"ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ"
#ውዳሴ_ማርያም ዘ አርብ
የውዳሴ ማርያም ጸአፊ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ ቢሆንም ቅሉ ደራሲው ግን መንፈስ ቅዱስ ነው። ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት ሊቁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ " ሲል አራቆ ጽፏል ።
አዎን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሰላል ነች ። በመሠላል እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እላይ ያለውም ወደታች ይወርድበታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የምድራዊ ሰዎችን ጸሎትና ልመና ወደ ሰማይ አባታቸው ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ታደርሳለች ታሳርጋለች የእግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረትን ደግሞ ወደ ሰው ልጆች ታወርዳለት ፣ታመጣለችና አማናዊት መሰላል ነች። ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማህሌተ ጽጌው "አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌከ ማርያም የዓአርግ ሉዓሌ" ድንግል ማርያም ሆይ ያላንቺ አማላጅነት ወደ ሰማይ የሚያርግ ጸሎትና ልመና የለም" እንዳለ
ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ስለ ጌታችን ዕርገት ሲናገር እንዲ ይላል "እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። " #ሉቃ 24÷50
ዕርገቱም እንደ ኤልያስ በሠረገላ እንደ ሄኖክም በመሰወር እንደ ሕዝራም ሱቱኤል በመላእክት እገዛ የሆነ አይደለም ። ደመና ከዐይናቸው ሰውራ እስክትቀበለው ድረስ ከፍ ከፍ አለ እንጂ አልጠፋባቸውም ሰማይን አተኩረው እስኪመለከቱ ድረስ የሰማይ መላእክትም እንኪገስጾቸው ድረስ በተመስጦ ሆነው ሲያርግ አዮት እንጂ አረቀቀባቸውም በሰው አምሮ በሚረዳና በሚገባ መልኩ በርዕቀት ከነርሱ ተለይቶ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ። " እናንት የገሊላ ሰዎች እንዲህ አተኩራችሁ ወደ ሰማይ የምትመለከቱት ስለምንድነው እንዲሁ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ደግሞ ይመጣልና " #ሐዋ 1÷11
መሰላል ሁለት ትይይዮ የሆኑ ቋሚ ዘንጎች ያሉት ሲሆን በመካከላቸውም በየተወሰነ ርቀቱ በተደረደሩ አግዳሚ ዘንጎች ሁለቱ ትይዮ ዘንጎች የተጋጠሙ ናቸው ::
ሁለቱ ትይዮ የሆኑ ረጃችም ዘንጎች በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን (ድንግል በክሌ) ያመሰጥራሉ። አንድም ብሉይና ሐዲስን ሲወክሉ በመካከላቸው ያሉ ርብራብ ዘንጎች ደግሞ የብሉይና የሐዲስ መገናኛው ድልድይ እመቤታችን መሆኟን ያስረዳሉ በቡሉይ መጨረሻ በሐዲስ መጀመሪያ ተገኝታለችን አንድም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለ ፈራጅ የሆነ ንጉሥ ሰው ሲሆን አምላክ አምላክ ሲሆን ደግሞ ሰው የሆነውን መካከለኛ ትወልደዋለችና። አንድም የጠቡ ግድግዳ የፈረሰባት ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ የታረቁባት የተቀራረቡባት የዕርቅ ሰነድ እመቤታችን ነችና መሰላል የእመቤታችን ምሳሌ ነው።
በመጻሕፍ ቅዱስ ላይም ይህ ነገር የጎላ የተረዳ ነው::..." ያዕቆብም ከቤርሳቤህ ወጥቶ ወደ ካራን ሄደ። ወደ አንድ ስፍራም ደረሰ፥ ፀሐይም ጠልቃ ነበርና ከዚያ አደረ፤ በዚያም ስፍራ ድንጋይ አነሣ፥ ከራሱም በታች ተንተርሶ በዚያ ስፍራ ተኛ። ሕልምም አለመ፤ #እነሆም_መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም_የእግዚአብሔር_መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። እነሆም፥# እግዚአብሔር በላይ ቆሞበት ነበር፥ #ዘፍ 28÷10-13
ታድያ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ አንቺ ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ሲል ግን እንደ መሰላል ተረግጧት ወጣ ማለት አይደለም የወጣው ወደ ሰማይ ነው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቁመትም እንደ ሰው ሁሉ ሦስት ክንድ ከስንዝር ብቻ ነው ።
በምሥጢር ሊናገር የፈለገው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም ነፍስን ባይነሳ ኖሮ ለመለኮት ወደ ሰማይ ዐረገ የሚልል ነገር ባልተነገረለት ነበር የሥጋን ገንዘብ ገንዘቡ ስላደረገ ውጣ ፣ከፍ ፣ከፍ አለ ዐረገ የሚሉት ነገሮች ተነገረለት ። ቅዱስ ኤፍሬም ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ብቻ ይበል እንጂ ቅሉ እመቤታችንስ ለቃል ከሰማይ ወደ ምድር ለመውረድም መሰላል ሆናዋለች። ድንግል ማርያም ባትኖር ኖሮ ከማን ሰው ይሆን ነበር? መንክር ኦ ዝ ምሥጢር!
እንዲያውም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕርገቱንና ሰው የመሆኑን ምሥጢር ሲያወዳጁ እንዲ ይላሉ"የቃል ርደት በማኅጸን የሥጋ ዕርገት በአርባ ቀን"
ምን ማለታቸው ነው ቢሉ ለቃል ርደትም ለሥጋ ዕርገትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ መሰላል ሆና ለች ያለ እመቤታችን የቃል ርደት (መውረድ) ሆነ የሥጋ ዕርገት አይታሰብምና ነው።
ክቡር ዳዊትም ይህን የሊቁን ሀሳብ የቅዱስ ኤፍሬምን ሀሳብ ሲደግፍ እንዲ ይላል። “ #በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ #ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል።” #መዝ (68) 68፥33 በምሥራቅ በኩል ማለቱ አቅጣጫን ብቻ የሚጠቁም ሳይሆን ከምሥራቅ ፀሐይ እንደሚወጣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምም ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወጣልና እመቤታችን #ምሥራቀ_ምሥራቃት_ሞጻ_ፀሐይ ትባላለችና ፀሐይ ክርስቶስ የወጣባት ምሥራቃዊ መሠላል እርሷ ነች ። መለኮት በሁሉ የመላ ፣ በሁሉ ያለ ነው የሌለበት ቦታ የለም በዚህ አለ በዚያ የለም አይባልለትም # መዝ 138 (139)÷7-10 ነገር ግን የምሥራቅ የእመቤታችንን ሥጋና ነፍስ በመዋሕዱ ግን ከምድር ወደ ሰማይ ሄደ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ተባለለት ። መለኮት ዐረገ እንዲባል ምክንያትቱ ምሥራቁ ሆነችው ።
የነዚህ የዳዊትና የኤፍሬም የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ምን ይረቅ?
__ #ለምን_ዐረገ ? ___
#ትንቢቱን_ለመፈጸም :-"አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ። #መዝ46(47)÷5-6 ነቢዮ ዳዊት ይህን የተናገረው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከአንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ ነው።
#ሥፍራን_ለማዘጋጀት :- መግሥተ ሠማያት ቀድማ ያልተዘጋጀች አሁን ሄዶ የሚያዘጋጃት ሆና ሳይሆን ለእናንተ ለአባቴ ብሩካኖች የተገባች ሆና በመጨረሻው ቀን ተገልጣ እንድትሰጣችሁ የማደርግ እኔ ነኝ አሁን ሄጄ በአባቴ ዕሪና (ትክክል ) በአብ ቀኝ በክብሩ ዙፋን ልቀመጥ ይገባኛል ሲል ነው “በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” #ዮሐንስ 14፥2
#መንፈስ_ቅዱስን_ለመላክ :- “እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።” #ዮሐንስ 16፥7
አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ ፫ቀን / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
#ውዳሴ_ማርያም ዘ አርብ
የውዳሴ ማርያም ጸአፊ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ ቢሆንም ቅሉ ደራሲው ግን መንፈስ ቅዱስ ነው። ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት ሊቁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ " ሲል አራቆ ጽፏል ።
አዎን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሰላል ነች ። በመሠላል እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እላይ ያለውም ወደታች ይወርድበታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የምድራዊ ሰዎችን ጸሎትና ልመና ወደ ሰማይ አባታቸው ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ታደርሳለች ታሳርጋለች የእግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረትን ደግሞ ወደ ሰው ልጆች ታወርዳለት ፣ታመጣለችና አማናዊት መሰላል ነች። ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማህሌተ ጽጌው "አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌከ ማርያም የዓአርግ ሉዓሌ" ድንግል ማርያም ሆይ ያላንቺ አማላጅነት ወደ ሰማይ የሚያርግ ጸሎትና ልመና የለም" እንዳለ
ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ስለ ጌታችን ዕርገት ሲናገር እንዲ ይላል "እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። " #ሉቃ 24÷50
ዕርገቱም እንደ ኤልያስ በሠረገላ እንደ ሄኖክም በመሰወር እንደ ሕዝራም ሱቱኤል በመላእክት እገዛ የሆነ አይደለም ። ደመና ከዐይናቸው ሰውራ እስክትቀበለው ድረስ ከፍ ከፍ አለ እንጂ አልጠፋባቸውም ሰማይን አተኩረው እስኪመለከቱ ድረስ የሰማይ መላእክትም እንኪገስጾቸው ድረስ በተመስጦ ሆነው ሲያርግ አዮት እንጂ አረቀቀባቸውም በሰው አምሮ በሚረዳና በሚገባ መልኩ በርዕቀት ከነርሱ ተለይቶ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ። " እናንት የገሊላ ሰዎች እንዲህ አተኩራችሁ ወደ ሰማይ የምትመለከቱት ስለምንድነው እንዲሁ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ደግሞ ይመጣልና " #ሐዋ 1÷11
መሰላል ሁለት ትይይዮ የሆኑ ቋሚ ዘንጎች ያሉት ሲሆን በመካከላቸውም በየተወሰነ ርቀቱ በተደረደሩ አግዳሚ ዘንጎች ሁለቱ ትይዮ ዘንጎች የተጋጠሙ ናቸው ::
ሁለቱ ትይዮ የሆኑ ረጃችም ዘንጎች በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን (ድንግል በክሌ) ያመሰጥራሉ። አንድም ብሉይና ሐዲስን ሲወክሉ በመካከላቸው ያሉ ርብራብ ዘንጎች ደግሞ የብሉይና የሐዲስ መገናኛው ድልድይ እመቤታችን መሆኟን ያስረዳሉ በቡሉይ መጨረሻ በሐዲስ መጀመሪያ ተገኝታለችን አንድም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለ ፈራጅ የሆነ ንጉሥ ሰው ሲሆን አምላክ አምላክ ሲሆን ደግሞ ሰው የሆነውን መካከለኛ ትወልደዋለችና። አንድም የጠቡ ግድግዳ የፈረሰባት ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ የታረቁባት የተቀራረቡባት የዕርቅ ሰነድ እመቤታችን ነችና መሰላል የእመቤታችን ምሳሌ ነው።
በመጻሕፍ ቅዱስ ላይም ይህ ነገር የጎላ የተረዳ ነው::..." ያዕቆብም ከቤርሳቤህ ወጥቶ ወደ ካራን ሄደ። ወደ አንድ ስፍራም ደረሰ፥ ፀሐይም ጠልቃ ነበርና ከዚያ አደረ፤ በዚያም ስፍራ ድንጋይ አነሣ፥ ከራሱም በታች ተንተርሶ በዚያ ስፍራ ተኛ። ሕልምም አለመ፤ #እነሆም_መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም_የእግዚአብሔር_መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። እነሆም፥# እግዚአብሔር በላይ ቆሞበት ነበር፥ #ዘፍ 28÷10-13
ታድያ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ አንቺ ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ሲል ግን እንደ መሰላል ተረግጧት ወጣ ማለት አይደለም የወጣው ወደ ሰማይ ነው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቁመትም እንደ ሰው ሁሉ ሦስት ክንድ ከስንዝር ብቻ ነው ።
በምሥጢር ሊናገር የፈለገው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም ነፍስን ባይነሳ ኖሮ ለመለኮት ወደ ሰማይ ዐረገ የሚልል ነገር ባልተነገረለት ነበር የሥጋን ገንዘብ ገንዘቡ ስላደረገ ውጣ ፣ከፍ ፣ከፍ አለ ዐረገ የሚሉት ነገሮች ተነገረለት ። ቅዱስ ኤፍሬም ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ብቻ ይበል እንጂ ቅሉ እመቤታችንስ ለቃል ከሰማይ ወደ ምድር ለመውረድም መሰላል ሆናዋለች። ድንግል ማርያም ባትኖር ኖሮ ከማን ሰው ይሆን ነበር? መንክር ኦ ዝ ምሥጢር!
እንዲያውም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕርገቱንና ሰው የመሆኑን ምሥጢር ሲያወዳጁ እንዲ ይላሉ"የቃል ርደት በማኅጸን የሥጋ ዕርገት በአርባ ቀን"
ምን ማለታቸው ነው ቢሉ ለቃል ርደትም ለሥጋ ዕርገትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ መሰላል ሆና ለች ያለ እመቤታችን የቃል ርደት (መውረድ) ሆነ የሥጋ ዕርገት አይታሰብምና ነው።
ክቡር ዳዊትም ይህን የሊቁን ሀሳብ የቅዱስ ኤፍሬምን ሀሳብ ሲደግፍ እንዲ ይላል። “ #በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ #ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል።” #መዝ (68) 68፥33 በምሥራቅ በኩል ማለቱ አቅጣጫን ብቻ የሚጠቁም ሳይሆን ከምሥራቅ ፀሐይ እንደሚወጣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምም ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወጣልና እመቤታችን #ምሥራቀ_ምሥራቃት_ሞጻ_ፀሐይ ትባላለችና ፀሐይ ክርስቶስ የወጣባት ምሥራቃዊ መሠላል እርሷ ነች ። መለኮት በሁሉ የመላ ፣ በሁሉ ያለ ነው የሌለበት ቦታ የለም በዚህ አለ በዚያ የለም አይባልለትም # መዝ 138 (139)÷7-10 ነገር ግን የምሥራቅ የእመቤታችንን ሥጋና ነፍስ በመዋሕዱ ግን ከምድር ወደ ሰማይ ሄደ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ተባለለት ። መለኮት ዐረገ እንዲባል ምክንያትቱ ምሥራቁ ሆነችው ።
የነዚህ የዳዊትና የኤፍሬም የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ምን ይረቅ?
__ #ለምን_ዐረገ ? ___
#ትንቢቱን_ለመፈጸም :-"አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ። #መዝ46(47)÷5-6 ነቢዮ ዳዊት ይህን የተናገረው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከአንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ ነው።
#ሥፍራን_ለማዘጋጀት :- መግሥተ ሠማያት ቀድማ ያልተዘጋጀች አሁን ሄዶ የሚያዘጋጃት ሆና ሳይሆን ለእናንተ ለአባቴ ብሩካኖች የተገባች ሆና በመጨረሻው ቀን ተገልጣ እንድትሰጣችሁ የማደርግ እኔ ነኝ አሁን ሄጄ በአባቴ ዕሪና (ትክክል ) በአብ ቀኝ በክብሩ ዙፋን ልቀመጥ ይገባኛል ሲል ነው “በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” #ዮሐንስ 14፥2
#መንፈስ_ቅዱስን_ለመላክ :- “እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።” #ዮሐንስ 16፥7
አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ ፫ቀን / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
#ወንድማማችነት_በመጽሐፍ_ቅዱስ
___________________________
በወንዶች ወገን መናገር የመጽሐፍ ቅዱስ ልማዱ ሆኖ ነው እንጂ ወንድማማችነት በሚለው እርዕስ ውስጥ እህታማችነት የሚል ሀሳብም እንዳለው ልብ ማለት ይገባል ።
መጽሐፍ ቅዱስ ወንድሞች ሆይ እያለ ሲናገር እህቶች ሆይ ማለቱ ጭምር እንደሆነ በአንጻሩ መረዳት አለብን። ጾታና ከአገልግሎት ድርሻ ውጪህ ያሉ ነገሮች ላይ መጻሕፍ ቅዱስ ጠቅለል አድርጎ ወንድሞች የሚለውን መጠሪያ ይጠቀማል ሴት ከወንድ ጎን ተገኝታለችና ውክልናው ለእርሷም ጭምር ነው ። እንዲያውም #እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን ከፈጠራቸው በኃላ ሁለቱንም አዳም ብሎ ይጠራቸው እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል “ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፥ ባረካቸውም። ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን #አዳም ብሎ ጠራቸው።” #ዘፍጥረት 5፥2 ስለዚህ ወንድማማችነት በመጽሐፍ ቅዱስ ሲባል እህታማችነት በመጽሐፍ ቅዱስ ማለት ጭምር ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ወንድም ወይም እህት የሚለውን መጠሪያ ለማግኘት የግድ የእናትና የአባት ወይም የአንዱ ብቻ ልጅ መሆን አያስፈልግም። መጽሐፍ ቅዱስ በተለየ ሁኔታ የሚቀራረቡ ሰዎችን ወንድማማቾች ወይም እህታማቶች እያለ ይጠራቸዋል።በቤተሰብ አንድ የሆኑ ሰዎች ወንድማማቾች መባላቸው ግልጽ ስለሆነ እርሱን ለጊዜው እናቆየዋለን።
#ባልንጀራ_ወንድም
_____________
መጽሐፍ ቅዱስ የቅርብ ወዳጅ የሆኑ ጓደኛማቾችን ወንድማማቾች ብሎ ይጠራቸዋል። ቅዱስ ዳዊትና የሳዖል ልጅ ዮናታን እጅግ በጣም ይወደዱ የነበሩ ባልንጀሮች ነበሩ ነገር ግን አንዳቸው ላንዳቸው ወንድሜ እየተባባሉ ነበር የሚጠራሩት። ለምሳሌ ዮናታን በሞተ ግዜ ዳዊት ሞሾ እያወጣ ሲያለቅስለት “ #ወንድሜ_ዮናታን_ሆይ ፥ እኔ ስለ አንተ እጨነቃለሁ፤ በእኔ ዘንድ ውድህ እጅግ የተለየ ነበረ፤ #ከሴት_ፍቅር_ይልቅ_ፍቅርህ_ለእኔ_ግሩም ነበረ።” #2ሳሙ 1፥26 ከዚህም የምንረዳው እጅግ የሚዋደዱ፣ የሚቀራረቡ ፣በደጉም ፣በክፉሁም ጊዜ የማይለያዮ ጓደኛማቾች ወንድማማቾች ተብለው ሊጠሩ እንደሚችሉ ነው።
ጓደኛ ማለት በራሱ ላላ አድርገን ስናነበው ጓ..ደ...ኛ... ጓዳ ከቤት በውስጥ እንደሚገኝ ጓደኛም የቤተ ልቡናችን ጓዳ ዘልቆ ገበናችንን የሚያውቅ የውስጥ ሰው ማለት ነው። ዘመናችን ከፋና አሁን አሁን ጓደኛ ጠፍቶ ጉደኛ በዛ እንጂ ይህ ጓደኛ ከእናት ልጅ ወንድም እኩል አንዳንዴም በልጦ ሊገኝ ይችላል።
#የዘመድ_ልጅ_ወንድም
________________
በእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት በቅዱስ ሚካኢል ተራዳኢነን ሙሴ ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ባሕረ ኤርትራን አሻግሮ ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲጓዝ የኤዶምያስ ንጉሥ በሰላም እንዲያሳልፋቸው መልእክት ሲልክ " #ወንድምህ_እስራኤል እንዲህ ይላል " ሲል መልክቱን ጀምሯል #ዘኁ20÷14 ከግብጽ የወጡት እስራኤላውያን ወይም እነ ሙሴ ለኤዶምና ለኤዶማውያን አንዴት ወንድም ሊሆኑ ይችላሉ? ሊባል ይችላል ምክንያቱም ሙሴና ኤዶምያስ የአንድ እናትና አባት ልጆች አይደሉምና። ነገሩ እንዲህ ነው ኤዶም የኤሳው ሌላኛው ስሙ ነው ኤሳውና ያዕቆብ ደግሞ የአንድ እናት ተከታታይ ልጆች ናቸው ።ያዕቆብ ደግሞ እግዚአብሔር እስራኤል ብሎ የጠራው ዘሮቹም እስራኤላውያን ተብለው በስሙየተጠሩለት ሰው ነው። #ዘፍ 36÷1
ስለሆነም ሙሴ ኤዶምያስ በተባለው በዔሳው እና እስራኤል በተባለው በያዕቆብ መካከል ያለውን ዝምድና አምጥቶ መናገሩ ነው።
#የነገድ_ልጅ_ወንድም
_______________
ንጉሥ ዳዊት ለካህናቱ ለሳዶቅና ለአብያታር መልዕክት ሲልክ "ለይሁዳ ሽማግሌዎች እንዲ ብላችሁ ተናገሯቸው የእስራኤል ሁሉ ነገር ወደ ንጉሡ ደርሷልና ንጉሡን ወደ ቤቱ ከመመለስ ስለምን ዘገያችሁ እናንተ ወንድሞቼ የአጥንቴ ፍላጭ ና የሥጋዬ ቁራጭ ናችሁ" 2ሳሙ 19÷11 በንግግሩ ንጉሥ ዳዊት የይሁዳ ሽማግሌዎችን ወንድሞቼ ብሎ የጠራቸው እርሱ ከ12ቱ ነገደ እስራኤል የይሁዳ ልጅ ስለሆነና በነገድ አንድ ስለሆኑ ነው እንጂ ከአንድ እናትና አባት ስለተወለዱ አይደለም።
#የሀገር_ልጅ_ወንድም
_______________
የአንድ ሀገር ልጆችን ወይም የሀንድ ሀገር ዜግነት ያላቸው ሰዎች ወንድማማቾች ተብለው ይጠራሉ። "ሙሴ ጎበዝ በሆነ ጊዜ ወደ #ወንድሞቹ ወጣ የሥራቸውንም መከራ ተመለከተ የግብጽም ሰው #የወንድሞቹን_የዕብራዊያንን_ሰው ሲመታ አየ " #ዘጸ2÷17 ዘዚህ ኃይለ ቃል ውስጥ የወንድሞቹን የዕብራዊያንን ሰው የሚለው ሐረግ የሀገሩ የዕብራዊያን ሰዎችን ሁሉ ወንድሞቹ እንዳላቸው ያመለክታል።ከዚህ ወንድም ለመባል የአንድ እናትና አባት ልጆች ወይም ከሁለቱ የአንዱ ልጆች መሆን እንደማይጠበቅብን ያሳያል እናስተውል የአንድ ሀገር ልጆችን ነው ያልነው የአንድ ብሔር ልጆችን፣ የአንድ ጎጥ ልጆችን፣የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ልጆችን አልተባለም ሀገር ከተባለ ሁሉን አቀፍ ነው ኦሮሞ፣ ትግሬ ፣አማራ፣ ሶማሌ አይልም ሀገር የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ናትና።
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሰኔ ፲ ፰ /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
___________________________
በወንዶች ወገን መናገር የመጽሐፍ ቅዱስ ልማዱ ሆኖ ነው እንጂ ወንድማማችነት በሚለው እርዕስ ውስጥ እህታማችነት የሚል ሀሳብም እንዳለው ልብ ማለት ይገባል ።
መጽሐፍ ቅዱስ ወንድሞች ሆይ እያለ ሲናገር እህቶች ሆይ ማለቱ ጭምር እንደሆነ በአንጻሩ መረዳት አለብን። ጾታና ከአገልግሎት ድርሻ ውጪህ ያሉ ነገሮች ላይ መጻሕፍ ቅዱስ ጠቅለል አድርጎ ወንድሞች የሚለውን መጠሪያ ይጠቀማል ሴት ከወንድ ጎን ተገኝታለችና ውክልናው ለእርሷም ጭምር ነው ። እንዲያውም #እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን ከፈጠራቸው በኃላ ሁለቱንም አዳም ብሎ ይጠራቸው እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል “ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፥ ባረካቸውም። ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን #አዳም ብሎ ጠራቸው።” #ዘፍጥረት 5፥2 ስለዚህ ወንድማማችነት በመጽሐፍ ቅዱስ ሲባል እህታማችነት በመጽሐፍ ቅዱስ ማለት ጭምር ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ወንድም ወይም እህት የሚለውን መጠሪያ ለማግኘት የግድ የእናትና የአባት ወይም የአንዱ ብቻ ልጅ መሆን አያስፈልግም። መጽሐፍ ቅዱስ በተለየ ሁኔታ የሚቀራረቡ ሰዎችን ወንድማማቾች ወይም እህታማቶች እያለ ይጠራቸዋል።በቤተሰብ አንድ የሆኑ ሰዎች ወንድማማቾች መባላቸው ግልጽ ስለሆነ እርሱን ለጊዜው እናቆየዋለን።
#ባልንጀራ_ወንድም
_____________
መጽሐፍ ቅዱስ የቅርብ ወዳጅ የሆኑ ጓደኛማቾችን ወንድማማቾች ብሎ ይጠራቸዋል። ቅዱስ ዳዊትና የሳዖል ልጅ ዮናታን እጅግ በጣም ይወደዱ የነበሩ ባልንጀሮች ነበሩ ነገር ግን አንዳቸው ላንዳቸው ወንድሜ እየተባባሉ ነበር የሚጠራሩት። ለምሳሌ ዮናታን በሞተ ግዜ ዳዊት ሞሾ እያወጣ ሲያለቅስለት “ #ወንድሜ_ዮናታን_ሆይ ፥ እኔ ስለ አንተ እጨነቃለሁ፤ በእኔ ዘንድ ውድህ እጅግ የተለየ ነበረ፤ #ከሴት_ፍቅር_ይልቅ_ፍቅርህ_ለእኔ_ግሩም ነበረ።” #2ሳሙ 1፥26 ከዚህም የምንረዳው እጅግ የሚዋደዱ፣ የሚቀራረቡ ፣በደጉም ፣በክፉሁም ጊዜ የማይለያዮ ጓደኛማቾች ወንድማማቾች ተብለው ሊጠሩ እንደሚችሉ ነው።
ጓደኛ ማለት በራሱ ላላ አድርገን ስናነበው ጓ..ደ...ኛ... ጓዳ ከቤት በውስጥ እንደሚገኝ ጓደኛም የቤተ ልቡናችን ጓዳ ዘልቆ ገበናችንን የሚያውቅ የውስጥ ሰው ማለት ነው። ዘመናችን ከፋና አሁን አሁን ጓደኛ ጠፍቶ ጉደኛ በዛ እንጂ ይህ ጓደኛ ከእናት ልጅ ወንድም እኩል አንዳንዴም በልጦ ሊገኝ ይችላል።
#የዘመድ_ልጅ_ወንድም
________________
በእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት በቅዱስ ሚካኢል ተራዳኢነን ሙሴ ሕዝቡን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ባሕረ ኤርትራን አሻግሮ ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲጓዝ የኤዶምያስ ንጉሥ በሰላም እንዲያሳልፋቸው መልእክት ሲልክ " #ወንድምህ_እስራኤል እንዲህ ይላል " ሲል መልክቱን ጀምሯል #ዘኁ20÷14 ከግብጽ የወጡት እስራኤላውያን ወይም እነ ሙሴ ለኤዶምና ለኤዶማውያን አንዴት ወንድም ሊሆኑ ይችላሉ? ሊባል ይችላል ምክንያቱም ሙሴና ኤዶምያስ የአንድ እናትና አባት ልጆች አይደሉምና። ነገሩ እንዲህ ነው ኤዶም የኤሳው ሌላኛው ስሙ ነው ኤሳውና ያዕቆብ ደግሞ የአንድ እናት ተከታታይ ልጆች ናቸው ።ያዕቆብ ደግሞ እግዚአብሔር እስራኤል ብሎ የጠራው ዘሮቹም እስራኤላውያን ተብለው በስሙየተጠሩለት ሰው ነው። #ዘፍ 36÷1
ስለሆነም ሙሴ ኤዶምያስ በተባለው በዔሳው እና እስራኤል በተባለው በያዕቆብ መካከል ያለውን ዝምድና አምጥቶ መናገሩ ነው።
#የነገድ_ልጅ_ወንድም
_______________
ንጉሥ ዳዊት ለካህናቱ ለሳዶቅና ለአብያታር መልዕክት ሲልክ "ለይሁዳ ሽማግሌዎች እንዲ ብላችሁ ተናገሯቸው የእስራኤል ሁሉ ነገር ወደ ንጉሡ ደርሷልና ንጉሡን ወደ ቤቱ ከመመለስ ስለምን ዘገያችሁ እናንተ ወንድሞቼ የአጥንቴ ፍላጭ ና የሥጋዬ ቁራጭ ናችሁ" 2ሳሙ 19÷11 በንግግሩ ንጉሥ ዳዊት የይሁዳ ሽማግሌዎችን ወንድሞቼ ብሎ የጠራቸው እርሱ ከ12ቱ ነገደ እስራኤል የይሁዳ ልጅ ስለሆነና በነገድ አንድ ስለሆኑ ነው እንጂ ከአንድ እናትና አባት ስለተወለዱ አይደለም።
#የሀገር_ልጅ_ወንድም
_______________
የአንድ ሀገር ልጆችን ወይም የሀንድ ሀገር ዜግነት ያላቸው ሰዎች ወንድማማቾች ተብለው ይጠራሉ። "ሙሴ ጎበዝ በሆነ ጊዜ ወደ #ወንድሞቹ ወጣ የሥራቸውንም መከራ ተመለከተ የግብጽም ሰው #የወንድሞቹን_የዕብራዊያንን_ሰው ሲመታ አየ " #ዘጸ2÷17 ዘዚህ ኃይለ ቃል ውስጥ የወንድሞቹን የዕብራዊያንን ሰው የሚለው ሐረግ የሀገሩ የዕብራዊያን ሰዎችን ሁሉ ወንድሞቹ እንዳላቸው ያመለክታል።ከዚህ ወንድም ለመባል የአንድ እናትና አባት ልጆች ወይም ከሁለቱ የአንዱ ልጆች መሆን እንደማይጠበቅብን ያሳያል እናስተውል የአንድ ሀገር ልጆችን ነው ያልነው የአንድ ብሔር ልጆችን፣ የአንድ ጎጥ ልጆችን፣የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ልጆችን አልተባለም ሀገር ከተባለ ሁሉን አቀፍ ነው ኦሮሞ፣ ትግሬ ፣አማራ፣ ሶማሌ አይልም ሀገር የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ናትና።
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሰኔ ፲ ፰ /፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ስለ ታቦቲቱ የባዕዳኑ መልከታ
...... #ካለፈው የቀጠለ.....
#ጀምስ_ብሩስ /james bruce/
____________________________
#የዓባይን ምንጭ ወይስ #ታቦቲቱን ፍለጋ ???
_________________________________
ባለፈው ጽሑፋችን ግራሃም ሐንኰክ የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/#Raiders_of_the_Lost_Ark/ በሚል ርእስ የተሠራውን የሆሊውድ ፊልም በ 1983 ናይሮቢ ውስጥ ካየ በኋላ ታቦቲቱን ለማግኘት እንደተነሳሳ ዓይተን ነበር። አሁን ደግሞ ጀምስ ብሩስን በሽፋን ስም ታቦቲቱንና መገኛዋን ለማግኘት ያደረገውን ምሥጢራዊ ጥረት እንመለከታለን።
#ከክርስቶፈር ደጋማ ሞት በኋላ "የክርስቶስ ሠራዊት" ስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ የነበረው ጉጉት እየቀዘቀዘ ሲመጣ የስኮትላንዱ "ምሥጢራዊ የወንድማማቶች ማህበርም " ስለ ሰሎሞን ቤተ መቅደስና የቃል ኪዳኑ ታቦት የወረሳቸው አንዳንድ ምሥጢራዊ የሃይማኖት ሥርዓቶች ሲኖሩ በነዚህም ውስጥ ታቦቱ ጉልህ ሚና አለው።
በመሆኑም በዚህ ረገድ በድፍረቱና በቆራጥነቱ ስለሚታወቀውና ቴምፕላሮችን ካዳነው ከንጉስ ብሩስ ጋር የዘር ግንዱን ስለሚቆጠረውና ኢትዮጵያ በስፋት ስለጎበኘው የእስኮትላንዱ ተወላጅ ጀምስ ብሩስ መለመለ።
#ረጅሙና ግዙፉ ጀምስ ብሩስ ስኮትላንድ ውስጥ 1730 ተወለዶ ከፍተኛ ትምህርቱን በኤደን ብራ ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቀ ምሁር ነው። በትምህርቱ በኋላ ኢስት ኢንድያ በተባለ ድርጅት ተቀጥሮ ሠርቷል። ይሁንና በ1754 ባለ ቤቱ ስለሞተች በደረሰበት ብስጭት የተነሣ ከሀገር ወደ ሀገር መዘዋወር የጀመረ ሰው ነው።
የነበረው የቋንቋ ችሎታው በማጤንም በሰሜን አፍሪካ አልጀርስ ውስጥ የብሪቲሽ ቆንጽላ በመሆን እንዲሰራ ከመደረጉም ባሻገር ወደ ቅድስቲቱ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌምም ተጉዟል። በቋንቋ ረገድ አረብኛ፣ፖርቱጋልኛ እንዲሁም ጥንታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ቋንቋ (ግእዝን) ያውቅ ነበር።
#ጀምስ_ብሩስ በ1759 የግእዝ ቋንቋ ያጠናበት ዋነኛ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ላሰበው ጉዞ ዝግጅት ለማድረግ ሲሆን ከእርሱ በፊት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የነበሩ ሰዎችን የጻፏቸውንም በማንበብ በማጥናት ስለ ሀገሪቱ በቂ ዕውቀት ጨብጦ ነበር ዘዚያም 1768ወደ ካይሮ በመሄድ ታሪካዊ ጉዞዎን ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
ብሩስ ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ምን አነሳሳው? እርሱ እንደሚለው የዓባይን ወንዝ ምንጭ ለማግኘትከ1768-1773በተከታታይ የተደረጉ ጉዞዎች( Travels to Discover The Source of Nile in The Years 1768-1773 የሚል ባለ 3ሺህ ገጽ መጻሕፍ በ5 ተከታታይ ጥራዝ ጽፎል። ቢሆንም ግን ቅሉ የዓባይን ወንዝ ምንጭ በትክክል እንኳ አላወቀውም፤አልደረሰበትም የዓባይ ወንዝ ጣና እንደሆነ አስፎሯልና
#ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት ግን የዓባይ ምንጭ ግሽ ዓባይ ሰከላ እንደሆነ እና ዋነኛ ምንጩም ገነት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስን ዋቢ አድርገው ይገልጻሉ ፤ያምናሉ #ዘፍ 2÷10 -13 የሱ ዓላማ ታቦቲቱን ማግኘት እንጂ የዓባይን ምንጭ ማግኘት ስላልነበረ ነው ያን የሚያክል ባለ ብዙ ገጽ መጽሐፍ ጽፎ ከስተት የደረሰው ። በኢትዮጵያም ሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ ሦስት የመጽሐፈ ሄኖክ ቅጂዎችን ሰርቆ ኮብልሏል።
ኢትዮጵያ አ.አ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፯ / ፳ ፻ ፲ ፫
...... #ካለፈው የቀጠለ.....
#ጀምስ_ብሩስ /james bruce/
____________________________
#የዓባይን ምንጭ ወይስ #ታቦቲቱን ፍለጋ ???
_________________________________
ባለፈው ጽሑፋችን ግራሃም ሐንኰክ የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/#Raiders_of_the_Lost_Ark/ በሚል ርእስ የተሠራውን የሆሊውድ ፊልም በ 1983 ናይሮቢ ውስጥ ካየ በኋላ ታቦቲቱን ለማግኘት እንደተነሳሳ ዓይተን ነበር። አሁን ደግሞ ጀምስ ብሩስን በሽፋን ስም ታቦቲቱንና መገኛዋን ለማግኘት ያደረገውን ምሥጢራዊ ጥረት እንመለከታለን።
#ከክርስቶፈር ደጋማ ሞት በኋላ "የክርስቶስ ሠራዊት" ስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ የነበረው ጉጉት እየቀዘቀዘ ሲመጣ የስኮትላንዱ "ምሥጢራዊ የወንድማማቶች ማህበርም " ስለ ሰሎሞን ቤተ መቅደስና የቃል ኪዳኑ ታቦት የወረሳቸው አንዳንድ ምሥጢራዊ የሃይማኖት ሥርዓቶች ሲኖሩ በነዚህም ውስጥ ታቦቱ ጉልህ ሚና አለው።
በመሆኑም በዚህ ረገድ በድፍረቱና በቆራጥነቱ ስለሚታወቀውና ቴምፕላሮችን ካዳነው ከንጉስ ብሩስ ጋር የዘር ግንዱን ስለሚቆጠረውና ኢትዮጵያ በስፋት ስለጎበኘው የእስኮትላንዱ ተወላጅ ጀምስ ብሩስ መለመለ።
#ረጅሙና ግዙፉ ጀምስ ብሩስ ስኮትላንድ ውስጥ 1730 ተወለዶ ከፍተኛ ትምህርቱን በኤደን ብራ ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቀ ምሁር ነው። በትምህርቱ በኋላ ኢስት ኢንድያ በተባለ ድርጅት ተቀጥሮ ሠርቷል። ይሁንና በ1754 ባለ ቤቱ ስለሞተች በደረሰበት ብስጭት የተነሣ ከሀገር ወደ ሀገር መዘዋወር የጀመረ ሰው ነው።
የነበረው የቋንቋ ችሎታው በማጤንም በሰሜን አፍሪካ አልጀርስ ውስጥ የብሪቲሽ ቆንጽላ በመሆን እንዲሰራ ከመደረጉም ባሻገር ወደ ቅድስቲቱ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌምም ተጉዟል። በቋንቋ ረገድ አረብኛ፣ፖርቱጋልኛ እንዲሁም ጥንታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ቋንቋ (ግእዝን) ያውቅ ነበር።
#ጀምስ_ብሩስ በ1759 የግእዝ ቋንቋ ያጠናበት ዋነኛ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ላሰበው ጉዞ ዝግጅት ለማድረግ ሲሆን ከእርሱ በፊት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የነበሩ ሰዎችን የጻፏቸውንም በማንበብ በማጥናት ስለ ሀገሪቱ በቂ ዕውቀት ጨብጦ ነበር ዘዚያም 1768ወደ ካይሮ በመሄድ ታሪካዊ ጉዞዎን ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
ብሩስ ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ምን አነሳሳው? እርሱ እንደሚለው የዓባይን ወንዝ ምንጭ ለማግኘትከ1768-1773በተከታታይ የተደረጉ ጉዞዎች( Travels to Discover The Source of Nile in The Years 1768-1773 የሚል ባለ 3ሺህ ገጽ መጻሕፍ በ5 ተከታታይ ጥራዝ ጽፎል። ቢሆንም ግን ቅሉ የዓባይን ወንዝ ምንጭ በትክክል እንኳ አላወቀውም፤አልደረሰበትም የዓባይ ወንዝ ጣና እንደሆነ አስፎሯልና
#ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት ግን የዓባይ ምንጭ ግሽ ዓባይ ሰከላ እንደሆነ እና ዋነኛ ምንጩም ገነት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስን ዋቢ አድርገው ይገልጻሉ ፤ያምናሉ #ዘፍ 2÷10 -13 የሱ ዓላማ ታቦቲቱን ማግኘት እንጂ የዓባይን ምንጭ ማግኘት ስላልነበረ ነው ያን የሚያክል ባለ ብዙ ገጽ መጽሐፍ ጽፎ ከስተት የደረሰው ። በኢትዮጵያም ሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ ሦስት የመጽሐፈ ሄኖክ ቅጂዎችን ሰርቆ ኮብልሏል።
ኢትዮጵያ አ.አ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፯ / ፳ ፻ ፲ ፫
| በድጋሚ የተለጠፈ
" #ከምድር_ወደ_ሰማይ_ለማረግ_መሰላል_ሆንሽ "
________
#ውዳሴ_ማርያም ዘ አርብ
የውዳሴ ማርያም ጸሐፊ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ ቢሆንም ቅሉ ደራሲው ግን መንፈስ ቅዱስ ነው። ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት ሊቁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ " ሲል አራቆ ጽፏል ።
አዎን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሰላል ነች ። በመሠላል እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እላይ ያለውም ወደታች ይወርድበታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የምድራዊ ሰዎችን ጸሎትና ልመና ወደ ሰማይ አባታቸው ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ታደርሳለች ታሳርጋለች የእግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረትን ደግሞ ወደ ሰው ልጆች ታወርዳለት ፣ታመጣለችና አማናዊት መሰላል ነች። #ሊቁ_አባ_ጽጌ_ድንግል በማህሌተ ጽጌው "አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌከ ማርያም የዓአርግ ሉዓሌ" #ድንግል_ማርያም_ሆይ ያላንቺ አማላጅነት ወደ ሰማይ የሚያርግ ጸሎትና ልመና የለም" እንዳለ
ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ስለ ጌታችን ዕርገት ሲናገር እንዲ ይላል "እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። " #ሉቃ 24÷50
ዕርገቱም እንደ ኤልያስ በሠረገላ እንደ ሄኖክም በመሰወር እንደ ሕዝራም ሱቱኤል በመላእክት እገዛ የሆነ አይደለም ። ደመና ከዐይናቸው ሰውራ እስክትቀበለው ድረስ ከፍ ከፍ አለ እንጂ አልጠፋባቸውም። ሰማይን አተኩረው እስኪመለከቱ ድረስ የሰማይ መላእክትም እንኪገስጾቸው ድረስ በተመስጦ ሆነው ሲያርግ አዮት እንጂ አረቀቀባቸውም በሰው አምሮ በሚረዳና በሚገባ መልኩ በርዕቀት ከነርሱ ተለይቶ ከፍ ከፍ እያለ ዐረገ ። "እናትት የገሊላ ሰዎች እንዲህ አትኩራችሁ ወደ ሰማይ የምትመለከቱ ስለምንድነው እንዲሁ ሲሄድ እንዳያችሁ እንዲሁ ደግሞ ይመጣልና" #ሐዋ1÷11
መሰላል ሁለት ትይይዮ የሆኑ ቋሚ ዘንጎች ያሉት ሲሆን በመካከላቸውም በየተወሰነ ርቀቱ በተደረደሩ አግዳሚ ዘንጎች ሁለቱ ትይዮ ዘንጎች የተጋጠሙ ናቸው ::
ሁለቱ ትይዮ የሆኑ ረጃችም ዘንጎች በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን (ድንግል በክሌ) ያመሰጥራሉ። አንድም ብሉይና ሐዲስን ሲወክሉ በመካከላቸው ያሉ ርብራብ ዘንጎች ደግሞ የብሉይና የሐዲስ መገናኛው ድልድይ እመቤታችን መሆኟን ያስረዳሉ በቡሉይ መጨረሻ በሐዲስ መጀመሪያ ተገኝታለችን አንድም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለ ፈራጅ የሆነ ንጉሥ ሰው ሲሆን አምላክ አምላክ ሲሆን ደግሞ ሰው የሆነውን መካከለኛ ትወልደዋለችና። አንድም የጠቡ ግድግዳ የፈረሰባት ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ የታረቁባት የተቀራረቡባት የዕርቅ ሰነድ እመቤታችን ነችና መሰላል የእመቤታችን ምሳሌ ነው።
በመጻሕፍ ቅዱስ ላይም ይህ ነገር የጎላ የተረዳ ነው::..." ያዕቆብም ከቤርሳቤህ ወጥቶ ወደ ካራን ሄደ። ወደ አንድ ስፍራም ደረሰ፥ ፀሐይም ጠልቃ ነበርና ከዚያ አደረ፤ በዚያም ስፍራ ድንጋይ አነሣ፥ ከራሱም በታች ተንተርሶ በዚያ ስፍራ ተኛ። ሕልምም አለመ፤ #እነሆም_መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም_የእግዚአብሔር_መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። እነሆም፥# እግዚአብሔር በላይ ቆሞበት ነበር፥ #ዘፍ 28÷10-13
ታድያ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ አንቺ ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ሲል ግን እንደ መሰላል ተረግጧት ወጣ ማለት አይደለም የወጣው ወደ ሰማይ ነው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቁመትም እንደ ሰው ሁሉ ሦስት ክንድ ከስንዝር ብቻ ነው ።
በምሥጢር ሊናገር የፈለገው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም ነፍስን ባይነሳ ኖሮ ለመለኮት ወደ ሰማይ ዐረገ የሚልል ነገር ባልተነገረለት ነበር የሥጋን ገንዘብ ገንዘቡ ስላደረገ ውጣ ፣ከፍ ፣ከፍ አለ ዐረገ የሚሉት ነገሮች ተነገረለት ። ቅዱስ ኤፍሬም ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ብቻ ይበል እንጂ ቅሉ እመቤታችንስ ለቃል ከሰማይ ወደ ምድር ለመውረድም መሰላል ሆናዋለች። ድንግል ማርያም ባትኖር ኖሮ ከማን ሰው ይሆን ነበር? መንክር ኦ ዝ ምሥጢር!
እንዲያውም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕርገቱንና ሰው የመሆኑን ምሥጢር ሲያወዳጁ እንዲ ይላሉ"የቃል ርደት በማኅጸን የሥጋ ዕርገት በአርባ ቀን"
ምን ማለታቸው ነው ቢሉ ለቃል ርደትም ለሥጋ ዕርገትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ መሰላል ሆና ለች ያለ እመቤታችን የቃል ርደት (መውረድ) ሆነ የሥጋ ዕርገት አይታሰብምና ነው።
ክቡር ዳዊትም ይህን የሊቁን ሀሳብ የቅዱስ ኤፍሬምን ሀሳብ ሲደግፍ እንዲ ይላል። “ #በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ #ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል።” #መዝ (68) 68፥33 በምሥራቅ በኩል ማለቱ አቅጣጫን ብቻ የሚጠቁም ሳይሆን ከምሥራቅ ፀሐይ እንደሚወጣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምም ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወጣልና እመቤታችን ምሥራቀ ምሥራቃት ሞጻ ፀሐይ ትባላለችና ፀሐይ ክርስቶስ የወጣባት ምሥራቃዊ መሠላል እርሷ ነች ። መለኮት በሁሉ የመላ ፣ በሁሉ ያለ ነው የሌለበት ቦታ የለም በዚህ አለ በዚያ የለም አይባልለትም #መዝ 138(139)÷7-10 ነገር ግን የምሥራቅ የእመቤታችንን ሥጋና ነፍስ በመዋሕዱ ግን ከምድር ወደ ሰማይ ሄደ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ተባለለት ። መለኮት ዐረገ እንዲባል ምክንያትቱ ምሥራቁ ሆነችው ።
የነዚህ የዳዊትና የኤፍሬም የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ምን ይረቅ?
__#ለምን_ዐረገ ? ___
#ትንቢቱን_ለመፈጸም :-"አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ። #መዝ46(47)÷5-6 ነቢዮ ዳዊት ይህን የተናገረው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከአንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ ነው።
#ሥፍራን_ለማዘጋጀት :- መግሥተ ሠማያት ቀድማ ያልተዘጋጀች አሁን ሄዶ የሚያዘጋጃት ሆና ሳይሆን ለእናንተ ለአባቴ ብሩካኖች የተገባች ሆና በመጨረሻው ቀን ተገልጣ እንድትሰጣችሁ የማደርግ እኔ ነኝ አሁን ሄጄ በአባቴ ዕሪና (ትክክል ) በአብ ቀኝ በክብሩ ዙፋን ልቀመጥ ይገባኛል ሲል ነው “በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” #ዮሐንስ 14፥2
#መንፈስ_ቅዱስን_ለመላክ :- “እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።” #ዮሐንስ 16፥7
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ ማርያም
ሰኔ ፫/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
" #ከምድር_ወደ_ሰማይ_ለማረግ_መሰላል_ሆንሽ "
________
#ውዳሴ_ማርያም ዘ አርብ
የውዳሴ ማርያም ጸሐፊ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ ቢሆንም ቅሉ ደራሲው ግን መንፈስ ቅዱስ ነው። ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ በገለጠለት መሠረት ሊቁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ " ሲል አራቆ ጽፏል ።
አዎን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መሰላል ነች ። በመሠላል እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እላይ ያለውም ወደታች ይወርድበታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የምድራዊ ሰዎችን ጸሎትና ልመና ወደ ሰማይ አባታቸው ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ታደርሳለች ታሳርጋለች የእግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረትን ደግሞ ወደ ሰው ልጆች ታወርዳለት ፣ታመጣለችና አማናዊት መሰላል ነች። #ሊቁ_አባ_ጽጌ_ድንግል በማህሌተ ጽጌው "አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንበሌከ ማርያም የዓአርግ ሉዓሌ" #ድንግል_ማርያም_ሆይ ያላንቺ አማላጅነት ወደ ሰማይ የሚያርግ ጸሎትና ልመና የለም" እንዳለ
ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ስለ ጌታችን ዕርገት ሲናገር እንዲ ይላል "እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። " #ሉቃ 24÷50
ዕርገቱም እንደ ኤልያስ በሠረገላ እንደ ሄኖክም በመሰወር እንደ ሕዝራም ሱቱኤል በመላእክት እገዛ የሆነ አይደለም ። ደመና ከዐይናቸው ሰውራ እስክትቀበለው ድረስ ከፍ ከፍ አለ እንጂ አልጠፋባቸውም። ሰማይን አተኩረው እስኪመለከቱ ድረስ የሰማይ መላእክትም እንኪገስጾቸው ድረስ በተመስጦ ሆነው ሲያርግ አዮት እንጂ አረቀቀባቸውም በሰው አምሮ በሚረዳና በሚገባ መልኩ በርዕቀት ከነርሱ ተለይቶ ከፍ ከፍ እያለ ዐረገ ። "እናትት የገሊላ ሰዎች እንዲህ አትኩራችሁ ወደ ሰማይ የምትመለከቱ ስለምንድነው እንዲሁ ሲሄድ እንዳያችሁ እንዲሁ ደግሞ ይመጣልና" #ሐዋ1÷11
መሰላል ሁለት ትይይዮ የሆኑ ቋሚ ዘንጎች ያሉት ሲሆን በመካከላቸውም በየተወሰነ ርቀቱ በተደረደሩ አግዳሚ ዘንጎች ሁለቱ ትይዮ ዘንጎች የተጋጠሙ ናቸው ::
ሁለቱ ትይዮ የሆኑ ረጃችም ዘንጎች በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን (ድንግል በክሌ) ያመሰጥራሉ። አንድም ብሉይና ሐዲስን ሲወክሉ በመካከላቸው ያሉ ርብራብ ዘንጎች ደግሞ የብሉይና የሐዲስ መገናኛው ድልድይ እመቤታችን መሆኟን ያስረዳሉ በቡሉይ መጨረሻ በሐዲስ መጀመሪያ ተገኝታለችን አንድም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለ ፈራጅ የሆነ ንጉሥ ሰው ሲሆን አምላክ አምላክ ሲሆን ደግሞ ሰው የሆነውን መካከለኛ ትወልደዋለችና። አንድም የጠቡ ግድግዳ የፈረሰባት ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ የታረቁባት የተቀራረቡባት የዕርቅ ሰነድ እመቤታችን ነችና መሰላል የእመቤታችን ምሳሌ ነው።
በመጻሕፍ ቅዱስ ላይም ይህ ነገር የጎላ የተረዳ ነው::..." ያዕቆብም ከቤርሳቤህ ወጥቶ ወደ ካራን ሄደ። ወደ አንድ ስፍራም ደረሰ፥ ፀሐይም ጠልቃ ነበርና ከዚያ አደረ፤ በዚያም ስፍራ ድንጋይ አነሣ፥ ከራሱም በታች ተንተርሶ በዚያ ስፍራ ተኛ። ሕልምም አለመ፤ #እነሆም_መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም_የእግዚአብሔር_መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር። እነሆም፥# እግዚአብሔር በላይ ቆሞበት ነበር፥ #ዘፍ 28÷10-13
ታድያ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ አንቺ ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ሲል ግን እንደ መሰላል ተረግጧት ወጣ ማለት አይደለም የወጣው ወደ ሰማይ ነው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቁመትም እንደ ሰው ሁሉ ሦስት ክንድ ከስንዝር ብቻ ነው ።
በምሥጢር ሊናገር የፈለገው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷም ነፍስን ባይነሳ ኖሮ ለመለኮት ወደ ሰማይ ዐረገ የሚልል ነገር ባልተነገረለት ነበር የሥጋን ገንዘብ ገንዘቡ ስላደረገ ውጣ ፣ከፍ ፣ከፍ አለ ዐረገ የሚሉት ነገሮች ተነገረለት ። ቅዱስ ኤፍሬም ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ ብቻ ይበል እንጂ ቅሉ እመቤታችንስ ለቃል ከሰማይ ወደ ምድር ለመውረድም መሰላል ሆናዋለች። ድንግል ማርያም ባትኖር ኖሮ ከማን ሰው ይሆን ነበር? መንክር ኦ ዝ ምሥጢር!
እንዲያውም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ዕርገቱንና ሰው የመሆኑን ምሥጢር ሲያወዳጁ እንዲ ይላሉ"የቃል ርደት በማኅጸን የሥጋ ዕርገት በአርባ ቀን"
ምን ማለታቸው ነው ቢሉ ለቃል ርደትም ለሥጋ ዕርገትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ መሰላል ሆና ለች ያለ እመቤታችን የቃል ርደት (መውረድ) ሆነ የሥጋ ዕርገት አይታሰብምና ነው።
ክቡር ዳዊትም ይህን የሊቁን ሀሳብ የቅዱስ ኤፍሬምን ሀሳብ ሲደግፍ እንዲ ይላል። “ #በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ #ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ የኃይል ቃል የሆነ ቃሉን፥ እነሆ፥ ይሰጣል።” #መዝ (68) 68፥33 በምሥራቅ በኩል ማለቱ አቅጣጫን ብቻ የሚጠቁም ሳይሆን ከምሥራቅ ፀሐይ እንደሚወጣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምም ፀሐየ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወጣልና እመቤታችን ምሥራቀ ምሥራቃት ሞጻ ፀሐይ ትባላለችና ፀሐይ ክርስቶስ የወጣባት ምሥራቃዊ መሠላል እርሷ ነች ። መለኮት በሁሉ የመላ ፣ በሁሉ ያለ ነው የሌለበት ቦታ የለም በዚህ አለ በዚያ የለም አይባልለትም #መዝ 138(139)÷7-10 ነገር ግን የምሥራቅ የእመቤታችንን ሥጋና ነፍስ በመዋሕዱ ግን ከምድር ወደ ሰማይ ሄደ ከፍ ከፍ አለ ዐረገ ተባለለት ። መለኮት ዐረገ እንዲባል ምክንያትቱ ምሥራቁ ሆነችው ።
የነዚህ የዳዊትና የኤፍሬም የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ምን ይረቅ?
__#ለምን_ዐረገ ? ___
#ትንቢቱን_ለመፈጸም :-"አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ። #መዝ46(47)÷5-6 ነቢዮ ዳዊት ይህን የተናገረው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከአንድ ሺህ ዓመት ቀደም ብሎ ነው።
#ሥፍራን_ለማዘጋጀት :- መግሥተ ሠማያት ቀድማ ያልተዘጋጀች አሁን ሄዶ የሚያዘጋጃት ሆና ሳይሆን ለእናንተ ለአባቴ ብሩካኖች የተገባች ሆና በመጨረሻው ቀን ተገልጣ እንድትሰጣችሁ የማደርግ እኔ ነኝ አሁን ሄጄ በአባቴ ዕሪና (ትክክል ) በአብ ቀኝ በክብሩ ዙፋን ልቀመጥ ይገባኛል ሲል ነው “በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” #ዮሐንስ 14፥2
#መንፈስ_ቅዱስን_ለመላክ :- “እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።” #ዮሐንስ 16፥7
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ ማርያም
ሰኔ ፫/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም