ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
"ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ"
#ውዳሴ_ማርያም ዘ አርብ

የውዳሴ ማርያም ጸአፊ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ ቢሆንም ቅሉ ደራሲው ግን መንፈስ ቅዱስ ነው። ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት ሊቁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ " ሲል አራቆ ጽፏል ።

አዎን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሰላል ነች ። በመሠላል እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እላይ ያለውም ወደታች ይወርድበታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የምድራዊ ሰዎችን ጸሎትና ልመና ወደ ሰማይ አባታቸው ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ታደርሳለች ታሳርጋለች የእግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረትን ደግሞ ወደ ሰው ልጆች ታወርዳለት ፣ታመጣለችና አማናዊት መሰላል ነች። ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማህሌተ ጽጌው "አልቦ ጸሎት  ወአልቦ ትንባሌ እንበሌከ ማርያም የዓአርግ ሉዓሌ" ድንግል ማርያም ሆይ ያላንቺ አማላጅነት ወደ ሰማይ የሚያርግ ጸሎትና ልመና የለም"  እንዳለ

ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ስለ ጌታችን ዕርገት ሲናገር እንዲ ይላል "እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። " #ሉቃ 24÷50

ዕርገቱም እንደ ኤልያስ በሠረገላ እንደ ሄኖክም በመሰወር እንደ ሕዝራም ሱቱኤል በመላእክት እገዛ የሆነ አይደለም ። ደመና ከዐይናቸው ሰውራ እስክትቀበለው ድረስ ከፍ ከፍ አለ እንጂ አልጠፋባቸውም ሰማይን አተኩረው እስኪመለከቱ ድረስ የሰማይ መላእክትም እንኪገስጾቸው ድረስ በተመስጦ ሆነው ሲያርግ አዮት እንጂ አረቀቀባቸውም በሰው አምሮ በሚረዳና በሚገባ መልኩ በርዕቀት ከነርሱ ተለይቶ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ። " እናንት የገሊላ ሰዎች እንዲህ አተኩራችሁ ወደ ሰማይ የምትመለከቱት ስለምንድነው እንዲሁ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ደግሞ ይመጣልና " #ሐዋ 1÷11

መሰላል ሁለት ትይይዮ የሆኑ ቋሚ ዘንጎች ያሉት ሲሆን በመካከላቸውም በየተወሰነ ርቀቱ በተደረደሩ አግዳሚ ዘንጎች ሁለቱ ትይዮ ዘንጎች የተጋጠሙ ናቸው ::

ሁለቱ ትይዮ የሆኑ ረጃችም ዘንጎች በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን (ድንግል በክሌ) ያመሰጥራሉ። አንድም ብሉይና ሐዲስን ሲወክሉ በመካከላቸው ያሉ ርብራብ ዘንጎች ደግሞ የብሉይና የሐዲስ መገናኛው ድልድይ እመቤታችን መሆኟን ያስረዳሉ በቡሉይ መጨረሻ በሐዲስ መጀመሪያ ተገኝታለችን አንድም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለ ፈራጅ የሆነ ንጉሥ ሰው ሲሆን አምላክ አምላክ ሲሆን ደግሞ ሰው የሆነውን መካከለኛ ትወልደዋለችና። አንድም የጠቡ ግድግዳ የፈረሰባት ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ የታረቁባት የተቀራረቡባት የዕርቅ ሰነድ እመቤታችን ነችና መሰላል የእመቤታችን ምሳሌ ነው።
በመጻሕፍ ቅዱስ ላይም ይህ ነገር የጎላ የተረዳ ነው::..." ያዕቆብም ከቤርሳቤህ ወጥቶ ወደ ካራን ሄደ። ወደ አንድ ስፍራም ደረሰ፥ ፀሐይም ጠልቃ ነበርና ከዚያ አደረ፤ በዚያም ስፍራ ድንጋይ አነሣ፥ ከራሱም በታች ተንተርሶ በዚያ ስፍራ ተኛ። ሕልምም አለመ፤ #እነሆም_መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም_የእግዚአብሔር_መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። እነሆም፥# እግዚአብሔር በላይ ቆሞበት ነበር፥ #ዘፍ 28÷10-13


ታድያ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ አንቺ ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ሲል ግን እንደ መሰላል ተረግጧት ወጣ ማለት አይደለም የወጣው ወደ ሰማይ ነው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቁመትም እንደ ሰው ሁሉ ሦስት ክንድ ከስንዝር ብቻ ነው ።

በምሥጢር ሊናገር የፈለገው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም ነፍስን ባይነሳ ኖሮ ለመለኮት ወደ ሰማይ ዐረገ የሚልል ነገር ባልተነገረለት ነበር የሥጋን ገንዘብ ገንዘቡ ስላደረገ ውጣ ፣ከፍ ፣ከፍ አለ ዐረገ የሚሉት ነገሮች ተነገረለት ። ቅዱስ ኤፍሬም ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ብቻ ይበል እንጂ ቅሉ እመቤታችንስ ለቃል ከሰማይ ወደ ምድር ለመውረድም መሰላል ሆናዋለች። ድንግል ማርያም ባትኖር ኖሮ ከማን ሰው ይሆን ነበር? መንክር ኦ ዝ ምሥጢር!

እንዲያውም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕርገቱንና ሰው የመሆኑን ምሥጢር ሲያወዳጁ እንዲ ይላሉ"የቃል ርደት በማኅጸን የሥጋ ዕርገት በአርባ ቀን"

ምን ማለታቸው ነው ቢሉ ለቃል ርደትም ለሥጋ ዕርገትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ መሰላል ሆና ለች ያለ እመቤታችን የቃል ርደት (መውረድ) ሆነ የሥጋ ዕርገት አይታሰብምና ነው።

ክቡር ዳዊትም ይህን የሊቁን ሀሳብ የቅዱስ ኤፍሬምን ሀሳብ ሲደግፍ እንዲ ይላል። “ #በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ #ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል።” #መዝ (68) 68፥33 በምሥራቅ በኩል ማለቱ አቅጣጫን ብቻ የሚጠቁም ሳይሆን ከምሥራቅ ፀሐይ እንደሚወጣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምም ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወጣልና እመቤታችን #ምሥራቀ_ምሥራቃት_ሞጻ_ፀሐይ ትባላለችና ፀሐይ ክርስቶስ የወጣባት ምሥራቃዊ መሠላል እርሷ ነች ። መለኮት በሁሉ የመላ ፣ በሁሉ ያለ ነው የሌለበት ቦታ የለም በዚህ አለ በዚያ የለም አይባልለትም # መዝ 138 (139)÷7-10 ነገር ግን የምሥራቅ የእመቤታችንን ሥጋና ነፍስ በመዋሕዱ ግን ከምድር ወደ ሰማይ ሄደ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ተባለለት ። መለኮት ዐረገ እንዲባል ምክንያትቱ ምሥራቁ ሆነችው ።

የነዚህ የዳዊትና የኤፍሬም የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ምን ይረቅ?
__ #ለምን_ዐረገ ? ___
#ትንቢቱን_ለመፈጸም :-"አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ። #መዝ46(47)÷5-6 ነቢዮ ዳዊት ይህን የተናገረው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከአንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ ነው።
#ሥፍራን_ለማዘጋጀት :- መግሥተ ሠማያት ቀድማ ያልተዘጋጀች አሁን ሄዶ የሚያዘጋጃት ሆና ሳይሆን ለእናንተ ለአባቴ ብሩካኖች የተገባች ሆና በመጨረሻው ቀን ተገልጣ እንድትሰጣችሁ የማደርግ እኔ ነኝ አሁን ሄጄ በአባቴ ዕሪና (ትክክል ) በአብ ቀኝ በክብሩ ዙፋን ልቀመጥ ይገባኛል ሲል ነው “በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” #ዮሐንስ 14፥2
#መንፈስ_ቅዱስን_ለመላክ :- “እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።” #ዮሐንስ 16፥7

አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ ፫ቀን / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
በአባ ገብረ ኪዳን ግርማ መጋቢ ሐዲሳት ወብሉያት
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
የአፎምያ ጥያቄ የባሕራን መልስ
#ቅዱስ_ሚካኤል
____________________

እርግብ የምታገባው አንድ ብቻ ነው። ቢሞት እንኳን ሌላ መጥቶ እንዳይተናኮላት ምላሷን ትሰነጥቃለች። ድንገት ቢመጣባት በደንብ መጮህ እንድትችል እና ሌሎች መጥተው ደርሰውላት እንዲያባርሩላት ነው። ቅድስት አፎምያም እንደ እርግ የምትኖር ደገኛ ሴት ነበረች።

የኬልቅያ መስፍን የነበረው የምትወደው ባሏ አስተራኒቆስ በሞት ከተለያት በኋላ በዕውቅ አስሎ የሰጣትን የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ይዛ በጾም በጸሎት ተስና ስትኖር ጸላዬ ሰናያት የመልካም ነገሮች ሁሉ ጠላት የሆነ ሰይጣን ዲያቢሎስ ደግ መነኩሴ መስሎ መቶ ጾም ጸሎት እንድትተው ሌላ ባል አግብታ ተድላ ደስታ እንድታደርግ መከራት እርሷ ግን አባ አለባበሶት ደግ ነበር ንግግሮት ግን የከፋ ነው። ጾም ፣ጸሎት ና ምጽዋት ደገኛ ሥርዓት አይደሉምን? ስለምንስ ዳግመኛ እንዳገባ ይመክሩኛል በሉ ከኔ ወግዱልኝ ብላ አሳፍረችው። ይህን ግዜ የደበቀውን ሰይጣናዊ ግብር ገልጦ ቆቡን ጥሎ ከቁራ ሰባት ጅ ጠቆረ ሰኔ አሥራሁለት ቀን ተመልሼ እመጣለሁ አጠፋሻለሁም ብሎ ዝቶባት እንደ ጢስ ተኞ እንደ ትብያ ተኖ ጠፍቶ ሄደ ።

ሰይጣን ዲያቢሎስ እንዳለሁም ግብሩን ለውጦ በሰኔ አሥራ ሁለት ቀንም የመላእከት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን መስሎ ባማረና በተዋበ ልብስ ወደ ቤቷ መጥቶ ተገለጠላት “ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።” ተብሎ እንደተጻፈ 2ኛ ቆሮ 11፥14

ቤቴን በብርሃንህ የሞላህ አንተ ማነህ ? አለችሁ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ይህ ከብርሃኔ ተረጂ አላት ቆየኝ መጣው ብላ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጂ የነበረው ባሏ አስተራኒቆስ አስሎ ነሰጣትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕለ አድህኖ ይዛ መጣች ። እያመሳሰለችሽ ንጉሥ ለጭፍሮቹ መታወቂያ ማኅተቡን አትሞ አስይዞ ይልካቸዋል የእግዚአብሔር መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ከሆንክ ማዕተመ መስቀልህ የንጉሥህ መታወቂያ በትረ መስቀልህ የታለ ?አለችሁ። እርሱም ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና እኛ በእግዚአብሔር ፊት የምንቆም መላእክት መስቀል መያዝ ለምናችን ጨርሶ አያስፈልገንም አላት ይህን ጊዜ አንተማ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል አይደለህም አላምንህም አለችሁ ያን ጊዜ እንዳ ወቀችበት ሲረዳ ግብሩ ቀይሮ በብርሃን የመላው ቤቷን በጽልመት መላው ቀንዱ በቀለ ፣ጥፍሩ እረዘረዘ፣ ዐይኑ ፈጠጠ ፣ጥርሱ ገጠጠ አንቺንስ ካላጠፋሁ ሠላሜን አላገኝም ብሎ ተወርውሮም አንቆ ያዛት ቅድስት እናት አፎምያም እውነተኛው ታላቁ መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እርዳኝ ብላ በጣር ውስጥ ሆና ተጣራች እውነተኛው የእግዚአብሔር መላእክም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጣና ዲያቢሎስን ረግጦ ያስጨንቀው ገባ ሰይጣንም ሚካኤል ሆይ ጊዜዬ ሳይደርስ እንዳታጠፋኝ በፈጣሪህ እለምንሃለው እያለ ጮኸ ቅዱስ ሚካኤልም ለቀቀው በኖ ተኖ ጠፋ ቅድስት እናት አፎምያንንም ያረጋጋት ጀመር ። “ #የእግዚአብሔር_መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” እዳለ መጻሕፍ #መዝ (33) 34፥7


*አንባቢ ሆይ አንተስ በክርስቶስ ክርስቲያን ነኝ ትላለህንን እንግዲያውስ መስቀልህ የታል?
*አንባቢት ሆይ የንጉሥሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ትያለሽን? መልካም ትያለሽ ግን የንጉሡ ደመ ማዕተብ በትረ መስቀልሽ ከወዴት አለ? የአፎምያ ጥያቄ ይህ ነበር መስቀልህ የታለህ? ለአፎምያ ትክለኛ ጥያቄ መልስ የሆናት እውነተኛው ቅዱስ ሚካዬል በትረ መስቀሉን ጨብጦ ይዞ በመታየት ነው።ወዳጄ የድልህ ዐርማ የሆነውም " ሁልጊዜ በልብህ አኑረው፥ በአንገትህም እሰረው። ስትሄድም ይመራሃል፤ ስትተኛ ይጠብቅሃል፤ ስትነሣ ያነጋግርሃል። " #ምሳ 6÷21-22 የደሃ አደጊቱ ልጅ ባሕራንም የሞት ደብዳቤውን ተቀብሎ የደስታ የፍስሐ የሰርግ ደብዳቤ አድርጎ የመለሰለት የደስታ ሁሉ መልስ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ዕለት በነገዱ ሁሉ ላይ የተሾመበት የሹመቱ በዓል ነው!

መንፈስ ቅዱስ ያወቀውን ሰይጣን የሸመቀው ከጠላት የተንኮል እንቆቅልሽ ሁሉ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የደስታ መልስ ይሁንልን!

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
ሰኔ ፲፪ ቀን /፳፻፲፫ ዓ.ም
" #በመንፈስ_ቅዱስም እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ #ከአብ የሠረጸ ፤ #ከአብና_ከወልድ ጋር በአንድነት እስግድለታለን እናመሰግነዋለን "
______ #ጸሎተ_ሃይማኖት ____

#የእግዚአብሔር_መንፈስ ፈጠረኝ፥ ሁሉንም የሚችል #የአምላክ_እስትንፋስ ሕይወት ሰጠኝ።”
#ኢዮብ 33፥4
ዐውደ ምሕረት
Photo
#እንኳን_ደስ አሎት ! #ሙሐዘ_ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት !

#በነጋውም ንጉሡ ማልዶ ተነሣ፥ ፈጥኖም ወደ አንበሶች ጕድጓድ ሄደ።

ወደ ጕድጓዱም ወደ ዳንኤል በቀረበ ጊዜ በኀዘን ቃል ጠራው፤ ንጉሡም ተናገረ ዳንኤልንም፦ የሕያው አምላክ ባሪያ ዳንኤል ሆይ፥ #ሁልጊዜ_የምታመልከው_አምላክህ_ከአንበሶች_ያድንህ_ዘንድ ችሎአልን? አለው።

#ዳንኤልም ንጉሡን፦ ንጉሥ ሆይ፥ ሺህ ዓመት ንገሥ። በፊቱ ቅንነት ተገኝቶብኛልና፥ በአንተም ፊት ደግሞ፥ ንጉሥ ሆይ፥ አልበደልሁምና #አምላኬ_መልአኩን_ልኮ_የአንበሶችን_አፍ_ዘጋ እነርሱም #አልጐዱኝም አለው።
___ #ት.ዳን 6÷19-22_____
#ወንድማማችነት_በመጽሐፍ_ቅዱስ
___________________________

በወንዶች ወገን መናገር የመጽሐፍ ቅዱስ ልማዱ ሆኖ ነው እንጂ ወንድማማችነት በሚለው እርዕስ ውስጥ እህታማችነት የሚል ሀሳብም እንዳለው ልብ ማለት ይገባል ።
መጽሐፍ ቅዱስ ወንድሞች ሆይ እያለ ሲናገር እህቶች ሆይ ማለቱ ጭምር እንደሆነ በአንጻሩ መረዳት አለብን። ጾታና ከአገልግሎት ድርሻ ውጪህ ያሉ ነገሮች ላይ መጻሕፍ ቅዱስ ጠቅለል አድርጎ ወንድሞች የሚለውን መጠሪያ ይጠቀማል ሴት ከወንድ ጎን ተገኝታለችና ውክልናው ለእርሷም ጭምር ነው ። እንዲያውም #እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን ከፈጠራቸው በኃላ ሁለቱንም አዳም ብሎ ይጠራቸው እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል “ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፥ ባረካቸውም። ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን #አዳም ብሎ ጠራቸው።” #ዘፍጥረት 5፥2 ስለዚህ ወንድማማችነት በመጽሐፍ ቅዱስ ሲባል እህታማችነት በመጽሐፍ ቅዱስ ማለት ጭምር ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ወንድም ወይም እህት የሚለውን መጠሪያ ለማግኘት የግድ የእናትና የአባት ወይም የአንዱ ብቻ ልጅ መሆን አያስፈልግም። መጽሐፍ ቅዱስ በተለየ ሁኔታ የሚቀራረቡ ሰዎችን ወንድማማቾች ወይም እህታማቶች እያለ ይጠራቸዋል።በቤተሰብ አንድ የሆኑ ሰዎች ወንድማማቾች መባላቸው ግልጽ ስለሆነ እርሱን ለጊዜው እናቆየዋለን።

#ባልንጀራ_ወንድም
_____________
መጽሐፍ ቅዱስ የቅርብ ወዳጅ የሆኑ ጓደኛማቾችን ወንድማማቾች ብሎ ይጠራቸዋል። ቅዱስ ዳዊትና የሳዖል ልጅ ዮናታን እጅግ በጣም ይወደዱ የነበሩ ባልንጀሮች ነበሩ ነገር ግን አንዳቸው ላንዳቸው ወንድሜ እየተባባሉ ነበር የሚጠራሩት። ለምሳሌ ዮናታን በሞተ ግዜ ዳዊት ሞሾ እያወጣ ሲያለቅስለት “ #ወንድሜ_ዮናታን_ሆይ ፥ እኔ ስለ አንተ እጨነቃለሁ፤ በእኔ ዘንድ ውድህ እጅግ የተለየ ነበረ፤ #ከሴት_ፍቅር_ይልቅ_ፍቅርህ_ለእኔ_ግሩም ነበረ።” #2ሳሙ 1፥26 ከዚህም የምንረዳው እጅግ የሚዋደዱ፣ የሚቀራረቡ ፣በደጉም ፣በክፉሁም ጊዜ የማይለያዮ ጓደኛማቾች ወንድማማቾች ተብለው ሊጠሩ እንደሚችሉ ነው።

ጓደኛ ማለት በራሱ ላላ አድርገን ስናነበው ጓ..ደ...ኛ... ጓዳ ከቤት በውስጥ እንደሚገኝ ጓደኛም የቤተ ልቡናችን ጓዳ ዘልቆ ገበናችንን የሚያውቅ የውስጥ ሰው ማለት ነው። ዘመናችን ከፋና አሁን አሁን ጓደኛ ጠፍቶ ጉደኛ በዛ እንጂ ይህ ጓደኛ ከእናት ልጅ ወንድም እኩል አንዳንዴም በልጦ ሊገኝ ይችላል።

#የዘመድ_ልጅ_ወንድም
________________
በእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት በቅዱስ ሚካኢል ተራዳኢነን ሙሴ ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ባሕረ ኤርትራን አሻግሮ ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲጓዝ የኤዶምያስ ንጉሥ በሰላም እንዲያሳልፋቸው መልእክት ሲልክ " #ወንድምህ_እስራኤል እንዲህ ይላል " ሲል መልክቱን ጀምሯል #ዘኁ20÷14 ከግብጽ የወጡት እስራኤላውያን ወይም እነ ሙሴ ለኤዶምና ለኤዶማውያን አንዴት ወንድም ሊሆኑ ይችላሉ? ሊባል ይችላል ምክንያቱም ሙሴና ኤዶምያስ የአንድ እናትና አባት ልጆች አይደሉምና። ነገሩ እንዲህ ነው ኤዶም የኤሳው ሌላኛው ስሙ ነው ኤሳውና ያዕቆብ ደግሞ የአንድ እናት ተከታታይ ልጆች ናቸው ።ያዕቆብ ደግሞ እግዚአብሔር እስራኤል ብሎ የጠራው ዘሮቹም እስራኤላውያን ተብለው በስሙየተጠሩለት ሰው ነው። #ዘፍ 36÷1
ስለሆነም ሙሴ ኤዶምያስ በተባለው በዔሳው እና እስራኤል በተባለው በያዕቆብ መካከል ያለውን ዝምድና አምጥቶ መናገሩ ነው።

#የነገድ_ልጅ_ወንድም
_______________
ንጉሥ ዳዊት ለካህናቱ ለሳዶቅና ለአብያታር መልዕክት ሲልክ "ለይሁዳ ሽማግሌዎች እንዲ ብላችሁ ተናገሯቸው የእስራኤል ሁሉ ነገር ወደ ንጉሡ ደርሷልና ንጉሡን ወደ ቤቱ ከመመለስ ስለምን ዘገያችሁ እናንተ ወንድሞቼ የአጥንቴ ፍላጭ ና የሥጋዬ ቁራጭ ናችሁ" 2ሳሙ 19÷11 በንግግሩ ንጉሥ ዳዊት የይሁዳ ሽማግሌዎችን ወንድሞቼ ብሎ የጠራቸው እርሱ ከ12ቱ ነገደ እስራኤል የይሁዳ ልጅ ስለሆነና በነገድ አንድ ስለሆኑ ነው እንጂ ከአንድ እናትና አባት ስለተወለዱ አይደለም።

#የሀገር_ልጅ_ወንድም
_______________
የአንድ ሀገር ልጆችን ወይም የሀንድ ሀገር ዜግነት ያላቸው ሰዎች ወንድማማቾች ተብለው ይጠራሉ። "ሙሴ ጎበዝ በሆነ ጊዜ ወደ #ወንድሞቹ ወጣ የሥራቸውንም መከራ ተመለከተ የግብጽም ሰው #የወንድሞቹን_የዕብራዊያንን_ሰው ሲመታ አየ " #ዘጸ2÷17 ዘዚህ ኃይለ ቃል ውስጥ የወንድሞቹን የዕብራዊያንን ሰው የሚለው ሐረግ የሀገሩ የዕብራዊያን ሰዎችን ሁሉ ወንድሞቹ እንዳላቸው ያመለክታል።ከዚህ ወንድም ለመባል የአንድ እናትና አባት ልጆች ወይም ከሁለቱ የአንዱ ልጆች መሆን እንደማይጠበቅብን ያሳያል እናስተውል የአንድ ሀገር ልጆችን ነው ያልነው የአንድ ብሔር ልጆችን፣ የአንድ ጎጥ ልጆችን፣የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ልጆችን አልተባለም ሀገር ከተባለ ሁሉን አቀፍ ነው ኦሮሞ፣ ትግሬ ፣አማራ፣ ሶማሌ አይልም ሀገር የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ናትና።

ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሰኔ ፲ ፰ /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#የቅዱስ_ገብርኤል ጸሎትና ምኞት !
___________________________
ጸሎት ና ምኞት እንዲሁም ተስፋ ማድረግ የሰው ልጆች ብቻ ጠባይ አይደለም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ያለ የፍጡር ሁሉ ጠባይ ጭምር ነው። ታድያ ጸሎት፣ምኞት፣ተስፋን መልካም ካልሆነ ውጤቱም መልካም አይሆንም ለምሳሌ ለእግዚአብሔር የቀረበ ቅሩበ #እግዚአብሔር የሚባል የነበረ ሳጥናኤል ከዚያ ሁሉ ክብሩ የተሻረው ባልተገባ ፈጣሪ የመሆን ምኞትና ተስፋ ነው።

ቅዱሳን መላእክት 24 ሰዓት ያለ ማቆረጥ ያለ መሰልቸት እረፍታቸው ምስጋናቸው ምስጋናቸው እረፍታቸው ሆኖላቸው ሥሉስ ቅዱስ እያሉ ያመሰግናሉ ይዘምራሉ። በምስጋናና በመዝሙር ውስጥ ደግሞ ጸሎትና ልመና አለ። የሰው ልጆችን ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር እንደሚያደርሱ ሁሉ ማር ይቅር በል እያሉ የራሳቸውንም ጸሎትና ልመና ያቀርባሉ ለዚህም ነው ቅዱሳን መላእክት ያማልዱናል የምንለው።ዛሬ ግን ልዮ ጸሎትና ልመና ወደለመነው ወደ ቅዱስ ገብርኤል ምኞትና ጸሎት እናምራ።
#እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለማብሰር የተመረጠው መላእክ ቅዱስ ገብርኤል ነው። ቢሆን ግን ይህን ዕድል ዝም ብሎ አላገኘውም ዕድል ፈንታ ጽዋ ተርታ ዝም ተብሎ የሚገኝ ነገር አይደለምና :: ይህን ዕድል ያገኘውን ቅዱስ ገብርኤልን አነሳን እንጂ ድንግል ማርያም ማብሰር የማኅበረ መላክት ሁሉ ምኞትና ጸሎት ነበር ማለት ይቻላል።
#እመቤታችንን ትጸንሲ ብሎ ለማብሰር መላእክ በሙሉ እኔ ብሆን እያሉ በእጅጉ ይመኑ፣ ይጓጉ ነበር :: ለምን ቢሉ ድንግል ፊት ቆሞ የሰማይና የምድር የሰውና የመላእክት የነፍስና የሥጋ መታረቂያ የጠቡ ግድግዳ መፍረሻ የሥግው ቃል የኢየሱስ ክርስቶስ ማደሪያ የሆንሽ አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ አዳም ከነ ልጆቹ ነፃ የሚወጣበት ጊዜው ደረሰ አንባው ፈረሰ ብሎ ከማብሰር የበለጠ ሌላ የምሥራች በዓለም ላይ የለምና ነው ፡፡
#ቅዱስ_ገብርኤል የዚህ ምሥራች ነጋሪ ሆኖ የተመረጠው አስቀድሞ በዓለመ መላእክ በተፈጠረው የነገደ መላእክት መለያየትን በማረጋጋቱ ነው ፡፡ መላዕክት በተፈጠሩበት በዕለተ እሁድ ቅድሥት ሥላሴ በፈጠርኩላቸው አህምሮ ተጠቅመው አምላክነቴን መርምረው ይወቁ ሲል በዚያው በተፈጠሩበት ቀን ከመንበሩ ተሰወራቸው መላእክትም ከዙፋኑ ቀና ብለው ሲያ አጡት እርስ በእርሳቸውም "መኑ ፈጠረነ?"የፈጠረን ማነው? ሲሉ ተጠያየቁ ሳጥናኤል በክብር ይበልጣቸው ነበርና ቀና ቡሎ ቢመለከት ሥላሴን ከመንበር አጣ ዝቅ ብሎም ቢያይ መላእክ እርስ በእርስ ሲጠያየቁ ተመለከተ ሐሰት የሐሰትም አባቷ እርሱ ነውና "አነ ፈጠረክሙ" እኔ ፈጠርኳችሁ አላቸው ::
ገሚሱ አዎ የበላያችን ስለሆንክ ፈጠርከን ሲሉ ተገዙለት የቀሩት እርሱ ይሆን እያሉ ተጠራጠሩ በዚህ ጊዜ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል ተነስቶ ሳጥናኤል የበላያችን በመሆኑ ወይም በሥልጣን ሰለበለጠን የፈጠረን ከሆነ እኛም የበታቹቻችንን ፈጠርን እንደ ማለት ነው ፈጣሪስ ከሆነ አሁንም ደግሞ ፈጥሮ ያሳየን አለ ሳጥናኤልም እፈጥር ብሎ እጁን ወደ እሳት ቢከት ተቃጥሏል ገብርኤልም እርሱ ፈጣሪ አለመሆኑን ካሳወቀ በኋላ " እንቁም በዕበ ሕላዊከ " የፈጠረንን እስከምናውቅ ባለንበት (በቀደመ እምነታችን) ጸንተን እንቁም ብሎ አረጋጋቸው ::
ከዚህ በኋላ ሥላሴ እራሱን ገለጠላቸው ለሳጥናኤል የተገዙትና የተጠራጠሩትም ከማህበረ ከመላክት ተለይተው ወደ ምድር ተጣሉ በቅዱስ ሳጥናኤል ፈንታ ቅዱስ ሚካኤል ተሾመ መቶ ነገደ መላእክትም ዘጠና ዘጠኝ ነገድ ሆነ በኃላም የሰው ልጅ ተተክቶበተ ነገዱ እንደ ቀድሞ መቶ መሆን ችሏል ::
ቅዱስ ገብርኤልም በዚህ ትልቅ የዕቅበተ እምነት ሥራውና በማረጋጋቱ ቅዱስት ድንግል ማርያምን ለማብሰር ተመረጠ ዕድለኛ መላእክ መሆን ቻለ። ከአዳም ውድቀት በኋላም 5500.ዘመን ሲፈጸም እንደ ተስፈው ቃል ዕድለኛው ቅዱስ ገብርኤል ድንግልን ለማብሰር ሊላክ ከሌሎቱ መላእክት ተለይቶ ወደ አምላኩ ተጠራ ናዝሪት ገሊላ ወደ ምትባለው ቦታ ሂድ ዮሴፍ ለተባለ ሰው የታጨች ድንግልም ታገኛለህ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነው።
ከሷ ደርሰህ የምሥራቹን ነገር ንገራት ስትነግራት ግን ቃልህን ባትቀበልህ በቀስታ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር እንደሌለ አስረዳት እንጂ እንደ ካህኑ ዘካሪያስ እንዳታሳዝናት አለው መላእኩም ክንፉን እያማታ ወደ ገሊላ መንደር ወረደ የክንፉም ድምጽ በገሊላ አውራጃ ሁሉ ይሰማ ነበር:: እመቤታችንም ከእስራኤል ሴቶች ጋር ውኃ ልትቀዳ ወደ ወንዝ ወርዳ ነበር ስተመለስም መላዕኩ እየተከተለ "ትፀንሲ"ትንሻለሽ "ይላት ጀመር
#እመቤታችንም አግብቶ ጸንሶ የመውለድ ሀሳቡ እንኳን አልነበራትምና ይህስ የቀደሙ እናትና አባቶቼን አዳምና ሔዋንን ያሳተ ከይሲ ሳይሆን አይቀርም አለች ወደ ቤተ ዮሴፍም ሄዳ የቀዳችሁን ውኃ ከጀርባዋ ስታወርድ በድጋሚ መላእኩ "ትጸንሲ" (ትጸንሻለሽ) አላት ይህ ነገር ተደጋገመሳ እንዲ ያለውን ነገር እውነት ከሆነ በቤተ መቅደስ መቶ ይነግረኛል ካሎነ ይቀራል ብላ ከእስራኤል ሴቶች የተካፈለችሁን ሐርና ወርቅ ይዛ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደች::
ቤተ መቅደስም ሆና ሐርና ወርቁ እያስማማች ስተፈት ለሦስተኛ ጊዜ መላእኩ ተገልጾ ደስ በሚያሰኝ ንግግር እያረጋጋ ትጸንሲ (ትጸንሻላሽ )አላት እመቤታችንም ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው " ምድር ያለ ዘር ሴት ያለ ወንድ እንዴት ሊያፈሩ ይቻላቸዋል "ይህ ነገር አይሆንም አለችሁ መላእኩም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ የመውለጃዋ ወራት ካለፈ በኃላ ፣ሙቀት ልምላሜ ከተለያት በኃላ ለመውለድ ጸንሳለች ከጸነሰችም ስድስት ወር አልፎታል አላት።
ኤልሳቤጥስ ብትጸንስ ምክንያት ሚሆን ዘካሪያስ አላት እኔ ማን አለኝ አለችሁ መላእኩም ኤልሳቤጥን የመውለጃዋ ጊዜ ካለፈ በኋላ እንድ ትጸንስ ያደረገ አምላክ አንችንም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንሽ ማድረግ ይቻለዋል #ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ::
#እመቤታችንም እውነተኛ መላእክ መሆኑን መርምራ ከተረዳች በኋላ እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ ስትል ምሥራቹን በደስታ ተቀበለች ከዚህች ሰዓት ጀምሮ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ በማህፀኟ ተቀረፀ:: መላእኩም የዚህ ድንቅ ምሥራች አብሳሪ በመሆኑ እየተደሰተ ወደ መጣበት ተመለሰ:: #ሉቃ 1÷26-

..........ይቆየን........
እግዚአብሔር አምላክ ከእመቤታችን እና እርሷን ለማብሰር ከተመረጠው ከዕድለኛው መላእክ ረድኤትና በረከት ይክፈለን !

ተክለ ኤል ኃ/ ማርያም
ታህሳስ ፳ ፪ ቀን ፳ ፻ ፲ ፪ ዓ.ም
ዕድለኛው መላእክ በሚል ርዕስ
ተለጥፎ የነበረ
" #በእናቴ ስም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲታነጽ ፍቃዴ ነው"
_________________________


#እመቤታች_ቅድስት_ድንግል_ማርያም እንደ ልጇ ባለ ሞት ሞታ እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ከሞት ተነስታ ባረገች በ4ዓመቷ ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ፊልጵስዮስ ገብተው አስተማሩ ሕዝቡም አምነው ተጠመቁ። ከእግዲህ ወደ ቤተ ጣዖት አትሂዱ አሏቸው የለመድነውን ከከለከላችሁንማ መካነ ጸሎት(የጸሎት ቦታ) ስጡን ፣ ሥሩልን አሏቸው።

#በእውነቱ የሚገባ ጥያቄ ነው ! አንድ ውኃ የያዘ ብርጭቆን ውኃውን ከገለበጥንለት በኋላ ባዶዎን የሚቀመጥ አይደለም ምንም እንኳ በዐይን ባናየውም በእርሱ ፋንታ ብርጭቆውን አየር ይሞላዋል። ሰውም እንዲሁ ነው ሲሰራው የነበረን አንድ ክፉ ልማድ ከሕይወቱ ሲያስወጣ በዛ ባስወጣው ቦታ ሌላ ሰናይ የሆነ ነገርን ሊተካበት ይገባል ።ካልሆነ ግን ክፉ መስራት ትቻለው ደግ ባልሰራ ችግር የለውም ብሎ ክፋትን ትቶ በጎንም ሳይሰሩ መቀመጥ አያጸድቅም " መልካም ሥራ መሥራትን እያወቀ ለማይሰራት ኃጢያት ትሆንበታለችና"


በተጨማሪም ያን ክፉሁን አስወጥቻለው ብሎ ያለ ደግ ሥራ የተቀመጠው ሰው ቤቱን ባዶ አድርጎ እንደጠረገ ሰው ይመስላል ከእርሱ የወጣ አጋንንትም በምድረ በዳ ሲዞር ቆይቶ የዚያ ሰው ቤት(ቤተ ልቡናው) በደግ ሥራ ያልተሞላ ሆኖ ሲመለከት ወደ ቀደመ ቤቴ ልመለስ ይልና ከእርሱ የከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትይ ይዞ ተመልሶ ይገባበታል ለሰውየውም ከድሮ ይልቅ የአሁኑ ሕይወቱ የከፋ ይሁንበታል #ማቴ 12÷45 #ሉቃ 10÷26

#የፊልጵስዮስ አማኞች ጥያቄ የተገባ ነው ያልነው ለዚሁ ነው ሰው ወደ ቤተ ጣዖት መሄዱን ሲያቆም በአንጻሩ በዚያ ፈንታ ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሄድ መጀመር አለበት አለበለዚያ ግን ከቤተ ጣዖት ከቀረው ወደ ቤተ እግዚአብሔር ባልሄድም ችግር የለውም ማለት አይገባውም እርሱ ወደ ቤተ ጣዖት መሄድ አቆመ ማለት የቤተ ጣዖቱ ሥርዓትና ልማድ በሀሳብ ሁሉ ወደ እርሱ መምጣታቸው አቆሙ ማለት አይደለምና።

ቤተ መቅደስ እንዲሰሩላቸው የተጠየቁት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ምንም እንኳ ጥያቄው የተገባና ደገኛ ጥያቄ ቢሆንም ማንንም ሳያማክሩ በራሳቸው ውሳኔ መሠረት ጣሉ ግድግዳ ለስኑ ጣራ ክደኑ መስቀል አኑሩ ቤተ ክርስቲያን ተከሉ ብለው ወዲያው አላዘዙም። ከዛይ ይልቅ ወደ ወንድሞቻቸው ወደ ጴጥሮስና ወደ ዮሐንስ የፊልጵስዮስ አማኞች ቤተ መቅደስ እንድንሰራላቸው ጠየቁን ምን ይሻላል ? ብለው መልክት ላኩባቸው እነርሱም ያለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቃድ አንዳች ልታደርጎ አይገባም እናንተም ጸልዮ እኛም እንጸልያለን ብለው መለሱላቸው። ቤተ መቅደስ ዝም ተብላ አትሰራም፣ አትተከልም" ሁሉ በአግባቡና በሥርዓት ይሁን" እንደተባለ በአግባቡና በሥርዓት ልትሰራ ያስፈልጋታል 1ኛ ቆሮ 14፥40

#ቤተ_መቅደስ ወይም ቤተ እግዚአብሔር ለመሥራት በመጀመሪያ ፈቃደ እግዚአብሔርን በጾም በጸሎት መጠየቅ ይገባል ። እንደ ቅድስ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ ለሰው ልጆች ቤዛ ሲል በመስቀሉ ብዙ ደም አፍስሷል ይህንንም ደም ቅዱስ ዑራኤል መላእክ በጽዋው ቀድቶ በብርሃን መነሳንስ ፍጥረት ዓለሙን ለመቀደስ ወደ ምድር እረጭቶታል። ታድያ ቤተ ክርስቲያን ስትሰራ ይህ የደሙ ነጠብጣብ ባለበት ወይም በነጠበበት ቦታ ላይ መሆን አለበት እስካሁን የተሰሩ ቤተ ክርስቲያናት ሁሉ እግዚአብሔር ባወቀ ለቅዱሳኑ በመግለጥ የተሰሩ ናቸው ታዲያ ይህን መሰሉን ቦታ ለማወቅ ከእግዚአብሔር ጋር በጸም በጸሎት መነጋገር ፍቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "ያለ እኔ አንዳች ልታደርጉ አይቻላችሁም" #ዮሐ 15÷5

ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስም የቅዱስ ጴጥሮስን እና የቅዱስ ዮሐንስ ምክር ተቀብለው በያሉበት ሱባዔ ያዙ ጾም ጸሎት በማድረግ ፍቃደ እግዚአብሔር ጠየቁ ሰባዔያቸውን ሲጨርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሩቅም ከቅርብም ያሉ ሐዋርያቱን በደመና እየጫነ በፊልጵስዮስ ከተማ ሰበሰባቸው። ቅዱስ ዮሐንስም ጌታዬ ስለምን ሰበሰብከን ብሎ ጠየቀው በእናቴ ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰራ ፍቃዴ ነው አሁንም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ሰበሰብኳቹ አለው።

#ከዚያም ምሳሌዋ ወደሆነው ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ወሰዳቸው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ሕዝቅኤት በትንቢቱ “ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ብሎ እንደጻፈ....።” #ት.ሕዝ 44፥1 በዚያም ተራርቀው የነበሩ ሦስት ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቧ ቁመቱን ወርዱን መጥኞ ሰጣቸው እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው ሳለ እየለመለመ ቁመቱ 24 ወርዱም12 ክንድ አድርጎ ሰርቶ አሳይቷቸዋል።

"ወይዜኒ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ" እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ ብሏቸው ዐረገ ። ዛሬም በቅድስሀ ቅዱሳን በእናቱና በድንግል ማርያም ስም እና በቅዱሳኑ ሰም ለምን ቤተ መቅደስ ትሠራላችሁ ፣ ለምን ታቦት ትቀርጻላችሁ ለሚሉን ሁሉ ልጇ ሰርቶ ስላሳየንና ፍቃዱ ስለሆነ ይልቁኑ እናንተም እንዲሁ ሥሩ እንላቸዋለን ።“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።” #ኢሳ 56፥5

#ቤቴ አላት ቤተ ክርስቲያንን በቅጥሬም ውጥ አለ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚታነጹ ጠቀል እና ጠበል ቤት፣ቤተ ልሔም ፣ ደውል ቤት ፣ሕሙማን ማረፊያ፣ ክርስትና ቤት ፍትሐት ቤት ግምጃ ቤት፣ወዘተ የመሳሰሉን በእናቴና በቅዱሳኖቼ ሰም ቢሰየም እወዳለው ፍቃዴ ነው ሲል ነው።


የእመቤታችን ቤተ ክርሰቲያን፣ የእመቤታችን ጽላት ፣የእመቤታችን ጠበል ፣የእመቤታችን እምነት ማለታችን ትክክል የሆነ ሁሉም በምስጢርና በምክንያት የሆነ ነው ።
#የጀመርነውን ለመጨረስ ያክል ሰኔ 20ቀን ጻሕጻ ቤተ ክርስቲያኗን ሰርቶ ከሰጣቸው በኋላ በማግስቱ ሰኔ 21ቀን በዛችሁ ቤተ መቅደስ እመቤታችንን መንበር ቅዱስ ጴጥሮስን ተራዲኢ ካህን(ንፍቅ) ካህን ፣ እስጢፋኖስን ሰራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል ።ዳግመኛም ቅዱስ ጴጥሮስን እጁን ጭኞ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል በዚህ ጊዜ ሰማያዊያን መላእክት ምድራዊያን ሐዋርያት በአንድነት ሆነው ይሰብሖ ለእግዚአብሔር እያሉ አመስግነዋል ።
______ይቆየን__________
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የልጇ የወዳጇ የኢየሱስ ክርስቶስም ቸርነት የቅዱሳኑም ሁሉ ረድኤትና በረከት አይለየን !

አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ 21/2013 ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
#በሁለት_ዝሆኞች ትግል የሚጎዳው ሳሩ ነው !
____________________________

በጥንት ጊዜ ሁለት ውርዘው ነጌ የሆኑ ሁለት ዝሆኖች ክፉኛ ይጋጩና በጨበጣ ውጊያ በክርኖቻቸው፣በግንባሮቻቸው ይጋጩ ፣በረጃጅም ኩምቢዎቻቸውም ይናረቱ ጀመር። ጠቡ እየከረረ ሄዶ ምድር ስትጨነቅ ከበላያቸው እጅግ ብዙ ጆፌ አሞሮች የተጣለ ግዳይ ለመዘንጠል ማንዣበብ ጀመሩ ። ይኸኔ የአሞሮቹን ማንዣበብ ያጤነው አንደኛው ዝሆን ጠቡን አስታግሶ
#ስማኝማ_አንዴ እነዚህ አሞሮች ምን ነክቷቸው ነው ከበላያችን በማንዣበብ የሚዞሩን ?" ሲል ሌላኛውን ዝሆን ይጠይቃል።
#ተጠያቂው ዝሆንም "እነዚህ አሞሮች የሚከታተሉት የእኛን ድብድብ ሲሆን የሚጠብቁትም የእኛን ሞት ነው። ከሁለት አንዳችን ወይም ሁለታችንም ስንሞት ይወርዱና ይቦጫጭቁንና ይበሉናል።" አለው።

የመጀመሪያ ጠያቂ ዝሆንም ቀበል አድርጎ "እንዲህ ከሆነ ታዲያ እኛ መጣላታችንን ለምን አንተወውም?"ሲል ሌላኛው ውርዝው ዝሆን በአሳቡ ተስማምቶ ሁለቱም ጠባቸውን ትተው በፍቅር ተነስተው ተያይዘው ሄዱ። ያንዣብቡ የነበሩ ጆፌ አሞሮችም የሚቦጫጭቁትና የሚዘነጣጥሉት ግዳይ ስላጡ አዝነው ተበታተኑ ይባላል።

#ዘንድሮ ግን አሞራዎቹ የኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ሳይገናኙ አይቀሩም የወንድማማቾች ጠብ የግዳይ ብፌን ከምድሪቱ አዘጋጅቶ ብሉልኝ ጠጡልኝ ሲል ጋብዟቸዋልና ጠሪ አክባሪ ብለው ይመጣሉ አይቀሩም ። ለዛውም ነጭ ጆፌ አሞሮች ! ልዮነትን በልባቸው ይዘው የጋራ የሠላም መንገድን በአንድ መጓዝ እንደሚቻል ከዝሆኖቹ አልተማሩምና ዝሆኖቹ ጠቡን አቁመው በሠላም መጓዝ የቻሉት ያጋጫቸው ነገር ተፈቶላቸው ላይ ሆን ይችላል በእርስ በእርስ ፍጭት ግን ተጠቃሚው አካል ሌላ መሆኑን ስለተገነዘቡ ግን በልዮ ነት ውስጥ አንድነትን መሠረቱ። ዝሆኖች እርስ በእርስ ሲጣሉ ወይም ሲታገሉ ከርመው ሳይጎዳዱ ሊለያዮ ይችላሉ ነገር ግን እነርሱ የተጣሉበት የሳር ምድር ወደፊት ምድረ በዳ ሊሆን ይችላል ። ለዛ ነው ብዙ ጊዜ በዝሆኖች ጠብ ወይም ትግል ተጎጂዎቹ ሳሮች ናቸው የሚባለው። ዛሬም በዝሆኖች ትግል እየታሸች ያለችሁ መከረኛዋ ቤተ ክርስቲያን ነችና ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ያሻታል!

በቀኝ ግዛት ይዘው ይግጡን ዘንድ ባይቻላቸው በእጅ አዙር በዘመናዊነት ሰበብ በሃይማኖት፣በፖለቲካ ፣በብሔር፣ እንድንበታተን Timer Explosive /በሰዓት የተጠመደ ፈንጂ/ በሕሊና ና በልቡናችን አጠመዱብን፤ ፈንጂውም እነሆ ጊዜውን ጠብቆ መፈንዳቱን ቀጠለ። የተበተነ መንጋ ለአዳኝ ምቹ ነውና አንበሳ እንዳገኘው ከመንጋው እንደተለየ የሜዳ አህያ ሰብሕናና ሞራላችንን ሰባብረው፣ ገነጣጥለው ሊበሉን በዙሪያችን አደቡ ።

#ለዚህም ዋነኛ ምክንያቱ እንደ ኖኅ እራሳችን የተከልነውን ሀገር በቀል በሆኑ ዕውቀቶች መመርመርና ጥንታዊ የሆኑ የአባቶቻችንን የጥበብ ወይን ጠጅ መጎንጨት አለ መፈለጋችን ነው። ከዚህ ይልቅ ከምዕራባውያን የተንኮል ጋን መናኛውን የወይን ጠጅ ጠጥተን እንጠግብ ዘንድ ተመኘን በመንፈሰ ስካርም የእናት ልጅ ወንድምን ገለን ዳኪራ መርገጥን አመጣን ካም የሆነች ዓለምም ኃፍረታችንን እያየች ሳቀችብን !
በወንድማማቾች ጠብ ሟችና ተቅበዝባዥ እንጂ ጀግና የለም! በመሆኑም በወንድሞቻችን ጥፋት እናዝናለን እንጂ ጮቤ አንረግጥም ።ሆኖም ግን ትናንታችንን መርሳት እንደሌለብን በእጅጉ አስተምረውናል ወደ ሥልጣን የመጡበትን ቀን እንደ አቡነ አረጋዊ በዓል ጠላ እየጠመቅን እናክብር እዳላሉ ዛሬ ስም አጣራራቸውም ሳይቀር ጠፍቷል ። ሃያ ሰባት ዓመት የታገሰ እግዚአብሔር ጫካ ነበርሽና ወደ ጫካም ተመለሺ ብሎ በ27ቀን ማዋረድም ይችላል።
#እግዚአብሔር ግን ሁል ጊዜም ይህችን ሀገር የአባታቸውን ኃፍረት ላለማየት ወደ ዋላቸው ሄደው የአባታቸውን እርቃን የሸፈኑ ሴምና ያፊትን የመሰሉ ቡሩካንን አያሳጣትምና ይህው ዛሬም በቸርነቱ ከነ ነፃነታችን ሳንሸማቀቅ አለን።
የፍቅርን፣የይቅር ባይነትን፣የአክብሮትን ጋቢ ይዘው ወደ ዋላ ታሪካቸው ሄድ ብለው አባት ሀገራቸው ከመውደቁ በፊት የነበረውን ክብርና ልዕልና የሚረዱና ወደ ፊትም በልዕልና ሊነሳ እንደሚችል ጭምር ተገንዝበው ብድራታቸውን በምረቃቱ ከነ ትርፉሁ ሊሰጣቸው እንደሚችልም አምነው የሀገርን አፍረት የሚሸፍኑ ሴም እና ያፌቶች ልንሆን ይገባል ። 🙏


የመነሻ ወግ ምጥን ቅመም /በመ/ር ምትኩ አበራ/

ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
አ.አ ኢትዮጵያ
ኅዳር 20/2013ዓ.ም