሮናል:: (1ቆሮ 10:1-5) በሙሴ ምስፍና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንዳወጣ ከእርሷ ከድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሐደው) ሥጋ እኛን ከሰይጣን አገዛዝ ከሲኦል ባርነት ነፃ አውጥቶናል:: (ዕብ 2:14-16 1ጴጥ 3:19 ዮሐ 1:14-15) በሙሴ ተልእኮ እስራኤል ከግብጽ ወጡ ከድንግል በነሳው ሥጋ ዓለም ከሲኦል ነፃ ወጣ:: በሙሴ ተልእኮ ፈርኦን ተሸነፈ ከድንግል በተዋሐደው ሥጋ በፈጸመው የማዳን ሥራ ዲያብሎስ አፈረ በመስቀሉም ተጠረቀ:: (ቆላ 2:14-16) እስራኤል ከሥጋ ባርነት ከፈርኦን አገዛዝ ነፃ ከወጡበት መንገድ ዓለም ከነፍስ ባርነት ከሰይጣን አገዛዝ የዳነበት መንገድ ይበልጣል :: በእርሱ ምክንያት በተፈጸመው እስራኤልን ነጻ የማውጣት ጉዞ ሙሴ ቤዛ ነጻ አውጪ ከተባለ በድንግል ማርያም በተፈጸመው የማዳን ሥራ ቤዛዊተ ዓለም ብትባል ምን ያንስባታል? እራሷ " ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ ( ማዳኑን ) አድርጓልና።" እንዳለች (ሉቃ 1:49-50)
+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናት +++
በተአምረ ማርያም መቅድም ከሠፈሩ እመቤታችንን እንድንወዳት ከሚያስገነዝቡን ኃይለ ቃላት አንዱ "ውደዷት እርሷ መድኃኒታችሁ ናት" ይላል:: እንግዲህ ይህን አንብበው ነው ሰዎቹ ለምን እንዲህ ትላላችሁ ብለው እንደ ጥህሎ ሊውጡን እንደ እንቀት ሊጠጡን የሚነሥሡብን ሳይመረምሩና ሳይገነዘቡም የሚተቹን :: እነዚህ ክፍሎች እርሷን እንዴት መድኃኒት ትሏታላችሁ? ብለውም ጉንጭ አልፋ መከራከርያ ያነሣሉ:: እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኒት አዳኝ ነው:: ማዳን የባሕርይው የሆነ እርሱ የወደዳቸውን በፍጹም ልባቸው ያመለኩት ወዳጆቹን ምክንያት አድርጎ በልዩ ልዩ መንገድ ማዳኑን ስለገለጠባቸው መድኃኒት አዳኝ እንዲባሉ ፈቀደ ያድኑም ዘንድ የማዳኑን ጥበብ ገለጠላቸው ኃይሉንም አስታጠቃቸው መንገዳቸውንም አቃና:: እስቲ የሚከተሉትን ለግንዛቤ እንመልከት
👇-ይቀጥላል-👇
ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናት ዓመታዊ በዓል (ብዙኃን ማርያም) እንኳን አደረሰን!!
(በትዕግሥት ሆነው ያንብቡት፣ ለሌላውም በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታዎን ይወጡ)
ላለመማርና ላለማወቅ አእምሯቸውን አሳልፈው የሰጡ ኦርቶዶክሳዊነትንና ኦርቶዶክሳውያንን አምርረው የጠሉ ሰዎች "ድንግል ማርያም ምክንያተ ድኂን እንጂ መድኃኒት አትባልም" ሲሉ ለይቶላቸው የወጡቱ ደግሞ ጥቅሶችን ከዓውድና ከተነገሩበት ዓላማ ውጭ በመጥቀስ "ማርያምን መድኃኒት ቤዛ አድኝን" አትበሏት ብለው በአፍም በመጽሐፍም ይናገራሉ:: ኦርቶዶክሳውያን ድንግል ማርያምን "መድኃኒት፣ ቤዛ" ብለን ስንጠራት በውስጥም በአፋ ያሉ ብዙዎች ባልተረዱት ባላወቁት ባልመረመሩት ነገር እርሷን ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያተካከልናት በእርሱ የማዳን ዙፋን ያስቀመጥናት አድርገው ያስባሉ ይናገራሉም:: ከዚያም አልፈው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ላይ የተንሸዋረረ እውቀትና እምነት እንዳለን አድርገው በሌሎች ዘንድ ያጠለሹናል:: ኦርቶዶክሳውያን ያዳነን ማን እንደሆነ ከምን እንዳዳነን ለምን እንዳዳነንና በማዳኑም ሥራ ውስጥ ማዳኑ የተፈጸመለት የሰው ልጅ ሱታፌና ድርሻ ምን መሆን እንደሚገባው ቤተክርስቲያን ታስተምረናለች:: ድንግል ማርያምና ቅዱሳኑን በመንቀፍና በመጥላት ስለ እነርሱም ላለመናገር ዳተኛ በመሆን ለክርስቶስ ያለኝን "ፍቅር" እገልጻለሁ ብሎ መድከም ምንኛ አለመታደል ነው? ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የ"ፓስተሮቻቸውን የ"መጋቤዎቻቸውን" የ"ነቢያቶቻቸውን" የ"ያድናሉ" መልእክት በፖስተር በብሮሸርና በትላልቅ "ባነሮች" እየለጠፋ ወደ የመስብሰቢያ አዳራሾቻቸው ሰዎችን ይጋብዛሉ : በየጉባኤዎቻቸውም የሚያምኑበትን የራሳቸውን ትምህርት ከማስተማር ይልቅ ኦርቶዶክሳዊነትን እያጨለሙና እያጠለሹ የሌለ ስም እየሰጡ ይሰብካሉ:: ኢየሱስ ክርስቶስ ከምንና ለምን አዳነን? እርሱ ካዳነን ከእኛ ምን ይጠበቃል? የሚሉትን ሀሳቦች ማየቱ እጅግ ሰፊ በመሆኑ ለጊዜው አቆይተነው ወደ ነጥባችን እንመለስ :-
+++ ድንግል ማርያም መድኃኒት አትባልምን ? +++
መልሱ ግልጽ ነው::መድኃኒት ትባላለች:: እርሷ መድኃኒት ማለታችን ግን ከክርስቶስ ጋር አስተካከልናት ማለት አይደለም ሊሆንም አይችልም::በመጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ብርሃን ተብሏል ቅዱሳንም ብርሃን ተብለዋል:: (ማቴ 5:14 ዮሐ 5:38፣ 8:12) እናስተውል እርሱን ብርሃን ስንለውና እነርሱን ብርሃናት ስንላቸው አንድ አይደለም:: እርሱን ብርሃን ስንለው ቃሉ እንደ አምላክነቱ ይረቃል ይመጥቃል ይረቃልም:: እነርሱን ብርሃናት ስንላቸውም እንደ ማዕረጋቸው እንደ ቅድስና ደረጃቸው ነው። (ማቴ 13: 8 1ቆሮ 15:41) ያ ባይሆን ቅዱስ መጽሐፍ ክርስቶስንም ብርሃን አገልጋዮቹንም ብርሃን በማለቱ እርሱንና ቅዱሳኑን አፎካከረ ያሰኝ ነበር:: ወዳጆቹን ብርሃናት ማለት የእርሱን ብርሃንነት መካድ አይደለም:: እርሱ እንደውም የብርሃናት (የቅዱሳን) አባት ተብሏል:: (ያዕ 1:17) ይህን እንደ መነሻ ካልን እርሷ መድኃኒት መባል እንደሚገባት መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርገን በንጽጽር እንመልከት::
+++ ቤዛ እስራኤል ቤዛዊተ ዓለም +++
በብሉይ ኪዳን እስራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ነጻ ያወጣ በጸናች እጅ በተዘረጋችም ክንድ ለሕዝቡ ቤዛ የሆነ ጠላቶቻቸውን የጣለ እርሱ እግዚአብሔር ነው::እግዚአብሔር ሕዝቡን ከባርነት ነፃ ሲያወጣ ነፃ ካወጣቸውም በኋላ የነፃነት ጉዞ ሲያደርጉ መላእክት ቀን በደመና ሌሊት በብርሃን እንደሚመራቸው ተነግሯቸው ነበር:: (ዘጸ 14:19 ዘጸ 23:20) በዚህ ነጻ የመውጣት ጉዞ ውስጥ ታላቅ ሚናና ድርሻ የነበረው ሰው መስፍኑ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነበር :: ሕዝቡን ይመራና ያስተዳድር ስለእነርሱም ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ነበር:: (ዘጸ 32:32) በዚህም ምክንያት የእግዚአብሔር የሆኑት እስራኤላውያን "የሙሴ ሕዝብ" ሲባሉ ሙሴም በፈጣሪው "የሕዝቡ ነፃ አውጪ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8) እስራኤል እግዚአብሔርን ባሳዘኑት ጊዜ ሙሴ ስለ እነርሱ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ ያጠፋቸው ነበር:: (መዝ 105:23) ከዚህ ሁሉ የተነሳ እግዚአብሔር ሙሴን ምክንያት አድርጎ ሕዝቡን ከባርነት ነጻ ስላወጣቸው ሙሴ "የእስራኤል ነፃ አውጪና ቤዛ" ተብሏል:: (ዘጸ 32:7-8፣ የሐዋ 7:35) ይህንም መጽሐፍ ሲመሠክር " ይህ ሰው (ሙሴ) በግብጽ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው" ብሏል :: (የሐዋ 7:36)
እስቲ ጥያቄ እናንሣ እስራኤልን ነፃ ያወጣ ማነው? ሙሴ እንዴት ነፃ አውጪ ተባለ? የእስራኤል ቤዛ ማነው? ሙሴ እንዴት የእስራኤል ቤዛ ተባለ? እስራኤል የማን ሕዝብ ናቸው? የእግዚአብሔር የሆኑት ሕዝቡ እንዴት የሙሴ ሕዝብ ተባሉ? ሙሴ በሕዝቡ መካከል ድንቅና ምልክት ካደረገ "ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ድንቅና ምልክቶችን አድርጋለች።" ተብሎ ሲነገር "ይህማ አይሆንም!" ብሎ ሽንጥ ገትሮ መከራከርን ምን አመጣው? (ማር 16:17 ዮሐ 14:15 ::) በሐዲስ ኪዳን ግብጽ የሲኦል እስራኤላውያን የምእመናነ ሐዲስ ጉዟቸው የጉዟችን የገጠሟቸው ፈተናዎች የፈተናዎቻችን ምሳሌዎች እንደሆኑ ተነግሮናል:: (1ቆሮ 10:1-5) በሙሴ ምስፍና እግዚአብሔር ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንዳወጣ ከእርሷ ከድንግል ማርያም በነሳው (በተዋሐደው) ሥጋ እኛን ከሰይጣን አገዛዝ ከሲኦል ባርነት ነፃ አውጥቶናል:: (ዕብ 2:14-16 1ጴጥ 3:19 ዮሐ 1:14-15) በሙሴ ተልእኮ እስራኤል ከግብጽ ወጡ ከድንግል በነሳው ሥጋ ዓለም ከሲኦል ነፃ ወጣ:: በሙሴ ተልእኮ ፈርኦን ተሸነፈ ከድንግል በተዋሐደው ሥጋ በፈጸመው የማዳን ሥራ ዲያብሎስ አፈረ በመስቀሉም ተጠረቀ:: (ቆላ 2:14-16) እስራኤል ከሥጋ ባርነት ከፈርኦን አገዛዝ ነፃ ከወጡበት መንገድ ዓለም ከነፍስ ባርነት ከሰይጣን አገዛዝ የዳነበት መንገድ ይበልጣል :: በእርሱ ምክንያት በተፈጸመው እስራኤልን ነጻ የማውጣት ጉዞ ሙሴ ቤዛ ነጻ አውጪ ከተባለ በድንግል ማርያም በተፈጸመው የማዳን ሥራ ቤዛዊተ ዓለም ብትባል ምን ያንስባታል? እራሷ " ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ ( ማዳኑን ) አድርጓልና።" እንዳለች (ሉቃ 1:49-50)
+++ እርሷ መድኃኒታችሁ ናት +++
በተአምረ ማርያም መቅድም ከሠፈሩ እመቤታችንን እንድንወዳት ከሚያስገነዝቡን ኃይለ ቃላት አንዱ "ውደዷት እርሷ መድኃኒታችሁ ናት" ይላል:: እንግዲህ ይህን አንብበው ነው ሰዎቹ ለምን እንዲህ ትላላችሁ ብለው እንደ ጥህሎ ሊውጡን እንደ እንቀት ሊጠጡን የሚነሥሡብን ሳይመረምሩና ሳይገነዘቡም የሚተቹን :: እነዚህ ክፍሎች እርሷን እንዴት መድኃኒት ትሏታላችሁ? ብለውም ጉንጭ አልፋ መከራከርያ ያነሣሉ:: እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኒት አዳኝ ነው:: ማዳን የባሕርይው የሆነ እርሱ የወደዳቸውን በፍጹም ልባቸው ያመለኩት ወዳጆቹን ምክንያት አድርጎ በልዩ ልዩ መንገድ ማዳኑን ስለገለጠባቸው መድኃኒት አዳኝ እንዲባሉ ፈቀደ ያድኑም ዘንድ የማዳኑን ጥበብ ገለጠላቸው ኃይሉንም አስታጠቃቸው መንገዳቸውንም አቃና:: እስቲ የሚከተሉትን ለግንዛቤ እንመልከት
👇-ይቀጥላል-👇
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በሁለት የቀደሙ የመጻሕፍት አበርክቷቸው የምናውቃቸው መምህራችን መካሪያችን አባታችን የጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተ ብርሐን ሰንበት ት/ቤት ፍሬ እና በቀድሞ አገልግሎታቸው በኮተቤ ሐገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አገልጋይ እና በአሁኑ ሰዓት በገነተ ጽጌ አራዳ ጊዮርጊስ የስብከተ ወንጌል አገልጋይ መምህር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ መርሐግብር ባለሙያና አገልጋይ
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ በአዲስ ክታብ
የክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫዎቹና ተጋድሎው
በሚል ግሩም መጽሐፍ ለኅትመት ይዘውልን ከተፍ ብለዋል። ... በአካል ሁሉን ማግኘት ባይችሉ እንኳን በመጽሐፍ ሊመክሩን ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ነውና በቅርቡ ገበያ ላይ ሲውል እንዳያመልጥዎ በትኩረት ይጠብቁን ይላሉ!!! 🙏🙏🙏
#አባቴ_ነውና_አዎን አውቀዋለሁ !
______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ግንቦት 11/2014ዓ.ም
______
#ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት
#ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ።
ሰይፍ አርእድ በተባለ በነዋየ ክርስቶስ መንግሥት ደግሞ ከንጉሥ ሠራዊት አንዱ ወደ ዋሊ ገዳም ሄደ ።ሁለት መነኮሳት አግኝቶ እጅ ነሳቸው ፤ ከወዴት ነህ? አሉት? ከሸዋ ክፍለ ሀገር ከዚያው ግራርያ ከምትባል አውራጃ ነኝ አላቸው። ተክለ ሃይማኖት የሚሉትን ታውቀዋለህ ? አሉት። #አባቴ_ነውና_አዎን_አውቀዋለሁ አላቸው።
#ወደ_መቃብሩ_ደርስሃል ? አሉት። አዎን ደርሻለሁ አላቸው። እነዚያም መነኮሳት ተነስሀው ሰገዱለት የእግሮቹንም ትቢያ ይልሱ እጆቹንም ይስሙ ጀመሩ። ጭፍራውም ጌቶቼ ይህንን ስለምን አደረጋችሁ?? አላቸው ። እኛ እናውቃለን አሉት። ዳግመኛም በተክለ ሃይማኖት የመቃብር ቦታ ሥጋ ወደሙን ተቀበልክን? አሉት። አልተቀበልኩም አላቸው። ከቅዱሱ መቃብር ዘንድ ቁርባን ያልተቀበልክ #እቡዘ_ልብ_ለምን_ሆንክ ? የተክለ ሃይማኖት አጽም ካረፈበት ቦታ ቁርባንን የተቀበለ ሁሉ ሲዖልን ዐያይም ሲል ከጌታ አንደበት በእውነት ሰማን ብለን በእውነት እንነግርሃለን አሉት።
#በውስጧም የሚቀበር ለዘለዓለም እንዳይጎዳም እኛም መንፈስ ቅዱስ በየሰዓቱ ይልቁንም በቁርባን ጊዜ እየወረደ በውስጧም መሥዋት ለሚያቀርቡ መዐዛ ያለውን ሽቱ ሲቀባቸው ዘወትር እናያለን ፤እንደ ብርሃን ደመና በላይዋ የረበበ ነው እንጂ ለሊትና ቀን ከእርሷ መንፈስ ቅዱስ አይርቅም።
እንዲሁ ዘወትር ይኖራል።በእርሷም የተቀመጠ የቆመ በውስጧም የተቀበረ በረድኤቷም የተጠጋ የተመሰገነ ነው። #ያለ_ተክለ_ሃይማኖት_ጸሎትና_ረድኤት_ለኢትዮጵያ_ሰዎች_የመዳን_ተስፋ_የላቸውም ። አሉት
ሌላም የተሰወረ ምሥጢር ነገሩትሌላውን ግን ልንጽፈው አንችልም መጽሐፍ የምንገልጠውም የምንሰውረውም ነገር አለ እንዳለ ይንንም ብለውት ከእርሱ ተሰወሩ።
" #አዎን_ለምንፍገመገም_ለኛ_ለኢትዮጵያውያን ያላንተ ረዳት የለንምና #ምልጃህ አትለየን " #አሜን!
#ገድለ_ተክለ_ሃይማኖት ምዕራፍ 50/60
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥንተ ጽሕፈቱ #ግንቦት 11/2014ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel
Photo
“ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።” (ቅዱስ ጳውሎስ 2ኛ ቆሮ 9፥14)
--------------------------------
☞ ጻድቃን "አያማልዱም" የሚለውን ክርክር ተወውና የዘፍጥረትን መጽሐፍ ገልጠህ ፈጣሪህን ጠይቅ። ደጋጎች አይደለም ማልደው ለጥፋት በተዘጋጀች ከተማ ቢኖሩ እንኳን በከተማይቱ ስለመኖራቸው ብሎ ምሕረትን ያወርዳል።
☞ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን በኃጢአታቸው ምክንያት በእሳትና በዲን አቃጥሎ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ለወዳጁ ለአብርሃም "እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።" ካለ በኋላ "የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።" በማለት ነገረው። ይህ ነገር በእግዚአብሔር የተነገረው አብርሃም ደጋግሞ ምን ብሎ እንደጸለየ ታስተውላለህን? "አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?"….... ዳግመኛም "ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? "… ሦስተኛም "ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ?… አራተኛም፦ "እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ?" አለ።" ቅዱሱ ሰው አብርሃም በመጨረሻ የጸለየውን ጸሎት ልብ በል "በእነዚህ በሁለት ታላላቅ ከተሞች አሥር ጻድቃንን ብታገኝ አትምርምን?" የሚል ነው። እግዚአብሔር ምን ብሎ የመለሰ ይመስልሃል? "አምሳ ሳይሆን አሥርም ጻድቃን ባገኝ እምራለሁ!!!" (ዘፍ 18:17-25)
☞ እስቲ ልጠይቅህ ዛሬ ግብረ ሰዶማዊነት የት ደርሶዋል? በደጅህ አልደረሰምን? ለቀደሙት ስለገባው ቃልኪዳን ታግሦዋል እንጂ ሰዶማውያኑ በጠፉበት ግብረ ሰዶም ዓለሙ ይጠፋ እንደነበር የታወቀ ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።” (ምሳ 29፥2) ብሎ ለምን ተናገረ? በጻድቃን ብዛት ሀገር እንደምትድን በተረዳ ነገር ስላወቀ አይደለምን?
☞ የጻድቃን ልመና ብቻ ሳይሆን መኖር እንኳን ከጥፋት ይታደግሃል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።” ብሎ በምሥጢረ ምጽዓት ትምህርቱ እንዳስተማረ። (ማቴ 24፥22) እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በሚገባው ቃልኪዳን ቁጣውን በምሕረት በትእግሥት እንደሚለውጥ መከራውን እንደሚያሳጥር ይህ የጌታ ቃል ምስክር ነው። ዓለም አልገባውም እንጂ ሐሳዊ መሲሕ የሚሠለጥንባቸው እነዚያ አስጨናቂ ወራት እንኳን የሚያጥሩት በጽኑ እምነታቸው በቀና ምግባራቸው እርሱን ላስደሰቱት ወዳጆቹ በገባው ቃልኪዳን ነው።
መድኅን ዓለም ክርስቶስ ሕያዋን ቅዱሳኑን "ሙታን" ለሚሉ ሰዱቃውያን “እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።” ብሎ የተናገረውን ቃል ልብ በልና ሙታን እንደሌሉን አውቀህ ወደ ሕይወት የተሻገሩበትን የዕረፍታቸውን ቀን እንደ ዳዊት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” (መዝ116፥15) እያልክ እየዘመርክ አክብር። (ማቴ 22፥31-32)
እባክዎን ቃለ እግዚአብሔርን በማጋራት ለወዳጆችዎ ያድርሱ።
ቢትወደድ ወርቁ
ሠኔ 24 ቀን 2017 ዓ ም
(ሥዕለ ተክለ ሃይማኖት በ Coptic ቤተ ክርስቲያን ሠዐሊ ዐይን)
--------------------------------
☞ ጻድቃን "አያማልዱም" የሚለውን ክርክር ተወውና የዘፍጥረትን መጽሐፍ ገልጠህ ፈጣሪህን ጠይቅ። ደጋጎች አይደለም ማልደው ለጥፋት በተዘጋጀች ከተማ ቢኖሩ እንኳን በከተማይቱ ስለመኖራቸው ብሎ ምሕረትን ያወርዳል።
☞ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን በኃጢአታቸው ምክንያት በእሳትና በዲን አቃጥሎ ከመቅጣቱ አስቀድሞ ለወዳጁ ለአብርሃም "እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው።" ካለ በኋላ "የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ።" በማለት ነገረው። ይህ ነገር በእግዚአብሔር የተነገረው አብርሃም ደጋግሞ ምን ብሎ እንደጸለየ ታስተውላለህን? "አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን?"….... ዳግመኛም "ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? "… ሦስተኛም "ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ?… አራተኛም፦ "እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ?" አለ።" ቅዱሱ ሰው አብርሃም በመጨረሻ የጸለየውን ጸሎት ልብ በል "በእነዚህ በሁለት ታላላቅ ከተሞች አሥር ጻድቃንን ብታገኝ አትምርምን?" የሚል ነው። እግዚአብሔር ምን ብሎ የመለሰ ይመስልሃል? "አምሳ ሳይሆን አሥርም ጻድቃን ባገኝ እምራለሁ!!!" (ዘፍ 18:17-25)
☞ እስቲ ልጠይቅህ ዛሬ ግብረ ሰዶማዊነት የት ደርሶዋል? በደጅህ አልደረሰምን? ለቀደሙት ስለገባው ቃልኪዳን ታግሦዋል እንጂ ሰዶማውያኑ በጠፉበት ግብረ ሰዶም ዓለሙ ይጠፋ እንደነበር የታወቀ ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል።” (ምሳ 29፥2) ብሎ ለምን ተናገረ? በጻድቃን ብዛት ሀገር እንደምትድን በተረዳ ነገር ስላወቀ አይደለምን?
☞ የጻድቃን ልመና ብቻ ሳይሆን መኖር እንኳን ከጥፋት ይታደግሃል። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ።” ብሎ በምሥጢረ ምጽዓት ትምህርቱ እንዳስተማረ። (ማቴ 24፥22) እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በሚገባው ቃልኪዳን ቁጣውን በምሕረት በትእግሥት እንደሚለውጥ መከራውን እንደሚያሳጥር ይህ የጌታ ቃል ምስክር ነው። ዓለም አልገባውም እንጂ ሐሳዊ መሲሕ የሚሠለጥንባቸው እነዚያ አስጨናቂ ወራት እንኳን የሚያጥሩት በጽኑ እምነታቸው በቀና ምግባራቸው እርሱን ላስደሰቱት ወዳጆቹ በገባው ቃልኪዳን ነው።
መድኅን ዓለም ክርስቶስ ሕያዋን ቅዱሳኑን "ሙታን" ለሚሉ ሰዱቃውያን “እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።” ብሎ የተናገረውን ቃል ልብ በልና ሙታን እንደሌሉን አውቀህ ወደ ሕይወት የተሻገሩበትን የዕረፍታቸውን ቀን እንደ ዳዊት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” (መዝ116፥15) እያልክ እየዘመርክ አክብር። (ማቴ 22፥31-32)
እባክዎን ቃለ እግዚአብሔርን በማጋራት ለወዳጆችዎ ያድርሱ።
ቢትወደድ ወርቁ
ሠኔ 24 ቀን 2017 ዓ ም
(ሥዕለ ተክለ ሃይማኖት በ Coptic ቤተ ክርስቲያን ሠዐሊ ዐይን)