ከሆነ ጊዜ በኋላ እኮ ምንም ነን ፥
ምድር አታስታውሰንም ፤
ከብታቿ ቀብራ በተረኛ ታስረግጠናለች ። 😔
ምድር አታስታውሰንም ፤
ከብታቿ ቀብራ በተረኛ ታስረግጠናለች ። 😔
👍49😢15❤6🔥4😁4🥰2
የግርማዊ ጃንሆይ ቤተሰቦች በዓለም በቃኝ ወሕኒ ቤት ፤አሳዛኝ ቆይታ😔
ዘውዳዊ ሥርዓትን አስወግዶ ስልጣን መያዙን መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም በይፋ ያወጀው የደርግ ወታደራዊ መንግስት ፣ በዚሁ እለት ንጉሠ ነገሥቱን ከቤተመንግሥታቸው ይዞ 4ተኛ ክፍለ ጦር በተባለው የወታደር ሰፈር እንዲታሰሩ በማድረግ ፣ እስከ ጊዜ ሞታቸው ድረስ ለአንድ አመት ያህል አቆይቷቸዋል፡፡
ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ንጉሳዊ ቤተሰቡ በጃንሆይ ልጅ በልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ መኖሪያ ቤት ውስጥ በቁም እስር እንዲጠበቁ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ መካከል አረጋውያን ፣ ሴቶች እና ሕፃናት ይገኙበት ነበር፡፡ ደርጉ የጃንሆይ ቤተሰቦች በቁም እስር የሚጠበቁት ምክንያት “ሰፊው ሕዝብ በግብታዊነት ተነሳስቶ የበቀል እርምጃ እንዳይወስድባቸው ነው” በማለት ለውጪ ተመልካቾች ገልፆ ነበር፡፡
ሕዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም “ስልሳዎቹ” ተብለው ከሚታወቁት ከዘውድ መንግሥት ባለስልጣናት ጋር የተሰውት፣ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል ጠቅላይ አዛዥና የጃንሆይ የልጅ ልጅ፣ ሪል አድሚራል እስክንድር ደስታ በደርግ የተገደሉ የመጀመሪያው የጃንሆይ ቤተሰብ አባል ናቸው፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ በነሐሴ 1967 ዓ.ም ያረፉት ግድያ ተፈፅሞባቸው ከሆነ ደግሞ ጃንሆይ በደርግ የተገደሉ ሁለተኛው የንጉሳዊ ቤተሰብ አባል ናቸው ማለት ነው፡፡
ደርግ በመስከረም ወር 1968 ዓ.ም በቁም እሥር የሚገኙትን ንጉሳዊ ቤተሰቦች በአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ውስጥ የእድሜ ልክ ፍርደኞች ከሚታሰሩበትና ዓለም በቃኝ ከተባለው ክልል ውስጥ በማዘዋወር አያያዛቸውም በእሥረኛ ደንብ እንዲሆን መወሰኑ ታወቀ፡፡ ከእነዚህ የንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች ውስጥ የሚበዙት ሴቶች የነበሩ ሲሆን ወጣት ወንዶችም ይገኙበት ነበር፡፡
እሥረኞቹ ልዑላን የአፄ ኃይለሥላሴ የቅርብ ዘመዶች ከመሆናቸው በስተቀር በዘውድ መንግሥት ውስጥ የያዙት ሥልጣን ወይም ሹመት አልነበረም። ለአንድ ዓመት በቁም እስር ሲቆዩም በወንጀል አልተከሰሱም ወይም ፍርድ አልተፈረደባቸውም፡፡ ከአንድ አመት የቁም እስር በኋላ ደግሞ ይባስ ብሎ ለረጅም ጊዜ ወደሚቆዩበትና የእድሜ ልክ ፍርደኞች ወደሚታሰሩበት የአለም በቃኝ የወህኒ ክልል ውስጥ እንዲዘዋወሩ ተደረገ፡፡
በዓለም በቃኝ ከታሰሩት ንጉሳዊ ቤተሰቦች ውስጥ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ እና ልጆቻቸው ልዕልት ሰብለ ደስታ ፣ ልዕልት አይዳ ደስታ ፣ ልዕልት ሒሩት ደስታ ፣ ልዕልት ሶፍያ ደስታ እንዲሁም ልዕልት ሳራ ግዛውና ልጆቻቸው ልዑል ወሰንሰገድ መኮንን ፣ ልዑል ሚካኤል መኮንን ፣ ልዑል በዕደማርያም መኮንንና ልዕልት ምሕረት መኮንን በተጨማሪም የልዑል አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን የመጀመሪያ ልጅ ልዕልት እጅጋየሁ ይገኙበት ነበር፡፡
ከእስረኞቹ በእድሜ ዝቅተኛው የ 17 አመቱ ወጣት ልዑል በዕደማርያም መኮንን ሲሆን ከፍተኛ እድሜ የነበራቸው ደግሞ የ63 አመቷ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ ነበሩ፡፡ በወህኒ ቤት ደንብ መሰረት ልዑላኑ ወንዶችና ሴቶች በዓለም በቃኝ የታሰሩት ተለያይተው በልዩ ልዩ ክፍሎች ውስጥ ነበር፡፡
የወህኒ ቤቱ ክፍሎች ከድንጋይ የተሰሩ እና የሚያዡ በመሆናቸው ዘወትር ቅዝቃዜ አይለያቸውም፡፡ ከጥቂት የመመገቢያ ቁሳቁሶች በስተቀር ሌላ መገልገያ እንዳያስገቡ የተከለከሉት እሥረኞች የሚተኙትም በወለሉ ላይ ፍራሽ ብቻ በማንጠፍ ነበር፡፡
የደርግ መንግስት የልዑላኑን ቤትና ንብረት የወረሰ በመሆኑ፣ በምትኩ በየወሩ ብር 120 እየቆረጠላቸው ለጥቂት ጊዜ ሲቀበሉ የቆዩ ሲሆን በኋላ ላይ “ይበዛል” ተብሎ ወደ 50 ብር ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡ እሥረኞቹ ከዘመዶቻቸው በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ለመቀበል፣ በሳምንት አንድ ጊዜ አጭር ደብዳቤ ለመፃፍ እንዲሁም ለጥልፍ የሚያገለግሉ ቁሳቁስ ለማስገባት የሚችሉ ቢሆንም ጠያቂ ለማነጋገር የሚፈቀድላቸው ግን በአመት ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ ብቻ ነበር፡፡
እሥረኞቹ ንጉሳዊ ቤተሰቦች በጣም በሚያስጨንቅ አካላዊና ሥነ ልቡናዊ ሁኔታ ላይ እንደነበሩ በጊዜው የፖለቲካ እሥረኞችን ሁናቴ እየተከታተለ መንግሥትን ይማፀን የነበረው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል በጊዜው ያወጣቸው ተከታታይ ሪፖርቶች ይጠቁማሉ፡፡
የንጉሳዊ ቤተሰቡ ከነበሩባቸው በርካታ ችግሮች አንዱ የመሰረታዊ ሕክምና እጦት ነበር፡፡ ምንም እንኳን በወህኒ ቤቱ ውስጥ የጤና አገልግሎት የሚሰጥ ክሊኒክ የነበረ ቢሆንም ፣ የንጉሳዊ ቤተሰቡ ሕክምና ሆነ ተብሎ እንዲዘገይ ይደረግ ነበር፡፡ ስለዚህም በጊዜ ቢደረስበት መፍትሄ ያገኝ የነበረ ቀላል ሕመም እየተባባሰ እሥረኞቹን ለከፋ አደጋ ሲያጋልጣቸው ተስተውሏል፡፡
ለዚህም አይነተኛ ምሳሌ የሚሆኑት ልዕልት እጅጋየሁ አስፋ ወሰን ናቸው፡፡ እኒህ ሴት በወህኒ ቤት በተቆራኛቸው ደዌ ለረጅም ጊዜ ሲሰቃዩ አሳሪዎቻቸው ሕክምና እንዲያገኙ አልፈቀዱላቸውም ነበር፡፡ ህመማቸው ተባብሶ ከፍተኛ ደረጃ ከደረሰ በኋላ ግን በፖሊስ ሆስፒታል ተኝተው እንዲታከሙ ተወሰነ። ሐኪሞች ልዕልቷን ኦፕራሲዮን ቢያደርጉዋቸውም ያደረባቸው ደዌ ለረጅም ጊዜ መፍትሄ ሳያገኝ የቆየ በመሆኑ፣ ጥር 23 ቀን 1970 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
እሥረኞቹን ያሰቃዩዋቸው የነበሩት ሕመሞች የመነጩት ወይም ሥር ሰደው የተባባሱት ለረጅም ጊዜ ያለ ሕክምና በቆዩበት በዚህ ወህኒ ቤት ውስጥ ነበር። በከባድ ህመም ይሰቃዩ ከነበሩት መካከል ልዕልት ሒሩት ደስታ አንዷ ናቸው፡፡ እኒህ ልዕልት በእሥር ላይ እያሉ ከተከሰተባቸውና ከባድ ደረጃ የደረሰ የቆዳ ካንሰር የተነሳ ኦፕራሲዮን የተደረገላቸው ሲሆን በሕመሙ ሳቢያ የሰውነት ክብደታቸው በአደገኛ ሁኔታ አሽቆልቁሎ ነበር፡፡
ሌላዋ የእሥር ቤት ሕመም ሰለባ ደግሞ ልዕልት አይዳ ደስታ የነበሩ ሲሆን ሕመማቸው ደግሞ የማያቋርጥና ብርቱ ራስ ምታት ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የሰውነታቸው አንዱ ክፍል እዚያው ወሕኒ ቤት ውስጥ ፓራላይዝድ በመሆኑ ከቦታ ወደ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚችሉት በከፍተኛ ችግር ነበር፡፡ የልዑል መኮንን ባለቤት የነበሩት ልዕልት ሣራ ግዛው በበኩላቸው፤ በወሕኒ ቤት በለከፋቸው የሄፒታይተስ በሽታ ክፉኛ ታመው ለረጅም ጊዜ ተሰቃይተዋል፡፡
መሰረታዊ የሕክምና እጦት፣ ከዛሬ ነገ ልንገደል እንችላለን የሚል ብርቱ ስጋት እንዲሁም በውጪ እና እዚያው እሥር ቤት ካሉ ልጆቻቸውና ዘመዶቻቸው ጋር ለመገናኘት አለመቻል፣ ተደራርቦ እሥረኞቹን ለአስከፊ ስነልቡናዊ ስቃይ ዳርጓቸዋል። የደረሰባቸውን የመንፈስ ጭንቀት ለማስታገስም ቤተሰቦቻቸው እንቅልፍ እንዲያስወስድ የሚያደርጉ እና አእምሮን የሚያረጋጉ እንክብሎች እንዲያመጡላቸው በመጠየቅ፣ ያለ ሐኪም ፈቃድ ይወስዱ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡
እነዚህ እሥረኞች ያለ ፍርድ ወደ ወህኒ የተወረወሩ በመሆኑ ለፍርድ እንዲቀርቡ ወይም እንዲለቀቁ፤ እንዲሁም አያያዛቸውም የሕግ እሥረኞች በሚጠበቁበት አግባብ ሆኖ መሰረታዊ ሕክምና ሳይዘገይ እንዲሰጣቸው፤ በማለት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ ባለማቋረጥ የደርጉን መንግሥት ሲማፀን ቆይቷል፡፡
ይሁን እንጂ ሕክምናን ማዘግየት ወይም መከልከል እንደ መደበኛ ቅጣት ተቆጥሮ፣ እሥረኞቹ እስከ 1980 ዓ.ም ድረስ መሰረታዊ ሕክምናን ተነፍገው ቆይተዋል። ንጉሳዊ ቤተሰቡ ከእሥር እንዲለቀቅ ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ሳያቋርጥ ለደርጉ ይቀርብ የነበረው ተማፅኖ ፍሬ ማሳየት የጀመረው እሥረኞቹ ወደ ወህኒ ከተወረወሩ ከስምንት አመታት በኋላ ነበር፡፡
ዘውዳዊ ሥርዓትን አስወግዶ ስልጣን መያዙን መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም በይፋ ያወጀው የደርግ ወታደራዊ መንግስት ፣ በዚሁ እለት ንጉሠ ነገሥቱን ከቤተመንግሥታቸው ይዞ 4ተኛ ክፍለ ጦር በተባለው የወታደር ሰፈር እንዲታሰሩ በማድረግ ፣ እስከ ጊዜ ሞታቸው ድረስ ለአንድ አመት ያህል አቆይቷቸዋል፡፡
ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ንጉሳዊ ቤተሰቡ በጃንሆይ ልጅ በልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ መኖሪያ ቤት ውስጥ በቁም እስር እንዲጠበቁ የተደረገ ሲሆን ከነዚህ መካከል አረጋውያን ፣ ሴቶች እና ሕፃናት ይገኙበት ነበር፡፡ ደርጉ የጃንሆይ ቤተሰቦች በቁም እስር የሚጠበቁት ምክንያት “ሰፊው ሕዝብ በግብታዊነት ተነሳስቶ የበቀል እርምጃ እንዳይወስድባቸው ነው” በማለት ለውጪ ተመልካቾች ገልፆ ነበር፡፡
ሕዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም “ስልሳዎቹ” ተብለው ከሚታወቁት ከዘውድ መንግሥት ባለስልጣናት ጋር የተሰውት፣ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል ጠቅላይ አዛዥና የጃንሆይ የልጅ ልጅ፣ ሪል አድሚራል እስክንድር ደስታ በደርግ የተገደሉ የመጀመሪያው የጃንሆይ ቤተሰብ አባል ናቸው፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ በነሐሴ 1967 ዓ.ም ያረፉት ግድያ ተፈፅሞባቸው ከሆነ ደግሞ ጃንሆይ በደርግ የተገደሉ ሁለተኛው የንጉሳዊ ቤተሰብ አባል ናቸው ማለት ነው፡፡
ደርግ በመስከረም ወር 1968 ዓ.ም በቁም እሥር የሚገኙትን ንጉሳዊ ቤተሰቦች በአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ውስጥ የእድሜ ልክ ፍርደኞች ከሚታሰሩበትና ዓለም በቃኝ ከተባለው ክልል ውስጥ በማዘዋወር አያያዛቸውም በእሥረኛ ደንብ እንዲሆን መወሰኑ ታወቀ፡፡ ከእነዚህ የንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች ውስጥ የሚበዙት ሴቶች የነበሩ ሲሆን ወጣት ወንዶችም ይገኙበት ነበር፡፡
እሥረኞቹ ልዑላን የአፄ ኃይለሥላሴ የቅርብ ዘመዶች ከመሆናቸው በስተቀር በዘውድ መንግሥት ውስጥ የያዙት ሥልጣን ወይም ሹመት አልነበረም። ለአንድ ዓመት በቁም እስር ሲቆዩም በወንጀል አልተከሰሱም ወይም ፍርድ አልተፈረደባቸውም፡፡ ከአንድ አመት የቁም እስር በኋላ ደግሞ ይባስ ብሎ ለረጅም ጊዜ ወደሚቆዩበትና የእድሜ ልክ ፍርደኞች ወደሚታሰሩበት የአለም በቃኝ የወህኒ ክልል ውስጥ እንዲዘዋወሩ ተደረገ፡፡
በዓለም በቃኝ ከታሰሩት ንጉሳዊ ቤተሰቦች ውስጥ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ እና ልጆቻቸው ልዕልት ሰብለ ደስታ ፣ ልዕልት አይዳ ደስታ ፣ ልዕልት ሒሩት ደስታ ፣ ልዕልት ሶፍያ ደስታ እንዲሁም ልዕልት ሳራ ግዛውና ልጆቻቸው ልዑል ወሰንሰገድ መኮንን ፣ ልዑል ሚካኤል መኮንን ፣ ልዑል በዕደማርያም መኮንንና ልዕልት ምሕረት መኮንን በተጨማሪም የልዑል አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን የመጀመሪያ ልጅ ልዕልት እጅጋየሁ ይገኙበት ነበር፡፡
ከእስረኞቹ በእድሜ ዝቅተኛው የ 17 አመቱ ወጣት ልዑል በዕደማርያም መኮንን ሲሆን ከፍተኛ እድሜ የነበራቸው ደግሞ የ63 አመቷ ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ ነበሩ፡፡ በወህኒ ቤት ደንብ መሰረት ልዑላኑ ወንዶችና ሴቶች በዓለም በቃኝ የታሰሩት ተለያይተው በልዩ ልዩ ክፍሎች ውስጥ ነበር፡፡
የወህኒ ቤቱ ክፍሎች ከድንጋይ የተሰሩ እና የሚያዡ በመሆናቸው ዘወትር ቅዝቃዜ አይለያቸውም፡፡ ከጥቂት የመመገቢያ ቁሳቁሶች በስተቀር ሌላ መገልገያ እንዳያስገቡ የተከለከሉት እሥረኞች የሚተኙትም በወለሉ ላይ ፍራሽ ብቻ በማንጠፍ ነበር፡፡
የደርግ መንግስት የልዑላኑን ቤትና ንብረት የወረሰ በመሆኑ፣ በምትኩ በየወሩ ብር 120 እየቆረጠላቸው ለጥቂት ጊዜ ሲቀበሉ የቆዩ ሲሆን በኋላ ላይ “ይበዛል” ተብሎ ወደ 50 ብር ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡ እሥረኞቹ ከዘመዶቻቸው በቀን አንድ ጊዜ ምግብ ለመቀበል፣ በሳምንት አንድ ጊዜ አጭር ደብዳቤ ለመፃፍ እንዲሁም ለጥልፍ የሚያገለግሉ ቁሳቁስ ለማስገባት የሚችሉ ቢሆንም ጠያቂ ለማነጋገር የሚፈቀድላቸው ግን በአመት ሁለት ወይም ሦስት ጊዜ ብቻ ነበር፡፡
እሥረኞቹ ንጉሳዊ ቤተሰቦች በጣም በሚያስጨንቅ አካላዊና ሥነ ልቡናዊ ሁኔታ ላይ እንደነበሩ በጊዜው የፖለቲካ እሥረኞችን ሁናቴ እየተከታተለ መንግሥትን ይማፀን የነበረው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል በጊዜው ያወጣቸው ተከታታይ ሪፖርቶች ይጠቁማሉ፡፡
የንጉሳዊ ቤተሰቡ ከነበሩባቸው በርካታ ችግሮች አንዱ የመሰረታዊ ሕክምና እጦት ነበር፡፡ ምንም እንኳን በወህኒ ቤቱ ውስጥ የጤና አገልግሎት የሚሰጥ ክሊኒክ የነበረ ቢሆንም ፣ የንጉሳዊ ቤተሰቡ ሕክምና ሆነ ተብሎ እንዲዘገይ ይደረግ ነበር፡፡ ስለዚህም በጊዜ ቢደረስበት መፍትሄ ያገኝ የነበረ ቀላል ሕመም እየተባባሰ እሥረኞቹን ለከፋ አደጋ ሲያጋልጣቸው ተስተውሏል፡፡
ለዚህም አይነተኛ ምሳሌ የሚሆኑት ልዕልት እጅጋየሁ አስፋ ወሰን ናቸው፡፡ እኒህ ሴት በወህኒ ቤት በተቆራኛቸው ደዌ ለረጅም ጊዜ ሲሰቃዩ አሳሪዎቻቸው ሕክምና እንዲያገኙ አልፈቀዱላቸውም ነበር፡፡ ህመማቸው ተባብሶ ከፍተኛ ደረጃ ከደረሰ በኋላ ግን በፖሊስ ሆስፒታል ተኝተው እንዲታከሙ ተወሰነ። ሐኪሞች ልዕልቷን ኦፕራሲዮን ቢያደርጉዋቸውም ያደረባቸው ደዌ ለረጅም ጊዜ መፍትሄ ሳያገኝ የቆየ በመሆኑ፣ ጥር 23 ቀን 1970 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
እሥረኞቹን ያሰቃዩዋቸው የነበሩት ሕመሞች የመነጩት ወይም ሥር ሰደው የተባባሱት ለረጅም ጊዜ ያለ ሕክምና በቆዩበት በዚህ ወህኒ ቤት ውስጥ ነበር። በከባድ ህመም ይሰቃዩ ከነበሩት መካከል ልዕልት ሒሩት ደስታ አንዷ ናቸው፡፡ እኒህ ልዕልት በእሥር ላይ እያሉ ከተከሰተባቸውና ከባድ ደረጃ የደረሰ የቆዳ ካንሰር የተነሳ ኦፕራሲዮን የተደረገላቸው ሲሆን በሕመሙ ሳቢያ የሰውነት ክብደታቸው በአደገኛ ሁኔታ አሽቆልቁሎ ነበር፡፡
ሌላዋ የእሥር ቤት ሕመም ሰለባ ደግሞ ልዕልት አይዳ ደስታ የነበሩ ሲሆን ሕመማቸው ደግሞ የማያቋርጥና ብርቱ ራስ ምታት ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የሰውነታቸው አንዱ ክፍል እዚያው ወሕኒ ቤት ውስጥ ፓራላይዝድ በመሆኑ ከቦታ ወደ ቦታ ለመንቀሳቀስ የሚችሉት በከፍተኛ ችግር ነበር፡፡ የልዑል መኮንን ባለቤት የነበሩት ልዕልት ሣራ ግዛው በበኩላቸው፤ በወሕኒ ቤት በለከፋቸው የሄፒታይተስ በሽታ ክፉኛ ታመው ለረጅም ጊዜ ተሰቃይተዋል፡፡
መሰረታዊ የሕክምና እጦት፣ ከዛሬ ነገ ልንገደል እንችላለን የሚል ብርቱ ስጋት እንዲሁም በውጪ እና እዚያው እሥር ቤት ካሉ ልጆቻቸውና ዘመዶቻቸው ጋር ለመገናኘት አለመቻል፣ ተደራርቦ እሥረኞቹን ለአስከፊ ስነልቡናዊ ስቃይ ዳርጓቸዋል። የደረሰባቸውን የመንፈስ ጭንቀት ለማስታገስም ቤተሰቦቻቸው እንቅልፍ እንዲያስወስድ የሚያደርጉ እና አእምሮን የሚያረጋጉ እንክብሎች እንዲያመጡላቸው በመጠየቅ፣ ያለ ሐኪም ፈቃድ ይወስዱ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡
እነዚህ እሥረኞች ያለ ፍርድ ወደ ወህኒ የተወረወሩ በመሆኑ ለፍርድ እንዲቀርቡ ወይም እንዲለቀቁ፤ እንዲሁም አያያዛቸውም የሕግ እሥረኞች በሚጠበቁበት አግባብ ሆኖ መሰረታዊ ሕክምና ሳይዘገይ እንዲሰጣቸው፤ በማለት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ ባለማቋረጥ የደርጉን መንግሥት ሲማፀን ቆይቷል፡፡
ይሁን እንጂ ሕክምናን ማዘግየት ወይም መከልከል እንደ መደበኛ ቅጣት ተቆጥሮ፣ እሥረኞቹ እስከ 1980 ዓ.ም ድረስ መሰረታዊ ሕክምናን ተነፍገው ቆይተዋል። ንጉሳዊ ቤተሰቡ ከእሥር እንዲለቀቅ ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ሳያቋርጥ ለደርጉ ይቀርብ የነበረው ተማፅኖ ፍሬ ማሳየት የጀመረው እሥረኞቹ ወደ ወህኒ ከተወረወሩ ከስምንት አመታት በኋላ ነበር፡፡
❤64👏3😢3👍1🤩1
ደርግ ዘጠነኛውን የአብዮት በዓል አስመልክቶ በጳጉሜ ወር 1975 ዓ.ም ለፖለቲካ እሥረኞች ይቅርታ ሲያደርግ ወጣቷ ልዕልት ምሕረት መኮንን ከንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች መካከል ለመለቀቅ የመጀመሪያዋ ሆነች፡፡ የደርግ “አብዮታዊ ምህረት” ሁሉንም እሥረኛ ንጉሳዊ ቤተሰብ ያካተተ ባይሆንም እሥረኞቹ እንዲፈቱ ለሚማፀኑት ዓለም አቀፍ ተቋማት ግን እንደ በጐ እርምጃ ተደርጐ ተወስዷል፡፡ ተቋማቱ ምህረቱን አስመልክተው ለኢትዮጵያ መንግሥት ምስጋናቸውን በማቅረብ ቀሪዎቹ እሥረኛ ንጉሳዊ ቤተሰቦች እንዲለቀቁ የተለመደውን ልመና አቅርበዋል፡፡
ደርግ ለንጉሳዊ እሥረኞቹ ያደረገው 2ኛ ምህረት የተከናወነው ከመጀመሪያው ምህረት አምስት አመት ያህል ቆይቶ ሚያዝያ 13 ቀን 1980 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአሥራ ሁለት አመት በኋላ ከእሥር የተለቀቁት የ75 አመቷ አዛውንት ልዕልት ተናኘ ወርቅ ኃይለሥላሴ፣ ልዕልት ሰብለ ደስታ፣ ልዕልት ሒሩት ደስታ፣ ልዕልት አይዳ ደስታ፣ ልዕልት ሶፍያ ደስታ እና ልዕልት ሳራ ግዛው ነበሩ፡፡
ደርጉ ለንጉሳዊ ቤተሰብ 2ኛውን ምህረት ከሰጠ ከአንድ አመት ከአራት ወራት በኋላ ደግሞ ሦስተኛውንና የመጨረሻውን ምህረት ጳጉሜ 2 ቀን 1981 ዓ.ም አደረገ፡፡ ከ13 አመታት በኋላ የተለቀቁት የንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች፣ ወርቃማውን የወጣትነት ጊዜያቸውን በወህኒ ቤት ያሳለፉት፡- ልዑል በዕደማርያም መኮንን ፣ ልዑል ሚካኤል መኮንን እና ልዑል ወሰንሰገድ መኮንን ነበሩ።
ደርግ ለንጉሳዊ እሥረኞቹ ያደረገው 2ኛ ምህረት የተከናወነው ከመጀመሪያው ምህረት አምስት አመት ያህል ቆይቶ ሚያዝያ 13 ቀን 1980 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአሥራ ሁለት አመት በኋላ ከእሥር የተለቀቁት የ75 አመቷ አዛውንት ልዕልት ተናኘ ወርቅ ኃይለሥላሴ፣ ልዕልት ሰብለ ደስታ፣ ልዕልት ሒሩት ደስታ፣ ልዕልት አይዳ ደስታ፣ ልዕልት ሶፍያ ደስታ እና ልዕልት ሳራ ግዛው ነበሩ፡፡
ደርጉ ለንጉሳዊ ቤተሰብ 2ኛውን ምህረት ከሰጠ ከአንድ አመት ከአራት ወራት በኋላ ደግሞ ሦስተኛውንና የመጨረሻውን ምህረት ጳጉሜ 2 ቀን 1981 ዓ.ም አደረገ፡፡ ከ13 አመታት በኋላ የተለቀቁት የንጉሳዊ ቤተሰብ እሥረኞች፣ ወርቃማውን የወጣትነት ጊዜያቸውን በወህኒ ቤት ያሳለፉት፡- ልዑል በዕደማርያም መኮንን ፣ ልዑል ሚካኤል መኮንን እና ልዑል ወሰንሰገድ መኮንን ነበሩ።
😢23❤16👍5
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ዘሪሁን_ገመቹ
ራሄል ከሁለት ረዳቷቾ ከሮቤልና ሎዛ ጋር ስብሰባ ላይ እያለች ነበር ስልኳ የጠራው…ንግግሯን ሳታቋርጥ ስልኩን አነሳችና አየችው፤ አባቷ አቶ ቸርነት ናቸው የደወሉላት ፡፡ስብሰባ ላይ ነኝ ብላ ልትዘጋባቸው አልፈለገችም…አባቷ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ባይሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት አይደውሉላትም ነበር፡፡
‹‹አንዴ ይቅርታ… ይሄንን ስልክ ማንሳት አለብኝ››ብላ ከተቀመጠችበት ግዙፍ ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳችና ቢሮውን ለቃ ወጣችና….ከዛ ስልኩን አነሳችው፡፡
‹‹ሄሎ አባዬ ..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ ልጄ››
ድምፃቸው ተጎተተባት‹‹ምነው አባዬ? ችግር አለ እንዴ?››
‹‹አይ ልጄ ሁሉ ነገር ሰላም ነው…እኔ እና እናትሽ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነበር››
‹‹ምንድነው?››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ምን መሰለሽ..እኔና እናትሽ ጡረታ ወጥተን ቤት መዋል ከጀመርን በኃላ ህይወታችንን ታውቂያለሽ…ብቸኞች ነን..አንቺም አሻፈረኝ ብለሽ በራስሽ ቤት ነው የምትኖሪው…፡፡››
ራሄል በምትሰማው ነገር ፊቷን አጨማደደች….የገመተችው አብረሽን ኑሪ የሚለውን የዘወትር ጥያቄያቸውን ደግመው ሊያነሱባት ነበር የመሰላት፡፡
አባቷ ትንፋሽ ወሰዱና ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹እህት እንዲኖርሽ ፈልገን ነበር››
ደነገጠች‹‹እህት!!››
‹‹አዎ ቅር ማይልሽ ከሆነ እኔ እና እናትሽ እህት እንዲኖርሽ ፈልገናል…የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት ያንቺን አስተያየት ማወቅ ስለፈለግን ነው የደወልንልሽ፡፡››
‹‹ብዥ አለባት…እናቴ በሰባ አመቷ አረገዘች እንዴ?››ስትል በውስጧ እራሷ ጠየቀች፡፡‹‹አባቴ የአብረሀምን አይነት የዋህነት ስላለው እግዜር በዚህ አድሜዋ የማዬን ማህፀን ቢከፍት አይገርመኝም››ስትል በራሷ ሀሳብ ሳቀችና ትኩረቷን ወደስልኩ መለሰች፡፡
‹‹አባዬ አልገባኝም..እንዴት ነው እህት ሊኖረኝ የሚችለው?››
አንድ የሁለት አመት ቆንጅዬ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልንወስድ ነው….››
‹‹በጉዲፈቻ…በጣም ደስ ይላል….ጥሩ ውሳኔ ነው የወሰናችሁት..››
ሀሳባቸውን ለመደገፍ ጥቂት ማሰብ እንኳን አላስፈለጋትም…የሁለት አመት ጣፋጭ ልጅ እዛ ግዙፍ ቪላ ቤት ውስጥ ስትሯሯጥ…አንዴ አባቷ ላይ አንዴ ደግሞ እናቷ ላይ እየተንጠለጠች ስታስቃቸውና ሰታዝናናቸው፣እነሱም ሲያሞላቅቋት…እሷን መሀላቸው አድርገው ግራና ቀኝ እጇን ይዘው ወደቤተክርስቲያን ይዘዋት ሲሄዱ .... በአይነ ህሊናዋ ታያትና በደስታ ተፍለቀለቀች፡፡
‹‹ልጄ አሁን እሷን ልናይ ሆስፒታል ነው ያለነው ..ከቻልሽ ጋንዲ ነን …ብትመጪ ደስ ይለኛል፡፡››
መልሶ መደነጋገር ውስጥ ገባች‹‹ሆስፒታል…ምን ትሰራለች?››
‹‹ትንሽ አሟታል…ከቻልሽ ነይ፡፡››ደገሙላት፡፡
‹‹በቃ መጣው››……ስልኩን ዘጋችና ወደቢሮዋ ተመልሳ ለረዳቶቾ ወደስራ እንዲመለሱ ትዕዛዝ ሰጥታ ቦርሳውን አንጠልጥላ ወጣችና ቀጥታ ከፓርክ መኪናዋን በማንቀሳቀስ ስለአዲሷ እጩ እህቷ ምን እንደምትመስልና…ምኗን ታማ ሆስፒታል ልትገባ እንደቻለች እያብሰለሰለች ወደጋንዲ ሆስፒታል ነዳችው፡፡
ደርሳ ወደውስጥ ስትገባ ሰውነቷ መንቀጥቀጥ ጀመረ…ይሄ የተለመደ ስሜቷ ነው…ሆሲፒታል ሂጂ ከሚሏት ጦርነት ዝመቺ ብትባል ትመርጣለች…እንደምንም ግን ወደውስጥ ዘለቀች… አባቷን ደውላ አገኘችው…እጇን ይዞ እየመራ የተባለቸው ህፃን ወደተኛችበት ክፍል ይዟት ገባ፡፡ክፍሉ ውስጥ ከህፃኗ ጋር የገዛ እናቷ ብቻ ነች ያለችው፡፡ ከበራፉ አንድ እርምጃ ወደውስጥ ተራምዳ እንደቆመች ደንዝዛ ቀረች …ከዛ ማለፍ አልቻለችም፡፡
ፍፅም የሚባል ድንዛዜ ውስጥ ነው የገባችው…ልጅቷ ቢያንስ ከሶስት ማሽን ጋር በቱቦ ተያይዛለች…መልኳ ውብ ፀጉሯ ግንቧሯ ላይ ድፍት ያለ አጎጊ ብትሆንም ስልምልም ብላ እራሷን ስታ ተዘርራለች..እንደውም ነፍሷ ውስጧ እንዳለ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም….
በቃ ውስጧ ግልብጥብጥ ነው ያለባት…ከአመታት በፊት ምትወደውና ልታገባው ስታልመው የነበረው እጮኛዋ ኪሩቤል እንዲህ እንደህፃኗ እራሱ ስቶና ዝርግትግት ብሎ በማሽን እገዛ ለመተንፈስ ሲያጣጥር የነበረው ትዝታ መጣባትና እራሷን ልትስት ተንገዳገደች..አጠገቧ ያለው አባቷ ፈጠን ብሎ ደገፋት…እናቷ በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ስሯ ደረሰች፡፡
‹‹ምነው ልጄ..አመመሽ እንዴ?››ሁለቱም ተቀባብለው ጠየቋት፡፡
‹‹አይ ደህና ነኝ …የመድሀኒት ሽታና የህክምና ማሽኖቹ ድምፅ ነው የረበሸኝ››
‹‹ቸሬ አንተ እኮ ነህ..እሷ ሆስፒታል እንዴት እንደምትጠላና እንደሚያማት እያወቅክ ነይ ያልካት፡፡››
‹‹እውነትሽን ነው አጥፍቻለው….በቃ ልጄ ነይ…ይሄን ያህል ካየሻት ይበቃሻል….ብለው እየጎተቱ ወደውጭ ወሰዷት…መኪናዋ ድረስ አደረሷት፡፡‹‹እርግጠኛ ነሽ ሰላም ነሽ…?መኪና መንዳት ትችያለሽ››
‹‹አታስብ አባዬ..ሰላም ነኝ..በቃ ተመለስ››
መኪና ውስጥ ገባታ ስትንቀሳቅስ አባትዬው ወደውስጥ ተመለሱ፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው፡፡የልጅቷ ምስል ከአእምሮዋ ሊወጣ አልቻለም….ወላጆቾ ምን አስበው ያቺን በህይወት እና በሞት መካከል ባለች ቀጭን ክር ተንጠልጥላ ያለችን ልጅ በማደጎ ለመውሰድ እንዳሰቡ ሊገባት አልቻሉም…እንዴት አድርገው ሊንከባከቧት ነው…?ከለመዷትና ከወደዷት በኃላ ብትሞትባቸውስ…..?የሚወዱትን ሰው በሞት መነጠቅ እንዴት ልብን እንደሚሰብር እና ተስፋን እንደሚያከስም በራሷ ታውቀዋለች…እና በእሷ የደረሰ አይነት ሀዘን በዚህ እድሜያቸው በወላጆቾ እንዲድርስ አትፈልግም…፡፡
‹‹ግን ምን ማድረግ እችላለው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡እንዲሁ ስትብሰለሰል አደረች…ሳምንት ሙሉ አሰበችበት..አንድ ውሳኔ ወስና ለወላጆቾ ምንም ነገር ማለት ሳትችል…ወላጆቹ ህጋዊ የአሳዳጊነት ፕሮሰሱን ጨርሰው ልጅቷን ወደቤታቸው እንደወሰዱ ሰማች፡፡በቃ ከዛ በጊዜ ሂደት የሚሆነውን ጠብቃ ለመመልከት ወሰነችና ወደወላጇቾ ቤት ሄዳ አዲሷን እህቷን አየቻት…ምንም እንኳን ከዛ ሁሉ ማሽን ነፃ ሆና ብታያትም..አሁንም ግን በጣም ደካማ እና የሰለለ ሰውነት ያለት ሆና ነው ያገኘቻት፡፡ግን ደግሞ በዛው ልክ አሳዛኝና ተወዳጅ ልጅ መሆኗን መካድ አልቻለችም፡፡
============
ራሄል ከረዳቷ ጋር እያወራች ነው፡፡
‹‹ሮቤል ወ.ሮ ላምሮት ልገሳዋን ለእኛ ፋውንዴሽን እንድታደርግ አሁን በስልክ አናግሬታለው፡፡እሷን ማሳመን ከቻልኩ እና ውሳኔዋ ለእኛ ለመለገስ ከሆነ ለፋውንዴሽናችን ትልቅ ስኬት ነው››
ራሄል ወረቀቶቿን ወደ ቦርሳዋ አስገባች፣ አንድ አይኗ በእንጨት በተሸፈነው የቢሮዋ ግድግዳ ላይ በተሰቀለው ሰዓት ላይ ተሰክቶ ነበር።
‹‹ ለማውራት ጊዜ የለኝም። በሃያ ደቂቃ ውስጥ በወላጆቼ መኖሪያ ቤት በተዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ መገኘት አለብኝ ››አለች፡፡
ረዳቷ ማንኛውንም አይነት ቅሬታ ከማንሳቱ በፊት አቋረጠችውና ‹‹ እንደገና ሴትዬዋ ከደወለች ብቻ አሳውቀኝ።››አለችው፡፡
ስልኳን ዘጋችና ሞባይሏን ቦርሳዋ ውስጥ ለትንሿ እህቷ ጸጋ ከገዛችው ትንሽ ስጦታ ጋር አስቀመጠችው፣ ፀጋ ወላጇቾ ሊያሳድጓት በቅርብ የተረከቧት እህቷ ነች፡፡ ራሄል ወደ መኪና ማቆሚያ ጋራዥ በፍጥነት በምትወርድበት ጊዜ የኖብል ፋውንዴሽን ቢሮዎችና ኮሪደሮች በፀጥታ ተውጠው ነበር።
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ዘሪሁን_ገመቹ
ራሄል ከሁለት ረዳቷቾ ከሮቤልና ሎዛ ጋር ስብሰባ ላይ እያለች ነበር ስልኳ የጠራው…ንግግሯን ሳታቋርጥ ስልኩን አነሳችና አየችው፤ አባቷ አቶ ቸርነት ናቸው የደወሉላት ፡፡ስብሰባ ላይ ነኝ ብላ ልትዘጋባቸው አልፈለገችም…አባቷ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ባይሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት አይደውሉላትም ነበር፡፡
‹‹አንዴ ይቅርታ… ይሄንን ስልክ ማንሳት አለብኝ››ብላ ከተቀመጠችበት ግዙፍ ተሸከርካሪ ወንበር ተነሳችና ቢሮውን ለቃ ወጣችና….ከዛ ስልኩን አነሳችው፡፡
‹‹ሄሎ አባዬ ..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ ልጄ››
ድምፃቸው ተጎተተባት‹‹ምነው አባዬ? ችግር አለ እንዴ?››
‹‹አይ ልጄ ሁሉ ነገር ሰላም ነው…እኔ እና እናትሽ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነበር››
‹‹ምንድነው?››
‹‹ይሄውልሽ ልጄ ምን መሰለሽ..እኔና እናትሽ ጡረታ ወጥተን ቤት መዋል ከጀመርን በኃላ ህይወታችንን ታውቂያለሽ…ብቸኞች ነን..አንቺም አሻፈረኝ ብለሽ በራስሽ ቤት ነው የምትኖሪው…፡፡››
ራሄል በምትሰማው ነገር ፊቷን አጨማደደች….የገመተችው አብረሽን ኑሪ የሚለውን የዘወትር ጥያቄያቸውን ደግመው ሊያነሱባት ነበር የመሰላት፡፡
አባቷ ትንፋሽ ወሰዱና ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹እህት እንዲኖርሽ ፈልገን ነበር››
ደነገጠች‹‹እህት!!››
‹‹አዎ ቅር ማይልሽ ከሆነ እኔ እና እናትሽ እህት እንዲኖርሽ ፈልገናል…የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ከመድረሳችን በፊት ያንቺን አስተያየት ማወቅ ስለፈለግን ነው የደወልንልሽ፡፡››
‹‹ብዥ አለባት…እናቴ በሰባ አመቷ አረገዘች እንዴ?››ስትል በውስጧ እራሷ ጠየቀች፡፡‹‹አባቴ የአብረሀምን አይነት የዋህነት ስላለው እግዜር በዚህ አድሜዋ የማዬን ማህፀን ቢከፍት አይገርመኝም››ስትል በራሷ ሀሳብ ሳቀችና ትኩረቷን ወደስልኩ መለሰች፡፡
‹‹አባዬ አልገባኝም..እንዴት ነው እህት ሊኖረኝ የሚችለው?››
አንድ የሁለት አመት ቆንጅዬ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልንወስድ ነው….››
‹‹በጉዲፈቻ…በጣም ደስ ይላል….ጥሩ ውሳኔ ነው የወሰናችሁት..››
ሀሳባቸውን ለመደገፍ ጥቂት ማሰብ እንኳን አላስፈለጋትም…የሁለት አመት ጣፋጭ ልጅ እዛ ግዙፍ ቪላ ቤት ውስጥ ስትሯሯጥ…አንዴ አባቷ ላይ አንዴ ደግሞ እናቷ ላይ እየተንጠለጠች ስታስቃቸውና ሰታዝናናቸው፣እነሱም ሲያሞላቅቋት…እሷን መሀላቸው አድርገው ግራና ቀኝ እጇን ይዘው ወደቤተክርስቲያን ይዘዋት ሲሄዱ .... በአይነ ህሊናዋ ታያትና በደስታ ተፍለቀለቀች፡፡
‹‹ልጄ አሁን እሷን ልናይ ሆስፒታል ነው ያለነው ..ከቻልሽ ጋንዲ ነን …ብትመጪ ደስ ይለኛል፡፡››
መልሶ መደነጋገር ውስጥ ገባች‹‹ሆስፒታል…ምን ትሰራለች?››
‹‹ትንሽ አሟታል…ከቻልሽ ነይ፡፡››ደገሙላት፡፡
‹‹በቃ መጣው››……ስልኩን ዘጋችና ወደቢሮዋ ተመልሳ ለረዳቶቾ ወደስራ እንዲመለሱ ትዕዛዝ ሰጥታ ቦርሳውን አንጠልጥላ ወጣችና ቀጥታ ከፓርክ መኪናዋን በማንቀሳቀስ ስለአዲሷ እጩ እህቷ ምን እንደምትመስልና…ምኗን ታማ ሆስፒታል ልትገባ እንደቻለች እያብሰለሰለች ወደጋንዲ ሆስፒታል ነዳችው፡፡
ደርሳ ወደውስጥ ስትገባ ሰውነቷ መንቀጥቀጥ ጀመረ…ይሄ የተለመደ ስሜቷ ነው…ሆሲፒታል ሂጂ ከሚሏት ጦርነት ዝመቺ ብትባል ትመርጣለች…እንደምንም ግን ወደውስጥ ዘለቀች… አባቷን ደውላ አገኘችው…እጇን ይዞ እየመራ የተባለቸው ህፃን ወደተኛችበት ክፍል ይዟት ገባ፡፡ክፍሉ ውስጥ ከህፃኗ ጋር የገዛ እናቷ ብቻ ነች ያለችው፡፡ ከበራፉ አንድ እርምጃ ወደውስጥ ተራምዳ እንደቆመች ደንዝዛ ቀረች …ከዛ ማለፍ አልቻለችም፡፡
ፍፅም የሚባል ድንዛዜ ውስጥ ነው የገባችው…ልጅቷ ቢያንስ ከሶስት ማሽን ጋር በቱቦ ተያይዛለች…መልኳ ውብ ፀጉሯ ግንቧሯ ላይ ድፍት ያለ አጎጊ ብትሆንም ስልምልም ብላ እራሷን ስታ ተዘርራለች..እንደውም ነፍሷ ውስጧ እንዳለ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም….
በቃ ውስጧ ግልብጥብጥ ነው ያለባት…ከአመታት በፊት ምትወደውና ልታገባው ስታልመው የነበረው እጮኛዋ ኪሩቤል እንዲህ እንደህፃኗ እራሱ ስቶና ዝርግትግት ብሎ በማሽን እገዛ ለመተንፈስ ሲያጣጥር የነበረው ትዝታ መጣባትና እራሷን ልትስት ተንገዳገደች..አጠገቧ ያለው አባቷ ፈጠን ብሎ ደገፋት…እናቷ በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ስሯ ደረሰች፡፡
‹‹ምነው ልጄ..አመመሽ እንዴ?››ሁለቱም ተቀባብለው ጠየቋት፡፡
‹‹አይ ደህና ነኝ …የመድሀኒት ሽታና የህክምና ማሽኖቹ ድምፅ ነው የረበሸኝ››
‹‹ቸሬ አንተ እኮ ነህ..እሷ ሆስፒታል እንዴት እንደምትጠላና እንደሚያማት እያወቅክ ነይ ያልካት፡፡››
‹‹እውነትሽን ነው አጥፍቻለው….በቃ ልጄ ነይ…ይሄን ያህል ካየሻት ይበቃሻል….ብለው እየጎተቱ ወደውጭ ወሰዷት…መኪናዋ ድረስ አደረሷት፡፡‹‹እርግጠኛ ነሽ ሰላም ነሽ…?መኪና መንዳት ትችያለሽ››
‹‹አታስብ አባዬ..ሰላም ነኝ..በቃ ተመለስ››
መኪና ውስጥ ገባታ ስትንቀሳቅስ አባትዬው ወደውስጥ ተመለሱ፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው፡፡የልጅቷ ምስል ከአእምሮዋ ሊወጣ አልቻለም….ወላጆቾ ምን አስበው ያቺን በህይወት እና በሞት መካከል ባለች ቀጭን ክር ተንጠልጥላ ያለችን ልጅ በማደጎ ለመውሰድ እንዳሰቡ ሊገባት አልቻሉም…እንዴት አድርገው ሊንከባከቧት ነው…?ከለመዷትና ከወደዷት በኃላ ብትሞትባቸውስ…..?የሚወዱትን ሰው በሞት መነጠቅ እንዴት ልብን እንደሚሰብር እና ተስፋን እንደሚያከስም በራሷ ታውቀዋለች…እና በእሷ የደረሰ አይነት ሀዘን በዚህ እድሜያቸው በወላጆቾ እንዲድርስ አትፈልግም…፡፡
‹‹ግን ምን ማድረግ እችላለው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡እንዲሁ ስትብሰለሰል አደረች…ሳምንት ሙሉ አሰበችበት..አንድ ውሳኔ ወስና ለወላጆቾ ምንም ነገር ማለት ሳትችል…ወላጆቹ ህጋዊ የአሳዳጊነት ፕሮሰሱን ጨርሰው ልጅቷን ወደቤታቸው እንደወሰዱ ሰማች፡፡በቃ ከዛ በጊዜ ሂደት የሚሆነውን ጠብቃ ለመመልከት ወሰነችና ወደወላጇቾ ቤት ሄዳ አዲሷን እህቷን አየቻት…ምንም እንኳን ከዛ ሁሉ ማሽን ነፃ ሆና ብታያትም..አሁንም ግን በጣም ደካማ እና የሰለለ ሰውነት ያለት ሆና ነው ያገኘቻት፡፡ግን ደግሞ በዛው ልክ አሳዛኝና ተወዳጅ ልጅ መሆኗን መካድ አልቻለችም፡፡
============
ራሄል ከረዳቷ ጋር እያወራች ነው፡፡
‹‹ሮቤል ወ.ሮ ላምሮት ልገሳዋን ለእኛ ፋውንዴሽን እንድታደርግ አሁን በስልክ አናግሬታለው፡፡እሷን ማሳመን ከቻልኩ እና ውሳኔዋ ለእኛ ለመለገስ ከሆነ ለፋውንዴሽናችን ትልቅ ስኬት ነው››
ራሄል ወረቀቶቿን ወደ ቦርሳዋ አስገባች፣ አንድ አይኗ በእንጨት በተሸፈነው የቢሮዋ ግድግዳ ላይ በተሰቀለው ሰዓት ላይ ተሰክቶ ነበር።
‹‹ ለማውራት ጊዜ የለኝም። በሃያ ደቂቃ ውስጥ በወላጆቼ መኖሪያ ቤት በተዘጋጀው የምሳ ግብዣ ላይ መገኘት አለብኝ ››አለች፡፡
ረዳቷ ማንኛውንም አይነት ቅሬታ ከማንሳቱ በፊት አቋረጠችውና ‹‹ እንደገና ሴትዬዋ ከደወለች ብቻ አሳውቀኝ።››አለችው፡፡
ስልኳን ዘጋችና ሞባይሏን ቦርሳዋ ውስጥ ለትንሿ እህቷ ጸጋ ከገዛችው ትንሽ ስጦታ ጋር አስቀመጠችው፣ ፀጋ ወላጇቾ ሊያሳድጓት በቅርብ የተረከቧት እህቷ ነች፡፡ ራሄል ወደ መኪና ማቆሚያ ጋራዥ በፍጥነት በምትወርድበት ጊዜ የኖብል ፋውንዴሽን ቢሮዎችና ኮሪደሮች በፀጥታ ተውጠው ነበር።
❤93🔥2😱1
እናቷ ከአዲሳባ ውጭ ለገጣፎ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው እንድትመጣ ነግራታለች፡፡ ይህ የግብዣና ጥሪ በየሳምንቱ የረፍት ቀኗን ጠብቆ የማይቀር ነው ፡፡ይሁን እንጂ የዛሬው የተለየ እንደሆነ ያወቀችው ፕሮቶኮሏን ጠብቃ እንድትመጣ ከሚያሳስብ ማስጠንቀቂ ጋር የተነገራት በመሆኑ ነው።ለምን ብላ እናቷን ስትጠይቅ ‹‹ወሳኝ እንግዳ ስለጋበዝኩ ዘንጠሸ እንድትገኚ ነው የምፈልገው ››ብለው ነበር በደፈናው የመለሱላት፡፡ እናቷ ሁል ጊዜ አንድትደሰትና እና ዘና እንድትል ከመምከር ተቆጥበው አያውቅም። ራሄል ግራጫ ቀለም ያለው ሙሉ ልብስ ለብሳ በላዩ ላይ የሐር ሻርፕ አንገቷ ላይ ጠምጥማ ቆንጆ ለመሆን ሞክራለች፡፡‹‹ እናቴ እኔን እንደፍላጎቴ እንድሆን መፍቀድ ነበረባት።››ስትል አጉረመረመች፡፡
ከአምስት አመት በኃላ ወላጆቿ ለገጣፎ ወደሚገኘው የእርሻ ቤታቸው ተመልሳ አብራቸው እንድትኖር ለምነዋት ነበር። ራሄል ግን ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጋ ለረጅም ጊዜ ብቻዋን መኖሯን ቀጠለች። በምትኩ መሀል ቦሌ በሚገኝ ባለሁለት መኝታ ክፍል አፓርታማ ቤት ውስጥ መኖርን መርጣለች።የእሷ ቤት በወላጇቾ ሀብት ልክ ዘመናዊ የሚባል ባይሆንም ለእሷ ግን ተስማሚ ነበር።
የተነሳችው ሰንጋ-ተራ ከሚገኘው የኖብል ፋውንዴሽን ዋና መስሪያ ቤት ነው፡፡መኪናዋን እራሷ እየሾፈረች በእጆቾ መሪውን እያሽከረከረች በአእምሮዋ ስለስራዋም ስለህይወቷም ብጥቅጣቂ ሀሳቦችን እያሰበች ፍጥነቷን ጠብቃ እየተጓዘች ሳለ…የትራፊክ መብራት አስቋማት፡፡ከኋላዋ የነበረ መኪና ከፊት ለፊቷ አልፏ ሲቀድማት በትዝብት ተመለከተችው፡፡ ከዛ ሌላ ሞተር ሳይክል በጎኗ ታኮ አጠገቧ ሲቆም ደነገጠች። የሞተሩ ጩኸት ከመኪናዋ ሲዲ ማጫወቻ የሚመጣውን የመሀመድ አህመድ ድምፅ ውጦ አስቀረው።ሞተረኛውን ተመለከተችው፡፡ የቆዳ ጃኬት፣ ጂንስ ሱሪ እና ቡትስ ጫማ አጥልቋል..ጭንቅላቱ ላይ ሄልሜት አድርጎል፡፡
ራሄል መሪውን አጥብቃ ያዘችው፡፡ ሞተር ሳይክሎችን ትጠላለች። እጮኛዋ ኪሩቤል በዚያ ምሽት መኪናውን እየነዳ ቢሆን ኖሮ-አሁን በዚህ ሰዓት ስለእሱ ሞት በማሰብ ልቧ በሀዘን አይኮመታተርም ነበር ። ይህም ሆኖ በሞተር ሳይክሉ ላይ ያለውን ሰው በጨረፍታ ለማየት ከመሞከር መቆጠብ አልቻለችም።ሄልሜቱን ወደ ኋላ ገፋ እና እያየችው እንደሆነ ሲመለከት ቀስ ብሎ ፈገግ አለላት፡፡ ረጅምና ባለፈርጣማ ጡንቻ ነው፡፡ጠይምና አይናማ ነው፡፡ለግላጋ ቁመናው በአእምሮዋ ብልጭ ድርግም እያለ ሲታያት ተናደደች ፡፡ወደ ፊት ተመለከተች።ወደ ወላጆቿ ቤት የሚያመራውን መንገድ ክፍት መሆኑን ተገነዘበች፡፡ ሞተር ሳይክሉን እየስጮኸ ቀድሟት ተፈተለከ፡፡
ሲዲውን አወጣች፣ የምትፈልገውን ሙዚቃ የሚጫወት ኤፍ ኤም ጣቢያ ፍልጋ አገኘች እና ድምጹን ከፍ አደረገች። በምቾት እየነዳች ነው ፣ ነገ ስለምትሰራው ሥራ ምን ማድረግ እንዳለባት እቅድ ማውጣት ጀመረች ።አዎ የእሷን ትኩረት በቀጥታ የሚፈልጉ በርካታ ስራዎች አሉ፤ውስጧን የሚሸረካክታትን በበፊት ህይወቷ የተከሰቱ ጨለማ ትዝታዎችን ወደኃላ መተው አለባት።በግዙፍ የዛፍ ጥላዎችና በተለያዩ አትክልቶች ወደተሞላው ግዙፉ የወላጆቾ ቤት ደረሰች፡፡ መኪናዋን በሁለት ረድፍ ተከርክመው ባማሩ የፅድ ቁጥቋጦዎች መካከል ባለው ጠባብ መንገድ እየሰነጠቀች ወደ ዋናው ቤት እየቀረበች ነው። ‹‹ምሽቱ ጥሩ ሊሆን ነው ››ስትል አሰበች ።እንደገና እራሷን መቆጣጠር እንደቻለች ተሰማት።
አራት መኪና ለማቆም ወደሚችለው ጋራዥ ስትቀርብ የልብ ምቷ ጨመረ ።መንገድ ላይ አበሰጭቷት ያለፈው ባለ ሞተር ሳይክል ሰውዬ አሁን ከጋራዡ ፊት ለፊት ባለው የጡብ ግድግዳ አጠገብ ቆሟል፣ ሄልሜቱን በሞተር ሳይክሉ መሪ ላይ አንጠልጥሏል።መኪናዋን አመቻችታ አቆመች፡፡ የዮጋ መምህሯ እንዳስተማራት ረጅም ትንፋሽ ወደውስጦ ሳበች…መልሳ አስወጣች ፣ከንደገና ሳበች …። እራሷን ያረጋጋች ሲመስላት ለፀጋ የገዛችላትን ስጦታ አንሥታ በጥንቃቄ እየተራመደች ወደ መግቢያው በር አመራች። ‹ምናልባት ባለሞተር ሳይክሉ የሽያጭ ሰራተኛ ወይንም የሆነ መልዕክት ሊያደርስ የመጣ ሰው ሊሆን ይችላል።›ስትል አሰበች …ወይም ከቤቱ አገልጋዬች የአንደኛዋ ውሽማ ሊሆን እንደሚችልም ገመተች፡፡
በሩን አልፋ ወደውስጥ ስትገባ የቤታቸው ሰራተኛ አለም ‹‹እንኳን በደህና መጣሽ!!›› ብላ በታላቅ ፈገግታ ተቀበለቻት፡፡
‹‹አመሰግናለው…አለም››
‹‹ እናትሽ ኩሽና ውስጥ ነች..››
‹‹…ለጥቆማው አመሰግናለሁ ።እማዬ ምን አይነት ምግብ እንደሰራች ልትነግሪኝ ትችያለሽ?››
አለም ሚስጥራዊ የሆነ ፈገግታ ፈገግ እያለች‹‹ ላንቺ እና ለእንግዳቸው የበለጠ ባህላዊ ነገር የሚያዘጋጁ ይመስለኛል…ከስጋ ጥብስ እና ክትፎ ሲኖር ሌላው ጠቅላላ የጎሯ ምርት የሆነ ቅጠላቅጠል ነው….››የሚል መልስ ሰጠቻት፡፡
ራሄል‹‹አይ እማዬ እና ቅጠላ ቅጠል መች ይሆን የሚለያዩት!!››አለችና ያንን አስጠሊታ ሞተር ሳይክል እያከነፈ የመጣው ሰው ማን እንደሆነ ሳትጠይቃት ወደ ቤቱ ጀርባ ሄደች። ራሄል የፊት ለፊት ክፍል ግድግዳ ላይ የተንጠለጠለው መስታወት ውስጥ የራሷን ምስል ነጸብራቅ ተመለከተችና ቆም አለች፡፡ በመጠኑ የተዘበራረቀውን ፀጉሯን ለማስተካከል ትንሽ ጊዜ ወሰደባት፡፡ መላ አካሏ ንፁህ እና የተስተካከለ እንደሆነ አሰበች ። በጠባቡ ኮሪደር በኩል ወደ ኩሽና አመራች፡፡ እናቷ በዘመናዊው ኩሽና ውስጥ እንደ ደሴት የሚያገለግለው ግዙፉ መደርደሪያ ላይ ቆመው አትክልት ሲከትፉ አገኘቻቸው፡፡ ብርቱካናማ ልቅ ሽርጥ አድርጋገዋል፡፡ ወ.ሮ ትርሀስ ልጇቸውን ስያዩ ቢላዋዋን አስቀምጠው በሽርጣቸው ዙሪያ እጆቻቸውን እየጠራረጉ, ራሄልን እቅፏቸው ውስጥ አስገብተው አገላብጠው በመሳም ሞቅ ባለ ስሜት ተቀበሏት ‹‹በሰዓቱ በመምጣትሽ በጣም ደስ ብሎኛል ። ››
ራሄል እናቷን ሀዘን ባጠላባቸው አይኖቿ ተመለከተቻቸው።
‹‹ትንሽ የገረጣሽ ትመስያለሽ …ውዴ።?››
ራሄል ግልጽ ባልሆነ ምልክት እጇን አነሳችና ።‹‹ ስራ በዝቶብኝ ነበር..ሰሞኑን በቂ እንቅልፍ አላገኘውም…ለዛ ነው››
ለፀጋ ያመጣችውን ስጦታ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች። እናቷ ማስጠንቀቂያቸውን አጠንክረው ቀጠሉበት ‹‹ራስህሽን መንከባከብ አለብሽ …ሰውነታችን የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ነው …እግዚአብሔር በምድር ላይ ሥራውን ለመሥራት ጤናማ አገልጋዮች ያስፈልጉታል።››አሏት፡፡
ራሄል በእናቷ የተለመደ አይነት ንግግር ፈገግ አለች። በእግዚአብሔር ጉዳይ ላይ ከእናቷ ጋር ለመወያየት አልፈለገችም።ላለፉት ስምንት አመታት እግዚአብሔርን ከህይወቷ አስወጥታለች ወይም ለማስወጣት ሞክሯለች። የዚህም ምክንያት ‹‹ከእግዚአብሔር ፀሎቴን ቀብሮታል.. ህልሜን አክስሞታል…››ብላ ስለምታስብ ነው።እናቷ እጇቸውን በራሔል ትከሻ ላይ አድርገው ወደ ባንኮኒው ወሰዷት።
‹‹እኔና አባትሽ አንድ ደስ የሚል አስገራሚ ነገር አለን።የፀጋ ሐኪም መጥቶ እንዲጎበኘን ጋብዘነዋል።››
‹‹አሁን እዚህ አለ?››
እናትዬው በአውንታ ግንባራቸውን ነቀነቁ
‹‹ማለት ሞተር ሳይክ እየነዳ ቀድሞኝ የገባው ሰውዬ እንዳይሆን?››
‹‹አዎ››እናትዬው አረጋገጡላት፡፡‹‹አንቺም እሱን ለማግኘት ትፈልጊ ይሆናል ብዬ አሰብኩ››በማለት አከሉበት፡፡
እናትዬው በዘዴ ከዶ/ሩ ጋር ፊት ለፊት ከመጋፈጧ በፊት ስለሰውዬው የተወሰነ ግንዛቤ ሊያስጨብጧት እየሞከሩ እንደሆነ ገብቷታል፡፡
‹‹በሞተር ሳይክል ላይ ሳየው ግን ሞኝ መስሎ ነው የሚታየው›› ስትል ተናገረች፡፡
ከአምስት አመት በኃላ ወላጆቿ ለገጣፎ ወደሚገኘው የእርሻ ቤታቸው ተመልሳ አብራቸው እንድትኖር ለምነዋት ነበር። ራሄል ግን ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጋ ለረጅም ጊዜ ብቻዋን መኖሯን ቀጠለች። በምትኩ መሀል ቦሌ በሚገኝ ባለሁለት መኝታ ክፍል አፓርታማ ቤት ውስጥ መኖርን መርጣለች።የእሷ ቤት በወላጇቾ ሀብት ልክ ዘመናዊ የሚባል ባይሆንም ለእሷ ግን ተስማሚ ነበር።
የተነሳችው ሰንጋ-ተራ ከሚገኘው የኖብል ፋውንዴሽን ዋና መስሪያ ቤት ነው፡፡መኪናዋን እራሷ እየሾፈረች በእጆቾ መሪውን እያሽከረከረች በአእምሮዋ ስለስራዋም ስለህይወቷም ብጥቅጣቂ ሀሳቦችን እያሰበች ፍጥነቷን ጠብቃ እየተጓዘች ሳለ…የትራፊክ መብራት አስቋማት፡፡ከኋላዋ የነበረ መኪና ከፊት ለፊቷ አልፏ ሲቀድማት በትዝብት ተመለከተችው፡፡ ከዛ ሌላ ሞተር ሳይክል በጎኗ ታኮ አጠገቧ ሲቆም ደነገጠች። የሞተሩ ጩኸት ከመኪናዋ ሲዲ ማጫወቻ የሚመጣውን የመሀመድ አህመድ ድምፅ ውጦ አስቀረው።ሞተረኛውን ተመለከተችው፡፡ የቆዳ ጃኬት፣ ጂንስ ሱሪ እና ቡትስ ጫማ አጥልቋል..ጭንቅላቱ ላይ ሄልሜት አድርጎል፡፡
ራሄል መሪውን አጥብቃ ያዘችው፡፡ ሞተር ሳይክሎችን ትጠላለች። እጮኛዋ ኪሩቤል በዚያ ምሽት መኪናውን እየነዳ ቢሆን ኖሮ-አሁን በዚህ ሰዓት ስለእሱ ሞት በማሰብ ልቧ በሀዘን አይኮመታተርም ነበር ። ይህም ሆኖ በሞተር ሳይክሉ ላይ ያለውን ሰው በጨረፍታ ለማየት ከመሞከር መቆጠብ አልቻለችም።ሄልሜቱን ወደ ኋላ ገፋ እና እያየችው እንደሆነ ሲመለከት ቀስ ብሎ ፈገግ አለላት፡፡ ረጅምና ባለፈርጣማ ጡንቻ ነው፡፡ጠይምና አይናማ ነው፡፡ለግላጋ ቁመናው በአእምሮዋ ብልጭ ድርግም እያለ ሲታያት ተናደደች ፡፡ወደ ፊት ተመለከተች።ወደ ወላጆቿ ቤት የሚያመራውን መንገድ ክፍት መሆኑን ተገነዘበች፡፡ ሞተር ሳይክሉን እየስጮኸ ቀድሟት ተፈተለከ፡፡
ሲዲውን አወጣች፣ የምትፈልገውን ሙዚቃ የሚጫወት ኤፍ ኤም ጣቢያ ፍልጋ አገኘች እና ድምጹን ከፍ አደረገች። በምቾት እየነዳች ነው ፣ ነገ ስለምትሰራው ሥራ ምን ማድረግ እንዳለባት እቅድ ማውጣት ጀመረች ።አዎ የእሷን ትኩረት በቀጥታ የሚፈልጉ በርካታ ስራዎች አሉ፤ውስጧን የሚሸረካክታትን በበፊት ህይወቷ የተከሰቱ ጨለማ ትዝታዎችን ወደኃላ መተው አለባት።በግዙፍ የዛፍ ጥላዎችና በተለያዩ አትክልቶች ወደተሞላው ግዙፉ የወላጆቾ ቤት ደረሰች፡፡ መኪናዋን በሁለት ረድፍ ተከርክመው ባማሩ የፅድ ቁጥቋጦዎች መካከል ባለው ጠባብ መንገድ እየሰነጠቀች ወደ ዋናው ቤት እየቀረበች ነው። ‹‹ምሽቱ ጥሩ ሊሆን ነው ››ስትል አሰበች ።እንደገና እራሷን መቆጣጠር እንደቻለች ተሰማት።
አራት መኪና ለማቆም ወደሚችለው ጋራዥ ስትቀርብ የልብ ምቷ ጨመረ ።መንገድ ላይ አበሰጭቷት ያለፈው ባለ ሞተር ሳይክል ሰውዬ አሁን ከጋራዡ ፊት ለፊት ባለው የጡብ ግድግዳ አጠገብ ቆሟል፣ ሄልሜቱን በሞተር ሳይክሉ መሪ ላይ አንጠልጥሏል።መኪናዋን አመቻችታ አቆመች፡፡ የዮጋ መምህሯ እንዳስተማራት ረጅም ትንፋሽ ወደውስጦ ሳበች…መልሳ አስወጣች ፣ከንደገና ሳበች …። እራሷን ያረጋጋች ሲመስላት ለፀጋ የገዛችላትን ስጦታ አንሥታ በጥንቃቄ እየተራመደች ወደ መግቢያው በር አመራች። ‹ምናልባት ባለሞተር ሳይክሉ የሽያጭ ሰራተኛ ወይንም የሆነ መልዕክት ሊያደርስ የመጣ ሰው ሊሆን ይችላል።›ስትል አሰበች …ወይም ከቤቱ አገልጋዬች የአንደኛዋ ውሽማ ሊሆን እንደሚችልም ገመተች፡፡
በሩን አልፋ ወደውስጥ ስትገባ የቤታቸው ሰራተኛ አለም ‹‹እንኳን በደህና መጣሽ!!›› ብላ በታላቅ ፈገግታ ተቀበለቻት፡፡
‹‹አመሰግናለው…አለም››
‹‹ እናትሽ ኩሽና ውስጥ ነች..››
‹‹…ለጥቆማው አመሰግናለሁ ።እማዬ ምን አይነት ምግብ እንደሰራች ልትነግሪኝ ትችያለሽ?››
አለም ሚስጥራዊ የሆነ ፈገግታ ፈገግ እያለች‹‹ ላንቺ እና ለእንግዳቸው የበለጠ ባህላዊ ነገር የሚያዘጋጁ ይመስለኛል…ከስጋ ጥብስ እና ክትፎ ሲኖር ሌላው ጠቅላላ የጎሯ ምርት የሆነ ቅጠላቅጠል ነው….››የሚል መልስ ሰጠቻት፡፡
ራሄል‹‹አይ እማዬ እና ቅጠላ ቅጠል መች ይሆን የሚለያዩት!!››አለችና ያንን አስጠሊታ ሞተር ሳይክል እያከነፈ የመጣው ሰው ማን እንደሆነ ሳትጠይቃት ወደ ቤቱ ጀርባ ሄደች። ራሄል የፊት ለፊት ክፍል ግድግዳ ላይ የተንጠለጠለው መስታወት ውስጥ የራሷን ምስል ነጸብራቅ ተመለከተችና ቆም አለች፡፡ በመጠኑ የተዘበራረቀውን ፀጉሯን ለማስተካከል ትንሽ ጊዜ ወሰደባት፡፡ መላ አካሏ ንፁህ እና የተስተካከለ እንደሆነ አሰበች ። በጠባቡ ኮሪደር በኩል ወደ ኩሽና አመራች፡፡ እናቷ በዘመናዊው ኩሽና ውስጥ እንደ ደሴት የሚያገለግለው ግዙፉ መደርደሪያ ላይ ቆመው አትክልት ሲከትፉ አገኘቻቸው፡፡ ብርቱካናማ ልቅ ሽርጥ አድርጋገዋል፡፡ ወ.ሮ ትርሀስ ልጇቸውን ስያዩ ቢላዋዋን አስቀምጠው በሽርጣቸው ዙሪያ እጆቻቸውን እየጠራረጉ, ራሄልን እቅፏቸው ውስጥ አስገብተው አገላብጠው በመሳም ሞቅ ባለ ስሜት ተቀበሏት ‹‹በሰዓቱ በመምጣትሽ በጣም ደስ ብሎኛል ። ››
ራሄል እናቷን ሀዘን ባጠላባቸው አይኖቿ ተመለከተቻቸው።
‹‹ትንሽ የገረጣሽ ትመስያለሽ …ውዴ።?››
ራሄል ግልጽ ባልሆነ ምልክት እጇን አነሳችና ።‹‹ ስራ በዝቶብኝ ነበር..ሰሞኑን በቂ እንቅልፍ አላገኘውም…ለዛ ነው››
ለፀጋ ያመጣችውን ስጦታ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች። እናቷ ማስጠንቀቂያቸውን አጠንክረው ቀጠሉበት ‹‹ራስህሽን መንከባከብ አለብሽ …ሰውነታችን የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ነው …እግዚአብሔር በምድር ላይ ሥራውን ለመሥራት ጤናማ አገልጋዮች ያስፈልጉታል።››አሏት፡፡
ራሄል በእናቷ የተለመደ አይነት ንግግር ፈገግ አለች። በእግዚአብሔር ጉዳይ ላይ ከእናቷ ጋር ለመወያየት አልፈለገችም።ላለፉት ስምንት አመታት እግዚአብሔርን ከህይወቷ አስወጥታለች ወይም ለማስወጣት ሞክሯለች። የዚህም ምክንያት ‹‹ከእግዚአብሔር ፀሎቴን ቀብሮታል.. ህልሜን አክስሞታል…››ብላ ስለምታስብ ነው።እናቷ እጇቸውን በራሔል ትከሻ ላይ አድርገው ወደ ባንኮኒው ወሰዷት።
‹‹እኔና አባትሽ አንድ ደስ የሚል አስገራሚ ነገር አለን።የፀጋ ሐኪም መጥቶ እንዲጎበኘን ጋብዘነዋል።››
‹‹አሁን እዚህ አለ?››
እናትዬው በአውንታ ግንባራቸውን ነቀነቁ
‹‹ማለት ሞተር ሳይክ እየነዳ ቀድሞኝ የገባው ሰውዬ እንዳይሆን?››
‹‹አዎ››እናትዬው አረጋገጡላት፡፡‹‹አንቺም እሱን ለማግኘት ትፈልጊ ይሆናል ብዬ አሰብኩ››በማለት አከሉበት፡፡
እናትዬው በዘዴ ከዶ/ሩ ጋር ፊት ለፊት ከመጋፈጧ በፊት ስለሰውዬው የተወሰነ ግንዛቤ ሊያስጨብጧት እየሞከሩ እንደሆነ ገብቷታል፡፡
‹‹በሞተር ሳይክል ላይ ሳየው ግን ሞኝ መስሎ ነው የሚታየው›› ስትል ተናገረች፡፡
❤68👍6
‹‹ራሄል እንደዚህ አይነት ቃላትን መጠቀም የለብሽም።በተለይ እንደ ኤሊያስ ላለ ድንቅ ሰው።››
ራሄል እናቷ የሁለት ዓመቷን ፀጋን በማደጎ ልጅነት ወደቤታቸው ስትመጣ ለልጅ ልጆች ያላቸውን ሥር የሰደደ ፍላጎት እንደምታረካላቸው ተስፋ አድርጋ ነበር።እናም እሷን አግቢ ..ውለጂና የልጅ ልጅ አሳይን ብለው በየእለቱ የሚጨቀጭቋትን ጭቅጭቅ እንደሚያቆሙላት ትጠብቅ ነበር፡፡ አሁን እንደምታው ግን ያ ሽንቁር አሁንም እንዳለ መሆኑን ነው የገባት፡፡
‹‹አዝናለሁ እማዬ፣ እኔ እስከሚገባኝ ድረስ ማንም ሞተር ሳይክል የሚነዳ ሰው ኃላፊነት የሚሰማውና የሚተማመኑበት ሰው ይሆናል ብዬ አላምንም።ለዛውም የሕፃናት ሐኪም ሆኖ…ሞተር ሳይክል መንዳት።››ራሄል በጠረጴዛው ላይ ከተቀመጠው ጎድጓዳ ሳህን ውስጥ አንድ አነስ ያለ ካሮት ወሰደች እና ገመጠች።
እናትዬው ልጇቸው ስለሞተር ሳይክል አንስታ ስታወራ ምን ለማለት እደፈለገች ስለገባቸው ምንም ሊመልሱላት አልፈለጉም፡፡
ራሄል ‹‹አባዬ የት ነው ያለው?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹እሱ እና ዶ/ር ዔሊያስ ከፀጋ ጋር ሆነው ወደ አትክልት ስፍራ ወጥተዋል።እስከአሁን ተመልሰው እየመጡ እንደሆነ አምናለሁ።››
ራሄል ግቢውን ለማየት ወደ መስኮቱ ዞረች፣የመጨረሻውን የካሮት ቁርጭ አፏ ውስጥ ከታ እየኮረሸመች መመልከቷን ቀጠለች፡፡ በበር ኤሊያስ ከአባቷ ጋር ብቅ አለ፣ እጁን ዘርግቶ የፀጋን ፀጉር ከፊቷ ላይ ገልጦ ወደኃላ እያስተኛላት በለስላሳው ፈገግ አለ።ፀጋ በሩቅ ስታያት ሳቀችላት እና ወደ አባቷ ተጠጋች።ራሄል ከፊትለፊቷ ከአባቷ ጎን ያለውን ሰውዬ የእህቷ ዶክተር ይሆናል ብላ በአእምሮዋ ከቀረፀችው ፎቶ ጋር ምስሉን ማጣመር አልቻለችም።
‹‹ሞተር ሳይክሉን እየነዳ የነበረው ሰውዬ ማን ነበር?።››ራሷን ጠየቀችና ከመስኮቱ ዞር ብላ ወደእነሱ ተጠጋች፡፡
ራሄል አባቷ ወደ ክፍል ሲገባ ተመለከተች። ወደ ፊት ተንቀሳቀሰችና አባቷ እቅፍ ውስጥ ገባች …ትንሹን ሴት ልጁን በሌላኛው ክንድ ላይ አስተካክሎ አቀፋት..።‹‹ሰላም አባዬ››።
‹‹የእኔ ውድ ስላየሁሽ ደስ ብሎኛል››ፀጋን በጨረፍታ ተመለከተቻት፣ ወደ እሷ በመመልከት ሣቅች፣ የተጠማዘዘ ቡናማ ፀጉሯ እና የልብ ቅርጽ ያለው ፊቷን አስተዋለች፡፡ ሮዝ ቲሸርት እና ሰማያዊ ጂንስ ቱታ ለብሳለች። የእናቷን የልብስ ጣዕም ግምት ውስጥ በማስገባት የተለመደ አለባበስ ነው ስትል አሰበች.፡፡እሷም ልጅ እያለች ተመሳሳይ አይነት አለባበስ ታዘወትር ነበር፡፡
ራሄል በፈጣን ፈገግታ የእህቷን ትከሻ እየዳበሰች‹‹ሄይ፣ እህቴ››አለች ።ፀጋ ሚዛናዊ ሆና እጆቿን ወደ ራሄል ዘረጋች። ራሄል ወደ አባቷ እቅፍ መለሰቻት እና አንድ እርምጃ ከእነርሱ ርቃ ቆመች። ፀጋ ቆንጆ እና አፍቃሪ ሴት ነበረች። ራሄል ግን ለእሷ ያላትን በጎ ስሜት አሳይታት ስለማታውቅ ትንሽ ትጨነቃለች።ራሄል የወላጆቿን ልብ የማረከችውን ትንሽ መልአክ ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ስታያት መተንፈሻ መሳሪያ ተገጥሟላት ፣ ከ IV እና ከሌሎች ማሽኖች ጋር ተሳስራና እራሷን ስታ ነበር ። ፀጋ ሴሬብራል ፓልሲ የሚባል በሽታ ነበረባት፡፡በዚህ የተነሳ እንቅስቃሴ ማድረግ በጣም የምትቸገር..አጥንቶቾ ያልጠነከሩና የተልፈሰፈሰች..ከዛም በላይ ብዙ ተያያዥ ችግሮች ያሉባት ህፃን ነበረች፡፡እና በወቅቱ የወላጆቾን ውሳኔ ደፍራ ለመቃወም ባትደፍርም በጣም ያሳሰባትና ያስጨነቃት ነበር፡፡አሁን ግን በብዙ የህክምና ክትትልና የመድሀኒት እገዛ ቀስ በቀስ ከበሽታዋ እያገገመች ነው።ከብዙ ጊዜ በፊት ወላጆቿ ልጅ ተቀብለው ለማሳደግ ለማደጎ ተቋም አመልክተው ነበር ፀጋን ሲያዬት ግን እሷን ለማሳደግ እንደሚፈልጉ በመናገር የራሔልን አስተያየት ጠየቋት። በሰዓቱ ራሄል ጋንዲ ሆስፒታል ተኝታ የነበረችውን ፀጋን ልታያት ስትሄድ ለሆስፒታሎች ያላትን ጥላቻ ማሸነፍ እንደምትችል አስባ ነበር፣ ነገር ግን ከአምስት ደቂቃ በላይ ከጸጋ አልጋ አጠገብ መቆም አልቻለችም ነበር ። የመተንፈሻ አካሉ ጩኸት እና በአየሩ ላይ የተንሰራፋው የጸረ-ተባይ ጠረን በውስጦ የተዳፈነውን ቀፋፊ ትዝታ ነበር የቀሰቀሰባት፡፡ከዛም አልፎ በማቅለሽለሽ ማዕበል ተመታች።ለወላጆቿ መልካም ምኞቷን በመግለፅ ሆስፒታሉን ለቃ ወጣች…ከዛ ፀጋ የተወሰነ የጤና መሻሻል አሳይታ ወደቤት ከመጣች በኃላ ነው ያየቻት፡፡ ።ይሁን እንጂ አሁን ድረስ ልጅቷን ስታያት አቅመቢስነት እና ጣር የታከለበት ህመም እና ቀፋፊ የሆስፒታል ምስል ነው የሚታያት ።በዛ ምክንያት ረዘም ላለ ጊዜ ከአጠገቧ ለመቆየት ምቾት አይሰማትም።
ራሔል‹‹ ታንሿ እህቴ እነሆ ስጦታ አመጣሁልሽ።›› በማለት ለፀጋ የተጠቀለለውን እሽግ ሰጠቻት።
‹‹ምን ትያለሽ ማር?››አባቷ ቸርነት ፀጋን ስለስጦታው ምን እንደተሰማት ጠየቋት።
በኮላታፈ እና በሚጎተት አንደበቷ ‹‹አመሰግ…ና..ለው›› አለች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ራሄል እናቷ የሁለት ዓመቷን ፀጋን በማደጎ ልጅነት ወደቤታቸው ስትመጣ ለልጅ ልጆች ያላቸውን ሥር የሰደደ ፍላጎት እንደምታረካላቸው ተስፋ አድርጋ ነበር።እናም እሷን አግቢ ..ውለጂና የልጅ ልጅ አሳይን ብለው በየእለቱ የሚጨቀጭቋትን ጭቅጭቅ እንደሚያቆሙላት ትጠብቅ ነበር፡፡ አሁን እንደምታው ግን ያ ሽንቁር አሁንም እንዳለ መሆኑን ነው የገባት፡፡
‹‹አዝናለሁ እማዬ፣ እኔ እስከሚገባኝ ድረስ ማንም ሞተር ሳይክል የሚነዳ ሰው ኃላፊነት የሚሰማውና የሚተማመኑበት ሰው ይሆናል ብዬ አላምንም።ለዛውም የሕፃናት ሐኪም ሆኖ…ሞተር ሳይክል መንዳት።››ራሄል በጠረጴዛው ላይ ከተቀመጠው ጎድጓዳ ሳህን ውስጥ አንድ አነስ ያለ ካሮት ወሰደች እና ገመጠች።
እናትዬው ልጇቸው ስለሞተር ሳይክል አንስታ ስታወራ ምን ለማለት እደፈለገች ስለገባቸው ምንም ሊመልሱላት አልፈለጉም፡፡
ራሄል ‹‹አባዬ የት ነው ያለው?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹እሱ እና ዶ/ር ዔሊያስ ከፀጋ ጋር ሆነው ወደ አትክልት ስፍራ ወጥተዋል።እስከአሁን ተመልሰው እየመጡ እንደሆነ አምናለሁ።››
ራሄል ግቢውን ለማየት ወደ መስኮቱ ዞረች፣የመጨረሻውን የካሮት ቁርጭ አፏ ውስጥ ከታ እየኮረሸመች መመልከቷን ቀጠለች፡፡ በበር ኤሊያስ ከአባቷ ጋር ብቅ አለ፣ እጁን ዘርግቶ የፀጋን ፀጉር ከፊቷ ላይ ገልጦ ወደኃላ እያስተኛላት በለስላሳው ፈገግ አለ።ፀጋ በሩቅ ስታያት ሳቀችላት እና ወደ አባቷ ተጠጋች።ራሄል ከፊትለፊቷ ከአባቷ ጎን ያለውን ሰውዬ የእህቷ ዶክተር ይሆናል ብላ በአእምሮዋ ከቀረፀችው ፎቶ ጋር ምስሉን ማጣመር አልቻለችም።
‹‹ሞተር ሳይክሉን እየነዳ የነበረው ሰውዬ ማን ነበር?።››ራሷን ጠየቀችና ከመስኮቱ ዞር ብላ ወደእነሱ ተጠጋች፡፡
ራሄል አባቷ ወደ ክፍል ሲገባ ተመለከተች። ወደ ፊት ተንቀሳቀሰችና አባቷ እቅፍ ውስጥ ገባች …ትንሹን ሴት ልጁን በሌላኛው ክንድ ላይ አስተካክሎ አቀፋት..።‹‹ሰላም አባዬ››።
‹‹የእኔ ውድ ስላየሁሽ ደስ ብሎኛል››ፀጋን በጨረፍታ ተመለከተቻት፣ ወደ እሷ በመመልከት ሣቅች፣ የተጠማዘዘ ቡናማ ፀጉሯ እና የልብ ቅርጽ ያለው ፊቷን አስተዋለች፡፡ ሮዝ ቲሸርት እና ሰማያዊ ጂንስ ቱታ ለብሳለች። የእናቷን የልብስ ጣዕም ግምት ውስጥ በማስገባት የተለመደ አለባበስ ነው ስትል አሰበች.፡፡እሷም ልጅ እያለች ተመሳሳይ አይነት አለባበስ ታዘወትር ነበር፡፡
ራሄል በፈጣን ፈገግታ የእህቷን ትከሻ እየዳበሰች‹‹ሄይ፣ እህቴ››አለች ።ፀጋ ሚዛናዊ ሆና እጆቿን ወደ ራሄል ዘረጋች። ራሄል ወደ አባቷ እቅፍ መለሰቻት እና አንድ እርምጃ ከእነርሱ ርቃ ቆመች። ፀጋ ቆንጆ እና አፍቃሪ ሴት ነበረች። ራሄል ግን ለእሷ ያላትን በጎ ስሜት አሳይታት ስለማታውቅ ትንሽ ትጨነቃለች።ራሄል የወላጆቿን ልብ የማረከችውን ትንሽ መልአክ ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ስታያት መተንፈሻ መሳሪያ ተገጥሟላት ፣ ከ IV እና ከሌሎች ማሽኖች ጋር ተሳስራና እራሷን ስታ ነበር ። ፀጋ ሴሬብራል ፓልሲ የሚባል በሽታ ነበረባት፡፡በዚህ የተነሳ እንቅስቃሴ ማድረግ በጣም የምትቸገር..አጥንቶቾ ያልጠነከሩና የተልፈሰፈሰች..ከዛም በላይ ብዙ ተያያዥ ችግሮች ያሉባት ህፃን ነበረች፡፡እና በወቅቱ የወላጆቾን ውሳኔ ደፍራ ለመቃወም ባትደፍርም በጣም ያሳሰባትና ያስጨነቃት ነበር፡፡አሁን ግን በብዙ የህክምና ክትትልና የመድሀኒት እገዛ ቀስ በቀስ ከበሽታዋ እያገገመች ነው።ከብዙ ጊዜ በፊት ወላጆቿ ልጅ ተቀብለው ለማሳደግ ለማደጎ ተቋም አመልክተው ነበር ፀጋን ሲያዬት ግን እሷን ለማሳደግ እንደሚፈልጉ በመናገር የራሔልን አስተያየት ጠየቋት። በሰዓቱ ራሄል ጋንዲ ሆስፒታል ተኝታ የነበረችውን ፀጋን ልታያት ስትሄድ ለሆስፒታሎች ያላትን ጥላቻ ማሸነፍ እንደምትችል አስባ ነበር፣ ነገር ግን ከአምስት ደቂቃ በላይ ከጸጋ አልጋ አጠገብ መቆም አልቻለችም ነበር ። የመተንፈሻ አካሉ ጩኸት እና በአየሩ ላይ የተንሰራፋው የጸረ-ተባይ ጠረን በውስጦ የተዳፈነውን ቀፋፊ ትዝታ ነበር የቀሰቀሰባት፡፡ከዛም አልፎ በማቅለሽለሽ ማዕበል ተመታች።ለወላጆቿ መልካም ምኞቷን በመግለፅ ሆስፒታሉን ለቃ ወጣች…ከዛ ፀጋ የተወሰነ የጤና መሻሻል አሳይታ ወደቤት ከመጣች በኃላ ነው ያየቻት፡፡ ።ይሁን እንጂ አሁን ድረስ ልጅቷን ስታያት አቅመቢስነት እና ጣር የታከለበት ህመም እና ቀፋፊ የሆስፒታል ምስል ነው የሚታያት ።በዛ ምክንያት ረዘም ላለ ጊዜ ከአጠገቧ ለመቆየት ምቾት አይሰማትም።
ራሔል‹‹ ታንሿ እህቴ እነሆ ስጦታ አመጣሁልሽ።›› በማለት ለፀጋ የተጠቀለለውን እሽግ ሰጠቻት።
‹‹ምን ትያለሽ ማር?››አባቷ ቸርነት ፀጋን ስለስጦታው ምን እንደተሰማት ጠየቋት።
በኮላታፈ እና በሚጎተት አንደበቷ ‹‹አመሰግ…ና..ለው›› አለች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤76👍8
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ፀጋ አባቷ እቅፍ ላይ እንዳለች ፈገግ በማለት የራሄልን ትኩረት ለመያዝ ሞከረች፣ በዚህ ጊዜ እናቷ ጣልቃ ገብታ መናገር ጀመሩ ፡፡
‹‹ራሄል፣ ከዶክተር ኤሊያስን ጋር እንድትተዋወቂ እፈልጋለሁ። እሱ የፀጋ ሐኪም ነው…ዔሊ ይህች ልጃችን ራሄል ናት።››
ዶ/ሩ በስሱ ፈገግ በማለት ‹‹ሰለአንቺ ብዙ ሰምቼያለው ..አንድ ቀን እንደምንገናኝ አምን ነበር›› በማለት እጁን ወደ እሷ ዘረጋ
ጨዋነት ያልጎደለው ፈገግታ ፈገግ አለችለት እና የዘረጋውን እጅን ጨበጠች፡፡ወላጆቿ ከእሱ ጋር አማች ለመሆን እያሴሩ እና እሱንም እያደፋፈሩት እንደሆነ ታውቃለች…ቢሆንም የሱ ጥፋት አልነበረም።
‹‹የሞተር ሳይክሉ ሰው ነህ አይደል?››
‹‹አዎ… ነኝ›› አላት፡፡
እጁ ሞቃታማ፣ ጣቶቹ ረዣዥም ነበሩ፣ እና ሲነካት ለረጅም ጊዜ በእንቅልፍ የመወሰድ አይነት የግንዛቤ ብልጭታ በአእምሯዋ ተንፀባረቆ ነበር….ስሜቱን አልወደደችውም። ‹‹በዛ ፍጥነት ስታበር ገርሞኝ ነበር››አለችው፣ትንፋሽ ወሰደችና ‹‹ደግሞ ዶክተር መሆን እና …..››
‹‹እና ምን?›› ከአንደበቷ ቀልቦ ጠየቃት።
‹‹ከተሸከምከው ሃላፊነት አንፃር ሞተር ማሽከርከር….አንድ ነገር ቢደርስብህስ?››
‹‹ለጊዜው አቅሜ የሚፈቅደው ርካሹ እና ፈጣኑ መጓጓዣ ሞተር ነው. እና ደግሞ አስፈላጊውን ጥንቃቄ አደርጋለሁ.››ሲል መለሰላት፡፡
ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ‹‹ሁሉም የሚያቀነቅናቸው ታዋቂ የመጨረሻ ቃላቶች ናቸው…ጥንቃቄ አደርጋለው..››አለች በንዴት፡፡
በመጠኑ ደፍረስ ባሉት አይኖቹ በትኩረት ተመለከታት…ከመተዋወቃቸው እየሰጠችው ያለው ጠንከር ያለ አስተያየት ግራ አጋብቷታል…
እናትዬው ፀጋን ከአቶ ቸርነት እቅፍ ወሰድና፡፡‹‹በሉ ወደምግብ ጠረጴዛው እንሄድ….ምሳ ዝግጁ ነው››ሲሉ አወጁ፡፡
ሁሉም ወደምግብ ጠረጴዛው ተከታትለው ሄዱ፡፡ራሄል፣ የተለመደውን ቦታዋ ላይ ተቀምጣለች፣ ዔሊያስ ከእሷ ፊት ለፊት ተቀምጠ።››
አቶ ቸርነት በቀኝ እጇቸው የሴት ልጇቸውን እጅ ግራ እጇቸው ደግሞ በዔሊያስ ትከሻ ላይ ዘረጉና። ‹‹ብዙውን ጊዜ ከምግብ በፊት እንፀልያለን››ሲሉ ለዔሊያስ ገለጹለት።
‹‹እኔ ደስተኛ ነኝ. በቤተሰቦቼ ቤትም ስርዓቱ እንዲሁ ነው.››ሲል መለሰ፡፡አባቷ እጇን ጨምቀው ነበር፣መጸለይ ሲጀምሩ አንገቷን ዝቅ አደረገች።አባቷ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገሩ ማዳመጥ ብትጀምርም ከጸሎቱ ጋር በልቧ መቀላቀል አልቻለችም። እሷ በሀይማኖት ስርዓት ውስጥ ተወልዳ ያደገች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ ከመስመር ወጥታለች። አምላክ በህይወቷ ጣልቃ እንዲገባ አትፈልግም ወይም ደግሞም እሱ ራሱም ለእሷ ደንታ እንደሌለው ታምናለች።ስለዚህ ለምን ትጨቀጭቀዋለች፡፡ ወላጆቿ በዚህ መሳኔዋ ደስተኛ እንዳልሆኑ በደንብ ታውቃለች ቢሆንም ግን ርቀታቸውን በመጠበቃቸው ታመሰግናቸዋለች። እና ምናልባት ወደቀልቧ እንድትመለስ ዘወትር ለእሷ በድብቅ ይፀልዩላት ይሆናል፡፡
ፀሎቱ ተገባዶ በ‹‹አሜን›› እንደተዘጋ እናትዬው ‹‹በሉ እራሳችሁን አስተናግዱ ››አለቻቸው፡፡ሁሉም ፊት ለፊቱ ባለው ሳህን ላይ ፊለፊታቸው ከተደረደሩት በርካታ የምግብ ዓይነቶች የሚፈልጉትን መጠን መውሰድ ጀመሩ፡፡ተ
‹‹ከቻልክ ክትፎውን አቀብለኝ››ስትል ራሄል ወደኤልያስ እያየች አጉተመተመች፣
እናትዬው የራሄልን አስተያየት ውድቅ በማድረግ እጆቿን እያወዛወዘ ‹‹እስኪ እንደአንበሳ ስጋ ማሳደድሽን አቁሚ።››በማለት ገሰፃት፡፡ ቀጠል አደረጉና ‹‹ለሚያገባሽ ሰው አዝንለታለው።››ሲሉ አከሉበት፡፡
‹‹ደህና፣ ደስ ሚለው ነገር ፍቅረኛ የለኝም ››አለች ራሄል፡፡
‹‹እነዚህማ የተለመዱ ቃላቷችሽ ናቸው››
እናቷ በራሄል ንግግር ተከፍተው ‹‹አንድ ቀን ያንን በብቸኝነት የቀዘቀዘ አፓርታማሽን እርግፍ አድርገሽ ጥለሽ እንደ ዶ/ር ኤሊያስ ቤት አይነት ግቢ ወዳለው ቤት ትቀይሪ ይሆናል።››ሲሉ ምኞታቸውን ተናገሩ፡፡
እናትዬው ወደ ዶ/ሩ ዘወር አሉን‹‹ቤትህን በማስተካከል ላይ እንዳለህ ሰምቼያለው?››
‹‹በእውነቱ ወንድሜ ቢንያም ነው እየተከታተለው ያለው። እሱ አናጺ ነው። ስለ ኩሽና አሰራር አንዳንድ ውሳኔዎችን እንድወስን እየጨቀጨቀኝ ነበር, ነገር ግን ዘመናዊ ይሁን ወይም ባህላዊ ጭብጥ ይኑረው የሚለውን ለመወሰን እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም››
አቶ ቸርነት‹‹ራሄልን ይዘሀት ብትሄድ ልትረዳህ ትችል ይሆናል››የሚል ሀሳብ አቀረቡለት። ዔሊያስ የራሔልን መኮሳተር ችላ በማለት እንደ ተወደደ ልጅ ፊቱ እያበራ ነው።
አንቷም ‹‹አዎ የእኔ ልጅ …በኢንቴርዬር ዲዛይን ላይ በጣም ጎበዝ ነች።››ሲሉ የአባትዬውን ሀሳብ ደገፉ፡፡
ራሄል ስለእሷ የተሰጠ ያለው አስተያየት ከየት እንደመጣ አታውቅም። ወላጆቿ አፓርታማዋን በሚጎበኙበት ጊዜ በዕቃዎቾ፤በምንጣፎች እና በመኝታ ቤቷ ቀለም ..ብዙ ብዙ ኔጌቲቨ የሆነ አስተያየት ሲሰጧት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡ እንደውም እናቷ ‹ጥቂት እንኳን ለስሜቷ ሳይጨነቁ ቤቷን መኖሪያ ቤት ሳይሆን ሙዚየም እንዳስመሰለችው ነግረዋት ነበር፡፡
‹‹የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ። ትልቁ ችግሬ ግን ውሳኔዎችን ለመወሰን ጊዜ ማግኘት አለመቻሌ ነው ›› ሲል ኤሊያስ መለሰ።
ራሄል የሆነውን ነገር የተረዳች መስላ‹‹እንድትጨርሰው የምትገፋፋህ ሴት የለችም?››ስትል ጠየቀችው፡፡
አባቷ ራሄልን በግንባራቸው ገፆት ፡፡
ዶ/ሩ ‹‹ለጊዜው አቋሜ ልክ እንደአንቺው ነው….ለሴት ዝግጁ አይደለሁም››ሲል መለሰ።
ራሄል ውይይቱ ወደ መሃል ከተማ የትራፊክ ፍሰት፣ የኑሮው ውድነትና ፣ እና የፖለቲካ ውዥንብር.እና የሰላም እጦት የመሳሰሉት ጉዳዬች ላይ ሲያተኩር እፎይ አለች፡፡
በመሀል ወደ ዶ/ሩ አትኩራ እየተመለከተች ‹‹በቅርቡ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አለ።በዝግጅቱ ላይ መገኘትህን ማረጋገጥ አለብህ››አለችው፡፡
‹አረ ችግር የለውም..አታስቢ እገኛለው››ሲል ቃል ገባላት፡፡
እናትዬው‹‹ቀኑ ደረሰ እንዴ..?እንግዲህ በስራ ጫና ድራሽሽ ሊጠፋ ነው››ሲሉ ስጋታቸውን ገለፁላት፡፡
ራሄል ‹‹እማዬ ደግሞ ….እኔ ብቻዬን የማደርገውን አስመሰልሺው ። አብዛኛውን ስራ የሚሰሩልኝ ትላልቅ ሰራተኞች አሉኝ እኮ››
‹‹ነገር ግን ለሰራተኞችሽ በቂ ውክልና አትሰጪም።ቅድስትን ለመተካት እነዚያን ሁለቱን ረዳቶች መቅጠርሽን ስሰማ ብዙ የስራ ጫናሽን ያቃልሉልሻል ብዬ አስቤ ነበር። ነገር ግን አሁን እንደማየው ከሆነ የበለጠ ስራ ነው ያበዛብሽ፡፡››
‹‹ሰራተኞቹ በጣም አዲስ ናቸው ። ፋይሎቹን ብቻ ሰጥቻቸው ሁሉንም ነገር በራሳቸው እንዲቋቋሙት መጠበቅ አልችልም።››
‹‹ዬኒቨርሲቲ ዲግሪ ያላቸውና …በደንብ የሰለጠኑ ናቸው እኮ።››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ግን የፋውንዴሽኑን ስራ በተመለከተ ትንሽ ተጨማሪ ልምድ ያስፈልጋቸዋል፣ሁሉም ሰው ወደሆነ አዲስ ስራ ሲሄድ ለተወሰነ ጊዜ ከአሰራሩ ጋር እስኪለማመድ አዲስ ሆኖ መገኘት አይቀርም››ለእናቷ ሌላ የማስጠንቀቂያ እይታ ሰጠቻት። ይህን ጉዳይ ሙሉ በሙሉ በማያውቁት ሰው ፊት መወያየታቸውን አልወደደችውም ።
‹‹ውዴ እወድሻለሁ፣ ግን ደግሞ አውቅሻለሁ።››ሲሉ እናትዬው በአቋማቸው መፅናታቸውን አረጋገጡላት፡፡
የራሄልን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት ‹‹እና ሁሉንም ነገር መቆጣጠር እንደምትችይ ማሰብ ማቆም አለብሽ። አንዳንድ ነገሮችን ለእግዚአብሔርን መልቀቅ አለብሽ።››ሲሉ ንግግራቸውን ደመደሙ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ፀጋ አባቷ እቅፍ ላይ እንዳለች ፈገግ በማለት የራሄልን ትኩረት ለመያዝ ሞከረች፣ በዚህ ጊዜ እናቷ ጣልቃ ገብታ መናገር ጀመሩ ፡፡
‹‹ራሄል፣ ከዶክተር ኤሊያስን ጋር እንድትተዋወቂ እፈልጋለሁ። እሱ የፀጋ ሐኪም ነው…ዔሊ ይህች ልጃችን ራሄል ናት።››
ዶ/ሩ በስሱ ፈገግ በማለት ‹‹ሰለአንቺ ብዙ ሰምቼያለው ..አንድ ቀን እንደምንገናኝ አምን ነበር›› በማለት እጁን ወደ እሷ ዘረጋ
ጨዋነት ያልጎደለው ፈገግታ ፈገግ አለችለት እና የዘረጋውን እጅን ጨበጠች፡፡ወላጆቿ ከእሱ ጋር አማች ለመሆን እያሴሩ እና እሱንም እያደፋፈሩት እንደሆነ ታውቃለች…ቢሆንም የሱ ጥፋት አልነበረም።
‹‹የሞተር ሳይክሉ ሰው ነህ አይደል?››
‹‹አዎ… ነኝ›› አላት፡፡
እጁ ሞቃታማ፣ ጣቶቹ ረዣዥም ነበሩ፣ እና ሲነካት ለረጅም ጊዜ በእንቅልፍ የመወሰድ አይነት የግንዛቤ ብልጭታ በአእምሯዋ ተንፀባረቆ ነበር….ስሜቱን አልወደደችውም። ‹‹በዛ ፍጥነት ስታበር ገርሞኝ ነበር››አለችው፣ትንፋሽ ወሰደችና ‹‹ደግሞ ዶክተር መሆን እና …..››
‹‹እና ምን?›› ከአንደበቷ ቀልቦ ጠየቃት።
‹‹ከተሸከምከው ሃላፊነት አንፃር ሞተር ማሽከርከር….አንድ ነገር ቢደርስብህስ?››
‹‹ለጊዜው አቅሜ የሚፈቅደው ርካሹ እና ፈጣኑ መጓጓዣ ሞተር ነው. እና ደግሞ አስፈላጊውን ጥንቃቄ አደርጋለሁ.››ሲል መለሰላት፡፡
ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ‹‹ሁሉም የሚያቀነቅናቸው ታዋቂ የመጨረሻ ቃላቶች ናቸው…ጥንቃቄ አደርጋለው..››አለች በንዴት፡፡
በመጠኑ ደፍረስ ባሉት አይኖቹ በትኩረት ተመለከታት…ከመተዋወቃቸው እየሰጠችው ያለው ጠንከር ያለ አስተያየት ግራ አጋብቷታል…
እናትዬው ፀጋን ከአቶ ቸርነት እቅፍ ወሰድና፡፡‹‹በሉ ወደምግብ ጠረጴዛው እንሄድ….ምሳ ዝግጁ ነው››ሲሉ አወጁ፡፡
ሁሉም ወደምግብ ጠረጴዛው ተከታትለው ሄዱ፡፡ራሄል፣ የተለመደውን ቦታዋ ላይ ተቀምጣለች፣ ዔሊያስ ከእሷ ፊት ለፊት ተቀምጠ።››
አቶ ቸርነት በቀኝ እጇቸው የሴት ልጇቸውን እጅ ግራ እጇቸው ደግሞ በዔሊያስ ትከሻ ላይ ዘረጉና። ‹‹ብዙውን ጊዜ ከምግብ በፊት እንፀልያለን››ሲሉ ለዔሊያስ ገለጹለት።
‹‹እኔ ደስተኛ ነኝ. በቤተሰቦቼ ቤትም ስርዓቱ እንዲሁ ነው.››ሲል መለሰ፡፡አባቷ እጇን ጨምቀው ነበር፣መጸለይ ሲጀምሩ አንገቷን ዝቅ አደረገች።አባቷ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገሩ ማዳመጥ ብትጀምርም ከጸሎቱ ጋር በልቧ መቀላቀል አልቻለችም። እሷ በሀይማኖት ስርዓት ውስጥ ተወልዳ ያደገች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ ከመስመር ወጥታለች። አምላክ በህይወቷ ጣልቃ እንዲገባ አትፈልግም ወይም ደግሞም እሱ ራሱም ለእሷ ደንታ እንደሌለው ታምናለች።ስለዚህ ለምን ትጨቀጭቀዋለች፡፡ ወላጆቿ በዚህ መሳኔዋ ደስተኛ እንዳልሆኑ በደንብ ታውቃለች ቢሆንም ግን ርቀታቸውን በመጠበቃቸው ታመሰግናቸዋለች። እና ምናልባት ወደቀልቧ እንድትመለስ ዘወትር ለእሷ በድብቅ ይፀልዩላት ይሆናል፡፡
ፀሎቱ ተገባዶ በ‹‹አሜን›› እንደተዘጋ እናትዬው ‹‹በሉ እራሳችሁን አስተናግዱ ››አለቻቸው፡፡ሁሉም ፊት ለፊቱ ባለው ሳህን ላይ ፊለፊታቸው ከተደረደሩት በርካታ የምግብ ዓይነቶች የሚፈልጉትን መጠን መውሰድ ጀመሩ፡፡ተ
‹‹ከቻልክ ክትፎውን አቀብለኝ››ስትል ራሄል ወደኤልያስ እያየች አጉተመተመች፣
እናትዬው የራሄልን አስተያየት ውድቅ በማድረግ እጆቿን እያወዛወዘ ‹‹እስኪ እንደአንበሳ ስጋ ማሳደድሽን አቁሚ።››በማለት ገሰፃት፡፡ ቀጠል አደረጉና ‹‹ለሚያገባሽ ሰው አዝንለታለው።››ሲሉ አከሉበት፡፡
‹‹ደህና፣ ደስ ሚለው ነገር ፍቅረኛ የለኝም ››አለች ራሄል፡፡
‹‹እነዚህማ የተለመዱ ቃላቷችሽ ናቸው››
እናቷ በራሄል ንግግር ተከፍተው ‹‹አንድ ቀን ያንን በብቸኝነት የቀዘቀዘ አፓርታማሽን እርግፍ አድርገሽ ጥለሽ እንደ ዶ/ር ኤሊያስ ቤት አይነት ግቢ ወዳለው ቤት ትቀይሪ ይሆናል።››ሲሉ ምኞታቸውን ተናገሩ፡፡
እናትዬው ወደ ዶ/ሩ ዘወር አሉን‹‹ቤትህን በማስተካከል ላይ እንዳለህ ሰምቼያለው?››
‹‹በእውነቱ ወንድሜ ቢንያም ነው እየተከታተለው ያለው። እሱ አናጺ ነው። ስለ ኩሽና አሰራር አንዳንድ ውሳኔዎችን እንድወስን እየጨቀጨቀኝ ነበር, ነገር ግን ዘመናዊ ይሁን ወይም ባህላዊ ጭብጥ ይኑረው የሚለውን ለመወሰን እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም››
አቶ ቸርነት‹‹ራሄልን ይዘሀት ብትሄድ ልትረዳህ ትችል ይሆናል››የሚል ሀሳብ አቀረቡለት። ዔሊያስ የራሔልን መኮሳተር ችላ በማለት እንደ ተወደደ ልጅ ፊቱ እያበራ ነው።
አንቷም ‹‹አዎ የእኔ ልጅ …በኢንቴርዬር ዲዛይን ላይ በጣም ጎበዝ ነች።››ሲሉ የአባትዬውን ሀሳብ ደገፉ፡፡
ራሄል ስለእሷ የተሰጠ ያለው አስተያየት ከየት እንደመጣ አታውቅም። ወላጆቿ አፓርታማዋን በሚጎበኙበት ጊዜ በዕቃዎቾ፤በምንጣፎች እና በመኝታ ቤቷ ቀለም ..ብዙ ብዙ ኔጌቲቨ የሆነ አስተያየት ሲሰጧት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡ እንደውም እናቷ ‹ጥቂት እንኳን ለስሜቷ ሳይጨነቁ ቤቷን መኖሪያ ቤት ሳይሆን ሙዚየም እንዳስመሰለችው ነግረዋት ነበር፡፡
‹‹የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ። ትልቁ ችግሬ ግን ውሳኔዎችን ለመወሰን ጊዜ ማግኘት አለመቻሌ ነው ›› ሲል ኤሊያስ መለሰ።
ራሄል የሆነውን ነገር የተረዳች መስላ‹‹እንድትጨርሰው የምትገፋፋህ ሴት የለችም?››ስትል ጠየቀችው፡፡
አባቷ ራሄልን በግንባራቸው ገፆት ፡፡
ዶ/ሩ ‹‹ለጊዜው አቋሜ ልክ እንደአንቺው ነው….ለሴት ዝግጁ አይደለሁም››ሲል መለሰ።
ራሄል ውይይቱ ወደ መሃል ከተማ የትራፊክ ፍሰት፣ የኑሮው ውድነትና ፣ እና የፖለቲካ ውዥንብር.እና የሰላም እጦት የመሳሰሉት ጉዳዬች ላይ ሲያተኩር እፎይ አለች፡፡
በመሀል ወደ ዶ/ሩ አትኩራ እየተመለከተች ‹‹በቅርቡ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አለ።በዝግጅቱ ላይ መገኘትህን ማረጋገጥ አለብህ››አለችው፡፡
‹አረ ችግር የለውም..አታስቢ እገኛለው››ሲል ቃል ገባላት፡፡
እናትዬው‹‹ቀኑ ደረሰ እንዴ..?እንግዲህ በስራ ጫና ድራሽሽ ሊጠፋ ነው››ሲሉ ስጋታቸውን ገለፁላት፡፡
ራሄል ‹‹እማዬ ደግሞ ….እኔ ብቻዬን የማደርገውን አስመሰልሺው ። አብዛኛውን ስራ የሚሰሩልኝ ትላልቅ ሰራተኞች አሉኝ እኮ››
‹‹ነገር ግን ለሰራተኞችሽ በቂ ውክልና አትሰጪም።ቅድስትን ለመተካት እነዚያን ሁለቱን ረዳቶች መቅጠርሽን ስሰማ ብዙ የስራ ጫናሽን ያቃልሉልሻል ብዬ አስቤ ነበር። ነገር ግን አሁን እንደማየው ከሆነ የበለጠ ስራ ነው ያበዛብሽ፡፡››
‹‹ሰራተኞቹ በጣም አዲስ ናቸው ። ፋይሎቹን ብቻ ሰጥቻቸው ሁሉንም ነገር በራሳቸው እንዲቋቋሙት መጠበቅ አልችልም።››
‹‹ዬኒቨርሲቲ ዲግሪ ያላቸውና …በደንብ የሰለጠኑ ናቸው እኮ።››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ግን የፋውንዴሽኑን ስራ በተመለከተ ትንሽ ተጨማሪ ልምድ ያስፈልጋቸዋል፣ሁሉም ሰው ወደሆነ አዲስ ስራ ሲሄድ ለተወሰነ ጊዜ ከአሰራሩ ጋር እስኪለማመድ አዲስ ሆኖ መገኘት አይቀርም››ለእናቷ ሌላ የማስጠንቀቂያ እይታ ሰጠቻት። ይህን ጉዳይ ሙሉ በሙሉ በማያውቁት ሰው ፊት መወያየታቸውን አልወደደችውም ።
‹‹ውዴ እወድሻለሁ፣ ግን ደግሞ አውቅሻለሁ።››ሲሉ እናትዬው በአቋማቸው መፅናታቸውን አረጋገጡላት፡፡
የራሄልን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት ‹‹እና ሁሉንም ነገር መቆጣጠር እንደምትችይ ማሰብ ማቆም አለብሽ። አንዳንድ ነገሮችን ለእግዚአብሔርን መልቀቅ አለብሽ።››ሲሉ ንግግራቸውን ደመደሙ፡፡
❤53👍5
‹‹እኔም ለእሱ ውክልና መስጠት አልፈልግም››ስትል ራሄል በመኮሳተር መለሰች።
የእናትና ልጅን ንግግር መክረርን የታዘቡት አባት ‹‹ርዕሱን መለወጥ እንችላለን?››ሲሉ ጣልቃ ገቡ፡፡
እናትዬው የፀጋን ፀጉር እየዳበሱ ‹እህትሽ መያዝ ትፈልጊያለሽ?››ብለው ጠየቋት።ራሄል በእናቷ እቅፍ ውስጥ ተመችቷት የተኛችውን ታዳጊ ተመለከተች። ይሄኛውም የሚመቻት የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ አልነበረም።እሺ ብላ ተቀብላ መያዝ እንዳለባት ታውቃለች፣ነገር ግን ስህተት እንዳትሰራ ፈራች።
ዔሊያስም ፍርሃቷን እንደተረዳ በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ‹‹አይዞሽ ..ታደርጊዋለሽ›› ሲል አበረታታት፡፡ማበረታቻውን ግን እንደለበጣ ነው የቆጠረችው፡፡ፀጋን በጎሪጥ ተመለከተች… ዓይኖቾ እየተቁለጨለጩ እሷን ሲመለከቱ አየች። እጆቾ ተዘርግተዋል …እግሮቿ ግትርትር እንዳሉ ነው…. ፀጋ በድንገት አሳዛኝ ለቅሶ አሰማች ።
‹‹ ልጄ፣አይዞሽ….›› ወ.ሮ ትራሀስ ለራሄል ሊያስታቅፏት ሞከሩ… ፀጋ ግን ፍቃደኛ አልሆነችም። ራሄል ወደ ፊት ተወረወረች እና የፀጋን የተወጣጠረ ሰውነት በማየቷ ልቧ ደረቷ ውስጥ ዘሎ የተሰነቀረ መሰላት።ዶ/ር ኤሊያስም መቀመጫውን ለቆ ፈጠን ብሎ ስሯ ተቀመጠና የፀጋን ሰውነት እያገለባበጠ ተመለከታት ‹‹ የጡንቻ መወጠር ይመስላል እግሮቿን መታሸት አለባቸው››አለ ፡፡ ወ.ሮ ትርሀስ እንደተናገረው የፀጋን እግሮች ማሻሸት ጀመሩ… እናም ሰውነቷ ቀስ እያለ ሲዝናና ራሄል በእፎይታ ተነፈሰች።
‹‹አየሽ? መጥፎ አይደለም››
‹‹አይ. ቢሆንም ትንሽ ፈርቼ ነበር››አለች ራሄል፡፡
ወ.ሮ ትርሀስ ወደ ራሄል ተመለከቱና እና ‹‹አሁንስ እሷን መያዝ ትችያለሽ?››ሲሉ ድጋሚ ጠየቋት፡፡
ራሄል መልስ ከመስጠቷ በፊት ኪሷ ውስጥ ያለው ስልክ ጮኸ ፡፡ አውጥታ ስታየው የደወለላትን ሮቤል ነበር፡፡ልክ እንደአዳኟ መልአክ ነበር የቆጠረችው።
‹‹ይቅርታ እማዬ ይህን ጥሪ ማንሳት አለብኝ››በማለት ይቅርታ ጠይቃና ለተፈጠረው ችግር አመሰግናለሁ፣ ኮሪደሩን ተጠቅማ ወደ ጓሮ በመሄድ ስልኩን አነሳችው፡፡
‹‹ሮቤል እንዴት ነህ?››አለችው።
‹‹ደህና ነኝ …ሴትዬዋ እንደገና ሀሳቧን ቀይራለች››አእምሮዋ በዚህ አዲስ ችግር ዙሪያ ተወጣጠረ፡፡ ራሄል ሁል ጊዜ ስትጨናነቅ እንደምታደርገው ጥፍሯን በጥርሶቿ ቀረጠፈች።‹‹ዛሬ ልታገኘን እንደምትፈልግ ተናግራለች›› ሮቤል ቀጠለ። ‹‹በእርግጥም ከአርባ አምስት ደቂቃ በፊት እዚያ መሆን ነበረብሽ.. ነገር ግን በወላጆችሽ ቤት እንደሆንሽ ስለሰማው ተውኩት።››አላት፡፡
የእህቷ ረዳት አልባ ለቅሶ ድምፅ ስታስታውስ ትንሽ ደነገጠች። ይህቺን በህመም የምትሰቃይ እና ከፍተኛ እንክብካቤ የምትፈልግ ህፃን ልጅ ለማሳደግ ወስነው በመውሰዳቸው ወላጆቿን በጣም አደነቀቻቸው። እሷ በእንሱ ቦታ ብትሆን ፈፅሞ ማድረግ እንደማትችል ታውቃለች።
‹‹ይቅርታ አድርግልኝ?››
‹‹ግድ የለም አሁን ችግሩ ምንድን ነው?››
‹‹ወ/ሮ ላምሮት የፋውንዴሽኑን የሩብ አመት ሪፖርት ማየት ትፈልጋለች። በእድገት ላይ እንደሆነ ማረጋገጥ ትፈልጋለች።››
ዔሊያስን በበሩ ላይ በዛ ቁመቱ ተጋርጦ ቆሞ ተመለከተችው።
‹‹እናትሽ በበረንዳው ላይ ኬክ እና ቡና እየቀረበ እንደሆነ እንድነግርሽ ጠይቃውኝ ነው›› አላት፡፡
‹‹አመሰግናለሁ… ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሁላችሁንም እቀላቀላችኋለው››በማለት ጠንከር ያለ ፈገግታ ሰጠችው፣
እሱ ግን ምንም አይነት የስሜት ለውጥ ሳያሳይ ፊቱን አዙሮ ሄደ። ከእሱ ጋር በመተዋወቋ ግልፅ ያልሆነ ምቾት እንደተሰማት መካድ አትችልም።የፀጋ ማራኪ ሐኪም ስለ እሷ ምን እንደሚያስብ ለማወቅ ለምን እንደምትጨነቅ አሰበች..እንደምንም እራሷን አረጋግታ ትኩረቷን ወደ ሮቤል መለሰች።
‹‹በሰዓቱ እንደምገኝ ለወይዘሮ ላምሮት ንገርልኝ››በመስኮቱ አሻግራ በአባቷ ጥናት ክፍል ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የአያቷን ሰዓት ተመለከተች። ‹‹አንድ ሰዓት ያህል አላት››
‹‹ራሄል አንቺን ማጨናነቅ አልፈልግም ነበር….ግን ቶሎ ልታደርጊው ትችያለሽ?››
‹‹አዎ እችላለው፣ሴትዬዋ የምትኖረው በቸርቸል ጎዳና አካባቢ ነው...በ50 ደቂቃ እዚያ ለመድረስ ብዙም የምቸገር አይመስለኝም… ወላጆቼን ብቻ ተሰናብቼ አሁኑኑ ወጣለው ። ››
‹‹እሺ እንግዲህ፣ ስትደርሺ እዛው ቀድሜ እጠብቅሻለው::›› ራሄል ከንፈሯን ነክሳ የስልኩን ቁልፉ ተጫነችና ዘጋችው።አሁን ልሄድ ነው በማለቷ ወላጇቾ ደስተኛ አይሆኑም, ነገር ግን በዚህ ጉዳይ ምንም ማድረግ አትችልም. ወ.ሮ ላምሮት ለፋውንዴሽኑ በጣም አስፈላጊ ሴት ነች። ዝግጅቶች በምታዘጋጅበት ጊዜ የታዋቂ እንግዶች ዝርዝር ለማውጣት በሚያስፈልግበት ጊዜ እሷ ከዋናዎቹ የዘወትር ለጋሾች ውስጥ ዋነኛዋ ነች።ወ.ሮ ላምሮት ባሏ ሲሞት ብዙ ገንዘብ በውርስ አግኝታለች፤በዛ ላይ በሀገሪቱ በብዙ ካምፓኒዎችን ታስተዳድራለች….እናም በባሏ ኑዛዜ መሰረት ከአመታዊ ትርፏ 25 ፐርሰንት ለበጎ አድራጎት ድርጅት መስጠት አለባት…እንግዲህ የእሷን ፋውንዴሽን ጨምሮ ሁሉም በሀገሪቱ በበጎአድራጎት ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች በጠቅላላ የእሷን ገንዘብ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ…. ። ራሄል ይህቺን ሴት በትክክል ካልያዘች፣በቀላሉ የእሷ ካምፑ በመልቀቅ ለተቀናቃኞ ፋውንዴሽን ገንዘቧን ለመስጠት ልትወስን ትችላለች። ህጋዊ የሚመስሉ ነገር ግን እስከ ሰማንያ በመቶ የሚሆነውን የለጋሾቻቸውን ገንዘብ “የአስተዳደር ክፍያ” ስም ለግል ጥቅማቸው ስለሚያውሉ ድርጅቶችን በሰማች ቁጥር የራሄል ደም እንዲፈላ ነው የሚያደርጋት፡፡እና የሴትዬዋን ልገሳ የማይሆኑ ድርጅቶች እጅ ገብቶ የግለሰቦች ኑሮ መዶጎሚያ እንዳይሆን መከላከልም አንደኛው አላማዋ ነው፡፡በእሷ ድርጅት የአስተዳደር ወጪ ከ25 በርሰንት መብለጥ እንደሌለበት ጥብቅ የሆነ መመሪያ አለ፡፡ለዛም ነው በዋናው ቢሮ ከሁለት ረዳቷቾ ጋር ሆና የአስር ሰው ስራ የምትሰራው፡፡
ወደውስጥ ስትገባ ወላጆቿ ቀደም ብለው በረንዳ ላይ ተቀምጠው ነበር ፣ የቀዘቀዘ ሻይ የያዘ ረጅም ኩባያ ከፊት ለፊታቸው ባለው የመስታወት ጠረጴዛ ላይ ይታያል።
ራሄል ስትደርስ ፀጋ በእግሮቾ ላይ ትልቅ ብርድ ልብስ ለብሳ እየተጫወተች ነበር፣ ለራሄል ፈገግ አለችላት፣ ቀላል ቡናማ አይኖቿ በምሽት መጀመሪያ ላይ ሲያበሩ ስትመለከት ደስ አላት። ራሄል ቆንጆ መሆኗን በውስጧ አሰበች፡፡
‹‹ እማዬ፣ አባዬ፣ ይቅርታ ዶ/ር …››ዓይኖቿ ዔሊያስ ላይ ተተከሉ ፣ ‹ አዝናለሁ ግን ሮቤል አሁን ደወሎኝ ነበር። ከለጋሾቻችን ከአንዷ ጋር ድንገተኛ ችግር ገጥሞናል ።ሄጄ ማስተካከል አለብኝ››
‹‹ኧረ ማር፣ ለምን እሱ ራሱ እንዲያስተካክለው አትተይለትም?››እናትዬው ተቃወሟት ፡፡
ወ.ሮ ትርሀስ ወደ ባላቸው ዞረው። ‹‹ቸርነት ፣ አናግራት እንጂ ።››አቶ ቸርነት ዝም ብለው ትከሻቸውን ከፍ በማድረግ ለልጃቸው ፈገግ አሉ።
‹‹ብትቆዪ ምኞቴ ነው ውዴ። ብዙ ጊዜ አናገኝሽም። ትንሿ እህትሽ እንኳን በደንብ አታውቅሽም…ከዚህ በተጨማሪ፣ እናትሽ ለአንቺ ብቻ ያዘጋጀችው የቸኮሌት ኬክ አለ›› አላት፡፡
ወ.ሮ ትርሀስም ‹‹አባትሽን ታውቂዋለሽ እና እኔም እንደዚህ አይነት ነገር አልበላም.››
‹‹በጣም አዝናለሁ እናቴ፣ ግን ኬኩን ብወስደው ደስ ይለኛል -››
‹‹እንግዲህ አልቆይም ካልሽ ምን አደርጋለው…አዘጋጅልሻለሁ።››ወ.ሮ ትርሀስ ከወንበራቸው ተነስተው ቆሙ‹‹በፍጥነት እመለሳለሁ››ብለው ወደውስጥ ገቡ፡፡
የእናትና ልጅን ንግግር መክረርን የታዘቡት አባት ‹‹ርዕሱን መለወጥ እንችላለን?››ሲሉ ጣልቃ ገቡ፡፡
እናትዬው የፀጋን ፀጉር እየዳበሱ ‹እህትሽ መያዝ ትፈልጊያለሽ?››ብለው ጠየቋት።ራሄል በእናቷ እቅፍ ውስጥ ተመችቷት የተኛችውን ታዳጊ ተመለከተች። ይሄኛውም የሚመቻት የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ አልነበረም።እሺ ብላ ተቀብላ መያዝ እንዳለባት ታውቃለች፣ነገር ግን ስህተት እንዳትሰራ ፈራች።
ዔሊያስም ፍርሃቷን እንደተረዳ በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ‹‹አይዞሽ ..ታደርጊዋለሽ›› ሲል አበረታታት፡፡ማበረታቻውን ግን እንደለበጣ ነው የቆጠረችው፡፡ፀጋን በጎሪጥ ተመለከተች… ዓይኖቾ እየተቁለጨለጩ እሷን ሲመለከቱ አየች። እጆቾ ተዘርግተዋል …እግሮቿ ግትርትር እንዳሉ ነው…. ፀጋ በድንገት አሳዛኝ ለቅሶ አሰማች ።
‹‹ ልጄ፣አይዞሽ….›› ወ.ሮ ትራሀስ ለራሄል ሊያስታቅፏት ሞከሩ… ፀጋ ግን ፍቃደኛ አልሆነችም። ራሄል ወደ ፊት ተወረወረች እና የፀጋን የተወጣጠረ ሰውነት በማየቷ ልቧ ደረቷ ውስጥ ዘሎ የተሰነቀረ መሰላት።ዶ/ር ኤሊያስም መቀመጫውን ለቆ ፈጠን ብሎ ስሯ ተቀመጠና የፀጋን ሰውነት እያገለባበጠ ተመለከታት ‹‹ የጡንቻ መወጠር ይመስላል እግሮቿን መታሸት አለባቸው››አለ ፡፡ ወ.ሮ ትርሀስ እንደተናገረው የፀጋን እግሮች ማሻሸት ጀመሩ… እናም ሰውነቷ ቀስ እያለ ሲዝናና ራሄል በእፎይታ ተነፈሰች።
‹‹አየሽ? መጥፎ አይደለም››
‹‹አይ. ቢሆንም ትንሽ ፈርቼ ነበር››አለች ራሄል፡፡
ወ.ሮ ትርሀስ ወደ ራሄል ተመለከቱና እና ‹‹አሁንስ እሷን መያዝ ትችያለሽ?››ሲሉ ድጋሚ ጠየቋት፡፡
ራሄል መልስ ከመስጠቷ በፊት ኪሷ ውስጥ ያለው ስልክ ጮኸ ፡፡ አውጥታ ስታየው የደወለላትን ሮቤል ነበር፡፡ልክ እንደአዳኟ መልአክ ነበር የቆጠረችው።
‹‹ይቅርታ እማዬ ይህን ጥሪ ማንሳት አለብኝ››በማለት ይቅርታ ጠይቃና ለተፈጠረው ችግር አመሰግናለሁ፣ ኮሪደሩን ተጠቅማ ወደ ጓሮ በመሄድ ስልኩን አነሳችው፡፡
‹‹ሮቤል እንዴት ነህ?››አለችው።
‹‹ደህና ነኝ …ሴትዬዋ እንደገና ሀሳቧን ቀይራለች››አእምሮዋ በዚህ አዲስ ችግር ዙሪያ ተወጣጠረ፡፡ ራሄል ሁል ጊዜ ስትጨናነቅ እንደምታደርገው ጥፍሯን በጥርሶቿ ቀረጠፈች።‹‹ዛሬ ልታገኘን እንደምትፈልግ ተናግራለች›› ሮቤል ቀጠለ። ‹‹በእርግጥም ከአርባ አምስት ደቂቃ በፊት እዚያ መሆን ነበረብሽ.. ነገር ግን በወላጆችሽ ቤት እንደሆንሽ ስለሰማው ተውኩት።››አላት፡፡
የእህቷ ረዳት አልባ ለቅሶ ድምፅ ስታስታውስ ትንሽ ደነገጠች። ይህቺን በህመም የምትሰቃይ እና ከፍተኛ እንክብካቤ የምትፈልግ ህፃን ልጅ ለማሳደግ ወስነው በመውሰዳቸው ወላጆቿን በጣም አደነቀቻቸው። እሷ በእንሱ ቦታ ብትሆን ፈፅሞ ማድረግ እንደማትችል ታውቃለች።
‹‹ይቅርታ አድርግልኝ?››
‹‹ግድ የለም አሁን ችግሩ ምንድን ነው?››
‹‹ወ/ሮ ላምሮት የፋውንዴሽኑን የሩብ አመት ሪፖርት ማየት ትፈልጋለች። በእድገት ላይ እንደሆነ ማረጋገጥ ትፈልጋለች።››
ዔሊያስን በበሩ ላይ በዛ ቁመቱ ተጋርጦ ቆሞ ተመለከተችው።
‹‹እናትሽ በበረንዳው ላይ ኬክ እና ቡና እየቀረበ እንደሆነ እንድነግርሽ ጠይቃውኝ ነው›› አላት፡፡
‹‹አመሰግናለሁ… ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሁላችሁንም እቀላቀላችኋለው››በማለት ጠንከር ያለ ፈገግታ ሰጠችው፣
እሱ ግን ምንም አይነት የስሜት ለውጥ ሳያሳይ ፊቱን አዙሮ ሄደ። ከእሱ ጋር በመተዋወቋ ግልፅ ያልሆነ ምቾት እንደተሰማት መካድ አትችልም።የፀጋ ማራኪ ሐኪም ስለ እሷ ምን እንደሚያስብ ለማወቅ ለምን እንደምትጨነቅ አሰበች..እንደምንም እራሷን አረጋግታ ትኩረቷን ወደ ሮቤል መለሰች።
‹‹በሰዓቱ እንደምገኝ ለወይዘሮ ላምሮት ንገርልኝ››በመስኮቱ አሻግራ በአባቷ ጥናት ክፍል ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የአያቷን ሰዓት ተመለከተች። ‹‹አንድ ሰዓት ያህል አላት››
‹‹ራሄል አንቺን ማጨናነቅ አልፈልግም ነበር….ግን ቶሎ ልታደርጊው ትችያለሽ?››
‹‹አዎ እችላለው፣ሴትዬዋ የምትኖረው በቸርቸል ጎዳና አካባቢ ነው...በ50 ደቂቃ እዚያ ለመድረስ ብዙም የምቸገር አይመስለኝም… ወላጆቼን ብቻ ተሰናብቼ አሁኑኑ ወጣለው ። ››
‹‹እሺ እንግዲህ፣ ስትደርሺ እዛው ቀድሜ እጠብቅሻለው::›› ራሄል ከንፈሯን ነክሳ የስልኩን ቁልፉ ተጫነችና ዘጋችው።አሁን ልሄድ ነው በማለቷ ወላጇቾ ደስተኛ አይሆኑም, ነገር ግን በዚህ ጉዳይ ምንም ማድረግ አትችልም. ወ.ሮ ላምሮት ለፋውንዴሽኑ በጣም አስፈላጊ ሴት ነች። ዝግጅቶች በምታዘጋጅበት ጊዜ የታዋቂ እንግዶች ዝርዝር ለማውጣት በሚያስፈልግበት ጊዜ እሷ ከዋናዎቹ የዘወትር ለጋሾች ውስጥ ዋነኛዋ ነች።ወ.ሮ ላምሮት ባሏ ሲሞት ብዙ ገንዘብ በውርስ አግኝታለች፤በዛ ላይ በሀገሪቱ በብዙ ካምፓኒዎችን ታስተዳድራለች….እናም በባሏ ኑዛዜ መሰረት ከአመታዊ ትርፏ 25 ፐርሰንት ለበጎ አድራጎት ድርጅት መስጠት አለባት…እንግዲህ የእሷን ፋውንዴሽን ጨምሮ ሁሉም በሀገሪቱ በበጎአድራጎት ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች በጠቅላላ የእሷን ገንዘብ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ…. ። ራሄል ይህቺን ሴት በትክክል ካልያዘች፣በቀላሉ የእሷ ካምፑ በመልቀቅ ለተቀናቃኞ ፋውንዴሽን ገንዘቧን ለመስጠት ልትወስን ትችላለች። ህጋዊ የሚመስሉ ነገር ግን እስከ ሰማንያ በመቶ የሚሆነውን የለጋሾቻቸውን ገንዘብ “የአስተዳደር ክፍያ” ስም ለግል ጥቅማቸው ስለሚያውሉ ድርጅቶችን በሰማች ቁጥር የራሄል ደም እንዲፈላ ነው የሚያደርጋት፡፡እና የሴትዬዋን ልገሳ የማይሆኑ ድርጅቶች እጅ ገብቶ የግለሰቦች ኑሮ መዶጎሚያ እንዳይሆን መከላከልም አንደኛው አላማዋ ነው፡፡በእሷ ድርጅት የአስተዳደር ወጪ ከ25 በርሰንት መብለጥ እንደሌለበት ጥብቅ የሆነ መመሪያ አለ፡፡ለዛም ነው በዋናው ቢሮ ከሁለት ረዳቷቾ ጋር ሆና የአስር ሰው ስራ የምትሰራው፡፡
ወደውስጥ ስትገባ ወላጆቿ ቀደም ብለው በረንዳ ላይ ተቀምጠው ነበር ፣ የቀዘቀዘ ሻይ የያዘ ረጅም ኩባያ ከፊት ለፊታቸው ባለው የመስታወት ጠረጴዛ ላይ ይታያል።
ራሄል ስትደርስ ፀጋ በእግሮቾ ላይ ትልቅ ብርድ ልብስ ለብሳ እየተጫወተች ነበር፣ ለራሄል ፈገግ አለችላት፣ ቀላል ቡናማ አይኖቿ በምሽት መጀመሪያ ላይ ሲያበሩ ስትመለከት ደስ አላት። ራሄል ቆንጆ መሆኗን በውስጧ አሰበች፡፡
‹‹ እማዬ፣ አባዬ፣ ይቅርታ ዶ/ር …››ዓይኖቿ ዔሊያስ ላይ ተተከሉ ፣ ‹ አዝናለሁ ግን ሮቤል አሁን ደወሎኝ ነበር። ከለጋሾቻችን ከአንዷ ጋር ድንገተኛ ችግር ገጥሞናል ።ሄጄ ማስተካከል አለብኝ››
‹‹ኧረ ማር፣ ለምን እሱ ራሱ እንዲያስተካክለው አትተይለትም?››እናትዬው ተቃወሟት ፡፡
ወ.ሮ ትርሀስ ወደ ባላቸው ዞረው። ‹‹ቸርነት ፣ አናግራት እንጂ ።››አቶ ቸርነት ዝም ብለው ትከሻቸውን ከፍ በማድረግ ለልጃቸው ፈገግ አሉ።
‹‹ብትቆዪ ምኞቴ ነው ውዴ። ብዙ ጊዜ አናገኝሽም። ትንሿ እህትሽ እንኳን በደንብ አታውቅሽም…ከዚህ በተጨማሪ፣ እናትሽ ለአንቺ ብቻ ያዘጋጀችው የቸኮሌት ኬክ አለ›› አላት፡፡
ወ.ሮ ትርሀስም ‹‹አባትሽን ታውቂዋለሽ እና እኔም እንደዚህ አይነት ነገር አልበላም.››
‹‹በጣም አዝናለሁ እናቴ፣ ግን ኬኩን ብወስደው ደስ ይለኛል -››
‹‹እንግዲህ አልቆይም ካልሽ ምን አደርጋለው…አዘጋጅልሻለሁ።››ወ.ሮ ትርሀስ ከወንበራቸው ተነስተው ቆሙ‹‹በፍጥነት እመለሳለሁ››ብለው ወደውስጥ ገቡ፡፡
❤41👍5🥰2
ራሄል ሰዓቷን ለማየት በድብቅ የሸሚዟን እጅጌ ወደላይ ሰብሰብ አደረገችና ተመለከተች። ለመሰናበት ካሰበችው ጊዜ በላይ እየወሰደባት ነው፡፡በቀራት ደቂቃ ቀጠሮው ቦታ ለመድረስ የመኪናዋን ፍጥነት ከተገቢው በላይ ለመልቅ ልትገደድ እንደምትችል አሰበች፡፡የተጨናነቀ ትራፊክ እንዳያጋጥማት እየተመኘች ሸሚዞን ወደ ቦታው መለሰች፡፡ድንገት ዶ/ሩ በግማሽ ፈገግታ በትኩረት ሲመለከታት ያዘችው። ራሄል ይህን አልለመደችም። አብዛኞቹ ወንዶች ከእሷ ጋር እንዲህ አይነት የዓይን ጫወታ መጫወት አይደፍሩም፡፡
አባቷ ፀጋን በእቅፋቸው ይዘው እያጫወታት ነው‹‹አይዞሽ ልጄ ..ትደርሺያለሽ. .አትጨናነቂ…ሁሉነገር እግዚያብሄር ከፈቀደ ይሆናል…ካልፈቀደ ደግሞ ምንም ብትለፊ የቱንም ያህል ብትጥሪ አይሆንም››የሚል ምክር አከሉበት፡፡
የአባቷን ስብከት ውጦ ለመቀበል ትዕግሥት አጣች፡፡ ወዲያው ደግሞ እሳቸው እንደሚያምኑት ማመን ባለመቻሏ እፍረት ተሰማት። አባቷ በእምነታቸው ቅን ሰው ናቸው። እሳቸው በዚያ መጠን በእግዚያብሄር እያመኑ መቀጠላቸው እሷን ሊያበሳጫት አይገባም ነበር፡፡ እንዲያውም እሷም እንደእሳቸው በአምላክ ላይ ያላትን እምነት ለመጋራት የምትመኝበት ጊዜ አልፎ አልፎ ነበር። ግን ማድረግ አልቻለችም፡፡
ለአባቷ መልስ መስጠቱን ተወችውና እይታዋን ወደ ዶ/ሩ አዞረች፡፡እጆቹን ቁልቁል እያየ ነበር፣ የአንዱን እጁን ጣቶች ወደ ደረቱ ወሰደ ፤ከዛ በኋላ ነበር ከክርኑ አንጓ እስከ አውራ ጣት ግርጌ ድረስ የሚሄድ ረዣዥም የተሰነጠቀ ጠባሳ እንዳለበት ያስተዋለችው። በደንብ ያልተሰፋ ይመስል ነጭ እና የተቦጫጨቀ ሆኖ ይታይ ነበር። ሞተር ሳይክሉን ሲያበር ያገኘው አደጋ ይሆናል ስትል አሰበች ፡፡በዚያን ጊዜ ቀና ብሎ አያት።
‹‹ኬክሽ ይኸውልሽ ውዴ።››ወ.ሮ ትርሀስ አንድ መለስተኛ የታሸገ ካርቶን በሰማያዊ ፔስታል ውስጥ አድርገው አቀበሏት፡፡ ራሄል ፔስታሉን ተቀበለችና በእጇ እየመዘነች ‹‹ይህ ግማሹ ነው››አለች ።
‹‹ቀሪውን ደግሞ እኔና አባትሽ አንበላዋለን - ››
‹‹ለሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ምግቦቼ የቸኮሌት ኬክ እንደሆነ በምናቤ ሳስብ ደስታ ተሰማኝ ።››
‹‹ማር, እንዳታደርጊው››ወ.ሮ ትርሀስ ፊታቸውን በማኮሳተር ኬኩን መልሰው ሊወስድባት ሞከሩ፡፡
‹‹አይ, አታደርጊውም››ራሄል እናቷ እቃውን እንዳይነጥቋት እየተከላከለች ‹አትጨነቂ እኔ እየቀለድኩ ነው. ዛሬ ማታ አንድ ቁራጭ ከላዩ ላይ በላለትና የቀረውን ወደ ሥራ ቦታ እወስደዋለው፡፡እርግጠኛ ነኝ ሮቤል እና ሎዛ በዚህ ኬክ ላይ ይጣሉበታል.››
‹‹አዎ እንደዛ ነው ማድረግ ያለብሽ››
‹‹አሁን ሳሙኝ እና ብሄድ ይሻላል።››
ራሄል እናቷን በፍጥነት አቅፋ ሳመች እና ከአባቷ እና ከፀጋ ጋር ተመሳሳይ ነገር ለማድረግ ጎንበስ ብላ ሳመቻቸው።ከመሄዷ በፊት በዔሊያስ ላይ ዓይኗን ጣለች። እሱ በሁለት ሜትር ርቀት ላይ ነበር፣ ነገር ግን በዚያ ርቀት ላይ ቢሆንም ሰውነቷን የዳሰሳት አይነት ስሜት ነው የተሰማት።ወደ መኪናዋ ስትሄድ ስሜቷን ተናወጠ።
ስትመለስ ለወላጆቿ ሁሉን ነገር ግልጽ የምታደርግላቸው መስሏት ነበር። አስፈላጊው የእናት እና የሴት ልጅ ውይይት ጊዜ እንደደረሰ አውቃለች። በተቃራኒው ራሄል በአጀንዳው ላይ የሚቀጥለውን ንጥል ፋይል ስትከፍት ማዛጋት ጀመረች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አባቷ ፀጋን በእቅፋቸው ይዘው እያጫወታት ነው‹‹አይዞሽ ልጄ ..ትደርሺያለሽ. .አትጨናነቂ…ሁሉነገር እግዚያብሄር ከፈቀደ ይሆናል…ካልፈቀደ ደግሞ ምንም ብትለፊ የቱንም ያህል ብትጥሪ አይሆንም››የሚል ምክር አከሉበት፡፡
የአባቷን ስብከት ውጦ ለመቀበል ትዕግሥት አጣች፡፡ ወዲያው ደግሞ እሳቸው እንደሚያምኑት ማመን ባለመቻሏ እፍረት ተሰማት። አባቷ በእምነታቸው ቅን ሰው ናቸው። እሳቸው በዚያ መጠን በእግዚያብሄር እያመኑ መቀጠላቸው እሷን ሊያበሳጫት አይገባም ነበር፡፡ እንዲያውም እሷም እንደእሳቸው በአምላክ ላይ ያላትን እምነት ለመጋራት የምትመኝበት ጊዜ አልፎ አልፎ ነበር። ግን ማድረግ አልቻለችም፡፡
ለአባቷ መልስ መስጠቱን ተወችውና እይታዋን ወደ ዶ/ሩ አዞረች፡፡እጆቹን ቁልቁል እያየ ነበር፣ የአንዱን እጁን ጣቶች ወደ ደረቱ ወሰደ ፤ከዛ በኋላ ነበር ከክርኑ አንጓ እስከ አውራ ጣት ግርጌ ድረስ የሚሄድ ረዣዥም የተሰነጠቀ ጠባሳ እንዳለበት ያስተዋለችው። በደንብ ያልተሰፋ ይመስል ነጭ እና የተቦጫጨቀ ሆኖ ይታይ ነበር። ሞተር ሳይክሉን ሲያበር ያገኘው አደጋ ይሆናል ስትል አሰበች ፡፡በዚያን ጊዜ ቀና ብሎ አያት።
‹‹ኬክሽ ይኸውልሽ ውዴ።››ወ.ሮ ትርሀስ አንድ መለስተኛ የታሸገ ካርቶን በሰማያዊ ፔስታል ውስጥ አድርገው አቀበሏት፡፡ ራሄል ፔስታሉን ተቀበለችና በእጇ እየመዘነች ‹‹ይህ ግማሹ ነው››አለች ።
‹‹ቀሪውን ደግሞ እኔና አባትሽ አንበላዋለን - ››
‹‹ለሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ምግቦቼ የቸኮሌት ኬክ እንደሆነ በምናቤ ሳስብ ደስታ ተሰማኝ ።››
‹‹ማር, እንዳታደርጊው››ወ.ሮ ትርሀስ ፊታቸውን በማኮሳተር ኬኩን መልሰው ሊወስድባት ሞከሩ፡፡
‹‹አይ, አታደርጊውም››ራሄል እናቷ እቃውን እንዳይነጥቋት እየተከላከለች ‹አትጨነቂ እኔ እየቀለድኩ ነው. ዛሬ ማታ አንድ ቁራጭ ከላዩ ላይ በላለትና የቀረውን ወደ ሥራ ቦታ እወስደዋለው፡፡እርግጠኛ ነኝ ሮቤል እና ሎዛ በዚህ ኬክ ላይ ይጣሉበታል.››
‹‹አዎ እንደዛ ነው ማድረግ ያለብሽ››
‹‹አሁን ሳሙኝ እና ብሄድ ይሻላል።››
ራሄል እናቷን በፍጥነት አቅፋ ሳመች እና ከአባቷ እና ከፀጋ ጋር ተመሳሳይ ነገር ለማድረግ ጎንበስ ብላ ሳመቻቸው።ከመሄዷ በፊት በዔሊያስ ላይ ዓይኗን ጣለች። እሱ በሁለት ሜትር ርቀት ላይ ነበር፣ ነገር ግን በዚያ ርቀት ላይ ቢሆንም ሰውነቷን የዳሰሳት አይነት ስሜት ነው የተሰማት።ወደ መኪናዋ ስትሄድ ስሜቷን ተናወጠ።
ስትመለስ ለወላጆቿ ሁሉን ነገር ግልጽ የምታደርግላቸው መስሏት ነበር። አስፈላጊው የእናት እና የሴት ልጅ ውይይት ጊዜ እንደደረሰ አውቃለች። በተቃራኒው ራሄል በአጀንዳው ላይ የሚቀጥለውን ንጥል ፋይል ስትከፍት ማዛጋት ጀመረች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤39👍7
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ጋር የተደረገው ስብሰባ በጣም ረጅም ጊዜ ወስዶ ነበር እና ውጤቱ በጣም ጥቂት የሚባል ነበር፡፡
ራሄል በጣም የደክማት ቢሆንም ቢሮዋ ገብታም ስራዋን ቀጥላለች፡፡
‹‹ጥሩ ነው…በብሮሹሮች ላይ ስህተቶችን አግኝቻለሁ.››
ሎዛ ወረቀቶቹን በመካከላቸው ባለው የእንጨት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች። ራሄል በተቀመጠችበት የቆዳ ሶፋ ላይ ወደ ኋላ ተደግፋ ከፊቷ ያለውን ብሮሹር ቃኘች። ‹‹ይህ ሰማያዊ ቀለም በጣም ደማቅ ነው….እና ይህ ቢጫው ደግሞ እንዲጠናከር እፈልጋለሁ። የቀረውን ደግሞ ደውዬ አሳውቃቸዋለሁ››
‹‹ለምን ያን እኔ ራሴ እንድከታተል አትፈቅጂልኝም?›› አለች ሎዛ
‹‹አመሰግናለሁ ሎዛ.. ግን ማየት የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ።››
ሎዛ ራሷን በይሁንታ ነቀነቀች፣ ራሄል ግን በእሷ ውሳኔ ደስተኛ እንዳልነበረች አይታለች።
‹‹ለአሁን እንዳደርግ የምትፈልጊው ሌላ ነገር አለ?››ሎዛ ጠየቀች።
‹‹ አይ ምንም የለም… በቃ እጅሽ ላይ ያሉ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጊ።››የሚል ትእዛዝ ሰጠቻት፡፡
ራሄል ወረቀቶቹን በጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጠች እና ሎዛ ቢሮዋን ስትለቅ ወደ ሮቤል ዞረች።
‹‹ሮቤል አንተ የሆነ ነገር አንድታደርግልኝ እፈልጋለው››አለችው፡፡
ሮቤል ጎንበስ ብሎ ከቆዳው ቦርሳ ውስጥ አንድ ወረቀት አወጣና‹‹ጥቂት ስልክ ደዋውዬ ከምንጩ ያገኘሁት መረጃ ነው።›› በማለት ተጨማሪ ወረቀቶችን አቀበላት።
‹‹ከስብሰባው ጥቂት ቀደም ብሎ ከድርጅቱ ኃላፊ ጋር በግል ተወያይቼ ነበር።››
‹‹ጉልበቱን ከየት አመጣው?››ስትል አሞገሰችው፡፡ ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ከተገናኘ በኋላ ስላከናወናቸው ውይይቶችና ስለተለዋወጦቸው ቃላቶች በማሰብ ደክሞት ነበር።‹‹ይህ በጣም ጥሩ ነው፣ቀጣዩ እርምጃችን የበጎ አድራጎት ልገሳ ሁኔታቸውን ማረጋገጥ እና ከቻልን በእነሱ ላይ አንዳንድ ጥልቅ የጀርባ ስራዎችን መስራት ነው።››
‹‹እንደተፈጸመ ቁጠሪው.››ሲል ሮቤል ፈገግ አለ። በዚህ ጊዜ ስልኳ ጠራ…እናቷ መስመር ላይ ነበረች።‹‹እንደገና አመሰግናለሁ ሮቤል።በቅርብ ጊዜ ፋውንዴሽኑን እንደተቀላቀለ ሰው ምርጥ ስራ ሰርተሃል.›› ብላ ስልኩን አነሳች፡፡
ራሱን ነቀነቀና ዞር ብሎ ከቢሮ ወጣ።ራሄል ከኋላው ባለው ትልቅ የቆዳ ወንበር ላይ ለመቀመጥ በጠረጴዟ ዙሪያ ዞራ ሄደች።
‹‹ጤና ይስጥልኝ እናቴ››
‹‹ደህና ነኝ የእኔ ልጅ››
‹‹ እየሮጥኩ ያለሁት ባንቺ ጉዳይ እንደሆነ ከግምት ውስጥ በማስገባት ልትደሰቺ ይገባሻል።››ስትል ራሄል ወንበሯ ላይ በመቀመጥ ተሸከረከረች፡፡
‹‹ውዴ፣ ሁሌም በአንቺ ደስተኛ ነኝ ፡ ታውቃያለሽ?››
‹‹እማዬ አውቃለው…የቸኮሌት ኬኩ በጣም ጥሩ ነበር. ሮቤል እና ሎዛ አመስግኚልኝ ብለዋል.››
‹‹እንደተካፈላችሁት በማወቄ ደስተኛ ነኝ። ግን አንቺን አንድ ውለታ ልጠይቅሽ ነው። አያቶችሽ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ወደ አድዋ ሄደን እንደንጠይቃቸው ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን ፀጋን ይዘን ለመሄድ መድፈር አልቻልንም ።እስክንመለሰ እሷን ለመጠበቅ ፈቃደኛ ነሸ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ራሄል በድንጋጤ ስልኩ ሊያመልጣት ነበር..በመከራ ነው አጥብቃ የያዘችው።
‹‹ፈቃደኛ? ምናልባት…ቆይ እስኪ ፕሮግራሜን ልመልከት››አለችና የቀጠሮ ደብተሯን ለማየት ማስታወሻ ደብተሯን ከፈተች። በዛን ወቅት የማይሰረዝ ፕሮግራም ኖሯት ያንን እንደምክንያት ማቅረብ እንድትችል በውስጧ ፀለየች፡፡
የወሩ የመጨረሻ ቅዳሜና እሁድ…..ቢንጎ …የበጎ አድራጎት ፈንድ የመሰብሰብ ፕሮግራም አለባት። ‹‹ይቅርታ እማዬ ባልሻቸው ቀናት መሰረዝ የማልችላቸው ፕሮግራሞች አሉብኝ…በነዛ ቀናት አመታዊ የፋውንዴሽኑ ፈንድ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አለብኝ ።››
‹‹ኦህ ውዴ፣ አያትሽ ቤት የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ብቻ ነው።›› በለሆሳስ ተነፈሰች። እና ፀጋን ከማንም ጋር ልተዋት እችላለው? ….እንደምታውቂው እስካሁን በጣም ደካማ ነች።››
‹‹ለምን ስለችግርሽ ከዶክተር ዔሊያስ ጋር አታወሪበትም››ስትል ሀሳብ አቀረበች።
‹‹በእርግጥ ትክክል ብለሻል .. እሱ የግል ነርሲንግ ኤጀንሲን ወይም ተመሳሳይ ነገርን ሊመክረኝ ይችላል?››
ራሄል አሰበች፤ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት አይገባም። ወላጆቿ ይችን ልጅ ለማሳደግ መወሰናቸው የሷ ሀሳብ አልነበረም። እና ፀጋ ብቃት እንደሌላት እና አቅመ ቢስነት እንዲሰማት ያደረጋት የሷ ስህተት አልነበረም።
‹‹እሷን መንከባከብ ካልቻልሽ ችግር የለውም…›› እናቷ ቀጠለች‹‹እርግጠኛ ነኝ ዔሊ ፀጋን የት ልንወስደት እንደምንችል ያውቃል።››
‹‹እንደሚያውቅ እርግጠኛ ነኝ››ስትል ራሄል ተስማማች፣ እፎይታም ተሰማት።
‹እና ስለ ዶክተር ዔሊያስ ምን አሰብሽ? ››እናትዬው እንደቀልድ ሌላ ርዕስ ከፈተች፡፡
‹‹እሱ በጣም ደስ የሚል ሰው ነው…. ከፀጋ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለው ››
ከእሷ ጋር ሊጣመር የሚችልበት ምንም እድል እንደማይኖር ለእናቷ ግልፅ ለማድረግ ጊዜው አሁን እንደሆነ ተሰማት ‹‹ግን እሱ የእኔ ምርጫ አይደለም ።››ስትል መለሰችላት፡፡
‹‹ምን አልሽ?››
‹‹እማዬ… እባክሽ አሁን ለማንም ቢሆን ጊዜ የለኝም… ታውቂያለሽ››
‹‹ባለፉት ስምንት አመታት ውስጥ ለማንም ጊዜ አልነበራሽም። ብዙ ማህበራዊ ህይወት የለሽም። የምታደርጊው አንድ ነገር ቢኖር ስራ መስራት ብቻ ነው።››
ራሄል ወንበሯን ትንሽ እያወዛወዘች ፊቷን ከሰከሰች። ‹‹ይህን ስራ እፈልገዋለሁ እናቴ…ለህይወቴ ትርጉም የሰጠኝ ስራዬ ነው››
‹‹ከጌታ ጋር ያለሽ ግንኙነትስ? ያ እንዴት አድርጎ ነው ስራሽን የሚጋፋው?››ወደ ማትፈልገው ሌላ ርዕስ ከተተቻት፡፡
‹‹‹እናቴ ሆይ፣ የእኔ ስራ የተቸገሩ ህፃናትንና አቅመ ደካሞችን መርዳት ነው። ኢየሱስ በዚህ ምድር እንድናደርግ የሚፈልገውን ተግባር ነው እያደረኩ ያለሁት።››ራሄል እናቷን የሚያስደስት ትክክለኛ ቃላቶችን ታውቃለች እና ያለ እፍረት ተጠቀመችባቸው፡፡
‹‹ያለ እምነት ሥራ የሞተ ነው ውዴ።›› እናቷ ወደ እምነቷ ሲመጣ…ጥልቅ የማሰብ ችሎታ ስላላት ሁሉንም የልጇን የማጭበርበሪያ ስልቶች ታውቃለች።
ራሄል በመጨረሻ ‹‹እኔ ማድረግ የምችለው ይህን ብቻ ነው እናቴ››አለች. ቀጠለችናም ‹‹ለወንድ ጓደኛ ጊዜ የለኝም እና ለአንድም ሰው ፍላጎት የለኝም። ስለዚህ እባካችሁ ከአሁን በኋላ የማልፈልገውን አይነት አስጨናቂ እራት ለማዘጋጀት አትሞክሩ።››ስትል ንግግሯን በመኮሳተር ደመደመች፡፡
የእናቷ ዝምታ እጅ የመስጠት ምልክት እንደሆነ ተስፋ አድርጋ ነበር።‹‹ደስተኛ ነኝ እማማ›› እናቷ ብርሃኑን እንድታይ ለማድረግ ቆርጣ ገፋችበት። ‹‹ዓላማ እና ትርጉም ያለው ንቁ ህይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት ። ጓደኞች አሉኝ እናም በማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ የሚባል ስራ አለኝ። እና አንቺ እና አባዬ እና ፀጋም አለችሁልኝ። ተጨማሪ አያስፈልገኝም።››
‹‹እሺ፣ ይቅርታ፣ አንቺና ዔሊ ትመጣጠናላችሁ ብዬ ስላሰብኩ ነው። እሱ ጥሩ እና ደግ ሰው ነው..ለዛ ነው ከእሱ መዛመድ የፈለኩት ።››
ራሄል ፊቱ ላይ ስለተመለከተችው ፈገግታ አሰበች‹ደህና፣ ለአንድ ሌላ ሴት ግሩም ባል እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። ግን ያቺ ሴት እኔ አይደለሁም፣ እማማ።››
ወ.ሮ ትርሀስ ቃተቱ። ‹‹ካስከፋሁሽ ይቅርታ።››
‹‹አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጠርሺብኝ እንጂ አላስከፋሺኝም።››
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ጋር የተደረገው ስብሰባ በጣም ረጅም ጊዜ ወስዶ ነበር እና ውጤቱ በጣም ጥቂት የሚባል ነበር፡፡
ራሄል በጣም የደክማት ቢሆንም ቢሮዋ ገብታም ስራዋን ቀጥላለች፡፡
‹‹ጥሩ ነው…በብሮሹሮች ላይ ስህተቶችን አግኝቻለሁ.››
ሎዛ ወረቀቶቹን በመካከላቸው ባለው የእንጨት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች። ራሄል በተቀመጠችበት የቆዳ ሶፋ ላይ ወደ ኋላ ተደግፋ ከፊቷ ያለውን ብሮሹር ቃኘች። ‹‹ይህ ሰማያዊ ቀለም በጣም ደማቅ ነው….እና ይህ ቢጫው ደግሞ እንዲጠናከር እፈልጋለሁ። የቀረውን ደግሞ ደውዬ አሳውቃቸዋለሁ››
‹‹ለምን ያን እኔ ራሴ እንድከታተል አትፈቅጂልኝም?›› አለች ሎዛ
‹‹አመሰግናለሁ ሎዛ.. ግን ማየት የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ።››
ሎዛ ራሷን በይሁንታ ነቀነቀች፣ ራሄል ግን በእሷ ውሳኔ ደስተኛ እንዳልነበረች አይታለች።
‹‹ለአሁን እንዳደርግ የምትፈልጊው ሌላ ነገር አለ?››ሎዛ ጠየቀች።
‹‹ አይ ምንም የለም… በቃ እጅሽ ላይ ያሉ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጊ።››የሚል ትእዛዝ ሰጠቻት፡፡
ራሄል ወረቀቶቹን በጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጠች እና ሎዛ ቢሮዋን ስትለቅ ወደ ሮቤል ዞረች።
‹‹ሮቤል አንተ የሆነ ነገር አንድታደርግልኝ እፈልጋለው››አለችው፡፡
ሮቤል ጎንበስ ብሎ ከቆዳው ቦርሳ ውስጥ አንድ ወረቀት አወጣና‹‹ጥቂት ስልክ ደዋውዬ ከምንጩ ያገኘሁት መረጃ ነው።›› በማለት ተጨማሪ ወረቀቶችን አቀበላት።
‹‹ከስብሰባው ጥቂት ቀደም ብሎ ከድርጅቱ ኃላፊ ጋር በግል ተወያይቼ ነበር።››
‹‹ጉልበቱን ከየት አመጣው?››ስትል አሞገሰችው፡፡ ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ከተገናኘ በኋላ ስላከናወናቸው ውይይቶችና ስለተለዋወጦቸው ቃላቶች በማሰብ ደክሞት ነበር።‹‹ይህ በጣም ጥሩ ነው፣ቀጣዩ እርምጃችን የበጎ አድራጎት ልገሳ ሁኔታቸውን ማረጋገጥ እና ከቻልን በእነሱ ላይ አንዳንድ ጥልቅ የጀርባ ስራዎችን መስራት ነው።››
‹‹እንደተፈጸመ ቁጠሪው.››ሲል ሮቤል ፈገግ አለ። በዚህ ጊዜ ስልኳ ጠራ…እናቷ መስመር ላይ ነበረች።‹‹እንደገና አመሰግናለሁ ሮቤል።በቅርብ ጊዜ ፋውንዴሽኑን እንደተቀላቀለ ሰው ምርጥ ስራ ሰርተሃል.›› ብላ ስልኩን አነሳች፡፡
ራሱን ነቀነቀና ዞር ብሎ ከቢሮ ወጣ።ራሄል ከኋላው ባለው ትልቅ የቆዳ ወንበር ላይ ለመቀመጥ በጠረጴዟ ዙሪያ ዞራ ሄደች።
‹‹ጤና ይስጥልኝ እናቴ››
‹‹ደህና ነኝ የእኔ ልጅ››
‹‹ እየሮጥኩ ያለሁት ባንቺ ጉዳይ እንደሆነ ከግምት ውስጥ በማስገባት ልትደሰቺ ይገባሻል።››ስትል ራሄል ወንበሯ ላይ በመቀመጥ ተሸከረከረች፡፡
‹‹ውዴ፣ ሁሌም በአንቺ ደስተኛ ነኝ ፡ ታውቃያለሽ?››
‹‹እማዬ አውቃለው…የቸኮሌት ኬኩ በጣም ጥሩ ነበር. ሮቤል እና ሎዛ አመስግኚልኝ ብለዋል.››
‹‹እንደተካፈላችሁት በማወቄ ደስተኛ ነኝ። ግን አንቺን አንድ ውለታ ልጠይቅሽ ነው። አያቶችሽ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ወደ አድዋ ሄደን እንደንጠይቃቸው ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን ፀጋን ይዘን ለመሄድ መድፈር አልቻልንም ።እስክንመለሰ እሷን ለመጠበቅ ፈቃደኛ ነሸ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ራሄል በድንጋጤ ስልኩ ሊያመልጣት ነበር..በመከራ ነው አጥብቃ የያዘችው።
‹‹ፈቃደኛ? ምናልባት…ቆይ እስኪ ፕሮግራሜን ልመልከት››አለችና የቀጠሮ ደብተሯን ለማየት ማስታወሻ ደብተሯን ከፈተች። በዛን ወቅት የማይሰረዝ ፕሮግራም ኖሯት ያንን እንደምክንያት ማቅረብ እንድትችል በውስጧ ፀለየች፡፡
የወሩ የመጨረሻ ቅዳሜና እሁድ…..ቢንጎ …የበጎ አድራጎት ፈንድ የመሰብሰብ ፕሮግራም አለባት። ‹‹ይቅርታ እማዬ ባልሻቸው ቀናት መሰረዝ የማልችላቸው ፕሮግራሞች አሉብኝ…በነዛ ቀናት አመታዊ የፋውንዴሽኑ ፈንድ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አለብኝ ።››
‹‹ኦህ ውዴ፣ አያትሽ ቤት የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ብቻ ነው።›› በለሆሳስ ተነፈሰች። እና ፀጋን ከማንም ጋር ልተዋት እችላለው? ….እንደምታውቂው እስካሁን በጣም ደካማ ነች።››
‹‹ለምን ስለችግርሽ ከዶክተር ዔሊያስ ጋር አታወሪበትም››ስትል ሀሳብ አቀረበች።
‹‹በእርግጥ ትክክል ብለሻል .. እሱ የግል ነርሲንግ ኤጀንሲን ወይም ተመሳሳይ ነገርን ሊመክረኝ ይችላል?››
ራሄል አሰበች፤ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት አይገባም። ወላጆቿ ይችን ልጅ ለማሳደግ መወሰናቸው የሷ ሀሳብ አልነበረም። እና ፀጋ ብቃት እንደሌላት እና አቅመ ቢስነት እንዲሰማት ያደረጋት የሷ ስህተት አልነበረም።
‹‹እሷን መንከባከብ ካልቻልሽ ችግር የለውም…›› እናቷ ቀጠለች‹‹እርግጠኛ ነኝ ዔሊ ፀጋን የት ልንወስደት እንደምንችል ያውቃል።››
‹‹እንደሚያውቅ እርግጠኛ ነኝ››ስትል ራሄል ተስማማች፣ እፎይታም ተሰማት።
‹እና ስለ ዶክተር ዔሊያስ ምን አሰብሽ? ››እናትዬው እንደቀልድ ሌላ ርዕስ ከፈተች፡፡
‹‹እሱ በጣም ደስ የሚል ሰው ነው…. ከፀጋ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለው ››
ከእሷ ጋር ሊጣመር የሚችልበት ምንም እድል እንደማይኖር ለእናቷ ግልፅ ለማድረግ ጊዜው አሁን እንደሆነ ተሰማት ‹‹ግን እሱ የእኔ ምርጫ አይደለም ።››ስትል መለሰችላት፡፡
‹‹ምን አልሽ?››
‹‹እማዬ… እባክሽ አሁን ለማንም ቢሆን ጊዜ የለኝም… ታውቂያለሽ››
‹‹ባለፉት ስምንት አመታት ውስጥ ለማንም ጊዜ አልነበራሽም። ብዙ ማህበራዊ ህይወት የለሽም። የምታደርጊው አንድ ነገር ቢኖር ስራ መስራት ብቻ ነው።››
ራሄል ወንበሯን ትንሽ እያወዛወዘች ፊቷን ከሰከሰች። ‹‹ይህን ስራ እፈልገዋለሁ እናቴ…ለህይወቴ ትርጉም የሰጠኝ ስራዬ ነው››
‹‹ከጌታ ጋር ያለሽ ግንኙነትስ? ያ እንዴት አድርጎ ነው ስራሽን የሚጋፋው?››ወደ ማትፈልገው ሌላ ርዕስ ከተተቻት፡፡
‹‹‹እናቴ ሆይ፣ የእኔ ስራ የተቸገሩ ህፃናትንና አቅመ ደካሞችን መርዳት ነው። ኢየሱስ በዚህ ምድር እንድናደርግ የሚፈልገውን ተግባር ነው እያደረኩ ያለሁት።››ራሄል እናቷን የሚያስደስት ትክክለኛ ቃላቶችን ታውቃለች እና ያለ እፍረት ተጠቀመችባቸው፡፡
‹‹ያለ እምነት ሥራ የሞተ ነው ውዴ።›› እናቷ ወደ እምነቷ ሲመጣ…ጥልቅ የማሰብ ችሎታ ስላላት ሁሉንም የልጇን የማጭበርበሪያ ስልቶች ታውቃለች።
ራሄል በመጨረሻ ‹‹እኔ ማድረግ የምችለው ይህን ብቻ ነው እናቴ››አለች. ቀጠለችናም ‹‹ለወንድ ጓደኛ ጊዜ የለኝም እና ለአንድም ሰው ፍላጎት የለኝም። ስለዚህ እባካችሁ ከአሁን በኋላ የማልፈልገውን አይነት አስጨናቂ እራት ለማዘጋጀት አትሞክሩ።››ስትል ንግግሯን በመኮሳተር ደመደመች፡፡
የእናቷ ዝምታ እጅ የመስጠት ምልክት እንደሆነ ተስፋ አድርጋ ነበር።‹‹ደስተኛ ነኝ እማማ›› እናቷ ብርሃኑን እንድታይ ለማድረግ ቆርጣ ገፋችበት። ‹‹ዓላማ እና ትርጉም ያለው ንቁ ህይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት ። ጓደኞች አሉኝ እናም በማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ የሚባል ስራ አለኝ። እና አንቺ እና አባዬ እና ፀጋም አለችሁልኝ። ተጨማሪ አያስፈልገኝም።››
‹‹እሺ፣ ይቅርታ፣ አንቺና ዔሊ ትመጣጠናላችሁ ብዬ ስላሰብኩ ነው። እሱ ጥሩ እና ደግ ሰው ነው..ለዛ ነው ከእሱ መዛመድ የፈለኩት ።››
ራሄል ፊቱ ላይ ስለተመለከተችው ፈገግታ አሰበች‹ደህና፣ ለአንድ ሌላ ሴት ግሩም ባል እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። ግን ያቺ ሴት እኔ አይደለሁም፣ እማማ።››
ወ.ሮ ትርሀስ ቃተቱ። ‹‹ካስከፋሁሽ ይቅርታ።››
‹‹አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጠርሺብኝ እንጂ አላስከፋሺኝም።››
❤61👍6
‹‹ደህና፣ በቃ ቻው፣ ከአንድ ፊዚዬቴራፒስት ጋር ቀጠሮ አለኝ እና ከዚያ በኋላ ዶ/ር ኤሊያስን አገኘዋለው። ሰላም እንዳልሽው ልንገረው?››እናቷ የማይበገሩ ነበሩ።
‹‹እናቴ የፈለግሽውን አድርጊ…. እወድሻለሁ።››
የእናቷ ድርጊት አንዳንድ ጊዜ እብድ ሲያደርጋት፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ እንድታፍር ያደርጋታል… እንደዛም ሆኖ ራሄል ወላጆቿን በጣም ትወዳለች።‹‹አንቺንም እወድሃሸለው ውዴ።››
ራሄል ስልኩን ዘግታ በሀሳብ ተዋጠች። ራሄል እናቷ ፀጋን በማደጎ ወደቤቷ ስያመጣት ውስጣዊ ስሜቷን እንደምታረካላቸው እና እሷ ላይ የሚያደርጉትን ትኩረት ይቀንሳሉ ብላ ገምታ ነበር ግን አሁን እንደምታየው ምንም የተቀየረ ነገር የለም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronoseቀ
‹‹እናቴ የፈለግሽውን አድርጊ…. እወድሻለሁ።››
የእናቷ ድርጊት አንዳንድ ጊዜ እብድ ሲያደርጋት፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ እንድታፍር ያደርጋታል… እንደዛም ሆኖ ራሄል ወላጆቿን በጣም ትወዳለች።‹‹አንቺንም እወድሃሸለው ውዴ።››
ራሄል ስልኩን ዘግታ በሀሳብ ተዋጠች። ራሄል እናቷ ፀጋን በማደጎ ወደቤቷ ስያመጣት ውስጣዊ ስሜቷን እንደምታረካላቸው እና እሷ ላይ የሚያደርጉትን ትኩረት ይቀንሳሉ ብላ ገምታ ነበር ግን አሁን እንደምታየው ምንም የተቀየረ ነገር የለም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronoseቀ
👍32❤13
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡
አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡
‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።
‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡
‹‹እባክህ አትጨነቅ›› የውስጥ ስሜቱን የሚቆሰቁስ አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።
ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡
‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››
ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››
‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡
‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ ሮጠው ከጎኑ ቆመ
‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››
ዔሊያስ ለወንድሙ ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው
ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ። ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡ በወቅቱ ጮርቃ ልጅ ነበር እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡
ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡
‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››
እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች። አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ ጥግ ወስደው ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡
ያሬድ የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹አዎ..ደህና ነኝ››
‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡
‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››
‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››
‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡
‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ እንደነበረ ላለማሰብ ታገለች።
ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡
‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡
ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡
‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡
‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን ጮኸች።
‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡
አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡
‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።
‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡
‹‹እባክህ አትጨነቅ›› የውስጥ ስሜቱን የሚቆሰቁስ አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።
ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡
‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››
ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››
‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡
‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ ሮጠው ከጎኑ ቆመ
‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡
‹‹እና ታዲያ?››
‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››
ዔሊያስ ለወንድሙ ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው
ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ። ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡ በወቅቱ ጮርቃ ልጅ ነበር እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡
ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡
‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››
እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች። አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ ጥግ ወስደው ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡
ያሬድ የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹አዎ..ደህና ነኝ››
‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡
‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››
‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››
‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡
‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ እንደነበረ ላለማሰብ ታገለች።
ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡
‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡
ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡
‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡
‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን ጮኸች።
‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
❤56👍3
‹‹አሁን ማዘዝ እንችላለን? እየራበኝ ነው።››በማለት ርዕሱን ለመቀየር ሞከረች፡፡
‹‹ኤሊ ወንደላጤ እንደሆነ ሰማሁ ›› አለች ሜሮን
‹‹ሊሆን ይችላል ግን…ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም›› ስትል ራሄል አጽንኦት ሰጥታ ተናገረች።
‹‹ይቺ ልጅ በፍቅር ፍላጻ የተመታች ይመስለኛል።››ያሬድ ነው ተናጋሪው፡፡
ራሄል‹‹ሞተር ሳይክል ይነዳል…እሺ?››ስትል በመኮሳተር ነገረቻቸው፡፡ከዚህ ቃል በኋላ ያለው ዝምታ ነበር…ፀጥታው ምን ማለት እንደፈለገች ጓደኞቿ እንደተረዱት ያሳያል። በባለ ሁለት ጎማ የሞት ማሽን የልቧን ሰው እዳጣች እና ምን ያህል የልብ ስብራት እንዳጋጠማትና ከዛም ስብራት እስካአሁን እንዳላገገመች የቅርቧ ሰዎች ስለሆኑ በደንብ ያውቃሉ፡፡
‹‹እናንተ ሰዎች ለማዘዝ ዝግጁ ናችሁ?››ደግማ ጠየቅች፡፡
አስተናጋጁ ተጠራ እና ሁሉም የየፍላጎታቸውን አዘዙ ፡፡ከዚያ በኋላ፣ ወደ ተለመደው ንግግራቸው ሲገቡ፣ አንዳቸው የሌላውን ሕይወት ሲመረምሩ፣ ሌንሳ ስለ መንታ ልጆቿ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላላት ስራ ስትነግራቸው ራሄል ስለ ድርጅቷ እንቅስቃሴ ስትተርክ ቆዩ…ያዘዘችው በርገር መጥቶ ለመብላት ስትዘጋጅ የሞባይል ስልኳ ጮኸ።
‹‹ተይው…አታንሺው››አላት ያሬድ… ። የጥሪ ማሳያውን ተመለከተች። አባቷ ነበሩ።ጓደኞቿን ይቅርታ ጠይቃ በፈገግታ ስልኩን አነሳች፣ ከጓደኞቿ ዞር ብላ ማውራት ጀመረች።
‹‹ ሄይ አባዬ››
‹‹ራሄል የእኔ ማር››ድምፃቸው የደከመ ነበር።በራሄል ጭንቅላት ውስጥ ጭንቀት ተፈጠረ።
‹‹አባዬ ምን ችግር አለ?››
‹‹እናትሽ ናት …እኛ ሆስፒታል ነው ያለነው….እግሯ ተሰብሯል።››
‹‹መጣው አባዬ…አሁኑኑ መጣሁ ››ስልኳን ዘጋችና ቦርሳዋን አነሳች። ‹‹አባቴ ነበር የደወለው››አለች፡፡ ድምጿ እየተንቀጠቀጠ ነው።‹‹ይቅርታ ጓደኞቼ, መሄድ አለብኝ. እናቴ እግሯን ተሰብሮ ሆስፒታል ውስጥ ነች.››ለምግብ ክፍያ የሚሆን የተወሰነ ብር ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች።
‹‹አብረንሽ እንድንመጣ ትፈልጊያለሽ››ስትል ሜሮን ጠየቀቻት ፡፡
‹‹አይ, አይሆንም.፣ችግር የለውም…እናንተ መብላታችሁን ቀጥሉ.››ራሄል ተቃወመች።
ራሄል ከምግብ ቤት ፈጥና ስትሄድ ያሬድ ‹‹ከደረሽ በኃላ ሁኔታውን አሳውቂን››አላት፡፡
ከአስራ አምስት ደቂቃ በኋላ የሆስፒታሉን በር ደርሳ እንደምንም እራሷን አደፋፍራ ወደውስጥ ገባች፡፡ እና በድፍረት ምትጋፈጠው የመሰላት የጸረ-ተባይ እና የአሞኒያ ጠረን በአፍንጫዋ ተመሰገ ። ያደፈነችውን ትዝታ እየጎተተ እንደ ማዕበል ያንገላታት ጀመር።እርምጃዋ ተንቀረፈፈ፣ ነገር ግን ስለእናቷ ህመም ስታስብ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ለሆስፒታሎችን ያላትን ፍራቻ ተቋቁማ እንድታልፍ የሚያስችላትን ብርታት አገኘች ።
‹‹ተይ…ተይ! አባትሽ ይፈልግሻል።››በማለት እራሷን ለማበርታት ሞከረች፡፡ከአንዱ ክፍል ውስጥ የአባቷን ድምፅ እንደሰማች በፍጥነት ወደእዛው ተራመደች። መጋረጃውን አልፋ ከፊት ለፊቷ ባለው ቦታ ላይ ቆመች።ፀጋ አልጋው ላይ ተቀምጣለች…እና ኤሊያስ ከሸሚዝና ከሰማያዊ ጂንስ በላይ ነጭ ጋወኑን ለብሶ ቆሟል ፡፡በየት በየት ብሎ ከእሷ ቀድሞ እዚህ እንደተገኘ ግራ ገባት፡፡ እንደገባች አባቷ ቀና ብለው አያትና በጥሩ ፈገግታ ተቀበላት።‹‹እናቴ የት አለች?››ራሄል እሷቸውን እቅፍ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ ማን እዚህ እንዳለ ለማየት ጭንቅላቷን አጠማዘዘች።
አባቷ ‹‹እናትሽ አሁን ቀዶ ጥገና ላይ ነች›› አሏት፡፡
‹‹እንዴት ሊሆን ቻለ?››ራሄል ጠየቀች።
‹‹ፀጋን ተሸክማ ደረጃውን እየወረደች ነበር፣ድንገት ሚዛኗን ስታ ወድቃ ተጠመዘዘች…ከዛ ተሰበረች። ››ሲሉ አስረዷት፡፡
‹‹አሁን ፀጋ እንዴት ናት?››ራሄል እህቷን በድጋሚ እየተመለከተች ጠየቀች፡፡
‹‹እስካሁን ደህና ነች ። ከመደበኛው ውጪ የሆነ ነገር አይታይባትም።››ኤሊያስ ጣልቃ ገብቶ ስለፀጋ ሊያስረዳት ሞከረ፡፡ አይኖቹ ራሔል ግንባር ላይ ብርሃን የሚረጩ ይመስላሉ ።
‹‹ራሄል ሆስፒታሎችን አትወድም። ››ሲሉ አባትዬው ለኤሊያስ ሊያስረዱት ሞከሩ፡፡
ዔሊም ‹‹አዝናለሁ፣ አላውቅም ነበር። ››አለ፡፡
‹‹ግን እናቴን ለማግኘት መሄድ እችላለሁ?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ትችያለሽ››
ራሄል በጥንቃቄ ፈገግታ ሰጠችው ። ለረጅም ጊዜ ያላጋጠማት ስሜት ተሰማት።‹‹አሁን እመለሳለሁ.››በማለት ፀጋን አፍንጫዋ ላይ ነክቶ ሄደ።
ከጎናቸው ካለ አንድ ኪዩቢክ የወጣው የኦክሲጅን ጩኸት፣ የጋሪዎቹ እና የነርሶች ወከባ ወደ ኅሊናዋ ውስጥ ገብተው ትዝታዎችን ቀሰቀሱባት። ትንፋሽም አጠራት።አባቷ ተሳስተዋል። ሆስፒታሎችን አለመውደድ አይደለም። ንቃቸው ነው። እነሱ ተስፋዋን ቀረጣጥፈው የበሉባት የመቃብር ጉድጓድ ናቸው ፣ በእያንዳንዱ ኮሪደር የሞት ሽታ ነው ወደአፍንጫዋ የሚመሰገው እና አሁን ሀሳቧ እናቷ ላይ ነው፡፡ በእውነቱ ምን ያህል ተጎድታ ይሆን ? ምን ይደርስባት ይሆን?
‹‹የእኔ ማር ..እዚህ ጋር ተቀመጪ››አባቷም እጇን ያዘና በመጋረጃ በተሸፈነው ክፍል ውስጥ ባለው ብቸኛ ወንበር ላይ አስቀመጧት ፡፡
‹ኤሊያስ ትክክል ነበር፣ በጣም ገርጥታለች ።››ራሄል እያደገ የመጣውን ድንጋጤዋን ለመቆጣጠር ሞከረች።
‹‹ደህና ነኝ አባባ›› አለች፡፡
ፀጋ እጆቿን ወደ አባቷ እየዘረጋች ‹‹ወደ ታች አውርደኝ›› ስትል ተናገረች።
አቶ ቸርነት ከአልጋው ላይ ልትወርድ ወደ ምትሞክረው ፀጋ እየጠቆሙ ‹‹ራሄል ልትወስጂያት ትችያለሽ?›› ሲሉ ጠየቋት።አባቷ ወደሚያዩት አቅጣጫ ቃኘች፣ ዔሊያስ መጋረጃውን ወደ ጎን ሲያንሸራትተው ሌላ ዶክተር ተከተለውና ወደእነሱ መጣ። በድጋሚ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ በምንም ነገር እርግጠኛ ሳትሆን ልጁቷን ከአልጋው ላይ አነሳችና አቀፈቻት።
‹‹…አዝናለው ጥሩ ያልሆነ ዜና ልነግራችሁ ነው›› አለ ደ/ር ኤሊያስ።
የዶተሩ ከባድ የድምፁ ቃና ራሄልን በፍርሃቷ እንድትርበደበድ እና እንዳትወድቅ በመፍራት ግድግዳውን እንድትይዝ አደረጋት ‹‹ይህ ዶ/ር ምንያህል ይባላል። ሁኔታውን ያብራራላችኋል›› ሲል ተናገረና ቦታውን አዲስ ለመጣው ዶክተር ለቀቀ ፡፡የዶ/ር ምንያህል ፊቱ ፈገግታ ያልተለየው ቢሆንም የዶክተሮችን ስሜት ማንበብ ከባድ እንደሆነ ከብዙ አመት በፊት በደንብ አውቃለች፡፡ እናም ፍርሃቷ ጨመረ።
ምንያህል የተባለው ዶ.ር ወደአባቷ እየተመለከተ ገለፃውን ቀጠለ‹‹የባለቤቶት X ሬይ ውጤት አግኝተናል።››ጥቁሩ አይኖቹ በጥልቅ ርህራሄ ሁለቱንም አስተዋላቸው።‹‹በጣም ከባድ የሆነ የጭን አጥንት ስብራት ገጥሟቸዋል።ከአጥንት በላይ የሆነ ስብራት በሚመስል ነገር የተወሳሰበ ነው። ለረጅም ጊዜ እዚሁ ሆስፒታል ተኝተው መታከም አለባቸው››
አቶ ቸርነት እራሳቸውን ለማረጋጋት ያህል አይናቸውን ጨፈኑ.. ከዛ ከፈቱ …።ራሄል አሁንም ፀጋን በአንድ እጇ ይዛ ቀስ በቀስ ስሯ ያለ ወንበር ላይ ልትቀመጥ ስትሞክር ድንገት ክንዷ ላይ ያለችው እህቷን እንደያዘች ሚዛኗን በመጠኑ ስታ ልትወድቅ ስትል ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተላት የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ተንደረደረና ክንዷን ይዞ በዝግታ እንድትቀመጥ ረዳት፡፡
‹‹አመሰግናለሁ››አለች ራሄል ።
ዔሊያስ እጁ አሁንም በትሁት ትከሻ ላይ ነው።
‹‹ኤሊ ወንደላጤ እንደሆነ ሰማሁ ›› አለች ሜሮን
‹‹ሊሆን ይችላል ግን…ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም›› ስትል ራሄል አጽንኦት ሰጥታ ተናገረች።
‹‹ይቺ ልጅ በፍቅር ፍላጻ የተመታች ይመስለኛል።››ያሬድ ነው ተናጋሪው፡፡
ራሄል‹‹ሞተር ሳይክል ይነዳል…እሺ?››ስትል በመኮሳተር ነገረቻቸው፡፡ከዚህ ቃል በኋላ ያለው ዝምታ ነበር…ፀጥታው ምን ማለት እንደፈለገች ጓደኞቿ እንደተረዱት ያሳያል። በባለ ሁለት ጎማ የሞት ማሽን የልቧን ሰው እዳጣች እና ምን ያህል የልብ ስብራት እንዳጋጠማትና ከዛም ስብራት እስካአሁን እንዳላገገመች የቅርቧ ሰዎች ስለሆኑ በደንብ ያውቃሉ፡፡
‹‹እናንተ ሰዎች ለማዘዝ ዝግጁ ናችሁ?››ደግማ ጠየቅች፡፡
አስተናጋጁ ተጠራ እና ሁሉም የየፍላጎታቸውን አዘዙ ፡፡ከዚያ በኋላ፣ ወደ ተለመደው ንግግራቸው ሲገቡ፣ አንዳቸው የሌላውን ሕይወት ሲመረምሩ፣ ሌንሳ ስለ መንታ ልጆቿ እና በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላላት ስራ ስትነግራቸው ራሄል ስለ ድርጅቷ እንቅስቃሴ ስትተርክ ቆዩ…ያዘዘችው በርገር መጥቶ ለመብላት ስትዘጋጅ የሞባይል ስልኳ ጮኸ።
‹‹ተይው…አታንሺው››አላት ያሬድ… ። የጥሪ ማሳያውን ተመለከተች። አባቷ ነበሩ።ጓደኞቿን ይቅርታ ጠይቃ በፈገግታ ስልኩን አነሳች፣ ከጓደኞቿ ዞር ብላ ማውራት ጀመረች።
‹‹ ሄይ አባዬ››
‹‹ራሄል የእኔ ማር››ድምፃቸው የደከመ ነበር።በራሄል ጭንቅላት ውስጥ ጭንቀት ተፈጠረ።
‹‹አባዬ ምን ችግር አለ?››
‹‹እናትሽ ናት …እኛ ሆስፒታል ነው ያለነው….እግሯ ተሰብሯል።››
‹‹መጣው አባዬ…አሁኑኑ መጣሁ ››ስልኳን ዘጋችና ቦርሳዋን አነሳች። ‹‹አባቴ ነበር የደወለው››አለች፡፡ ድምጿ እየተንቀጠቀጠ ነው።‹‹ይቅርታ ጓደኞቼ, መሄድ አለብኝ. እናቴ እግሯን ተሰብሮ ሆስፒታል ውስጥ ነች.››ለምግብ ክፍያ የሚሆን የተወሰነ ብር ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች።
‹‹አብረንሽ እንድንመጣ ትፈልጊያለሽ››ስትል ሜሮን ጠየቀቻት ፡፡
‹‹አይ, አይሆንም.፣ችግር የለውም…እናንተ መብላታችሁን ቀጥሉ.››ራሄል ተቃወመች።
ራሄል ከምግብ ቤት ፈጥና ስትሄድ ያሬድ ‹‹ከደረሽ በኃላ ሁኔታውን አሳውቂን››አላት፡፡
ከአስራ አምስት ደቂቃ በኋላ የሆስፒታሉን በር ደርሳ እንደምንም እራሷን አደፋፍራ ወደውስጥ ገባች፡፡ እና በድፍረት ምትጋፈጠው የመሰላት የጸረ-ተባይ እና የአሞኒያ ጠረን በአፍንጫዋ ተመሰገ ። ያደፈነችውን ትዝታ እየጎተተ እንደ ማዕበል ያንገላታት ጀመር።እርምጃዋ ተንቀረፈፈ፣ ነገር ግን ስለእናቷ ህመም ስታስብ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ለሆስፒታሎችን ያላትን ፍራቻ ተቋቁማ እንድታልፍ የሚያስችላትን ብርታት አገኘች ።
‹‹ተይ…ተይ! አባትሽ ይፈልግሻል።››በማለት እራሷን ለማበርታት ሞከረች፡፡ከአንዱ ክፍል ውስጥ የአባቷን ድምፅ እንደሰማች በፍጥነት ወደእዛው ተራመደች። መጋረጃውን አልፋ ከፊት ለፊቷ ባለው ቦታ ላይ ቆመች።ፀጋ አልጋው ላይ ተቀምጣለች…እና ኤሊያስ ከሸሚዝና ከሰማያዊ ጂንስ በላይ ነጭ ጋወኑን ለብሶ ቆሟል ፡፡በየት በየት ብሎ ከእሷ ቀድሞ እዚህ እንደተገኘ ግራ ገባት፡፡ እንደገባች አባቷ ቀና ብለው አያትና በጥሩ ፈገግታ ተቀበላት።‹‹እናቴ የት አለች?››ራሄል እሷቸውን እቅፍ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ ማን እዚህ እንዳለ ለማየት ጭንቅላቷን አጠማዘዘች።
አባቷ ‹‹እናትሽ አሁን ቀዶ ጥገና ላይ ነች›› አሏት፡፡
‹‹እንዴት ሊሆን ቻለ?››ራሄል ጠየቀች።
‹‹ፀጋን ተሸክማ ደረጃውን እየወረደች ነበር፣ድንገት ሚዛኗን ስታ ወድቃ ተጠመዘዘች…ከዛ ተሰበረች። ››ሲሉ አስረዷት፡፡
‹‹አሁን ፀጋ እንዴት ናት?››ራሄል እህቷን በድጋሚ እየተመለከተች ጠየቀች፡፡
‹‹እስካሁን ደህና ነች ። ከመደበኛው ውጪ የሆነ ነገር አይታይባትም።››ኤሊያስ ጣልቃ ገብቶ ስለፀጋ ሊያስረዳት ሞከረ፡፡ አይኖቹ ራሔል ግንባር ላይ ብርሃን የሚረጩ ይመስላሉ ።
‹‹ራሄል ሆስፒታሎችን አትወድም። ››ሲሉ አባትዬው ለኤሊያስ ሊያስረዱት ሞከሩ፡፡
ዔሊም ‹‹አዝናለሁ፣ አላውቅም ነበር። ››አለ፡፡
‹‹ግን እናቴን ለማግኘት መሄድ እችላለሁ?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ትችያለሽ››
ራሄል በጥንቃቄ ፈገግታ ሰጠችው ። ለረጅም ጊዜ ያላጋጠማት ስሜት ተሰማት።‹‹አሁን እመለሳለሁ.››በማለት ፀጋን አፍንጫዋ ላይ ነክቶ ሄደ።
ከጎናቸው ካለ አንድ ኪዩቢክ የወጣው የኦክሲጅን ጩኸት፣ የጋሪዎቹ እና የነርሶች ወከባ ወደ ኅሊናዋ ውስጥ ገብተው ትዝታዎችን ቀሰቀሱባት። ትንፋሽም አጠራት።አባቷ ተሳስተዋል። ሆስፒታሎችን አለመውደድ አይደለም። ንቃቸው ነው። እነሱ ተስፋዋን ቀረጣጥፈው የበሉባት የመቃብር ጉድጓድ ናቸው ፣ በእያንዳንዱ ኮሪደር የሞት ሽታ ነው ወደአፍንጫዋ የሚመሰገው እና አሁን ሀሳቧ እናቷ ላይ ነው፡፡ በእውነቱ ምን ያህል ተጎድታ ይሆን ? ምን ይደርስባት ይሆን?
‹‹የእኔ ማር ..እዚህ ጋር ተቀመጪ››አባቷም እጇን ያዘና በመጋረጃ በተሸፈነው ክፍል ውስጥ ባለው ብቸኛ ወንበር ላይ አስቀመጧት ፡፡
‹ኤሊያስ ትክክል ነበር፣ በጣም ገርጥታለች ።››ራሄል እያደገ የመጣውን ድንጋጤዋን ለመቆጣጠር ሞከረች።
‹‹ደህና ነኝ አባባ›› አለች፡፡
ፀጋ እጆቿን ወደ አባቷ እየዘረጋች ‹‹ወደ ታች አውርደኝ›› ስትል ተናገረች።
አቶ ቸርነት ከአልጋው ላይ ልትወርድ ወደ ምትሞክረው ፀጋ እየጠቆሙ ‹‹ራሄል ልትወስጂያት ትችያለሽ?›› ሲሉ ጠየቋት።አባቷ ወደሚያዩት አቅጣጫ ቃኘች፣ ዔሊያስ መጋረጃውን ወደ ጎን ሲያንሸራትተው ሌላ ዶክተር ተከተለውና ወደእነሱ መጣ። በድጋሚ ወደ ፀጋ ተመለከተች፣ በምንም ነገር እርግጠኛ ሳትሆን ልጁቷን ከአልጋው ላይ አነሳችና አቀፈቻት።
‹‹…አዝናለው ጥሩ ያልሆነ ዜና ልነግራችሁ ነው›› አለ ደ/ር ኤሊያስ።
የዶተሩ ከባድ የድምፁ ቃና ራሄልን በፍርሃቷ እንድትርበደበድ እና እንዳትወድቅ በመፍራት ግድግዳውን እንድትይዝ አደረጋት ‹‹ይህ ዶ/ር ምንያህል ይባላል። ሁኔታውን ያብራራላችኋል›› ሲል ተናገረና ቦታውን አዲስ ለመጣው ዶክተር ለቀቀ ፡፡የዶ/ር ምንያህል ፊቱ ፈገግታ ያልተለየው ቢሆንም የዶክተሮችን ስሜት ማንበብ ከባድ እንደሆነ ከብዙ አመት በፊት በደንብ አውቃለች፡፡ እናም ፍርሃቷ ጨመረ።
ምንያህል የተባለው ዶ.ር ወደአባቷ እየተመለከተ ገለፃውን ቀጠለ‹‹የባለቤቶት X ሬይ ውጤት አግኝተናል።››ጥቁሩ አይኖቹ በጥልቅ ርህራሄ ሁለቱንም አስተዋላቸው።‹‹በጣም ከባድ የሆነ የጭን አጥንት ስብራት ገጥሟቸዋል።ከአጥንት በላይ የሆነ ስብራት በሚመስል ነገር የተወሳሰበ ነው። ለረጅም ጊዜ እዚሁ ሆስፒታል ተኝተው መታከም አለባቸው››
አቶ ቸርነት እራሳቸውን ለማረጋጋት ያህል አይናቸውን ጨፈኑ.. ከዛ ከፈቱ …።ራሄል አሁንም ፀጋን በአንድ እጇ ይዛ ቀስ በቀስ ስሯ ያለ ወንበር ላይ ልትቀመጥ ስትሞክር ድንገት ክንዷ ላይ ያለችው እህቷን እንደያዘች ሚዛኗን በመጠኑ ስታ ልትወድቅ ስትል ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተላት የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ተንደረደረና ክንዷን ይዞ በዝግታ እንድትቀመጥ ረዳት፡፡
‹‹አመሰግናለሁ››አለች ራሄል ።
ዔሊያስ እጁ አሁንም በትሁት ትከሻ ላይ ነው።
❤44👍4🥰2
የራሄል ሆዷ ሲገለባበጥ ይታወቃታል እንደገና የማዞር ስሜት ተሰማት።ራሄል ፀጋ ከእጇ ሾልካ ከመውደቋ በፊት ‹‹እባክህ ልትወሰዳት ትችላለህ?››በማለት ወደ ዔሊያስ ገፋቻት፣ ዶ/ር ኤልያስ ግራ አጋቢ እይታ ካያት በኃላ ፀጋን ወሰዳት እና በቀላሉ ወደ እቅፍ አስገባት።ራሄል ወደ ዶ/ር ምንያህል ትኩረቷን ሰበሰበችና ‹‹ይቅርታ ስለ እናቴ እየነገርከን ነበር …ሙሉ በሙሉ የማገገም እድሏ ምን ያህል ነው?"ስትል ጠየቀችው፡፡መልሱን ለመስማት ግን ብርታቱ አልነበራትም፡፡
‹‹በጣም ጥሩ የሚባል ነው:፡፡እርግጥ እንደእሷቸው ብርታትና ጥረት ይወሰናል…ቢሆንም ጊዜ ይወሳዳል እንጂ መዳናቸው አይቀርም፡፡››
‹‹ምን ያህል ጊዜ በሆስፒታል የምትቆይ ይመስልሀል?››አቶ ቸርነት ጠየቁት፡፡
‹‹ከሦስት እስከ አራት ሳምንታት ገደማ ምን አልባትም ከወር በላይ የግድ በሆስፒታል መቆየት አለባቸው…ከዛ በኃላ ያለውን ህክምና ምን አልባት እቤታቸው ሆነው የሚከታተሉበት መንገድ እናመቻች ይሆናል፡፡››
አቶ ቸርነት በቆሙበት አገጫቸውን በእጇቸው እያሻሹ፣ የቦዙ ዓይኖቻቸውን ግድግዳው ላይ ሰክተው በሀሳብ ጠፋ።ወደ ራሔል ተመለከቱ ‹‹ከእናትሽ ጋር ያን ያህል ረጅም ጊዜ መለየት አልችልም..አብሬት እዚህ ምቆየው እኔ ነኝ›› አሉ፡፡
‹‹አውቃለሁ አባዬ›› እጇቸውን ያዘችና ጨመቀቻቸው።
‹‹እና ስለ ፀጋስ?››አባቷ በጭንቀት እና ግራ በመጋባት ጠየቁ።
ዶ/ር ምንያህል ዔሊያስን ተመለከተ። ‹‹ዶክተር ዓሊ የቀሩትን ጥያቄዎችችሁን ሊመልስላችሁ ይችላል ብዬ አስባለሁ. አሁን ወደ ባለቤቶት ሄጄ አንዳንድ ምርመራዎችን ማድረግ አለብኝ፡፡››ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
‹‹አስደሳች ዜና ስለሌለኝ አዝናለሁ፣ ግን ደግሞ ከዚህም የከፋ ጉዳት ስላልደረሰባቸው ልናመሰግነው ይገባል።››ኤልያስ ነው ተናጋሪው፡፡
አቶ ቸርነት በኤልያስ ሀሳብ በመስማማት ‹‹ለቸሩ ጌታ ምስጋና ይድረሰው ››ሲሉ ተናገረሩ፡፡
‹‹ፀጋን ከእኛ ጋር እዚህ መሆን ትችላለች?›› አቶ ቸርነት ዶ/ር ኤሊያስን ጠየቁት፡፡
ኤልያስ ራሱን በአሉታ ነቀነቀ። ‹‹አይ እሷ እቤት መሆን ነው ያለባት … ።›› አለና ወደ ራሔል ተመለከተ፣ ከዚያም ወደ አቶ ቸርነት ተመለሰ። ‹‹እናትሽን ለመርዳት አባትሽ ሙሉ ትኩረታቸውን እሷቸው ላይ ማድረግ አለባቸው… እና ለፀጋ ጤና ደግሞ በዚህ ሁኔታ ውስጥ መገኘት ጥሩ ውጤት አያመጣም።››
‹‹ደህና, ስለ ትንሹ ልጃችን የሆነ ውሳኔ መወሰን እንዳለብኝ ይሰማኛል.››እጇቸውን ራሰ በራ ጭንቅላታቸው ላይ አሳርፈው ወደ ራሄል ዞሩና ፈገግ አሉ‹‹ራሄል፣ ማሬ፣ ፀጋን መንከባከብ ትችያለሽ?››ሲሉ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ? ፀጋን መንከባከብ?››የራሄል ድንጋጤ አስፈሪ ነበር፡፡
እጆቿን እርስ በርሳቸው አቆላለፈች….‹‹ግን ብዙ ስራ መስራት አለብኝ … ማለቴ ፀጋ የምትፈልገውን ያህል ጊዜ አብሬያት ለማሳለፍ እንደምችል እርግጠኛ አይደለሁም›› ራሄል ተርበተበተች፡፡ አቶ ቸርነት ተነፈሱ።
‹‹ሞግዚት እቀጥርላት ነበር፣ ግን እንደምታውቂው እሷ ከአዲስ ሰው ጋር በቶሎ መልመድ አትችልም…በዛ ላይ ትእግስት ኖሮት እሷን በስርዓቱ የሚንከባከብ ሰው ለማግኘት ይከብዳል….ቤት ካሉት ሰራኞች ጋር እንኳን ያላትን ግንኙነት የምታውቂው ነው››በማለት ያሳሰባቸውን ነገር በዝርዝር አስረዷት፡፡
ውይይታቸውን እና በአባትና ልጅ መሀከል የተፈጠረውን ውጥረት በትኩረት ሲከታተል የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ሌላ አማራጭ ፕሮፖዛል ሊያቀርብ ሲዘጋጅ ድንገት ራሄል እጇን በአባቷ ትከሻ ላይ አድርጋ ፈገግ በማለት‹‹ ያልኩት የስራ ጫና እንዳለ ቢሆንም ..ነገር ግን ፀጋ እህቴ ነች። ለእሷ ቅድሚያ መስጠት እንዳለብኝ እገነዘባለው…እና አባዬ አንተ ምንም አታስብ ለእሷ አስፈላጊውን እንክብካቤ እንደማደርግላት አረጋግጥልሀለው።››ስትል ሁለቱም ባልጠበቁት ወኔና ቁርጠኝነት ቃል በመግባት አስደመመቻቸው፡፡
አቶ ቸርነትም ትልቋን ሴት ልጇቸውን በፍቅር ትከሻዋን መታ መታ እያደረጉ ‹‹እናመሰግናለን ውዴ››ሲሉ አመሰገኗት ። ወደ ፀጋ ዞረው አቀፏትና‹‹ ከእህቷ ጋር ከመሄዷ በፊት እናቷን እንድታይ ማድረግ እችላለሁ?›› ሲል ደ/ር ዔሊያስን ጠየቁት።
ዔሊ መጋረጃውን ወደ ጎን ያዘና ‹‹ምን አልባት የመድሀኒቱ ተፅዕኖ ማንንም እንዳይለዩ ሊያደርጋቸው ይችላል ግን መሞከር እንችላለን።››
አቶ ቸርነት ፀጋን ይዘው ወደባለቤታቸው ክፍል ገቡ ፣ ራሄል ተከትላቸው ልትሄድ ስትል ዔሊ ትከሻዋን ያዘና አስቆማት። ወደ ኋላ ተመለሰች። ኮስተርተር አለችበት፡፡
‹‹ለአንድ አፍታ ላናግርሽ ፈልጌ ነበር››አለ ። ራሄል ወደ አባቷ ተመለከተች፣ ከዚያም ወደኃላ ቀረችና ‹‹ እሺ ይቻላል፡፡›› አለችው፡፡
‹‹ፀጋን መንከባከብ የሚከብድሽ ከሆነ ለአንቺ አማራጭ እንደማገኝልሽ እርግጠኛ ነኝ።››አላት፡፡
ራሄል አይኗ ጠበበ። ‹‹አማራጭ አያስፈልገኝም… እህቴ ነች። እሷን በጥንቃቄ መንከባከብና መጠበቅ እችላለሁ።››በንግግሯ ውስጥ ያለውን እርግጠኝነት አስገረመው።
በአስተያየቱ በእሷ እርግጠኛ እንዳልሆነ ተረዳች‹‹አውቃለው…ከዚህ በፊት ልጅ ተንከባክቤ አላውቅም፣ ግን...››በራስ የመተማመን አቅሟ ለአፍታ ቢሆን ሲወርድ ታወቃት። ‹‹ይህን አደርጋለሁ››
‹‹ጥሩ እንደምታደርጊው እርግጠኛ ነኝ ..ወደ ቢሮዬ ለመምጣት ፈቃደኛ ከሆንሽ የሚያስፈልጉሽን መረጃ ልሰጥሽ እችላለሁ›› አላት፡፡
‹‹እሺ››አለችው።
ዔሊያስ የትንሿ ልጅ ጤንነትን በቅርበት የመከታተል ሞያዊም ሆነ ሞራላዊ ግዴታ እንዳለበት ያውቃል። ለዚች ሴት ኩራት ሲባል ያቺ ሚስኪን ልጅ እንድትሰቃይ አይፈቅድም።
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹በጣም ጥሩ የሚባል ነው:፡፡እርግጥ እንደእሷቸው ብርታትና ጥረት ይወሰናል…ቢሆንም ጊዜ ይወሳዳል እንጂ መዳናቸው አይቀርም፡፡››
‹‹ምን ያህል ጊዜ በሆስፒታል የምትቆይ ይመስልሀል?››አቶ ቸርነት ጠየቁት፡፡
‹‹ከሦስት እስከ አራት ሳምንታት ገደማ ምን አልባትም ከወር በላይ የግድ በሆስፒታል መቆየት አለባቸው…ከዛ በኃላ ያለውን ህክምና ምን አልባት እቤታቸው ሆነው የሚከታተሉበት መንገድ እናመቻች ይሆናል፡፡››
አቶ ቸርነት በቆሙበት አገጫቸውን በእጇቸው እያሻሹ፣ የቦዙ ዓይኖቻቸውን ግድግዳው ላይ ሰክተው በሀሳብ ጠፋ።ወደ ራሔል ተመለከቱ ‹‹ከእናትሽ ጋር ያን ያህል ረጅም ጊዜ መለየት አልችልም..አብሬት እዚህ ምቆየው እኔ ነኝ›› አሉ፡፡
‹‹አውቃለሁ አባዬ›› እጇቸውን ያዘችና ጨመቀቻቸው።
‹‹እና ስለ ፀጋስ?››አባቷ በጭንቀት እና ግራ በመጋባት ጠየቁ።
ዶ/ር ምንያህል ዔሊያስን ተመለከተ። ‹‹ዶክተር ዓሊ የቀሩትን ጥያቄዎችችሁን ሊመልስላችሁ ይችላል ብዬ አስባለሁ. አሁን ወደ ባለቤቶት ሄጄ አንዳንድ ምርመራዎችን ማድረግ አለብኝ፡፡››ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
‹‹አስደሳች ዜና ስለሌለኝ አዝናለሁ፣ ግን ደግሞ ከዚህም የከፋ ጉዳት ስላልደረሰባቸው ልናመሰግነው ይገባል።››ኤልያስ ነው ተናጋሪው፡፡
አቶ ቸርነት በኤልያስ ሀሳብ በመስማማት ‹‹ለቸሩ ጌታ ምስጋና ይድረሰው ››ሲሉ ተናገረሩ፡፡
‹‹ፀጋን ከእኛ ጋር እዚህ መሆን ትችላለች?›› አቶ ቸርነት ዶ/ር ኤሊያስን ጠየቁት፡፡
ኤልያስ ራሱን በአሉታ ነቀነቀ። ‹‹አይ እሷ እቤት መሆን ነው ያለባት … ።›› አለና ወደ ራሔል ተመለከተ፣ ከዚያም ወደ አቶ ቸርነት ተመለሰ። ‹‹እናትሽን ለመርዳት አባትሽ ሙሉ ትኩረታቸውን እሷቸው ላይ ማድረግ አለባቸው… እና ለፀጋ ጤና ደግሞ በዚህ ሁኔታ ውስጥ መገኘት ጥሩ ውጤት አያመጣም።››
‹‹ደህና, ስለ ትንሹ ልጃችን የሆነ ውሳኔ መወሰን እንዳለብኝ ይሰማኛል.››እጇቸውን ራሰ በራ ጭንቅላታቸው ላይ አሳርፈው ወደ ራሄል ዞሩና ፈገግ አሉ‹‹ራሄል፣ ማሬ፣ ፀጋን መንከባከብ ትችያለሽ?››ሲሉ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ? ፀጋን መንከባከብ?››የራሄል ድንጋጤ አስፈሪ ነበር፡፡
እጆቿን እርስ በርሳቸው አቆላለፈች….‹‹ግን ብዙ ስራ መስራት አለብኝ … ማለቴ ፀጋ የምትፈልገውን ያህል ጊዜ አብሬያት ለማሳለፍ እንደምችል እርግጠኛ አይደለሁም›› ራሄል ተርበተበተች፡፡ አቶ ቸርነት ተነፈሱ።
‹‹ሞግዚት እቀጥርላት ነበር፣ ግን እንደምታውቂው እሷ ከአዲስ ሰው ጋር በቶሎ መልመድ አትችልም…በዛ ላይ ትእግስት ኖሮት እሷን በስርዓቱ የሚንከባከብ ሰው ለማግኘት ይከብዳል….ቤት ካሉት ሰራኞች ጋር እንኳን ያላትን ግንኙነት የምታውቂው ነው››በማለት ያሳሰባቸውን ነገር በዝርዝር አስረዷት፡፡
ውይይታቸውን እና በአባትና ልጅ መሀከል የተፈጠረውን ውጥረት በትኩረት ሲከታተል የነበረው ዶ/ር ኤልያስ ሌላ አማራጭ ፕሮፖዛል ሊያቀርብ ሲዘጋጅ ድንገት ራሄል እጇን በአባቷ ትከሻ ላይ አድርጋ ፈገግ በማለት‹‹ ያልኩት የስራ ጫና እንዳለ ቢሆንም ..ነገር ግን ፀጋ እህቴ ነች። ለእሷ ቅድሚያ መስጠት እንዳለብኝ እገነዘባለው…እና አባዬ አንተ ምንም አታስብ ለእሷ አስፈላጊውን እንክብካቤ እንደማደርግላት አረጋግጥልሀለው።››ስትል ሁለቱም ባልጠበቁት ወኔና ቁርጠኝነት ቃል በመግባት አስደመመቻቸው፡፡
አቶ ቸርነትም ትልቋን ሴት ልጇቸውን በፍቅር ትከሻዋን መታ መታ እያደረጉ ‹‹እናመሰግናለን ውዴ››ሲሉ አመሰገኗት ። ወደ ፀጋ ዞረው አቀፏትና‹‹ ከእህቷ ጋር ከመሄዷ በፊት እናቷን እንድታይ ማድረግ እችላለሁ?›› ሲል ደ/ር ዔሊያስን ጠየቁት።
ዔሊ መጋረጃውን ወደ ጎን ያዘና ‹‹ምን አልባት የመድሀኒቱ ተፅዕኖ ማንንም እንዳይለዩ ሊያደርጋቸው ይችላል ግን መሞከር እንችላለን።››
አቶ ቸርነት ፀጋን ይዘው ወደባለቤታቸው ክፍል ገቡ ፣ ራሄል ተከትላቸው ልትሄድ ስትል ዔሊ ትከሻዋን ያዘና አስቆማት። ወደ ኋላ ተመለሰች። ኮስተርተር አለችበት፡፡
‹‹ለአንድ አፍታ ላናግርሽ ፈልጌ ነበር››አለ ። ራሄል ወደ አባቷ ተመለከተች፣ ከዚያም ወደኃላ ቀረችና ‹‹ እሺ ይቻላል፡፡›› አለችው፡፡
‹‹ፀጋን መንከባከብ የሚከብድሽ ከሆነ ለአንቺ አማራጭ እንደማገኝልሽ እርግጠኛ ነኝ።››አላት፡፡
ራሄል አይኗ ጠበበ። ‹‹አማራጭ አያስፈልገኝም… እህቴ ነች። እሷን በጥንቃቄ መንከባከብና መጠበቅ እችላለሁ።››በንግግሯ ውስጥ ያለውን እርግጠኝነት አስገረመው።
በአስተያየቱ በእሷ እርግጠኛ እንዳልሆነ ተረዳች‹‹አውቃለው…ከዚህ በፊት ልጅ ተንከባክቤ አላውቅም፣ ግን...››በራስ የመተማመን አቅሟ ለአፍታ ቢሆን ሲወርድ ታወቃት። ‹‹ይህን አደርጋለሁ››
‹‹ጥሩ እንደምታደርጊው እርግጠኛ ነኝ ..ወደ ቢሮዬ ለመምጣት ፈቃደኛ ከሆንሽ የሚያስፈልጉሽን መረጃ ልሰጥሽ እችላለሁ›› አላት፡፡
‹‹እሺ››አለችው።
ዔሊያስ የትንሿ ልጅ ጤንነትን በቅርበት የመከታተል ሞያዊም ሆነ ሞራላዊ ግዴታ እንዳለበት ያውቃል። ለዚች ሴት ኩራት ሲባል ያቺ ሚስኪን ልጅ እንድትሰቃይ አይፈቅድም።
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤51👍17
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
❤66👍3
‹‹ለጊዜህ አመሰግናለሁ፣ ዶ/ር ኤሊያስ እንደምንገናኝ እርግጠኛ ነኝ።››አለችው፡፡
ዔሊያስም በሩን ሊከፍትላት በጠረጴዛው ዙሪያ ዞሮ ተራመደ..
ራሄል ስለጸጋ የጤና ችግር የሰማችው ነገር አእምሮዋ ሊሸከም ከሚችለው በላይ ነው የሆነባት፡፡እንዴት እንደምትወጣውም መገመት አልቻለችም፡፡
ዓሊ ከዚህ በፊት በግዴለሽነት የፍቅር ግንኙነት ቢጀምርም፣ ዘላቂነት ላለው ግንኙነት ግን ዝግጁ ሀኖ አያውቅም ነበር ። አሁንም እንደ ራሄል ካለች ሴት ጋር ተመሳሳዩን ማድረግ እንደማይችል ያውቃል፡፡ እሷ ሌሎች ምታስቀድማቸው ጉዳዮች እንዳሏት ተረድቷል, እርግጥ ቤተሰቦቿ ከእሱ ጋር እንዳትገናኝ ተስፋ እንዳደረጉ ያውቃል፡፡ በዋነኛነት የእሱን ጀርባ ምን እንደሆነ ባለማወቃቸው ነው። ወላጆቹን ማንነት ቢያውቁ እንደዛ እንደማያስብ እርግጠኛ ነው፡፡ ኮፍያውን ይዞ ቢሮውን ለቆ ወደ ቤቱ አመራ።
ወደ ቤቱ ሲገባ ስልኩ እየጮኸ ነበር እና የጥሪ ማሳያውን በጨረፍታ ተመለከተ ፈገግ አለና አነሳው።‹‹ሄይ እናቴ እንዴት ነሽ?›› ስልኩን በትከሻውና በጆሮው መካከል አድርጎ ጠየቀ። እናቱ የቤቱን ሁኔታ ማየት እንደማትችል ቢያውቅም የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶታል።
‹‹ደህና ነኝ። ጧት የት ነበርክ?›› አሳዳጊ እናቱ ጠየቀችው፡፡ ‹‹ሁለት ጊዜ ሞክሬልህ ነበር.›› በድምጿ ውስጥ የስጋት ስሜት ይነበባል ፣ ይህም ዔሊን የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት›› እንዲሰማው አድርጎታል።
‹‹ የእረፍት ቀኔ ነበር ..ግን ሆስፒታል ድንገተኛ ተደወለልኝና ስራ ገባው…ገና በር ከፍቼ ስገባ ነው የደወልሺልኝ.››
‹‹አንተም ሆንክ ቢኒ ቤተክርስቲያን ትመጣላችሁ ብዬ ጠብቄ ነበር..አንተስ እሺ ስራ ላይ ነኝ አልክ… የእሱስ ሰበብ ምንድነው?››
ሰበቡን ያውቃል..እሱ ብቻ ሳይሆን አሳዳጊ እናቱም ጭምር ለምን በቤተክርስቲያን መሄድ እንዳቆመ በደንብ ያውቃሉ..እሱ እንኳን ድሮም ለቤተክርስቲያን እስከዚህም ነበር ወንድሙ ግን ባለቤቱ በአንድሳምንት በሽታ ታማ ሳይታሰብ እስክትሞትበት ድረስ በጣም አካራሪ የሚባል ሀይማኖተኛ ሰው ነበር…ከዛ በኋላ ግን ቀስ በቀስ እግሩን ከቤተክርስቲያን ልቡን ደግሞ ከእግዚያብሄር ሰበሰበ…..በዚህ ጉዳይ ከራሄል ጋር ተመሳሳይ ታሪክ እንዳላቸው ያውቃል…አሁን ግን ይህንን የወንድሙን ጉዳይ ከእናቱ ጋር አንስቶ መጨቃጨቅ ስላልፈለገ በዝምታ ዘለለው
እሱ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ጋር የነበረው ዝምድና ሁል ጊዜ ወጣ ገባ ያለው ነበር ። አሳዳጊዎቹ ከእሱ ይልቅ ከቢኒያም ጋር ንፁህ በፍቅር የተሞላ የወላጅ እና የልጅ ግንኙነት ነው ያላቸው፡፡ እሱ ግን ስለ ስጋ ወላጆቹ ማወቅ ይፈልግ ስለነበር ብዙ ጊዜ ባየተዋርነት ይሰማው ነበርና እቤት ውስጥ በራሱ ችግር ይፈጥራ ል… ስለወላጆቹ የሚያውቁትን እንዲነግሩት ያስቸግራቸው ነበር ..እነሱ ግን ምንም ሊነግሩት አልቻሉም።
ባለፈው ዓመት እሱ እና ቢንያም የወላጆቻቸውን ቤት እያፀዱ ሳለ በሰገነት ላይ የፎቶ ሳጥን አገኘ. እነዛን ፎቶዎች ከዚህ በፊት አይቷቸው አያውቅም ነበር ፡ የእሱ የስጋ ወላጆቹ ነበሩ። አሳዳጊዎቹ እሱን ከማደጎ ቤት በተረከቡት ጊዜ ፎቶውንም አብረው ነበር የተረከቡት… ከዛ ግን አርቀው አስቀመጡና ረሱት ፡፡
‹‹ወደ ሆስፒታል እንደተጠራህ ተናግረሃል›› ስትል እናቱ ተናገረች። ‹‹በጣም ከባድ ነገር እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ.››ዔሊ ራሔልን እና ጸጋን አሰበ እና ግንባሩን በጣቱ አሻሸ።
‹‹ከታካሚዬ አንዷ ወደቀች፣ ግን ደህና ነች፣ አንቺ እና አባ እንዴት ናችሁ?››
‹‹ደህና ነን ፡ ግን አንዳንድ ጊዜ መጥተን አንተን እና ቢኒን ቤቱን እንደትጨረሱት ልንረዳችሁ እንፈልግ ነበር።››
‹‹እሺ እማማ፣ አንቺና አባባ በዚህ ጉዳይ ላይ እንድትጨናነቁ አልፈልግም። ››
የእናቱ ዝምታ ሌላ የጥፋተኝነት ስሜት ፈጠረ።
ተሰናበታቸውና እና ስልኩን ዘጋው፡፡
በዚህ ቤት ጉዳይ ወላጆቹንም ሆነ ወንድሙ ቢኒያምን ብዙ ማስቸገር አይፈልግም፡፡
- ይህንን ቤት መስራት መጀመሩ ለእሱ ትልቅ ስኬት ነው ፣ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የራሱን ቦታ ይፈልግ ነበር ፡፡ እራሱን የሚገነባበት ቦታ። ይህንን ለአሳዳጊ ወላጆቹ በቀላሉ ማስረዳት የሚችለው ነገር አልነበረም፣ ። ገና ወንደላጤነቱን ሳያጣጥም ብድር ውስጥ ገብቶ እቤት ወደመገንባት ውስጥ የገባበትን ምክንያት ቢኒያም እንኳን አልተረዳውም።ምክንያቱም ወንድሙ እንደ እሱ ስለ ስጋ ወላጅቹ ምንም አይነት ትዝታ አልነበረውም። ለእሱ አሳዳጊ ወላጆቹ የስጋ ወላጆቹ እንደሆኑ ነው የሚሰማውም…የሚያምነውም፡፡
እርግጥ ኤልያስም አሳዳጊ ወላጆቹን ይወዳል ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከእነሱ ጋር ለመኖር ወደቤታቸው ሲወስዱት የስጋ ወላጆቹን ትዝታዎች በጀርባው አዝሎ ስለነበረ በተለየ ሁኔታ በጣም ያስቸግራቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ስለ ወላጆቹ በጭራሽ ማውራት አቆሙ፡፡ ኤሊ የዛሬ አመት ፎቶዎቹን እስኪያገኝ ድረስ ይህን ተቀብሎ ነበር።አሁን .የፎቶ ሣጥኑን ወደቤቱ አምጥቶታል እነኚያ ሰዎች እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ሙከራ ላይ ነው፡፡ ህይወት የሰጡት ወደዚህ ምድር ጎትተው ያመጡት፤እነዛን የመጀመሪያዎቹን ጥቂት የህፃንነት አመታትን ይንከባከቡት የነበሩትን ሰዎች ማነነት የማወቅ ጉጉት እያሰቃየው ነው።
ሳያውቅ እጁን አዞረና ጀርባ ላይ ያለውን ጠባሳ አሻሸው፣ከአደጋውን ያተረፈው ቅሪት ነው ።ስለ ፀጋ አሰበ። ገና ህፃን ስለሆነች ወደፊት ስለ እናቷ ምንም ትዝታ እንዳማይኖራት ተስፋ አደረገ ። ግን ቢያንስ ለእሷ እሱ አለላት..እናቷ ምን አይነት ሰው እንደሆነች….ስለደግነቷ..ስለውበቷ እና ስለአስቂኝ ጫወታዋ …በዝርዝር ሊነግራት ይችላል፡፡ከፈለገችም…አሁን በህይወት ስለሌሉት አያቶቹም ጭምር ሊነግራት ይችላል…ምክንያቱም የእናቷ የፅጌረዳን እናትና አባት ከልጅነቱ ጀምሮ በደንብ ያውቃቸዋል…ፅጌረዳ ተከትሎ ብዙ ጊዜ እቤታቸው የመመላለስ እድል ነበረው..ደሆች ቢሆኑም ልበ ቀና መልካም ሰዎች ነበሩ…ይሄንን ሁሉ ሊያስረዳት ይችላል..ለእሱ ግን እንደዚህ አይነት ስለዋላጆቹ ጥቂት እንኳን አውቃለው የሚል ሰው የማግኘት እድል የለውም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ዔሊያስም በሩን ሊከፍትላት በጠረጴዛው ዙሪያ ዞሮ ተራመደ..
ራሄል ስለጸጋ የጤና ችግር የሰማችው ነገር አእምሮዋ ሊሸከም ከሚችለው በላይ ነው የሆነባት፡፡እንዴት እንደምትወጣውም መገመት አልቻለችም፡፡
ዓሊ ከዚህ በፊት በግዴለሽነት የፍቅር ግንኙነት ቢጀምርም፣ ዘላቂነት ላለው ግንኙነት ግን ዝግጁ ሀኖ አያውቅም ነበር ። አሁንም እንደ ራሄል ካለች ሴት ጋር ተመሳሳዩን ማድረግ እንደማይችል ያውቃል፡፡ እሷ ሌሎች ምታስቀድማቸው ጉዳዮች እንዳሏት ተረድቷል, እርግጥ ቤተሰቦቿ ከእሱ ጋር እንዳትገናኝ ተስፋ እንዳደረጉ ያውቃል፡፡ በዋነኛነት የእሱን ጀርባ ምን እንደሆነ ባለማወቃቸው ነው። ወላጆቹን ማንነት ቢያውቁ እንደዛ እንደማያስብ እርግጠኛ ነው፡፡ ኮፍያውን ይዞ ቢሮውን ለቆ ወደ ቤቱ አመራ።
ወደ ቤቱ ሲገባ ስልኩ እየጮኸ ነበር እና የጥሪ ማሳያውን በጨረፍታ ተመለከተ ፈገግ አለና አነሳው።‹‹ሄይ እናቴ እንዴት ነሽ?›› ስልኩን በትከሻውና በጆሮው መካከል አድርጎ ጠየቀ። እናቱ የቤቱን ሁኔታ ማየት እንደማትችል ቢያውቅም የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶታል።
‹‹ደህና ነኝ። ጧት የት ነበርክ?›› አሳዳጊ እናቱ ጠየቀችው፡፡ ‹‹ሁለት ጊዜ ሞክሬልህ ነበር.›› በድምጿ ውስጥ የስጋት ስሜት ይነበባል ፣ ይህም ዔሊን የበለጠ የጥፋተኝነት ስሜት›› እንዲሰማው አድርጎታል።
‹‹ የእረፍት ቀኔ ነበር ..ግን ሆስፒታል ድንገተኛ ተደወለልኝና ስራ ገባው…ገና በር ከፍቼ ስገባ ነው የደወልሺልኝ.››
‹‹አንተም ሆንክ ቢኒ ቤተክርስቲያን ትመጣላችሁ ብዬ ጠብቄ ነበር..አንተስ እሺ ስራ ላይ ነኝ አልክ… የእሱስ ሰበብ ምንድነው?››
ሰበቡን ያውቃል..እሱ ብቻ ሳይሆን አሳዳጊ እናቱም ጭምር ለምን በቤተክርስቲያን መሄድ እንዳቆመ በደንብ ያውቃሉ..እሱ እንኳን ድሮም ለቤተክርስቲያን እስከዚህም ነበር ወንድሙ ግን ባለቤቱ በአንድሳምንት በሽታ ታማ ሳይታሰብ እስክትሞትበት ድረስ በጣም አካራሪ የሚባል ሀይማኖተኛ ሰው ነበር…ከዛ በኋላ ግን ቀስ በቀስ እግሩን ከቤተክርስቲያን ልቡን ደግሞ ከእግዚያብሄር ሰበሰበ…..በዚህ ጉዳይ ከራሄል ጋር ተመሳሳይ ታሪክ እንዳላቸው ያውቃል…አሁን ግን ይህንን የወንድሙን ጉዳይ ከእናቱ ጋር አንስቶ መጨቃጨቅ ስላልፈለገ በዝምታ ዘለለው
እሱ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ጋር የነበረው ዝምድና ሁል ጊዜ ወጣ ገባ ያለው ነበር ። አሳዳጊዎቹ ከእሱ ይልቅ ከቢኒያም ጋር ንፁህ በፍቅር የተሞላ የወላጅ እና የልጅ ግንኙነት ነው ያላቸው፡፡ እሱ ግን ስለ ስጋ ወላጆቹ ማወቅ ይፈልግ ስለነበር ብዙ ጊዜ ባየተዋርነት ይሰማው ነበርና እቤት ውስጥ በራሱ ችግር ይፈጥራ ል… ስለወላጆቹ የሚያውቁትን እንዲነግሩት ያስቸግራቸው ነበር ..እነሱ ግን ምንም ሊነግሩት አልቻሉም።
ባለፈው ዓመት እሱ እና ቢንያም የወላጆቻቸውን ቤት እያፀዱ ሳለ በሰገነት ላይ የፎቶ ሳጥን አገኘ. እነዛን ፎቶዎች ከዚህ በፊት አይቷቸው አያውቅም ነበር ፡ የእሱ የስጋ ወላጆቹ ነበሩ። አሳዳጊዎቹ እሱን ከማደጎ ቤት በተረከቡት ጊዜ ፎቶውንም አብረው ነበር የተረከቡት… ከዛ ግን አርቀው አስቀመጡና ረሱት ፡፡
‹‹ወደ ሆስፒታል እንደተጠራህ ተናግረሃል›› ስትል እናቱ ተናገረች። ‹‹በጣም ከባድ ነገር እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ.››ዔሊ ራሔልን እና ጸጋን አሰበ እና ግንባሩን በጣቱ አሻሸ።
‹‹ከታካሚዬ አንዷ ወደቀች፣ ግን ደህና ነች፣ አንቺ እና አባ እንዴት ናችሁ?››
‹‹ደህና ነን ፡ ግን አንዳንድ ጊዜ መጥተን አንተን እና ቢኒን ቤቱን እንደትጨረሱት ልንረዳችሁ እንፈልግ ነበር።››
‹‹እሺ እማማ፣ አንቺና አባባ በዚህ ጉዳይ ላይ እንድትጨናነቁ አልፈልግም። ››
የእናቱ ዝምታ ሌላ የጥፋተኝነት ስሜት ፈጠረ።
ተሰናበታቸውና እና ስልኩን ዘጋው፡፡
በዚህ ቤት ጉዳይ ወላጆቹንም ሆነ ወንድሙ ቢኒያምን ብዙ ማስቸገር አይፈልግም፡፡
- ይህንን ቤት መስራት መጀመሩ ለእሱ ትልቅ ስኬት ነው ፣ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የራሱን ቦታ ይፈልግ ነበር ፡፡ እራሱን የሚገነባበት ቦታ። ይህንን ለአሳዳጊ ወላጆቹ በቀላሉ ማስረዳት የሚችለው ነገር አልነበረም፣ ። ገና ወንደላጤነቱን ሳያጣጥም ብድር ውስጥ ገብቶ እቤት ወደመገንባት ውስጥ የገባበትን ምክንያት ቢኒያም እንኳን አልተረዳውም።ምክንያቱም ወንድሙ እንደ እሱ ስለ ስጋ ወላጅቹ ምንም አይነት ትዝታ አልነበረውም። ለእሱ አሳዳጊ ወላጆቹ የስጋ ወላጆቹ እንደሆኑ ነው የሚሰማውም…የሚያምነውም፡፡
እርግጥ ኤልያስም አሳዳጊ ወላጆቹን ይወዳል ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከእነሱ ጋር ለመኖር ወደቤታቸው ሲወስዱት የስጋ ወላጆቹን ትዝታዎች በጀርባው አዝሎ ስለነበረ በተለየ ሁኔታ በጣም ያስቸግራቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ስለ ወላጆቹ በጭራሽ ማውራት አቆሙ፡፡ ኤሊ የዛሬ አመት ፎቶዎቹን እስኪያገኝ ድረስ ይህን ተቀብሎ ነበር።አሁን .የፎቶ ሣጥኑን ወደቤቱ አምጥቶታል እነኚያ ሰዎች እነማን እንደሆኑ ለማወቅ ሙከራ ላይ ነው፡፡ ህይወት የሰጡት ወደዚህ ምድር ጎትተው ያመጡት፤እነዛን የመጀመሪያዎቹን ጥቂት የህፃንነት አመታትን ይንከባከቡት የነበሩትን ሰዎች ማነነት የማወቅ ጉጉት እያሰቃየው ነው።
ሳያውቅ እጁን አዞረና ጀርባ ላይ ያለውን ጠባሳ አሻሸው፣ከአደጋውን ያተረፈው ቅሪት ነው ።ስለ ፀጋ አሰበ። ገና ህፃን ስለሆነች ወደፊት ስለ እናቷ ምንም ትዝታ እንዳማይኖራት ተስፋ አደረገ ። ግን ቢያንስ ለእሷ እሱ አለላት..እናቷ ምን አይነት ሰው እንደሆነች….ስለደግነቷ..ስለውበቷ እና ስለአስቂኝ ጫወታዋ …በዝርዝር ሊነግራት ይችላል፡፡ከፈለገችም…አሁን በህይወት ስለሌሉት አያቶቹም ጭምር ሊነግራት ይችላል…ምክንያቱም የእናቷ የፅጌረዳን እናትና አባት ከልጅነቱ ጀምሮ በደንብ ያውቃቸዋል…ፅጌረዳ ተከትሎ ብዙ ጊዜ እቤታቸው የመመላለስ እድል ነበረው..ደሆች ቢሆኑም ልበ ቀና መልካም ሰዎች ነበሩ…ይሄንን ሁሉ ሊያስረዳት ይችላል..ለእሱ ግን እንደዚህ አይነት ስለዋላጆቹ ጥቂት እንኳን አውቃለው የሚል ሰው የማግኘት እድል የለውም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤71👍12
የራሄል ልብ በእፎይታ ተነፈሰ።አብሮት እየተራመደ ያለውን ተለማማጅ ዶ/ር ወደ ጎን ተመለከተው፣ እያወሩ ነበር ። ድንገት ዞር ሲል ከራሄል ጋር አይን ለአይን ተገጣጠሙ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገናኙ የተሰማትን አይነት ተመሳሳይ ምላሽ ተሰማት። ተንደርድሮ ወደእሷ መጣ፡፡
ከዚያም የፀጋን የህክምና ቻርት ላይ የሆነ ምልክት እያደረገች ወዳለችው ነርስ ተጠጋና ተመለከተ። ‹ታዲያ ችግሩ ምን ይመስላሻል ?›› ብሎ ጠየቀ ከራሄል ወደ ፀጋ ከዚያም ወደ ነርሷ ተመለከተ። ራሄል ‹‹ከፍኛ ትኩሳት አላት›› አለችው.
ነርሷ ‹‹አሁን የሙቀት መጠንዋን ወስጃለሁ….ትንሽ ከፍ ያለ ነው፣ ግን ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም።››
ራሔል ነርሷ ላይ አፈጠጠች ፣ግራ ተጋባች፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለከተች። ‹‹ በጣም እኮ ነበር የምትሞቀው.››
ዔሊ ሰንጠረዡን ከነርሷ ተቀብሎ ተመለከተ እና እጁን በህፃኗ ግንባሩ ላይ አደረገ። ፀጋ በድንገት ሁሉም ነገር ደህና የሆነ ይመስል ፈገግ አለችለት‹‹አሁንም አንቲ ባዮቲኮችን እየሰጠሻት ነው?›››
‹‹አዎ ››
‹‹ደህና፣ እየሰሩ ያሉ ይመስላሉ፣ ግን ፈገግታዋ ጠፍቷል፣ የድምፁ ቃናዋም ተለውጣል፣ እሷን መናደድ የለባትም››
‹‹የምን መናደድ …ከሰአት በኋላ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ለመንከባከብ የተመሰከረለትን የመዋለ ሕጻናት አገኘሁ።እና እዛ ወሰድኳት..ከስራ ተመልሼ ልወስዳት ስሄድ ታማ አገኘኋት… እና አሁን የሚያስፈልገኝ በእሷ ላይ ያለውን ችግር እንድትነግሩኝ ነው።››
ዔሊያስ በትንሹ ተነፈሰ… ነገር ግን ዓይኖቿን ራሄል ላይ እያንከራተተች ወዳለችው ታዳጊ ልጅ ተመለከተ። የታችኛው ከንፈሯ ያብለጨልጭ ጀመር እና እንደገና ልታለቅስ ያሰበች ይመስላል ። ራሄል ጀርባዋን እየደባበሰች አባበለቻት፡፡
በወረቀት ላይ ማስታወሻዎችን እየጻፈ። ‹‹ደህና ነች..አዎ፣ የሙቀት መጠኑ በትንሹ ከፍ ብሏል፣ ግን ያ ስለተበሳጨች ሊሆን ይችላል። አንድ ጆሮዋ ትንሽ ቀላ ያለ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ በፀረ-ባዮቲክስ መድሀኒት ይወርዳል። መበሳጨት ከጀመረች ስጧት። የሙቀት መጠኗን መቆጣጠሪያ በእጅሽ ላይ ሊኖርሽ ይገባል.. የሚያስፈልጉሽን ነገሮች ዝርዝር ነገ እሰጥሻለሁ፤››አለና ወረቀቱን ከፓድ ላይ ቀዶ ዘረጋላት።ራሄል በድንገት ሞኝነት ተሰማት፣ነገር ግን ፀጋ ደህና መሆኗን በማወቋ እፎይታ አግኝታለች።
ወረቀቱን ወደ ቦርሳዋ እያስገባች‹‹ለምክርህ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹በዚህ ኢንፌክሽን ደረጃ ለማረጋገጥ ከነገ ወዲያ እሷን ማየት እፈልጋለሁ። ለአንቺ ስንት ሰዓት ይምችሻል?››በጥያቄው ስለተበሳጨች እኩለ ሌሊት ልትለው አሰበች. ፡፡
‹‹ለምን አንተ ቀጠሮ አትይዝልኝም እኔ ፕሮግራሜን ማሸጋሸግ እችላለው፡፡ ››አለችው፡፡
‹‹ቤት ላገኝሽ ካልቻልኩ… የት ላገኝሽ እችላለሁ?››
የቢሮ ቁጥሯን እና የሞባይል ስልኳን ሰጠችው።በስራ ቦታ ልታገኘኝ ካልቻልክ ለሎዛ መልእክት ተውልኝ። ሞባይል ስልኬ በአብዛኛው ክፍት ነው። በተጨማሪም የወላጆቼ ቁጥር አለህ። ››
የንዴት ፈገግታ አሳያት።‹‹እነዚህ ሁሉ ቁጥሮች አያስፈልጉኝም?››
በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከወ.ሮ ላምሮት ጋር መገናኘት ነበረባት እና አሁን ለፀጋ የምትገዛቸው መድሀኒቶች አሉ..በዛ ላይ ምግቧንም መመገብ አለባት….በዚህ ሁኔታ ላይም እያለች ጥላት መሄድ አትችልም ፡፡ያላት ምርጫ ሴትዬዋን ይቅርታ ጠይቃ ሌላ ቀጠሮ ማስያዝ ነው፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››አለች.
‹‹ትሁትን ስላየህልኝ አመሰግናለሁ፣››አለችው በድጋሜ
‹‹ ከሁለት ቀናት በኋላ እንገናኝ።››አለና የድንገተኛ ክፍልን ለቅ ወጣ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ከዚያም የፀጋን የህክምና ቻርት ላይ የሆነ ምልክት እያደረገች ወዳለችው ነርስ ተጠጋና ተመለከተ። ‹ታዲያ ችግሩ ምን ይመስላሻል ?›› ብሎ ጠየቀ ከራሄል ወደ ፀጋ ከዚያም ወደ ነርሷ ተመለከተ። ራሄል ‹‹ከፍኛ ትኩሳት አላት›› አለችው.
ነርሷ ‹‹አሁን የሙቀት መጠንዋን ወስጃለሁ….ትንሽ ከፍ ያለ ነው፣ ግን ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም።››
ራሔል ነርሷ ላይ አፈጠጠች ፣ግራ ተጋባች፣ ከዚያም ወደ ዔሊ ተመለከተች። ‹‹ በጣም እኮ ነበር የምትሞቀው.››
ዔሊ ሰንጠረዡን ከነርሷ ተቀብሎ ተመለከተ እና እጁን በህፃኗ ግንባሩ ላይ አደረገ። ፀጋ በድንገት ሁሉም ነገር ደህና የሆነ ይመስል ፈገግ አለችለት‹‹አሁንም አንቲ ባዮቲኮችን እየሰጠሻት ነው?›››
‹‹አዎ ››
‹‹ደህና፣ እየሰሩ ያሉ ይመስላሉ፣ ግን ፈገግታዋ ጠፍቷል፣ የድምፁ ቃናዋም ተለውጣል፣ እሷን መናደድ የለባትም››
‹‹የምን መናደድ …ከሰአት በኋላ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ልጆች ለመንከባከብ የተመሰከረለትን የመዋለ ሕጻናት አገኘሁ።እና እዛ ወሰድኳት..ከስራ ተመልሼ ልወስዳት ስሄድ ታማ አገኘኋት… እና አሁን የሚያስፈልገኝ በእሷ ላይ ያለውን ችግር እንድትነግሩኝ ነው።››
ዔሊያስ በትንሹ ተነፈሰ… ነገር ግን ዓይኖቿን ራሄል ላይ እያንከራተተች ወዳለችው ታዳጊ ልጅ ተመለከተ። የታችኛው ከንፈሯ ያብለጨልጭ ጀመር እና እንደገና ልታለቅስ ያሰበች ይመስላል ። ራሄል ጀርባዋን እየደባበሰች አባበለቻት፡፡
በወረቀት ላይ ማስታወሻዎችን እየጻፈ። ‹‹ደህና ነች..አዎ፣ የሙቀት መጠኑ በትንሹ ከፍ ብሏል፣ ግን ያ ስለተበሳጨች ሊሆን ይችላል። አንድ ጆሮዋ ትንሽ ቀላ ያለ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ በፀረ-ባዮቲክስ መድሀኒት ይወርዳል። መበሳጨት ከጀመረች ስጧት። የሙቀት መጠኗን መቆጣጠሪያ በእጅሽ ላይ ሊኖርሽ ይገባል.. የሚያስፈልጉሽን ነገሮች ዝርዝር ነገ እሰጥሻለሁ፤››አለና ወረቀቱን ከፓድ ላይ ቀዶ ዘረጋላት።ራሄል በድንገት ሞኝነት ተሰማት፣ነገር ግን ፀጋ ደህና መሆኗን በማወቋ እፎይታ አግኝታለች።
ወረቀቱን ወደ ቦርሳዋ እያስገባች‹‹ለምክርህ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹በዚህ ኢንፌክሽን ደረጃ ለማረጋገጥ ከነገ ወዲያ እሷን ማየት እፈልጋለሁ። ለአንቺ ስንት ሰዓት ይምችሻል?››በጥያቄው ስለተበሳጨች እኩለ ሌሊት ልትለው አሰበች. ፡፡
‹‹ለምን አንተ ቀጠሮ አትይዝልኝም እኔ ፕሮግራሜን ማሸጋሸግ እችላለው፡፡ ››አለችው፡፡
‹‹ቤት ላገኝሽ ካልቻልኩ… የት ላገኝሽ እችላለሁ?››
የቢሮ ቁጥሯን እና የሞባይል ስልኳን ሰጠችው።በስራ ቦታ ልታገኘኝ ካልቻልክ ለሎዛ መልእክት ተውልኝ። ሞባይል ስልኬ በአብዛኛው ክፍት ነው። በተጨማሪም የወላጆቼ ቁጥር አለህ። ››
የንዴት ፈገግታ አሳያት።‹‹እነዚህ ሁሉ ቁጥሮች አያስፈልጉኝም?››
በግማሽ ሰዓት ውስጥ ከወ.ሮ ላምሮት ጋር መገናኘት ነበረባት እና አሁን ለፀጋ የምትገዛቸው መድሀኒቶች አሉ..በዛ ላይ ምግቧንም መመገብ አለባት….በዚህ ሁኔታ ላይም እያለች ጥላት መሄድ አትችልም ፡፡ያላት ምርጫ ሴትዬዋን ይቅርታ ጠይቃ ሌላ ቀጠሮ ማስያዝ ነው፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››አለች.
‹‹ትሁትን ስላየህልኝ አመሰግናለሁ፣››አለችው በድጋሜ
‹‹ ከሁለት ቀናት በኋላ እንገናኝ።››አለና የድንገተኛ ክፍልን ለቅ ወጣ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤31🤔13👏6
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
❤43