#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡
አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡
‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።
‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡
‹‹እባክህ አትጨነቅ›› የውስጥ ስሜቱን የሚቆሰቁስ አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።
ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡
‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››
ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››
‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡
‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ ሮጠው ከጎኑ ቆመ
‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››
ዔሊያስ ለወንድሙ ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው
ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ። ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡ በወቅቱ ጮርቃ ልጅ ነበር እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡
ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡
‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››
እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች። አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ ጥግ ወስደው ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡
ያሬድ የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹አዎ..ደህና ነኝ››
‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡
‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››
‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››
‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡
‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ እንደነበረ ላለማሰብ ታገለች።
ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡
‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡
ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡
‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡
‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን ጮኸች።
‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡
አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡
‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።
‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡
‹‹እባክህ አትጨነቅ›› የውስጥ ስሜቱን የሚቆሰቁስ አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።
ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡
‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››
ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››
‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡
‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ ሮጠው ከጎኑ ቆመ
‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››
ዔሊያስ ለወንድሙ ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው
ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ። ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡ በወቅቱ ጮርቃ ልጅ ነበር እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡
ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡
‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››
እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች። አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ ጥግ ወስደው ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡
ያሬድ የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹አዎ..ደህና ነኝ››
‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡
‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››
‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››
‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡
‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ እንደነበረ ላለማሰብ ታገለች።
ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡
‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡
ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡
‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡
‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን ጮኸች።
‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
❤56👍3
‹‹አሁን ማዘዝ እንችላለን? እየራበኝ ነው።››በማለት ርዕሱን ለመቀየር ሞከረች፡፡
‹‹ኤሊ ወንደላጤ እንደሆነ ሰማሁ ›› አለች ሜሮን
‹‹ሊሆን ይችላል ግን…ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም›› ስትል ራሄል አጽንኦት ሰጥታ ተናገረች።
‹‹ይቺ ልጅ በፍቅር ፍላጻ የተመታች ይመስለኛል።››ያሬድ ነው ተናጋሪው፡፡
ራሄል‹‹ሞተር ሳይክል ይነዳል…እሺ?››ስትል በመኮሳተር ነገረቻቸው፡፡ከዚህ ቃል በኋላ ያለው ዝምታ ነበር…ፀጥታው ምን ማለት እንደፈለገች ጓደኞቿ እንደተረዱት ያሳያል። በባለ ሁለት ጎማ የሞት ማሽን የልቧን ሰው እዳጣች እና ምን ያህል የልብ ስብራት እንዳጋጠማትና ከዛም ስብራት እስካአሁን እንዳላገገመች የቅርቧ ሰዎች ስለሆኑ በደንብ ያውቃሉ፡፡
‹‹እናንተ ሰዎች ለማዘዝ ዝግጁ ናችሁ?››ደግማ ጠየቅች፡፡
አስተናጋጁ ተጠራ እና ሁሉም የየፍላጎታቸውን አዘዙ ፡፡ከዚያ በኋላ፣ ወደ ተለመደው ንግግራቸው ሲገቡ፣ አንዳቸው የሌላውን ሕይወት ሲመረምሩ፣ ሌንሳ ስለ መንታ ልጆቿ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላላት ስራ ስትነግራቸው ራሄል ስለ ድርጅቷ እንቅስቃሴ ስትተርክ ቆዩ…ያዘዘችው በርገር መጥቶ ለመብላት ስትዘጋጅ የሞባይል ስልኳ ጮኸ።
‹‹ተይው…አታንሺው››አላት ያሬድ… ። የጥሪ ማሳያውን ተመለከተች። አባቷ ነበሩ።ጓደኞቿን ይቅርታ ጠይቃ በፈገግታ ስልኩን አነሳች፣ ከጓደኞቿ ዞር ብላ ማውራት ጀመረች።
‹‹ ሄይ አባዬ››
‹‹ራሄል የእኔ ማር››ድምፃቸው የደከመ ነበር።በራሄል ጭንቅላት ውስጥ ጭንቀት ተፈጠረ።
‹‹አባዬ ምን ችግር አለ?››
‹‹እናትሽ ናት …እኛ ሆስፒታል ነው ያለነው….እግሯ ተሰብሯል።››
‹‹መጣው አባዬ…አሁኑኑ መጣሁ ››ስልኳን ዘጋችና ቦርሳዋን አነሳች። ‹‹አባቴ ነበር የደወለው››አለች፡፡ ድምጿ እየተንቀጠቀጠ ነው።‹‹ይቅርታ ጓደኞቼ, መሄድ አለብኝ. እናቴ እግሯን ተሰብሮ ሆስፒታል ውስጥ ነች.››ለምግብ ክፍያ የሚሆን የተወሰነ ብር ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች።
‹‹አብረንሽ እንድንመጣ ትፈልጊያለሽ››ስትል ሜሮን ጠየቀቻት ፡፡
‹‹አይ, አይሆንም.፣ችግር የለውም…እናንተ መብላታችሁን ቀጥሉ.››ራሄል ተቃወመች።
ራሄል ከምግብ ቤት ፈጥና ስትሄድ ያሬድ ‹‹ከደረሽ በኃላ ሁኔታውን አሳውቂን››አላት፡፡
ከአስራ አምስት ደቂቃ በኋላ የሆስፒታሉን በር ደርሳ እንደምንም እራሷን አደፋፍራ ወደውስጥ ገባች፡፡ እና በድፍረት ምትጋፈጠው የመሰላት የጸረ-ተባይ እና የአሞኒያ ጠረን በአፍንጫዋ ተመሰገ ። ያደፈነችውን ትዝታ እየጎተተ እንደ ማዕበል ያንገላታት ጀመር።እርምጃዋ ተንቀረፈፈ፣ ነገር ግን ስለእናቷ ህመም ስታስብ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ለሆስፒታሎችን ያላትን ፍራቻ ተቋቁማ እንድታልፍ የሚያስችላትን ብርታት አገኘች ።
‹‹ተይ…ተይ! አባትሽ ይፈልግሻል።››በማለት እራሷን ለማበርታት ሞከረች፡፡ከአንዱ ክፍል ውስጥ የአባቷን ድምፅ እንደሰማች በፍጥነት ወደእዛው ተራመደች። መጋረጃውን አልፋ ከፊት ለፊቷ ባለው ቦታ ላይ ቆመች።ፀጋ አልጋው ላይ ተቀምጣለች…እና ኤሊያስ ከሸሚዝና ከሰማያዊ ጂንስ በላይ ነጭ ጋወኑን ለብሶ ቆሟል ፡፡በየት በየት ብሎ ከእሷ ቀድሞ እዚህ እንደተገኘ ግራ ገባት፡፡ እንደገባች አባቷ ቀና ብለው አያትና በጥሩ ፈገግታ ተቀበላት።‹‹እናቴ የት አለች?››ራሄል እሷቸውን እቅፍ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ ማን እዚህ እንዳለ ለማየት ጭንቅላቷን አጠማዘዘች።
አባቷ ‹‹እናትሽ አሁን ቀዶ ጥገና ላይ ነች›› አሏት፡፡
‹‹እንዴት ሊሆን ቻለ?››ራሄል ጠየቀች።
‹‹ፀጋን ተሸክማ ደረጃውን እየወረደች ነበር፣ድንገት ሚዛኗን ስታ ወድቃ ተጠመዘዘች…ከዛ ተሰበረች። ››ሲሉ አስረዷት፡፡
‹‹አሁን ፀጋ እንዴት ናት?››ራሄል እህቷን በድጋሚ እየተመለከተች ጠየቀች፡፡
‹‹እስካሁን ደህና ነች ። ከመደበኛው ውጪ የሆነ ነገር አይታይባትም።››ኤሊያስ ጣልቃ ገብቶ ስለፀጋ ሊያስረዳት ሞከረ፡፡ አይኖቹ ራሔል ግንባር ላይ ብርሃን የሚረጩ ይመስላሉ ።
‹‹ራሄል ሆስፒታሎችን አትወድም። ››ሲሉ አባትዬው ለኤሊያስ ሊያስረዱት ሞከሩ፡፡
ዔሊም ‹‹አዝናለሁ፣ አላውቅም ነበር። ››አለ፡፡
‹‹ግን እናቴን ለማግኘት መሄድ እችላለሁ?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ትችያለሽ››
ራሄል በጥንቃቄ ፈገግታ ሰጠችው ። ለረጅም ጊዜ ያላጋጠማት ስሜት ተሰማት።‹‹አሁን እመለሳለሁ.››በማለት ፀጋን አፍንጫዋ ላይ ነክቶ ሄደ።
ከጎናቸው ካለ አንድ ኪዩቢክ የወጣው የኦክሲጅን ጩኸት፣ የጋሪዎቹ እና የነርሶች ወከባ ወደ ኅሊናዋ ውስጥ ገብተው ትዝታዎችን ቀሰቀሱባት። ትንፋሽም አጠራት።አባቷ ተሳስተዋል። ሆስፒታሎችን አለመውደድ አይደለም። ንቃቸው ነው። እነሱ ተስፋዋን ቀረጣጥፈው የበሉባት የመቃብር ጉድጓድ ናቸው ፣ በእያንዳንዱ ኮሪደር የሞት ሽታ ነው ወደአፍንጫዋ የሚመሰገው እና አሁን ሀሳቧ እናቷ ላይ ነው፡፡ በእውነቱ ምን ያህል ተጎድታ ይሆን ? ምን ይደርስባት ይሆን?
‹‹የእኔ ማር ..እዚህ ጋር ተቀመጪ››አባቷም እጇን ያዘና በመጋረጃ በተሸፈነው ክፍል ውስጥ ባለው ብቸኛ ወንበር ላይ አስቀመጧት ፡፡
‹ኤሊያስ ትክክል ነበር፣ በጣም ገርጥታለች ።››ራሄል እያደገ የመጣውን ድንጋጤዋን ለመቆጣጠር ሞከረች።
‹‹ደህና ነኝ አባባ›› አለች፡፡
ፀጋ እጆቿን ወደ አባቷ እየዘረጋች ‹‹ወደ ታች አውርደኝ›› ስትል ተናገረች።
አቶ ቸርነት ከአልጋው ላይ ልትወርድ ወደ ምትሞክረው ፀጋ እየጠቆሙ ‹‹ራሄል ልትወስጂያት ትችያለሽ?›› ሲሉ ጠየቋት።አባቷ ወደሚያዩት አቅጣጫ ቃኘች፣ ዔሊያስ መጋረጃውን ወደ ጎን ሲያንሸራትተው ሌላ ዶክተር ተከተለውና ወደእነሱ መጣ። በድጋሚ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ በምንም ነገር እርግጠኛ ሳትሆን ልጁቷን ከአልጋው ላይ አነሳችና አቀፈቻት።
‹‹…አዝናለው ጥሩ ያልሆነ ዜና ልነግራችሁ ነው›› አለ ደ/ር ኤሊያስ።
የዶተሩ ከባድ የድምፁ ቃና ራሄልን በፍርሃቷ እንድትርበደበድ እና እንዳትወድቅ በመፍራት ግድግዳውን እንድትይዝ አደረጋት ‹‹ይህ ዶ/ር ምንያህል ይባላል። ሁኔታውን ያብራራላችኋል›› ሲል ተናገረና ቦታውን አዲስ ለመጣው ዶክተር ለቀቀ ፡፡የዶ/ር ምንያህል ፊቱ ፈገግታ ያልተለየው ቢሆንም የዶክተሮችን ስሜት ማንበብ ከባድ እንደሆነ ከብዙ አመት በፊት በደንብ አውቃለች፡፡ እናም ፍርሃቷ ጨመረ።
ምንያህል የተባለው ዶ.ር ወደአባቷ እየተመለከተ ገለፃውን ቀጠለ‹‹የባለቤቶት X ሬይ ውጤት አግኝተናል።››ጥቁሩ አይኖቹ በጥልቅ ርህራሄ ሁለቱንም አስተዋላቸው።‹‹በጣም ከባድ የሆነ የጭን አጥንት ስብራት ገጥሟቸዋል።ከአጥንት በላይ የሆነ ስብራት በሚመስል ነገር የተወሳሰበ ነው። ለረጅም ጊዜ እዚሁ ሆስፒታል ተኝተው መታከም አለባቸው››
አቶ ቸርነት እራሳቸውን ለማረጋጋት ያህል አይናቸውን ጨፈኑ.. ከዛ ከፈቱ …።ራሄል አሁንም ፀጋን በአንድ እጇ ይዛ ቀስ በቀስ ስሯ ያለ ወንበር ላይ ልትቀመጥ ስትሞክር ድንገት ክንዷ ላይ ያለችው እህቷን እንደያዘች ሚዛኗን በመጠኑ ስታ ልትወድቅ ስትል ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተላት የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ተንደረደረና ክንዷን ይዞ በዝግታ እንድትቀመጥ ረዳት፡፡
‹‹አመሰግናለሁ››አለች ራሄል ።
ዔሊያስ እጁ አሁንም በትሁት ትከሻ ላይ ነው።
‹‹ኤሊ ወንደላጤ እንደሆነ ሰማሁ ›› አለች ሜሮን
‹‹ሊሆን ይችላል ግን…ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም›› ስትል ራሄል አጽንኦት ሰጥታ ተናገረች።
‹‹ይቺ ልጅ በፍቅር ፍላጻ የተመታች ይመስለኛል።››ያሬድ ነው ተናጋሪው፡፡
ራሄል‹‹ሞተር ሳይክል ይነዳል…እሺ?››ስትል በመኮሳተር ነገረቻቸው፡፡ከዚህ ቃል በኋላ ያለው ዝምታ ነበር…ፀጥታው ምን ማለት እንደፈለገች ጓደኞቿ እንደተረዱት ያሳያል። በባለ ሁለት ጎማ የሞት ማሽን የልቧን ሰው እዳጣች እና ምን ያህል የልብ ስብራት እንዳጋጠማትና ከዛም ስብራት እስካአሁን እንዳላገገመች የቅርቧ ሰዎች ስለሆኑ በደንብ ያውቃሉ፡፡
‹‹እናንተ ሰዎች ለማዘዝ ዝግጁ ናችሁ?››ደግማ ጠየቅች፡፡
አስተናጋጁ ተጠራ እና ሁሉም የየፍላጎታቸውን አዘዙ ፡፡ከዚያ በኋላ፣ ወደ ተለመደው ንግግራቸው ሲገቡ፣ አንዳቸው የሌላውን ሕይወት ሲመረምሩ፣ ሌንሳ ስለ መንታ ልጆቿ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላላት ስራ ስትነግራቸው ራሄል ስለ ድርጅቷ እንቅስቃሴ ስትተርክ ቆዩ…ያዘዘችው በርገር መጥቶ ለመብላት ስትዘጋጅ የሞባይል ስልኳ ጮኸ።
‹‹ተይው…አታንሺው››አላት ያሬድ… ። የጥሪ ማሳያውን ተመለከተች። አባቷ ነበሩ።ጓደኞቿን ይቅርታ ጠይቃ በፈገግታ ስልኩን አነሳች፣ ከጓደኞቿ ዞር ብላ ማውራት ጀመረች።
‹‹ ሄይ አባዬ››
‹‹ራሄል የእኔ ማር››ድምፃቸው የደከመ ነበር።በራሄል ጭንቅላት ውስጥ ጭንቀት ተፈጠረ።
‹‹አባዬ ምን ችግር አለ?››
‹‹እናትሽ ናት …እኛ ሆስፒታል ነው ያለነው….እግሯ ተሰብሯል።››
‹‹መጣው አባዬ…አሁኑኑ መጣሁ ››ስልኳን ዘጋችና ቦርሳዋን አነሳች። ‹‹አባቴ ነበር የደወለው››አለች፡፡ ድምጿ እየተንቀጠቀጠ ነው።‹‹ይቅርታ ጓደኞቼ, መሄድ አለብኝ. እናቴ እግሯን ተሰብሮ ሆስፒታል ውስጥ ነች.››ለምግብ ክፍያ የሚሆን የተወሰነ ብር ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች።
‹‹አብረንሽ እንድንመጣ ትፈልጊያለሽ››ስትል ሜሮን ጠየቀቻት ፡፡
‹‹አይ, አይሆንም.፣ችግር የለውም…እናንተ መብላታችሁን ቀጥሉ.››ራሄል ተቃወመች።
ራሄል ከምግብ ቤት ፈጥና ስትሄድ ያሬድ ‹‹ከደረሽ በኃላ ሁኔታውን አሳውቂን››አላት፡፡
ከአስራ አምስት ደቂቃ በኋላ የሆስፒታሉን በር ደርሳ እንደምንም እራሷን አደፋፍራ ወደውስጥ ገባች፡፡ እና በድፍረት ምትጋፈጠው የመሰላት የጸረ-ተባይ እና የአሞኒያ ጠረን በአፍንጫዋ ተመሰገ ። ያደፈነችውን ትዝታ እየጎተተ እንደ ማዕበል ያንገላታት ጀመር።እርምጃዋ ተንቀረፈፈ፣ ነገር ግን ስለእናቷ ህመም ስታስብ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ለሆስፒታሎችን ያላትን ፍራቻ ተቋቁማ እንድታልፍ የሚያስችላትን ብርታት አገኘች ።
‹‹ተይ…ተይ! አባትሽ ይፈልግሻል።››በማለት እራሷን ለማበርታት ሞከረች፡፡ከአንዱ ክፍል ውስጥ የአባቷን ድምፅ እንደሰማች በፍጥነት ወደእዛው ተራመደች። መጋረጃውን አልፋ ከፊት ለፊቷ ባለው ቦታ ላይ ቆመች።ፀጋ አልጋው ላይ ተቀምጣለች…እና ኤሊያስ ከሸሚዝና ከሰማያዊ ጂንስ በላይ ነጭ ጋወኑን ለብሶ ቆሟል ፡፡በየት በየት ብሎ ከእሷ ቀድሞ እዚህ እንደተገኘ ግራ ገባት፡፡ እንደገባች አባቷ ቀና ብለው አያትና በጥሩ ፈገግታ ተቀበላት።‹‹እናቴ የት አለች?››ራሄል እሷቸውን እቅፍ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ ማን እዚህ እንዳለ ለማየት ጭንቅላቷን አጠማዘዘች።
አባቷ ‹‹እናትሽ አሁን ቀዶ ጥገና ላይ ነች›› አሏት፡፡
‹‹እንዴት ሊሆን ቻለ?››ራሄል ጠየቀች።
‹‹ፀጋን ተሸክማ ደረጃውን እየወረደች ነበር፣ድንገት ሚዛኗን ስታ ወድቃ ተጠመዘዘች…ከዛ ተሰበረች። ››ሲሉ አስረዷት፡፡
‹‹አሁን ፀጋ እንዴት ናት?››ራሄል እህቷን በድጋሚ እየተመለከተች ጠየቀች፡፡
‹‹እስካሁን ደህና ነች ። ከመደበኛው ውጪ የሆነ ነገር አይታይባትም።››ኤሊያስ ጣልቃ ገብቶ ስለፀጋ ሊያስረዳት ሞከረ፡፡ አይኖቹ ራሔል ግንባር ላይ ብርሃን የሚረጩ ይመስላሉ ።
‹‹ራሄል ሆስፒታሎችን አትወድም። ››ሲሉ አባትዬው ለኤሊያስ ሊያስረዱት ሞከሩ፡፡
ዔሊም ‹‹አዝናለሁ፣ አላውቅም ነበር። ››አለ፡፡
‹‹ግን እናቴን ለማግኘት መሄድ እችላለሁ?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ትችያለሽ››
ራሄል በጥንቃቄ ፈገግታ ሰጠችው ። ለረጅም ጊዜ ያላጋጠማት ስሜት ተሰማት።‹‹አሁን እመለሳለሁ.››በማለት ፀጋን አፍንጫዋ ላይ ነክቶ ሄደ።
ከጎናቸው ካለ አንድ ኪዩቢክ የወጣው የኦክሲጅን ጩኸት፣ የጋሪዎቹ እና የነርሶች ወከባ ወደ ኅሊናዋ ውስጥ ገብተው ትዝታዎችን ቀሰቀሱባት። ትንፋሽም አጠራት።አባቷ ተሳስተዋል። ሆስፒታሎችን አለመውደድ አይደለም። ንቃቸው ነው። እነሱ ተስፋዋን ቀረጣጥፈው የበሉባት የመቃብር ጉድጓድ ናቸው ፣ በእያንዳንዱ ኮሪደር የሞት ሽታ ነው ወደአፍንጫዋ የሚመሰገው እና አሁን ሀሳቧ እናቷ ላይ ነው፡፡ በእውነቱ ምን ያህል ተጎድታ ይሆን ? ምን ይደርስባት ይሆን?
‹‹የእኔ ማር ..እዚህ ጋር ተቀመጪ››አባቷም እጇን ያዘና በመጋረጃ በተሸፈነው ክፍል ውስጥ ባለው ብቸኛ ወንበር ላይ አስቀመጧት ፡፡
‹ኤሊያስ ትክክል ነበር፣ በጣም ገርጥታለች ።››ራሄል እያደገ የመጣውን ድንጋጤዋን ለመቆጣጠር ሞከረች።
‹‹ደህና ነኝ አባባ›› አለች፡፡
ፀጋ እጆቿን ወደ አባቷ እየዘረጋች ‹‹ወደ ታች አውርደኝ›› ስትል ተናገረች።
አቶ ቸርነት ከአልጋው ላይ ልትወርድ ወደ ምትሞክረው ፀጋ እየጠቆሙ ‹‹ራሄል ልትወስጂያት ትችያለሽ?›› ሲሉ ጠየቋት።አባቷ ወደሚያዩት አቅጣጫ ቃኘች፣ ዔሊያስ መጋረጃውን ወደ ጎን ሲያንሸራትተው ሌላ ዶክተር ተከተለውና ወደእነሱ መጣ። በድጋሚ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ በምንም ነገር እርግጠኛ ሳትሆን ልጁቷን ከአልጋው ላይ አነሳችና አቀፈቻት።
‹‹…አዝናለው ጥሩ ያልሆነ ዜና ልነግራችሁ ነው›› አለ ደ/ር ኤሊያስ።
የዶተሩ ከባድ የድምፁ ቃና ራሄልን በፍርሃቷ እንድትርበደበድ እና እንዳትወድቅ በመፍራት ግድግዳውን እንድትይዝ አደረጋት ‹‹ይህ ዶ/ር ምንያህል ይባላል። ሁኔታውን ያብራራላችኋል›› ሲል ተናገረና ቦታውን አዲስ ለመጣው ዶክተር ለቀቀ ፡፡የዶ/ር ምንያህል ፊቱ ፈገግታ ያልተለየው ቢሆንም የዶክተሮችን ስሜት ማንበብ ከባድ እንደሆነ ከብዙ አመት በፊት በደንብ አውቃለች፡፡ እናም ፍርሃቷ ጨመረ።
ምንያህል የተባለው ዶ.ር ወደአባቷ እየተመለከተ ገለፃውን ቀጠለ‹‹የባለቤቶት X ሬይ ውጤት አግኝተናል።››ጥቁሩ አይኖቹ በጥልቅ ርህራሄ ሁለቱንም አስተዋላቸው።‹‹በጣም ከባድ የሆነ የጭን አጥንት ስብራት ገጥሟቸዋል።ከአጥንት በላይ የሆነ ስብራት በሚመስል ነገር የተወሳሰበ ነው። ለረጅም ጊዜ እዚሁ ሆስፒታል ተኝተው መታከም አለባቸው››
አቶ ቸርነት እራሳቸውን ለማረጋጋት ያህል አይናቸውን ጨፈኑ.. ከዛ ከፈቱ …።ራሄል አሁንም ፀጋን በአንድ እጇ ይዛ ቀስ በቀስ ስሯ ያለ ወንበር ላይ ልትቀመጥ ስትሞክር ድንገት ክንዷ ላይ ያለችው እህቷን እንደያዘች ሚዛኗን በመጠኑ ስታ ልትወድቅ ስትል ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተላት የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ተንደረደረና ክንዷን ይዞ በዝግታ እንድትቀመጥ ረዳት፡፡
‹‹አመሰግናለሁ››አለች ራሄል ።
ዔሊያስ እጁ አሁንም በትሁት ትከሻ ላይ ነው።
❤45👍4🥰2
የራሄል ሆዷ ሲገለባበጥ ይታወቃታል እንደገና የማዞር ስሜት ተሰማት።ራሄል ፀጋ ከእጇ ሾልካ ከመውደቋ በፊት ‹‹እባክህ ልትወሰዳት ትችላለህ?››በማለት ወደ ዔሊያስ ገፋቻት፣ ዶ/ር ኤልያስ ግራ አጋቢ እይታ ካያት በኃላ ፀጋን ወሰዳት እና በቀላሉ ወደ እቅፍ አስገባት።ራሄል ወደ ዶ/ር ምንያህል ትኩረቷን ሰበሰበችና ‹‹ይቅርታ ስለ እናቴ እየነገርከን ነበር …ሙሉ በሙሉ የማገገም እድሏ ምን ያህል ነው?"ስትል ጠየቀችው፡፡መልሱን ለመስማት ግን ብርታቱ አልነበራትም፡፡
‹‹በጣም ጥሩ የሚባል ነው:፡፡እርግጥ እንደእሷቸው ብርታትና ጥረት ይወሰናል…ቢሆንም ጊዜ ይወሳዳል እንጂ መዳናቸው አይቀርም፡፡››
‹‹ምን ያህል ጊዜ በሆስፒታል የምትቆይ ይመስልሀል?››አቶ ቸርነት ጠየቁት፡፡
‹‹ከሦስት እስከ አራት ሳምንታት ገደማ ምን አልባትም ከወር በላይ የግድ በሆስፒታል መቆየት አለባቸው…ከዛ በኃላ ያለውን ህክምና ምን አልባት እቤታቸው ሆነው የሚከታተሉበት መንገድ እናመቻች ይሆናል፡፡››
አቶ ቸርነት በቆሙበት አገጫቸውን በእጇቸው እያሻሹ፣ የቦዙ ዓይኖቻቸውን ግድግዳው ላይ ሰክተው በሀሳብ ጠፋ።ወደ ራሔል ተመለከቱ ‹‹ከእናትሽ ጋር ያን ያህል ረጅም ጊዜ መለየት አልችልም..አብሬት እዚህ ምቆየው እኔ ነኝ›› አሉ፡፡
‹‹አውቃለሁ አባዬ›› እጇቸውን ያዘችና ጨመቀቻቸው።
‹‹እና ስለ ፀጋስ?››አባቷ በጭንቀት እና ግራ በመጋባት ጠየቁ።
ዶ/ር ምንያህል ዔሊያስን ተመለከተ። ‹‹ዶክተር ዓሊ የቀሩትን ጥያቄዎችችሁን ሊመልስላችሁ ይችላል ብዬ አስባለሁ. አሁን ወደ ባለቤቶት ሄጄ አንዳንድ ምርመራዎችን ማድረግ አለብኝ፡፡››ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
‹‹አስደሳች ዜና ስለሌለኝ አዝናለሁ፣ ግን ደግሞ ከዚህም የከፋ ጉዳት ስላልደረሰባቸው ልናመሰግነው ይገባል።››ኤልያስ ነው ተናጋሪው፡፡
አቶ ቸርነት በኤልያስ ሀሳብ በመስማማት ‹‹ለቸሩ ጌታ ምስጋና ይድረሰው ››ሲሉ ተናገረሩ፡፡
‹‹ፀጋን ከእኛ ጋር እዚህ መሆን ትችላለች?›› አቶ ቸርነት ዶ/ር ኤሊያስን ጠየቁት፡፡
ኤልያስ ራሱን በአሉታ ነቀነቀ። ‹‹አይ እሷ እቤት መሆን ነው ያለባት … ።›› አለና ወደ ራሔል ተመለከተ፣ ከዚያም ወደ አቶ ቸርነት ተመለሰ። ‹‹እናትሽን ለመርዳት አባትሽ ሙሉ ትኩረታቸውን እሷቸው ላይ ማድረግ አለባቸው… እና ለፀጋ ጤና ደግሞ በዚህ ሁኔታ ውስጥ መገኘት ጥሩ ውጤት አያመጣም።››
‹‹ደህና, ስለ ትንሹ ልጃችን የሆነ ውሳኔ መወሰን እንዳለብኝ ይሰማኛል.››እጇቸውን ራሰ በራ ጭንቅላታቸው ላይ አሳርፈው ወደ ራሄል ዞሩና ፈገግ አሉ‹‹ራሄል፣ ማሬ፣ ፀጋን መንከባከብ ትችያለሽ?››ሲሉ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ? ፀጋን መንከባከብ?››የራሄል ድንጋጤ አስፈሪ ነበር፡፡
እጆቿን እርስ በርሳቸው አቆላለፈች….‹‹ግን ብዙ ስራ መስራት አለብኝ … ማለቴ ፀጋ የምትፈልገውን ያህል ጊዜ አብሬያት ለማሳለፍ እንደምችል እርግጠኛ አይደለሁም›› ራሄል ተርበተበተች፡፡ አቶ ቸርነት ተነፈሱ።
‹‹ሞግዚት እቀጥርላት ነበር፣ ግን እንደምታውቂው እሷ ከአዲስ ሰው ጋር በቶሎ መልመድ አትችልም…በዛ ላይ ትእግስት ኖሮት እሷን በስርዓቱ የሚንከባከብ ሰው ለማግኘት ይከብዳል….ቤት ካሉት ሰራኞች ጋር እንኳን ያላትን ግንኙነት የምታውቂው ነው››በማለት ያሳሰባቸውን ነገር በዝርዝር አስረዷት፡፡
ውይይታቸውን እና በአባትና ልጅ መሀከል የተፈጠረውን ውጥረት በትኩረት ሲከታተል የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ሌላ አማራጭ ፕሮፖዛል ሊያቀርብ ሲዘጋጅ ድንገት ራሄል እጇን በአባቷ ትከሻ ላይ አድርጋ ፈገግ በማለት‹‹ ያልኩት የስራ ጫና እንዳለ ቢሆንም ..ነገር ግን ፀጋ እህቴ ነች። ለእሷ ቅድሚያ መስጠት እንዳለብኝ እገነዘባለው…እና አባዬ አንተ ምንም አታስብ ለእሷ አስፈላጊውን እንክብካቤ እንደማደርግላት አረጋግጥልሀለው።››ስትል ሁለቱም ባልጠበቁት ወኔና ቁርጠኝነት ቃል በመግባት አስደመመቻቸው፡፡
አቶ ቸርነትም ትልቋን ሴት ልጇቸውን በፍቅር ትከሻዋን መታ መታ እያደረጉ ‹‹እናመሰግናለን ውዴ››ሲሉ አመሰገኗት ። ወደ ፀጋ ዞረው አቀፏትና‹‹ ከእህቷ ጋር ከመሄዷ በፊት እናቷን እንድታይ ማድረግ እችላለሁ?›› ሲል ደ/ር ዔሊያስን ጠየቁት።
ዔሊ መጋረጃውን ወደ ጎን ያዘና ‹‹ምን አልባት የመድሀኒቱ ተፅዕኖ ማንንም እንዳይለዩ ሊያደርጋቸው ይችላል ግን መሞከር እንችላለን።››
አቶ ቸርነት ፀጋን ይዘው ወደባለቤታቸው ክፍል ገቡ ፣ ራሄል ተከትላቸው ልትሄድ ስትል ዔሊ ትከሻዋን ያዘና አስቆማት። ወደ ኋላ ተመለሰች። ኮስተርተር አለችበት፡፡
‹‹ለአንድ አፍታ ላናግርሽ ፈልጌ ነበር››አለ ። ራሄል ወደ አባቷ ተመለከተች፣ ከዚያም ወደኃላ ቀረችና ‹‹ እሺ ይቻላል፡፡›› አለችው፡፡
‹‹ፀጋን መንከባከብ የሚከብድሽ ከሆነ ለአንቺ አማራጭ እንደማገኝልሽ እርግጠኛ ነኝ።››አላት፡፡
ራሄል አይኗ ጠበበ። ‹‹አማራጭ አያስፈልገኝም… እህቴ ነች። እሷን በጥንቃቄ መንከባከብና መጠበቅ እችላለሁ።››በንግግሯ ውስጥ ያለውን እርግጠኝነት አስገረመው።
በአስተያየቱ በእሷ እርግጠኛ እንዳልሆነ ተረዳች‹‹አውቃለው…ከዚህ በፊት ልጅ ተንከባክቤ አላውቅም፣ ግን...››በራስ የመተማመን አቅሟ ለአፍታ ቢሆን ሲወርድ ታወቃት። ‹‹ይህን አደርጋለሁ››
‹‹ጥሩ እንደምታደርጊው እርግጠኛ ነኝ ..ወደ ቢሮዬ ለመምጣት ፈቃደኛ ከሆንሽ የሚያስፈልጉሽን መረጃ ልሰጥሽ እችላለሁ›› አላት፡፡
‹‹እሺ››አለችው።
ዔሊያስ የትንሿ ልጅ ጤንነትን በቅርበት የመከታተል ሞያዊም ሆነ ሞራላዊ ግዴታ እንዳለበት ያውቃል። ለዚች ሴት ኩራት ሲባል ያቺ ሚስኪን ልጅ እንድትሰቃይ አይፈቅድም።
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹በጣም ጥሩ የሚባል ነው:፡፡እርግጥ እንደእሷቸው ብርታትና ጥረት ይወሰናል…ቢሆንም ጊዜ ይወሳዳል እንጂ መዳናቸው አይቀርም፡፡››
‹‹ምን ያህል ጊዜ በሆስፒታል የምትቆይ ይመስልሀል?››አቶ ቸርነት ጠየቁት፡፡
‹‹ከሦስት እስከ አራት ሳምንታት ገደማ ምን አልባትም ከወር በላይ የግድ በሆስፒታል መቆየት አለባቸው…ከዛ በኃላ ያለውን ህክምና ምን አልባት እቤታቸው ሆነው የሚከታተሉበት መንገድ እናመቻች ይሆናል፡፡››
አቶ ቸርነት በቆሙበት አገጫቸውን በእጇቸው እያሻሹ፣ የቦዙ ዓይኖቻቸውን ግድግዳው ላይ ሰክተው በሀሳብ ጠፋ።ወደ ራሔል ተመለከቱ ‹‹ከእናትሽ ጋር ያን ያህል ረጅም ጊዜ መለየት አልችልም..አብሬት እዚህ ምቆየው እኔ ነኝ›› አሉ፡፡
‹‹አውቃለሁ አባዬ›› እጇቸውን ያዘችና ጨመቀቻቸው።
‹‹እና ስለ ፀጋስ?››አባቷ በጭንቀት እና ግራ በመጋባት ጠየቁ።
ዶ/ር ምንያህል ዔሊያስን ተመለከተ። ‹‹ዶክተር ዓሊ የቀሩትን ጥያቄዎችችሁን ሊመልስላችሁ ይችላል ብዬ አስባለሁ. አሁን ወደ ባለቤቶት ሄጄ አንዳንድ ምርመራዎችን ማድረግ አለብኝ፡፡››ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
‹‹አስደሳች ዜና ስለሌለኝ አዝናለሁ፣ ግን ደግሞ ከዚህም የከፋ ጉዳት ስላልደረሰባቸው ልናመሰግነው ይገባል።››ኤልያስ ነው ተናጋሪው፡፡
አቶ ቸርነት በኤልያስ ሀሳብ በመስማማት ‹‹ለቸሩ ጌታ ምስጋና ይድረሰው ››ሲሉ ተናገረሩ፡፡
‹‹ፀጋን ከእኛ ጋር እዚህ መሆን ትችላለች?›› አቶ ቸርነት ዶ/ር ኤሊያስን ጠየቁት፡፡
ኤልያስ ራሱን በአሉታ ነቀነቀ። ‹‹አይ እሷ እቤት መሆን ነው ያለባት … ።›› አለና ወደ ራሔል ተመለከተ፣ ከዚያም ወደ አቶ ቸርነት ተመለሰ። ‹‹እናትሽን ለመርዳት አባትሽ ሙሉ ትኩረታቸውን እሷቸው ላይ ማድረግ አለባቸው… እና ለፀጋ ጤና ደግሞ በዚህ ሁኔታ ውስጥ መገኘት ጥሩ ውጤት አያመጣም።››
‹‹ደህና, ስለ ትንሹ ልጃችን የሆነ ውሳኔ መወሰን እንዳለብኝ ይሰማኛል.››እጇቸውን ራሰ በራ ጭንቅላታቸው ላይ አሳርፈው ወደ ራሄል ዞሩና ፈገግ አሉ‹‹ራሄል፣ ማሬ፣ ፀጋን መንከባከብ ትችያለሽ?››ሲሉ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ? ፀጋን መንከባከብ?››የራሄል ድንጋጤ አስፈሪ ነበር፡፡
እጆቿን እርስ በርሳቸው አቆላለፈች….‹‹ግን ብዙ ስራ መስራት አለብኝ … ማለቴ ፀጋ የምትፈልገውን ያህል ጊዜ አብሬያት ለማሳለፍ እንደምችል እርግጠኛ አይደለሁም›› ራሄል ተርበተበተች፡፡ አቶ ቸርነት ተነፈሱ።
‹‹ሞግዚት እቀጥርላት ነበር፣ ግን እንደምታውቂው እሷ ከአዲስ ሰው ጋር በቶሎ መልመድ አትችልም…በዛ ላይ ትእግስት ኖሮት እሷን በስርዓቱ የሚንከባከብ ሰው ለማግኘት ይከብዳል….ቤት ካሉት ሰራኞች ጋር እንኳን ያላትን ግንኙነት የምታውቂው ነው››በማለት ያሳሰባቸውን ነገር በዝርዝር አስረዷት፡፡
ውይይታቸውን እና በአባትና ልጅ መሀከል የተፈጠረውን ውጥረት በትኩረት ሲከታተል የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ሌላ አማራጭ ፕሮፖዛል ሊያቀርብ ሲዘጋጅ ድንገት ራሄል እጇን በአባቷ ትከሻ ላይ አድርጋ ፈገግ በማለት‹‹ ያልኩት የስራ ጫና እንዳለ ቢሆንም ..ነገር ግን ፀጋ እህቴ ነች። ለእሷ ቅድሚያ መስጠት እንዳለብኝ እገነዘባለው…እና አባዬ አንተ ምንም አታስብ ለእሷ አስፈላጊውን እንክብካቤ እንደማደርግላት አረጋግጥልሀለው።››ስትል ሁለቱም ባልጠበቁት ወኔና ቁርጠኝነት ቃል በመግባት አስደመመቻቸው፡፡
አቶ ቸርነትም ትልቋን ሴት ልጇቸውን በፍቅር ትከሻዋን መታ መታ እያደረጉ ‹‹እናመሰግናለን ውዴ››ሲሉ አመሰገኗት ። ወደ ፀጋ ዞረው አቀፏትና‹‹ ከእህቷ ጋር ከመሄዷ በፊት እናቷን እንድታይ ማድረግ እችላለሁ?›› ሲል ደ/ር ዔሊያስን ጠየቁት።
ዔሊ መጋረጃውን ወደ ጎን ያዘና ‹‹ምን አልባት የመድሀኒቱ ተፅዕኖ ማንንም እንዳይለዩ ሊያደርጋቸው ይችላል ግን መሞከር እንችላለን።››
አቶ ቸርነት ፀጋን ይዘው ወደባለቤታቸው ክፍል ገቡ ፣ ራሄል ተከትላቸው ልትሄድ ስትል ዔሊ ትከሻዋን ያዘና አስቆማት። ወደ ኋላ ተመለሰች። ኮስተርተር አለችበት፡፡
‹‹ለአንድ አፍታ ላናግርሽ ፈልጌ ነበር››አለ ። ራሄል ወደ አባቷ ተመለከተች፣ ከዚያም ወደኃላ ቀረችና ‹‹ እሺ ይቻላል፡፡›› አለችው፡፡
‹‹ፀጋን መንከባከብ የሚከብድሽ ከሆነ ለአንቺ አማራጭ እንደማገኝልሽ እርግጠኛ ነኝ።››አላት፡፡
ራሄል አይኗ ጠበበ። ‹‹አማራጭ አያስፈልገኝም… እህቴ ነች። እሷን በጥንቃቄ መንከባከብና መጠበቅ እችላለሁ።››በንግግሯ ውስጥ ያለውን እርግጠኝነት አስገረመው።
በአስተያየቱ በእሷ እርግጠኛ እንዳልሆነ ተረዳች‹‹አውቃለው…ከዚህ በፊት ልጅ ተንከባክቤ አላውቅም፣ ግን...››በራስ የመተማመን አቅሟ ለአፍታ ቢሆን ሲወርድ ታወቃት። ‹‹ይህን አደርጋለሁ››
‹‹ጥሩ እንደምታደርጊው እርግጠኛ ነኝ ..ወደ ቢሮዬ ለመምጣት ፈቃደኛ ከሆንሽ የሚያስፈልጉሽን መረጃ ልሰጥሽ እችላለሁ›› አላት፡፡
‹‹እሺ››አለችው።
ዔሊያስ የትንሿ ልጅ ጤንነትን በቅርበት የመከታተል ሞያዊም ሆነ ሞራላዊ ግዴታ እንዳለበት ያውቃል። ለዚች ሴት ኩራት ሲባል ያቺ ሚስኪን ልጅ እንድትሰቃይ አይፈቅድም።
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤51👍17
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
❤66👍3
‹‹ለጊዜህ አመሰግናለሁ፣ ዶ/ር ኤሊያስ እንደምንገናኝ እርግጠኛ ነኝ።››አለችው፡፡
ዔሊያስም በሩን ሊከፍትላት በጠረጴዛው ዙሪያ ዞሮ ተራመደ..
ራሄል ስለጸጋ የጤና ችግር የሰማችው ነገር አእምሮዋ ሊሸከም ከሚችለው በላይ ነው የሆነባት፡፡እንዴት እንደምትወጣውም መገመት አልቻለችም፡፡
ዓሊ ከዚህ በፊት በግዴለሽነት የፍቅር ግንኙነት ቢጀምርም፣ ዘላቂነት ላለው ግንኙነት ግን ዝግጁ ሀኖ አያውቅም ነበር ። አሁንም እንደ ራሄል ካለች ሴት ጋር ተመሳሳዩን ማድረግ እንደማይችል ያውቃል፡፡ እሷ ሌሎች ምታስቀድማቸው ጉዳዮች እንዳሏት ተረድቷል, እርግጥ ቤተሰቦቿ ከእሱ ጋር እንዳትገናኝ ተስፋ እንዳደረጉ ያውቃል፡፡ በዋነኛነት የእሱን ጀርባ ምን እንደሆነ ባለማወቃቸው ነው። ወላጆቹን ማንነት ቢያውቁ እንደዛ እንደማያስብ እርግጠኛ ነው፡፡ ኮፍያውን ይዞ ቢሮውን ለቆ ወደ ቤቱ አመራ።
ወደ ቤቱ ሲገባ ስልኩ እየጮኸ ነበር እና የጥሪ ማሳያውን በጨረፍታ ተመለከተ ፈገግ አለና አነሳው።‹‹ሄይ እናቴ እንዴት ነሽ?›› ስልኩን በትከሻውና በጆሮው መካከል አድርጎ ጠየቀ። እናቱ የቤቱን ሁኔታ ማየት እንደማትችል ቢያውቅም የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶታል።
‹‹ደህና ነኝ። ጧት የት ነበርክ?›› አሳዳጊ እናቱ ጠየቀችው፡፡ ‹‹ሁለት ጊዜ ሞክሬልህ ነበር.›› በድምጿ ውስጥ የስጋት ስሜት ይነበባል ፣ ይህም ዔሊን የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት›› እንዲሰማው አድርጎታል።
‹‹ የእረፍት ቀኔ ነበር ..ግን ሆስፒታል ድንገተኛ ተደወለልኝና ስራ ገባው…ገና በር ከፍቼ ስገባ ነው የደወልሺልኝ.››
‹‹አንተም ሆንክ ቢኒ ቤተክርስቲያን ትመጣላችሁ ብዬ ጠብቄ ነበር..አንተስ እሺ ስራ ላይ ነኝ አልክ… የእሱስ ሰበብ ምንድነው?››
ሰበቡን ያውቃል..እሱ ብቻ ሳይሆን አሳዳጊ እናቱም ጭምር ለምን በቤተክርስቲያን መሄድ እንዳቆመ በደንብ ያውቃሉ..እሱ እንኳን ድሮም ለቤተክርስቲያን እስከዚህም ነበር ወንድሙ ግን ባለቤቱ በአንድሳምንት በሽታ ታማ ሳይታሰብ እስክትሞትበት ድረስ በጣም አካራሪ የሚባል ሀይማኖተኛ ሰው ነበር…ከዛ በኋላ ግን ቀስ በቀስ እግሩን ከቤተክርስቲያን ልቡን ደግሞ ከእግዚያብሄር ሰበሰበ…..በዚህ ጉዳይ ከራሄል ጋር ተመሳሳይ ታሪክ እንዳላቸው ያውቃል…አሁን ግን ይህንን የወንድሙን ጉዳይ ከእናቱ ጋር አንስቶ መጨቃጨቅ ስላልፈለገ በዝምታ ዘለለው
እሱ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ጋር የነበረው ዝምድና ሁል ጊዜ ወጣ ገባ ያለው ነበር ። አሳዳጊዎቹ ከእሱ ይልቅ ከቢኒያም ጋር ንፁህ በፍቅር የተሞላ የወላጅ እና የልጅ ግንኙነት ነው ያላቸው፡፡ እሱ ግን ስለ ስጋ ወላጆቹ ማወቅ ይፈልግ ስለነበር ብዙ ጊዜ ባየተዋርነት ይሰማው ነበርና እቤት ውስጥ በራሱ ችግር ይፈጥራ ል… ስለወላጆቹ የሚያውቁትን እንዲነግሩት ያስቸግራቸው ነበር ..እነሱ ግን ምንም ሊነግሩት አልቻሉም።
ባለፈው ዓመት እሱ እና ቢንያም የወላጆቻቸውን ቤት እያፀዱ ሳለ በሰገነት ላይ የፎቶ ሳጥን አገኘ. እነዛን ፎቶዎች ከዚህ በፊት አይቷቸው አያውቅም ነበር ፡ የእሱ የስጋ ወላጆቹ ነበሩ። አሳዳጊዎቹ እሱን ከማደጎ ቤት በተረከቡት ጊዜ ፎቶውንም አብረው ነበር የተረከቡት… ከዛ ግን አርቀው አስቀመጡና ረሱት ፡፡
‹‹ወደ ሆስፒታል እንደተጠራህ ተናግረሃል›› ስትል እናቱ ተናገረች። ‹‹በጣም ከባድ ነገር እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ.››ዔሊ ራሔልን እና ጸጋን አሰበ እና ግንባሩን በጣቱ አሻሸ።
‹‹ከታካሚዬ አንዷ ወደቀች፣ ግን ደህና ነች፣ አንቺ እና አባ እንዴት ናችሁ?››
‹‹ደህና ነን ፡ ግን አንዳንድ ጊዜ መጥተን አንተን እና ቢኒን ቤቱን እንደትጨረሱት ልንረዳችሁ እንፈልግ ነበር።››
‹‹እሺ እማማ፣ አንቺና አባባ በዚህ ጉዳይ ላይ እንድትጨናነቁ አልፈልግም። ››
የእናቱ ዝምታ ሌላ የጥፋተኝነት ስሜት ፈጠረ።
ተሰናበታቸውና እና ስልኩን ዘጋው፡፡
በዚህ ቤት ጉዳይ ወላጆቹንም ሆነ ወንድሙ ቢኒያምን ብዙ ማስቸገር አይፈልግም፡፡
- ይህንን ቤት መስራት መጀመሩ ለእሱ ትልቅ ስኬት ነው ፣ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የራሱን ቦታ ይፈልግ ነበር ፡፡ እራሱን የሚገነባበት ቦታ። ይህንን ለአሳዳጊ ወላጆቹ በቀላሉ ማስረዳት የሚችለው ነገር አልነበረም፣ ። ገና ወንደላጤነቱን ሳያጣጥም ብድር ውስጥ ገብቶ እቤት ወደመገንባት ውስጥ የገባበትን ምክንያት ቢኒያም እንኳን አልተረዳውም።ምክንያቱም ወንድሙ እንደ እሱ ስለ ስጋ ወላጅቹ ምንም አይነት ትዝታ አልነበረውም። ለእሱ አሳዳጊ ወላጆቹ የስጋ ወላጆቹ እንደሆኑ ነው የሚሰማውም…የሚያምነውም፡፡
እርግጥ ኤልያስም አሳዳጊ ወላጆቹን ይወዳል ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከእነሱ ጋር ለመኖር ወደቤታቸው ሲወስዱት የስጋ ወላጆቹን ትዝታዎች በጀርባው አዝሎ ስለነበረ በተለየ ሁኔታ በጣም ያስቸግራቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ስለ ወላጆቹ በጭራሽ ማውራት አቆሙ፡፡ ኤሊ የዛሬ አመት ፎቶዎቹን እስኪያገኝ ድረስ ይህን ተቀብሎ ነበር።አሁን .የፎቶ ሣጥኑን ወደቤቱ አምጥቶታል እነኚያ ሰዎች እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ሙከራ ላይ ነው፡፡ ህይወት የሰጡት ወደዚህ ምድር ጎትተው ያመጡት፤እነዛን የመጀመሪያዎቹን ጥቂት የህፃንነት አመታትን ይንከባከቡት የነበሩትን ሰዎች ማነነት የማወቅ ጉጉት እያሰቃየው ነው።
ሳያውቅ እጁን አዞረና ጀርባ ላይ ያለውን ጠባሳ አሻሸው፣ከአደጋውን ያተረፈው ቅሪት ነው ።ስለ ፀጋ አሰበ። ገና ህፃን ስለሆነች ወደፊት ስለ እናቷ ምንም ትዝታ እንዳማይኖራት ተስፋ አደረገ ። ግን ቢያንስ ለእሷ እሱ አለላት..እናቷ ምን አይነት ሰው እንደሆነች….ስለደግነቷ..ስለውበቷ እና ስለአስቂኝ ጫወታዋ …በዝርዝር ሊነግራት ይችላል፡፡ከፈለገችም…አሁን በህይወት ስለሌሉት አያቶቹም ጭምር ሊነግራት ይችላል…ምክንያቱም የእናቷ የፅጌረዳን እናትና አባት ከልጅነቱ ጀምሮ በደንብ ያውቃቸዋል…ፅጌረዳ ተከትሎ ብዙ ጊዜ እቤታቸው የመመላለስ እድል ነበረው..ደሆች ቢሆኑም ልበ ቀና መልካም ሰዎች ነበሩ…ይሄንን ሁሉ ሊያስረዳት ይችላል..ለእሱ ግን እንደዚህ አይነት ስለዋላጆቹ ጥቂት እንኳን አውቃለው የሚል ሰው የማግኘት እድል የለውም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ዔሊያስም በሩን ሊከፍትላት በጠረጴዛው ዙሪያ ዞሮ ተራመደ..
ራሄል ስለጸጋ የጤና ችግር የሰማችው ነገር አእምሮዋ ሊሸከም ከሚችለው በላይ ነው የሆነባት፡፡እንዴት እንደምትወጣውም መገመት አልቻለችም፡፡
ዓሊ ከዚህ በፊት በግዴለሽነት የፍቅር ግንኙነት ቢጀምርም፣ ዘላቂነት ላለው ግንኙነት ግን ዝግጁ ሀኖ አያውቅም ነበር ። አሁንም እንደ ራሄል ካለች ሴት ጋር ተመሳሳዩን ማድረግ እንደማይችል ያውቃል፡፡ እሷ ሌሎች ምታስቀድማቸው ጉዳዮች እንዳሏት ተረድቷል, እርግጥ ቤተሰቦቿ ከእሱ ጋር እንዳትገናኝ ተስፋ እንዳደረጉ ያውቃል፡፡ በዋነኛነት የእሱን ጀርባ ምን እንደሆነ ባለማወቃቸው ነው። ወላጆቹን ማንነት ቢያውቁ እንደዛ እንደማያስብ እርግጠኛ ነው፡፡ ኮፍያውን ይዞ ቢሮውን ለቆ ወደ ቤቱ አመራ።
ወደ ቤቱ ሲገባ ስልኩ እየጮኸ ነበር እና የጥሪ ማሳያውን በጨረፍታ ተመለከተ ፈገግ አለና አነሳው።‹‹ሄይ እናቴ እንዴት ነሽ?›› ስልኩን በትከሻውና በጆሮው መካከል አድርጎ ጠየቀ። እናቱ የቤቱን ሁኔታ ማየት እንደማትችል ቢያውቅም የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶታል።
‹‹ደህና ነኝ። ጧት የት ነበርክ?›› አሳዳጊ እናቱ ጠየቀችው፡፡ ‹‹ሁለት ጊዜ ሞክሬልህ ነበር.›› በድምጿ ውስጥ የስጋት ስሜት ይነበባል ፣ ይህም ዔሊን የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት›› እንዲሰማው አድርጎታል።
‹‹ የእረፍት ቀኔ ነበር ..ግን ሆስፒታል ድንገተኛ ተደወለልኝና ስራ ገባው…ገና በር ከፍቼ ስገባ ነው የደወልሺልኝ.››
‹‹አንተም ሆንክ ቢኒ ቤተክርስቲያን ትመጣላችሁ ብዬ ጠብቄ ነበር..አንተስ እሺ ስራ ላይ ነኝ አልክ… የእሱስ ሰበብ ምንድነው?››
ሰበቡን ያውቃል..እሱ ብቻ ሳይሆን አሳዳጊ እናቱም ጭምር ለምን በቤተክርስቲያን መሄድ እንዳቆመ በደንብ ያውቃሉ..እሱ እንኳን ድሮም ለቤተክርስቲያን እስከዚህም ነበር ወንድሙ ግን ባለቤቱ በአንድሳምንት በሽታ ታማ ሳይታሰብ እስክትሞትበት ድረስ በጣም አካራሪ የሚባል ሀይማኖተኛ ሰው ነበር…ከዛ በኋላ ግን ቀስ በቀስ እግሩን ከቤተክርስቲያን ልቡን ደግሞ ከእግዚያብሄር ሰበሰበ…..በዚህ ጉዳይ ከራሄል ጋር ተመሳሳይ ታሪክ እንዳላቸው ያውቃል…አሁን ግን ይህንን የወንድሙን ጉዳይ ከእናቱ ጋር አንስቶ መጨቃጨቅ ስላልፈለገ በዝምታ ዘለለው
እሱ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ጋር የነበረው ዝምድና ሁል ጊዜ ወጣ ገባ ያለው ነበር ። አሳዳጊዎቹ ከእሱ ይልቅ ከቢኒያም ጋር ንፁህ በፍቅር የተሞላ የወላጅ እና የልጅ ግንኙነት ነው ያላቸው፡፡ እሱ ግን ስለ ስጋ ወላጆቹ ማወቅ ይፈልግ ስለነበር ብዙ ጊዜ ባየተዋርነት ይሰማው ነበርና እቤት ውስጥ በራሱ ችግር ይፈጥራ ል… ስለወላጆቹ የሚያውቁትን እንዲነግሩት ያስቸግራቸው ነበር ..እነሱ ግን ምንም ሊነግሩት አልቻሉም።
ባለፈው ዓመት እሱ እና ቢንያም የወላጆቻቸውን ቤት እያፀዱ ሳለ በሰገነት ላይ የፎቶ ሳጥን አገኘ. እነዛን ፎቶዎች ከዚህ በፊት አይቷቸው አያውቅም ነበር ፡ የእሱ የስጋ ወላጆቹ ነበሩ። አሳዳጊዎቹ እሱን ከማደጎ ቤት በተረከቡት ጊዜ ፎቶውንም አብረው ነበር የተረከቡት… ከዛ ግን አርቀው አስቀመጡና ረሱት ፡፡
‹‹ወደ ሆስፒታል እንደተጠራህ ተናግረሃል›› ስትል እናቱ ተናገረች። ‹‹በጣም ከባድ ነገር እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ.››ዔሊ ራሔልን እና ጸጋን አሰበ እና ግንባሩን በጣቱ አሻሸ።
‹‹ከታካሚዬ አንዷ ወደቀች፣ ግን ደህና ነች፣ አንቺ እና አባ እንዴት ናችሁ?››
‹‹ደህና ነን ፡ ግን አንዳንድ ጊዜ መጥተን አንተን እና ቢኒን ቤቱን እንደትጨረሱት ልንረዳችሁ እንፈልግ ነበር።››
‹‹እሺ እማማ፣ አንቺና አባባ በዚህ ጉዳይ ላይ እንድትጨናነቁ አልፈልግም። ››
የእናቱ ዝምታ ሌላ የጥፋተኝነት ስሜት ፈጠረ።
ተሰናበታቸውና እና ስልኩን ዘጋው፡፡
በዚህ ቤት ጉዳይ ወላጆቹንም ሆነ ወንድሙ ቢኒያምን ብዙ ማስቸገር አይፈልግም፡፡
- ይህንን ቤት መስራት መጀመሩ ለእሱ ትልቅ ስኬት ነው ፣ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የራሱን ቦታ ይፈልግ ነበር ፡፡ እራሱን የሚገነባበት ቦታ። ይህንን ለአሳዳጊ ወላጆቹ በቀላሉ ማስረዳት የሚችለው ነገር አልነበረም፣ ። ገና ወንደላጤነቱን ሳያጣጥም ብድር ውስጥ ገብቶ እቤት ወደመገንባት ውስጥ የገባበትን ምክንያት ቢኒያም እንኳን አልተረዳውም።ምክንያቱም ወንድሙ እንደ እሱ ስለ ስጋ ወላጅቹ ምንም አይነት ትዝታ አልነበረውም። ለእሱ አሳዳጊ ወላጆቹ የስጋ ወላጆቹ እንደሆኑ ነው የሚሰማውም…የሚያምነውም፡፡
እርግጥ ኤልያስም አሳዳጊ ወላጆቹን ይወዳል ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከእነሱ ጋር ለመኖር ወደቤታቸው ሲወስዱት የስጋ ወላጆቹን ትዝታዎች በጀርባው አዝሎ ስለነበረ በተለየ ሁኔታ በጣም ያስቸግራቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ስለ ወላጆቹ በጭራሽ ማውራት አቆሙ፡፡ ኤሊ የዛሬ አመት ፎቶዎቹን እስኪያገኝ ድረስ ይህን ተቀብሎ ነበር።አሁን .የፎቶ ሣጥኑን ወደቤቱ አምጥቶታል እነኚያ ሰዎች እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ሙከራ ላይ ነው፡፡ ህይወት የሰጡት ወደዚህ ምድር ጎትተው ያመጡት፤እነዛን የመጀመሪያዎቹን ጥቂት የህፃንነት አመታትን ይንከባከቡት የነበሩትን ሰዎች ማነነት የማወቅ ጉጉት እያሰቃየው ነው።
ሳያውቅ እጁን አዞረና ጀርባ ላይ ያለውን ጠባሳ አሻሸው፣ከአደጋውን ያተረፈው ቅሪት ነው ።ስለ ፀጋ አሰበ። ገና ህፃን ስለሆነች ወደፊት ስለ እናቷ ምንም ትዝታ እንዳማይኖራት ተስፋ አደረገ ። ግን ቢያንስ ለእሷ እሱ አለላት..እናቷ ምን አይነት ሰው እንደሆነች….ስለደግነቷ..ስለውበቷ እና ስለአስቂኝ ጫወታዋ …በዝርዝር ሊነግራት ይችላል፡፡ከፈለገችም…አሁን በህይወት ስለሌሉት አያቶቹም ጭምር ሊነግራት ይችላል…ምክንያቱም የእናቷ የፅጌረዳን እናትና አባት ከልጅነቱ ጀምሮ በደንብ ያውቃቸዋል…ፅጌረዳ ተከትሎ ብዙ ጊዜ እቤታቸው የመመላለስ እድል ነበረው..ደሆች ቢሆኑም ልበ ቀና መልካም ሰዎች ነበሩ…ይሄንን ሁሉ ሊያስረዳት ይችላል..ለእሱ ግን እንደዚህ አይነት ስለዋላጆቹ ጥቂት እንኳን አውቃለው የሚል ሰው የማግኘት እድል የለውም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤71👍12
የራሄል ልብ በእፎይታ ተነፈሰ።አብሮት እየተራመደ ያለውን ተለማማጅ ዶ/ር ወደ ጎን ተመለከተው፣ እያወሩ ነበር ። ድንገት ዞር ሲል ከራሄል ጋር አይን ለአይን ተገጣጠሙ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገናኙ የተሰማትን አይነት ተመሳሳይ ምላሽ ተሰማት። ተንደርድሮ ወደእሷ መጣ፡፡
ከዚያም የፀጋን የህክምና ቻርት ላይ የሆነ ምልክት እያደረገች ወዳለችው ነርስ ተጠጋና ተመለከተ። ‹ታዲያ ችግሩ ምን ይመስላሻል ?›› ብሎ ጠየቀ ከራሄል ወደ ፀጋ ከዚያም ወደ ነርሷ ተመለከተ። ራሄል ‹‹ከፍኛ ትኩሳት አላት›› አለችው.
ነርሷ ‹‹አሁን የሙቀት መጠንዋን ወስጃለሁ….ትንሽ ከፍ ያለ ነው፣ ግን ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም።››
ራሔል ነርሷ ላይ አፈጠጠች ፣ግራ ተጋባች፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለከተች። ‹‹ በጣም እኮ ነበር የምትሞቀው.››
ዔሊ ሰንጠረዡን ከነርሷ ተቀብሎ ተመለከተ እና እጁን በህፃኗ ግንባሩ ላይ አደረገ። ፀጋ በድንገት ሁሉም ነገር ደህና የሆነ ይመስል ፈገግ አለችለት‹‹አሁንም አንቲ ባዮቲኮችን እየሰጠሻት ነው?›››
‹‹አዎ ››
‹‹ደህና፣ እየሰሩ ያሉ ይመስላሉ፣ ግን ፈገግታዋ ጠፍቷል፣ የድምፁ ቃናዋም ተለውጣል፣ እሷን መናደድ የለባትም››
‹‹የምን መናደድ …ከሰአት በኋላ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ለመንከባከብ የተመሰከረለትን የመዋለ ሕጻናት አገኘሁ።እና እዛ ወሰድኳት..ከስራ ተመልሼ ልወስዳት ስሄድ ታማ አገኘኋት… እና አሁን የሚያስፈልገኝ በእሷ ላይ ያለውን ችግር እንድትነግሩኝ ነው።››
ዔሊያስ በትንሹ ተነፈሰ… ነገር ግን ዓይኖቿን ራሄል ላይ እያንከራተተች ወዳለችው ታዳጊ ልጅ ተመለከተ። የታችኛው ከንፈሯ ያብለጨልጭ ጀመር እና እንደገና ልታለቅስ ያሰበች ይመስላል ። ራሄል ጀርባዋን እየደባበሰች አባበለቻት፡፡
በወረቀት ላይ ማስታወሻዎችን እየጻፈ። ‹‹ደህና ነች..አዎ፣ የሙቀት መጠኑ በትንሹ ከፍ ብሏል፣ ግን ያ ስለተበሳጨች ሊሆን ይችላል። አንድ ጆሮዋ ትንሽ ቀላ ያለ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ በፀረ-ባዮቲክስ መድሀኒት ይወርዳል። መበሳጨት ከጀመረች ስጧት። የሙቀት መጠኗን መቆጣጠሪያ በእጅሽ ላይ ሊኖርሽ ይገባል.. የሚያስፈልጉሽን ነገሮች ዝርዝር ነገ እሰጥሻለሁ፤››አለና ወረቀቱን ከፓድ ላይ ቀዶ ዘረጋላት።ራሄል በድንገት ሞኝነት ተሰማት፣ነገር ግን ፀጋ ደህና መሆኗን በማወቋ እፎይታ አግኝታለች።
ወረቀቱን ወደ ቦርሳዋ እያስገባች‹‹ለምክርህ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹በዚህ ኢንፌክሽን ደረጃ ለማረጋገጥ ከነገ ወዲያ እሷን ማየት እፈልጋለሁ። ለአንቺ ስንት ሰዓት ይምችሻል?››በጥያቄው ስለተበሳጨች እኩለ ሌሊት ልትለው አሰበች. ፡፡
‹‹ለምን አንተ ቀጠሮ አትይዝልኝም እኔ ፕሮግራሜን ማሸጋሸግ እችላለው፡፡ ››አለችው፡፡
‹‹ቤት ላገኝሽ ካልቻልኩ… የት ላገኝሽ እችላለሁ?››
የቢሮ ቁጥሯን እና የሞባይል ስልኳን ሰጠችው።በስራ ቦታ ልታገኘኝ ካልቻልክ ለሎዛ መልእክት ተውልኝ። ሞባይል ስልኬ በአብዛኛው ክፍት ነው። በተጨማሪም የወላጆቼ ቁጥር አለህ። ››
የንዴት ፈገግታ አሳያት።‹‹እነዚህ ሁሉ ቁጥሮች አያስፈልጉኝም?››
በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከወ.ሮ ላምሮት ጋር መገናኘት ነበረባት እና አሁን ለፀጋ የምትገዛቸው መድሀኒቶች አሉ..በዛ ላይ ምግቧንም መመገብ አለባት….በዚህ ሁኔታ ላይም እያለች ጥላት መሄድ አትችልም ፡፡ያላት ምርጫ ሴትዬዋን ይቅርታ ጠይቃ ሌላ ቀጠሮ ማስያዝ ነው፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››አለች.
‹‹ትሁትን ስላየህልኝ አመሰግናለሁ፣››አለችው በድጋሜ
‹‹ ከሁለት ቀናት በኋላ እንገናኝ።››አለና የድንገተኛ ክፍልን ለቅ ወጣ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ከዚያም የፀጋን የህክምና ቻርት ላይ የሆነ ምልክት እያደረገች ወዳለችው ነርስ ተጠጋና ተመለከተ። ‹ታዲያ ችግሩ ምን ይመስላሻል ?›› ብሎ ጠየቀ ከራሄል ወደ ፀጋ ከዚያም ወደ ነርሷ ተመለከተ። ራሄል ‹‹ከፍኛ ትኩሳት አላት›› አለችው.
ነርሷ ‹‹አሁን የሙቀት መጠንዋን ወስጃለሁ….ትንሽ ከፍ ያለ ነው፣ ግን ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም።››
ራሔል ነርሷ ላይ አፈጠጠች ፣ግራ ተጋባች፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለከተች። ‹‹ በጣም እኮ ነበር የምትሞቀው.››
ዔሊ ሰንጠረዡን ከነርሷ ተቀብሎ ተመለከተ እና እጁን በህፃኗ ግንባሩ ላይ አደረገ። ፀጋ በድንገት ሁሉም ነገር ደህና የሆነ ይመስል ፈገግ አለችለት‹‹አሁንም አንቲ ባዮቲኮችን እየሰጠሻት ነው?›››
‹‹አዎ ››
‹‹ደህና፣ እየሰሩ ያሉ ይመስላሉ፣ ግን ፈገግታዋ ጠፍቷል፣ የድምፁ ቃናዋም ተለውጣል፣ እሷን መናደድ የለባትም››
‹‹የምን መናደድ …ከሰአት በኋላ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ለመንከባከብ የተመሰከረለትን የመዋለ ሕጻናት አገኘሁ።እና እዛ ወሰድኳት..ከስራ ተመልሼ ልወስዳት ስሄድ ታማ አገኘኋት… እና አሁን የሚያስፈልገኝ በእሷ ላይ ያለውን ችግር እንድትነግሩኝ ነው።››
ዔሊያስ በትንሹ ተነፈሰ… ነገር ግን ዓይኖቿን ራሄል ላይ እያንከራተተች ወዳለችው ታዳጊ ልጅ ተመለከተ። የታችኛው ከንፈሯ ያብለጨልጭ ጀመር እና እንደገና ልታለቅስ ያሰበች ይመስላል ። ራሄል ጀርባዋን እየደባበሰች አባበለቻት፡፡
በወረቀት ላይ ማስታወሻዎችን እየጻፈ። ‹‹ደህና ነች..አዎ፣ የሙቀት መጠኑ በትንሹ ከፍ ብሏል፣ ግን ያ ስለተበሳጨች ሊሆን ይችላል። አንድ ጆሮዋ ትንሽ ቀላ ያለ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ በፀረ-ባዮቲክስ መድሀኒት ይወርዳል። መበሳጨት ከጀመረች ስጧት። የሙቀት መጠኗን መቆጣጠሪያ በእጅሽ ላይ ሊኖርሽ ይገባል.. የሚያስፈልጉሽን ነገሮች ዝርዝር ነገ እሰጥሻለሁ፤››አለና ወረቀቱን ከፓድ ላይ ቀዶ ዘረጋላት።ራሄል በድንገት ሞኝነት ተሰማት፣ነገር ግን ፀጋ ደህና መሆኗን በማወቋ እፎይታ አግኝታለች።
ወረቀቱን ወደ ቦርሳዋ እያስገባች‹‹ለምክርህ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹በዚህ ኢንፌክሽን ደረጃ ለማረጋገጥ ከነገ ወዲያ እሷን ማየት እፈልጋለሁ። ለአንቺ ስንት ሰዓት ይምችሻል?››በጥያቄው ስለተበሳጨች እኩለ ሌሊት ልትለው አሰበች. ፡፡
‹‹ለምን አንተ ቀጠሮ አትይዝልኝም እኔ ፕሮግራሜን ማሸጋሸግ እችላለው፡፡ ››አለችው፡፡
‹‹ቤት ላገኝሽ ካልቻልኩ… የት ላገኝሽ እችላለሁ?››
የቢሮ ቁጥሯን እና የሞባይል ስልኳን ሰጠችው።በስራ ቦታ ልታገኘኝ ካልቻልክ ለሎዛ መልእክት ተውልኝ። ሞባይል ስልኬ በአብዛኛው ክፍት ነው። በተጨማሪም የወላጆቼ ቁጥር አለህ። ››
የንዴት ፈገግታ አሳያት።‹‹እነዚህ ሁሉ ቁጥሮች አያስፈልጉኝም?››
በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከወ.ሮ ላምሮት ጋር መገናኘት ነበረባት እና አሁን ለፀጋ የምትገዛቸው መድሀኒቶች አሉ..በዛ ላይ ምግቧንም መመገብ አለባት….በዚህ ሁኔታ ላይም እያለች ጥላት መሄድ አትችልም ፡፡ያላት ምርጫ ሴትዬዋን ይቅርታ ጠይቃ ሌላ ቀጠሮ ማስያዝ ነው፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››አለች.
‹‹ትሁትን ስላየህልኝ አመሰግናለሁ፣››አለችው በድጋሜ
‹‹ ከሁለት ቀናት በኋላ እንገናኝ።››አለና የድንገተኛ ክፍልን ለቅ ወጣ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤31🤔13👏6
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
❤43
የራሄል ልብ በእፎይታ ተነፈሰ።አብሮት እየተራመደ ያለውን ተለማማጅ ዶ/ር ወደ ጎን ተመለከተው፣ እያወሩ ነበር ። ድንገት ዞር ሲል ከራሄል ጋር አይን ለአይን ተገጣጠሙ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገናኙ የተሰማትን አይነት ተመሳሳይ ምላሽ ተሰማት። ተንደርድሮ ወደእሷ መጣ፡፡
ከዚያም የፀጋን የህክምና ቻርት ላይ የሆነ ምልክት እያደረገች ወዳለችው ነርስ ተጠጋና ተመለከተ። ‹ታዲያ ችግሩ ምን ይመስላሻል ?›› ብሎ ጠየቀ ከራሄል ወደ ፀጋ ከዚያም ወደ ነርሷ ተመለከተ። ራሄል ‹‹ከፍኛ ትኩሳት አላት›› አለችው.
ነርሷ ‹‹አሁን የሙቀት መጠንዋን ወስጃለሁ….ትንሽ ከፍ ያለ ነው፣ ግን ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም።››
ራሔል ነርሷ ላይ አፈጠጠች ፣ግራ ተጋባች፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለከተች። ‹‹ በጣም እኮ ነበር የምትሞቀው.››
ዔሊ ሰንጠረዡን ከነርሷ ተቀብሎ ተመለከተ እና እጁን በህፃኗ ግንባሩ ላይ አደረገ። ፀጋ በድንገት ሁሉም ነገር ደህና የሆነ ይመስል ፈገግ አለችለት‹‹አሁንም አንቲ ባዮቲኮችን እየሰጠሻት ነው?›››
‹‹አዎ ››
‹‹ደህና፣ እየሰሩ ያሉ ይመስላሉ፣ ግን ፈገግታዋ ጠፍቷል፣ የድምፁ ቃናዋም ተለውጣል፣ እሷን መናደድ የለባትም››
‹‹የምን መናደድ …ከሰአት በኋላ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ለመንከባከብ የተመሰከረለትን የመዋለ ሕጻናት አገኘሁ።እና እዛ ወሰድኳት..ከስራ ተመልሼ ልወስዳት ስሄድ ታማ አገኘኋት… እና አሁን የሚያስፈልገኝ በእሷ ላይ ያለውን ችግር እንድትነግሩኝ ነው።››
ዔሊያስ በትንሹ ተነፈሰ… ነገር ግን ዓይኖቿን ራሄል ላይ እያንከራተተች ወዳለችው ታዳጊ ልጅ ተመለከተ። የታችኛው ከንፈሯ ያብለጨልጭ ጀመር እና እንደገና ልታለቅስ ያሰበች ይመስላል ። ራሄል ጀርባዋን እየደባበሰች አባበለቻት፡፡
በወረቀት ላይ ማስታወሻዎችን እየጻፈ። ‹‹ደህና ነች..አዎ፣ የሙቀት መጠኑ በትንሹ ከፍ ብሏል፣ ግን ያ ስለተበሳጨች ሊሆን ይችላል። አንድ ጆሮዋ ትንሽ ቀላ ያለ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ በፀረ-ባዮቲክስ መድሀኒት ይወርዳል። መበሳጨት ከጀመረች ስጧት። የሙቀት መጠኗን መቆጣጠሪያ በእጅሽ ላይ ሊኖርሽ ይገባል.. የሚያስፈልጉሽን ነገሮች ዝርዝር ነገ እሰጥሻለሁ፤››አለና ወረቀቱን ከፓድ ላይ ቀዶ ዘረጋላት።ራሄል በድንገት ሞኝነት ተሰማት፣ነገር ግን ፀጋ ደህና መሆኗን በማወቋ እፎይታ አግኝታለች።
ወረቀቱን ወደ ቦርሳዋ እያስገባች‹‹ለምክርህ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹በዚህ ኢንፌክሽን ደረጃ ለማረጋገጥ ከነገ ወዲያ እሷን ማየት እፈልጋለሁ። ለአንቺ ስንት ሰዓት ይምችሻል?››በጥያቄው ስለተበሳጨች እኩለ ሌሊት ልትለው አሰበች. ፡፡
‹‹ለምን አንተ ቀጠሮ አትይዝልኝም እኔ ፕሮግራሜን ማሸጋሸግ እችላለው፡፡ ››አለችው፡፡
‹‹ቤት ላገኝሽ ካልቻልኩ… የት ላገኝሽ እችላለሁ?››
የቢሮ ቁጥሯን እና የሞባይል ስልኳን ሰጠችው።በስራ ቦታ ልታገኘኝ ካልቻልክ ለሎዛ መልእክት ተውልኝ። ሞባይል ስልኬ በአብዛኛው ክፍት ነው። በተጨማሪም የወላጆቼ ቁጥር አለህ። ››
የንዴት ፈገግታ አሳያት።‹‹እነዚህ ሁሉ ቁጥሮች አያስፈልጉኝም?››
በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከወ.ሮ ላምሮት ጋር መገናኘት ነበረባት እና አሁን ለፀጋ የምትገዛቸው መድሀኒቶች አሉ..በዛ ላይ ምግቧንም መመገብ አለባት….በዚህ ሁኔታ ላይም እያለች ጥላት መሄድ አትችልም ፡፡ያላት ምርጫ ሴትዬዋን ይቅርታ ጠይቃ ሌላ ቀጠሮ ማስያዝ ነው፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››አለች.
‹‹ትሁትን ስላየህልኝ አመሰግናለሁ፣››አለችው በድጋሜ
‹‹ ከሁለት ቀናት በኋላ እንገናኝ።››አለና የድንገተኛ ክፍልን ለቅ ወጣ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ከዚያም የፀጋን የህክምና ቻርት ላይ የሆነ ምልክት እያደረገች ወዳለችው ነርስ ተጠጋና ተመለከተ። ‹ታዲያ ችግሩ ምን ይመስላሻል ?›› ብሎ ጠየቀ ከራሄል ወደ ፀጋ ከዚያም ወደ ነርሷ ተመለከተ። ራሄል ‹‹ከፍኛ ትኩሳት አላት›› አለችው.
ነርሷ ‹‹አሁን የሙቀት መጠንዋን ወስጃለሁ….ትንሽ ከፍ ያለ ነው፣ ግን ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም።››
ራሔል ነርሷ ላይ አፈጠጠች ፣ግራ ተጋባች፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለከተች። ‹‹ በጣም እኮ ነበር የምትሞቀው.››
ዔሊ ሰንጠረዡን ከነርሷ ተቀብሎ ተመለከተ እና እጁን በህፃኗ ግንባሩ ላይ አደረገ። ፀጋ በድንገት ሁሉም ነገር ደህና የሆነ ይመስል ፈገግ አለችለት‹‹አሁንም አንቲ ባዮቲኮችን እየሰጠሻት ነው?›››
‹‹አዎ ››
‹‹ደህና፣ እየሰሩ ያሉ ይመስላሉ፣ ግን ፈገግታዋ ጠፍቷል፣ የድምፁ ቃናዋም ተለውጣል፣ እሷን መናደድ የለባትም››
‹‹የምን መናደድ …ከሰአት በኋላ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ለመንከባከብ የተመሰከረለትን የመዋለ ሕጻናት አገኘሁ።እና እዛ ወሰድኳት..ከስራ ተመልሼ ልወስዳት ስሄድ ታማ አገኘኋት… እና አሁን የሚያስፈልገኝ በእሷ ላይ ያለውን ችግር እንድትነግሩኝ ነው።››
ዔሊያስ በትንሹ ተነፈሰ… ነገር ግን ዓይኖቿን ራሄል ላይ እያንከራተተች ወዳለችው ታዳጊ ልጅ ተመለከተ። የታችኛው ከንፈሯ ያብለጨልጭ ጀመር እና እንደገና ልታለቅስ ያሰበች ይመስላል ። ራሄል ጀርባዋን እየደባበሰች አባበለቻት፡፡
በወረቀት ላይ ማስታወሻዎችን እየጻፈ። ‹‹ደህና ነች..አዎ፣ የሙቀት መጠኑ በትንሹ ከፍ ብሏል፣ ግን ያ ስለተበሳጨች ሊሆን ይችላል። አንድ ጆሮዋ ትንሽ ቀላ ያለ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ በፀረ-ባዮቲክስ መድሀኒት ይወርዳል። መበሳጨት ከጀመረች ስጧት። የሙቀት መጠኗን መቆጣጠሪያ በእጅሽ ላይ ሊኖርሽ ይገባል.. የሚያስፈልጉሽን ነገሮች ዝርዝር ነገ እሰጥሻለሁ፤››አለና ወረቀቱን ከፓድ ላይ ቀዶ ዘረጋላት።ራሄል በድንገት ሞኝነት ተሰማት፣ነገር ግን ፀጋ ደህና መሆኗን በማወቋ እፎይታ አግኝታለች።
ወረቀቱን ወደ ቦርሳዋ እያስገባች‹‹ለምክርህ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹በዚህ ኢንፌክሽን ደረጃ ለማረጋገጥ ከነገ ወዲያ እሷን ማየት እፈልጋለሁ። ለአንቺ ስንት ሰዓት ይምችሻል?››በጥያቄው ስለተበሳጨች እኩለ ሌሊት ልትለው አሰበች. ፡፡
‹‹ለምን አንተ ቀጠሮ አትይዝልኝም እኔ ፕሮግራሜን ማሸጋሸግ እችላለው፡፡ ››አለችው፡፡
‹‹ቤት ላገኝሽ ካልቻልኩ… የት ላገኝሽ እችላለሁ?››
የቢሮ ቁጥሯን እና የሞባይል ስልኳን ሰጠችው።በስራ ቦታ ልታገኘኝ ካልቻልክ ለሎዛ መልእክት ተውልኝ። ሞባይል ስልኬ በአብዛኛው ክፍት ነው። በተጨማሪም የወላጆቼ ቁጥር አለህ። ››
የንዴት ፈገግታ አሳያት።‹‹እነዚህ ሁሉ ቁጥሮች አያስፈልጉኝም?››
በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከወ.ሮ ላምሮት ጋር መገናኘት ነበረባት እና አሁን ለፀጋ የምትገዛቸው መድሀኒቶች አሉ..በዛ ላይ ምግቧንም መመገብ አለባት….በዚህ ሁኔታ ላይም እያለች ጥላት መሄድ አትችልም ፡፡ያላት ምርጫ ሴትዬዋን ይቅርታ ጠይቃ ሌላ ቀጠሮ ማስያዝ ነው፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››አለች.
‹‹ትሁትን ስላየህልኝ አመሰግናለሁ፣››አለችው በድጋሜ
‹‹ ከሁለት ቀናት በኋላ እንገናኝ።››አለና የድንገተኛ ክፍልን ለቅ ወጣ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤27👍7🔥1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ራሄልም እህቷን ይዛ እቤት እንደገባች ጓደኛዋ ሜሮን ቤት እየጠበቀቻት ነው፡፡መጀመሪያ ቀጠሮውን ለመሰረዝ ፈልጋ ነበር…በኋላ ስታስበው ግን ሴትዬዋ ለስብሰባው ትኩረት እንዳልሰጠች አድርጋ ልትረዳት እንደምትችል ስላሰበች ለመሄድ ወሰነች፡፡ ከሆስፒታል እንደተነሳች ነበር ደውላ ቤት እንድትጠብቃት የጠየቀቻት፡፡፡‹‹ቀጠሮው በጣም ወሳኝ ስለሆነ ነው ያስቸገርኩሽ፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም..ያንቺ እህት ማለት እኮ የእኔ እህት ነች››አለች ሜሮን፡፡
‹‹እሱስ እውነት ነው››
‹‹አዎ ደግሞም አሪፍ የምስራች አለኝ…››
‹‹እባክሽ ንገሪኝ ቀኑን ሙሉ ስጨናነቅ ነው የዋልኩት…ፈገግ ማለት አምሮኛል››
‹‹አንድ እምቅ ችሎታ ያላት እና በነርሲንግ የሰለጠነች ሞግዚት አግኝቼልሻለው›› አለቻት….ከሁለት ቀን በፊት ለሁሉም ጓደኞቾ ስለፀጋ ነግራቸው የሰለጠነች ሞግዚት እንዲፈልጉላት አደራ ብላቸው ነበር፡፡
‹‹አንቺ እኮ ሕይወት አድን ነሽ›› አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጯን ሳመቻት፡፡
ወደቀጠሮ ቦታ ይዛ የምትሄደቸውን ወረቀቶች ወደ ቦርሳዋ አስገባች።
‹‹ሞግዚት ማግኘት ከቻልኩ የፀጋ ዶ/ር የሰጠውን መመሪያ በሙሉ በጥንቃቄ እንዲተገበር ማድረግ እችላለው። ውዴ ለአሁን ፀጋን ልትጠብቂልኝ ስለወሰንሽ ደስተኛ ነኝ። ነገሮች ሁሉ ሰላም እንደሚሆኑ አምናለው?››
‹‹ሄይ. ታውቂያለሽ እኔ በጣም ጥሩ ጓደኛሽ ነኝ.››
‹‹ብቃት ያለው ሞግዚት አግኝተሸልኝማ ያንን መካድ አልችልም… በጣም ጥሩ ጓደኛ መሆን ብቻ ሳይሆን ህይወት አድንም ነሽ።››
‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ እስኪ በመጠኑ ዘና ለማለት ሞክሪ….››
ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ላላት ቀጠሮ የምትጠቀምባቸውን መረጀጃዎች የያዙ ወረቀቶች እየለየች ‹‹ዘና ማለት እንኳን የምችል አይመስለኝም…ደክሞኛል… በአእምሮዬ ውስጥ ብዙ ነገሮች አሉ,››ስትል መለሰችላት፡፡ቀጥላም‹‹‹‹በፋውንዴሽን ውስጥ ነገሮች በጥሩ መንገድ እየሄዱ አይደለም ፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ለጋሾችን አጥቻለሁ አሁን የምሄድባትን ሴትዬ ከዋና ለጋሾቻችን የመጀመሪያዋ ነች….እሷን የግድ ማሳመን አለብኝ ››
‹‹ለምን ሎዛ እንድትሰራው አታደርጊም?››
ራሄል ነገሩን በማሰብ ትንሽ ቆም ብላ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።‹‹ይህን ከባድ ኃላፊነት በእሷ ትከሻ ላይ መጣል አልችልም››
‹‹ስለዚህ በራስሽ ላይ ትጥያለሽ ..እሱ ችግር የለውም ማለት ነው?››
‹‹ትከሻዬ ከሷ የበለጠ ልምድ ያለው ነው›› አለች ፡፡
‹‹ጓደኛዬ ጥቂት ስራዎችን ለሌላ ሰው ብታስተላልፊ አለም አትገለባበጥም።እና ደግሞ የህይወት ሸክማችንን የሚያቀልልን ክርስቶስ ነው….በእሱ መታመን ችግራቸንን ያቀልልናል፡፡››
‹‹እና ለምን ያቺን አሁን በስቃይ የምታለቅሰውን ትንሽ ልጅ እንዲህ አጎጉል አደረጋት? በኢየሱስ አላምንም ብላ ይሆን ?››በራሄል ንግግር ሜሮን በጣም ደነገጠች፣
‹‹ራሄል .. አንቺ እኮ ከዚህ የበለጠ አስተዋይ ነሽ ››ራሄል እጇን ወደ ላይ ዘረጋች።
‹‹አዝናለሁ ስለ ኃጢአት እና ክፋት ሁሉን ነገር አውቃለሁ እናም እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር እንደሆነም አምናለው, ስለዚህ ስብከት አንዳትጀምሪኝ››
ሜሮን የጓደኛዋን ትከሻው በፍቅር እየዳበሰች‹‹ታውቂያለሽ አይደል …?ማመን ስለማትፈልጊ ብቻ ነው. እንዲህ የምትይው…ግን እወቂ አሁንም በኢየሱስ ጥበቃ ውስጥ ነሽ …አዎ፣ በግንኙነቶች ውስጥ ህመም አለ…በሆነ ግንኙነት ተሰብረን ሊሆን ይችላል፣ ቢሆንም ልባችንን ሁሌ ለፍቅር ክፍት መሆን አለበት ››
‹‹ደህና፣ አሁን ለልብ ጉዳዬች ጊዜ የለኝም።ደግሞ እስከአሁን ለእኔ የሚሆን ሰው አላጋጠመኝም።›› መስታወት አወጣች እና ሜካፕ እና ፀጉሯን በፍጥነት አስተካከለች።
ሜሮን ‹‹ዶ/ሩ በጣም የሚስብ ይመስለኛል››ስትል አዲስ ድንገተኛ ርዕስ ከፈተች፡፡
ራሄል የጓደኛዋን ሹፈት ችላ በማለት ቦርሳዋን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች ፡፡
‹‹እሱ ማራኪ ነው…እንዳልኩሽ ግን ለጊዜው ለማንም ጊዜ የለኝም ።››በማለት መለሰችላት፡፡
ራሄል ወደ በሩ ስትሄድ ሜሮን ‹‹መልካም ጊዜ ይሁንልሽ›› ብላ ጮኸች።
////
ራሄል ከሴትዬዋ ጋር እያካሄደች ያለውን ስብሰባ አንድ ሰዓት በላይ ብታሳልፍም..እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ልታሳምናት አልቻለችም፡፡
‹‹ባለቤቴ በዚህ ገንዘብ በጣም ነው የሚያምነኝ… እናም ይህን በትክክለኛው መንገድ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹ይገባኛል››አለች ራሄል። ነገር ግን የባለቤቷትን እምነትን ለመጠበቅ ምርጡ መንገድ ገንዘቡን ለትክክለኛው ዓላማ ብቻ ለሚጠቀም በጎ አድራጎት መስጠት ነው።››
ወ.ሮ ላምሮት ፈገግ አለችላት፡፡
ወ.ሮ ላምሮት ራሄልን በትኩረት አየቻትና ‹‹አባትሽን ትመስያለሽ›› አለቻት። ‹‹እሱ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚሰራ የእግዚአብሔር ፍቅር ሁልጊዜ ምሳሌ ነው.››ስትል አከለችበት፡፡
ራሄል መራራ ህመም ተሰማት። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአምላክ ጋር ብዙ ጊዜ አላጠፋችም። የወ.ሮዋ ቃላት አብዝታ ወደ ጸለየችበት፣ መጽሐፍ ቅዱሷን በሰፊው ታንብበት ወደ ነበረችበት ጊዜ አመጣት። ቤተክርስቲያን እና እምነት የመተንፈስ ያህል የእርሷ አካል ነበር። እምነቷን መልሶ ለማግኘት እና በአምላክ ላይ መታመን ለምን እንደሚያስፈልጓት አሰበች። ››
በወ.ሮ ላምሮት ፈገግ ብላ ሰዓቷን በጥበብ ተመለከተች። ለመውጣት ጊዜው ነበር፡፡
‹‹እኔ እንዳልኩት፣ እባኮት ይህን በትክክለኛው መንገድ ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ስጡኝ..ያንን ብቻ ነው የምጠይቀው››አለች ራሄል፣
ወ.ሮ ላምሮት ከግዙፉ መኖሪያ ቤቷ ስትሸኛት ራሄል የመጨረሻ የማሳመኛ ንግግሯን ተናገረች‹‹እርግጠኛ ነኝ .. ባለቤቷት በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲቸኩሉ አይፈልግም ››
ነገር ግን ከወ.ሮዋ ፊት ምንም ነገር ማንበብ አልቻለችም ፡፡ሴትዬዋን ለማሳመን የተቻላትን ሁሉ አድርጋለች..ግን ይሳካላት አይሳካላት መገመት ስላልቻለች በጣም ተበሳጨች ፣ መኪናውን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው…መኪናዋን አቁማ ወደአፓርታማዋ ተጠጋች… የአሳንሰሩን ቁልፍ ተጫነች እና ገባች፤ውስጥ ያልጠበቀችውን ሰው አገኘች፡፡የቆዳ ጃኬት ለብሶ ነበር። የሞተር ሳይክል ሄልሜት በእጁ ይዟል።
‹‹ሰላም. እዚህ ምን እየሰራህ ነው?››ብላ ጠየቀችው፣ እስትንፋሶ ተቆራረጠባት፡፡
‹‹በቃ ጎራ ብዬ ከፀጋ ጋር እንዴት እየተለማመድሽ እንዳለሽ ለማየት አስቤ ነበር።››
‹‹ጥሩ አደረክ››አለችው
‹‹ወደ ውጭ ወጥተሽ ነበር?››
‹‹አዎ ጠቃሚ ስብሰባ ነበረኝ›
‹‹እንደ ሁሉም ስብሰባዎችሽ››አለ
‹‹አይዞህ አታስብ ጓደኛዬ በጣም ብቃት ያለት ሞግዚት ነች።እርግጠኛ ነኝ እሷ ከእኔ በተሻለ ከፀጋ ጋር ትግባባለች።››ሊፍት ሲቆም ወደ ኋላ ዞር አለላት።ራሄል ቀድማ ወጣች..ተከተላት፡፡ ኮሪደሩን እንደረገጡ የሚያለቅስ የህፃን ድምፅ በሁለቱም ጆሮ ገባ። የመጣው ከራሷ ቤት ነው።ሁለቱም ርምጃቸውን አፈጠኑና ተከታትለው ወደቤት ገቡ ፡፡ሜሮን የምትጮኸውን ፀጋን ተሸክማ እቤት ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትሽከረከራለች፣ የልጁቷ ክንዶች በሜሮን ጀርባ ላይ ተዝለፍልፋው ይታያሉ፡፡
ራሄል ቦርሳዋን ጥላ ወደ ጓደኛዋ ሮጣ ሄደች። ጸጋ ራሄልን እንዳየች ከሜሮን እቅፍ ውስጥ ተስፈንጥራ እጇን ዘረጋች። እንባዋ በጉንጮቾ እየተንከባለሉ በመርገፍ ላይ ናቸው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ራሄልም እህቷን ይዛ እቤት እንደገባች ጓደኛዋ ሜሮን ቤት እየጠበቀቻት ነው፡፡መጀመሪያ ቀጠሮውን ለመሰረዝ ፈልጋ ነበር…በኋላ ስታስበው ግን ሴትዬዋ ለስብሰባው ትኩረት እንዳልሰጠች አድርጋ ልትረዳት እንደምትችል ስላሰበች ለመሄድ ወሰነች፡፡ ከሆስፒታል እንደተነሳች ነበር ደውላ ቤት እንድትጠብቃት የጠየቀቻት፡፡፡‹‹ቀጠሮው በጣም ወሳኝ ስለሆነ ነው ያስቸገርኩሽ፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም..ያንቺ እህት ማለት እኮ የእኔ እህት ነች››አለች ሜሮን፡፡
‹‹እሱስ እውነት ነው››
‹‹አዎ ደግሞም አሪፍ የምስራች አለኝ…››
‹‹እባክሽ ንገሪኝ ቀኑን ሙሉ ስጨናነቅ ነው የዋልኩት…ፈገግ ማለት አምሮኛል››
‹‹አንድ እምቅ ችሎታ ያላት እና በነርሲንግ የሰለጠነች ሞግዚት አግኝቼልሻለው›› አለቻት….ከሁለት ቀን በፊት ለሁሉም ጓደኞቾ ስለፀጋ ነግራቸው የሰለጠነች ሞግዚት እንዲፈልጉላት አደራ ብላቸው ነበር፡፡
‹‹አንቺ እኮ ሕይወት አድን ነሽ›› አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጯን ሳመቻት፡፡
ወደቀጠሮ ቦታ ይዛ የምትሄደቸውን ወረቀቶች ወደ ቦርሳዋ አስገባች።
‹‹ሞግዚት ማግኘት ከቻልኩ የፀጋ ዶ/ር የሰጠውን መመሪያ በሙሉ በጥንቃቄ እንዲተገበር ማድረግ እችላለው። ውዴ ለአሁን ፀጋን ልትጠብቂልኝ ስለወሰንሽ ደስተኛ ነኝ። ነገሮች ሁሉ ሰላም እንደሚሆኑ አምናለው?››
‹‹ሄይ. ታውቂያለሽ እኔ በጣም ጥሩ ጓደኛሽ ነኝ.››
‹‹ብቃት ያለው ሞግዚት አግኝተሸልኝማ ያንን መካድ አልችልም… በጣም ጥሩ ጓደኛ መሆን ብቻ ሳይሆን ህይወት አድንም ነሽ።››
‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ እስኪ በመጠኑ ዘና ለማለት ሞክሪ….››
ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ላላት ቀጠሮ የምትጠቀምባቸውን መረጀጃዎች የያዙ ወረቀቶች እየለየች ‹‹ዘና ማለት እንኳን የምችል አይመስለኝም…ደክሞኛል… በአእምሮዬ ውስጥ ብዙ ነገሮች አሉ,››ስትል መለሰችላት፡፡ቀጥላም‹‹‹‹በፋውንዴሽን ውስጥ ነገሮች በጥሩ መንገድ እየሄዱ አይደለም ፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ለጋሾችን አጥቻለሁ አሁን የምሄድባትን ሴትዬ ከዋና ለጋሾቻችን የመጀመሪያዋ ነች….እሷን የግድ ማሳመን አለብኝ ››
‹‹ለምን ሎዛ እንድትሰራው አታደርጊም?››
ራሄል ነገሩን በማሰብ ትንሽ ቆም ብላ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።‹‹ይህን ከባድ ኃላፊነት በእሷ ትከሻ ላይ መጣል አልችልም››
‹‹ስለዚህ በራስሽ ላይ ትጥያለሽ ..እሱ ችግር የለውም ማለት ነው?››
‹‹ትከሻዬ ከሷ የበለጠ ልምድ ያለው ነው›› አለች ፡፡
‹‹ጓደኛዬ ጥቂት ስራዎችን ለሌላ ሰው ብታስተላልፊ አለም አትገለባበጥም።እና ደግሞ የህይወት ሸክማችንን የሚያቀልልን ክርስቶስ ነው….በእሱ መታመን ችግራቸንን ያቀልልናል፡፡››
‹‹እና ለምን ያቺን አሁን በስቃይ የምታለቅሰውን ትንሽ ልጅ እንዲህ አጎጉል አደረጋት? በኢየሱስ አላምንም ብላ ይሆን ?››በራሄል ንግግር ሜሮን በጣም ደነገጠች፣
‹‹ራሄል .. አንቺ እኮ ከዚህ የበለጠ አስተዋይ ነሽ ››ራሄል እጇን ወደ ላይ ዘረጋች።
‹‹አዝናለሁ ስለ ኃጢአት እና ክፋት ሁሉን ነገር አውቃለሁ እናም እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር እንደሆነም አምናለው, ስለዚህ ስብከት አንዳትጀምሪኝ››
ሜሮን የጓደኛዋን ትከሻው በፍቅር እየዳበሰች‹‹ታውቂያለሽ አይደል …?ማመን ስለማትፈልጊ ብቻ ነው. እንዲህ የምትይው…ግን እወቂ አሁንም በኢየሱስ ጥበቃ ውስጥ ነሽ …አዎ፣ በግንኙነቶች ውስጥ ህመም አለ…በሆነ ግንኙነት ተሰብረን ሊሆን ይችላል፣ ቢሆንም ልባችንን ሁሌ ለፍቅር ክፍት መሆን አለበት ››
‹‹ደህና፣ አሁን ለልብ ጉዳዬች ጊዜ የለኝም።ደግሞ እስከአሁን ለእኔ የሚሆን ሰው አላጋጠመኝም።›› መስታወት አወጣች እና ሜካፕ እና ፀጉሯን በፍጥነት አስተካከለች።
ሜሮን ‹‹ዶ/ሩ በጣም የሚስብ ይመስለኛል››ስትል አዲስ ድንገተኛ ርዕስ ከፈተች፡፡
ራሄል የጓደኛዋን ሹፈት ችላ በማለት ቦርሳዋን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች ፡፡
‹‹እሱ ማራኪ ነው…እንዳልኩሽ ግን ለጊዜው ለማንም ጊዜ የለኝም ።››በማለት መለሰችላት፡፡
ራሄል ወደ በሩ ስትሄድ ሜሮን ‹‹መልካም ጊዜ ይሁንልሽ›› ብላ ጮኸች።
////
ራሄል ከሴትዬዋ ጋር እያካሄደች ያለውን ስብሰባ አንድ ሰዓት በላይ ብታሳልፍም..እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ልታሳምናት አልቻለችም፡፡
‹‹ባለቤቴ በዚህ ገንዘብ በጣም ነው የሚያምነኝ… እናም ይህን በትክክለኛው መንገድ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹ይገባኛል››አለች ራሄል። ነገር ግን የባለቤቷትን እምነትን ለመጠበቅ ምርጡ መንገድ ገንዘቡን ለትክክለኛው ዓላማ ብቻ ለሚጠቀም በጎ አድራጎት መስጠት ነው።››
ወ.ሮ ላምሮት ፈገግ አለችላት፡፡
ወ.ሮ ላምሮት ራሄልን በትኩረት አየቻትና ‹‹አባትሽን ትመስያለሽ›› አለቻት። ‹‹እሱ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚሰራ የእግዚአብሔር ፍቅር ሁልጊዜ ምሳሌ ነው.››ስትል አከለችበት፡፡
ራሄል መራራ ህመም ተሰማት። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአምላክ ጋር ብዙ ጊዜ አላጠፋችም። የወ.ሮዋ ቃላት አብዝታ ወደ ጸለየችበት፣ መጽሐፍ ቅዱሷን በሰፊው ታንብበት ወደ ነበረችበት ጊዜ አመጣት። ቤተክርስቲያን እና እምነት የመተንፈስ ያህል የእርሷ አካል ነበር። እምነቷን መልሶ ለማግኘት እና በአምላክ ላይ መታመን ለምን እንደሚያስፈልጓት አሰበች። ››
በወ.ሮ ላምሮት ፈገግ ብላ ሰዓቷን በጥበብ ተመለከተች። ለመውጣት ጊዜው ነበር፡፡
‹‹እኔ እንዳልኩት፣ እባኮት ይህን በትክክለኛው መንገድ ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ስጡኝ..ያንን ብቻ ነው የምጠይቀው››አለች ራሄል፣
ወ.ሮ ላምሮት ከግዙፉ መኖሪያ ቤቷ ስትሸኛት ራሄል የመጨረሻ የማሳመኛ ንግግሯን ተናገረች‹‹እርግጠኛ ነኝ .. ባለቤቷት በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲቸኩሉ አይፈልግም ››
ነገር ግን ከወ.ሮዋ ፊት ምንም ነገር ማንበብ አልቻለችም ፡፡ሴትዬዋን ለማሳመን የተቻላትን ሁሉ አድርጋለች..ግን ይሳካላት አይሳካላት መገመት ስላልቻለች በጣም ተበሳጨች ፣ መኪናውን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው…መኪናዋን አቁማ ወደአፓርታማዋ ተጠጋች… የአሳንሰሩን ቁልፍ ተጫነች እና ገባች፤ውስጥ ያልጠበቀችውን ሰው አገኘች፡፡የቆዳ ጃኬት ለብሶ ነበር። የሞተር ሳይክል ሄልሜት በእጁ ይዟል።
‹‹ሰላም. እዚህ ምን እየሰራህ ነው?››ብላ ጠየቀችው፣ እስትንፋሶ ተቆራረጠባት፡፡
‹‹በቃ ጎራ ብዬ ከፀጋ ጋር እንዴት እየተለማመድሽ እንዳለሽ ለማየት አስቤ ነበር።››
‹‹ጥሩ አደረክ››አለችው
‹‹ወደ ውጭ ወጥተሽ ነበር?››
‹‹አዎ ጠቃሚ ስብሰባ ነበረኝ›
‹‹እንደ ሁሉም ስብሰባዎችሽ››አለ
‹‹አይዞህ አታስብ ጓደኛዬ በጣም ብቃት ያለት ሞግዚት ነች።እርግጠኛ ነኝ እሷ ከእኔ በተሻለ ከፀጋ ጋር ትግባባለች።››ሊፍት ሲቆም ወደ ኋላ ዞር አለላት።ራሄል ቀድማ ወጣች..ተከተላት፡፡ ኮሪደሩን እንደረገጡ የሚያለቅስ የህፃን ድምፅ በሁለቱም ጆሮ ገባ። የመጣው ከራሷ ቤት ነው።ሁለቱም ርምጃቸውን አፈጠኑና ተከታትለው ወደቤት ገቡ ፡፡ሜሮን የምትጮኸውን ፀጋን ተሸክማ እቤት ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትሽከረከራለች፣ የልጁቷ ክንዶች በሜሮን ጀርባ ላይ ተዝለፍልፋው ይታያሉ፡፡
ራሄል ቦርሳዋን ጥላ ወደ ጓደኛዋ ሮጣ ሄደች። ጸጋ ራሄልን እንዳየች ከሜሮን እቅፍ ውስጥ ተስፈንጥራ እጇን ዘረጋች። እንባዋ በጉንጮቾ እየተንከባለሉ በመርገፍ ላይ ናቸው፡፡
❤50👍3🥰1😢1
ራሄል ወስዳ አቀፈቻትና ጀርባዋን እየደባበሰች‹‹ምንም አይደለም የእኔ እህት..አይዞሽ መጥቻለው ››እያለች ታባብላት ጀመር ። ፀጋ ምን ያህል ሙቀቷ እንደጨመረ ሲታወቃት የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማት።
‹‹ምንድን ነው ችግሯ ?››
‹‹ከግማሽ ሰአት በፊት እያለቀሰች ከእንቅልፏ ነቃች። መድሃኒቷን ሰጥቻታለሁ፣ ግን እየሰራላት ያለ አይመስለኝም።››
ከዚያም ፀጋ በእሷ ላይ ዝልፍልፍ አለች…ራሄል ደነገጠች። ‹‹ምን እየሆነች ነው? ደህና ናት? ››
ደ/ር ዔሊያስ እጁን በትሁት ጀርባ ላይ አደረገ፣ እሷን አረጋጋት። ‹‹ስንት ኪኒን ሰጠሻት?" ብሎ ራሄልን ጠየቃት።ነገረችው ፡፡
‹‹የእሷን የሙቀት መጠን መውሰድ አለብን.››ራሄል ወደ መታጠቢያ ቤት እያመራች ነው፡፡
‹‹ ቴርሞ ሜትር አለኝ››አለች.
ኤሊ ቴርሞሜትሩን በትሁት ጆሮ ውስጥ አስገባ። ከንፈሩን ነከሰው።
‹‹መድኃኒቱ እስከአሁን መስራት ነበረበት። በፍጥነት ማቀዝቀዝ አለብን። ››
ዔሊ በመታጠቢያ ገንዳው አጠገብ ተንበረከከ። ‹‹ውሃውን ላዘጋጅ, አንቺ ልብሷን አውልቂላት."
ኮቱን አውልቆ ቧንቧዎቹን ከፍቶ እጁን ከውሃው በታች በመደቀን… የሙቀት መጠኑን ፈትሸ።ራሄል ከመታጠቢያ ገንዳው አጠገብ ያለች ትንሽ አግዳሚ ወንበር ላይ ተቀመጠች የፀጋን ልብስ በጥንቃቄ አወለቀችላት። ዳይፐርዋን አወለቀችላት። አሁንም ደረቅ ነበር. እሷ እየተቃጠለች ነው እና ራሄል እንደዚህ ያለ ትንሽ አካል እንዴት በዚህ መጠን የሚፋጅ ሙቀት ማመንጨት እንደቻለች አሰበችና ተገረመች፡፡
‹‹እሺ በጣም በዝግታ ወደ ውሃው ውስጥ ንከሪያት።››
ራሄል ከጎኑ ተንበርክካ እንዳላት አደረገች። የፀጋ ገላ ውሃው እንደነካት በራሄል እቅፍ ውስጥ ሆና መጮህ ጀመረች።‹‹በጣም ይቀዘቅዛል ›› አለች፡፡ ራሄል እንደገና ወደ ኋላ ጎተተቻት እና ከውሀው አወጣቻት።
ዔሊ የራሄልን ክንድ ይዞ አስቆማት። ‹‹በጣም ስለሞቀች ለእሷ ቅዝቃዜ ይሰማታል.››ራሄል አንገቷን አዙራ አይኖቹን አየች። በአንድ ጉንጭ ላይ የዲምፕል ምልክት ተመለከተች.
‹‹አይዞሽ.. ደህና ትሆናለች›› ብሎ ሊያፅናናት ሞከረ፡፡ ራሄል ፀጋን በዝግታ ከእንደገና ወደውሀው መለሰቻት። እንደገና ጮኸች፣ በዚህ ጊዜ ግን ራሄል በተሻለ ሁኔታ ዘና ብላ ተሰማት።
‹‹ግንባሯ ላይ ትንሽ ውሃ አንጠባጥቢላት" አለ ዔሊ አጠገቧ ተቀምጦ።
በዚህ ጊዜ ሜሮን ስልክ ጆሮዋ ላይ ለጥፋ የመታጠቢያ ክፍሉን በር ከፍታ ‹‹ እኔን ትፈልጊኛለሽ እንዴ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ ‹‹አሁን ማስተላለፍ የማልችለው አስቸኳይ ጥሪ ደረሰኝ።››
ራሄል አንገቷን ነቀነቀች እና እንድትሄድ በመፍቀድ ትኩረቷን ወደ እህቷ መለሰች። ‹‹ደህና እንሆናለን ብዬ አስባለሁ.››አጠገቧ የተንበረከከውን ዔሊን ተመለከተች።
‹‹አዎ ሁሉ ነገር ሰላም ይሆናል….እናደርገዋለን›› ብሎ አረጋገጠላት።
‹‹እሺ በቃ ሄጃለው።›› በማለት በራፉን መልሳ ዘግታላቸው ሄደች፣ እና በድንገት ራሄልና ዔሊ ብቻቸውን ቀሩ።ሲጨርሱ ፀጋ እየተንቀጠቀጠች ነበር እና ከንፈሮቿ ከደማቅ ቀይ ወደ ገረጣ አመዳም ቀለም እየተቀየሩ ነበር። ራሄል የሚንጠባጠበውን የፀጋን ገላ ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ በማውጣት ዔሊ በሰጣት ለስላሳ ፎጣ ጠቀለለቻት።
ራሄል ፀጋን አደራረቀቻትና ይዛት ወደመኝታ ክፍሏ ስትወስዳት እሱ ወደሳሎን ሄደ፡፡
ከዛ ልብስ ቀይራለት፣ መድሀኒት ሰጥታት አስተኛቻት፡፡ ወዲያው በተረጋጋ ሁኔታ እንቅልፍ ወሰዳት ፡፡ራሄል ከአልጋዋ አጠገብ ቆማ ለረጅም ደቂቃ በሰስት አየቻት…ሳታስበው ይህቺን ልጅ እየወደደቻት ነው…በዚህ ጮርቃ እድሜዋ ለነፍሶ ስትታገልና በዚህ መጠን ስትሰቃይ ማየት ልቧ እንዲደማ ነው ያደረጋት፡፡
ቀስ አለችና ክፍሉን ለቃ ወጣች…ዶ/ሩን ሳሎኑ ውስጥ ሲንጎራደድ አገኘችው፡፡
የኮቴ ድምፅ እንደሰማ ወደእሷ ዞር አለና ‹‹እንዴት ነች?››ብሎ ጠየቃት፡፡
‹‹ተኝታለች ብዬ አስባለሁ…ቆይ ፀጋ በህፃንነቷም እንዲህ ቶሎ ቶሎ ትታመም ነበር እንዴ?››ስትል ጠየቀችው
ዔሊያስ ፈገግ አለ‹‹እናቷ ቅዳሜና እሁድን እሷን ላለመያዝ ስትል ሁሉ ጊዜ ወደ ሆስፒታል ላለመምጣት ሰበብ ትደረድር ነበር።››
‹‹ወላጆቼ ስለ ስለፀጋ እናት ብዙ ሲናገሩ አልሰማሁም ››
‹‹እሷን በጭራሽ አላገኟትም … የሆስፒታሉ ማህበራዊ ሰራተኛ ጉዳዩን በሚያውቅበት ጊዜ, ፀጋ ለብዙ ሳምንታት ከበሽታዋ እየታገለች እናቷ ከአሁን አሁን መጥታ ትወስደኛለች በሚል ጉጉት አይኖቾ እየተንከራተቱ ስትጠብቅ ነበር….የሰው ልጅ ሆነሽ ያንን የልጅቷን የናፍቆት ስቃይ ማየት እንዴት ልብን እንደሚሸረካክት ልነግርሽ አልችልም..ይገርምሻል እናትዬው ግን ተመልሳ ልትመጣላት አልቻለችም…ስናጠያይቅ አንደኛውን ሀገር ጥላ እንደጠፋች ሰማንና ተስፋ ቆረጥን… ለሚመለከተው አካል አመለከትን…እና እንዳጋጣሚ ከወላጆችሽ ጋር የተገናኘሁት በዛ ጊዜ ነበር…በአጋጣሚ ስለልጅቷ ሁኔታ እንደሰሙ ሆስፒታል ሄደን ካላየናት አሉ..ይዣቸው ሄድኩ…ልክ እንዳዮት ሁለቱም ወደዷት…ከዚህ በፊት እንደነገርኩሽ ያለባትን የጤና ችግር፤ምን አይነት እንክብካቤ እደሚስፈልጋት…ለእሷ ህክምና ሊያወጡት የሚችሉትን ገንዘብ ..እንደዛም ሆኖ ለመዳን ያላት እድል አናሳ እንደሆነ ሁሉንም በግልፅ አስረድቻቸውም እነሱ እሷን እንደልጃቸው አድርገው ለመቀበልና ወደቤታቸው ለመውሰድ ቅንጣት ያህል አላቅማሙም…እኔ በህይወት ዘመኔ እንደወላጆችሽ አይነት ትክክለኛ መንፈሳዊ ሰው አላውቅም….ከአእምሮዬ በላይ ናቸው፡፡እኔም በተቻኝ መጠን ከፀጋ ጎን ላለመራቅ የወሰንኩት የእነሱን ደግነት ካየው በኋላ ነው፡፡››
‹‹አዎ..እነሱ እንደዛ ናቸው…እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ..መጀመሪየ ውሳኔያቸውን ስሰማና ሆስፒታል ሄጄ ፀጋን የሀገር ቱቦና ማሽኑ ሰውነቷ ላይ ተሰክቶ ሳይ ምለውና ምናገረው ጠፍቶኝ ነበር…አፍ አውጥቼ ባልቃወምም በውስጤ ግን በጣም ተበሳጭቼ ነበር….አሁን ያንን ስሜቴን ትዝ ሲለኝ በጣም አፍራለው፡፡››
‹‹አትፈሪ…በሆድሽ አስበሽ ቢሆን እንኳን..በአፍሽ ተቃውሞ አለማሰማትሽ እራሱ አንድ ጥሩ ነገር ነው….አየሽ ልጅቷ በጣም አሳዝናሽ ነበር..ግን ደግሞ እድሜያቸው ለገፋ ወላጆችሽም የበለጥ ማሰብሽ እና መጨነቅሽ የሚያስወቅስሽ አይደለም…ተመልከቺ እናትሽ አሁን የት ነው ያለችው ሆስፒታል አልጋ ላይ …ምን ሆና..?ፀጋን አቅፋ ደረጃ ስትወርድ ሚዛኗን ስታ…እና አንቺ ክፉ ሴት ብትሆኜ ‹‹እናቴን እንድትሰበር አድርጋ ለዚህ አደጋ የዳረገችብኝ ይህቺ ልጅ ነች …ገፊ ነች ምናምን ብለሽ..እሷን ከህይወትሽ ለማስወገድ ነበር የምትጥሪው..ይሄው ግን አንቺ ከእሷ ጋር እየተሰቃየሽ ነው…ልክ እንደእናቷ ሲያማት እያመመሽ….ስታለቅስ እያለቀሽ ነው፡፡››
‹‹አንተ ….እስከአሁን እናቴ በእሷ ምክንያ እንደወደቀች እራሱ አያይዤ አላሰብኩትም ነበር››
‹‹እና ክፉ ነገር አሳሰብከኝ እያልሽ ነው?››
‹‹አረ በፍፅም…ለማለት የፈለኩት..አሁን ትክክለኛ እህቴ እንደሆነች ነው የማስበው….እናቴ እኔን አቅፋ ብትወድቅ እኔ ልወቀስ እንደማልችል ሁሉ ፀጋንም አቅፋ ወድቃ በመሰበሯ ህፃኗ መወቀስ የለባትም ልልህ ፈልጌ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ..ስቀልድ ነው..ግን ልነግርሽ የምፈልገው ትሁት ማለቴ ፀጋ ሰዎች ጥለዋት ሲሄድ በጣም ብትናደድ ምንም አያስደንቅም…ምትወዳቸው ሁሉም ሰዎች ልክ እንደእናቷ ጥሏት ሚሄድ ይመስላታል….››
ራሄል በሰማችው ነገር ደነገጠች…‹‹እንደዛ ነው እንዴ…ሚስኪን !!እናም የሙቀት መጠኗ ከፍ የሚለው በዚህ ምክንያት ነው እንዴ?››
‹‹አዎ..ችግሯ ተያያዥ ነው…››
‹‹ምንድን ነው ችግሯ ?››
‹‹ከግማሽ ሰአት በፊት እያለቀሰች ከእንቅልፏ ነቃች። መድሃኒቷን ሰጥቻታለሁ፣ ግን እየሰራላት ያለ አይመስለኝም።››
ከዚያም ፀጋ በእሷ ላይ ዝልፍልፍ አለች…ራሄል ደነገጠች። ‹‹ምን እየሆነች ነው? ደህና ናት? ››
ደ/ር ዔሊያስ እጁን በትሁት ጀርባ ላይ አደረገ፣ እሷን አረጋጋት። ‹‹ስንት ኪኒን ሰጠሻት?" ብሎ ራሄልን ጠየቃት።ነገረችው ፡፡
‹‹የእሷን የሙቀት መጠን መውሰድ አለብን.››ራሄል ወደ መታጠቢያ ቤት እያመራች ነው፡፡
‹‹ ቴርሞ ሜትር አለኝ››አለች.
ኤሊ ቴርሞሜትሩን በትሁት ጆሮ ውስጥ አስገባ። ከንፈሩን ነከሰው።
‹‹መድኃኒቱ እስከአሁን መስራት ነበረበት። በፍጥነት ማቀዝቀዝ አለብን። ››
ዔሊ በመታጠቢያ ገንዳው አጠገብ ተንበረከከ። ‹‹ውሃውን ላዘጋጅ, አንቺ ልብሷን አውልቂላት."
ኮቱን አውልቆ ቧንቧዎቹን ከፍቶ እጁን ከውሃው በታች በመደቀን… የሙቀት መጠኑን ፈትሸ።ራሄል ከመታጠቢያ ገንዳው አጠገብ ያለች ትንሽ አግዳሚ ወንበር ላይ ተቀመጠች የፀጋን ልብስ በጥንቃቄ አወለቀችላት። ዳይፐርዋን አወለቀችላት። አሁንም ደረቅ ነበር. እሷ እየተቃጠለች ነው እና ራሄል እንደዚህ ያለ ትንሽ አካል እንዴት በዚህ መጠን የሚፋጅ ሙቀት ማመንጨት እንደቻለች አሰበችና ተገረመች፡፡
‹‹እሺ በጣም በዝግታ ወደ ውሃው ውስጥ ንከሪያት።››
ራሄል ከጎኑ ተንበርክካ እንዳላት አደረገች። የፀጋ ገላ ውሃው እንደነካት በራሄል እቅፍ ውስጥ ሆና መጮህ ጀመረች።‹‹በጣም ይቀዘቅዛል ›› አለች፡፡ ራሄል እንደገና ወደ ኋላ ጎተተቻት እና ከውሀው አወጣቻት።
ዔሊ የራሄልን ክንድ ይዞ አስቆማት። ‹‹በጣም ስለሞቀች ለእሷ ቅዝቃዜ ይሰማታል.››ራሄል አንገቷን አዙራ አይኖቹን አየች። በአንድ ጉንጭ ላይ የዲምፕል ምልክት ተመለከተች.
‹‹አይዞሽ.. ደህና ትሆናለች›› ብሎ ሊያፅናናት ሞከረ፡፡ ራሄል ፀጋን በዝግታ ከእንደገና ወደውሀው መለሰቻት። እንደገና ጮኸች፣ በዚህ ጊዜ ግን ራሄል በተሻለ ሁኔታ ዘና ብላ ተሰማት።
‹‹ግንባሯ ላይ ትንሽ ውሃ አንጠባጥቢላት" አለ ዔሊ አጠገቧ ተቀምጦ።
በዚህ ጊዜ ሜሮን ስልክ ጆሮዋ ላይ ለጥፋ የመታጠቢያ ክፍሉን በር ከፍታ ‹‹ እኔን ትፈልጊኛለሽ እንዴ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ ‹‹አሁን ማስተላለፍ የማልችለው አስቸኳይ ጥሪ ደረሰኝ።››
ራሄል አንገቷን ነቀነቀች እና እንድትሄድ በመፍቀድ ትኩረቷን ወደ እህቷ መለሰች። ‹‹ደህና እንሆናለን ብዬ አስባለሁ.››አጠገቧ የተንበረከከውን ዔሊን ተመለከተች።
‹‹አዎ ሁሉ ነገር ሰላም ይሆናል….እናደርገዋለን›› ብሎ አረጋገጠላት።
‹‹እሺ በቃ ሄጃለው።›› በማለት በራፉን መልሳ ዘግታላቸው ሄደች፣ እና በድንገት ራሄልና ዔሊ ብቻቸውን ቀሩ።ሲጨርሱ ፀጋ እየተንቀጠቀጠች ነበር እና ከንፈሮቿ ከደማቅ ቀይ ወደ ገረጣ አመዳም ቀለም እየተቀየሩ ነበር። ራሄል የሚንጠባጠበውን የፀጋን ገላ ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ በማውጣት ዔሊ በሰጣት ለስላሳ ፎጣ ጠቀለለቻት።
ራሄል ፀጋን አደራረቀቻትና ይዛት ወደመኝታ ክፍሏ ስትወስዳት እሱ ወደሳሎን ሄደ፡፡
ከዛ ልብስ ቀይራለት፣ መድሀኒት ሰጥታት አስተኛቻት፡፡ ወዲያው በተረጋጋ ሁኔታ እንቅልፍ ወሰዳት ፡፡ራሄል ከአልጋዋ አጠገብ ቆማ ለረጅም ደቂቃ በሰስት አየቻት…ሳታስበው ይህቺን ልጅ እየወደደቻት ነው…በዚህ ጮርቃ እድሜዋ ለነፍሶ ስትታገልና በዚህ መጠን ስትሰቃይ ማየት ልቧ እንዲደማ ነው ያደረጋት፡፡
ቀስ አለችና ክፍሉን ለቃ ወጣች…ዶ/ሩን ሳሎኑ ውስጥ ሲንጎራደድ አገኘችው፡፡
የኮቴ ድምፅ እንደሰማ ወደእሷ ዞር አለና ‹‹እንዴት ነች?››ብሎ ጠየቃት፡፡
‹‹ተኝታለች ብዬ አስባለሁ…ቆይ ፀጋ በህፃንነቷም እንዲህ ቶሎ ቶሎ ትታመም ነበር እንዴ?››ስትል ጠየቀችው
ዔሊያስ ፈገግ አለ‹‹እናቷ ቅዳሜና እሁድን እሷን ላለመያዝ ስትል ሁሉ ጊዜ ወደ ሆስፒታል ላለመምጣት ሰበብ ትደረድር ነበር።››
‹‹ወላጆቼ ስለ ስለፀጋ እናት ብዙ ሲናገሩ አልሰማሁም ››
‹‹እሷን በጭራሽ አላገኟትም … የሆስፒታሉ ማህበራዊ ሰራተኛ ጉዳዩን በሚያውቅበት ጊዜ, ፀጋ ለብዙ ሳምንታት ከበሽታዋ እየታገለች እናቷ ከአሁን አሁን መጥታ ትወስደኛለች በሚል ጉጉት አይኖቾ እየተንከራተቱ ስትጠብቅ ነበር….የሰው ልጅ ሆነሽ ያንን የልጅቷን የናፍቆት ስቃይ ማየት እንዴት ልብን እንደሚሸረካክት ልነግርሽ አልችልም..ይገርምሻል እናትዬው ግን ተመልሳ ልትመጣላት አልቻለችም…ስናጠያይቅ አንደኛውን ሀገር ጥላ እንደጠፋች ሰማንና ተስፋ ቆረጥን… ለሚመለከተው አካል አመለከትን…እና እንዳጋጣሚ ከወላጆችሽ ጋር የተገናኘሁት በዛ ጊዜ ነበር…በአጋጣሚ ስለልጅቷ ሁኔታ እንደሰሙ ሆስፒታል ሄደን ካላየናት አሉ..ይዣቸው ሄድኩ…ልክ እንዳዮት ሁለቱም ወደዷት…ከዚህ በፊት እንደነገርኩሽ ያለባትን የጤና ችግር፤ምን አይነት እንክብካቤ እደሚስፈልጋት…ለእሷ ህክምና ሊያወጡት የሚችሉትን ገንዘብ ..እንደዛም ሆኖ ለመዳን ያላት እድል አናሳ እንደሆነ ሁሉንም በግልፅ አስረድቻቸውም እነሱ እሷን እንደልጃቸው አድርገው ለመቀበልና ወደቤታቸው ለመውሰድ ቅንጣት ያህል አላቅማሙም…እኔ በህይወት ዘመኔ እንደወላጆችሽ አይነት ትክክለኛ መንፈሳዊ ሰው አላውቅም….ከአእምሮዬ በላይ ናቸው፡፡እኔም በተቻኝ መጠን ከፀጋ ጎን ላለመራቅ የወሰንኩት የእነሱን ደግነት ካየው በኋላ ነው፡፡››
‹‹አዎ..እነሱ እንደዛ ናቸው…እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ..መጀመሪየ ውሳኔያቸውን ስሰማና ሆስፒታል ሄጄ ፀጋን የሀገር ቱቦና ማሽኑ ሰውነቷ ላይ ተሰክቶ ሳይ ምለውና ምናገረው ጠፍቶኝ ነበር…አፍ አውጥቼ ባልቃወምም በውስጤ ግን በጣም ተበሳጭቼ ነበር….አሁን ያንን ስሜቴን ትዝ ሲለኝ በጣም አፍራለው፡፡››
‹‹አትፈሪ…በሆድሽ አስበሽ ቢሆን እንኳን..በአፍሽ ተቃውሞ አለማሰማትሽ እራሱ አንድ ጥሩ ነገር ነው….አየሽ ልጅቷ በጣም አሳዝናሽ ነበር..ግን ደግሞ እድሜያቸው ለገፋ ወላጆችሽም የበለጥ ማሰብሽ እና መጨነቅሽ የሚያስወቅስሽ አይደለም…ተመልከቺ እናትሽ አሁን የት ነው ያለችው ሆስፒታል አልጋ ላይ …ምን ሆና..?ፀጋን አቅፋ ደረጃ ስትወርድ ሚዛኗን ስታ…እና አንቺ ክፉ ሴት ብትሆኜ ‹‹እናቴን እንድትሰበር አድርጋ ለዚህ አደጋ የዳረገችብኝ ይህቺ ልጅ ነች …ገፊ ነች ምናምን ብለሽ..እሷን ከህይወትሽ ለማስወገድ ነበር የምትጥሪው..ይሄው ግን አንቺ ከእሷ ጋር እየተሰቃየሽ ነው…ልክ እንደእናቷ ሲያማት እያመመሽ….ስታለቅስ እያለቀሽ ነው፡፡››
‹‹አንተ ….እስከአሁን እናቴ በእሷ ምክንያ እንደወደቀች እራሱ አያይዤ አላሰብኩትም ነበር››
‹‹እና ክፉ ነገር አሳሰብከኝ እያልሽ ነው?››
‹‹አረ በፍፅም…ለማለት የፈለኩት..አሁን ትክክለኛ እህቴ እንደሆነች ነው የማስበው….እናቴ እኔን አቅፋ ብትወድቅ እኔ ልወቀስ እንደማልችል ሁሉ ፀጋንም አቅፋ ወድቃ በመሰበሯ ህፃኗ መወቀስ የለባትም ልልህ ፈልጌ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ..ስቀልድ ነው..ግን ልነግርሽ የምፈልገው ትሁት ማለቴ ፀጋ ሰዎች ጥለዋት ሲሄድ በጣም ብትናደድ ምንም አያስደንቅም…ምትወዳቸው ሁሉም ሰዎች ልክ እንደእናቷ ጥሏት ሚሄድ ይመስላታል….››
ራሄል በሰማችው ነገር ደነገጠች…‹‹እንደዛ ነው እንዴ…ሚስኪን !!እናም የሙቀት መጠኗ ከፍ የሚለው በዚህ ምክንያት ነው እንዴ?››
‹‹አዎ..ችግሯ ተያያዥ ነው…››
❤51
‹‹እሷን ለማገዝ በአቅራቢያዋ ስለነበርክ ደስ ብሎኛል.››አለችው
‹‹ምንም አይደል…ሁሌ ከእሷ ጎን ለመገኘት ለራሴ ቃል ገብቻለው..እሷ ለእኔ ትልቅ ትርጉም አላት››
‹‹በጣም ጥሩ ››አለች፡፡
ውይይቱ ወደ ስንብት ወይም ለቡና ግብዣ እየቀረበ ነበር። ራሄል ትንሽ እንዲቆይ ልትጠይቀው አስባ ከንፈሯን ነከሰች። የወንድ ጓደኛ ረጅም ጊዜ አልነበራትም። እጮኛዋ ኪሩቤል በአደጋ ከሞተ በኋላ የፍቅር ጓደኛ ለመያዝ የተወሰነ ሙከራ ሞክራ ነበር ፣ ነገር ግን ሁሉም ወንድ ከእሷ ሚዛን ቀሊል እየሆኑ ተቸገረችና እርግፍ አድርጋ ተወችው ፡፡ አሁን ምንም እንኳን የእጮኛዋ ትውስታዎች ቢደበዝዙም ፣ እምቅ ህመሟ በህይወቷ ውስጥ የተደበቀ ቁስል ነበር ።እንደገና ልቧን ለመክፈት አልፈለገችም፡፡
ኤሊያስ ከተቀመጠበት ተነሳ ፡፡የሞተር ብስክሌቱን ሄልሜት ከአንድ እጁ ወደ ሌላው አዘዋወረ ፡፡ ራሄል ከእሱ ለመራቅ ባደረገችው ውሳኔ ፀናች።
‹‹መልካም፣ የሆነ ነገር ከተቀየረ አሳውቂኝ››በማለት ሌላ ፈገግታ ፈገግ አለላትና ሄደ።በሩ ከኋላዋ ሲዘጋ፣ ራሄል በረጅሙ ተነፈሰች። እሱን እንዲቆይ አለመጠየቋ ትክክለኛ ውሳኔ እንደሆነ አሰበች። እንኳን ፍቅር ተጨምሮበት ህይወቷ አሁንም በጣም የተወሳሰበ ነው፡፡ ታዲያ ለምን ድንገት ብቸኝነት ተሰማት? ለምን ታዲያ በአንድ ወቅት አስደሳችና ውብ የሆነው አፓርታማዋ አሁን በቅፅበት በጣም ቀዝቃዛ እና ባዶ መሰላት?የጭንቀት ስሜት ወረራት… ከተቀመጠበት ተነሳችና ወደ ፀጋ ክፍል ተመልሳ ሄደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ምንም አይደል…ሁሌ ከእሷ ጎን ለመገኘት ለራሴ ቃል ገብቻለው..እሷ ለእኔ ትልቅ ትርጉም አላት››
‹‹በጣም ጥሩ ››አለች፡፡
ውይይቱ ወደ ስንብት ወይም ለቡና ግብዣ እየቀረበ ነበር። ራሄል ትንሽ እንዲቆይ ልትጠይቀው አስባ ከንፈሯን ነከሰች። የወንድ ጓደኛ ረጅም ጊዜ አልነበራትም። እጮኛዋ ኪሩቤል በአደጋ ከሞተ በኋላ የፍቅር ጓደኛ ለመያዝ የተወሰነ ሙከራ ሞክራ ነበር ፣ ነገር ግን ሁሉም ወንድ ከእሷ ሚዛን ቀሊል እየሆኑ ተቸገረችና እርግፍ አድርጋ ተወችው ፡፡ አሁን ምንም እንኳን የእጮኛዋ ትውስታዎች ቢደበዝዙም ፣ እምቅ ህመሟ በህይወቷ ውስጥ የተደበቀ ቁስል ነበር ።እንደገና ልቧን ለመክፈት አልፈለገችም፡፡
ኤሊያስ ከተቀመጠበት ተነሳ ፡፡የሞተር ብስክሌቱን ሄልሜት ከአንድ እጁ ወደ ሌላው አዘዋወረ ፡፡ ራሄል ከእሱ ለመራቅ ባደረገችው ውሳኔ ፀናች።
‹‹መልካም፣ የሆነ ነገር ከተቀየረ አሳውቂኝ››በማለት ሌላ ፈገግታ ፈገግ አለላትና ሄደ።በሩ ከኋላዋ ሲዘጋ፣ ራሄል በረጅሙ ተነፈሰች። እሱን እንዲቆይ አለመጠየቋ ትክክለኛ ውሳኔ እንደሆነ አሰበች። እንኳን ፍቅር ተጨምሮበት ህይወቷ አሁንም በጣም የተወሳሰበ ነው፡፡ ታዲያ ለምን ድንገት ብቸኝነት ተሰማት? ለምን ታዲያ በአንድ ወቅት አስደሳችና ውብ የሆነው አፓርታማዋ አሁን በቅፅበት በጣም ቀዝቃዛ እና ባዶ መሰላት?የጭንቀት ስሜት ወረራት… ከተቀመጠበት ተነሳችና ወደ ፀጋ ክፍል ተመልሳ ሄደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤37👍8
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ወደ ሆስፒታሉ በሚወስደው መንገድ ላይ ሞተሩን እያስጎራ በመብረር ላይ ነው፡፡ ሀሳቡ ግን አሁንም ወደኋላ እየጎተተው ነው፡፡ በዚህ የሰንበት ማለዳ ወደእነራሄል ወላጆች ቤት የሄድኩት ራሄል ፀጋን እንዴት እያስተዳደረች እንደሆነ ለማየት ብቻ ነበር። ጉብኝቱ የህፃኗ ሐኪም በመሆኔ ያደረግኩት ነው።››ሲል ለራሱ ነገረው፡
አሁን፣ ፀጉሯን በትና እና የደበዘዘ ቲሸርት የለበሰች እንዲት ቆንጆ ሴት በአእምሮው ሰሌዳ ላይ ብልጭ ድርግም እያለች እየረበሸችው ነው፡፡ በባዶ እግሯ እና በሰማያዊ ጂንስዋ ምን ያህል ውብ እንደሆነች እያሰበ ነበር፣እሷ የምትኖርበትን ቤት እንዴት ግዙፍ እንደሆነ እና ወላጆቿ ምን ያህል ገንዘብ እንዳላቸው እያሰበ ነበር። እና የተከበረ የመኳንንት ዝርያ አለን ብለው የሚያስቡ ወላጇች እንዳሏት እያሰበ ነበር… እና ደግሞ እሱ ሰለወላጇቹ ምን ይሁኑ ምን የሚያውቀው ነገር እንደሌለም እያሰበ ነበር፡፡በዚህም ሆነ በዚያ ሀሳቡ በራሄል ዙሪያ ከመሽከርከር ሊያቅበው አልተቻለውም፡፡
ኤልያስ አሳዳጊ ወላጆቹ ስለስጋ ወላጇቹ ብዙ ጊዜ አይናገሩም ወይም የበለጠ እንዲያውቅ አያበረታቱትም። ወደፊት ፀጋም ልክ እንደእሱ ስለ እናቷ እና አባቷ ማወቅ እንደምትፈልግ ገመተ።ስለ ፀጋ ማሰቡ በትክክል ወደ ራሄል መለሰው።ሸሩባ የተሰራው ጥቁር ፀጉሯ ፊቷን እንዴት እንደአሳመረው እና ሀዘን ያጠላባቸው ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿ ከብለል ሲሉ እንዴት ልብን እንደሚያርዱ አሰበ። ሆስፒታል ደርሶ ሞተሩን ሲያቆም እንኳ ሀሳብን መግታት አልቻለም ነበር፡፡
///
ራሄል ትሁት ቁርስ ስትበላ ፊቷ ላይ የተዝረከረከውን በደረቅ ጨርቅ በጥንቃቄ ጠራረገችላት። እቃዎችን እያጣጠበች ሳለ ፀጋ ወደ በረንዳ በሮች ስትሄድ አየች። ሰራተኛዋ አለም ሁል ጊዜ መስኮቶቹን በሚያብረቀርቅ ንፅህና ነው የምትይዛቸው ፣ ዛሬ ግን እሷና ፀጋ ብቻቸውን ናቸው..ሰራተኛዋ የረፍት ቀኗ ስለሆነ ዘመድ ጥየቃ ሄዳለች።እቃ ማጠቧን እንዳጠናቀቀች..ትንሿን እህቷን ለማየት ወደበረንዳ ስትወጣ የጸጋ ትንሽዬ የእጅ ህትመቶች መስታወቱን ጠቅላላ አዳርሰውት ሌላ ቅርፅ ሰጥተውት አገኘች፡፡ መጀመሪያ መልሳ ለማፅዳት ስትሞከር ፀጋ ከኋላዋ እየተከተለች መልሳ ስታቆሽሽባት…በመናደድ ፋንታ ከት ብላ ሳቀችና ማፅዳቱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡
‹‹ከአንድ በላይ ልጅ ያላቸው ሰዎች እንዴት በህይወት መቆየት ቻሉ?››ስትል ገረሜታዋን ገለፀች ፡፡ከፀጋ ጋር በቀጣይ ምን ማድረግ እንደምትችል አሰበች.. ።ሰዓቱን ተመለከተች, ከዚያም ወደ እሷ ተመለሰች. ወላጆቿ ዘወትር እሁድ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሄዱ ታውቃለች። ወጣት ሳለች ሁልጊዜ አብራቸው ትሄድ ነበር፣ ነገር ግን እጮኛዋ ኪሩቤል ከሞተ በኋላ ወደቤተክርስቲያን መሄዱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ ይህ ድርጊቷ ወላጆቿን በጣም እንደሚያበሳጫቸው ታውቃለች፣ እነሱ ስለሚፈልጉ ብቻ ነገሮችን ማድረግ እንዳለባት አታምንም። እሷ የራሷን ሕይወት እየመራች ነበር፣ እና እግዚአብሔር የህይወቷ አካል አይደለም።
ፀጋን ስትመለከት ግን በድንገት ተጨማሪ ሀላፊነት እንዳለባት ተሰማት። በእርግጥ የሁለት ዓመት ልጅ ነበረች፣ … ስለግል እምነቷ ለራሷ ውሳኔ ማድረግ እንደምትችል ብታምንም ለዚህች ልጅም ተመሳሳይ ነገር ማድረጉ ትክክል ሆኖ አልተሰማትም።ወላጇቾ ቢኖሩ ይዘዋት እንደሚሄዱ እርግጠኛ ነች፡፡
‹ስለዚህ ወደ ፀጋ ጎንበስ አለችና‹‹የእኔ ቆንጅዬ እህት .. ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ትፈልጊያለሽ?›› ብላ ጠየቀቻት ፡፡
ህፃኗ በደስታ እየዘለለች‹‹ቤተክርስትያን እንሂድ፣ ቤተክርስትያን እንሂድ››አለች ፡፡ ራሄልም ልብሷን ቀያይራ ካለባበሰቻት በኋላ ወደቤተክርስቲያን ይዛት ሄደች፡፡
ራሄል የኮሌጅ ትምህርቷን እስካጠናቀቀች ድረስ ንቁ ተሳታፊ ነበረች።ሁሉ ነገር የተቀየረው እጮኛዋ ከሞት በኋላ ነው።እና አሁን የመቅደሱ ዙሪያ ስትመለከት፣ የልጅነትና የጉልምስና ትውስታዎች ሁሉ ተግተልትለው በአእምሯ ውስጥ ብልጭ ድርግም አሉባት። የዚህ ቤተክርስቲያን መዘምራን አባል ሆና ለረጅም አመት አገልግላለች ፤እዚህ መድረክ ላይ ወጥታ ስለጌታ የአዳኝነት ስራ ስትዘምር ትዝ ይላታል፡፡ ድምፆ ተስረቅራቂ የሚባል አይነት ስለነበር ብዙውን ጊዜ ድምጽ ማጉያውን ይዛ መዝምራኖችን የምትመራው እሷ ነበረች፡፡እጮኛዋ ኪሩቤልንም እዚሁ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው የተዋወቀችው፡፡እሱም ልክ እንደ እሷ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነበር…. ከዚያ ከመቀራረብና አብሮ ከመዋል ብዛት የፍቅር ስሜት በመሀከላቸው ተፈጠረ፡፡በቤተክርስቲያኒቷ ፊት ቃልኪዳን ተግባቡ …ሀይስኩል ጨረሱ ..ኮሌጅ ገቡ….እስከዛን ድረስ ሁለቱም በእምነታቸው የፀኑ ወጣቶች ነበሩ…ሁሉን ነገር ሀይማኖቱ በሚያዘው እና ቤተሰቦቻቸው በሚደሰቱበት አግባብ ለማድረግ ነበር እቅዳቸው…ሰርጋቸውን ባደጉበትና ባገለገሉበት ቤተክርስቲያን አደባባይ ላይ ለማድረግ ነበር ውጥናቸውና ጉጉታቸውም…ግን ምን ሆነ ህልማቸውን ሊኖሩ ወራት ሲቀራቸው..፣ኪሩቤል ድንገት ከእሷ ጋር ወደተቀጣጠረበት ቦታ ሞተር ሳይክሉን እያበረረ ሲመጣ እየተክለፈለፍ በፍጥነት ከሚያበር መኪና ጋር ተላትሞ በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ…ይድንልኛል..መልሶ በእግሮቹ ቆሞ እንጋባላን ብላ ሆስፒታል ደረቅ ወንበር ላይ እየተኛች አንድ ወር ከግማሽ አካባቢ አስታመመችው…ግን አልተሳካም….የኪሩቤል ነፍስ ወደፈጣሪዋ ተጠርታ ሄደች..ከዛ ወዲህ ራሄል ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ሆነች…ሆስፒታል አስጠላት…የመድሀኒት ሽታ ቀፈፋት…ቤተክርስቲያንና እምነት አንገሸገሻት..የታመመ ሰው ማየት አቃታት…ይሄው አሁን ለታናሽ እህቷ ስትል እዚህ ያደገችበት ቤተክርስቲያን ስትመጣ ቁስሏ ሁሉ ክፉኛ ተቀሰቀሰ፡፡ እና የሚቀስፍ አይነት ህመም ተሰማት፣ ከዚሁ ሁሉ በጣም የሚገርመው ግን ለአፍታ ያህል ኪሩቤል ምን እንደሚመስል እንኳ ማስታወስ አለመቻሏ ነው ። ከሞቱ በኋላ አብዛኛዎቹን የኪሩቤልን ምስሎች በወላጆቿ ቤት አስቀምጧቸው ነበር እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አልተመለከቷቸውም። በጣም ተጎድታ ነበር። አሁን ምን እንደሚሰማት ግራ ተገባች።በመጨረሻም ጓዳኛዋ ሌንሳ ከወላጆቿ እና ከሁለት መንታ ልጇቾ ጋር ተቀምጣ አየች። ራሄል ከጎኗ ሾልካ ገባች።
‹‹ቤተክርስትያን መሄድ እርግፍ አድርገሽ የተውሽ መስሎኝ ነበር›› ስትል ወደጀ ጆሮዋ ቀርባ አንሾካሾከችላት፡፡
ሌንሳ ወደኋላ ዞረችና እያወራቻት ያለችው ራሄል መሆኗን ስታውቅ በመገረም ‹‹ራሄል እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?›› ስትል ወደኋላ ተስባ አቀፈቻት፡፡
‹‹ፀጋን ማምጣት እንዳለብኝ ተሰማኝ››ስትል የመጣችበትን ምክንያት ነገረቻት፡፡
‹‹እሺ በምንም ምክንያት ይሁን በምንም እዚህ በመገኘትሽ ደስ ብሎኛል.››
የሌንሳ ወላጆችም በደስታ ሰላም አሏት፡፡
ዝግጅቱ እናዳለቀ ፀጋን እንዳቀፈች እነ ለሌንሳን ተከትላ ወደአውደ ምህረቱ ሄደች…ከረጅም ጊዜ በፊት የምታውቃቸውን በጣም ብዙ የድሮ ጎደኞቾንና ወዳጆቾን አገኘች፡፡ ብዙ ሰው ለምን እንደጠፋች እየጠየቃት በመምጣቷ እንደተደሰቱ ይነግሯት ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ወደ ሆስፒታሉ በሚወስደው መንገድ ላይ ሞተሩን እያስጎራ በመብረር ላይ ነው፡፡ ሀሳቡ ግን አሁንም ወደኋላ እየጎተተው ነው፡፡ በዚህ የሰንበት ማለዳ ወደእነራሄል ወላጆች ቤት የሄድኩት ራሄል ፀጋን እንዴት እያስተዳደረች እንደሆነ ለማየት ብቻ ነበር። ጉብኝቱ የህፃኗ ሐኪም በመሆኔ ያደረግኩት ነው።››ሲል ለራሱ ነገረው፡
አሁን፣ ፀጉሯን በትና እና የደበዘዘ ቲሸርት የለበሰች እንዲት ቆንጆ ሴት በአእምሮው ሰሌዳ ላይ ብልጭ ድርግም እያለች እየረበሸችው ነው፡፡ በባዶ እግሯ እና በሰማያዊ ጂንስዋ ምን ያህል ውብ እንደሆነች እያሰበ ነበር፣እሷ የምትኖርበትን ቤት እንዴት ግዙፍ እንደሆነ እና ወላጆቿ ምን ያህል ገንዘብ እንዳላቸው እያሰበ ነበር። እና የተከበረ የመኳንንት ዝርያ አለን ብለው የሚያስቡ ወላጇች እንዳሏት እያሰበ ነበር… እና ደግሞ እሱ ሰለወላጇቹ ምን ይሁኑ ምን የሚያውቀው ነገር እንደሌለም እያሰበ ነበር፡፡በዚህም ሆነ በዚያ ሀሳቡ በራሄል ዙሪያ ከመሽከርከር ሊያቅበው አልተቻለውም፡፡
ኤልያስ አሳዳጊ ወላጆቹ ስለስጋ ወላጇቹ ብዙ ጊዜ አይናገሩም ወይም የበለጠ እንዲያውቅ አያበረታቱትም። ወደፊት ፀጋም ልክ እንደእሱ ስለ እናቷ እና አባቷ ማወቅ እንደምትፈልግ ገመተ።ስለ ፀጋ ማሰቡ በትክክል ወደ ራሄል መለሰው።ሸሩባ የተሰራው ጥቁር ፀጉሯ ፊቷን እንዴት እንደአሳመረው እና ሀዘን ያጠላባቸው ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿ ከብለል ሲሉ እንዴት ልብን እንደሚያርዱ አሰበ። ሆስፒታል ደርሶ ሞተሩን ሲያቆም እንኳ ሀሳብን መግታት አልቻለም ነበር፡፡
///
ራሄል ትሁት ቁርስ ስትበላ ፊቷ ላይ የተዝረከረከውን በደረቅ ጨርቅ በጥንቃቄ ጠራረገችላት። እቃዎችን እያጣጠበች ሳለ ፀጋ ወደ በረንዳ በሮች ስትሄድ አየች። ሰራተኛዋ አለም ሁል ጊዜ መስኮቶቹን በሚያብረቀርቅ ንፅህና ነው የምትይዛቸው ፣ ዛሬ ግን እሷና ፀጋ ብቻቸውን ናቸው..ሰራተኛዋ የረፍት ቀኗ ስለሆነ ዘመድ ጥየቃ ሄዳለች።እቃ ማጠቧን እንዳጠናቀቀች..ትንሿን እህቷን ለማየት ወደበረንዳ ስትወጣ የጸጋ ትንሽዬ የእጅ ህትመቶች መስታወቱን ጠቅላላ አዳርሰውት ሌላ ቅርፅ ሰጥተውት አገኘች፡፡ መጀመሪያ መልሳ ለማፅዳት ስትሞከር ፀጋ ከኋላዋ እየተከተለች መልሳ ስታቆሽሽባት…በመናደድ ፋንታ ከት ብላ ሳቀችና ማፅዳቱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡
‹‹ከአንድ በላይ ልጅ ያላቸው ሰዎች እንዴት በህይወት መቆየት ቻሉ?››ስትል ገረሜታዋን ገለፀች ፡፡ከፀጋ ጋር በቀጣይ ምን ማድረግ እንደምትችል አሰበች.. ።ሰዓቱን ተመለከተች, ከዚያም ወደ እሷ ተመለሰች. ወላጆቿ ዘወትር እሁድ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሄዱ ታውቃለች። ወጣት ሳለች ሁልጊዜ አብራቸው ትሄድ ነበር፣ ነገር ግን እጮኛዋ ኪሩቤል ከሞተ በኋላ ወደቤተክርስቲያን መሄዱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ ይህ ድርጊቷ ወላጆቿን በጣም እንደሚያበሳጫቸው ታውቃለች፣ እነሱ ስለሚፈልጉ ብቻ ነገሮችን ማድረግ እንዳለባት አታምንም። እሷ የራሷን ሕይወት እየመራች ነበር፣ እና እግዚአብሔር የህይወቷ አካል አይደለም።
ፀጋን ስትመለከት ግን በድንገት ተጨማሪ ሀላፊነት እንዳለባት ተሰማት። በእርግጥ የሁለት ዓመት ልጅ ነበረች፣ … ስለግል እምነቷ ለራሷ ውሳኔ ማድረግ እንደምትችል ብታምንም ለዚህች ልጅም ተመሳሳይ ነገር ማድረጉ ትክክል ሆኖ አልተሰማትም።ወላጇቾ ቢኖሩ ይዘዋት እንደሚሄዱ እርግጠኛ ነች፡፡
‹ስለዚህ ወደ ፀጋ ጎንበስ አለችና‹‹የእኔ ቆንጅዬ እህት .. ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ትፈልጊያለሽ?›› ብላ ጠየቀቻት ፡፡
ህፃኗ በደስታ እየዘለለች‹‹ቤተክርስትያን እንሂድ፣ ቤተክርስትያን እንሂድ››አለች ፡፡ ራሄልም ልብሷን ቀያይራ ካለባበሰቻት በኋላ ወደቤተክርስቲያን ይዛት ሄደች፡፡
ራሄል የኮሌጅ ትምህርቷን እስካጠናቀቀች ድረስ ንቁ ተሳታፊ ነበረች።ሁሉ ነገር የተቀየረው እጮኛዋ ከሞት በኋላ ነው።እና አሁን የመቅደሱ ዙሪያ ስትመለከት፣ የልጅነትና የጉልምስና ትውስታዎች ሁሉ ተግተልትለው በአእምሯ ውስጥ ብልጭ ድርግም አሉባት። የዚህ ቤተክርስቲያን መዘምራን አባል ሆና ለረጅም አመት አገልግላለች ፤እዚህ መድረክ ላይ ወጥታ ስለጌታ የአዳኝነት ስራ ስትዘምር ትዝ ይላታል፡፡ ድምፆ ተስረቅራቂ የሚባል አይነት ስለነበር ብዙውን ጊዜ ድምጽ ማጉያውን ይዛ መዝምራኖችን የምትመራው እሷ ነበረች፡፡እጮኛዋ ኪሩቤልንም እዚሁ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው የተዋወቀችው፡፡እሱም ልክ እንደ እሷ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነበር…. ከዚያ ከመቀራረብና አብሮ ከመዋል ብዛት የፍቅር ስሜት በመሀከላቸው ተፈጠረ፡፡በቤተክርስቲያኒቷ ፊት ቃልኪዳን ተግባቡ …ሀይስኩል ጨረሱ ..ኮሌጅ ገቡ….እስከዛን ድረስ ሁለቱም በእምነታቸው የፀኑ ወጣቶች ነበሩ…ሁሉን ነገር ሀይማኖቱ በሚያዘው እና ቤተሰቦቻቸው በሚደሰቱበት አግባብ ለማድረግ ነበር እቅዳቸው…ሰርጋቸውን ባደጉበትና ባገለገሉበት ቤተክርስቲያን አደባባይ ላይ ለማድረግ ነበር ውጥናቸውና ጉጉታቸውም…ግን ምን ሆነ ህልማቸውን ሊኖሩ ወራት ሲቀራቸው..፣ኪሩቤል ድንገት ከእሷ ጋር ወደተቀጣጠረበት ቦታ ሞተር ሳይክሉን እያበረረ ሲመጣ እየተክለፈለፍ በፍጥነት ከሚያበር መኪና ጋር ተላትሞ በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ…ይድንልኛል..መልሶ በእግሮቹ ቆሞ እንጋባላን ብላ ሆስፒታል ደረቅ ወንበር ላይ እየተኛች አንድ ወር ከግማሽ አካባቢ አስታመመችው…ግን አልተሳካም….የኪሩቤል ነፍስ ወደፈጣሪዋ ተጠርታ ሄደች..ከዛ ወዲህ ራሄል ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ሆነች…ሆስፒታል አስጠላት…የመድሀኒት ሽታ ቀፈፋት…ቤተክርስቲያንና እምነት አንገሸገሻት..የታመመ ሰው ማየት አቃታት…ይሄው አሁን ለታናሽ እህቷ ስትል እዚህ ያደገችበት ቤተክርስቲያን ስትመጣ ቁስሏ ሁሉ ክፉኛ ተቀሰቀሰ፡፡ እና የሚቀስፍ አይነት ህመም ተሰማት፣ ከዚሁ ሁሉ በጣም የሚገርመው ግን ለአፍታ ያህል ኪሩቤል ምን እንደሚመስል እንኳ ማስታወስ አለመቻሏ ነው ። ከሞቱ በኋላ አብዛኛዎቹን የኪሩቤልን ምስሎች በወላጆቿ ቤት አስቀምጧቸው ነበር እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አልተመለከቷቸውም። በጣም ተጎድታ ነበር። አሁን ምን እንደሚሰማት ግራ ተገባች።በመጨረሻም ጓዳኛዋ ሌንሳ ከወላጆቿ እና ከሁለት መንታ ልጇቾ ጋር ተቀምጣ አየች። ራሄል ከጎኗ ሾልካ ገባች።
‹‹ቤተክርስትያን መሄድ እርግፍ አድርገሽ የተውሽ መስሎኝ ነበር›› ስትል ወደጀ ጆሮዋ ቀርባ አንሾካሾከችላት፡፡
ሌንሳ ወደኋላ ዞረችና እያወራቻት ያለችው ራሄል መሆኗን ስታውቅ በመገረም ‹‹ራሄል እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?›› ስትል ወደኋላ ተስባ አቀፈቻት፡፡
‹‹ፀጋን ማምጣት እንዳለብኝ ተሰማኝ››ስትል የመጣችበትን ምክንያት ነገረቻት፡፡
‹‹እሺ በምንም ምክንያት ይሁን በምንም እዚህ በመገኘትሽ ደስ ብሎኛል.››
የሌንሳ ወላጆችም በደስታ ሰላም አሏት፡፡
ዝግጅቱ እናዳለቀ ፀጋን እንዳቀፈች እነ ለሌንሳን ተከትላ ወደአውደ ምህረቱ ሄደች…ከረጅም ጊዜ በፊት የምታውቃቸውን በጣም ብዙ የድሮ ጎደኞቾንና ወዳጆቾን አገኘች፡፡ ብዙ ሰው ለምን እንደጠፋች እየጠየቃት በመምጣቷ እንደተደሰቱ ይነግሯት ነበር፡፡
❤36👍4👎1😁1
ከዛ መዝሙር መዘመር ጀመረ…መዝሙሩ ለእሷ አዲስ ነበር ፣ዜማው ግን ደስ ስለሚል
በተመስጦ ነበር ስታዳምጥ የነበረው…ሁለተኛውን መዝሙር ግን ከልቧ ነበር ስትዘምር የነበር …
ልጅ እያለች ጀምሮ ሁልጊዜም በመዝሙሩ ትደሰት ነበር፣
ሰባኪው ስብከቱን ሲጀምር ሁሉም በፀጥታ ማዳመጥ ጀመሩ
///
…. እግዚአብሔር በህይወታችን ስለሚያደርገው ነገር እንበሳጫለን። እኛን ሊያስተምረን እየሞከረ እንደሆነ አይገባንም። እግዚአብሔርን ችላ ለማለት ልንሞክር እንችላለን፣ነገር ግን ያንን ማድረግ በግድግዳው ላይ‹‹ጨለማ››የሚለውን ቃል በመጻፍ ብርሃንን ለማስወገድ እንደመሞከር ነው። በችግር እና በስቃይ ውስጥ ልንሆን እንችላለን፣ ነገር ግን ‹‹እግዚአብሔር በሹክሹክታ በሕሊናችን ይናገራል .. በሥቃያችን ምክንያት የሚያሰማው ጩኻት መስማት የተሳነውን ዓለም ለመቀስቀስ የሚጠቀምበት የእሱ ሜጋፎን ነው። ህመማችን እና ሀዘናችን የእኛን የፈዘዘ ትኩረት የሚስብበት መንገድ ይሆናል ብዬ አምናለሁ። ራሳችንን የቻልን ፍጥረታት ነን ብለን ስለምናስብ… ሁሉንም ነገር በራሳችን ማድረግ እንደምንችል እናስባለን. ከእግዚአብሔር ተለይተን መኖር የምንችል ይመስለናል ይህም የአበባው ሽታ ከአበባው ለመለየት እንደመሞከር ነው። እግዚአብሔር ሁል ጊዜ አለ እና የህይወታችንን ቁጥጥር ለእርሱ አሳልፈን እንድንሰጥ እየጠበቀን ነው።
ራሄል ስብከቱ ለእሷ ታቅዶ የተዘጋጀ መስሎ ተሰማት…ኪሩቤል ከሞተ በኃላ እግዚአብሔር የሚናገራትን ነገር ሁሉ ላለመስማት ጆሮዋን ዘጋች። የህይወቷ የበላይ ለመሆን እና ለመቆጣጠር ጣረች።ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ፣ በህይወቷ ውስጥ የተከሰቱት ክስተቶች ይህ ምን ያህል ከንቱ እንደሆነ አሳይቷታል።ግን ሌላ ምን ማድረግ ነበረባት? እሷ ፋውንዴሽን ውስጥ መልካም ነገር እየሰራች ነበር. ሰዎችን ከችግራቸው ለማላቀቅ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በስራዋ ላይ ይደገፋሉ.
ሰባኪው ስብከቱን ቀጥሏል ….
..እኛ በሕይወታችን ውስጥ ኃላፊ እንደሆንን በማሰብ፣እንዴት ራሳችንን እንዲህ እናቆስላለን? በእውነቱ እኛ የራሳችን ህይወት ሀለቆች አይደለንም…አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር የራሳችንን መንገድ ለማወቅ እንድንችል በራሳችን መንገድ እንድንሄድ ይፈቅድልናል። ነፍሶች ወደርሱ እስኪጠጉ ድረስ ዕረፍት የላቸውም። ስለዚህ አሁን በመዝሙራዊው ዳዊት መዝሙረ 139፡6 ላይ ባለው የእግዚያብሄር ቃል የእለቱን ትምህርታችንን እንዘጋለን፡፡
‹‹በሰማይእና በምድር በባሕር እና በጥልቆች ሁሉ፣እግዚያብሄር የወደደውን ሁሉ አደረገ ..
….››ቃላቱ በህንፃው ውስጥ ተስተጋብተው በራሔል ልብ ውስጥ አረፉ። ለእግዚአብሔር ጀርባዋን ሰጥታው ነበር። አላመነችበትም ነበር። እና ይህ ሁሉ ቢሆንም ፣ በእሷ ውስጥ ግልፅ የሆነ እረፍት አልነበረም…. ያለ ምንም ጥርጣሬ፣ እግዚአብሔር የለም ማለት አልቻለችም።አዎ ለአመታት በኪሩቤል ሞት አዝናለች… አዎ…እሱን እንዴት እንዳጣችው በማሰብ አሁንም ለብስጭት እና ተስፋ ለመቁረጥ ተጋላጭ እንድትሆን አድርጓታል። አሁንም አምላክ ለምን ጸሎቷን እንዳልመለሰላት ግራ ተጋብታለች። ለዚያ መልሱን አላወቀችም። ነገር ግን በሕይወቷ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት እንዲህ በቀላሉ መካድ እንደማትችል ታውቃለች። ዛሬ የእሱ የተለመደ መነካካት ተሰምቷታል። የመጨረሻው መዝሙር ሲዘመር ፀጋን አቀፈቻትና ከማንም ሰው በመራቅ ከምዕመናኑ መሀከል ሾልካ ወጣች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በተመስጦ ነበር ስታዳምጥ የነበረው…ሁለተኛውን መዝሙር ግን ከልቧ ነበር ስትዘምር የነበር …
ልጅ እያለች ጀምሮ ሁልጊዜም በመዝሙሩ ትደሰት ነበር፣
ሰባኪው ስብከቱን ሲጀምር ሁሉም በፀጥታ ማዳመጥ ጀመሩ
///
…. እግዚአብሔር በህይወታችን ስለሚያደርገው ነገር እንበሳጫለን። እኛን ሊያስተምረን እየሞከረ እንደሆነ አይገባንም። እግዚአብሔርን ችላ ለማለት ልንሞክር እንችላለን፣ነገር ግን ያንን ማድረግ በግድግዳው ላይ‹‹ጨለማ››የሚለውን ቃል በመጻፍ ብርሃንን ለማስወገድ እንደመሞከር ነው። በችግር እና በስቃይ ውስጥ ልንሆን እንችላለን፣ ነገር ግን ‹‹እግዚአብሔር በሹክሹክታ በሕሊናችን ይናገራል .. በሥቃያችን ምክንያት የሚያሰማው ጩኻት መስማት የተሳነውን ዓለም ለመቀስቀስ የሚጠቀምበት የእሱ ሜጋፎን ነው። ህመማችን እና ሀዘናችን የእኛን የፈዘዘ ትኩረት የሚስብበት መንገድ ይሆናል ብዬ አምናለሁ። ራሳችንን የቻልን ፍጥረታት ነን ብለን ስለምናስብ… ሁሉንም ነገር በራሳችን ማድረግ እንደምንችል እናስባለን. ከእግዚአብሔር ተለይተን መኖር የምንችል ይመስለናል ይህም የአበባው ሽታ ከአበባው ለመለየት እንደመሞከር ነው። እግዚአብሔር ሁል ጊዜ አለ እና የህይወታችንን ቁጥጥር ለእርሱ አሳልፈን እንድንሰጥ እየጠበቀን ነው።
ራሄል ስብከቱ ለእሷ ታቅዶ የተዘጋጀ መስሎ ተሰማት…ኪሩቤል ከሞተ በኃላ እግዚአብሔር የሚናገራትን ነገር ሁሉ ላለመስማት ጆሮዋን ዘጋች። የህይወቷ የበላይ ለመሆን እና ለመቆጣጠር ጣረች።ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ፣ በህይወቷ ውስጥ የተከሰቱት ክስተቶች ይህ ምን ያህል ከንቱ እንደሆነ አሳይቷታል።ግን ሌላ ምን ማድረግ ነበረባት? እሷ ፋውንዴሽን ውስጥ መልካም ነገር እየሰራች ነበር. ሰዎችን ከችግራቸው ለማላቀቅ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በስራዋ ላይ ይደገፋሉ.
ሰባኪው ስብከቱን ቀጥሏል ….
..እኛ በሕይወታችን ውስጥ ኃላፊ እንደሆንን በማሰብ፣እንዴት ራሳችንን እንዲህ እናቆስላለን? በእውነቱ እኛ የራሳችን ህይወት ሀለቆች አይደለንም…አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር የራሳችንን መንገድ ለማወቅ እንድንችል በራሳችን መንገድ እንድንሄድ ይፈቅድልናል። ነፍሶች ወደርሱ እስኪጠጉ ድረስ ዕረፍት የላቸውም። ስለዚህ አሁን በመዝሙራዊው ዳዊት መዝሙረ 139፡6 ላይ ባለው የእግዚያብሄር ቃል የእለቱን ትምህርታችንን እንዘጋለን፡፡
‹‹በሰማይእና በምድር በባሕር እና በጥልቆች ሁሉ፣እግዚያብሄር የወደደውን ሁሉ አደረገ ..
….››ቃላቱ በህንፃው ውስጥ ተስተጋብተው በራሔል ልብ ውስጥ አረፉ። ለእግዚአብሔር ጀርባዋን ሰጥታው ነበር። አላመነችበትም ነበር። እና ይህ ሁሉ ቢሆንም ፣ በእሷ ውስጥ ግልፅ የሆነ እረፍት አልነበረም…. ያለ ምንም ጥርጣሬ፣ እግዚአብሔር የለም ማለት አልቻለችም።አዎ ለአመታት በኪሩቤል ሞት አዝናለች… አዎ…እሱን እንዴት እንዳጣችው በማሰብ አሁንም ለብስጭት እና ተስፋ ለመቁረጥ ተጋላጭ እንድትሆን አድርጓታል። አሁንም አምላክ ለምን ጸሎቷን እንዳልመለሰላት ግራ ተጋብታለች። ለዚያ መልሱን አላወቀችም። ነገር ግን በሕይወቷ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት እንዲህ በቀላሉ መካድ እንደማትችል ታውቃለች። ዛሬ የእሱ የተለመደ መነካካት ተሰምቷታል። የመጨረሻው መዝሙር ሲዘመር ፀጋን አቀፈቻትና ከማንም ሰው በመራቅ ከምዕመናኑ መሀከል ሾልካ ወጣች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤60👍7
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡
‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች.. ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣ ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።
ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች… ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››
‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››
‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››
ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡
‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡
‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡
‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡
‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ ፈልጌ ነበር.››
‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ ወንበርና ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡
‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡
ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡
በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ, ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።
‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››
‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››
‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።
‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››
‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።
‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።
የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡
‹‹በቂ ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው… ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።
ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ
‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው የፈቀደልኝ የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡
‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች.. ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣ ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።
ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች… ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››
‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››
‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››
ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡
‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡
‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡
‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡
‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ ፈልጌ ነበር.››
‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ ወንበርና ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡
‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡
ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡
በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ, ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።
‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››
‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››
‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።
‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››
‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።
‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።
የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡
‹‹በቂ ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው… ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።
ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ
‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው የፈቀደልኝ የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
❤65👍4👏1
እርግጠኛ ያልሆነውን ስሜት ወደ ጎን ገሸሽ አድርጎ በአዘኔታ ስሜት እጇን ያዛት።የሚገርመው ጣቶቿን ዘርግታለት እንደፈለገው እንዲያፍተለትላት ፈቀደችለት… ፣ እና ቀስ በቀስ በልቡ ውስጥ ለእሷ ሚሆን ቦታ ሲከፈት ታወቀው።
ኤልያስ ቀና ብሎ ተመለከታት …አንድ የእንባ ዘለላ በጉንጯ ላይ ሲንሸራተት በማየቱ ተገረመ። ወደራሱ አስጠጋትና ቀስ ብሎ ጠረገላት።
‹‹ይቅርታ››አለች በሹክሹክታ። ወደ ኋላ ዞራ ተመለከተች። እጇን ከእጁ አውጥታ ወደ ፀጋ አመራች።በእነዚህ ጥቂት ጊዜያት ጥቂት ሰዎች እንዳዩ የጠረጠረውን የራሷን ክፍል እንዳሳየችው ተረዳ።
ራሄል ኩኪሶችን በሰሀን አድርጋ ስታቀራርብ ዔሊ ቡናውን ቀዳ ፡፡የተለያዩ ስሜቶች በእሱ ውስጥ እየተሽከረከሩ ነበር። ስለ ኪሩቤል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ስለ ራሄል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ቢሆንም ግን የእርሷን መመሪያ መከተል እንዳለበት ያውቅ ነበር….ለዚህ ነው የበለጠ እንድታወራ ሊጎተጉታት ያልፈቀደው፡፡
‹‹ቡናው ጥሩ መዓዛ አለው››አላት፡፡
‹‹አመሰግናለው››አለችና .. ለፀጋ ኩኪስ ሰጥታ ብርጭቆዋን ወሰደች።በሻይ እየነከረች ታጎርሳት ጀመር፡፡
ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተል ከቆየ በኃላ‹‹ጥሩ እናት ይወጣሻል ››አላት
‹‹..ቢያንስ እየተማርኩ ነው››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹አዎ…የሚገርመው እኮ እናትነት ቀድመሽ ተምረሽ ካወቅሽ በኃላ አይደለም እናት የምትሆኚው….በድንገት እናት ትሆኚያለሽ ከዛ የግድሽን ትማሪያለሽ…ይሄ አንቺን ብቻ ሳይሆን ሁሉም እናቶች የሚያጋጥማቸው ነው፡፡አይደለም ለመጀመሪያ ጊዜ ልጅ ስትወልጂ ይቅርና….የመጀመሪያ ልጅ ከሁለተኛ ልጅ..ሁለተኛው ልጅ ከሶስተኛው ልጅ በፀባይ ..በሚወዳቸውና በሚጠላቸው ነገሮች በብዙ ብዙ ነገር ስለሚለያይ በእያንዳንዱ ልጅ በማሳደግ ሄደት ውስጥ የተለየ አይነት ልምድ ነው የምታገኚው… ››
‹‹አረ ከባድ ነው…..አይደለም ሁለት ሶስት አንዱም ከባድ ነው›››አለችው፡፡
ጥቂት ተጨማሪ ጥያቄዎችን ጠየቃት እና ንግግራቸው በቀላሉ ከስራ ወደ ቤተሰብ ተዛወረ።
እሱም ልክ እንደ እሷ ያደገው በክርስቲያን ቤት ውስጥ እንደሆነ ነገራት። እንደ እሱ፣ እሷም ምንም አይነት የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያዎች አልነበራትም።ስለ ወላጆቹ ጠየቀችው።ስለ አሳዳጊዎቹ ነገራት። እና ስለስጋ ወላጆቹም አወራት፡፡ .
‹‹አሁንም ታስታውሳቸዋለህ?››ራሄል ጠየቀች፣ የፀጋን እጆች እርጥብ በሆነ ፎጣ ለመጥረግ ጎንበስ አለች።
‹‹በመኪና አደጋ ሲሞቱ ስድስት አመቴ ነበር:: ዔሊ በእጁ ጀርባ ላይ የተጋደመውን ጠባሳ ተመለከተ።‹‹እኔ ብቸኛ ልጅ ነበርኩ እና በሕይወት የተረፈኩት እኔ ብቻ ነኝ.››
‹‹ስለዚህ አንተም ሀዘንን ታውቃታለህ ማለትነው.››
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር››
‹‹አዎ። ግን እነሱ የስጋ ወላጆችህ ስለሆኑ ትዝታቸው እና ሀዘኑ ከውስጥህ መቼም አይጠፋም ።››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ››
‹‹እናቴና አባቴ ይህችን ትንሽ ልጅ በጣም እንደሚወዷት አውቃለሁ፣ ነገር ግን እሷ አሁንም አንዳንድ ታሪክ ያላት ሰው ሆና ነው ወደ እነርሱ የመጣቸው…ይታይህ የስድስት አመት ልጅ ሆና ቢሆን ኖሮ በጣም ጠንካራ ትዝታ ይኖራት ነበር ብዬ አስባለሁ። ››
‹‹እኔ ግን ወላጆቼ ሞተዋል. ትዝታዎች ብቻ ናቸው የቀሩኝ…. ለማንኛውም ስለግንኙነት ብዙ ነገር አላውቅም ትያለሽ ግን ሌላ የማስበውን ነገር ሰጥተሺኛል፡፡: ትርጉም ያለው ነገር ነው የተናገርሽው:››
ፈገግ አለችለት…ፈገግታዋ ሳበው። የሆነ ነገር ልትለው አፏን ስትከፍት የእሱ ስልክ ጠራ….
‹‹ይቅርታ ይህ ሆስፒታል ስልክ ነው…ማንሳት አለብኝ። ››
አነሳና አናገረ..ዘጋውና ወደእሷ ዞረ፡፡
‹‹አዝናለው ጥያችሁ ልሄድ ነው…..ችግር አጋጥሞት መግባት ያልቻለ ዶክተር አለ…የእሱን ተራ መሸፈን አለብኝ…እንዲህ ከእናንተ ጋር እደምገናኝ ስላላወቅኩ ቀድሜ ነው ቃል የገባሁለት››
‹‹አረ ችግር የለውም ..እስከአሁን አብረኸን ስለቆየህ በጣም ደስ ብሎናል››አለችው
ሁለቱንም ተሰናበተ እና ሄደ…ራሄል ከእይታዋ እስኪሰወር በትኩረት እያየችው ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ኤልያስ ቀና ብሎ ተመለከታት …አንድ የእንባ ዘለላ በጉንጯ ላይ ሲንሸራተት በማየቱ ተገረመ። ወደራሱ አስጠጋትና ቀስ ብሎ ጠረገላት።
‹‹ይቅርታ››አለች በሹክሹክታ። ወደ ኋላ ዞራ ተመለከተች። እጇን ከእጁ አውጥታ ወደ ፀጋ አመራች።በእነዚህ ጥቂት ጊዜያት ጥቂት ሰዎች እንዳዩ የጠረጠረውን የራሷን ክፍል እንዳሳየችው ተረዳ።
ራሄል ኩኪሶችን በሰሀን አድርጋ ስታቀራርብ ዔሊ ቡናውን ቀዳ ፡፡የተለያዩ ስሜቶች በእሱ ውስጥ እየተሽከረከሩ ነበር። ስለ ኪሩቤል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ስለ ራሄል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ቢሆንም ግን የእርሷን መመሪያ መከተል እንዳለበት ያውቅ ነበር….ለዚህ ነው የበለጠ እንድታወራ ሊጎተጉታት ያልፈቀደው፡፡
‹‹ቡናው ጥሩ መዓዛ አለው››አላት፡፡
‹‹አመሰግናለው››አለችና .. ለፀጋ ኩኪስ ሰጥታ ብርጭቆዋን ወሰደች።በሻይ እየነከረች ታጎርሳት ጀመር፡፡
ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተል ከቆየ በኃላ‹‹ጥሩ እናት ይወጣሻል ››አላት
‹‹..ቢያንስ እየተማርኩ ነው››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹አዎ…የሚገርመው እኮ እናትነት ቀድመሽ ተምረሽ ካወቅሽ በኃላ አይደለም እናት የምትሆኚው….በድንገት እናት ትሆኚያለሽ ከዛ የግድሽን ትማሪያለሽ…ይሄ አንቺን ብቻ ሳይሆን ሁሉም እናቶች የሚያጋጥማቸው ነው፡፡አይደለም ለመጀመሪያ ጊዜ ልጅ ስትወልጂ ይቅርና….የመጀመሪያ ልጅ ከሁለተኛ ልጅ..ሁለተኛው ልጅ ከሶስተኛው ልጅ በፀባይ ..በሚወዳቸውና በሚጠላቸው ነገሮች በብዙ ብዙ ነገር ስለሚለያይ በእያንዳንዱ ልጅ በማሳደግ ሄደት ውስጥ የተለየ አይነት ልምድ ነው የምታገኚው… ››
‹‹አረ ከባድ ነው…..አይደለም ሁለት ሶስት አንዱም ከባድ ነው›››አለችው፡፡
ጥቂት ተጨማሪ ጥያቄዎችን ጠየቃት እና ንግግራቸው በቀላሉ ከስራ ወደ ቤተሰብ ተዛወረ።
እሱም ልክ እንደ እሷ ያደገው በክርስቲያን ቤት ውስጥ እንደሆነ ነገራት። እንደ እሱ፣ እሷም ምንም አይነት የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያዎች አልነበራትም።ስለ ወላጆቹ ጠየቀችው።ስለ አሳዳጊዎቹ ነገራት። እና ስለስጋ ወላጆቹም አወራት፡፡ .
‹‹አሁንም ታስታውሳቸዋለህ?››ራሄል ጠየቀች፣ የፀጋን እጆች እርጥብ በሆነ ፎጣ ለመጥረግ ጎንበስ አለች።
‹‹በመኪና አደጋ ሲሞቱ ስድስት አመቴ ነበር:: ዔሊ በእጁ ጀርባ ላይ የተጋደመውን ጠባሳ ተመለከተ።‹‹እኔ ብቸኛ ልጅ ነበርኩ እና በሕይወት የተረፈኩት እኔ ብቻ ነኝ.››
‹‹ስለዚህ አንተም ሀዘንን ታውቃታለህ ማለትነው.››
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር››
‹‹አዎ። ግን እነሱ የስጋ ወላጆችህ ስለሆኑ ትዝታቸው እና ሀዘኑ ከውስጥህ መቼም አይጠፋም ።››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ››
‹‹እናቴና አባቴ ይህችን ትንሽ ልጅ በጣም እንደሚወዷት አውቃለሁ፣ ነገር ግን እሷ አሁንም አንዳንድ ታሪክ ያላት ሰው ሆና ነው ወደ እነርሱ የመጣቸው…ይታይህ የስድስት አመት ልጅ ሆና ቢሆን ኖሮ በጣም ጠንካራ ትዝታ ይኖራት ነበር ብዬ አስባለሁ። ››
‹‹እኔ ግን ወላጆቼ ሞተዋል. ትዝታዎች ብቻ ናቸው የቀሩኝ…. ለማንኛውም ስለግንኙነት ብዙ ነገር አላውቅም ትያለሽ ግን ሌላ የማስበውን ነገር ሰጥተሺኛል፡፡: ትርጉም ያለው ነገር ነው የተናገርሽው:››
ፈገግ አለችለት…ፈገግታዋ ሳበው። የሆነ ነገር ልትለው አፏን ስትከፍት የእሱ ስልክ ጠራ….
‹‹ይቅርታ ይህ ሆስፒታል ስልክ ነው…ማንሳት አለብኝ። ››
አነሳና አናገረ..ዘጋውና ወደእሷ ዞረ፡፡
‹‹አዝናለው ጥያችሁ ልሄድ ነው…..ችግር አጋጥሞት መግባት ያልቻለ ዶክተር አለ…የእሱን ተራ መሸፈን አለብኝ…እንዲህ ከእናንተ ጋር እደምገናኝ ስላላወቅኩ ቀድሜ ነው ቃል የገባሁለት››
‹‹አረ ችግር የለውም ..እስከአሁን አብረኸን ስለቆየህ በጣም ደስ ብሎናል››አለችው
ሁለቱንም ተሰናበተ እና ሄደ…ራሄል ከእይታዋ እስኪሰወር በትኩረት እያየችው ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤65👍5👏1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
___
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው ጠቀለለቻት።
ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡ ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡
በዛው ቅፅበት የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…
‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር ኤልያስ ነበረ፡፡
ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››
‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት
‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››
‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡
ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››
‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››
‹‹እሺ ይህችን ልጅ ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››
‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡
ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡
የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››
‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››
ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››
‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው። ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።
መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።
‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
___
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው ጠቀለለቻት።
ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡ ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡
በዛው ቅፅበት የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…
‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር ኤልያስ ነበረ፡፡
ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››
‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት
‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››
‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡
ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››
‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››
‹‹እሺ ይህችን ልጅ ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››
‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡
ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡
የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››
‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››
ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››
‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው። ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።
መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።
‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
❤55👍2👏1
ራሄል በትህትና ፈገግ ብላ የዘረጋችውን እጅ ጨበጠችና ወደኃላዋ ዞር ብላ‹‹ ዶ/ር ዔሊያስ ይባላል…እሷ ደግሞ እህቴ ነች››በማለት አስተዋወቀቻቸው፡፡ቀጠለችናም‹‹ከሁለት ሳምንት በፊት እናታችን ወድቃ እግሯን ተሰብሮ ህክምና ላይ ስላለች እህቴን ፀጋን እየተንከባከብኳት ነው…ዶ/ር ደግሞ የእሷ ሀኪም ነው …።››
ፀጋ ለታላቅዋ ሴት ብሩህ ፈገግታ ሰጠቻት ‹‹እንዴት የምታምር ልጅ ነች… ወላጆችሽ ትንሽ ልጅ እያሳደጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ። ሴሬብራል ፓልሲ አለባት አይደል?››
‹‹አዎ ››ስትል መለሰች ራሄል።
‹‹ልዩ ፍላጎት ያለው ህፃን በማደጎ ለመውሰድ መወሰናቸውን ስሰማ አእምሮአቸውን የሳቱ መስሎኝ ነበር፣ነገር ግን አሁን ሳያት ጠንካራ የጤና እክል ቢኖርባትም ለምን እርሷን ለማሳደግ እንደወሰኑ አሁን ገባኝ.. ።ተቀመጡ.. ምን ይምጣ ቡና? ጣፋጭ ሻይ? ለትንሿ ሴት ጭማቂ?››
ሁሉም ወንበር ይዘው እየተቀመጡ‹‹እኔ ሻይ እጠጣለሁ እና ለፀጋ የአፕል ወይም የብርቱካን ጭማቂ ብታገኝ ትደሰታለች››አለች ፡፡ኤሊያስ ሁለቱንም አልተቀበለም።ወይዘሮዋ ትዕዛዙን ለሰራተኞቾ አስተላለፈች፡፡
ያዘዙት መጠጥ መጣላቸው…ኤልያስ ጭማቂውን ወስዶ ፀጋን ያጠጣት ጀመር፡፡
ራሄል ከኤሊያስ ጸጋን ልትቀበለው ስትለ‹‹ችግር የለውም እኔ አጠጣታለው…እንደውም ግቢውን ዞር ዞር እያልን እያየን ጭማቂያችንን ብንጠጣ ጥሩ ይመስለኛል…ችግር የለውም አይደል ወ.ሮ ላምሮት?፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም …እንደፈለጋችሁ ዘና በሉ››
ተነሳና በአንድ እጁ ጭማቂውን በሌላ እጁ ፀጋን ይዞ ከእነሱ እራቅ ብሎ ወደ አትክልት ስፍራው በጥልቀት ገባ…
ወ.ሮ ላምሮት ከፀጋ ጋር አይኗቾ ተንከራተቱ ..ከዛ ድንገት መናገር ጀመረች‹‹እኛ ..ማለቴ እኔና ባሌ ልጆች አልነበረንም። ››በማለት ትካዜ ውስጥ ገባች፡፡
ራሄል እንደመደነጋገር አላትና ‹‹አንድ ጊዜ ልጅ ነበረሽ አይደል?›› ስትል ድንገት ከአፏ አመለጣትና ጠየቀቻት፡፡
‹‹አዎ ነበረኝ…ገና የሶስት አመት ልጅ ነበር። ከዚህች ከአንቺ እህት ትንሽ ይበልጣል››አለች
‹‹ምን ሆነ?›› ራሄል ጠየቀች፣
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር. ረጅም ጊዜ.… ሊገለጽ የማይችል በሽታ ነበረበት..ድንገት ታመመና ሞተብኝ…ምንም ልረዳው አልቻልኩም ››
ራሄልን በሀዘን ፈገግታ ተመለከተቻት።
‹‹ ይገባኛል›› አለች ራሄል ። የራሷን ህመም በወ.ሮዋ አይን ውስጥ ማየት ቻለች። ፡፡
ወ.ሮ ላምሮት በጣቷ ላይ ያለውን ቀለበት ማዞር በመቀጠል. ‹‹እንደገና ሞክረን ነበር… ግን አልተሳካልንም..አንድን ሰው መውደድ ሁልጊዜ እድል ነው. ግን ደግሞ ህመም ሊያመጣ እንደሚችልም ቀድመን አውቀን መዘጋጀት አለብን››
‹‹ለማንኛውም፣ ያ ያለፈው ታሪክ ነው››አለች ወይዘሮዋ፣ እጆቿን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች፣ ቀለበቷ መስታወቱ ላይ አስተጋባ። ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ለመወያየት ወደዚህ እንዳልመጣሽ እርግጠኛ ነኝ። ››ወደ ራሄል መለስ ብላ ተመለከተች፣
ቀጠለች‹‹ፋውንዴሽኑ በዚህ አመት ከእኔ የሚያገኘውን ገንዘብ ምን አይነት ቁምነገር ላይ ለማዋል እንዳሰበ ወይንም ለየትኞቹ የበጓ አድራጎት ድርጅቶች ለማከፋፈል እቅድ እንዳወጣና ….ብሩን ካከፋፈለ ብኃላ አፈፃፀማቸውን እንዴት መከታተል እንዳሰብ እንድታብራሪልኝ ነው የምፈልገው››አለቻት፡፡
ራሄል‹‹ጥሩ›› ብላ የተዘጋጀችበትን ወረቀት አውጥታ አንድ በአንድ እየተነተነች ለ30ደቂቃ ያህል አብራራችላት፡፡
‹‹ጥሩ ነው..ማለቴ ስራችሁ በደንብ የታቀደበት ይመስላል..ግን የበጎ አድራጎት ድርጅቷችን ዝርዝር ስትገልጪልን በቀደም ያንቺ ሰራተኛ እዚህ መታ ካስረዳችኝ ጋር ልዩነት ያለው መሰለን፡፡እሷ በዚህ አመት ስለተመሰረተው ጎህ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት አስረድታኝ ነበር..አብዛኛውን ብር ለዛ ድርጅት ልትሰጡ እንዳሰባችው ነበር የተነገረኝ፡፡››
‹‹ጎህ!!››ራሄል ድንግርግሯ ወጣ…እደዚህ አይነት በጎ አድራጎት ድርጅት መኖሩንም ዛሬ መስማቷ ነው፡፡
‹‹ሮቤል ነው አይደል…ምን ነገረሽ?››ፊቷን አኳሳትራ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ.. ንግግሩን ሁሉ ያደረገችው ወጣቷ ሴት ነበረች። እዚህ በየቦታው የተጣሉ ህጻናትን የሚሰበሰቡ እና እነሱን በእንክብካቤ የሚያሳድጉ ድርጅት በመሆናቸው ሀሳብን ወድጄዋለሁ።››
ራሄል ‹‹ይህ ቡድን በእኔ ተመርምሮ አያውቅም››ንዴቷ እየጨመረ ሄደ።
‹‹ምን ማለትሽ ነው?››ወ.ሮ ላምሮት አሁን ግራ የተጋባች ይመስላል።
‹‹የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ወይም ገንዘባቸውን ለማሰባሰብ የሚያመለክቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በትክክለኛው መንገድ ስራቸውን እንደሚሰሩ እና ከፍተኛ የአስተዳደር ወጪዎችን እንደማይከፍሉ ቀድመን እናረጋግጣለን። አንዳንድ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች አሉ እስከ ሰማንያ በመቶ የአስተዳደር ወጪዎችን የሚከፍሉ በመሆናቸው ለተረጂዎች የሚደርሰው እርዳታ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ፡፡ለማንኛውም ይሁንታ አልሰጧሻትም አይደል?››
‹‹አላደረግኩትም።ከንቺ ጋር ቀድሜ ልነጋገር ብዬ እንጂ ላደርገው ፈልጌ ነበር።››
ራሄል በእፎይታ ተነፈሰች..በገዛ ረዳቷ ተጭበርብራ የአገር መሳቂያ ሆና ነበር፡፡
‹‹ስላላደረግሽው ደስ ብሎኛል፡ እኔ በግሌ ያልመረመርኩትን ማንኛውንም ድርጅት በፍጹም እንደማልመክርሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ። እና ይሄ ትልቅ የገንዘብ ጉድጓድ ነው፤ብሩን ካንቺ ስንረከብ ኃላፊነትን ነው አብረን የምንረከበው..ለእያንዷንዷ ሳንቲም ተጠያቂዋ እኔ ነኝ። ››
‹‹ልጅቷ ለአንቺ ነው የምትሰራው አይደል?››
‹‹አዎ ረዳቴ ነች ወይም ነበርች››ራሄል ረጅም ትንፋሽ ወስዳ የጣቶቿን ጫፍ እርስ በርሳቸው አሻሸች። ከቀናት በፊት አንድ ሰው ኮምፒተሯን ሰብሮ ሊገባ ሲመሞከር እንደነበር አስተውላለች ፡፡ በዛን ቀን በአካባቢው ያለችው ብቸኛዋ ሰው ሎዛ ነበረች።አሁን ነው ያሳታወሰችው፡፡
‹‹ይህን እንዴት ማድረግ ቻለች? ራሔል በሮቤል ተጠራጥራው ነበር..ሎዛን ግን በፍፅም እንዲህ ታደርጋለች ብላ ግምቱ አልነበራትም ። በሎዛ የክህደት ሀሳብ ትንሽ የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰማት… ወንበሯ ተደገፈች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ፀጋ ለታላቅዋ ሴት ብሩህ ፈገግታ ሰጠቻት ‹‹እንዴት የምታምር ልጅ ነች… ወላጆችሽ ትንሽ ልጅ እያሳደጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ። ሴሬብራል ፓልሲ አለባት አይደል?››
‹‹አዎ ››ስትል መለሰች ራሄል።
‹‹ልዩ ፍላጎት ያለው ህፃን በማደጎ ለመውሰድ መወሰናቸውን ስሰማ አእምሮአቸውን የሳቱ መስሎኝ ነበር፣ነገር ግን አሁን ሳያት ጠንካራ የጤና እክል ቢኖርባትም ለምን እርሷን ለማሳደግ እንደወሰኑ አሁን ገባኝ.. ።ተቀመጡ.. ምን ይምጣ ቡና? ጣፋጭ ሻይ? ለትንሿ ሴት ጭማቂ?››
ሁሉም ወንበር ይዘው እየተቀመጡ‹‹እኔ ሻይ እጠጣለሁ እና ለፀጋ የአፕል ወይም የብርቱካን ጭማቂ ብታገኝ ትደሰታለች››አለች ፡፡ኤሊያስ ሁለቱንም አልተቀበለም።ወይዘሮዋ ትዕዛዙን ለሰራተኞቾ አስተላለፈች፡፡
ያዘዙት መጠጥ መጣላቸው…ኤልያስ ጭማቂውን ወስዶ ፀጋን ያጠጣት ጀመር፡፡
ራሄል ከኤሊያስ ጸጋን ልትቀበለው ስትለ‹‹ችግር የለውም እኔ አጠጣታለው…እንደውም ግቢውን ዞር ዞር እያልን እያየን ጭማቂያችንን ብንጠጣ ጥሩ ይመስለኛል…ችግር የለውም አይደል ወ.ሮ ላምሮት?፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም …እንደፈለጋችሁ ዘና በሉ››
ተነሳና በአንድ እጁ ጭማቂውን በሌላ እጁ ፀጋን ይዞ ከእነሱ እራቅ ብሎ ወደ አትክልት ስፍራው በጥልቀት ገባ…
ወ.ሮ ላምሮት ከፀጋ ጋር አይኗቾ ተንከራተቱ ..ከዛ ድንገት መናገር ጀመረች‹‹እኛ ..ማለቴ እኔና ባሌ ልጆች አልነበረንም። ››በማለት ትካዜ ውስጥ ገባች፡፡
ራሄል እንደመደነጋገር አላትና ‹‹አንድ ጊዜ ልጅ ነበረሽ አይደል?›› ስትል ድንገት ከአፏ አመለጣትና ጠየቀቻት፡፡
‹‹አዎ ነበረኝ…ገና የሶስት አመት ልጅ ነበር። ከዚህች ከአንቺ እህት ትንሽ ይበልጣል››አለች
‹‹ምን ሆነ?›› ራሄል ጠየቀች፣
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር. ረጅም ጊዜ.… ሊገለጽ የማይችል በሽታ ነበረበት..ድንገት ታመመና ሞተብኝ…ምንም ልረዳው አልቻልኩም ››
ራሄልን በሀዘን ፈገግታ ተመለከተቻት።
‹‹ ይገባኛል›› አለች ራሄል ። የራሷን ህመም በወ.ሮዋ አይን ውስጥ ማየት ቻለች። ፡፡
ወ.ሮ ላምሮት በጣቷ ላይ ያለውን ቀለበት ማዞር በመቀጠል. ‹‹እንደገና ሞክረን ነበር… ግን አልተሳካልንም..አንድን ሰው መውደድ ሁልጊዜ እድል ነው. ግን ደግሞ ህመም ሊያመጣ እንደሚችልም ቀድመን አውቀን መዘጋጀት አለብን››
‹‹ለማንኛውም፣ ያ ያለፈው ታሪክ ነው››አለች ወይዘሮዋ፣ እጆቿን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች፣ ቀለበቷ መስታወቱ ላይ አስተጋባ። ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ለመወያየት ወደዚህ እንዳልመጣሽ እርግጠኛ ነኝ። ››ወደ ራሄል መለስ ብላ ተመለከተች፣
ቀጠለች‹‹ፋውንዴሽኑ በዚህ አመት ከእኔ የሚያገኘውን ገንዘብ ምን አይነት ቁምነገር ላይ ለማዋል እንዳሰበ ወይንም ለየትኞቹ የበጓ አድራጎት ድርጅቶች ለማከፋፈል እቅድ እንዳወጣና ….ብሩን ካከፋፈለ ብኃላ አፈፃፀማቸውን እንዴት መከታተል እንዳሰብ እንድታብራሪልኝ ነው የምፈልገው››አለቻት፡፡
ራሄል‹‹ጥሩ›› ብላ የተዘጋጀችበትን ወረቀት አውጥታ አንድ በአንድ እየተነተነች ለ30ደቂቃ ያህል አብራራችላት፡፡
‹‹ጥሩ ነው..ማለቴ ስራችሁ በደንብ የታቀደበት ይመስላል..ግን የበጎ አድራጎት ድርጅቷችን ዝርዝር ስትገልጪልን በቀደም ያንቺ ሰራተኛ እዚህ መታ ካስረዳችኝ ጋር ልዩነት ያለው መሰለን፡፡እሷ በዚህ አመት ስለተመሰረተው ጎህ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት አስረድታኝ ነበር..አብዛኛውን ብር ለዛ ድርጅት ልትሰጡ እንዳሰባችው ነበር የተነገረኝ፡፡››
‹‹ጎህ!!››ራሄል ድንግርግሯ ወጣ…እደዚህ አይነት በጎ አድራጎት ድርጅት መኖሩንም ዛሬ መስማቷ ነው፡፡
‹‹ሮቤል ነው አይደል…ምን ነገረሽ?››ፊቷን አኳሳትራ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ.. ንግግሩን ሁሉ ያደረገችው ወጣቷ ሴት ነበረች። እዚህ በየቦታው የተጣሉ ህጻናትን የሚሰበሰቡ እና እነሱን በእንክብካቤ የሚያሳድጉ ድርጅት በመሆናቸው ሀሳብን ወድጄዋለሁ።››
ራሄል ‹‹ይህ ቡድን በእኔ ተመርምሮ አያውቅም››ንዴቷ እየጨመረ ሄደ።
‹‹ምን ማለትሽ ነው?››ወ.ሮ ላምሮት አሁን ግራ የተጋባች ይመስላል።
‹‹የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ወይም ገንዘባቸውን ለማሰባሰብ የሚያመለክቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በትክክለኛው መንገድ ስራቸውን እንደሚሰሩ እና ከፍተኛ የአስተዳደር ወጪዎችን እንደማይከፍሉ ቀድመን እናረጋግጣለን። አንዳንድ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች አሉ እስከ ሰማንያ በመቶ የአስተዳደር ወጪዎችን የሚከፍሉ በመሆናቸው ለተረጂዎች የሚደርሰው እርዳታ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ፡፡ለማንኛውም ይሁንታ አልሰጧሻትም አይደል?››
‹‹አላደረግኩትም።ከንቺ ጋር ቀድሜ ልነጋገር ብዬ እንጂ ላደርገው ፈልጌ ነበር።››
ራሄል በእፎይታ ተነፈሰች..በገዛ ረዳቷ ተጭበርብራ የአገር መሳቂያ ሆና ነበር፡፡
‹‹ስላላደረግሽው ደስ ብሎኛል፡ እኔ በግሌ ያልመረመርኩትን ማንኛውንም ድርጅት በፍጹም እንደማልመክርሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ። እና ይሄ ትልቅ የገንዘብ ጉድጓድ ነው፤ብሩን ካንቺ ስንረከብ ኃላፊነትን ነው አብረን የምንረከበው..ለእያንዷንዷ ሳንቲም ተጠያቂዋ እኔ ነኝ። ››
‹‹ልጅቷ ለአንቺ ነው የምትሰራው አይደል?››
‹‹አዎ ረዳቴ ነች ወይም ነበርች››ራሄል ረጅም ትንፋሽ ወስዳ የጣቶቿን ጫፍ እርስ በርሳቸው አሻሸች። ከቀናት በፊት አንድ ሰው ኮምፒተሯን ሰብሮ ሊገባ ሲመሞከር እንደነበር አስተውላለች ፡፡ በዛን ቀን በአካባቢው ያለችው ብቸኛዋ ሰው ሎዛ ነበረች።አሁን ነው ያሳታወሰችው፡፡
‹‹ይህን እንዴት ማድረግ ቻለች? ራሔል በሮቤል ተጠራጥራው ነበር..ሎዛን ግን በፍፅም እንዲህ ታደርጋለች ብላ ግምቱ አልነበራትም ። በሎዛ የክህደት ሀሳብ ትንሽ የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰማት… ወንበሯ ተደገፈች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤57👍11😱3
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ቤት እንደተመለሱ ቀጥታ ወደራሄል ወላጇቾ ቤት ነው የሄዱት፡፡ኤልያስ ቤት ድረስ አብሯቸው የመጣው በሁለት ምክንያት ነው…አንድም ሊሸኛቸው ሲሆን ሌላው ግን ጥዋት ከቤት ወጥቶ አብሯቸው ሲሄድ ሞተር ሳይክሉን እዛው ጥሎ ስለነበረው የሄደው እሱን ለመውሰድ ነው…"ካለበለዚይ ጥዋት ወደስራ ለመግባት ታኪሲ ፍለጋ መጋፋት ሊጠበቅበት ነው…ያ ደግሞ በጣም የሚጠላው ነገር ነው፡፡
ደርሰው ራሄል መኪናውን ፓርክ አድርጋ እንዳቆመች እሱ ፈጠን ብሎ ወረደና ፀጋን አንስቶ አቀፋት..ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዷት ስለነበረ ሲያቅፍት ልጥፍ አለችበት፡፡ራሄል ቦርሳውን አንስታ አንጠለጠለችና ተከተለቻቸው እና ወደ ግዙፍ ቤት ተከታለው ሲገቡ ጥዋት ተሰምቷት የነበረ ስሜት ተመልሷ ተሰማት…ባሏ… ተወዳጅ ልጇን አቅፎ ወደቤት ሲገቡ….ሀሳቡ የደስታ ውስጧ በደስታ ስሜት እንዲጥለቀለቅ ስላደረጋት ‹‹እንዴት ደስ ይላል››ስትል በለሆሳሳ አንሾካሾከች፡፡ከፊት ቀደመችና ሳሎኑን ሰንጥቃ እየመራች ወደፀጋ ክፍል ይዛው ሄደች… ቶሎ ብላ ብርድ ልብሱን ገለጠችለት…ቀስ ብሎ አስተኛትና ተጋግዘው አለባበሳትና ቆመ…ተከትላው ቆመች…በመሀከላቸው ያለው ርቀት ከአንድሜትር አይበልጥም…አንደኛው ሌለኛው ላይ አፍጥጧል….በሚገርም ሁኔታ የትንፋሽ ማጠር አጋጠማት. …ቀስ እያለ ተጠጋትና እጇቹን በወገቧ ላይ አሳረፈ፡፡
ውርር የሚያደርግ ጥሩ ስሜት ተሰማት…ከዛ በምን ፍጥነት እንደሆነ ሳታውቅ ከንፈሮቹ በእሷ ከንፈር ላይ አረፉ …የራሄል አይኖች ተዘጉ፤ እና ለአፍታ ድንጋጤ ተሰማት ፣ እጆቹ በወገቧ ዙሪያ ተጠመጠሙባት እና ወደራሱ ጎትቶ አስጠጋት። ራሄል ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ በቀጣይ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር የማወቅ ጉጉት ተሰማት። የበለጠ ልትለጠፍበትና ልትደገፍበት ፈቀደች፡፡ ‹‹ይህ ጥሩ ሥነ ምግባር አይደለም?››በውስጧ ነበር ያሰበችው… በድንገት የከበደውን ከባቢ አየር ማቅለል ፈለገች። ለብዙ ዓመታት ሳትወድቅ ከቆየችበት ቦታ ለመመለስ ተፍጨረጨረች።
‹‹የእህቴን ሐኪም መሳም ?››ከእቅፉ ሳትወጣ የሹክሹክታ ድምፅ አሰማች።ወደፊቷ የተደፋውን ፀጉሯን ወደኃላ በመመለስ አስተካከለላት፡፡ከዚያም , ቀስ ብሎ ከከንፈሯም ከአካሏ ተላቀቀ እና እራቅ አለ።
‹‹ ፀጋ ቅሬታ እንደማታቀርብ አምናለው››አለችና ዓይኗን በእፍረት ደፍች፡፡ ለእሱ ያላትን መስህብ በውስጧ መቅበር እስከቻለች ድረስ፣ እራሷን ከእሱ ለይታ ማቆየት እስከቻለች ድረስ፣ እነዚህን አዳዲስ እና አደገኛ ስሜቶች መቋቋም እንደምትችል ታስብ ነበር።አሁን ግን?በጣም ለረጅም ጊዜ የናፈቀችውን ነገር ቀምሳለች። ከንፈሯ ላይ መች ተጠግቶ እንደተጣበቀባት እንኳን አላወቀችውም። ፍቃዷን እና ሙሉ ስሜቷን ለዚህ ሰው እስክትሰጥ ቅፅበት ድረስ ልቧን በኪሩቤል የመቃብር ቦታ ለዘመናት ቀብራው ነበር፡፡ በደረሰባት ኪሳራ ተበሳጭታ ስለነበረ ራሷን ዳግመኛ እንደዚህ ላለ ሁኔታ ለማጋለጠ ፈፅሞ እንደማትፈቅድ ቃል ገብታ ነበር። አንድን ሰው በጥልቀት ለመንከባከብ መፍቀድ ራስን ነገ በድንገት ለሚመጣ ህመም ማመቻቸት እንደሆነ ህይወት አስተምራታለች።ከዛ ስቃይ ለማገገም እና እንደገና ወደህይወት ለመመለስ ዓመታት ፈጅቶባታል።
‹‹ይሄ ጉዳይ በጣም ያስፈራኛል።››አለችው፡፡
አገጯን በአውራ ጣት ዳባበሳት እና ‹‹ምንም አይደለም እኔም እፈራለሁ:: ግን ፍርሀታችንን ለማለስለስ ብዙ ጊዜ አለን››አለና ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
በረጅሙ ተነፈሰች፣ ከዚያም ፈገግ አለች።
ጭንቅላቷ ላይ ሳማትና ከዚያም በሹክሹክታ ‹‹ባዬ ራሄል››በማለት ክፍሉንም ቤቱንም ለቆ ወጣ ።ራሄል እስከሳሎን ተከተለችውና ከኋላው በሩን ዘጋች፡፡ የሞተር ሳይክሉን ድምፅ በመኪና መንገዱ ላይ ሲንደቀደቅ ሰማች። ጭንቅላቷን ቀዝቃዛው መስታወት ላይ አስደገፈች፡፡ …በድንገት መጸለይ እንዳለባት ተሰማት።‹‹ጌታ ሆይ እሱን ጠብቀው›› አለች ‹‹ራሷን ለሌላ ሰው በዚህ መንገድ እከፍታለው ብላ ፈፅሞ አስባ አታውቅም ነበር? የፀጋ የታፈነ ጩኸት ተሰማት…ራሷን ከተደገፈችበት መስታወት ቀና አደረገች እና ተንቀሳቀሰች…ከዛ ወደ ፀጋ ሄደች። እህቷን ለመከታተል ወደ ደረጃው እየሮጠች ስትሄድ፣ ቀድሞ የነበረባትን ስሜት እየሰመጠ እንደሆነ ተረዳች።
///
ዔሊያስ የቤቱን ዙሪያ ገባ ተመለከተ። ምንም ያማረ ነገር የለም። በራሱ ቤት ውስጥ በራሱ ሶፋ ላይ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም፣ አእምሮው ከአንድ በሰአት በፊትና በተለያት ሴት ላይ ተጣብቆ ነበር።ከአንድ ሰአት በፊት የሳማት ሴት አሁንም ልቡ ውስጥ እየተገላበጠች ነው።እንደዛ ያለ ድንገተኛ እርምጃ እንዲወስድ ያነሳሳው ምንድን ነበር?ቢያስብ ቢያስብ ሊገለፅለት አልቻለም፡፡
እረፍት አጥቶ ከሶፋው በመነሳት ቢንያም ወደተኛበት ክፍል ተራመደ… ሀሳቡ ዋና መኝታ ቤቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ማለቅ እንዳለበት ሊነግረው ነበር ። ነገሮች እንዳሰበው ሚሄዱ ከሆነ እና የገንዘብ እጥረት ካላጋጠመው ቤቱ በስድስት ወር ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይፈልጋል። በእቅዱ መሰረት ቤቱን ካጠናቀቀ በኃላ ቀጣዩ እቅዱ አዲስ መኪና መግዛት ነው። እና ከዚያ ምናልባት ይህንን ንፁህ እና በስርዓት የተቀነበበ ህይወቱን የምትካፍለው ሴት መፈለግ ይኖርበት ይሆናል። ከአመታ በፊት እቅዱን በዚህ መንገድ በቅደም ተከተል ሲያስቀምጥ ሁሉም ነገር እንከን የለሽ እንደሆነ እርግጠኛ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ ራሔል ከፊቱ ከመጋረጧ በፊት ነበር ።
የወንዱሙን ክፍል ለመክፈት እጄታውን ከያዘ በኃላ ሀሰቡን ቀየረ…ራሴ ተረብሼ ለምን እሱን እረብሸዋለው..በማለት ወደኃላ ተመለሰና ወደራሱ መኝታክፍል ገባ፡፡የልብሱን መሳቢያ ከፍቶ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ቤት ያመጣውን የስጋ ወላጇቹን የፎቶ ሳጥን አወጣ ፡፡ራሄል ያቀረበችለትን ሀሳብ በድጋሚ አሰበበት። ምናልባት አሳዳጊዎቹ ይሄንን የወላጆቹን ፎቶ ከእሱ ለማራቅ ጥሩ ምክንያቶች ነበሯቸው።በወላጆቹ ፊት ላይ የራሱን አሻራ ለማግኘት እየሞከረ ፎቶውን አገላብጧ ተመለከተ። አገጩን በእናቱ፣ ዓይኖቹ በአባቱ መልክ ላይ በጨረፍታ የተመለከተ መስሎት ነበር። ወይም ምናልባት ምኞት እንደዛ ስለሆነ ይሆናል፡፡ ፡፡እሱ እንደ አብዛኛው የማደጎ ልጆች ፣ስለ ወላጆቹ ይበልጥ ለመማር እና ለማወቅ ፍላጎት ነበረው ።እሱን በተመለከተ በህፃናት ማሳደጊያ ተቋሙ ውስጥ ያለው ፋይል ውድ የሆኑ ጥቂት መረጃዎችን የያዘ ሲሆን አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውቅ አድርገውታል፡፡ታዲያ ለምን መርካት አልቻለም?
ራሄል የማንቂያ ሰዓቱን ላይ ባለማመን አፈጠጠች።እንቅልፍ አልወስዳት ብሎ ከግራ ወደቀኝ እየተገላበጠች ለአንድ ሰአት ተሰቃየች… የሰዓቱ መንቀርፈፍ የዘለአለም መሰላት። ደጋግማ ከኤሊ ጋር ስታጫውተው የነበረውን ትዕይንት አዲስ እንደወጣ ተወዳጅ ፊልም ደጋግማ በምልሰት በማሰብ አጣጣመችው፣ የከንፈሮቹን ንክኪ እንደገና ተሰማት።መላልሳ ባሰበችው ቁጥር በእያንዳንዱ ትውስታ አዲስ ስሜት ይሰማት ነበር። በቀጣይ ምንድነው የሚሆነው….?እራሷን ትጠይቃለች….አእምሯዋ ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግራ መጋባት ውስጥ አሽቀንጥሮ ይጥላታል፡፡
ያለፈውን የልቧን ጭለማ ጓዝ እንዴት መልቀቅ እንዳለባት እስከአሁን አላወቀችም፣ አልደፈረችም።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ቤት እንደተመለሱ ቀጥታ ወደራሄል ወላጇቾ ቤት ነው የሄዱት፡፡ኤልያስ ቤት ድረስ አብሯቸው የመጣው በሁለት ምክንያት ነው…አንድም ሊሸኛቸው ሲሆን ሌላው ግን ጥዋት ከቤት ወጥቶ አብሯቸው ሲሄድ ሞተር ሳይክሉን እዛው ጥሎ ስለነበረው የሄደው እሱን ለመውሰድ ነው…"ካለበለዚይ ጥዋት ወደስራ ለመግባት ታኪሲ ፍለጋ መጋፋት ሊጠበቅበት ነው…ያ ደግሞ በጣም የሚጠላው ነገር ነው፡፡
ደርሰው ራሄል መኪናውን ፓርክ አድርጋ እንዳቆመች እሱ ፈጠን ብሎ ወረደና ፀጋን አንስቶ አቀፋት..ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዷት ስለነበረ ሲያቅፍት ልጥፍ አለችበት፡፡ራሄል ቦርሳውን አንስታ አንጠለጠለችና ተከተለቻቸው እና ወደ ግዙፍ ቤት ተከታለው ሲገቡ ጥዋት ተሰምቷት የነበረ ስሜት ተመልሷ ተሰማት…ባሏ… ተወዳጅ ልጇን አቅፎ ወደቤት ሲገቡ….ሀሳቡ የደስታ ውስጧ በደስታ ስሜት እንዲጥለቀለቅ ስላደረጋት ‹‹እንዴት ደስ ይላል››ስትል በለሆሳሳ አንሾካሾከች፡፡ከፊት ቀደመችና ሳሎኑን ሰንጥቃ እየመራች ወደፀጋ ክፍል ይዛው ሄደች… ቶሎ ብላ ብርድ ልብሱን ገለጠችለት…ቀስ ብሎ አስተኛትና ተጋግዘው አለባበሳትና ቆመ…ተከትላው ቆመች…በመሀከላቸው ያለው ርቀት ከአንድሜትር አይበልጥም…አንደኛው ሌለኛው ላይ አፍጥጧል….በሚገርም ሁኔታ የትንፋሽ ማጠር አጋጠማት. …ቀስ እያለ ተጠጋትና እጇቹን በወገቧ ላይ አሳረፈ፡፡
ውርር የሚያደርግ ጥሩ ስሜት ተሰማት…ከዛ በምን ፍጥነት እንደሆነ ሳታውቅ ከንፈሮቹ በእሷ ከንፈር ላይ አረፉ …የራሄል አይኖች ተዘጉ፤ እና ለአፍታ ድንጋጤ ተሰማት ፣ እጆቹ በወገቧ ዙሪያ ተጠመጠሙባት እና ወደራሱ ጎትቶ አስጠጋት። ራሄል ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ በቀጣይ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር የማወቅ ጉጉት ተሰማት። የበለጠ ልትለጠፍበትና ልትደገፍበት ፈቀደች፡፡ ‹‹ይህ ጥሩ ሥነ ምግባር አይደለም?››በውስጧ ነበር ያሰበችው… በድንገት የከበደውን ከባቢ አየር ማቅለል ፈለገች። ለብዙ ዓመታት ሳትወድቅ ከቆየችበት ቦታ ለመመለስ ተፍጨረጨረች።
‹‹የእህቴን ሐኪም መሳም ?››ከእቅፉ ሳትወጣ የሹክሹክታ ድምፅ አሰማች።ወደፊቷ የተደፋውን ፀጉሯን ወደኃላ በመመለስ አስተካከለላት፡፡ከዚያም , ቀስ ብሎ ከከንፈሯም ከአካሏ ተላቀቀ እና እራቅ አለ።
‹‹ ፀጋ ቅሬታ እንደማታቀርብ አምናለው››አለችና ዓይኗን በእፍረት ደፍች፡፡ ለእሱ ያላትን መስህብ በውስጧ መቅበር እስከቻለች ድረስ፣ እራሷን ከእሱ ለይታ ማቆየት እስከቻለች ድረስ፣ እነዚህን አዳዲስ እና አደገኛ ስሜቶች መቋቋም እንደምትችል ታስብ ነበር።አሁን ግን?በጣም ለረጅም ጊዜ የናፈቀችውን ነገር ቀምሳለች። ከንፈሯ ላይ መች ተጠግቶ እንደተጣበቀባት እንኳን አላወቀችውም። ፍቃዷን እና ሙሉ ስሜቷን ለዚህ ሰው እስክትሰጥ ቅፅበት ድረስ ልቧን በኪሩቤል የመቃብር ቦታ ለዘመናት ቀብራው ነበር፡፡ በደረሰባት ኪሳራ ተበሳጭታ ስለነበረ ራሷን ዳግመኛ እንደዚህ ላለ ሁኔታ ለማጋለጠ ፈፅሞ እንደማትፈቅድ ቃል ገብታ ነበር። አንድን ሰው በጥልቀት ለመንከባከብ መፍቀድ ራስን ነገ በድንገት ለሚመጣ ህመም ማመቻቸት እንደሆነ ህይወት አስተምራታለች።ከዛ ስቃይ ለማገገም እና እንደገና ወደህይወት ለመመለስ ዓመታት ፈጅቶባታል።
‹‹ይሄ ጉዳይ በጣም ያስፈራኛል።››አለችው፡፡
አገጯን በአውራ ጣት ዳባበሳት እና ‹‹ምንም አይደለም እኔም እፈራለሁ:: ግን ፍርሀታችንን ለማለስለስ ብዙ ጊዜ አለን››አለና ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
በረጅሙ ተነፈሰች፣ ከዚያም ፈገግ አለች።
ጭንቅላቷ ላይ ሳማትና ከዚያም በሹክሹክታ ‹‹ባዬ ራሄል››በማለት ክፍሉንም ቤቱንም ለቆ ወጣ ።ራሄል እስከሳሎን ተከተለችውና ከኋላው በሩን ዘጋች፡፡ የሞተር ሳይክሉን ድምፅ በመኪና መንገዱ ላይ ሲንደቀደቅ ሰማች። ጭንቅላቷን ቀዝቃዛው መስታወት ላይ አስደገፈች፡፡ …በድንገት መጸለይ እንዳለባት ተሰማት።‹‹ጌታ ሆይ እሱን ጠብቀው›› አለች ‹‹ራሷን ለሌላ ሰው በዚህ መንገድ እከፍታለው ብላ ፈፅሞ አስባ አታውቅም ነበር? የፀጋ የታፈነ ጩኸት ተሰማት…ራሷን ከተደገፈችበት መስታወት ቀና አደረገች እና ተንቀሳቀሰች…ከዛ ወደ ፀጋ ሄደች። እህቷን ለመከታተል ወደ ደረጃው እየሮጠች ስትሄድ፣ ቀድሞ የነበረባትን ስሜት እየሰመጠ እንደሆነ ተረዳች።
///
ዔሊያስ የቤቱን ዙሪያ ገባ ተመለከተ። ምንም ያማረ ነገር የለም። በራሱ ቤት ውስጥ በራሱ ሶፋ ላይ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም፣ አእምሮው ከአንድ በሰአት በፊትና በተለያት ሴት ላይ ተጣብቆ ነበር።ከአንድ ሰአት በፊት የሳማት ሴት አሁንም ልቡ ውስጥ እየተገላበጠች ነው።እንደዛ ያለ ድንገተኛ እርምጃ እንዲወስድ ያነሳሳው ምንድን ነበር?ቢያስብ ቢያስብ ሊገለፅለት አልቻለም፡፡
እረፍት አጥቶ ከሶፋው በመነሳት ቢንያም ወደተኛበት ክፍል ተራመደ… ሀሳቡ ዋና መኝታ ቤቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ማለቅ እንዳለበት ሊነግረው ነበር ። ነገሮች እንዳሰበው ሚሄዱ ከሆነ እና የገንዘብ እጥረት ካላጋጠመው ቤቱ በስድስት ወር ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይፈልጋል። በእቅዱ መሰረት ቤቱን ካጠናቀቀ በኃላ ቀጣዩ እቅዱ አዲስ መኪና መግዛት ነው። እና ከዚያ ምናልባት ይህንን ንፁህ እና በስርዓት የተቀነበበ ህይወቱን የምትካፍለው ሴት መፈለግ ይኖርበት ይሆናል። ከአመታ በፊት እቅዱን በዚህ መንገድ በቅደም ተከተል ሲያስቀምጥ ሁሉም ነገር እንከን የለሽ እንደሆነ እርግጠኛ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ ራሔል ከፊቱ ከመጋረጧ በፊት ነበር ።
የወንዱሙን ክፍል ለመክፈት እጄታውን ከያዘ በኃላ ሀሰቡን ቀየረ…ራሴ ተረብሼ ለምን እሱን እረብሸዋለው..በማለት ወደኃላ ተመለሰና ወደራሱ መኝታክፍል ገባ፡፡የልብሱን መሳቢያ ከፍቶ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ቤት ያመጣውን የስጋ ወላጇቹን የፎቶ ሳጥን አወጣ ፡፡ራሄል ያቀረበችለትን ሀሳብ በድጋሚ አሰበበት። ምናልባት አሳዳጊዎቹ ይሄንን የወላጆቹን ፎቶ ከእሱ ለማራቅ ጥሩ ምክንያቶች ነበሯቸው።በወላጆቹ ፊት ላይ የራሱን አሻራ ለማግኘት እየሞከረ ፎቶውን አገላብጧ ተመለከተ። አገጩን በእናቱ፣ ዓይኖቹ በአባቱ መልክ ላይ በጨረፍታ የተመለከተ መስሎት ነበር። ወይም ምናልባት ምኞት እንደዛ ስለሆነ ይሆናል፡፡ ፡፡እሱ እንደ አብዛኛው የማደጎ ልጆች ፣ስለ ወላጆቹ ይበልጥ ለመማር እና ለማወቅ ፍላጎት ነበረው ።እሱን በተመለከተ በህፃናት ማሳደጊያ ተቋሙ ውስጥ ያለው ፋይል ውድ የሆኑ ጥቂት መረጃዎችን የያዘ ሲሆን አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውቅ አድርገውታል፡፡ታዲያ ለምን መርካት አልቻለም?
ራሄል የማንቂያ ሰዓቱን ላይ ባለማመን አፈጠጠች።እንቅልፍ አልወስዳት ብሎ ከግራ ወደቀኝ እየተገላበጠች ለአንድ ሰአት ተሰቃየች… የሰዓቱ መንቀርፈፍ የዘለአለም መሰላት። ደጋግማ ከኤሊ ጋር ስታጫውተው የነበረውን ትዕይንት አዲስ እንደወጣ ተወዳጅ ፊልም ደጋግማ በምልሰት በማሰብ አጣጣመችው፣ የከንፈሮቹን ንክኪ እንደገና ተሰማት።መላልሳ ባሰበችው ቁጥር በእያንዳንዱ ትውስታ አዲስ ስሜት ይሰማት ነበር። በቀጣይ ምንድነው የሚሆነው….?እራሷን ትጠይቃለች….አእምሯዋ ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግራ መጋባት ውስጥ አሽቀንጥሮ ይጥላታል፡፡
ያለፈውን የልቧን ጭለማ ጓዝ እንዴት መልቀቅ እንዳለባት እስከአሁን አላወቀችም፣ አልደፈረችም።
❤47👍9👏3