አትሮኖስ
280K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
471 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሰን። ፍቅርን አንድነትን መቻቻልን መተሳሰብን እመኛለው። መጪው ዘመን ፀዓዳ የተላበሰ እንደ አደይ ያበበ ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቴ ነው።
#መልካም #አዲስ #ዓመት! 5/13/10
#ሁቱትሲ


#ምዕራፍ_አስራ_ሁለት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ


#አዲስ_መንገድ


#የነጻነት_ሕመም

የምሽቱ ድባብ የማልቆጣጠረው ስሜት አሳደረብኝ፡፡ የአየሩ ቅዝቃዜ ቆዳዬን ሲነካው፣ ለሳንባዎቼ አየሩ ሲቀላቸው፣ በዓይኔ ላይ የሚጨፍሩት እልፍ አዕላፍ ክዋክብት በውበታቸው ሲያፈዙኝ ነፍሴን ‹‹ተመስገን አምላኬ!›› ብላ እንድትዘምር አደረጓት፡፡
‹‹ምን ላይ ነው ያፈጠጥሺው? እንሂድ እንጂ - በአስቸኳይ መሄድ
አለብን!›› ሲሉ የመጀመሪያዋን የነጻነት መጠጥ እንደተጎነጨሁ ቄስ ሙሪንዚ ትዕግሥት አጥተው ሾር ብዬ እንድሄድ ተናገሩ፡፡ ቄሱ ከሌሎቹ ሴቶችና ወደ ፈረንሳዮች ምሽግ አብሮን ሊሄድ ከተነሣው ከዮሃንስ ጋር በሩ ጋ ይጠብቁናል፡፡ ዮሃንስ በጣም አረፈደ እንጂ መባነኑና እፊት እፊት ማለቱ ባልከፋ፡፡ በዚህ ጊዜ ከዘር ጭፍጨፋው መትረፌንም ሆነ ንጋትን እንደገና ለማየት መቻሌን አላወቅሁም - የግንኙነታችንም መሞት አልታወቀኝ፡፡ ቄሱ በራቸውን ሲከፍቱት ከቤት ወንድ ልጆቻቸው (ከሴምቤባ በስተቀር) ጦሮች፣ ቢላዎችና ቀስቶች ይዘው ወጡ፡፡ ዙሪያችንን በሚገባ ከበው በሩን አስወጡን፡፡ ከጠርጣራ ወንድ የቤት ሠራተኞቻቸውና ክፉ ጎረቤቶቻቸው አደገኛ ዓይኖች ከለሉን፡፡ ከዚያም ወደ ውጪ ወጣንና ወደ መታጠቢያ ቤቱ ከሦስት ወራት በፊት ባመጣኝ በአቧራማው የእግር መንገድ በፍጥነት ተራመድን፡፡ ዓይኖቼ ጨለማውን እየተላመዱት ሲሄዱም ቄስ ሙሪንዚም ሆኑ ዮሃንስ እንደታጠቁ አየሁ፤ ዮሃንስ ረጅም ጦር የያዘ ሲሆን ቄሱ በበኩላቸው ጠመንጃቸውን በትከሻቸው አንግተዋል፡፡ የገዳዮች ቡድን መንገዳችን ላይ ቢያጋጥመን ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ አሰብኩ፡፡ ሰዎች በመንገዱ ሌላኛው አቅጣጫ ከጨለማው ውስጥ ብቅ ሲሉ በድንገት አየናቸው፡፡ ምን አልባትም 60 የሚሆኑ ኢንተርሃምዌዎች በሁለት መስመሮች በሰልፍ ይመጣሉ፡፡ አስፈሪ የደንብ ልብሶቻቸውን ያልለበሱ ቢሆንም ቅሉ ትዕይንቱ ያስበረግጋል፡- እስካፍንጫቸው ታጥቀው በፍጥነት ይጓዛሉ፤ ገጀራዎችን፣ ጠመንጃዎችን፣ ቦንቦችን፣ ጦሮችንና ረጃጅም ማረጃ ቢላዎቻቸውን ይዘው ወደ እኛ በመጠጋት ላይ ናቸው - አንደኛው እንዲያውም ቀስት ይዟል፡፡በአጠገባቸው በጣም ተጠግተን ስለሄድን እንዲያውም የሰውነታቸውን ጠረንና ከትንፋሻቸው የሚመጣውን የሚተናፈግ አልኮል ሳይቀር ማሽተት ችያለሁ፡፡ በሚገርም ሁኔታ በመታጠቢያ ቤቱ ከእነርሱ ተደብቄ ከነበርኩበት ጊዜ ይልቅ በአጠገባቸው ሳልፍ በአንጻራዊነት ፍርሃቴ ቀንሷል፡፡ በዚህም ጊዜ እግዚአብሔርን በደኅና እንዲያቆየንና ፍራቻዬን እንዲያረግብልኝ ለመንኩት፡፡
ሌሎቹ ሴቶችና እኔ ኢንተርሃምዌዎቹ ሴቶች መሆናችንን እንዳይለዩ በማለት በቡድን አጀባችን መካከል ራሳችንን ዝቅ አደረግን፡፡ ያለ ምንም ችግርም አለፍን፡፡ እንዲያውም የተወሰኑት ገዳዮች ሰላምታ አቀረቡልን፤ ሲያልፉም ለዮሃንስና ለቄሱ መልካም ዕድል ተመኙላቸው፡፡ አንድም እኛን ሌሊት ድረስ ቆይተን እያደንን ያለን ገዳዮች አድርገው አስበውናል አለያም አምላክ ዓይናቸውን አሳውሯቸዋል … ሁለቱም ምክንያት እንደሆነ አሰብኩ፡፡ በተጨማሪም አሁን ባለው የዘር ፍጅቱ ደረጃ ይህን ያህል ቁጥር ያላቸው ቱትሲዎች በአንድ ቦታ በሕይወት ይኖራሉ ብለው አልጠበቁም፤ ወይንም አላመኑም፡፡ በየመንገዱ አስከሬኖች ስለወደቁ እንደዚያ ብለው ለማመን ጥሩ ምክንያት ነበራቸው፡፡
አምላክ ለጸሎቴ ምላሽ ሰጠኝ፡፡ ለገዳዮቹ ያለኝንም ፍራቻ አሽቀንጥሮ ጣለልኝ፡፡ ግን ከሁኔታው ሳየው ጌታ ለቄስ ሙሪንዚና ለዮሃንስ ተመሳሳይ በረከት ያጋራቸው አይመስልም፡፡ ኢንተርሃምዌዎችን በማግኘታችን ሁለቱም ተደናግጠዋል፡፡ ዮሃንስና ቄስ ሙሪንዚ ገዳዮቹ ከእይታችን እንደተሰወሩ የገቡበትን ጣጣ እንደገና አጤኑት፡፡ ቄሱ ‹‹እናንተ ሴቶች ከዚህ በኋላ ብቻችሁን ሂዱ›› አሉን፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ከዚህ ቅርብ ናቸው… ሂዱ ቀጥሉ፤ ከእይታችን እስክትሰወሩ እናያችኋለን፡፡›› ቄሱና እኔ በፍጥነት ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ እርሳቸው፣ ወንዶች ልጆቻቸውና ዮሃንስ ከመንገዱ ወደ ጥሻ ውስጥ ለመደበቅ በችኮላ ሄዱ፡፡ ያኔ ሌሎቹ ሴቶችና እኔ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ቦታ ላይ ስለሆንን የምናባክነው ምንም ዓይነት ጊዜ አልነበረንም፡፡ የፈረንሳውያኑ ምሽግ 500 እርምጃዎች ገደማ ይርቃል፤ ስለሆነም እግሮቻችን በቻሉት መጠን በፍጥነት ተጓዝን፡፡
የተተወ የወንጌላውያን ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በተቋቋመው ምሽግ ጋ ስንደርስ ልቤ ድው ድው ይል ጀመር፡፡ የተቀረው ቡድን ከዋናው በር ፊት ለፊት በጣም ፈርቶ ተመስጎ ሳለ እኔ በቻልኩት መጠን በሩን እደበድብና በጣም ጮኬ
‹‹እባካችሁ እርዱን! እባካችሁ እገዛችሁን እንፈልጋለን!›› እል ጀመር፡፡ ከሹክሹክታ በላይ ከተናገርኩ በጣም ረጅም ጊዜ ስለሆነኝ ለመጮህ ካደረግሁት ጥረት የተነሣ ጉሮሮዬን አመመኝ፡፡ ድምጼ የታፈነና በጣም ዝግ ያለ ስለሆነ አይሰማም ለማለት ይቻላል፡፡ ሊያድነን የሚጠብቀን ማንም ሰው ሳናገኝ ስንቀር ሴቶቹ በፍርሃት ራዱ፤ ለቅሶና እዬዬም ጀመሩ፡፡ ከአፍታ በኋላ ስድስት ወይም ሰባት ወታደሮች መትረየሶቻቸውን ወደ እኛ ደግነው በአጥሩ በአንደኛው አቅጣጫ ብቅ አሉ፡፡ ፈረንሳይኛ የምናገረው እኔ ብቻ ስለሆንኩ ባልንጀሮቼን ዝም አስባልኩና ለወታደሮቹ ስለማንነታችንና ስለአመጣጣችን ነገርኳቸው፡፡
ወታደሮቹም በጥርጣሬ ተመለከቱን፣ ጠመንጃዎቻቸውንም እንዳቀባበሉ ናቸው፡፡ ‹‹እውነት ነው! የነገርኳችሁ ሁሉ እውነት ነው… ታድኑን ዘንድ እናንተን ስንጠብቅ ቆይተናል›› አልኳቸው በተስፋ መቁረጥ፡፡
በቡድኑ ውስጥ ካሉት ወታደሮች ትንሹ፣ ኮስታራው፣ መልኩ ፈገግ ያለውና ጸጉሩን የተላጨው ሰውዬ ወደ ዋናው በር መጥቶ በፊታችን ላይ ባትሪ አበራብን፡፡ የአፍንጮቻችንን ቅርጽ እየተመለከተ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ነባሩ አስተሳሰብ ሁቱዎች ደፍጣጣ ቱትሲዎች ደግሞ ሰልካካ አፍንጫ አላቸው የሚል ነው፡፡ ስለሆነም ፈተናውን አልፈን ሳይሆን አይቀርም በሩን ከፍቶ አስገባን፡፡ ይሁን እንጂ መታወቂያ ደብተሮቻችንን ለማየት ሲጠይቀንም መሣሪያውን እንደደገነ ነው፡፡ሴቶቹ በኃይል ሲተነፍሱ ይሰማኛል - ማናቸውም ቢሆኑ መታወቂያዎቻቸውን አልያዙም፡፡ በዚህም ምክንያት ፈረንሳውያኑ እዚያው የሚረሽኗቸው መስሏቸዋል፡፡ ደግነቱ በኔ በኩል መታወቂያዬን ከሦስት ወር በፊት ቤቴን ለቅቄ ስወጣ በኋላ ኪሴ ይዤዋለሁ፡፡ ወታደሩ ቱትሲ የሚል ቃል ከዳር እስከዳር የታተመበትን የኔን መታወቂያ አይቶ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ፡፡ ወዲያውኑ ለሌሎቹ ሴቶች በእርግጠኝነት
‹‹ምንም የምንሆን አይመስለኝም›› ስል አረጋገጥኩላቸው፡፡
ለወራት የታመቀ ፍራቻ፣ ብስጭትና ሥጋት ከነፍሳችን ወንዝ ፈሰሰ፤ በውስጣችን ያለው የስሜት ግድብ ፈረሰ፤ የተወሰኑት ሴቶች ሊቆጣጠሩት በማይችሉት መልኩ አለቀሱ፡፡ የወታደሮቹም አቀራረብ ከዚያ በኋላ ተቀየረ - ድምጻቸው በደግነትና በያገባኛል ስሜት ተሞልቶ ጠመንጃዎቻቸውን ዝቅ አድርገው በሐዘኔታ ያነጋገሩን ጀመር፡፡ በወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየነው የታሸገ ውሃና አይብ ተሰጠን፡፡ ቄሱ እንደገመቱት ፈረንሳውያኑ እንደማይገድሉን አውቀን በጣም ሰፍ ብለን መጉረስ ጀመርን፡፡
‹‹አይዟችሁ ምንም ችግር የለም›› አለ ትንሹ ወታደር፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ ቅንጣት ታክል ልትጨነቁ አይገባችሁም … ቅዠታችሁ አክትሟል፡፡ ማንም ሰው እንዲጎዳችሁ አንፈቅድም፡፡ ገባችሁ? ምንም ሥጋት አይግባችሁ፤
👍2
#ሁቱትሲ


#ክፍል_አስራ_ስምንት
(የመጨረሻ ክፍል)


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ

#ድህረ_ታሪክ


#አዲስ_ፍቅር_አዲስ_ሕይወት

አንድ የተሰበረ ልብ ለማገገም ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል ብሎ ለመተንበይ ያዳግታል፤ እኔ ግን ተባርኬያለሁ፡- በእግዚአብሔር እርዳታ ልቤ ከሁለት ዓመት በኋላ ሌላ ለማፍቀር ችሏል፡፡ ስድን ግን የኖርኩት ዝምተኛና አመዛዛኝ ሕይወት ነው ፡፡በተመድ እየሠራሁና ከሳራ ቤተሰብ ጋር እየኖርኩ በትርፍ ጊዜዬ ኪጋሊ በሚገኝ አንድ የእጓለማውታ ማሳደጊያ በደርዘኖች ለሚቆጠሩ የተሸበሩ ብቸኛ ልጆች በታላቅ እህትነት በማገልገል በበጎ ፈቃደኝነት ሥራ አሳለፍኩ፡፡ በፈረንሳይ ምሽግ እንከባከባቸው የነበሩትን ሁለት ወንድማማቾች ሥራዬ ብዬ ብፈልጋቸውም ላገኛቸው አልቻልኩም፡፡ ይሁን እንጂ ሌሎች ብዙ ፍቅር ፈላጊ ወጣቶችን አግኝቻለሁ፡፡ በ1995 መጨረሻ ከኤይማብል ጋር ተገናኘሁ፡፡ ነጻ የትምህርት ዕድል የሰጠው አካል በሩዋንዳ ሰላም ተመልሷል ብሎ ስላመነ ወደ አገሩ የሚመጣበትን የአየር መጓጓዣ ወጪ ሸፈነለት፡፡ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ጊዜ ተጻጽፈናል፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያትም በስልክ አውርተናል፡፡ በአካል ለመገናኘት ግን በመንፈስ አልተዘጋጀንም፡፡ በአየር ማረፊያው የተገናኘንበትን ሁኔታ መቼም አልረሳውም፡፡ ልቦቻችንን ከክፉ እየጠበቅን ይመስል ስሜታችን ፈንቅሎ በመውጣት ወይም እንባ በመራጨት ፈንታ አቀባበሉ በስሱ ተከናወነ፡፡ ተቃቀፍን፣ ተሳሳምን፤ እኔ የእርሱን፣ እርሱም የኔን ህመም ላለመንካት ግን ተፈራርተን ጥንቃቄ አደረግን፡፡ ዓይን ለዓይን ለመተያየት ተፈራራን፡፡ እውነተኛ ስሜታችን ከወጣ መቆጣጠር እንደሚያቅተን አውቀን ከበደን፡፡ ማልቀስ ከጀመርን ማቆሚያ እንደሌለን ገብቶናል፡፡
ወንድሜና እኔ ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ምግብ ቤት ሄደን ራት እየበላን ስለ እርሱ ትምህርትና ስለኔ ሥራ እያወራንና በጓደኞቼም ቀልዶች እየሣቅን እናስመስል ያዝን፡፡ በዚያ ሌሊት ግን ብቻዬን መኝታዬ ላይ ሆኜ እንባዬን ዘረገፍኩት፡፡ ወንድሜም እንዲሁ እንዳደረገ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን አብሮ መሆኑ ይበልጥ ቀለለን፡፡ ምንም እንኳን እርስ በርስ መተያየቱ የቤተሰባችንን አሳዛኝ ፍጻሜ አሰቃቂ ትውስታ የሚቀሰቅስብን ቢሆንም በጣም ስለምንዋደድ አንዳችን በሌላችን መኖር ምቾት ተሰምቶናል፡፡ ህመሙን ለመቋቋም የሚያግዘኝን ጥንካሬ እንዳገኘሁ ልነግረውና ላጽናናውም ፈልጌያለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የማያጽናኑት ዓይነት እንዳልሆነ ወዲያውኑ ታወቀኝ፡፡ ከአፍታ በኋላም በቤተሰባችን ስለተከሰተው ሰቆቃ ላለማንሳት ሳንነጋገር እንደተስማማን ገባን፡፡ የቤተሰባችንን አባላት ሁሉ በስም ጠቃቀስን፡፡ ያኔም ቢሆን አሁንም በሕይወት እንዳሉ አድርገን ነበር ያወራነው - የምንቋቋምበት ብቸኛው መንገዳችን ይህ ነው፡፡ ለቀጣዮቹም ሁለት ዓመታት በደብዳቤና በስልክ እንደዚያው ስናደርግ ቆየን፡፡ ኤይማብል የእንስሳት ሕክምና የድህረ ምረቃ መርሃ-ግብሩን ጨርሶ ወደ ኪጋሊ ሲመለስም ሁኔታው አልተቀየረም፡፡ በየቀኑ በአካል ብንገናኝም ስለ ዘር ጭፍጨፋው የምናወራው አንድ የሆነ ሰው ላይ የተከሰተ ይመስል እንዲያው በደምሳሳው ነው፡፡ የእማማንና የዳማሲንን መቃብርም ሲያይ እንኳን እንዳካሂደው አልጠየቀኝም፤ ብቻውን ሄደ፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያው እንዲሁ አለን፡፡ ኤይማብል አሁንም የሚኖረው ኪጋሊ ነው፤ ስኬታማ ሐኪም ሲሆን ቆንጅዬ ሚስትና ልጆች አሉት፡፡ እርስ በርሳችን በጣም እንዋደዳለን፤ ከመቼውም በላይ ቅርርብ አለን፡፡ በየጊዜው እንደዋወላለን፤ ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜም እንጻጻፋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላም ስለቤተሰባችን ስንነጋገር ‹ነበር› አንልም፡፡ ትዝታቸውን ህያው አድርጎ ማቆያ መንገዳችን ይህ ነው ብዬ እገምታለሁ፡፡

ብዙ ምሽቶቼን በአቅራቢያዬ ባለና ሁለተኛ ቤቴ ሆኖ በነበረው በጀስዊቶች ማእከል በጸሎትና ተመስጦ ተጠምጄ አሳልፋሁ፡፡ በተደበቅሁባቸው ረጅም ወራት ወቅት ያዳነኝን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረኝን የጠበቀ ቁርኝቴን በድጋሚ የጀመርኩት በነዚያ ርጭ ባሉ ስፍራዎች ነው፡፡
ልቤ ቀስ በቀስ ሲያገግምልኝ የወደፊቱን ሕይወቴን አብሬ የሚጋራ አንድ ልዩ የራሴ የምለው ሰውና የምንከባከበው ቤተሰብ ማለም ጀመርኩ፡፡ ግን ሐሳብ ገባኝ … ከዮሃንስ ጋር የነበረኝን ሁኔታ አስታወስኩና በቀላሉ ሊሰበር የሚችለውን ልቤን የትም ለማይደርስና በሚያሳምም መልኩ ለሚቋጭ ግንኙነት ላለመስጠት ወሰንኩ፡፡ ስለዚህ ችግር ወይም ፈተና በሚያጋጥመኝ ጊዜ ሁሉ እንደማደርገው የአምላክን እገዛ ጠየቅሁ፡፡ በገነት የሚሆን ጋብቻ ከፈለግሁ ከአምላኬ በተሻለ የሚኩለኝና የሚድረኝ ከቶ ማን ይኖራል?
መጽሐፍ ቅዱስ ከጠየቅን እንደምናገኝ ይነግረናል፤ በእርግጥም ያንን አደረግሁ፡፡ እግዚአብሔርን የማልመውን ሰው እንዲያመጣልኝ ጠየቅሁት፡፡ ራሴን ማጭበርበር አልፈልግሁም - እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የምፈልገው ሰው ምን ዓይነት እንደሆነ በጣም ግልጽ ማድረግ ነበረብኝ፡፡ ስለሆነም ወረቀት ይዤ ተቀመጥኩና ላገባው የምፈልገውን ሰው ፊት ነደፍኩ፡፡ ከዚያም ቁመቱንና ሌሎቹን ገጽታዎቹን ዘረዘርኩ፡፡ ጠንካራ ማንነትና ምቹ ስብዕና ያለው፣ ደግ፣ አፍቃሪና ርህሩህ፣ ተጨዋች፣ ምግባረመልካም፣ ማንነቴን የሚወድልኝ፣ እንደኔ ልጆችን የሚያፈቅርና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን የሚወድ ሰው ይሰጠኝ ዘንድ ጠየቅሁ፡፡
ለእግዚአብሔር ቀን አልቆረጥኩለትም፡፡ በዘር፣ በዜግነት ወይንም የቆዳ ቀለም ላይም ምንም ገደብ አልጣልኩ፡፡ በዓለም ላይ ከአምስት ቢሊየን በላይ ሰዎች እንደመኖራቸው - ጌታዬ የሕይወቴን አጋር የሚልክበትና እኔም የምጠብቅበት አግባብ ያለው የቆይታ ጊዜ ስድስት ወራት እንዲሆን አቀድኩ፡፡ አንድ ማስጠንቀቂያንም ጨመርኩ፡- ድንግል ማርያምን እጅግ ስለምወዳት እግዚአብሔር ከእምነቴ ተመሳሳይ የሆነ ባል ቢልክልኝ እንደሚሻል ነገርኩት፡፡ በሃይማኖት ሳቢያ በትዳሬ ምንም ዓይነት ውጥረት እንደማይኖር ማረጋገጥ እንዲሁም ባሌ እግዚአብሔርን እኔ በማመልከው መልኩ እንዲያመልክ ፈለግሁ፡፡
ምን እንደምፈልግ በትክክል ካወቅሁ በኋላ ፍላጎቴን አልመው ጀመር፡፡ ጌታ የተመኘሁትን ባርኮ እንደሚሰጠኝ፣ የልቤ መሻት እንደሚሆንልኝና የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነ አምኜ ሁሉንም ለእርሱ ተውኩት፡፡ ሂደቱን ለማፋጠን የአባቴን ቀይና ነጭ መቁጠሪያ አወጣሁና ባሌ እንዲመጣልኝ መጸለይ ጀመርኩ፡፡ ከሦስት ወራት በኋላም መጣልኝ፡- ከእግዚአብሔር የተላከውና የተመድ የሸለመኝ አቶ ብርያን ብላክ ከአሜሪካ ድረስ ከተፍ አለ! የነገሩ መገጣጠም ደሞ ብርያን ወደ ሀገሪቱ የመጣው የዘር ማጥፋቱን በማቀድ የተሳተፉትን ለፍርድ ለማቅረብ የሚጥረውን የተመዱን ዓለም አቀፍ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት በማቋቋሙ ሂደት ለማገዝ ሆኖ እርፍ፡፡ ብርያን ለተመድ ለብዙ ዓመታት ስለሠራ ገዳዮቹን ፍትሃዊ ቅጣት እንዲያገኙ የሚያደርገው የተልዕኮው አካል በመሆኑ ይደሰታል፡፡ በግሌ እርሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ ነው፡፡
ብርያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ ግቢ ሳየው በትክክል እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የጠየቅሁትን ሰውዬ መሰለኝ፡፡ በኋላ በአዳራሹ ሳልፈውና በዓይኖቹ የነበረውን ጥልቅ እርጋታ ሳይ እርሱ እንደሆነ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ግን በእግዚአብሔር እምነቴን ስላደረግሁ ብርያንን ወደኔ እንዲያመጣው ጠበቅሁት አመጣልኛ ብርያን አብረን እንድንዝናና ጋብዞኝ ግሩም ጊዜ አሳለፍን
👍2
#አዲስ_ዓመት

ፈጣሪ ከሞት ጠብቆ
ዕድሜ ሰጥቶናል መርቆ
ሰማይ ጥቁር ሰሌዳ
ከጉም ጠመኔ የጸዳ፣
ፀሓይ ፊቷን ገለጠች
ለዓለም ብርሃኗን ሰጠች፡፡
ከዋክብት ከጨረቃ ጋር
እንጸባርቂ በክብር፡፡
ማዕበል ዶፉ ጸጥ አለ
የወንዞች ሙላት ጎደላ፡፡
ምድር አሸበረቀች
በአበቦች ተንቆጠቆጠች፡፡
ጎመን ወጥቶ ከድስቱ
ገንፎው ገባ ምንቸቱ
ዕለታት ሒሳብ ሳይስቱ
መስከረም ጠባ በዓመቱ፡ ፡
ጨለማው ጠፍቶ በሀሓይ
ክረምት ተተካ በጸደይ፡፡
አዝርዕት ከሞት ተነሡ
ድርቀታቸውን ረሱ፡፡
በአበባ በፍሬ ደምቀው
ምግብን ሰጡ አሽተው፡፡
እንግዲህ እኛም ሕያዋን
እንመሳለሰ በብርሃን።
ሐሚት ቂምና ቁጣ
ጥላቻን ከልብ እናውጣ!
ክፋት የተንኮል ወጥመድ
ከዓለናችን ይወገድ”
የዝሙት የኃጢአት ጎመን
ከቤታችን ይውጣልን
ምግባር የእምነት ገንፎ
ከዘመን ዘመንን አልፎ
ለትውልድ ይቀመጥ ተርፎ
አምላክ ቅዱሰ መንፈስ
ሕይወታችንን ይቀድስ
ሥጋችንም በጽድቅ ይታደስ
መስከረም እዲሰ ዘመን
የሰላም የጤና እንዲሆን
ፈጣሪ ፈቃዱ ይሁን
አምላክ የፍቅር ጌታ
ዓመቱን ያድርግ የደስታ፡፡

🔘በኤፍሬም የኔሰው🔘
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_አርባ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


#አዲስ_ዓለም

..የመንገዱ መብራቶች ተበላሽተው ብርሃን አይሰጡም። አካባቢው ፀጥ እረጭ ብሏል። ትናንትና ማታ እስከ ስድስት ሰዓት የነበረው ጩኸት፣ ሁካታ የሰካራሞች ልፍለፋ፣ የሴተኛ አዳሪዎች ስድብ፣ በየቀይ መብራቱ ውስጥ የነበዙ ጠጪዎች ዳንኪራና ጭፈራ ትርምሱ ሁሉ እዚህ ቦታ
የነበረ መሆኑ የሚያጠራጥር ነው፡፡ የሥጋ ቤቶቹ ብርሃን ድምቀት፣ከቡና ቤት ቡና ቤት የሚያማርጠው ጠጪ ብዛት፣ የሙዚቃው ጩኽትና የመኪናው ኳኳታ ጆሮ ሲያደነቁር እንዳላመሽ ሁሉ እንደዚህ እንደ አሁኑ እረጭ ብሎ ሲታይ በግርግርና በፀጥታ መካከል ያለውን ልዩነት
ለማሳየት ደፈጣ የያዘ ይመስል ነበር፡፡

የወዳደቀ አጥንት ለመለቃቀም የሚያነፈንፉ ውሾች ውር ውር
ይላሉ፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ውስጥ ግን ያን ሰው የማይታይበትን አካባቢ ፀጥታ በማደፍረስ የጠዋት ገበያዋን ለመላፍ የተጣደፈች ታክሲ ከእሪ በከንቱ ወደ አራት ኪሎ አቅጣጫ በረረች፡፡ በዚያው ቅጽበት ደግሞ
ቁልቁል ከፒያሳ ወደ እሪ በከንቱ እየዘለለ የሚወርድ ሰው ታዬ። መላ ሰውነቱን ሬንጅና ጥላሸት የተቀባ ፀጉሩ እዚህም እዚያም ተገምዶ እንደ ጭራሮ የቆመ፣ ጎድኖቹ ሥጋ ባልለበሰ አጥንት የገጠጡት እብዱ ምን ሽንሽ! ብቻውን በመንገዱ ግራና ቀኝ ቱር ቱር እያለ እየተሯሯጠ ሽቅብ
ይወጣል ቁልቁል ይወርዳል። ዐይኖቹ እንደ በርበሬ ቀልተው ለተመልካች ያስፈራራሉ። ከወገቡ በታች እዚህም እዚያም የተቦጫጨቀ ሱሪ መልበስ
ከተባለ ለብሷል። ቆም ይልና ድንጋይ ይፈነቅላል ያነሳውን መልሶ ይወረውረዋል። ደግሞ ወደታች ይወርዳል። ከዚያም ጉንበስ ይልና የሲጋራ ቁራጭ ለመልቀም ያነፈንፋል።እንደገና ወደ ላይ ይወጣል። የዚያ አስፈሪ
የጨለማ ንጉሥ ሁሉም በየቤቱ በተከተተበት ሰዓት እሱ እየዘለለና እየቦረቀ ብቻውን በየመንገዱ ላይ ሲሯሯጥ ምሽቱን ለብርሃን ለማስረከብ የተዘጋጀ ባለሥልጣን ይመስል ነበር።

ከለሊቱ አሥራ አንድ ሰዓት ሆኗል። ወደየጠቅላይ ግዛቱ የሚጓዙ መንገደኞች አውቶቡስ ተራ ለመድረስ በዋናው አስፋልት መንገድ ላይ ብቅ ብቅ ብለዋል። በዚያ ሰዓት በእግር የሚጓዝ መንገደኛ አንድም በራሱ የተማመነ አሊያም ከወሮበላና ከማጅራት መቺው ሰይፍ እግዚአብሔር እንዲጠብቀው በልቡ ፀሎት እያደረስ በፍርሃት የሚራመድበት እንጂ ልቡ
በድፍረት ተሞልቶ የሚንቀሳቀስበት ሰዓት አልነበረም፡፡ ለሁሉ ነገር ግድ
የለሌው ለማጅራት መቺው ለብርዱ ለፀሀዩ ለሞትም ለህይወትም ደንታ የሌለው እብዱ ምንሽንሽ ብቻ ነበር። የእሪ በከንቱን ድልድይ ተሻግሮ
ወደ አራት ኪሎ ሲያቀና አንድ ዕድሜው ከሰላሳ ስምንት እስከ አርባ አመት የሚገመት ወደ ወሎ ጠቅላይ ግዛት ለመሄድ የሚገስግስ ሰው ብቅ! አለ። ሰውዬው ምንሽንሽን ሲያየው “በስመአብ ወልድ ጌታዬ” አለና
አማተበ፡ የሰይጣን ቤት አጋፋሪ የመሰለውን እብድ ሲመለከት ከመንገዱ ፈንጠር አለና ወደ ዳር ወጣ፡፡ ካደረበት ከዘውዲቱ ሆቴል ቁልቁል ወደ እሪ በከንቱ የሚወስደውን መንገድ ሲጀምረው ዳፍንቱ በብርሃን ባለመተካቱ ልቡ ፈራ ተባ እያለ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
የአራት ልጆች አባት የሆነው ጓንጉል ቢሆነኝ አዲስ አበባ የመጣው ያደለባቸውን ሁለት ሠንጋዎች ወልዲያ ገበያ ሸጦ ባገኘው ገንዘብ ለሚስቱና ለልጆቹ ልብስና ጫማ ለራሱ ደግሞ የፋሲካን በዓል መዋያ ልብስ
አማርጦ በርካሽ ዋጋ ገዝቶ ቀሪውን ገንዘብ ለልዩ ልዩ ችግሮች ማቃለያ ሊያደርግና በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ የመጀመሪያ አመት ተማሪ የሆነችው የታናሽ እህቱን ልጅ ሊጠይቅ በዚያውም የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የሆነችው አዲስ አበባን ሊጎበኛት ነው።
በዚሁ መሠረት ጣጣውን ጨርሶ ለአራቱ ልጆቹ ልብስ ሲያማርጥ ቆይቶ ሻንጣ ገዝቶ ከቆጣጠረና አዳሩን ዘውዲቱ ሆቴል ካደረገ በኋላ ወደ ቤተሰቦቹ ለመገስገስ ከዚያም ቤት ደርሶ ልጆቹና ሚስቱ ከበውት ሲንጫጩ የኔ ያምራል የኔ ይበልጣል እያሉ ህፃናቱ እርስ በርሳቸው ሲሟገቱ፣ሚስቱ ደግሞ የገዛላትን ቀሚስ እየላካች ረዝሞ ከሆነ ሰነፍ ልኬን እንኳን
የማታውቅ? ስትለው፣ ልኳ ከሆነ ደግሞ እሰይ የኔ አንበሳ” ብላ ስታደንቀው፣ ጉንጬን ሳም ስታደርገው በሀሳቡ እየታየው ቶሎ ሊደርስላቸው ነበር ለሊቱ አልነጋልህ ብሎት ዐይኑ ፈጥጦ ያደረውና ከለሊቱ ለአሥራ
አንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ያውም የረፈደበት መስሎት ልብሱን በፍጥነት ለባብሶ የወጣው...

ጓንጉል ምንሽንሽን ሲያየው በድንገጤ እግሩ ተሽመደመደበት እንደዚህ አይነት አጋንንት መሳይ ሰው ሚልኪው ጥሩ አይደለም አለ በልቡ። የሰው ዘር ሳያይ ዐይኑ ያረፈው በእብዱ ላይ ነበር። እብዱ ምንሽንሽ ወደሱ እንደመጠጋት ብሎ ፊት ለፊት ሲመጣበት በድንጋጤ ወደ ግራ
በኩል እሸሻለሁ ሲል አደናቀፈው።
“ወንዱ!” አለና ፎክሮ ተንገዳገደ። እብዱ ጠጋ አለውና እጁን ዘረጋለት።
ፍራንክ እንደሚጠይቀው አወቀ። ወይ ይቺ ፍራንክ? አለ በልቡ።እብዱም፣ጤነኛውም፣አዋቂውም፣ ህፃኑም ሁሉም ይወዷታል ሲል ተገረመ::
የመጨረሻዋ የስድስት ወር ህፃን ልጁ እንኳን ወሪቀት በግራ እጁ ብር በቀኝ እጁ ይዞ ሲያስጠጋላት እጅዋ ወደ ቀኝ እጁ ነበር የሄደው። ይሄን አስታወሰና ትንሽ እንደ መሳቅ ብሎ እጁን ወደ ኪሱ ከተተና ያገኘውን ድፍን ሃያ አምስት ሣንቲም ኣውጥቶ ወረወረለት። ምንሽንሽ ሳንቲሟን
ለማንሳት ጐንበስ ሲል እሱ ደግሞ አውቶቡሱ እንዳያመልጠው በሩጫ ዳገቱን ተያያዘው፡፡
የሆነ ነገር ውልብ አለበት፡፡ የሰው ቁመና መስለው። ከግራ ወደ ቀኝ
የሮጠ ነገር ነበር፡፡

“ጅብ ነው! ጅብ መሆን አለበት። ከወዲህኛው ገደል ዘሎ ወደዚያኛው መግባቱ ነው! ልክ ነው አውሬ መሆን አለበት! አቋረጠኝ እኮ ልክ ነው ደግሞ ጠቆር ያለ ነገር ነው! ወይኔ ዛሬ እግዚአብሔር ከዚህ ጉድ ያውጣኝ እንጂ ያጋጠመኝን ሁሉ ቤት ገብቼ ለሚስቴ ነው የማጫውታት፡፡ ገና በጠዋቱ ቀንዳም ጋኔን የመሰለ እብድ ለከፈኝ እሱን ሳልፍ ደግሞ ይኸውና ጥቁር ጅብ አቋረጠኝ። እግዚአብሔር ያውቃል” እያለ በልቡ እያወራ ወደ ድልድዩ ተጠጋ፡፡ ሰግጠጥ እንደማለት
አደረገው። ድልድዩ ላይ ሲደርስ ከበደው፡፡ ገልመጥ፣ ገልመጥ አለ። ሰላም ይመስላል። ፀጥ ረጭ ብሏል። ብቅ ብቅ ብለው መታየት የጀመ ሩት ሰዎች በተለያየ አቅጣጫ ሄደዋል። በዚያ መንገድ ላይ ተፍ ተፍ የሚለው እሱ ብቻ ነበር፡፡

“ስው ሊሆን አይችልም፡፡ በዚህ ሰዓት ሰው እዚህ ድንጋይ ውስጥ እገደል ስር ምን ይሰራል? ሰው አይደለም አውሬ መሆን አለበት...” ፈራ ተባ እያለ ወደ ድልድዩ ገባ፡፡ እንደፈራው አይደለም፡፡ ምንም ነገር የለም።
ወደ ኋላው ገልመጥ ብሎ አየ፡፡ እብዱ በተሰጠው ሳንቲም ተደስቶ እየዘለለ ወደ አራት ኪሎ ሲያቀና ተመለከተው፡፡ አካባቢው ጭር.እረጭ...ያሉ የሞት ጥላ የሚያንዣብብበት መሰለ፡፡ ሁለቱን ሠንጋዎቹን ሸጦ ሸቀጣ ሸቀጥ ከሽመተበት ሌላ በኪሱ ውስጥ ሁለት መቶ አርባ ብር ቀርታዋለች፡፡
እሷንም ጥሩ ቦታ አስቀምጧታል፡፡ መጀመሪያ ከሱሪው ኪስ ከተታት፡፡ ደስ አላለውም፡፡ ወደ ኮቱ የውስጥ ኪስ ወሰዳት። አላመናትም፡፡ የአንድ ዓመት ሙሉ የልፋቱ ውጤት እነዚያ ቤት ቤት የሚያካክሉ ሠንጋዎቹ የተለወጡባት ትንሽ ነገር ብትጠፋ ሁለት ሠንጋዎች ቀለጡ ማለት ነው። በየኪሱ ሁሉ አዟዟራት። በመጨረሻ ላይ ጥሩ የማስቀመጫ ቦታ አገኘላት። በጥንቃቄ የሚደብቀበት አስተማማኝ ቦታ! ወደ ጫማው ወረደ። እንደገና እጁን መለሰው። አሁንም አሰላስለ። ፊቱ ፈካ አለ፡፡የመጨረሻውን አስተማማኝ ቦታ አገኘላት። በመታጠቂያው ዘልቆ በውስጥ ሱሪው መካከል በደንብ አድርጐ አጣጥፎ ቀረቀራት። የአሁኑ ከፍተኛ ሥጋቱ ይቺኑ እንቅልፍ ያጣባትን
👍3