ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
በዚህ ፍቅርን አውቀናልና.mp3
2.6 MB
ዓውደ ስብከት

አስተማሪ: #ልዑል እግዚአብሔር

ተናጋሪ:#ዲ/ን ኢዮኤል ዳኛቸው


ርዕስ:#በዚህ ፍቅርን አውቀናል
#ኃበ_ብዙኃን_አባታችን_አብርሃም ደግሶ ያበላቸው ዘንድ እንደ ወትሮው ይጠብቅ የነበረው ብዙ ሰዎችን ነበር።
ጸላዬ ሰናያት የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ዲያቢሎስ ግን ከመንገድ ቆሞ እራሱን በምትአት ገምሶ ደሙን አፍስሶ እያንጠባጠበ ወደ አብርሃም የሚመጡትን እንግዶች የድሮ አብርሃም ያለ መስሏችሁ ወደ አብርሃም አትሂዱ አብርሃም የድሮ ደግነቱን ትቷል።
#ይህው_እኔም እንደ ወትሮው መስሎኝ ያበላኛል ያጠጣኛል ብዬ ወደ እርሱ ብሄድ እራሴን ገምሶ ደሜን አፍሶ መለሰኝ ይላቸው ጀመር ። ሕዝቡም መቼም ደግ ሰው አይበረክትም እያሉ እያዘኑ ተመለሱ።
#ምስኪኑ_አብርሃም ግን እነርሱ መጥተው ሳይበሉማ እኔ አልበላም ብሎ ሳይበላ ፣ሳይጠጣ ከነገ ዛሬ ይመጣሉ እያለ ሦስት ቀን በተስፋ ጠበቃቸው ማንም ግን ዝር አላለም።
በሦስተኛው ቀን በቀትር ሰዓት ከድንኳኑ በር ቁጭ ብሎ ሳለ ከመምሬ የአድባር ዛፍ ሥር ሦስት ሽማግሌ ሰዎችን ተመለከተ ሰው የተራቡ አይኞቹም በደስታ ተሞሉ ሰው መቀበል የለመዱ እጆቹ ተዘረጉ እግሮቹም ወደ ፊት ሮጡ። በቀረባቸውም ጊዜ ስለ ግርማቸው ከፊታቸው ተምበርክኮ ሰገደላቸው።
#ጥቂት_ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና ። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።
አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።
#አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። የዛሬ ዓመትም ልጅ በመስጠት ወደእርሱ በረድኤት እንደሚመጡ ቃል ገብተውለት ተሰናብተውት ሄዱ ።

ሰው ብቀህ ሰው ቀርቶብ ብዙ ጊዜ ሐዝነህ ታውቅ ይሆናል ነገር ግን ሁል ጊዜ ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣልና ሰው በቀረብህ ጊዜ ደስ ይበልህ! ሰው በዲያቢሎስ የሐሰት ወሬና ምክር ከመንገድ ሊቀር ይችላል ሰው ቀረ ብለህ ግን የቀደመ ልማድህን አትተው ሳትበላ የምጠብቃቸው ከሆነ ቢመጡም ቢቀሩም ሳትበላ ጠብቃቸው እነርሱ ቢቀሩ ሥላሴ አይቀሩምና! ግን ወዳጄ ሥላሴ ሲመጡ እኔ ሥላሴ ነኝ እያሉ ላይመጡ ይችላሉ ።

#የተቀዳደደ ልብስ ለብሰው ጎልዳፉ አንደበት ይዘው አንድ ወይም ሦስት ሆነው ሊመጡ ይችላሉ ያን ጊዜ በእነርሱ ደስ ብሎህ ለሌላው የምታደርገውን ሳታጓድል አድርገህ ደስ አሰኝተህ ላካቸው እንጂ እኔ የጠራሁት ነጭ ለባሽ የመጣብኝ ብጣሽ ለባሻ ብለት ከመቀበል ወደ ኋላ አትበል። "ተርቤ አላበላህኝም፥ ተጠምቼ አላጠጣህኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበልከኝምና " ትባለለህና #ማቴ 24÷42

“ የወንድማማች መዋደድ ይኑር። #እንግዶችን_መቀበል አትርሱ፤ #በዚህ_አንዳንዶች_ሳያውቁ_መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” #ዕብ 13፥1-2
" ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣል! "
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክ ኤል ኃ ማርያም
ሐምሌ ፯/ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#ስለ_ታቦቲቱ የባዕዳኑ ምልከታ !
______________________________

( The sign and the seal /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ )
ግራሃም ሐንኰክ

ታላቁ የመጻሕፍ ቅዱስ ምሥጢር
________________________ ገጽ 3-4

#በዘመነ ኦሪት እስራኤልላዊያን የቃል ኪዳኑን ታቦት የእግዚአብሔር ማደሪያ በመሆኑ የሚያመልኩትና በምድር ላይ ያኖረው ምልክቱንና ማኀተሙን እንዲሁም የኃይሉ መገለጫ ነው ብለው ያምኑ ነበር።
አሥርቱ ቃላት የተፃፉባቸው ሁለት ክንድ ርዝማኔ አንድ ክንድ ተኩል ቁመትና ወርድ ያለው በውስጥና በውጭ በወርቅ የተለበጠ ነው ከተቀጠቀጠ ንፁህ ወርቅ የተሠሩ ሁለት ኪሩቤል አንዱ ኪሩብ በአንድ ወገን ሁለተኛው ኪሩብ በሌላ ወገን ክንፎቻቸውን ወደ ላይ ዘርግተው ወደ መክደኛው በትይዮ ሲመለከቱ የሚያሳይ ነው ።
#መጽሐፍ_ቅዱስና ሌሎችም ጥንታውያን መዛግብት እንደሚሉት ታቦተ ሕጉ በሚንቀለቀል ብርሃኑና እሳቱ በነቀርሳ በእባጭ ና በለምጽ የመምታት የማቃጠል ተራራዎችን ወደ ሜዳማነት የመለወጥ ፣ ወንዞችን የማድረቅ ታላላቅ ሠራዊትን የመደምሰስ ፣ከተማዎችን የማፈራረስ ኃይል አለው።
እነዚሁ ምንጮች አክለውም ታቦተ ሕጉ የአይሁዶች የእምነት መሠረት እንደሆነ ና ንጉሥ ሰሎሞንንም የመጀመሪያውን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም ያሠራው ይህንኑ ታቦት በክብር ለማኖር አስቦ መሆኑን ይገልጻሉ።
#ይሁንና_ከክርስቶስ_ልደት በፊት በአንድ ሺህና ስድስት መቶ ዓመታት መካከል በገበረው ጊዜ ይህ እጅግ ድንቅና ተአምራዊ ታቦት የትና ወዴት እንደሄደ ሳይታወቅ በመሠወሩ ጉዳዩ ለብዙ ሺህ ዓመታት እንቆቅልሽ ሆኖ ቆይቷል ማስረጃው እንደሚጠቁመው በ587ዓመቸ ዓለም የናቡ ከደ ነጾር ሠራዊት ኢየሩሳሌምን ባቃጠለ ጊዜ ታቦቱ በቦታው አልነበረም ።
በጦርነቱ የተማረኩት እስራኤላውያን ከባቢሎን ወደ ሀገራቸው ኢየሩሳሌም በ538ዓመተ ዓለም ተመልሰው ሁለተኛውን ቤተ መቅደስ በሠሩበት ወቅትም ታቦቱ በዚያ አልነበረም ። ይህም ቀደም ሲልታቦቱ በባቢሎናዊያን አለመዘረፉን ያረጋግጣል።
#በካሊፎርኒያ ዮኒቨርስቲ ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሪቻርድ ኤሊየት ፍሬድማን በ1987ይህን ጉዳይ አስመልክተው ሲጽፋ "የታቦቱ መጥፋት ከመጽሐፍ ቅዱስ አስደናቂው ምሥጢሮቾ እንደ አንዱ ይቆጠራል"ብለዋል።
ብሉይ ኪዳን መጻሕፍ ውስጥ እስከ ንጉሥ ሰሎሞን ዘመነ መንግሥት (970-931 ቅድመ ልደተ ክርስቶስ) ድረስ ከሁለት መቶ ጊዜ በላይ ስለ ታቦቱ ተጠቅሷል። ከዚህ ብልህና አስተዋይ መሪ ዘመነ መንግሥት በኋላ ግን ታሪኩ አንድም ጊዜ እንኳን ተነስቶ አያውቅም። ይህን የመሰለ ክቡርና ውድ ቅርስ በተለይም ደግሞ ሃይማኖታዊ ከበሬታ ያለው በብሉይ ኪዳን የኋለኞቹ መጻሕፍት ጨርሶ አለመወሳቱ የሚያስገርም ነው።
#በዚህ የተነሳ በዘመኑ የነበሩ ጸሐፍትና ቀሳውስት የዚህን ቅዱስ ቅርስ የመሰወር ምሥጢር ላለማሳወቅ ከፍተኛ የሆነ የመሸፋፈን ጥረት ያደረጉ አስመስሎባቸዋል። የተሰወሩ ቅርሳ ቅርሶችን የሚያስሱ ወገኖች የዚህን ታላቅ ቅርስት መሰወር አውቀው በርካታ ዘመቻዎችን ቢያካሂዱም አንዳቸውም አልተሳካላቸውም።
በ1981/የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/( #Raiders_of_the_Lost_Ark ) በሚል ርእስ ሐሪሰን ፎርድ እንደኢንዲያና ጆንሰ ሆና የተወነችበት የሆሊውድፊልም ውስጥ በአሜሪካና በአውሮፓ ለዕይታ ቀርቦ ነበር። እኔም 1983 ናይሮቢ ውስጥ ይህንኑ ፊልም የማየት ዕድሉ አጋጥሞኝ ነበር።
#ፊልሙን ካየው በኋላ የታቦቱን ዱካ አነፍንፌ የለማግኘት ሀሳብ አደረብኝ።ከጥቂት ወራት በኋላም ሀሳቤን ለመተግበሮ ወደ ኢትዮጵያ አመራሁኝ። ጉዞዬንም ወደ ትግራይ አቅንቼ የኢትዮጵያውያን ቅድስት ከተማ የምትባለውን አክሱምን ጎበኘሁ። በዚህ ጊዜ ነበር ጠባቂውን መነኩሴ ያገኘኋቸው።
( The sign and the seal /ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ)
በግራሃም ሐንኰክ
............... #ይቀጥላል ..........
በቀጣይ
#ታቦቲቱ በኦሪቱ_ምልከታ
#ታቦቲቱ በአዲሳት ምልከታ
#ታቦቲቱ_በኢትዮጵያውያን እምነትና መልከታ
#የአድዋ_ተራሮች ትዝብት
_____

ቲሺ ምናለ ከዚህ ንበር ትንሽ ቀቅ ብዬ በተፈጠርኩ ካድማሱ ባሻገር እንደ ሰንሰለት ከተያያዙት ከአድዋ ተራሮች በመጠኑ ተለቅ የሚለው የአንዱ ተራራ የምሬት ንግግር ነበር

#እንዴ ይህ እኮ እኛ የተፈጠርንበትን የነጻነት ጀንበር የተፈነጠቀበት የኢትዮጱያ መሬት ነው ይህን መሬት ስንቱ ተራራ ሊፈጠርበት እንደሚመኝ እረስተህው ነው ።

ሌላኛው ከግራ ያለው ተራራ ቀበል አርጎ የዓለምና የአፍሪካ ስመ ጥር ተራሮች ኤቨረስትና ኪሊማንጃሮ እራሳቸው ረጃጅሞች ስመ ጥር ተራራሮች ሆነው ከሚታወቁ ይልቅ እዚህ ቦታ ተፈጥረው የጥቁር ሕዝብ ድልን የሰውልጅ እኩልነት የነጻነት ቀንዲል መለኮሰን ዕብሪተኝነት አንገት ሲደፈ ጨዋነት ሲረታ ቢያዮና የጀግኞች የዐይን መስክር ቢሆኑ የበለጠ ደስተኛ ይሆኑ ነበር። አንተ እዚህ በመፈጠረህ ታማርራለህ

#ግዙፉ ተራራ ከመካከላቸው ሆኖ ዐይ የልጅ ነገር እሱ መቼ ጠፋኝ " ለቀባሪው አረዱት አሉ " እናንተ በዚህች ምድር ከመፈጠራችሁ በፊት እኔ ቀድሜ ነበርኩ አድዋ ጦርነት እራሱ ከእናንተ የተሻለ ቁመናና ርዝመት ያለኝ በመሆኔ ከናንተ በተሻለ የጦርነቱን ሙሉ እንቅስቃሴ ለማየት ታድያለው የአባ ነብሶ ድፍረት መድፉን ለብቻ ሲያጓራው ፣የገበየው ደረት ደልብጦ መግባት ፣የጣይቱ ብልሐት፣ የምኒልክ ጽናት የሰማዕቱ እርዳታ ሁለም እንደ ትላንትና ሆኖ በሐይኔ ሕሊናዬ ተሰሎ ተቀምጧል መቼም ልረሳው አልችልም ያቺ የኃላ ደጀን የነበረች አዝማሪ ጻድቄ እራሱ ሳትቀር ከነ ግጥሞቿና ከነ አበረታች መሰንቆዋ የዕለት ለዕለት ትዝታዬ ነች እንዲያውም አንድ ጊዜ ጠላት በአድዋ ሥላሴ በኩል ገፍቶ ሲያይል "የአድዋን ሥላሴ ጠላት አረከሰው ገበየው በሞቴ ግባና ቀድሰው " ብላ ገጥማ ነበር።
ታድያ ይህን ያክል የምታስታውሰው ከሆነ ምን ቢመር ነው ከዚህች የነጻነት ድንበር ውጪ መፈጠርን የፈለክ? ሆ ሰው እንዴት ሰው አልኩ እንዴ ተራራ እንዴት በተመረጠ መሬት በነፃነት ሀገር ተፈጥሮ ሲያበቃ ለምን በዚህ የነፃነት ሀገር ተፈጠርኩ ብሎእንዴት በከንቱ ያማርራል?
#በከንቱ_አይደለም ማማረሬ እውነት ይዤ እንጂ ። በግራና በቀኝ ያሉት በመጠናቸው አነስ የሚሉት ተራሮች በተመሳሳይ ሰዓትና ቃል ማለት አልገባንም? አሉ።

ከመካከላቸው መሆኑ እንደፈለጉ ጥያቄ እየጠየቁ እንደ ገና ዳቦ በጥያቄ ሊጠብሱት የተዘጋጁ አስመስሏቸዋል። ከዛ አንደኛው ተራራ ከአድመኝነት መንፈስ ወጣ ለማለት ብሎ ሀሳቡን ለመረዳት ትንሽ ፋታ ከወሰደ በኋላ እስቲ በል ንገረን ምንድነው ይህን ያክል ቁጭት አሳድሮ የተፈጠርክበትን የነፃነት ምድር ለመጸየፍ ያበቃህ? ሲል በእርጋታ ጠየቀው
እሳት አመድ ወልዶ ሳይ እንዴት የቁጭት ቆፈን አይውረሰኝ? በዕድሜ አንጋፈ አዛውንት የሚመስለው ተራራ ሳግ እየተናነቀው እንዳይታወቅበት ጉረሮውን እያጸዳ ቀስ ብሎ ቁጭቱን ሊያስረዳቸው ጀመር።
#በዚህ ቦታ በኖርኩበት በእስኳሁኑ ዕድሜ እንዲህ ዐይነት ውርደትና መሸማቀቅ ደርሶብኝ አያውቅም ። ጥንት ኢትዮጵያዊያን አርበኞች ጠላትን በዚህ ሥፈራ ድል ሲነሱ ለ ሀገር ለድንበር ለሃይማኖት ለአንድነት ለአንድ ሕዝብ ብለው ዋጋ ፍለው ደም አፍስሰው ሥጋ ቆርሰው አጥንት ገብረው ባለፉበት በዚሁ ሥፍራ በገደሉበት ሥፍራ ሲገዳደሉ ነጻ በወጡበት ሰፈር ምርኮ ሲገቡ ድል በነሱበት ሀገር ድል ሲነሳሱ ከማየት ሌላ ምን ውርደት አለ? የዘንድሮስ አድዋ ፋሽሽት ኢጣሊያንን ወይስ የእናት ልጅ ወንድምን ድን የነሳንበት በዓል ነው ብለው ሊያከብሩት ነው ?

የጀግኖች ደም ዋጋ ቢስ ሲሆን ከማየት ሌላ ምን አስቆጪ ነገርስ ይኖራል ? እነሱስ አንዴ ለሀገር ለድንበር ለነፃነትና ለሃይማኖት የሚገባቸውን ዋጋ ከፍለው በክብር አርፈዋል ይብላኝ እንጂ ለኔ ሞት ወስዶ ለማይገላግለኝ ግዑዝ ነው ይሉኛል ምንም የማይሰማኝ ንግግሬን ማድመጥ ያልቻሉ እነሱ መሆናቸው ማን በነሱ ቋንቋ በነገረልኝ

#ያኔ ቋንቋ ብሔር ዘር ሳይለያቸው እንደ አንድ ልብ መካሪ አንደ አንድ ቃል ተናጋረ ሆነው ጠላትን ያስጨነቁ ዛሬ ብሔሬ ቋንቋዬ ተባብለው ሲተላለቁ በዚሁ ሥፍራ ሳይ ለምን አልበግን

ደሞኮ ቋንቋውም ቢሆን በቅጡ የአባቶቻቸውን ቋንቋ አቀላጥፈው አያውቁትም ሁሉም ባለ ቋንቋ ነኝ ባይ ከእንግሊዘኛ ሳያዳቅል ማን በቅጡ የሚናገራቸው አለ እስቲ ቆንጆ ኦሮምኛ ተናጋሪ አምጡልኝ እስቲ ንጹሑ አማርኛ አንደበት ያለው ፈልጉልኝ እስቲ ትግርኛን አቀላጥፎ የሚያወራ የሰሜን ሰው ፈልጉልን የለም አታገኙም ። ለመጠፋፋትና ለመገዳደል ሲሆን ግን ብሔሬ ቋንቋዬ ይባልልኛል አስቀድመህ በቅጡ ውረስወ እስቲ ።

#ሁለቱ ተራሮች ምንም ሊመልሱለት አልቻሉም ከልብ ያልኖረ እውነት ከየት ይገለጣል።

እሱማ እውነትህን ነው በሚል በተጸጸተ አስተያየት ከግራም ከቀኝም ተመለከቱት

የላሊበላ መቅደስ ሰሪዎች እናንተ አይደላችሁም ቢሆንማ ኖሮ ሌላም አስደማሚ የኪነ ሕንጻ አብዝታችሁ ሰርታችሁ ከድኅነት አረንቋ በወጣችሁ ነበር የሚሉን የቀደመ ሥልጣኔያችንን ሊያስክዱን የሚዳዱ የነጭ እባቦች ከንፈር አደዋም የናንተ የኢትዮጵያዊያዊያን ድል አይደለም ቢሆንማ ዛሬ አንድነታችሁን ምን ፈታው መተባበራችሁን ማን ወሰደው ቢሉን ምን እንመልስ ይሆን?
በዚህ የመበላላት መንፈስ ውስጥ ሆነን የአፍሪካዊያን የነፃነት ቀንዲል የተለኮሰው ከዚህ ሀገር በነዚህ ተራሮች ሥር ነው ቢባል ማን ያምናል?

#አንዱ ወጣት እግር የሆነ ተራራ ይህማ አይሆንም እኔ አንደበት አውጥቼ እንደ ቢታንያ ድንጋይ አድዋ የኢትዮጵያዊያን ድል ነው ስል ጮክ ብዬ እመሰክራለዋ ሲል ሌላላው ቀበል አርጎ አዎ እኔም ዝም አልልም አድዋ ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ የጥቁር ሕዝበ ሁሉ ድል ነው ሲል አሳቡን ተጋራው
አንጋፈው ተራራ ግን ከሰማይ ደመናትን ሰብስቦ እንደ ጋቢ ተከናንቦ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚል በሽሙጥ ተከናነበ ቀጠል አርጎም አንድነቱና ህብረቱ እንዲመጣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ካልጣረ እመሆኝ ወደፊት እኔ እንዳልኳችሁ ሳይሆን አይቀርም በርግጥ ሁሉም ነገር ከትምህት ቤት መማር አይቻልም የዕድሜ ባለ ፀጋ ሲነግራችሁ ግን እህ ብላችሁ ብሰሙ መልካም ነው ዕድሜ እዚህች ዮኒቨርስ ላይ ያልተገነባና የማይገነባ ትልቅ ዮኒቨርስቲ ነው ።

እናንተ ይህ ትላላችሁ አክሱም፣ ጀጎል፣ አባይ ፣ጣና ሁሉ ሳይቀር ከሀገር ሊወጡ ሲሉ አገኘዋቸውና ስለምን ይህችን ምድር ለቃችሁ ትወጣላችሁ ስል ሞገትኳቸው ሲሉ የነበሩ ኢትዮጵያ አብጠርጥረው ያውቋታል የሚባሉ ለምድ የከበዱ ሰዎች እንኳ ሳይቀሩ ዛሬ መሀመድ ግራኝ ወራሪአይደለም ሲሉ እየተደመጡ ነው ተደምጠዋል ምን ያርጉ ሥልጣን ወደ ሐሰት ዘወረቻቸው ። ታድያ ግራኝ ወራሪ ካልሆነ አርበኛ ነውንን? አምባ ሳደር ነውን? ወይ ብሔራዊ ጀግናችን ነው? በዚህ ዓይነትኮ ወደፊት ዐውልት ይቁምለት መንገድ ይሰየምለት መባሉ አይቀሬ ነው ። በዕድሜ የምታንሱኝ ልጆቼና ወንድሞቼ ይህ አበክራችሁ ስሙኝ በልባችሁም ጽላት ጽፋችሁ አኑሩት እውነት ሁል ጊዜም እውነት ነች ለማቻቻልና ሚዛን ለመጠበቅ አልያም ዲሞክራት ለመሆን ብለህ ልትሸፉፍናት መልኳን አጥፍተህ ልታጠይማት አትችልም ። መሀመድ ግራኝ ሀገር ያፈረሰ ሃይማኖት ያጠፈ ወራሪ ነው። ግራኝ ወራሪ አይደለም ካልን 11 ሚሊየን አይሁዳዊያንን በዘራቸው ምክንያት የጨፈጨፋቸው ኢትለር ቅዱስ ነው ሀገሩም ከደጋጎቹ ሀገር ከመንግሥተ ሠማይ ነው ማለት ነው
#ኃበ_ብዙኃን_አባታችን_አብርሃም ደግሶ ያበላቸው ዘንድ እንደ ወትሮው ይጠብቅ የነበረው ብዙ ሰዎችን ነበር።
ጸላዬ ሰናያት የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ዲያቢሎስ ግን ከመንገድ ቆሞ እራሱን በምትአት ገምሶ ደሙን አፍስሶ እያንጠባጠበ ወደ አብርሃም የሚመጡትን እንግዶች የድሮ አብርሃም ያለ መስሏችሁ ወደ አብርሃም አትሂዱ አብርሃም የድሮ ደግነቱን ትቷል።
#ይህው_እኔም እንደ ወትሮው መስሎኝ ያበላኛል ያጠጣኛል ብዬ ወደ እርሱ ብሄድ እራሴን ገምሶ ደሜን አፍሶ መለሰኝ ይላቸው ጀመር ። ሕዝቡም መቼም ደግ ሰው አይበረክትም እያሉ እያዘኑ ተመለሱ።
#ምስኪኑ_አብርሃም ግን እነርሱ መጥተው ሳይበሉማ እኔ አልበላም ብሎ ሳይበላ ፣ሳይጠጣ ከነገ ዛሬ ይመጣሉ እያለ ሦስት ቀን በተስፋ ጠበቃቸው ማንም ግን ዝር አላለም።
በሦስተኛው ቀን በቀትር ሰዓት ከድንኳኑ በር ቁጭ ብሎ ሳለ ከመምሬ የአድባር ዛፍ ሥር ሦስት ሽማግሌ ሰዎችን ተመለከተ ሰው የተራቡ አይኞቹም በደስታ ተሞሉ ሰው መቀበል የለመዱ እጆቹ ተዘረጉ እግሮቹም ወደ ፊት ሮጡ። በቀረባቸውም ጊዜ ስለ ግርማቸው ከፊታቸው ተምበርክኮ ሰገደላቸው።
#ጥቂት_ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና ። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።
አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።
#አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። የዛሬ ዓመትም ልጅ በመስጠት ወደእርሱ በረድኤት እንደሚመጡ ቃል ገብተውለት ተሰናብተውት ሄዱ ።

ሰው ብቀህ ሰው ቀርቶብ ብዙ ጊዜ ሐዝነህ ታውቅ ይሆናል ነገር ግን ሁል ጊዜ ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣልና ሰው በቀረብህ ጊዜ ደስ ይበልህ! ሰው በዲያቢሎስ የሐሰት ወሬና ምክር ከመንገድ ሊቀር ይችላል ሰው ቀረ ብለህ ግን የቀደመ ልማድህን አትተው ሳትበላ የምጠብቃቸው ከሆነ ቢመጡም ቢቀሩም ሳትበላ ጠብቃቸው እነርሱ ቢቀሩ ሥላሴ አይቀሩምና! ግን ወዳጄ ሥላሴ ሲመጡ እኔ ሥላሴ ነኝ እያሉ ላይመጡ ይችላሉ ።

#የተቀዳደደ ልብስ ለብሰው ጎልዳፉ አንደበት ይዘው አንድ ወይም ሦስት ሆነው ሊመጡ ይችላሉ ያን ጊዜ በእነርሱ ደስ ብሎህ ለሌላው የምታደርገውን ሳታጓድል አድርገህ ደስ አሰኝተህ ላካቸው እንጂ እኔ የጠራሁት ነጭ ለባሽ የመጣብኝ ብጣሽ ለባሻ ብለት ከመቀበል ወደ ኋላ አትበል። "ተርቤ አላበላህኝም፥ ተጠምቼ አላጠጣህኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበልከኝምና " ትባለለህና #ማቴ 24÷42

“ የወንድማማች መዋደድ ይኑር። #እንግዶችን_መቀበል አትርሱ፤ #በዚህ_አንዳንዶች_ሳያውቁ_መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።” #ዕብ 13፥1-2
" ሰው ሲቀር እግዚአብሔር ይመጣል! "
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክ ኤል ኃ ማርያም
ሐምሌ ፯/ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
"ዕርገተ ክርስቶስ"

#ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ፤ዘምሩ ለአምላካችን ዘምሩ፤ዘምሩ ለንጉሣችን ዘምሩ"(መዝ46:5) በማለት ጌታው ሲሆን ልጁ ልጁ ሲሆን ጌታው ስለሚሆን ስለ ኢየሱስ ክርሰቶስ ትንቢት ተናግሯል።

#በዚህ ኃይለ ቃል ያለው ምሥጢረ ተዋሕዶ ምንድን ነው? ቢሉ "አምላክ" ብሎ አምላክነቱን "ዐረገ" ብሎ ሰውነቱን ያስረዳል።ማረግ (ከፍ ከፍ ማለት፣ወደ ሰማይ መውጣት) የሚስማማው ሥጋ ነውና በተዋሕደው "ሥጋ ማርያም" በሁሉ ላለ "ቃል ለሚባል እግዚአብሔር" ዕርገት ተነገረለት።

#ነገሩን ትንሽ ለመግለጥ ያህል፦አምላክ በሁሉ ቦታ (በምልዐት) የሚገኝ ስለሆነ ከዚህ ተነሥቶ እዚያ ደረሰ አይባልም።አምላክ በተዋሕዶ ሰው ሲሆን ግን ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር ለእኛ የሚነገረው ሁሉ ለእርሱም ተነገረለት።ተፀነሰ፣ተወለደ፣ተሰደደ፣ተጠመቀ፣ተሰቀለ፣ሞተ፣ተቀበረ፣ተነሣ፣ዐረገ ተባለለት።ይህ ሁሉ ግን በበጎ ፈቃዱ የተከናወነ ነው ፤ እንደኛ ግዳጅ ያለበት አይደለም።

#ክርስትና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን የእግር አሻራ የመከተል ሕይወት ነውና እርሱ ስለኛ የፈጸማቸውን ሁሉ እንፈጽማለን።ኋላም እርሱ በኃይሉና በሥልጣኑ ተነሥቶ እንዳረገ እንዲሁ እኛንም አስነሥቶ ያሳርገናል።ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ "እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ" ማለቱም ለዚህ ነው።

#ወደ እኔ እወስዳችኋለሁ ብሎ ጌታችን የነገረን ቃል እኔን በመመሰል እንድታድጉ (Theosis:ሱታፌ አምላክ) አደርጋችኋለሁ ሲል ነው።ይኸውም በመንግሥተ ሰማያት የምንኖረው ኑሮ "ዕርገታዊ" (ከፍ ከፍ የማለት) እንደሆነ ያስረዳል።ከቅዱሳን መላእክቱ ጋር "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" በማለት ውስጥ እየተቀደስን በጸጋ ላይ ጸጋ በክብር ላይ ክብር በጣዕም ላይ ጣዕም እየተጨመረልን እግዚአብሔርን እየመሰልን ከፍ እንላለን።

ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን አሜን!!!