#ሰኞ
#መርገመ_በለስ እና #አንጾሖተ_ቤተ መቅደስ
‹‹ያቺ በለስ ጌታ ወደርሷ ከመምጣቱ በፊት ለምልማ ቅጠል አውጥታ ነበር››
#ቅ/ዮሐንስ_አፈወርቅ
#በማለዳ(ሲነጋ) ወደ ከተማ(ሀገር) መጣ ሲል:- ጌታችን አዳም ወደ ወደቀበት ስፍራ ወደዚያ ሀገር መጣ፤ያን ጊዜም ተራበ መራቡም እንጀራና ሕብስትን ሳይሆን ስለ ሰው ድኅነት ተራበ ራሱ በወንጌልም ሲናገር ‹‹የእኔስ መብል የላከኝን የአባቴን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ነው እናንተም በላከኝ በአባቴ ታምኑ ዘንድ ነው ››ዮሐ4፤34 ፤ክርስቶስ ወደ ዓለም ሲመጣ እንደ ማለዳ ጸሐይ ነው (የቀትርም የአመሻሽም ያይደለ) የማለዳ ጸሐይ ጨለማውን ገፎ ነው የሚመጣው ክርስቶስም ጨለማ የተባለ ክፉ ከይሲ ዲያብሎስን በጽንሰቱ ድል እየነሳው ተገለጠ፤የማለዳ ጸሐይ እንደ ቀትር ፀሐይ አይፋጅም አይለበልብም ክርስቶስም ለዓለሙ ተመጥኖ የሕይወት ብርሃን ሆኖ ከመዓቱ ምሕረቱ የቀረበ ሆኖ የተገለጠ ነው፡፡ጌታችን በወንጌሉም “የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ የሚከተሉኝ የሕይወት ብርሃንን ያገኛል እንጂ በጨለማ ውስጥ አይመላለስም “ዮሐ8፤12 ሲል በቃሉትምህርት በተአምራቱ በደሙ ፈሳሽነት በብዙ ወገን ድኅነተ-ብርሃኑን ሊሰጠን በመምጣቱ ነው፡፡ ፀሐይ ለሁለቱም እኩል ታበራለች ስለርሷ ብርሃንነት ራሷም ትመሰክራለች ሆኖም ግን ጸሐይን ማየት የተሳነው ሕልውናዋን አይረዳም እንዲሁ ክርስቶስም ጸሐይ ሆኖ ለእስራኤል ቢመጣ ፀሐይነቱን ተረድተው ለሞቁት ለሰውነታቸው ኃይልን ለልብ ዓይናቸው ማየትን የሰጠ ነው፡፡
#የበለስ_ፍሬ ፡- የተባሉ ጉባኤ አይሁድ (ቤተ አይሁድ) ናቸው፤ጌታችንም የሃይማኖት ፍሬ ፈልጎባቸው ቢመጣ ከመጽሐፍተ ኦሪት ከነቢያት በቀር አላገኘም ፤የተጻፈውን በተግባር ፍሬ አልተመለከተባቸውም፡፡ ያንጊዜም ረገማት ቤተ አይሁድም ክርስቶስን ባለማመናቸው በኋላም እንደ ወንበዴ በመስቀላቸው ርግማንን አትርፈዋል፡፡ነገር ግን አይሁዳውያን ቢረገሙም እነርሱን ያልመሰሉትን ቀትቷቸዋል ማለት አይደለም፡፡ምክንያቱም ከቤተ አይሁድ እስጢፋኖስን የመሰለ ሰማዕት ተገኝቷል፤እነ ቅዱስ ጳውሎስን የመሰለ ሐዋርያም ተገኝቷል ‹‹ በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ ከእስራኤል ትውልድ ከብንያም ወገን ከዕብራውያን ዕብራዊ ኝ ስለ ሕግ ብትጠይቁ ፈሪሳዊ ነበርሁ›› #ፊል3፤5
#የበለስ_ፍሬ :- ጌታችን የረገማት በለስ አዳምና ሔዋንን የጣለች ዕጸ በለስ ናት፤ጌታም ለዘላለም ፍሬ አይገኝብሽ ማለት በሰው ላይ አትሰልጥኚ ብሎ ፍዳ መርገምን እንዳጠፋት አስረዳን፡፡ በርግጥ ፍዳ መርገሙን የፈጸመው በጽንሰት ጀምሮ በስቅለት ነው፡፡ በለስ ፍሬ የተባለ በሰው ላይ ሰልጥኖ የነበረ ምልዓተ ኃጢአት ነው መጽሐፍት ኃጢአትን በለስ ይሏታል፤ምክንያቱም የበለስ ቅጠል ሰፊ ደስ የምታሰኝ ናት እንዲሁም የኃጢአት መንገድ ወደ ጥፋት የምትወስድ ሰፊ በር ናት፤የበለስ ፍሬ በመብላትና በማላመጥ ጊዜ ጣፋጭ ናት እንዲሁ ኃጢአት ሲሠርዋት ደስ ታሰኛለች ከሠርዋት በኋላ ግን መከራ ታመጣለች በሚሠርዋት ጊዜ ጣፋጭ ከሠርዋት በኋላ ግን መራራ ናት፡፡ አዳምና ሔዋንም ለጊዜው በለሷ ጣፋጭና ውብ ሆና ታየቻቸው በውሃላ ግን መራራ ሞት አመጣችባቸው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹ከአመንዝራ ሴት ከንፈር ማር ይንጠባጠባልና አፍዋም ከቅ የለሰለሰ ነውና ፍጻሜዋ ግን እንደ እሬት የመረረ ነው ሁለት አፍ እንዳው ሰይም የተሳለ ነው እግሮችዋ ወደ ሞት ይወርዳሉ አረማመድዋም ወደ ሲዖል ነው›› #ምሳ5፤3-5 ማርን በቀመስናት ጊጊ ለአፍና ለጉሮሮ ጣፋጭ ናት ከዚያ በውሃላ ግን የሚጎዳ መራራ ሆኖ እናገኘዋለን፤አመንዝራም ሴት አንደበተ ለስላሳ ናት ከማር ከስኳር የሚጣፍጥ ነገርን ትናገርሃለች ወዲያውኑ መራራ ሞትም ከእርሷ ያገኝሃል ሲል ነው፡፡ አርዌ ምድር እባብም(ሰይጣን ተዋሕዷት) ሔዋንን ስትናገራት አንደበቷ የጣፈጠ ነበር፤በሽንገላዋ ግን መራራ ነበረች፡፡
#የበለስ ፍሬ:- የተባለ አዳም የበለስ ፍሬ ከበላ በውሃላ ፈርቶ የተሸሸገባት የበለስ ቅጠል ናት፡፡ ‹‹የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድ አደረጉ›› ዘፍ3፤7 አዳምና ሔዋን ፈርተው የተሸሸጉበት በለስ አስቀድሞ ዕጸ በለስን የቀጠፉባስ ዛፍ ቅጠል ነው፡፡
ነገር ግን በዚህ ቅጠል ይሸፈን ዘንድ የቁርበት ልብስ አለበሳቸው ፡፡ ጌታችን ያደረቃት በለስ ይህቺ አዳምና ሔዋን ተሸሽገውባት የነበረችውን ምክንያተ ፍዳ ወመርገም የሆነችውን ነው፡፡ ሊቁ አፈወርቅ ዕደ ወርቅ ዮሐንስ ‹‹አዳም በገነት ዕርቃኑን ሆኖ ሳለ በየትኛው ቅጠል ነበር መሸፈኛ ሰፍቶ ዕርቃኑን የሸፈነ ይህች ቅጠል እንዴት እንደደረቀች አየህን አዳም የለበሳት ዕርቃኑን የሸፈነባት አይደለችምን ጌታ ኢየሱስ ወደ ለመለመችው ዛፍ መጥቶ አዳም ዕርቃን የሸፈነባትን ቅጠል በቃ አደረቃት አዳምን ድኃ ሁኖ ስለዘገኘው ንጹሕ የሆነ የብርሃንንም
ልብስ ሰጠው ይኸውም ብርሃን ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ የተሰራ ነው ፤የበለስን ቅጠል አድርቆ የነፍስን ድኅነት ሰጠው ተድላ ደስታ ባለባት ገነት ፍጹም የሆነ የተድላ ደስታ ልብስ ተጎናጽፎ እንደ መላእክት ሕያው ሁኖ ሲኖር ከይሲ ያሳተችው አዳምን እንዴት እንደዳነ አስባለሁ›› #ግብረ_ሕማማት ገጽ 163/164 ቁ.ጀ50-54
#ፍሬ_ግን_አላገኘባትም
________________
ወንጌሉ እንዳስቀመጠው ጊዜው የፍሬ ወር አልነበረም;ለምስጢሩ ግን ወዲያውኑም ደረቀች ሲል ደግሞ ለዘመናት የሰለጠነ ፍዳ መርገም ሞት ዲያብሎስ ጠፋ ተሸረ ሲል ነው፡፡ #ኛ_ቆሮ 15÷55 ‹‹ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ፤ሲዖል ሆይ ድል መንሳትህ የት አለ››የሚለው ተፈጸመ፤ምክንያቱም አስቀድሞ በትንቢት ተነግሮ ነበርና ‹‹ከሲዖል እጅ እታደጋቸዋለሁ ከሞትም እቤዣቸዋለሁ ሞት ሆይ ቸነፈርህ ወዴት አለ ሲዖል ሆይ ማጥፋትህ ወዴት አለ ርኅራኄ ከዓይኔ ተሰወረች›› #ት.ሆሴዕ 13፤14 ክርስቶስ በሰው ላይ የሰለጠኑ ክፉ በለሶችን አድርቆ አጥፍቶልናል ይህንንም ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹‹መጥቶም ፍትወታት እያትን ኃጣውዕ ርኩሳንን አጠፋ ሁከቱን ጸጥ አደረገ ዕጸ በለስንም አድርቆ
ብሩህ በሆነ ሕይወት በሃይማኖት የበቀለውን ዕጸ መስቀል ተከለልን ›› #ግብረ_ሕማማት ገጽ 167 ቁ.104 በበለስ የመጣውንም ርግማን በዕጸ መስቀሉ ድል ነሳው ፤በለሷን ሲረግም በአንጻሩ በለስ ዕጸ መስቀልን ተከለልን፡፡
#ይህ_የከበረ የተዘረጋ መስቀል ሥሩ በምድር ጫፉ በሰማይ ያለ ቅጠሉ የማይረግፍ አበባው ለጥፋት ፍሬው ለሞት ያልሆነ ነው፡፡ባለ በገናው ነቢዩ ዳዊትም ‹‹ወይከውን ከመዕጽ እንተ ትክልት ኅበ ሙሐዘ ማይ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ ወቁጽላኒ ኢይትነገፍ -በውኃ ዳር የተተከለ በየጊዜው ፍሬውን የሚሰጥ ቅጠሉም የማይረግፍ ›› #መዝ1÷3 ክርስቶስ በዕጸ መስቀሉ ክፉ በለስ የተባሉ ዲያብሎስና ሠራዊቱን የቀጣበት ፤ዛሬም ለሚያምኑበት ወደ ሰማይ የሚያወጣ መሰላል ነው፡፡ይቺ ዕለትም መርገመ በለስ ተብላለች
#ከዚህ ቀጥሎ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደ፤ ቤተ መቅደስ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምሥያጥ /የንግድ ቤት/ ሆኖ ቢያገኘው፤ «ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች… እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት» ማቴ. 21፤13 ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸዉ፣ ገርፎም አስወጣቸዉ፣ ይህም የሚያሳየዉ ማደሪያው ቤቱ የነበርን እኛ የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታ ችንን ሁሉ እንዳራቀልን
............ #ይቆየን ..........
ግብሐት :- ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት ቤት ሰሌዳ መጽሔት
#መርገመ_በለስ እና #አንጾሖተ_ቤተ መቅደስ
‹‹ያቺ በለስ ጌታ ወደርሷ ከመምጣቱ በፊት ለምልማ ቅጠል አውጥታ ነበር››
#ቅ/ዮሐንስ_አፈወርቅ
#በማለዳ(ሲነጋ) ወደ ከተማ(ሀገር) መጣ ሲል:- ጌታችን አዳም ወደ ወደቀበት ስፍራ ወደዚያ ሀገር መጣ፤ያን ጊዜም ተራበ መራቡም እንጀራና ሕብስትን ሳይሆን ስለ ሰው ድኅነት ተራበ ራሱ በወንጌልም ሲናገር ‹‹የእኔስ መብል የላከኝን የአባቴን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ነው እናንተም በላከኝ በአባቴ ታምኑ ዘንድ ነው ››ዮሐ4፤34 ፤ክርስቶስ ወደ ዓለም ሲመጣ እንደ ማለዳ ጸሐይ ነው (የቀትርም የአመሻሽም ያይደለ) የማለዳ ጸሐይ ጨለማውን ገፎ ነው የሚመጣው ክርስቶስም ጨለማ የተባለ ክፉ ከይሲ ዲያብሎስን በጽንሰቱ ድል እየነሳው ተገለጠ፤የማለዳ ጸሐይ እንደ ቀትር ፀሐይ አይፋጅም አይለበልብም ክርስቶስም ለዓለሙ ተመጥኖ የሕይወት ብርሃን ሆኖ ከመዓቱ ምሕረቱ የቀረበ ሆኖ የተገለጠ ነው፡፡ጌታችን በወንጌሉም “የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ የሚከተሉኝ የሕይወት ብርሃንን ያገኛል እንጂ በጨለማ ውስጥ አይመላለስም “ዮሐ8፤12 ሲል በቃሉትምህርት በተአምራቱ በደሙ ፈሳሽነት በብዙ ወገን ድኅነተ-ብርሃኑን ሊሰጠን በመምጣቱ ነው፡፡ ፀሐይ ለሁለቱም እኩል ታበራለች ስለርሷ ብርሃንነት ራሷም ትመሰክራለች ሆኖም ግን ጸሐይን ማየት የተሳነው ሕልውናዋን አይረዳም እንዲሁ ክርስቶስም ጸሐይ ሆኖ ለእስራኤል ቢመጣ ፀሐይነቱን ተረድተው ለሞቁት ለሰውነታቸው ኃይልን ለልብ ዓይናቸው ማየትን የሰጠ ነው፡፡
#የበለስ_ፍሬ ፡- የተባሉ ጉባኤ አይሁድ (ቤተ አይሁድ) ናቸው፤ጌታችንም የሃይማኖት ፍሬ ፈልጎባቸው ቢመጣ ከመጽሐፍተ ኦሪት ከነቢያት በቀር አላገኘም ፤የተጻፈውን በተግባር ፍሬ አልተመለከተባቸውም፡፡ ያንጊዜም ረገማት ቤተ አይሁድም ክርስቶስን ባለማመናቸው በኋላም እንደ ወንበዴ በመስቀላቸው ርግማንን አትርፈዋል፡፡ነገር ግን አይሁዳውያን ቢረገሙም እነርሱን ያልመሰሉትን ቀትቷቸዋል ማለት አይደለም፡፡ምክንያቱም ከቤተ አይሁድ እስጢፋኖስን የመሰለ ሰማዕት ተገኝቷል፤እነ ቅዱስ ጳውሎስን የመሰለ ሐዋርያም ተገኝቷል ‹‹ በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ ከእስራኤል ትውልድ ከብንያም ወገን ከዕብራውያን ዕብራዊ ኝ ስለ ሕግ ብትጠይቁ ፈሪሳዊ ነበርሁ›› #ፊል3፤5
#የበለስ_ፍሬ :- ጌታችን የረገማት በለስ አዳምና ሔዋንን የጣለች ዕጸ በለስ ናት፤ጌታም ለዘላለም ፍሬ አይገኝብሽ ማለት በሰው ላይ አትሰልጥኚ ብሎ ፍዳ መርገምን እንዳጠፋት አስረዳን፡፡ በርግጥ ፍዳ መርገሙን የፈጸመው በጽንሰት ጀምሮ በስቅለት ነው፡፡ በለስ ፍሬ የተባለ በሰው ላይ ሰልጥኖ የነበረ ምልዓተ ኃጢአት ነው መጽሐፍት ኃጢአትን በለስ ይሏታል፤ምክንያቱም የበለስ ቅጠል ሰፊ ደስ የምታሰኝ ናት እንዲሁም የኃጢአት መንገድ ወደ ጥፋት የምትወስድ ሰፊ በር ናት፤የበለስ ፍሬ በመብላትና በማላመጥ ጊዜ ጣፋጭ ናት እንዲሁ ኃጢአት ሲሠርዋት ደስ ታሰኛለች ከሠርዋት በኋላ ግን መከራ ታመጣለች በሚሠርዋት ጊዜ ጣፋጭ ከሠርዋት በኋላ ግን መራራ ናት፡፡ አዳምና ሔዋንም ለጊዜው በለሷ ጣፋጭና ውብ ሆና ታየቻቸው በውሃላ ግን መራራ ሞት አመጣችባቸው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹ከአመንዝራ ሴት ከንፈር ማር ይንጠባጠባልና አፍዋም ከቅ የለሰለሰ ነውና ፍጻሜዋ ግን እንደ እሬት የመረረ ነው ሁለት አፍ እንዳው ሰይም የተሳለ ነው እግሮችዋ ወደ ሞት ይወርዳሉ አረማመድዋም ወደ ሲዖል ነው›› #ምሳ5፤3-5 ማርን በቀመስናት ጊጊ ለአፍና ለጉሮሮ ጣፋጭ ናት ከዚያ በውሃላ ግን የሚጎዳ መራራ ሆኖ እናገኘዋለን፤አመንዝራም ሴት አንደበተ ለስላሳ ናት ከማር ከስኳር የሚጣፍጥ ነገርን ትናገርሃለች ወዲያውኑ መራራ ሞትም ከእርሷ ያገኝሃል ሲል ነው፡፡ አርዌ ምድር እባብም(ሰይጣን ተዋሕዷት) ሔዋንን ስትናገራት አንደበቷ የጣፈጠ ነበር፤በሽንገላዋ ግን መራራ ነበረች፡፡
#የበለስ ፍሬ:- የተባለ አዳም የበለስ ፍሬ ከበላ በውሃላ ፈርቶ የተሸሸገባት የበለስ ቅጠል ናት፡፡ ‹‹የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደሆኑ አወቁ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድ አደረጉ›› ዘፍ3፤7 አዳምና ሔዋን ፈርተው የተሸሸጉበት በለስ አስቀድሞ ዕጸ በለስን የቀጠፉባስ ዛፍ ቅጠል ነው፡፡
ነገር ግን በዚህ ቅጠል ይሸፈን ዘንድ የቁርበት ልብስ አለበሳቸው ፡፡ ጌታችን ያደረቃት በለስ ይህቺ አዳምና ሔዋን ተሸሽገውባት የነበረችውን ምክንያተ ፍዳ ወመርገም የሆነችውን ነው፡፡ ሊቁ አፈወርቅ ዕደ ወርቅ ዮሐንስ ‹‹አዳም በገነት ዕርቃኑን ሆኖ ሳለ በየትኛው ቅጠል ነበር መሸፈኛ ሰፍቶ ዕርቃኑን የሸፈነ ይህች ቅጠል እንዴት እንደደረቀች አየህን አዳም የለበሳት ዕርቃኑን የሸፈነባት አይደለችምን ጌታ ኢየሱስ ወደ ለመለመችው ዛፍ መጥቶ አዳም ዕርቃን የሸፈነባትን ቅጠል በቃ አደረቃት አዳምን ድኃ ሁኖ ስለዘገኘው ንጹሕ የሆነ የብርሃንንም
ልብስ ሰጠው ይኸውም ብርሃን ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ የተሰራ ነው ፤የበለስን ቅጠል አድርቆ የነፍስን ድኅነት ሰጠው ተድላ ደስታ ባለባት ገነት ፍጹም የሆነ የተድላ ደስታ ልብስ ተጎናጽፎ እንደ መላእክት ሕያው ሁኖ ሲኖር ከይሲ ያሳተችው አዳምን እንዴት እንደዳነ አስባለሁ›› #ግብረ_ሕማማት ገጽ 163/164 ቁ.ጀ50-54
#ፍሬ_ግን_አላገኘባትም
________________
ወንጌሉ እንዳስቀመጠው ጊዜው የፍሬ ወር አልነበረም;ለምስጢሩ ግን ወዲያውኑም ደረቀች ሲል ደግሞ ለዘመናት የሰለጠነ ፍዳ መርገም ሞት ዲያብሎስ ጠፋ ተሸረ ሲል ነው፡፡ #ኛ_ቆሮ 15÷55 ‹‹ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ፤ሲዖል ሆይ ድል መንሳትህ የት አለ››የሚለው ተፈጸመ፤ምክንያቱም አስቀድሞ በትንቢት ተነግሮ ነበርና ‹‹ከሲዖል እጅ እታደጋቸዋለሁ ከሞትም እቤዣቸዋለሁ ሞት ሆይ ቸነፈርህ ወዴት አለ ሲዖል ሆይ ማጥፋትህ ወዴት አለ ርኅራኄ ከዓይኔ ተሰወረች›› #ት.ሆሴዕ 13፤14 ክርስቶስ በሰው ላይ የሰለጠኑ ክፉ በለሶችን አድርቆ አጥፍቶልናል ይህንንም ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹‹መጥቶም ፍትወታት እያትን ኃጣውዕ ርኩሳንን አጠፋ ሁከቱን ጸጥ አደረገ ዕጸ በለስንም አድርቆ
ብሩህ በሆነ ሕይወት በሃይማኖት የበቀለውን ዕጸ መስቀል ተከለልን ›› #ግብረ_ሕማማት ገጽ 167 ቁ.104 በበለስ የመጣውንም ርግማን በዕጸ መስቀሉ ድል ነሳው ፤በለሷን ሲረግም በአንጻሩ በለስ ዕጸ መስቀልን ተከለልን፡፡
#ይህ_የከበረ የተዘረጋ መስቀል ሥሩ በምድር ጫፉ በሰማይ ያለ ቅጠሉ የማይረግፍ አበባው ለጥፋት ፍሬው ለሞት ያልሆነ ነው፡፡ባለ በገናው ነቢዩ ዳዊትም ‹‹ወይከውን ከመዕጽ እንተ ትክልት ኅበ ሙሐዘ ማይ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ ወቁጽላኒ ኢይትነገፍ -በውኃ ዳር የተተከለ በየጊዜው ፍሬውን የሚሰጥ ቅጠሉም የማይረግፍ ›› #መዝ1÷3 ክርስቶስ በዕጸ መስቀሉ ክፉ በለስ የተባሉ ዲያብሎስና ሠራዊቱን የቀጣበት ፤ዛሬም ለሚያምኑበት ወደ ሰማይ የሚያወጣ መሰላል ነው፡፡ይቺ ዕለትም መርገመ በለስ ተብላለች
#ከዚህ ቀጥሎ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደ፤ ቤተ መቅደስ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምሥያጥ /የንግድ ቤት/ ሆኖ ቢያገኘው፤ «ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች… እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት» ማቴ. 21፤13 ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸዉ፣ ገርፎም አስወጣቸዉ፣ ይህም የሚያሳየዉ ማደሪያው ቤቱ የነበርን እኛ የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታ ችንን ሁሉ እንዳራቀልን
............ #ይቆየን ..........
ግብሐት :- ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት ቤት ሰሌዳ መጽሔት
ዐውደ ምሕረት
Photo
#እንኳን_ደስ አሎት ! #ሙሐዘ_ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት !
#በነጋውም ንጉሡ ማልዶ ተነሣ፥ ፈጥኖም ወደ አንበሶች ጕድጓድ ሄደ።
ወደ ጕድጓዱም ወደ ዳንኤል በቀረበ ጊዜ በኀዘን ቃል ጠራው፤ ንጉሡም ተናገረ ዳንኤልንም፦ የሕያው አምላክ ባሪያ ዳንኤል ሆይ፥ #ሁልጊዜ_የምታመልከው_አምላክህ_ከአንበሶች_ያድንህ_ዘንድ ችሎአልን? አለው።
#ዳንኤልም ንጉሡን፦ ንጉሥ ሆይ፥ ሺህ ዓመት ንገሥ። በፊቱ ቅንነት ተገኝቶብኛልና፥ በአንተም ፊት ደግሞ፥ ንጉሥ ሆይ፥ አልበደልሁምና #አምላኬ_መልአኩን_ልኮ_የአንበሶችን_አፍ_ዘጋ እነርሱም #አልጐዱኝም አለው።
___ #ት.ዳን 6÷19-22_____
#በነጋውም ንጉሡ ማልዶ ተነሣ፥ ፈጥኖም ወደ አንበሶች ጕድጓድ ሄደ።
ወደ ጕድጓዱም ወደ ዳንኤል በቀረበ ጊዜ በኀዘን ቃል ጠራው፤ ንጉሡም ተናገረ ዳንኤልንም፦ የሕያው አምላክ ባሪያ ዳንኤል ሆይ፥ #ሁልጊዜ_የምታመልከው_አምላክህ_ከአንበሶች_ያድንህ_ዘንድ ችሎአልን? አለው።
#ዳንኤልም ንጉሡን፦ ንጉሥ ሆይ፥ ሺህ ዓመት ንገሥ። በፊቱ ቅንነት ተገኝቶብኛልና፥ በአንተም ፊት ደግሞ፥ ንጉሥ ሆይ፥ አልበደልሁምና #አምላኬ_መልአኩን_ልኮ_የአንበሶችን_አፍ_ዘጋ እነርሱም #አልጐዱኝም አለው።
___ #ት.ዳን 6÷19-22_____
" #በእናቴ ስም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲታነጽ ፍቃዴ ነው"
_________________________
#እመቤታች_ቅድስት_ድንግል_ማርያም እንደ ልጇ ባለ ሞት ሞታ እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ከሞት ተነስታ ባረገች በ4ዓመቷ ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ፊልጵስዮስ ገብተው አስተማሩ ሕዝቡም አምነው ተጠመቁ። ከእግዲህ ወደ ቤተ ጣዖት አትሂዱ አሏቸው የለመድነውን ከከለከላችሁንማ መካነ ጸሎት(የጸሎት ቦታ) ስጡን ፣ ሥሩልን አሏቸው።
#በእውነቱ የሚገባ ጥያቄ ነው ! አንድ ውኃ የያዘ ብርጭቆን ውኃውን ከገለበጥንለት በኋላ ባዶዎን የሚቀመጥ አይደለም ምንም እንኳ በዐይን ባናየውም በእርሱ ፋንታ ብርጭቆውን አየር ይሞላዋል። ሰውም እንዲሁ ነው ሲሰራው የነበረን አንድ ክፉ ልማድ ከሕይወቱ ሲያስወጣ በዛ ባስወጣው ቦታ ሌላ ሰናይ የሆነ ነገርን ሊተካበት ይገባል ።ካልሆነ ግን ክፉ መስራት ትቻለው ደግ ባልሰራ ችግር የለውም ብሎ ክፋትን ትቶ በጎንም ሳይሰሩ መቀመጥ አያጸድቅም " መልካም ሥራ መሥራትን እያወቀ ለማይሰራት ኃጢያት ትሆንበታለችና"
በተጨማሪም ያን ክፉሁን አስወጥቻለው ብሎ ያለ ደግ ሥራ የተቀመጠው ሰው ቤቱን ባዶ አድርጎ እንደጠረገ ሰው ይመስላል ከእርሱ የወጣ አጋንንትም በምድረ በዳ ሲዞር ቆይቶ የዚያ ሰው ቤት(ቤተ ልቡናው) በደግ ሥራ ያልተሞላ ሆኖ ሲመለከት ወደ ቀደመ ቤቴ ልመለስ ይልና ከእርሱ የከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትይ ይዞ ተመልሶ ይገባበታል ለሰውየውም ከድሮ ይልቅ የአሁኑ ሕይወቱ የከፋ ይሁንበታል #ማቴ 12÷45 #ሉቃ 10÷26
#የፊልጵስዮስ አማኞች ጥያቄ የተገባ ነው ያልነው ለዚሁ ነው ሰው ወደ ቤተ ጣዖት መሄዱን ሲያቆም በአንጻሩ በዚያ ፈንታ ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሄድ መጀመር አለበት አለበለዚያ ግን ከቤተ ጣዖት ከቀረው ወደ ቤተ እግዚአብሔር ባልሄድም ችግር የለውም ማለት አይገባውም እርሱ ወደ ቤተ ጣዖት መሄድ አቆመ ማለት የቤተ ጣዖቱ ሥርዓትና ልማድ በሀሳብ ሁሉ ወደ እርሱ መምጣታቸው አቆሙ ማለት አይደለምና።
ቤተ መቅደስ እንዲሰሩላቸው የተጠየቁት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ምንም እንኳ ጥያቄው የተገባና ደገኛ ጥያቄ ቢሆንም ማንንም ሳያማክሩ በራሳቸው ውሳኔ መሠረት ጣሉ ግድግዳ ለስኑ ጣራ ክደኑ መስቀል አኑሩ ቤተ ክርስቲያን ተከሉ ብለው ወዲያው አላዘዙም። ከዛይ ይልቅ ወደ ወንድሞቻቸው ወደ ጴጥሮስና ወደ ዮሐንስ የፊልጵስዮስ አማኞች ቤተ መቅደስ እንድንሰራላቸው ጠየቁን ምን ይሻላል ? ብለው መልክት ላኩባቸው እነርሱም ያለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቃድ አንዳች ልታደርጎ አይገባም እናንተም ጸልዮ እኛም እንጸልያለን ብለው መለሱላቸው። ቤተ መቅደስ ዝም ተብላ አትሰራም፣ አትተከልም" ሁሉ በአግባቡና በሥርዓት ይሁን" እንደተባለ በአግባቡና በሥርዓት ልትሰራ ያስፈልጋታል 1ኛ ቆሮ 14፥40
#ቤተ_መቅደስ ወይም ቤተ እግዚአብሔር ለመሥራት በመጀመሪያ ፈቃደ እግዚአብሔርን በጾም በጸሎት መጠየቅ ይገባል ። እንደ ቅድስ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ ለሰው ልጆች ቤዛ ሲል በመስቀሉ ብዙ ደም አፍስሷል ይህንንም ደም ቅዱስ ዑራኤል መላእክ በጽዋው ቀድቶ በብርሃን መነሳንስ ፍጥረት ዓለሙን ለመቀደስ ወደ ምድር እረጭቶታል። ታድያ ቤተ ክርስቲያን ስትሰራ ይህ የደሙ ነጠብጣብ ባለበት ወይም በነጠበበት ቦታ ላይ መሆን አለበት እስካሁን የተሰሩ ቤተ ክርስቲያናት ሁሉ እግዚአብሔር ባወቀ ለቅዱሳኑ በመግለጥ የተሰሩ ናቸው ታዲያ ይህን መሰሉን ቦታ ለማወቅ ከእግዚአብሔር ጋር በጸም በጸሎት መነጋገር ፍቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "ያለ እኔ አንዳች ልታደርጉ አይቻላችሁም" #ዮሐ 15÷5
ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስም የቅዱስ ጴጥሮስን እና የቅዱስ ዮሐንስ ምክር ተቀብለው በያሉበት ሱባዔ ያዙ ጾም ጸሎት በማድረግ ፍቃደ እግዚአብሔር ጠየቁ ሰባዔያቸውን ሲጨርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሩቅም ከቅርብም ያሉ ሐዋርያቱን በደመና እየጫነ በፊልጵስዮስ ከተማ ሰበሰባቸው። ቅዱስ ዮሐንስም ጌታዬ ስለምን ሰበሰብከን ብሎ ጠየቀው በእናቴ ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰራ ፍቃዴ ነው አሁንም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ሰበሰብኳቹ አለው።
#ከዚያም ምሳሌዋ ወደሆነው ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ወሰዳቸው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ሕዝቅኤት በትንቢቱ “ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ብሎ እንደጻፈ....።” #ት.ሕዝ 44፥1 በዚያም ተራርቀው የነበሩ ሦስት ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቧ ቁመቱን ወርዱን መጥኞ ሰጣቸው እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው ሳለ እየለመለመ ቁመቱ 24 ወርዱም12 ክንድ አድርጎ ሰርቶ አሳይቷቸዋል።
"ወይዜኒ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ" እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ ብሏቸው ዐረገ ። ዛሬም በቅድስሀ ቅዱሳን በእናቱና በድንግል ማርያም ስም እና በቅዱሳኑ ሰም ለምን ቤተ መቅደስ ትሠራላችሁ ፣ ለምን ታቦት ትቀርጻላችሁ ለሚሉን ሁሉ ልጇ ሰርቶ ስላሳየንና ፍቃዱ ስለሆነ ይልቁኑ እናንተም እንዲሁ ሥሩ እንላቸዋለን ።“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።” #ኢሳ 56፥5
#ቤቴ አላት ቤተ ክርስቲያንን በቅጥሬም ውጥ አለ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚታነጹ ጠቀል እና ጠበል ቤት፣ቤተ ልሔም ፣ ደውል ቤት ፣ሕሙማን ማረፊያ፣ ክርስትና ቤት ፍትሐት ቤት ግምጃ ቤት፣ወዘተ የመሳሰሉን በእናቴና በቅዱሳኖቼ ሰም ቢሰየም እወዳለው ፍቃዴ ነው ሲል ነው።
የእመቤታችን ቤተ ክርሰቲያን፣ የእመቤታችን ጽላት ፣የእመቤታችን ጠበል ፣የእመቤታችን እምነት ማለታችን ትክክል የሆነ ሁሉም በምስጢርና በምክንያት የሆነ ነው ።
#የጀመርነውን ለመጨረስ ያክል ሰኔ 20ቀን ጻሕጻ ቤተ ክርስቲያኗን ሰርቶ ከሰጣቸው በኋላ በማግስቱ ሰኔ 21ቀን በዛችሁ ቤተ መቅደስ እመቤታችንን መንበር ቅዱስ ጴጥሮስን ተራዲኢ ካህን(ንፍቅ) ካህን ፣ እስጢፋኖስን ሰራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል ።ዳግመኛም ቅዱስ ጴጥሮስን እጁን ጭኞ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል በዚህ ጊዜ ሰማያዊያን መላእክት ምድራዊያን ሐዋርያት በአንድነት ሆነው ይሰብሖ ለእግዚአብሔር እያሉ አመስግነዋል ።
______ይቆየን__________
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የልጇ የወዳጇ የኢየሱስ ክርስቶስም ቸርነት የቅዱሳኑም ሁሉ ረድኤትና በረከት አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ 21/2013 ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
_________________________
#እመቤታች_ቅድስት_ድንግል_ማርያም እንደ ልጇ ባለ ሞት ሞታ እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ከሞት ተነስታ ባረገች በ4ዓመቷ ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ፊልጵስዮስ ገብተው አስተማሩ ሕዝቡም አምነው ተጠመቁ። ከእግዲህ ወደ ቤተ ጣዖት አትሂዱ አሏቸው የለመድነውን ከከለከላችሁንማ መካነ ጸሎት(የጸሎት ቦታ) ስጡን ፣ ሥሩልን አሏቸው።
#በእውነቱ የሚገባ ጥያቄ ነው ! አንድ ውኃ የያዘ ብርጭቆን ውኃውን ከገለበጥንለት በኋላ ባዶዎን የሚቀመጥ አይደለም ምንም እንኳ በዐይን ባናየውም በእርሱ ፋንታ ብርጭቆውን አየር ይሞላዋል። ሰውም እንዲሁ ነው ሲሰራው የነበረን አንድ ክፉ ልማድ ከሕይወቱ ሲያስወጣ በዛ ባስወጣው ቦታ ሌላ ሰናይ የሆነ ነገርን ሊተካበት ይገባል ።ካልሆነ ግን ክፉ መስራት ትቻለው ደግ ባልሰራ ችግር የለውም ብሎ ክፋትን ትቶ በጎንም ሳይሰሩ መቀመጥ አያጸድቅም " መልካም ሥራ መሥራትን እያወቀ ለማይሰራት ኃጢያት ትሆንበታለችና"
በተጨማሪም ያን ክፉሁን አስወጥቻለው ብሎ ያለ ደግ ሥራ የተቀመጠው ሰው ቤቱን ባዶ አድርጎ እንደጠረገ ሰው ይመስላል ከእርሱ የወጣ አጋንንትም በምድረ በዳ ሲዞር ቆይቶ የዚያ ሰው ቤት(ቤተ ልቡናው) በደግ ሥራ ያልተሞላ ሆኖ ሲመለከት ወደ ቀደመ ቤቴ ልመለስ ይልና ከእርሱ የከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትይ ይዞ ተመልሶ ይገባበታል ለሰውየውም ከድሮ ይልቅ የአሁኑ ሕይወቱ የከፋ ይሁንበታል #ማቴ 12÷45 #ሉቃ 10÷26
#የፊልጵስዮስ አማኞች ጥያቄ የተገባ ነው ያልነው ለዚሁ ነው ሰው ወደ ቤተ ጣዖት መሄዱን ሲያቆም በአንጻሩ በዚያ ፈንታ ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሄድ መጀመር አለበት አለበለዚያ ግን ከቤተ ጣዖት ከቀረው ወደ ቤተ እግዚአብሔር ባልሄድም ችግር የለውም ማለት አይገባውም እርሱ ወደ ቤተ ጣዖት መሄድ አቆመ ማለት የቤተ ጣዖቱ ሥርዓትና ልማድ በሀሳብ ሁሉ ወደ እርሱ መምጣታቸው አቆሙ ማለት አይደለምና።
ቤተ መቅደስ እንዲሰሩላቸው የተጠየቁት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ምንም እንኳ ጥያቄው የተገባና ደገኛ ጥያቄ ቢሆንም ማንንም ሳያማክሩ በራሳቸው ውሳኔ መሠረት ጣሉ ግድግዳ ለስኑ ጣራ ክደኑ መስቀል አኑሩ ቤተ ክርስቲያን ተከሉ ብለው ወዲያው አላዘዙም። ከዛይ ይልቅ ወደ ወንድሞቻቸው ወደ ጴጥሮስና ወደ ዮሐንስ የፊልጵስዮስ አማኞች ቤተ መቅደስ እንድንሰራላቸው ጠየቁን ምን ይሻላል ? ብለው መልክት ላኩባቸው እነርሱም ያለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቃድ አንዳች ልታደርጎ አይገባም እናንተም ጸልዮ እኛም እንጸልያለን ብለው መለሱላቸው። ቤተ መቅደስ ዝም ተብላ አትሰራም፣ አትተከልም" ሁሉ በአግባቡና በሥርዓት ይሁን" እንደተባለ በአግባቡና በሥርዓት ልትሰራ ያስፈልጋታል 1ኛ ቆሮ 14፥40
#ቤተ_መቅደስ ወይም ቤተ እግዚአብሔር ለመሥራት በመጀመሪያ ፈቃደ እግዚአብሔርን በጾም በጸሎት መጠየቅ ይገባል ። እንደ ቅድስ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ ለሰው ልጆች ቤዛ ሲል በመስቀሉ ብዙ ደም አፍስሷል ይህንንም ደም ቅዱስ ዑራኤል መላእክ በጽዋው ቀድቶ በብርሃን መነሳንስ ፍጥረት ዓለሙን ለመቀደስ ወደ ምድር እረጭቶታል። ታድያ ቤተ ክርስቲያን ስትሰራ ይህ የደሙ ነጠብጣብ ባለበት ወይም በነጠበበት ቦታ ላይ መሆን አለበት እስካሁን የተሰሩ ቤተ ክርስቲያናት ሁሉ እግዚአብሔር ባወቀ ለቅዱሳኑ በመግለጥ የተሰሩ ናቸው ታዲያ ይህን መሰሉን ቦታ ለማወቅ ከእግዚአብሔር ጋር በጸም በጸሎት መነጋገር ፍቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "ያለ እኔ አንዳች ልታደርጉ አይቻላችሁም" #ዮሐ 15÷5
ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስም የቅዱስ ጴጥሮስን እና የቅዱስ ዮሐንስ ምክር ተቀብለው በያሉበት ሱባዔ ያዙ ጾም ጸሎት በማድረግ ፍቃደ እግዚአብሔር ጠየቁ ሰባዔያቸውን ሲጨርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሩቅም ከቅርብም ያሉ ሐዋርያቱን በደመና እየጫነ በፊልጵስዮስ ከተማ ሰበሰባቸው። ቅዱስ ዮሐንስም ጌታዬ ስለምን ሰበሰብከን ብሎ ጠየቀው በእናቴ ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰራ ፍቃዴ ነው አሁንም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ሰበሰብኳቹ አለው።
#ከዚያም ምሳሌዋ ወደሆነው ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ወሰዳቸው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ሕዝቅኤት በትንቢቱ “ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ብሎ እንደጻፈ....።” #ት.ሕዝ 44፥1 በዚያም ተራርቀው የነበሩ ሦስት ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቧ ቁመቱን ወርዱን መጥኞ ሰጣቸው እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው ሳለ እየለመለመ ቁመቱ 24 ወርዱም12 ክንድ አድርጎ ሰርቶ አሳይቷቸዋል።
"ወይዜኒ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ" እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ ብሏቸው ዐረገ ። ዛሬም በቅድስሀ ቅዱሳን በእናቱና በድንግል ማርያም ስም እና በቅዱሳኑ ሰም ለምን ቤተ መቅደስ ትሠራላችሁ ፣ ለምን ታቦት ትቀርጻላችሁ ለሚሉን ሁሉ ልጇ ሰርቶ ስላሳየንና ፍቃዱ ስለሆነ ይልቁኑ እናንተም እንዲሁ ሥሩ እንላቸዋለን ።“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።” #ኢሳ 56፥5
#ቤቴ አላት ቤተ ክርስቲያንን በቅጥሬም ውጥ አለ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚታነጹ ጠቀል እና ጠበል ቤት፣ቤተ ልሔም ፣ ደውል ቤት ፣ሕሙማን ማረፊያ፣ ክርስትና ቤት ፍትሐት ቤት ግምጃ ቤት፣ወዘተ የመሳሰሉን በእናቴና በቅዱሳኖቼ ሰም ቢሰየም እወዳለው ፍቃዴ ነው ሲል ነው።
የእመቤታችን ቤተ ክርሰቲያን፣ የእመቤታችን ጽላት ፣የእመቤታችን ጠበል ፣የእመቤታችን እምነት ማለታችን ትክክል የሆነ ሁሉም በምስጢርና በምክንያት የሆነ ነው ።
#የጀመርነውን ለመጨረስ ያክል ሰኔ 20ቀን ጻሕጻ ቤተ ክርስቲያኗን ሰርቶ ከሰጣቸው በኋላ በማግስቱ ሰኔ 21ቀን በዛችሁ ቤተ መቅደስ እመቤታችንን መንበር ቅዱስ ጴጥሮስን ተራዲኢ ካህን(ንፍቅ) ካህን ፣ እስጢፋኖስን ሰራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል ።ዳግመኛም ቅዱስ ጴጥሮስን እጁን ጭኞ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል በዚህ ጊዜ ሰማያዊያን መላእክት ምድራዊያን ሐዋርያት በአንድነት ሆነው ይሰብሖ ለእግዚአብሔር እያሉ አመስግነዋል ።
______ይቆየን__________
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የልጇ የወዳጇ የኢየሱስ ክርስቶስም ቸርነት የቅዱሳኑም ሁሉ ረድኤትና በረከት አይለየን !
አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ 21/2013 ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም