"እንጃ ውስጤ ሰላም አይሰማኝም፡፡ ዛሬ ደግሞ ሲያቃዠኝ ነው ያደረው"፡፡
ተመስገን ቅዠት ይሁን ህልም መፍታት ባይችልም ፤ ለመስማት ስለፈለገ ብቻ "ምንድ ነው ያቃዠሽ ንገሪኝ" አላት፡፡
"ቅዠት ይሁን ህልም ባላቀውም የሆነ ሰው ይመስለኛል ፤ ሲያባርረኝ እየሮጥሁ ከእሱ ለማምለጥ ስል ገደል ገባሁ፡፡ ከዚያ ብንን ስል ያለሁት መኝታየ ላይ ነው" አለች፡፡ አሁንም የፍራትና የጭንቀት ምልክት እየተሰማት፡፡
ተመስገን በግምትም ቢሆን ገደል መግባቷ መጥፎ ህልም ሳይሆን አይቀርም ብሎ በውስጡ አሰበ፡፡
እድላዊት የነገረችውን ህልም ከአሁን አሁን ፈቶ ይነግረኛል ብላ ብትጠብቅም ሳይፈታላትና ሳይመልስላት ትምህርት ቤት ደረሱ፡፡
"ታመመሽ አስፈቅደን እንመለሳለን" አላትና ሁለቱም የሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ቢሆኑም ክላሳቸው ስለሚለያይ ተጨባብጠው ወደዬ ክላሳቸው ገቡ፡፡
እድላዊት ለትምህርት ያላት ፍላጎት ወደር የለውም ነበር፡፡ ዛሬ ግን በተፈጠረባት የጭንቀት ስሜት የምትወደው ትምህርት አስጠልቷታል፡፡ እንደ ነብር ዘሎ የሚውጣት መስሎም ታይቷታል፡፡
መድረስ አይቀርም ሰዓት ደርሶ ተማሪ ተለቀቀ፡፡ እድላዊት ትምህርት ቤት ይሁን የፀሎት ቦታ ያለችበት ተዘንግቷታል፡፡ የመለቀቂያ ሰዓት ደርሶ ውጡ ሲባል እንኳን አላመነችም ነበር፡፡ ከተማሪዎች ቀድማ ወጣች፡፡ ወንድሟን መንገድ ላይ ስትጠብቅ ቆይታ ሲመጣ አብረው ጉዟቸውን ወደ ቤት ቀጠሉ፡፡
"አሁንም አልተሻለሽም እንዴ? ብሎ እጇን ጨበጥ አደረጋት፡፡
"ከጥዋቱ አሁን ተሸሎኛል" አለች፡፡ የሆዷ መረበሽና ጭንቀት እየባሰባት ቢመጣም ወንድሟ ላለማስጨነቅ ብላ፡፡
ተመስገንም አይዞሽ፡፡ እያለ እያፅናናት እቤት ደረሱ፡፡
እናታቸው ወ/ሮ አሰገደች "መጣችሁ አሉ፡፡
"አዎ ፤ መጥተናል" አለች እድላዊት፡፡
በይ! ምሳችሁን ብሉና ተመስገን ከብቶቹን ውሃ ያጠጣ፡፡ አንች ስራ ትረጅኛለሽ ብለው ወደ ማድቤት ገቡ፡፡ እንጀራ ለመጋገር የገለባ ማገዷቸውን ማቀጣጠል ጀመሩ፡፡
እድላዊት ምሳዋን ተመግባ እንደደበራት እናቷን ለማገዝ ወደ ማድቤት ገባች፡፡ "ምን ልርዳሽ ? አለች፡፡ ወደ እናቷ እየተጠጋች፡፡
"አንች ወጡን ስሪ ፤ እኔ እንጀራውን ቶሎ ቶሎ ልጋግር፡፡ አባትሽም ከቤተክርስቲያን መምጫው ሰዓት ደርሷል"አሏት፡፡
እሽ ብላ መስራት ጀመረች፡፡ እናትና ልጅ የተኮራረፉ ይመስላል፡፡ ሁለቱም በዝምታ ተውጠው ስራ ስራቸውን ይላሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የእድላዊት ዝምታ ከምን የመጣ እንደሆነ ግራ ገብቷቸዋል፡፡ ዝም በማለቷ ተጠራጠሩ ፤ ሰምታ ይሆን እንዴ? ባል እንደመጣላት ; ማንስ ይነግራታል? ለነገሩ የዛሬ ወሬ አይደበቅም፡፡ ንፋስ የሚያወራው ይመስል ውሎ ሳያድር አገሩን ያዳርሰዋል፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሲከራከሩ ከቆዩ በኋላ፤ "ምን ሆነሽ ነው ዛሬ ያለወትሮሽ ዝም ያልሽው?
አሞሻል እንዴ? አሉ፡፡ ቁጣ የተቀላቀለበት በሚመስል ንግግር፡፡
"አላመመኝም" አለች እድላዊት፡፡
"እና ምን ሆነሽ ነው? አሏት፡፡ አሁንም ቁጣ ቁጣ በሚል ንግግራቸው፡፡
እድላዊት የእናቷ ቁጣ የተቀላቀለበት ንግግር አልገባትም፡፡ "ከትምህርት ስለመጣሁ ደከሞኝ ይሆናል፡፡ ሌላ ምንም አልሆንኩም" አለች፡፡ አቀርቅራ የወጥ መስሪያ ሽንኩርቷን እየላጠች፡፡
አይ! ድካም ከሆነ ምንም ማለት አይደለም፡፡ የሰማሽው ወሬ እንዳለ ብየ ነው አሉ፡፡ የልጃቸው መልስ ባይዋጥላቸውም፡፡
እድላዊት ግን የሆነችውንና የተሰማትን ለመናገር አልፈለገችም፡፡ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ "የምን ወሬ ነው የምሰማው? አለች እንደ መደንገጥ ብላ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ገና ሳይነግሯት የልብ ትርታቸው ጨመረ፡፡ እየፈሩ ብነግራት ምን ትል ይሆን? ብትደነግጥስ ምን ትሆናለች? በማለት እራሳቸውን አፅናኑ፡፡ ለመናገር ወሰኑ፡፡ ስልታዊ አነጋገር እንኳን አልተጠቀሙም፡፡ በቀጥታ "ካልሰማሽማ እኔው ልንገርሽ ባል መቶልሻል፡፡ ከነገ ጀምረሽ ትምህርት ቤት አትሔጅም፡፡ ትምህርቱን ትተሸ የቤት ውስጥ ሙያ ትለምጃለሽ አሏት፡፡
ታዲያ ወ/ሮ አሰገደች ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረው በመናገራቸው ለራሳቸው ቢቀላቸውም ለልጃቸው ግን ከሰማይ የመጣ ዱብዳ ሆኖባታል፡፡
እድላዊት በሰማችው ነገር ደነገጠች፡፡ በተቀመጠችበት ጉጉት ሆና ቀረች፡፡ አትናገር አትጋገር ፍጥጥ ብላ
እናቷን ታያለች፡፡
‹‹የአፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽ ሆነና ነገሩ›› ወ/ሮ አሰገደች በልጃቸው ሁኔታ ተደናግጠው ምነው ባልነገርኳት፡፡ እያወኩ ፣ ሆዴ እየፈራ ፣ እየተርበተበቱ ራሳቸውን መውቀስ ጀመሩ፡፡
እድላዊት እናቷ የተናገሯትን ማመን አቃታት፡፡ መልስም አልሰጠችም፡፡ ቀኑ ሁሉ ሲጨንቃት የነበረውና ሲያምሳት የዋለው ይሔ የወደፊት አላማዋንና ሃሳቧን ከግብ አይደለም ከማሃል እንኳን ሳይደርስ ወሽመጧን የሚቆርጥ መርዶ ሊያሰማት መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ ከሔደችበት የሀሳብ ሰመመን አልተመለሰችም፡፡ ባል! ባል! ባል! እኮ ባል መጥቶልሻል ታገቢያለሽ አለች እናቴ፡፡ በቃ ወስነዋል ማለት ነው?፡፡ የእኔ መጨረሻ ይሔ ሆነ?፡፡ በውስጧ እልህና ቁጭት አደረባት፡፡ ከወሰዳት የድንጋጤ መንፈስ መለስ አለች፡፡ ከየት መጣ ሳይባል እንባዋ ግራና ቀኝ በጉንጮቿ ላይ መውረዱን ተያያዙት፡፡
ቄስ መልካሙ ከቤተክርስቲያን ተመልሰው መጡ፡፡ እድላዊት እያለቀሰች ደረሱ፡፡ ምን ሆና ነው የምታለቅሰው ነገርሻት እንዴ? ባል እንደመጣላት" አሉ ለባቤታቸው፡፡
አዎ"ነግሬያት ነበር፡፡
"እና እሷስ ምንም አላለችሽም"?፡
"ምንም አላለችም፡፡ ይኸው እንደምታያት ዝም ብላ ትነፋረቃለች፡፡ እስኪ አንተን የምሰማህ ከሆነ ዝም እንድትል አድርጋት''
የባለቤታቸው መርበትበትና መረበሽን የተካፈሉት ይመስላል፡፡ እድላዊትን ለማናገር ሆዳቸው ፈራ ተባ አለ፡፡ "ምን ሆነሽ ነው? የምትነፋረቂው" አሏት፡፡ በፊታቸው ላይ የቁጣ ምልክት በማሳየት፡፡
እድላዊት የባሰ አባቷን ስታይ እንባዋን መቆጣጠር አቃታት፡፡ መልስ ለመስጠት ተርበተበተች፡፡ እልህ ተናነቃት፡፡ "ምን ሆነሽ ነው ትለኛለህ ? ስራህን ሰርተህ ከጨረስህ በኋላ!፡፡ ግን የማገባ ይመስልሃል ትምህርቴን ሳልጨርስ አላገባም፡፡ ቆሜ እቀራለሁ እንጅ ብላ እልህና ንዴት በተቀላቀለበት ንግግር አባቷን ከአሁን በፊት ደፍራ ተናግራቸው የማታውቀውን ተናገረቻቸው፡፡
ቄስ መልካሙ ከልጃቸው የሰሙት ንዴት የተቀላቀለበት ንግግር አስከፊና መመለሻ የሌለው መስሎ ታያቸው፡፡ ልጃቸውን ተቆጥተውና አስፈራርተው መናገር ስላለባቸው "ታገቢያለሽ"፡፡ ስለ ማግባትሽ ደግሞ አንች ሳትሆኝ የምትወስኝው እኔ አባትሽ ነኝ፡፡ አሁን ተነስተሸ ወደ ቤት ግቢ መነፋረቁን ትተሸ" አሉ፡፡ በዱላ የመምታት ያህል በሚሰማ ንግግራቸው፡፡
እድላዊት በአባቷ ቁጣ ብትደነግጥም እንባዋ ግን መውረዱን ቀጥሏል፡፡ እንባዋን ሳያቋርጥ እያለቀሰች ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ እራሷን አሟት ስለነበር መኝታዋን ሳታነጥፍ ጋደም እንዳለች እንቅልፍ ሸለብ አደረጋት፡፡
ተመስገን እቤት ሲገባ የሰማውንና ያየውን ትርኢት ማመን አቃተው፡፡ በሰማው ነገር ግራ ተጋባ፡፡ ሃዘንም ተሰማው፡፡ ሆዱ ተረበሸ፡፡ አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ በማይል የማይለካ እሩቅ የመድረስ አላማና ተስፋው ፍሬ ሳያፈራ አይደለም እንቡጥ እንኳን ሳይዝ መቀጨቱ ታወቀው፡፡ የእህቴ ምኞትና ተስፋ የእኔም ነበር፡፡ አሁን ግን አበቃለት ፤ አከተመለት፡፡ በሃዘን በተሞላ እና እንባ በተናነቀው አንደበቱ ሰው ሳይሰማው ለራሱ እየተጨናነቀና እያማረረ የተናገረው ነበር፡፡
ተመስገን ቅዠት ይሁን ህልም መፍታት ባይችልም ፤ ለመስማት ስለፈለገ ብቻ "ምንድ ነው ያቃዠሽ ንገሪኝ" አላት፡፡
"ቅዠት ይሁን ህልም ባላቀውም የሆነ ሰው ይመስለኛል ፤ ሲያባርረኝ እየሮጥሁ ከእሱ ለማምለጥ ስል ገደል ገባሁ፡፡ ከዚያ ብንን ስል ያለሁት መኝታየ ላይ ነው" አለች፡፡ አሁንም የፍራትና የጭንቀት ምልክት እየተሰማት፡፡
ተመስገን በግምትም ቢሆን ገደል መግባቷ መጥፎ ህልም ሳይሆን አይቀርም ብሎ በውስጡ አሰበ፡፡
እድላዊት የነገረችውን ህልም ከአሁን አሁን ፈቶ ይነግረኛል ብላ ብትጠብቅም ሳይፈታላትና ሳይመልስላት ትምህርት ቤት ደረሱ፡፡
"ታመመሽ አስፈቅደን እንመለሳለን" አላትና ሁለቱም የሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ቢሆኑም ክላሳቸው ስለሚለያይ ተጨባብጠው ወደዬ ክላሳቸው ገቡ፡፡
እድላዊት ለትምህርት ያላት ፍላጎት ወደር የለውም ነበር፡፡ ዛሬ ግን በተፈጠረባት የጭንቀት ስሜት የምትወደው ትምህርት አስጠልቷታል፡፡ እንደ ነብር ዘሎ የሚውጣት መስሎም ታይቷታል፡፡
መድረስ አይቀርም ሰዓት ደርሶ ተማሪ ተለቀቀ፡፡ እድላዊት ትምህርት ቤት ይሁን የፀሎት ቦታ ያለችበት ተዘንግቷታል፡፡ የመለቀቂያ ሰዓት ደርሶ ውጡ ሲባል እንኳን አላመነችም ነበር፡፡ ከተማሪዎች ቀድማ ወጣች፡፡ ወንድሟን መንገድ ላይ ስትጠብቅ ቆይታ ሲመጣ አብረው ጉዟቸውን ወደ ቤት ቀጠሉ፡፡
"አሁንም አልተሻለሽም እንዴ? ብሎ እጇን ጨበጥ አደረጋት፡፡
"ከጥዋቱ አሁን ተሸሎኛል" አለች፡፡ የሆዷ መረበሽና ጭንቀት እየባሰባት ቢመጣም ወንድሟ ላለማስጨነቅ ብላ፡፡
ተመስገንም አይዞሽ፡፡ እያለ እያፅናናት እቤት ደረሱ፡፡
እናታቸው ወ/ሮ አሰገደች "መጣችሁ አሉ፡፡
"አዎ ፤ መጥተናል" አለች እድላዊት፡፡
በይ! ምሳችሁን ብሉና ተመስገን ከብቶቹን ውሃ ያጠጣ፡፡ አንች ስራ ትረጅኛለሽ ብለው ወደ ማድቤት ገቡ፡፡ እንጀራ ለመጋገር የገለባ ማገዷቸውን ማቀጣጠል ጀመሩ፡፡
እድላዊት ምሳዋን ተመግባ እንደደበራት እናቷን ለማገዝ ወደ ማድቤት ገባች፡፡ "ምን ልርዳሽ ? አለች፡፡ ወደ እናቷ እየተጠጋች፡፡
"አንች ወጡን ስሪ ፤ እኔ እንጀራውን ቶሎ ቶሎ ልጋግር፡፡ አባትሽም ከቤተክርስቲያን መምጫው ሰዓት ደርሷል"አሏት፡፡
እሽ ብላ መስራት ጀመረች፡፡ እናትና ልጅ የተኮራረፉ ይመስላል፡፡ ሁለቱም በዝምታ ተውጠው ስራ ስራቸውን ይላሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የእድላዊት ዝምታ ከምን የመጣ እንደሆነ ግራ ገብቷቸዋል፡፡ ዝም በማለቷ ተጠራጠሩ ፤ ሰምታ ይሆን እንዴ? ባል እንደመጣላት ; ማንስ ይነግራታል? ለነገሩ የዛሬ ወሬ አይደበቅም፡፡ ንፋስ የሚያወራው ይመስል ውሎ ሳያድር አገሩን ያዳርሰዋል፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሲከራከሩ ከቆዩ በኋላ፤ "ምን ሆነሽ ነው ዛሬ ያለወትሮሽ ዝም ያልሽው?
አሞሻል እንዴ? አሉ፡፡ ቁጣ የተቀላቀለበት በሚመስል ንግግር፡፡
"አላመመኝም" አለች እድላዊት፡፡
"እና ምን ሆነሽ ነው? አሏት፡፡ አሁንም ቁጣ ቁጣ በሚል ንግግራቸው፡፡
እድላዊት የእናቷ ቁጣ የተቀላቀለበት ንግግር አልገባትም፡፡ "ከትምህርት ስለመጣሁ ደከሞኝ ይሆናል፡፡ ሌላ ምንም አልሆንኩም" አለች፡፡ አቀርቅራ የወጥ መስሪያ ሽንኩርቷን እየላጠች፡፡
አይ! ድካም ከሆነ ምንም ማለት አይደለም፡፡ የሰማሽው ወሬ እንዳለ ብየ ነው አሉ፡፡ የልጃቸው መልስ ባይዋጥላቸውም፡፡
እድላዊት ግን የሆነችውንና የተሰማትን ለመናገር አልፈለገችም፡፡ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ "የምን ወሬ ነው የምሰማው? አለች እንደ መደንገጥ ብላ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ገና ሳይነግሯት የልብ ትርታቸው ጨመረ፡፡ እየፈሩ ብነግራት ምን ትል ይሆን? ብትደነግጥስ ምን ትሆናለች? በማለት እራሳቸውን አፅናኑ፡፡ ለመናገር ወሰኑ፡፡ ስልታዊ አነጋገር እንኳን አልተጠቀሙም፡፡ በቀጥታ "ካልሰማሽማ እኔው ልንገርሽ ባል መቶልሻል፡፡ ከነገ ጀምረሽ ትምህርት ቤት አትሔጅም፡፡ ትምህርቱን ትተሸ የቤት ውስጥ ሙያ ትለምጃለሽ አሏት፡፡
ታዲያ ወ/ሮ አሰገደች ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረው በመናገራቸው ለራሳቸው ቢቀላቸውም ለልጃቸው ግን ከሰማይ የመጣ ዱብዳ ሆኖባታል፡፡
እድላዊት በሰማችው ነገር ደነገጠች፡፡ በተቀመጠችበት ጉጉት ሆና ቀረች፡፡ አትናገር አትጋገር ፍጥጥ ብላ
እናቷን ታያለች፡፡
‹‹የአፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽ ሆነና ነገሩ›› ወ/ሮ አሰገደች በልጃቸው ሁኔታ ተደናግጠው ምነው ባልነገርኳት፡፡ እያወኩ ፣ ሆዴ እየፈራ ፣ እየተርበተበቱ ራሳቸውን መውቀስ ጀመሩ፡፡
እድላዊት እናቷ የተናገሯትን ማመን አቃታት፡፡ መልስም አልሰጠችም፡፡ ቀኑ ሁሉ ሲጨንቃት የነበረውና ሲያምሳት የዋለው ይሔ የወደፊት አላማዋንና ሃሳቧን ከግብ አይደለም ከማሃል እንኳን ሳይደርስ ወሽመጧን የሚቆርጥ መርዶ ሊያሰማት መሆኑን አላወቀችም ነበር፡፡ ከሔደችበት የሀሳብ ሰመመን አልተመለሰችም፡፡ ባል! ባል! ባል! እኮ ባል መጥቶልሻል ታገቢያለሽ አለች እናቴ፡፡ በቃ ወስነዋል ማለት ነው?፡፡ የእኔ መጨረሻ ይሔ ሆነ?፡፡ በውስጧ እልህና ቁጭት አደረባት፡፡ ከወሰዳት የድንጋጤ መንፈስ መለስ አለች፡፡ ከየት መጣ ሳይባል እንባዋ ግራና ቀኝ በጉንጮቿ ላይ መውረዱን ተያያዙት፡፡
ቄስ መልካሙ ከቤተክርስቲያን ተመልሰው መጡ፡፡ እድላዊት እያለቀሰች ደረሱ፡፡ ምን ሆና ነው የምታለቅሰው ነገርሻት እንዴ? ባል እንደመጣላት" አሉ ለባቤታቸው፡፡
አዎ"ነግሬያት ነበር፡፡
"እና እሷስ ምንም አላለችሽም"?፡
"ምንም አላለችም፡፡ ይኸው እንደምታያት ዝም ብላ ትነፋረቃለች፡፡ እስኪ አንተን የምሰማህ ከሆነ ዝም እንድትል አድርጋት''
የባለቤታቸው መርበትበትና መረበሽን የተካፈሉት ይመስላል፡፡ እድላዊትን ለማናገር ሆዳቸው ፈራ ተባ አለ፡፡ "ምን ሆነሽ ነው? የምትነፋረቂው" አሏት፡፡ በፊታቸው ላይ የቁጣ ምልክት በማሳየት፡፡
እድላዊት የባሰ አባቷን ስታይ እንባዋን መቆጣጠር አቃታት፡፡ መልስ ለመስጠት ተርበተበተች፡፡ እልህ ተናነቃት፡፡ "ምን ሆነሽ ነው ትለኛለህ ? ስራህን ሰርተህ ከጨረስህ በኋላ!፡፡ ግን የማገባ ይመስልሃል ትምህርቴን ሳልጨርስ አላገባም፡፡ ቆሜ እቀራለሁ እንጅ ብላ እልህና ንዴት በተቀላቀለበት ንግግር አባቷን ከአሁን በፊት ደፍራ ተናግራቸው የማታውቀውን ተናገረቻቸው፡፡
ቄስ መልካሙ ከልጃቸው የሰሙት ንዴት የተቀላቀለበት ንግግር አስከፊና መመለሻ የሌለው መስሎ ታያቸው፡፡ ልጃቸውን ተቆጥተውና አስፈራርተው መናገር ስላለባቸው "ታገቢያለሽ"፡፡ ስለ ማግባትሽ ደግሞ አንች ሳትሆኝ የምትወስኝው እኔ አባትሽ ነኝ፡፡ አሁን ተነስተሸ ወደ ቤት ግቢ መነፋረቁን ትተሸ" አሉ፡፡ በዱላ የመምታት ያህል በሚሰማ ንግግራቸው፡፡
እድላዊት በአባቷ ቁጣ ብትደነግጥም እንባዋ ግን መውረዱን ቀጥሏል፡፡ እንባዋን ሳያቋርጥ እያለቀሰች ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ እራሷን አሟት ስለነበር መኝታዋን ሳታነጥፍ ጋደም እንዳለች እንቅልፍ ሸለብ አደረጋት፡፡
ተመስገን እቤት ሲገባ የሰማውንና ያየውን ትርኢት ማመን አቃተው፡፡ በሰማው ነገር ግራ ተጋባ፡፡ ሃዘንም ተሰማው፡፡ ሆዱ ተረበሸ፡፡ አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ በማይል የማይለካ እሩቅ የመድረስ አላማና ተስፋው ፍሬ ሳያፈራ አይደለም እንቡጥ እንኳን ሳይዝ መቀጨቱ ታወቀው፡፡ የእህቴ ምኞትና ተስፋ የእኔም ነበር፡፡ አሁን ግን አበቃለት ፤ አከተመለት፡፡ በሃዘን በተሞላ እና እንባ በተናነቀው አንደበቱ ሰው ሳይሰማው ለራሱ እየተጨናነቀና እያማረረ የተናገረው ነበር፡፡
👍74❤11
ቤተሰቦቹንም ሆነ እህቱን ሳያነጋግር ወደ መኝታው ሄደ፡፡ ጭንቀቱና መረበሹ የሚቀልለት መስሎት እራት እንኳን ሳይበላ መኝታው ላይ ጋደም አለ፡፡ መረበሹና ጭንቀቱን ሊያስታግስለት ግን አልቻለም፡፡ እንቅልፍ የሚባል አልወስድ ብሎታል፡፡ መኝታው የቆረቆረው ይመስል እየተገላበጠ ሌሊቱን ሁሉ አሳልፎ
ሳይወስደው ያደረው እንቅልፍ ሊነጋጋ አካባቢ መጥቶ ሸለብ አደረገው፡፡
ቄስ መልካሙ የተፈጠረው ነገር ሁሉ አሳስቧቸዋል፡፡ እድላዊትን በመቆጣታቸው እና በማስፈራራታቸው ተፀፅተዋል፡፡ ምነው? ባልተቆጣኋት፤ ቀስ ብየ ብመክራት ይሻል ነበር፡፡ አሁን ከሆነ ወዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እንግዲህ ነገ የተሻላት እንደሆነ ቀስብየ እመክራታለሁ፡፡ በስጋ ከባለቤታቸው ጋር ቢሆኑም በመንፈስ ግን የት እንደደረሱ ባይታወቃቸውም እራሳቸውን ለማረጋጋት ያወሩት ነበር፡፡
ወ/ሮ አሰገደች እንደ ባለቤታቸው በሃሳብ ፈረስ ነጉደው ሲመለሱ "የተመስገን ደግሞ ተደርቦ ማኩረፍ ምን ይሉታል?" አሉ ፤ ከባለቤታቸው መልስ የሚያገኙ መስሏቸው፡፡
ተመስገንና እድላዊት በተፈጠረው ነገር ከእናት አባታቸው ጋር አለማምሽታቸው ቤቱን በሃዘን የተዋጠ አስመስሎታል፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
ሳይወስደው ያደረው እንቅልፍ ሊነጋጋ አካባቢ መጥቶ ሸለብ አደረገው፡፡
ቄስ መልካሙ የተፈጠረው ነገር ሁሉ አሳስቧቸዋል፡፡ እድላዊትን በመቆጣታቸው እና በማስፈራራታቸው ተፀፅተዋል፡፡ ምነው? ባልተቆጣኋት፤ ቀስ ብየ ብመክራት ይሻል ነበር፡፡ አሁን ከሆነ ወዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እንግዲህ ነገ የተሻላት እንደሆነ ቀስብየ እመክራታለሁ፡፡ በስጋ ከባለቤታቸው ጋር ቢሆኑም በመንፈስ ግን የት እንደደረሱ ባይታወቃቸውም እራሳቸውን ለማረጋጋት ያወሩት ነበር፡፡
ወ/ሮ አሰገደች እንደ ባለቤታቸው በሃሳብ ፈረስ ነጉደው ሲመለሱ "የተመስገን ደግሞ ተደርቦ ማኩረፍ ምን ይሉታል?" አሉ ፤ ከባለቤታቸው መልስ የሚያገኙ መስሏቸው፡፡
ተመስገንና እድላዊት በተፈጠረው ነገር ከእናት አባታቸው ጋር አለማምሽታቸው ቤቱን በሃዘን የተዋጠ አስመስሎታል፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍62❤2
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቄስ አሻግሬ
ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡
ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡
አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡
"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡
"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡
"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::
"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡
አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡
"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡
ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡
አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡
እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?
ተመስገን
ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡
እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡
ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡
የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡
ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡
ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡
ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡
የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ
"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡
እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡
ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቄስ አሻግሬ
ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡
ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡
አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡
"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡
"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡
"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::
"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡
አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡
"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡
ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡
አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡
እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?
ተመስገን
ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡
እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡
ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡
የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡
ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡
ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡
ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡
የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ
"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡
እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡
ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
👍73❤5👏3
ተመስገን እህቱን ፍለጋ እንደወጣ ቶሎ አልተመለሰም፡፡ እየተንከራተተ አንዴ እራራቲ ፤ አንዴ ዶፋ ፤ አንዴ ብቻሽ እና በየቤተክርስቲያኑ እየዞረ ቢጠይቅም ቢያጠያይቅም ፤ ቢያስስም ፣ ቢያሳስስም እድላዊትን ግን ሊያገኛት አልቻለም ነበር፡፡ ተንከራቶ እህቱን ባለማግኘቱ በጣም አዘነ፡፡ የተፈጠረበት ቀን እስከ ሚያስጠላው ድረስ አምርሮ ረገመ፡፡ እያለቀሰ ቢውልና ቢያድርም የሱን እንባ እድላዊት ልትሰማለት አልቻለችም፡፡
እድላዊት እና ተመስገን ትምህርት ቤት እንኳን ሲሔዱ አንድ ቀንም ተለያይተው አያውቁም ነበር፡፡ በጣም ሲዋደዱ እና ፍቅራቸውን ላየ የሚያስቀኑም ልጆች ነበሩ፡፡
ተመስገን እህቱን ፍለጋ ሲወጣ በቅርብ የሚመለስ መስሎት ስንቅ እንኳን አልያዘም፡፡ እርሃብ ሲብስበት እና ሲጠናበት ከሰው ቤት እዳይለምን እፍረት እየያዘው ሳይጠይቅ ሲርበው ውሎ ሲርበው ያድራል፡፡ ለማደር ሲፈልግ ፀበለተኛ መስሎ ሲመሽበት ወደ አገኘው ቤተክርስቲያን ይሄዳል፡፡ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና ፀበለተኞች ከያዙት ስንቅ አካፍለውት በልቶ ሳይሆን ቀምሶ ያድር ነበር፡፡
ታዲያ የሚያውቀውንም ፣ የማያውቀውንም ፣ አገር አካሎ ከመድከም ውጭ ምንም ባለ ማግኘቱ ሲንከራተት ከርሞ ወደ ቤቱ ለመመለስ ሲያስብ የእናት አባቱን አይን ለማየት አስጠልቶት እኔም እንደ እድላዊት ብን ብየ በዚሁ ልጥፋ ወይስ ገደል እና ውሃ ውስጥ ገብቼ ብሞት ይሻላል፡፡ በውስጡ የተሰማውን ተናግሮ ሳይጨርስ ልቡ በሌላ ሃሳብ ይቀየርበታል፡፡ እህቴን ሳላያት ከምሞት ከቤት ከወጣሁ ቆይቻለሁ፡፡ ምን አልባት ተመልሳ እቤት መጥታ ሊሆን ይችላል፡፡ ብሎ በማሰብ ከራሱ ሃሳብ ጋር ሲሟገት እና ሲከራከር ቆይቶ ወደ ቤቱ ለመሔድ ወሰነ ።
ተመስገን ጉዞ ላይም እያለ በሃሳቡ ስለ እህቱ ማብሰልሰሉን ይሁን መጨነቁን አላቋረጠም፡፡ ምነው ያን እለት ማታ ባናግራት፡የምትሔድበትን እንኳን ትነግረኝ ነበር፡፡ ለእኔ አትደብቀኝም ነበር፡፡ ይሔ ሁሉ ስቃይና መንከራተትም አይደርስብኝም ነበር፡፡ ያለፈው እያናደደው ሲጓዝ መድረስ አይቀርም እቤቱ ደረሰ፡፡
እናት እና ልጅ ለብዙ ቀን ተለያይተው እንዳልቆዩ አብረው እንደከረሙ እና አብረው እንዳደሩ ሰላም እንኳን አልተባባሉም፡፡ በቀጥታ እድላዊት አልመጣችም እንዴ?" አላቸው፡፡ እልህ እና ንዴት በተቀላቀለበት አንደበት፡፡
"አይ! ልጄ ከየት ትመጣለች፡፡ እሳት የገባ ቅቤ ይታፈሳል እንዴ? እግዚአብሔር ባያድለኝ ነው እንጅ፡፡ ምነው እንዳሁኑስ የነገርኳት እለት ሞቴን ቢያደርግልኝ ይሻል ነበር"፡፡ እስካሁን በሔድህበት ቦታ እና አካባቢ ምንም ወሬዋን አልሰማህም ? አየኋት ፣ አልፋለች የሚል ሰው ጠፋ ልጄ? "አሉት፡፡ የአይናቸውን እንባ እየጠራረጉ ፡፡
ተመስገን ከእናቱ የሰማው መልስ ተስፋ አስቆረጠው፡፡ እድላዊት ወደ ቤት መታ እቤት አገኛታለሁ ያለው ሃሳብ አልተሳካለትም፡፡ መጓጓቱ እና ማሰቡ ከንቱ ሆነ፡፡ እንዳትገኝ አድርጋችሁ ከሸኛችኋት በኋላ፤ ማንስ አየሁ ይለኛል ? የትስ አገኛታለሁ?"፡፡
ወደ ቤት ሲመጣ እመንገድ ላይ እህል አምጣ እያለ እንደ አዲስ መሬት ያስቸገረው ሆዱ እቤት ሲገባ እድላዊትን ባለማግኝቱ በንዴት እና በብስጭት የራበው ሁሉ ጠፋ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የልጃቸው ብሶትና ብስጭት ተሰማቸው፡፡ ሳይታወቃቸው በግራና በቀኝ ጉንጫቸው ላይ እንባቸው እንደ ሃምሌ ዝናብ መውረዱን ተያያዘው፡፡ ታዲያ እንባቸው ሲወርድ ላየው ሰው ወላድ መሆን አይደለም ሰው መሆንም ያስጠላ ነበር፡፡ ደግመው ለመናገር እንባ ተናነቃቸው፡፡ መናገር አልቻሉም፡፡ አንደበታቸው ተሳሰረ፡፡ ከተቀመጡበት ተነሱ፡፡ እንባቸውን በቀሚሳቸው እየጠራረጉ ወደ ጓዳ ሊገቡ ሲሉ ራሳቸውን አዞራቸው ፤ ከቤቱ ግድግዳ ጋር ተላተሙ፡፡
ተመስገን እናቱ በልጇ መጥፋት ሆድ እንደባሳቸውና በሃዘን እንደ ተጎዱ ታወቀው የእድላዊት መጥፋት ሳያንሰው የእናቱ እንደዚህ መሆን የባሰ ስቅስቅ አድርጎ አስለቀሰው፡፡
ከተላተሙበት የቤት ግድግዳ ተመለሱ፡፡ እንደገና አዙሯቸው የቤቱ ወለል ላይ ወደቁ፡፡ ከወደቁበት ሳይነሱ
ጆሮ ግንዳቸውን በቀኝ እጃቸው ደግፈው አቀረቀሩ፡፡ ምን ነክቷቸው ከግድግዳ እንደተላተሙ ለማስታወስ እየሞከሩ ፤ ካቀረቀሩበት ቀና ሲሉ ልጃቸው እያለቀሰ አዩት፡፡ ማፅናናታቸውን ትተው ያቋረጡት ለቅሶ ተያያዙት፡፡
ቄስ መልካሙ ከስራ ቆይተው ሲመለሱ ቤቱ በሃዘን እና በለቅሶ ተሞልቷል፡፡ "ምንድነው ለቅሶው ; ልጄ መሞቷ ተሰማ እንዴ ? ምን ተፈጥሮ ነው "አሉ፡፡ አይኖቻቸው ላይ የእንባ ብዥታ እየታየባቸው፡፡
"የልጄን መሞት እማ ብሰማ አንዴ አልቅሼ እና እርሜን አውጥቸ አርፍ ነበር"፡፡ የገባችበትን እና የበላትን ጅብ አለመጮሁ ነው እንጅ ፤ የሚያስለቅሰኝ" አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡
ተመስገን አባቱ ሲመጡ ማልቀሱን ባያቋርጥም እያለቀሰ በአባቱ ፊት መቆየት አልፈለገም፡፡ እረስቷት ወደ ሰነበተው የመኝታ ቤቱ ተነስቶ ሄደ፡፡
"ተመስገን ምን አለሽ ? እንዴው ወሬዋን እንኳን የሰማ ሰው አላገኘም ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ ለባለቤታቸው ፡፡
"ያየ አይደለም ሰማሁ የሚልም አላገኘም፡፡ እሱም እንዴው ሲንከራተት ከርሞ ይሔው ሰውነቱ አልቆ መጣ፡፡ እኔ ደግሞ ሲሰነብት ጊዜ በዛው ሔደ ብየ ፈርቼ ነበር፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ፊቱን ወደ ቤት መለሰልኝ" እንጅ ፡፡ቄስ መልካሙ ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረውን እንባ በጋቢያቸው ጠራርገው መለሱት፡፡
"ምን እናደርጋለን ታዲያ እንግዴህ አንዴ ሲፈጥረን ተሰቃዩ ብሎን የለ፡፡ የእኔ መሞቻ የቀረው እናት አባቴን ያጣሁ ዕለት ነበር"፡፡ ምነው ያኔ ከነሱ ጋር ሞቴን ብታደርግልኝ፡፡ ምን አለ ፈጣሪየ ፣ ምን በደልኩህ ; ምንስ አልኩህ ? የአንተ አገልጋይ እንኳን ነበርኩ፡፡ ስቃየን እነደዚህ ባታበዛብኝ ምን ? አለ"፡፡
መጀመሪያ ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረውን እንባ በጋቢያቸው ጠርገው ቢመልሱትም አሁን ግን ገፍቶ መጥቷል፡፡ ሊመልሱት አልቻሉም፡፡ የተናነቃቸውን እንባ ዘረገፉት፡፡
ቄስ መልካሙ በምንጃር አውራጃ ውስጥ ጉራንባ ማርያም በሚባል ጎጥ ተወልደው ባደጉበት አካባቢ የድቁና ትምህርታቸውን በጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን እየተከታተሉ ባሉበት ሰዓት ነበር፡፡ እናት አባታቸውን በመብረቅ አደጋ በሞት የተነጠቁት፡፡ ለእናት አባታቸው አንድ ልጅ ብቻ ነበሩ፡፡ እናት አባታቸው ከሞቱባቸው በኋላ ፤ ያላሳዳጊ ብቻቸውን በባዶ ቤት ሲሰቃዩ ቆይተው ከአራት አመት እንግልት በኋላ፤ ነበር፡፡ ወ/ሮ አሰገደችን አግብተው ተመስገንን እና እድላዊትን ማፍራት የቻሉት፡፡
ታዲያ ተመስገን የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን እድላዊት ሁለተኛ ልጃቸውም ነበረች፡፡
"በቃህ! አይበቃህም ወይ! ለቅሶ አልነው ፤ አልነው፡፡ እድላዊት በለቅሶ የምትመጣ ቢሆን እስካሁን ባልቆየች ነበር፡፡ የባሰ ስታለቅስ አይንህን እንዳታጣና በንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዳይሆን፡፡ እንግዴህ እግዚአብሔር ከፈቀደ ልቧን አራርቶት ተመልሳ ልትመጣ ትችላለች፡፡ አይታወቅም፡፡ ሰጭውም ነሽውም እሱ አንድ አምላክ እስከሆነ ድረስ አደራውን ለሱ መስጠት ነው አሉ ፤ ወ/ ሮ አሰገደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
እድላዊት እና ተመስገን ትምህርት ቤት እንኳን ሲሔዱ አንድ ቀንም ተለያይተው አያውቁም ነበር፡፡ በጣም ሲዋደዱ እና ፍቅራቸውን ላየ የሚያስቀኑም ልጆች ነበሩ፡፡
ተመስገን እህቱን ፍለጋ ሲወጣ በቅርብ የሚመለስ መስሎት ስንቅ እንኳን አልያዘም፡፡ እርሃብ ሲብስበት እና ሲጠናበት ከሰው ቤት እዳይለምን እፍረት እየያዘው ሳይጠይቅ ሲርበው ውሎ ሲርበው ያድራል፡፡ ለማደር ሲፈልግ ፀበለተኛ መስሎ ሲመሽበት ወደ አገኘው ቤተክርስቲያን ይሄዳል፡፡ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና ፀበለተኞች ከያዙት ስንቅ አካፍለውት በልቶ ሳይሆን ቀምሶ ያድር ነበር፡፡
ታዲያ የሚያውቀውንም ፣ የማያውቀውንም ፣ አገር አካሎ ከመድከም ውጭ ምንም ባለ ማግኘቱ ሲንከራተት ከርሞ ወደ ቤቱ ለመመለስ ሲያስብ የእናት አባቱን አይን ለማየት አስጠልቶት እኔም እንደ እድላዊት ብን ብየ በዚሁ ልጥፋ ወይስ ገደል እና ውሃ ውስጥ ገብቼ ብሞት ይሻላል፡፡ በውስጡ የተሰማውን ተናግሮ ሳይጨርስ ልቡ በሌላ ሃሳብ ይቀየርበታል፡፡ እህቴን ሳላያት ከምሞት ከቤት ከወጣሁ ቆይቻለሁ፡፡ ምን አልባት ተመልሳ እቤት መጥታ ሊሆን ይችላል፡፡ ብሎ በማሰብ ከራሱ ሃሳብ ጋር ሲሟገት እና ሲከራከር ቆይቶ ወደ ቤቱ ለመሔድ ወሰነ ።
ተመስገን ጉዞ ላይም እያለ በሃሳቡ ስለ እህቱ ማብሰልሰሉን ይሁን መጨነቁን አላቋረጠም፡፡ ምነው ያን እለት ማታ ባናግራት፡የምትሔድበትን እንኳን ትነግረኝ ነበር፡፡ ለእኔ አትደብቀኝም ነበር፡፡ ይሔ ሁሉ ስቃይና መንከራተትም አይደርስብኝም ነበር፡፡ ያለፈው እያናደደው ሲጓዝ መድረስ አይቀርም እቤቱ ደረሰ፡፡
እናት እና ልጅ ለብዙ ቀን ተለያይተው እንዳልቆዩ አብረው እንደከረሙ እና አብረው እንዳደሩ ሰላም እንኳን አልተባባሉም፡፡ በቀጥታ እድላዊት አልመጣችም እንዴ?" አላቸው፡፡ እልህ እና ንዴት በተቀላቀለበት አንደበት፡፡
"አይ! ልጄ ከየት ትመጣለች፡፡ እሳት የገባ ቅቤ ይታፈሳል እንዴ? እግዚአብሔር ባያድለኝ ነው እንጅ፡፡ ምነው እንዳሁኑስ የነገርኳት እለት ሞቴን ቢያደርግልኝ ይሻል ነበር"፡፡ እስካሁን በሔድህበት ቦታ እና አካባቢ ምንም ወሬዋን አልሰማህም ? አየኋት ፣ አልፋለች የሚል ሰው ጠፋ ልጄ? "አሉት፡፡ የአይናቸውን እንባ እየጠራረጉ ፡፡
ተመስገን ከእናቱ የሰማው መልስ ተስፋ አስቆረጠው፡፡ እድላዊት ወደ ቤት መታ እቤት አገኛታለሁ ያለው ሃሳብ አልተሳካለትም፡፡ መጓጓቱ እና ማሰቡ ከንቱ ሆነ፡፡ እንዳትገኝ አድርጋችሁ ከሸኛችኋት በኋላ፤ ማንስ አየሁ ይለኛል ? የትስ አገኛታለሁ?"፡፡
ወደ ቤት ሲመጣ እመንገድ ላይ እህል አምጣ እያለ እንደ አዲስ መሬት ያስቸገረው ሆዱ እቤት ሲገባ እድላዊትን ባለማግኝቱ በንዴት እና በብስጭት የራበው ሁሉ ጠፋ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የልጃቸው ብሶትና ብስጭት ተሰማቸው፡፡ ሳይታወቃቸው በግራና በቀኝ ጉንጫቸው ላይ እንባቸው እንደ ሃምሌ ዝናብ መውረዱን ተያያዘው፡፡ ታዲያ እንባቸው ሲወርድ ላየው ሰው ወላድ መሆን አይደለም ሰው መሆንም ያስጠላ ነበር፡፡ ደግመው ለመናገር እንባ ተናነቃቸው፡፡ መናገር አልቻሉም፡፡ አንደበታቸው ተሳሰረ፡፡ ከተቀመጡበት ተነሱ፡፡ እንባቸውን በቀሚሳቸው እየጠራረጉ ወደ ጓዳ ሊገቡ ሲሉ ራሳቸውን አዞራቸው ፤ ከቤቱ ግድግዳ ጋር ተላተሙ፡፡
ተመስገን እናቱ በልጇ መጥፋት ሆድ እንደባሳቸውና በሃዘን እንደ ተጎዱ ታወቀው የእድላዊት መጥፋት ሳያንሰው የእናቱ እንደዚህ መሆን የባሰ ስቅስቅ አድርጎ አስለቀሰው፡፡
ከተላተሙበት የቤት ግድግዳ ተመለሱ፡፡ እንደገና አዙሯቸው የቤቱ ወለል ላይ ወደቁ፡፡ ከወደቁበት ሳይነሱ
ጆሮ ግንዳቸውን በቀኝ እጃቸው ደግፈው አቀረቀሩ፡፡ ምን ነክቷቸው ከግድግዳ እንደተላተሙ ለማስታወስ እየሞከሩ ፤ ካቀረቀሩበት ቀና ሲሉ ልጃቸው እያለቀሰ አዩት፡፡ ማፅናናታቸውን ትተው ያቋረጡት ለቅሶ ተያያዙት፡፡
ቄስ መልካሙ ከስራ ቆይተው ሲመለሱ ቤቱ በሃዘን እና በለቅሶ ተሞልቷል፡፡ "ምንድነው ለቅሶው ; ልጄ መሞቷ ተሰማ እንዴ ? ምን ተፈጥሮ ነው "አሉ፡፡ አይኖቻቸው ላይ የእንባ ብዥታ እየታየባቸው፡፡
"የልጄን መሞት እማ ብሰማ አንዴ አልቅሼ እና እርሜን አውጥቸ አርፍ ነበር"፡፡ የገባችበትን እና የበላትን ጅብ አለመጮሁ ነው እንጅ ፤ የሚያስለቅሰኝ" አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡
ተመስገን አባቱ ሲመጡ ማልቀሱን ባያቋርጥም እያለቀሰ በአባቱ ፊት መቆየት አልፈለገም፡፡ እረስቷት ወደ ሰነበተው የመኝታ ቤቱ ተነስቶ ሄደ፡፡
"ተመስገን ምን አለሽ ? እንዴው ወሬዋን እንኳን የሰማ ሰው አላገኘም ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ ለባለቤታቸው ፡፡
"ያየ አይደለም ሰማሁ የሚልም አላገኘም፡፡ እሱም እንዴው ሲንከራተት ከርሞ ይሔው ሰውነቱ አልቆ መጣ፡፡ እኔ ደግሞ ሲሰነብት ጊዜ በዛው ሔደ ብየ ፈርቼ ነበር፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ፊቱን ወደ ቤት መለሰልኝ" እንጅ ፡፡ቄስ መልካሙ ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረውን እንባ በጋቢያቸው ጠራርገው መለሱት፡፡
"ምን እናደርጋለን ታዲያ እንግዴህ አንዴ ሲፈጥረን ተሰቃዩ ብሎን የለ፡፡ የእኔ መሞቻ የቀረው እናት አባቴን ያጣሁ ዕለት ነበር"፡፡ ምነው ያኔ ከነሱ ጋር ሞቴን ብታደርግልኝ፡፡ ምን አለ ፈጣሪየ ፣ ምን በደልኩህ ; ምንስ አልኩህ ? የአንተ አገልጋይ እንኳን ነበርኩ፡፡ ስቃየን እነደዚህ ባታበዛብኝ ምን ? አለ"፡፡
መጀመሪያ ልውጣ ልውጣ እያለ ሲተናነቃቸው የነበረውን እንባ በጋቢያቸው ጠርገው ቢመልሱትም አሁን ግን ገፍቶ መጥቷል፡፡ ሊመልሱት አልቻሉም፡፡ የተናነቃቸውን እንባ ዘረገፉት፡፡
ቄስ መልካሙ በምንጃር አውራጃ ውስጥ ጉራንባ ማርያም በሚባል ጎጥ ተወልደው ባደጉበት አካባቢ የድቁና ትምህርታቸውን በጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን እየተከታተሉ ባሉበት ሰዓት ነበር፡፡ እናት አባታቸውን በመብረቅ አደጋ በሞት የተነጠቁት፡፡ ለእናት አባታቸው አንድ ልጅ ብቻ ነበሩ፡፡ እናት አባታቸው ከሞቱባቸው በኋላ ፤ ያላሳዳጊ ብቻቸውን በባዶ ቤት ሲሰቃዩ ቆይተው ከአራት አመት እንግልት በኋላ፤ ነበር፡፡ ወ/ሮ አሰገደችን አግብተው ተመስገንን እና እድላዊትን ማፍራት የቻሉት፡፡
ታዲያ ተመስገን የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን እድላዊት ሁለተኛ ልጃቸውም ነበረች፡፡
"በቃህ! አይበቃህም ወይ! ለቅሶ አልነው ፤ አልነው፡፡ እድላዊት በለቅሶ የምትመጣ ቢሆን እስካሁን ባልቆየች ነበር፡፡ የባሰ ስታለቅስ አይንህን እንዳታጣና በንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዳይሆን፡፡ እንግዴህ እግዚአብሔር ከፈቀደ ልቧን አራርቶት ተመልሳ ልትመጣ ትችላለች፡፡ አይታወቅም፡፡ ሰጭውም ነሽውም እሱ አንድ አምላክ እስከሆነ ድረስ አደራውን ለሱ መስጠት ነው አሉ ፤ ወ/ ሮ አሰገደች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍98❤3
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡
የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡
መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡
ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡
መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡
እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡
ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡
ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡
እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡
እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡
እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡
ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡
"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡
እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡
እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡
አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?
እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;
እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡
እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡
ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡
እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡
ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡
እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡
አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡
የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡
መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡
ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡
መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡
እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡
ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡
ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡
እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡
እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡
እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡
ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡
"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡
እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡
እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡
አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?
እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;
እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡
እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡
ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡
እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡
ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡
እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡
አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
👍86❤7🔥1👏1
እረኞቹ እድላዊትን ለቀው እግሬ አውጭኝ እያሉ ተበታተኑ፡፡ አቶ አርምዴ እረኞቹን ትቶ በደምና በአቧራ ተለውሳ ወደ ወደቀችው እድላዊት ተጠጋ፡፡ ጥልቅ ሃዘን ተሰማው፡፡ አይኖቹ እንባ ቋጠሩ፡፡
ከወደቀችበት አነሳት፡፡ አይዞሽ አይዞሽ አላት፡፡ ደፈሩሽ እንዴ ብሎ ጠየቃት፡፡ እድላዊት የዋለባት ውሃ ጥም ሳያንሳት ተጨማሪ በደረሰባት ጉዳት የድረሱልኝ ጩኸት ስትጮህበት የቆየችው ድምጿ ለመናገር ተሳነው፡፡ የሞት ሞቷን አልደፈሩኝም አለች፡፡
"ደብድበውሻል እንዴ" አላት፡፡ እድላዊት ግን መናገር አቃታት፡፡ መልስ አልሰጠችውም፡፡
እሱም ከእድላዊት መልስ አልጠበቀም፡፡ እረኞቹ ሲጎትቷት ደምቶ የነበረው ጉልበቷን የለበሰውን ሸሚዝ ቀዶ ደሟን ጠራርጎላት፡፡ በቀረው ጨርቅ ቁስሏን አሰረላት፡፡ እድላዊት እራሷን ችላ መሄድ አልቻለችም፡፡ የያዘውን መሳሪያ በፊት ደረቱ አንግቶ…..
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
ከወደቀችበት አነሳት፡፡ አይዞሽ አይዞሽ አላት፡፡ ደፈሩሽ እንዴ ብሎ ጠየቃት፡፡ እድላዊት የዋለባት ውሃ ጥም ሳያንሳት ተጨማሪ በደረሰባት ጉዳት የድረሱልኝ ጩኸት ስትጮህበት የቆየችው ድምጿ ለመናገር ተሳነው፡፡ የሞት ሞቷን አልደፈሩኝም አለች፡፡
"ደብድበውሻል እንዴ" አላት፡፡ እድላዊት ግን መናገር አቃታት፡፡ መልስ አልሰጠችውም፡፡
እሱም ከእድላዊት መልስ አልጠበቀም፡፡ እረኞቹ ሲጎትቷት ደምቶ የነበረው ጉልበቷን የለበሰውን ሸሚዝ ቀዶ ደሟን ጠራርጎላት፡፡ በቀረው ጨርቅ ቁስሏን አሰረላት፡፡ እድላዊት እራሷን ችላ መሄድ አልቻለችም፡፡ የያዘውን መሳሪያ በፊት ደረቱ አንግቶ…..
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...
ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍105❤13
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
👍88❤10🥰3👎1
አቶ አርምዴ እድላዊት ወደ ተኛችበት ፍራሽ ተጠጋ፡፡ ትንፏሿን ለማዳመጥ በርጩማ ላይ ተቀምጦ ከአንገቱ አቀረቀረ፡፡ በቤቱ ወለል ላይ አይኖቹን ተከላቸው፡፡ እድላዊት ከተኛችበት ፍራሽ ላይ ገልበጥ አለች፡፡
"እንዴት አደርሽ ? ተሻለሽ ? አለ፡፡ ጥድፍ ጥድፍ እያለ ስሟን እንኳን ሳይጠራ፡፡
እድላዊት ከተኛችበት እንደመባነን አለች፡፡ የሰማችውን ድምፅ እያስታወሰች፡፡ ትናንት ከአንበሳ ጉሮሮ ውስጥ ነጥቆ ያወጣት የእግዚአብሔር መላዕክተኛው አቶ አርምዴ መሆኑን በድምፁ
ለመለየት አልተቸገረችም፡፡
ተሽሎኛል የሚለውን ቃል ለመናገር ጉሮሮዋ በቶንሲሏ ምክንያትና የጮኸችበት በተራው ተዘግቶ የወንድ ድምፅ ይሁን የሴት ድምፅ በማይለይ ተክሎኛል አለች፡፡
አቶ አርምዴ በሚያደናግር እና በተኮላተፈ አማርኛ የተናገረችው ተሸሎኛል የሚል እንደሆነ ተረድቷል፡፡ በልቡ ላይ ያደረበት ስጋት እና ፍርሃት ለቀቅ አድርጎት በተራው የደስታና የፈገግታ ምንጭ አደረበት፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ "አናገረችህ? ተሽሎኛል አለችህ ? ልጄ አሉ፡፡ የደስታውን ምንጭ ለመስማት እየተጣደፉ፡፡
እናቱ መጣደፋቸው ለምን እንደሆነ ተረድቷቸዋል፡፡ "አዎ፤ በደንብ ባይሻላትም ከትላንቱ ትንሽ የተሻላት ይመስላል አለ፡፡
"እሰይ ደግ ትንሽ መናገር ከጀመረች ቶንሲሏ ተመልሶላታል ማለት ነው፡፡
፡"አሁን ከምንቀሰቅሳት ትንሽ ትተኛና ሞቅ ሲል ብትነሳ ይሻላል? ለቀቅ ያድርግ እኔም ለከብቶቹ የሚበላ ሰጥቼ ተመልሸ እመጣለሁ፡፡ አንችም የሚበላ ትናንት ካሰናዳሽላትም ቢሆን አዘጋጅላት፡፡ እንዴው ሳትበላ ጦሟን አደረች፡፡ እኔም እነ ፈጠነ ጋር በዛው ሔጄ ላሟ አላስጣለች እንደሆን ወተት ይዠላት እመጣለሁ፡፡ በባለፈው አጨዳ ለምኖኝ የሄድኩ ቀን ሲያልቡ አይቸ ነበር፡፡ ብሎ ተመልሶ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ ቤታቸውን ቀጥፈው ባመጡት ቅጠል ጠራርገው ማገዶ የሚያመጣላቸው ስለሌለ አብዛኛውን ጊዜ የሚጠቀሙት በደከመ አቅማቸው ከዶሮ ተሻምተው በሚጠፈጥፉት የማገዶ ኩበት ነው፡፡
ኩበታቸውን ከተከመረበት መዘው እሳት አቀጣጠሉ፡፡ ውሃ አሙቀው ለእድላዊት ትላንት ካስተረፉት የስንዴ ዱቄት ትንሽ እንኳን ብትቀምስ ብለው ገንፎውን አገነፉላት፡፡ ልጃቸው እስከሚመጣ ቡና እያፈሉ እና ለእድላዊት መታጠቢያ ውሃ አሙቀው እንዳይፈጃት በቀዝቃዛ ውሃ ትንሽ በረዝ አደረጉት፡፡
"ልጄ ደህና አደርሽ ? እንዴት ነሽ ? ቶንሲልሽን ተሻለሽ ? አሉ፡፡ ወደ ተኛችበት እየተጠጉ፡፡
እድላዊት አቶ አርምዴን ካነጋገረችበት ሰዓት አንስቶ እመኝታ ላይ ትተኛ እንጅ እንቅልፍ አልወሰዳትም፡፡ የደረሰባትን ስቃይ እና መከራ በሃሳቧ እያወጣችና እያወረደች ለዚህ ሁሉ ስቃይና መከራ የዳረጓትን ቤተሰቦቿን እየረገመች በአንድ ፊት ደግሞ አቶ አርምዴን የእግዚአብሔር መላክተኛ ሆኖ እንዳዳናት እያመሰገነች ደህና አደርሽ ልጄ የሚል ድምፅ ሰማች፡፡
ከሄደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ "እግዚአብሔር ይመስገን ተሸሎኛል" አለች፡፡ አሁንም የሴት ይሁን የወንድ በማይለየው ድምፃዋ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ እስኪ ትንሽ ቀና በይ ሰውነትሽን ለቀቅ እንዲያደርግሽ፡፡ ፊትሽንና እጅሽን ታጠቢ ፤ እህልም አፍሽ አድርጊ፡፡ እዴው ምንም ሳትቀምሽ ጦምሽን አደርሽ፡፡ ብለው ስለደረሰባት ስቃይና መከራ ሲያስቡ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
እምባቸው በአይኗቻቸው ሞላ፡፡ እድላዊት እንባቸውን እንዳታይባቸው ፊታቸውን ዞር አደረጉ፡፡ በውስጥ ቀሚሳቸው ጠራርገው ፊታቸውን መለስ አድርገው "ተነሽ ልጄ" አሉ፡፡
እድላዊት እረኞቹ መሬት ለመሬት የጎተቷት ሰውነቷ ቆስሏል፡፡ ወገቧ ቀና ለማለት አልቻለም፡፡ እንደምንም ብላ ቀና አለች፡፡ ግን ወደ ውጭ መውጣት አልቻለችም፡፡ በተኛችበት መኝታ ላይ ቁጭ ለማለት ሞከረች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ እጇን አስታጠቧት፡፡ "ፊትሽን ቢያምሽም እንደምንም ብለሽ ታጠቢው ያበጠው እንዲለቅሽ ፤ አይዞሽ አሁን ይሻልሻል አሏት፡፡
እድላዊት ያሏትን እያመማት እጇ አልታጠፍ ቢላትም እንደምን ብላ ፊቷን ታጠበች፡፡
በደካማ አቅማቸው የሰሩላትን ገንፎ ብይ እስቲ ፣ አፍሽ አድርጊ ፣ አትፍሪ ሲሏት ሆድ ባሳት፡፡ የቀረበላትን ገንፎ ገና ሳትቀምሰው ሳይታወቃት አይኖቿ የእንባ ዘለላዎችን መፈንጠቅ ጀመሩ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ ለማፅናናት አልቻሉም፡፡ ከእድላዊት ብሰው እራሳቸው የእንባ ጎርፍ አዘነቡት፡፡ አሁንም በውስጥ ቀሚሳቸው እየጠራረጉ "አንችን አይዞሽ ማለቱን ትቼ እኔው አባባስኩሽ? እባክሽ እባክሽ ልጄ አፈር ስሆንልሽ አታልቅሽ እያሉ እድላዊትን ተማፀኗት፡፡
እድላዊት የወ/ሮ በሰልፏ ልመናና መንሰፍሰፍ ማልቀሷን አባባሰው፡፡ እንደምንም ለመቋቋም ሞከረች፡፡ እናንተንም አስቸገርኳችሁ ብላ ሌላም ሳትናገር አሁንም እንባዋ በአይኖቿ ግጥም አሉ፡፡
"እባክሽ ስለ ፈጠረሽ አምላክ ፤ በፈጠረሽ አታልቅሽ፡፡ ምንም አላስቸገርሽንም፡፡ ስለኛ ምንም አታስቢ፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ነብስሽን አተረፈሽ፡፡ ብለው እድላዊትን ትንሽ ለማረጋጋት ሞክረው "እንዴው ከየት ነው አመጣጥሽ" ? አሉ፡፡
እድላዊት የመጣችበትን ለመናገር አልፈለገችም፡፡ ምን ማለት እንዳለባት አሰበች፡፡ ከሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ወደ ቤቴ ስመለስ ነው አለች፡፡
"እንዴው አብሮሽ የሚሔድ ሰው አልነበረም ? ቤተሰቦችሽስ ወዴት ናቸው ?
"ተሸሎኝ ስለነበር ሰው አያስፈልገኝም ብዬ ብቻዬን ነው የተነሳሁት፡፡ ቤተሰቦቼ ጉራንባ ውስጥ ናቸው" አለች፡፡
እድላዊት ትንሽ ተሸሏት ስታነጋግራቸው ከየት እንደመጣችና ወዴት እንደምትሄድ ጠይቀው ለማወቅ ቻሉ፡፡
"ገንፎውም ቀዘቀዘ እስኪ ትንሽ እንኳን ቅመሽ እባክሽ፡፡ እኔም እንዴው በወሬ ያዝኩሽ አይ! የኔ ነገር ብለው የጣዱትን ቡና ለማፍላት ሲመለሱ ልጃቸው ከቤቱ ተመልሶ የውጭውን በር ከፍቶ ገባ፡፡
"መጣህ ልጄ ቡናው ሲፈላ ደረስክ፡፡
አቶ አርምዴ እቤት እንደ ገባ እድላዊትን ከመኝታዋ ባትነሳም በመኝታዋ ላይ ተቀምጣ አያት፡፡ ደስ አለው፡፡
እንዴት ነሽ ? ተሻለሽ ? አላት፡፡ በጥዋት መጥቶ እንደጠየቃት ታስታውሳለች፡፡ "ከጥዋቱ አሁን ተሸሎኛል ደህናነኝ" አለችው፡፡
አቶ አርምዴ ለእድላዊት ብዙ ጥያቄ ሳያበዛባት ለእናቱ እንዴው ትንሽ ተሸሏት አነጋገረችሽ ? ከየት እንደመጣችስ ነገረችሽ ? አለ፡፡
"አዎ ፤ ትንሽ አነጋግራኛለች፡፡ ከሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል እንደምትመጣና ወደ ቤተሰቦቿ እንደምትሔድ፡፡ ቤተሰቦቿም ጉራንባ ውስጥ እንደሚኖሩ ነጋራኛለች" አሉ፡፡ የቡና ቁርሱን እየሰጡት፡፡
አርምዴ ለእድላዊ አይዞሽ ሲሻልሽ እሸኝሻለሁ፡፡ ምንም አታስቢ፡፡ ይችም እናቴ ናት፡፡ የሚያስፈልግሽን ጠይቂያት ትሰጥሻለች፡፡ ብሏት ስራ ለመሔድ ስለቸኮለ እድላዊትን ለእናቱ አደራ ብሎ ተነስቶ ሔደ፡፡
እድላዊት አርምዴ ሲጨነቅላትና ሲያስብላት ትህትናው ልክ እንደወንድሟ እንደተመስገን ሆነባት፡፡...
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...34 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
"እንዴት አደርሽ ? ተሻለሽ ? አለ፡፡ ጥድፍ ጥድፍ እያለ ስሟን እንኳን ሳይጠራ፡፡
እድላዊት ከተኛችበት እንደመባነን አለች፡፡ የሰማችውን ድምፅ እያስታወሰች፡፡ ትናንት ከአንበሳ ጉሮሮ ውስጥ ነጥቆ ያወጣት የእግዚአብሔር መላዕክተኛው አቶ አርምዴ መሆኑን በድምፁ
ለመለየት አልተቸገረችም፡፡
ተሽሎኛል የሚለውን ቃል ለመናገር ጉሮሮዋ በቶንሲሏ ምክንያትና የጮኸችበት በተራው ተዘግቶ የወንድ ድምፅ ይሁን የሴት ድምፅ በማይለይ ተክሎኛል አለች፡፡
አቶ አርምዴ በሚያደናግር እና በተኮላተፈ አማርኛ የተናገረችው ተሸሎኛል የሚል እንደሆነ ተረድቷል፡፡ በልቡ ላይ ያደረበት ስጋት እና ፍርሃት ለቀቅ አድርጎት በተራው የደስታና የፈገግታ ምንጭ አደረበት፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ "አናገረችህ? ተሽሎኛል አለችህ ? ልጄ አሉ፡፡ የደስታውን ምንጭ ለመስማት እየተጣደፉ፡፡
እናቱ መጣደፋቸው ለምን እንደሆነ ተረድቷቸዋል፡፡ "አዎ፤ በደንብ ባይሻላትም ከትላንቱ ትንሽ የተሻላት ይመስላል አለ፡፡
"እሰይ ደግ ትንሽ መናገር ከጀመረች ቶንሲሏ ተመልሶላታል ማለት ነው፡፡
፡"አሁን ከምንቀሰቅሳት ትንሽ ትተኛና ሞቅ ሲል ብትነሳ ይሻላል? ለቀቅ ያድርግ እኔም ለከብቶቹ የሚበላ ሰጥቼ ተመልሸ እመጣለሁ፡፡ አንችም የሚበላ ትናንት ካሰናዳሽላትም ቢሆን አዘጋጅላት፡፡ እንዴው ሳትበላ ጦሟን አደረች፡፡ እኔም እነ ፈጠነ ጋር በዛው ሔጄ ላሟ አላስጣለች እንደሆን ወተት ይዠላት እመጣለሁ፡፡ በባለፈው አጨዳ ለምኖኝ የሄድኩ ቀን ሲያልቡ አይቸ ነበር፡፡ ብሎ ተመልሶ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ ቤታቸውን ቀጥፈው ባመጡት ቅጠል ጠራርገው ማገዶ የሚያመጣላቸው ስለሌለ አብዛኛውን ጊዜ የሚጠቀሙት በደከመ አቅማቸው ከዶሮ ተሻምተው በሚጠፈጥፉት የማገዶ ኩበት ነው፡፡
ኩበታቸውን ከተከመረበት መዘው እሳት አቀጣጠሉ፡፡ ውሃ አሙቀው ለእድላዊት ትላንት ካስተረፉት የስንዴ ዱቄት ትንሽ እንኳን ብትቀምስ ብለው ገንፎውን አገነፉላት፡፡ ልጃቸው እስከሚመጣ ቡና እያፈሉ እና ለእድላዊት መታጠቢያ ውሃ አሙቀው እንዳይፈጃት በቀዝቃዛ ውሃ ትንሽ በረዝ አደረጉት፡፡
"ልጄ ደህና አደርሽ ? እንዴት ነሽ ? ቶንሲልሽን ተሻለሽ ? አሉ፡፡ ወደ ተኛችበት እየተጠጉ፡፡
እድላዊት አቶ አርምዴን ካነጋገረችበት ሰዓት አንስቶ እመኝታ ላይ ትተኛ እንጅ እንቅልፍ አልወሰዳትም፡፡ የደረሰባትን ስቃይ እና መከራ በሃሳቧ እያወጣችና እያወረደች ለዚህ ሁሉ ስቃይና መከራ የዳረጓትን ቤተሰቦቿን እየረገመች በአንድ ፊት ደግሞ አቶ አርምዴን የእግዚአብሔር መላክተኛ ሆኖ እንዳዳናት እያመሰገነች ደህና አደርሽ ልጄ የሚል ድምፅ ሰማች፡፡
ከሄደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ "እግዚአብሔር ይመስገን ተሸሎኛል" አለች፡፡ አሁንም የሴት ይሁን የወንድ በማይለየው ድምፃዋ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ እስኪ ትንሽ ቀና በይ ሰውነትሽን ለቀቅ እንዲያደርግሽ፡፡ ፊትሽንና እጅሽን ታጠቢ ፤ እህልም አፍሽ አድርጊ፡፡ እዴው ምንም ሳትቀምሽ ጦምሽን አደርሽ፡፡ ብለው ስለደረሰባት ስቃይና መከራ ሲያስቡ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
እምባቸው በአይኗቻቸው ሞላ፡፡ እድላዊት እንባቸውን እንዳታይባቸው ፊታቸውን ዞር አደረጉ፡፡ በውስጥ ቀሚሳቸው ጠራርገው ፊታቸውን መለስ አድርገው "ተነሽ ልጄ" አሉ፡፡
እድላዊት እረኞቹ መሬት ለመሬት የጎተቷት ሰውነቷ ቆስሏል፡፡ ወገቧ ቀና ለማለት አልቻለም፡፡ እንደምንም ብላ ቀና አለች፡፡ ግን ወደ ውጭ መውጣት አልቻለችም፡፡ በተኛችበት መኝታ ላይ ቁጭ ለማለት ሞከረች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ እጇን አስታጠቧት፡፡ "ፊትሽን ቢያምሽም እንደምንም ብለሽ ታጠቢው ያበጠው እንዲለቅሽ ፤ አይዞሽ አሁን ይሻልሻል አሏት፡፡
እድላዊት ያሏትን እያመማት እጇ አልታጠፍ ቢላትም እንደምን ብላ ፊቷን ታጠበች፡፡
በደካማ አቅማቸው የሰሩላትን ገንፎ ብይ እስቲ ፣ አፍሽ አድርጊ ፣ አትፍሪ ሲሏት ሆድ ባሳት፡፡ የቀረበላትን ገንፎ ገና ሳትቀምሰው ሳይታወቃት አይኖቿ የእንባ ዘለላዎችን መፈንጠቅ ጀመሩ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ ለማፅናናት አልቻሉም፡፡ ከእድላዊት ብሰው እራሳቸው የእንባ ጎርፍ አዘነቡት፡፡ አሁንም በውስጥ ቀሚሳቸው እየጠራረጉ "አንችን አይዞሽ ማለቱን ትቼ እኔው አባባስኩሽ? እባክሽ እባክሽ ልጄ አፈር ስሆንልሽ አታልቅሽ እያሉ እድላዊትን ተማፀኗት፡፡
እድላዊት የወ/ሮ በሰልፏ ልመናና መንሰፍሰፍ ማልቀሷን አባባሰው፡፡ እንደምንም ለመቋቋም ሞከረች፡፡ እናንተንም አስቸገርኳችሁ ብላ ሌላም ሳትናገር አሁንም እንባዋ በአይኖቿ ግጥም አሉ፡፡
"እባክሽ ስለ ፈጠረሽ አምላክ ፤ በፈጠረሽ አታልቅሽ፡፡ ምንም አላስቸገርሽንም፡፡ ስለኛ ምንም አታስቢ፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ነብስሽን አተረፈሽ፡፡ ብለው እድላዊትን ትንሽ ለማረጋጋት ሞክረው "እንዴው ከየት ነው አመጣጥሽ" ? አሉ፡፡
እድላዊት የመጣችበትን ለመናገር አልፈለገችም፡፡ ምን ማለት እንዳለባት አሰበች፡፡ ከሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ወደ ቤቴ ስመለስ ነው አለች፡፡
"እንዴው አብሮሽ የሚሔድ ሰው አልነበረም ? ቤተሰቦችሽስ ወዴት ናቸው ?
"ተሸሎኝ ስለነበር ሰው አያስፈልገኝም ብዬ ብቻዬን ነው የተነሳሁት፡፡ ቤተሰቦቼ ጉራንባ ውስጥ ናቸው" አለች፡፡
እድላዊት ትንሽ ተሸሏት ስታነጋግራቸው ከየት እንደመጣችና ወዴት እንደምትሄድ ጠይቀው ለማወቅ ቻሉ፡፡
"ገንፎውም ቀዘቀዘ እስኪ ትንሽ እንኳን ቅመሽ እባክሽ፡፡ እኔም እንዴው በወሬ ያዝኩሽ አይ! የኔ ነገር ብለው የጣዱትን ቡና ለማፍላት ሲመለሱ ልጃቸው ከቤቱ ተመልሶ የውጭውን በር ከፍቶ ገባ፡፡
"መጣህ ልጄ ቡናው ሲፈላ ደረስክ፡፡
አቶ አርምዴ እቤት እንደ ገባ እድላዊትን ከመኝታዋ ባትነሳም በመኝታዋ ላይ ተቀምጣ አያት፡፡ ደስ አለው፡፡
እንዴት ነሽ ? ተሻለሽ ? አላት፡፡ በጥዋት መጥቶ እንደጠየቃት ታስታውሳለች፡፡ "ከጥዋቱ አሁን ተሸሎኛል ደህናነኝ" አለችው፡፡
አቶ አርምዴ ለእድላዊት ብዙ ጥያቄ ሳያበዛባት ለእናቱ እንዴው ትንሽ ተሸሏት አነጋገረችሽ ? ከየት እንደመጣችስ ነገረችሽ ? አለ፡፡
"አዎ ፤ ትንሽ አነጋግራኛለች፡፡ ከሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል እንደምትመጣና ወደ ቤተሰቦቿ እንደምትሔድ፡፡ ቤተሰቦቿም ጉራንባ ውስጥ እንደሚኖሩ ነጋራኛለች" አሉ፡፡ የቡና ቁርሱን እየሰጡት፡፡
አርምዴ ለእድላዊ አይዞሽ ሲሻልሽ እሸኝሻለሁ፡፡ ምንም አታስቢ፡፡ ይችም እናቴ ናት፡፡ የሚያስፈልግሽን ጠይቂያት ትሰጥሻለች፡፡ ብሏት ስራ ለመሔድ ስለቸኮለ እድላዊትን ለእናቱ አደራ ብሎ ተነስቶ ሔደ፡፡
እድላዊት አርምዴ ሲጨነቅላትና ሲያስብላት ትህትናው ልክ እንደወንድሟ እንደተመስገን ሆነባት፡፡...
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...34 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍67❤13
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
👍74❤6😁2🔥1
በደከመ አቅማቸው ምነው? ይበቃ ነበር፡፡ የኔ መሰቃየት ልጄን ከምታሰቃይብኝ ምነው ፈጣሪዬ የእለት ሞቴን ብሰጠኝ ? እባክህን ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን ስታለቅስ
ከምታሳየኝ ውሰደኝ፡፡ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ልማደኛውና ማለቂያ የሌለው እስኪመስል ድረስ ድምፁን ሳያሰማ ስቃይና በሽታ ያስታግስ ይመስል የአይናቸው እንባ ግራና ቀኝ በጉንጫቸው ላይ ኮለል እያለ ፤ የለበሱትን ሸማ እስከሚያርስ ድረስ መውረዱን ይያያዘዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿና ከተወለደችበት ቀዬ ተለይታ ፤ በሸንኮራ ጅማ አካባቢ ከወ/ሮ በሰልፏ ቤት በደስታና በምቾት ሳይሆን ፤ በመከራና በስቃይ ፤ ማይክሮ ሰከንድ ወደ ሰከንዶች ፣ ሰከንዶች ወደ ደቂቃ ፣ ደቂቃዎች ወደ ሰዓታትት ፣ ሰዓታቶች ወደ ቀናት ፣ ቀናቶች ወደ ሳምንታት ፣ ሳምንታቶች ወደ ወራት ፣ ወራቶች ወደ ዓመትት ተቆጥረው ለስምንት ዓመታት አሳለፈች፡፡
ታዲያ ወ/ሮ በሰልፏን በአልጋ ላይ ተኝተው ከቤት ውስጥ ያለውን የቤት ስራ እየሰራች ከውጭም ውሃ እየቀዳች ፤ ወፍጮም እየሄደች ፤ በማገልገል ለስምንት ዓመት አስታመመቻቸው፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ እየተሸላቸው መጣ፡፡ እድላዊትም ከዛሬ ስምንት ዓመት በፊት ያሰበችውን ሐሳብ ሳትቀይር ወደ ሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ለመሄድ ተነሳች፡፡
"እኔም ወደ ፀበል ልሂድ፡፡ ይሔኔ ቤተሰቦቸም ፀበል ቦታ መተው ፈልገው ሲያጡኝ ሞታለች ብለው እርማቸውን አውተው ይሆናል፡፡ አሁን ሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ትንሽ ተቀምጨ ወደ ቤተሰቦቼ እመለሳለሁ አለች፡፡
እድላዊት ውሸት ቀላቅላ በመናገሯ ተፀፀተች፡፡ አንገቷን ወደ መሬት አስደፋት፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ ከበፊቱ ትንሽ ተሸሏቸዋል፡፡ አልጋ ላይ ቁጭ ብለው ማነጋገርና ትንሽ እህል መቅመስ ከጀመሩ አንድ ወር አድርገዋል፡፡ ልጃቸው እድላዊት ለመሔድ በመነሳሳቷ ውስጣቸው ተረበሸ፡፡ ሰውነታቸው እንደእስስት ተለዋወጠ፡፡
"ልጄ እስካሁን አስታምመሽኝ አፈር ሳታለብሽኝ ጥለሽኝ ልትሔጅ ነው? አሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ የእድላዊትን ሃሳብ ቢረዱ ኖሮ እንዲህ ባልተናገሯት ነበር፡፡
እድላዊት መለየትን ወዳ ሳይሆን የሰው ቤት ተቀምጣና የመጨረሻ መውደቂያዋን ባለማወቋ እንጅ እያስታመመች ከስራቸው ብትሆን በተደሰተች ነበር፡፡
የወ/ሮ በሰልፏ መረበሽ ለእሷም የባሰ ጨለማ ሆነባት፡፡ ያልጠበቀችውን ነገር በመስማቷ ሆዷ እንዲረበሽ እና እንድትጨነቅ አደረጋት፡፡
"ምነው ፈጣሪዬ? አይበቃኝም መከራና ስቃይ? አንተን ለሚያምኑ ሁሉ ታማኝ ነህ፡፡ በችግር ጊዜ ለሚጠሩህ ሁሉ ደራሽ ነህ፡፡ ለሚለምኑህ ሁሉ ሰሚነህ፡፡ ምነው ታዲያ በእኔ ጨከንህ ?፡፡ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ለመነችው፡፡
በዛው መኝታዋ ላይ ጋደም አለች፡፡ እንቅልፍ ግን ሊወስዳት አልቻለም፡፡ በአይኗ ሳያልፍ ለሊቱ ተገባደደ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ በልጃቸው ለመሔድ መነሳሳት በሽታቸው እንደገና አገርሽቶባቸዋል፡፡ ትንፋሻቸው ቁርጥ ፣ ቁርጥ ፤ ሰውነታቸው ድካም ድካም ተሰማቸው፡፡ እኩለ ሌሊት ሆኗል፡፡ እድላዊትን ውሃ ስጭኝ አሉ፡፡እድላዊት በድንጋጤ ተነሳች፡፡ ውሃ ቀድታ ሰጠቻቸው፡፡ ትንሽ ከአንገቴ ቀና አድርጊኝ፡፡ በእጅሽም ደግፊኝ ልጄ ፤ አቃተኝ ምነው?፡፡ አንችንም አስቸገርኩሽ እስካሁን አስታመምሽኝ እግዚአብሔር ይስጥሽ፡፡ ውለታሽን እሱ ይክፈልሽ ፡፡ በሄድሽበት ቦታ ሁሉ ክፉ አይንካሽ፡፡ እያሉ በእድላዊትን ክንድ ላይ እንቅልፍ ሸለብ አድርጓቸው፡፡
ታዲያ ከእንቅልፋቸው ሳይነቁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይችን አለም ተሰናበቷት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...34 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
ከምታሳየኝ ውሰደኝ፡፡ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ልማደኛውና ማለቂያ የሌለው እስኪመስል ድረስ ድምፁን ሳያሰማ ስቃይና በሽታ ያስታግስ ይመስል የአይናቸው እንባ ግራና ቀኝ በጉንጫቸው ላይ ኮለል እያለ ፤ የለበሱትን ሸማ እስከሚያርስ ድረስ መውረዱን ይያያዘዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿና ከተወለደችበት ቀዬ ተለይታ ፤ በሸንኮራ ጅማ አካባቢ ከወ/ሮ በሰልፏ ቤት በደስታና በምቾት ሳይሆን ፤ በመከራና በስቃይ ፤ ማይክሮ ሰከንድ ወደ ሰከንዶች ፣ ሰከንዶች ወደ ደቂቃ ፣ ደቂቃዎች ወደ ሰዓታትት ፣ ሰዓታቶች ወደ ቀናት ፣ ቀናቶች ወደ ሳምንታት ፣ ሳምንታቶች ወደ ወራት ፣ ወራቶች ወደ ዓመትት ተቆጥረው ለስምንት ዓመታት አሳለፈች፡፡
ታዲያ ወ/ሮ በሰልፏን በአልጋ ላይ ተኝተው ከቤት ውስጥ ያለውን የቤት ስራ እየሰራች ከውጭም ውሃ እየቀዳች ፤ ወፍጮም እየሄደች ፤ በማገልገል ለስምንት ዓመት አስታመመቻቸው፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ እየተሸላቸው መጣ፡፡ እድላዊትም ከዛሬ ስምንት ዓመት በፊት ያሰበችውን ሐሳብ ሳትቀይር ወደ ሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ለመሄድ ተነሳች፡፡
"እኔም ወደ ፀበል ልሂድ፡፡ ይሔኔ ቤተሰቦቸም ፀበል ቦታ መተው ፈልገው ሲያጡኝ ሞታለች ብለው እርማቸውን አውተው ይሆናል፡፡ አሁን ሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ትንሽ ተቀምጨ ወደ ቤተሰቦቼ እመለሳለሁ አለች፡፡
እድላዊት ውሸት ቀላቅላ በመናገሯ ተፀፀተች፡፡ አንገቷን ወደ መሬት አስደፋት፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ ከበፊቱ ትንሽ ተሸሏቸዋል፡፡ አልጋ ላይ ቁጭ ብለው ማነጋገርና ትንሽ እህል መቅመስ ከጀመሩ አንድ ወር አድርገዋል፡፡ ልጃቸው እድላዊት ለመሔድ በመነሳሳቷ ውስጣቸው ተረበሸ፡፡ ሰውነታቸው እንደእስስት ተለዋወጠ፡፡
"ልጄ እስካሁን አስታምመሽኝ አፈር ሳታለብሽኝ ጥለሽኝ ልትሔጅ ነው? አሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ የእድላዊትን ሃሳብ ቢረዱ ኖሮ እንዲህ ባልተናገሯት ነበር፡፡
እድላዊት መለየትን ወዳ ሳይሆን የሰው ቤት ተቀምጣና የመጨረሻ መውደቂያዋን ባለማወቋ እንጅ እያስታመመች ከስራቸው ብትሆን በተደሰተች ነበር፡፡
የወ/ሮ በሰልፏ መረበሽ ለእሷም የባሰ ጨለማ ሆነባት፡፡ ያልጠበቀችውን ነገር በመስማቷ ሆዷ እንዲረበሽ እና እንድትጨነቅ አደረጋት፡፡
"ምነው ፈጣሪዬ? አይበቃኝም መከራና ስቃይ? አንተን ለሚያምኑ ሁሉ ታማኝ ነህ፡፡ በችግር ጊዜ ለሚጠሩህ ሁሉ ደራሽ ነህ፡፡ ለሚለምኑህ ሁሉ ሰሚነህ፡፡ ምነው ታዲያ በእኔ ጨከንህ ?፡፡ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ለመነችው፡፡
በዛው መኝታዋ ላይ ጋደም አለች፡፡ እንቅልፍ ግን ሊወስዳት አልቻለም፡፡ በአይኗ ሳያልፍ ለሊቱ ተገባደደ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ በልጃቸው ለመሔድ መነሳሳት በሽታቸው እንደገና አገርሽቶባቸዋል፡፡ ትንፋሻቸው ቁርጥ ፣ ቁርጥ ፤ ሰውነታቸው ድካም ድካም ተሰማቸው፡፡ እኩለ ሌሊት ሆኗል፡፡ እድላዊትን ውሃ ስጭኝ አሉ፡፡እድላዊት በድንጋጤ ተነሳች፡፡ ውሃ ቀድታ ሰጠቻቸው፡፡ ትንሽ ከአንገቴ ቀና አድርጊኝ፡፡ በእጅሽም ደግፊኝ ልጄ ፤ አቃተኝ ምነው?፡፡ አንችንም አስቸገርኩሽ እስካሁን አስታመምሽኝ እግዚአብሔር ይስጥሽ፡፡ ውለታሽን እሱ ይክፈልሽ ፡፡ በሄድሽበት ቦታ ሁሉ ክፉ አይንካሽ፡፡ እያሉ በእድላዊትን ክንድ ላይ እንቅልፍ ሸለብ አድርጓቸው፡፡
ታዲያ ከእንቅልፋቸው ሳይነቁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይችን አለም ተሰናበቷት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...34 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍40😢14❤9😱2🥰1👏1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ደላላው
ያዋጣኝ ይሆን ? ወይስ ያከስረኝ ? ይሆን ? ተጠራጠረ ፤ የአልባሳት ንግዱ ግን ውጤታማ አድርጎታል፡፡ እየተመላለሰ መነገዱን ቀጥሏል፡፡
የባልጪ መኪና ቶሎ ያሬድ ወደ ድሬድዋ ሊሄድ ረፍዶበት ተቻኩሏል፡፡ መኪናው ግን ሳይሞላ መውጣት አልቻም፡፡ አዳማ አርፍዶ ደረሰ፡፡ ወደ ድሬደዋ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦታል፡፡
ተናደደ ፣ ተበሳጨ፡፡ ምነው ዛሬ ባልመጣሁ ኖሯል፡፡ እንደሚረፍድብኝ እያወቅሁ፡፡ ከባልጪ መመለስ ሲኖርብኝ፡፡ ወደ አዳማ መንከርፈፍ ምን ይሉታል? ራሱን እየወቀሰ ከአሰላ መውጫ መነሃሪያ ወጥቶ በስተቀኝ በኩል ወደ ምትገኝ አንድ ሻይ ቤት አመራ፡፡
አንድን ጠቆር ያለ ወጣት ነው፡፡ ቁመተ አጭር ዳክየ፡፡ የተከረከመ ጉቶ ይመስላል፡፡ ፀጉሩ በአቧራ የተለወሰ ፣ የተንጨበረረ ፣ ቁጥርጥር ፀጉራም፡፡
ከመነሃሪያ ውጭ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው የቀረው እያለ ይለፈልፋል፡፡
ቀኝ እግሩን አንስቶ ግራ እግሩን አልደገመም፡፡ ድሬ አንድ ሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ ወደ ፊት መራመዱን ትቶ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ብስጭትና ንዴቱ ለቀቀው፡፡ እየተጣደፈ ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው እያለ ወደ ሚለፈልፈው ደላላ ተጠጋ፡፡ እኔ አለሁ ድሬ አለ፡፡
"ኧረ! ድሬ ነህ ና ተከተለኝ፡፡ አሁን ልንወጣ ነው"፡፡ ብሎት ወደ መኪናው ወሰደው፡፡ ሂሳብ ክፈልና እዚህኛው መኪና ግባ አለው፡፡
ለመሳፈሪያ ብሎ ለይቶ ካስቀመጠው የሱሪ ኪሱ አውጥቶ ከፈለ፡፡ ደረሰኝ ግን አልተቀበለም፡፡ ደላላው ገንዘቡን ተቀብሎት ታጠፈ፡፡
ያሬድ ግባ ወደ ተባለበት አውቶቢስ ገባ፡፡ እውነትም አንድ ሰው ብቻ ነበር የቀረው፡፡ አንድ ተሳፋሪ ቀርቷት የነበረች ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡
እረዳቱ የአውቶቢሱን በር ዘጋ፡፡ ሹፌሩ መኪናውን አስነሳ፡፡ ጉዞው ከአዳማ ወደ ድሬደዋ ተጀመረ፡፡
"ምዕመናን ሂሳብ ወጣ! ወጣ! አድርጉ አለ እረዳቱ፡፡ እየተቀበለ ያሬድ ጋር ደረሰ፡፡
"ለእኔ ደረሰኝ ብቻ ስጠኝ ገንዘቡን ከፍያለሁ አለ ያሬድ፡፡
"ለማነው የከፈልከው አለ እረዳቱ?፡፡
"ሊያሳፍረኝ ይዞኝ ለመጣው ሰውየ ፡፡
"አባት የከፈሉት ሂሳብ ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ አሁን ለእኔ ይክፈሉኝ አለ፡፡ ትህትና በተሞላበት ንግግር፡፡
"አልከፍልም" አለ ያሬድ፡፡
"እባክዎት ይክፈሉኝ" አባት ቢልም ፤ ምንም ቢል ያሬድ ሊሰማ አልቻለም፡፡ ክፈል ፣ ጭቅጭቅና ንትርኩ ተባባሰ፡፡ ሹፌር መኪናውን መንዳቱን አቆመ፡፡ በረዳቱና በያሬድ መሃል ጣልቃ ገባ
"ለምንድ ነው የማከፍለው? በነፃ ተሳፍረህ የምትሄደው የአባትህ ፈረስ አደረግከው አለ ሹፌሩ፡፡ በፊቱ ላይ የደም ስሮቹ ተወጣጠሩ፡፡
"የአባቴ ፈረስ ባይሆንም ገንዘብ ከፍየ ነው የተሳፈርኩት፡፡ ያጭበረበራችሁኝ እናንተ ናችሁ፡፡ በማስፈራራት ደግማችሁ ልታስከፍሉኝ ነው? አልከፍልም፡፡ ወደ ህግ እንሄዳለን እንጅ አለ ያሬድ፡፡
ከመኪናው ውስጥ ጎትተው አወጡት፡፡ ሊደበድቡት ተጋበዙ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ገላገሏቸው፡፡ ክርክሩና ንትርኩ አላቋረጠም፡፡
አቶ ላንቻ ባልቻ የሚባሉ ከያሬድ ጋር አንድ ወንበር ላይ አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጭቅጭቁ አበሳጭቷቸዋል፡፡ ቶሎ ለመድረስ ያሰቡበት ቦታ እየረፈደባቸው ነው፡፡
"ለረዳቱ በቃ! ተወው እኔ እከፍለዋለሁ፡፡ ንትርኩን ተውና ቶሎ ቶሎ ንዳ፡፡ እውነት ይሄ ሰውዬ ሳይከፍልም የተከራከረ አይመስለኝም፡፡ የአዳማ ሞጭላፋ ጩልሌዎች ጨልፈውት ይሆናል፡፡ እንኳን የክፍለ ሃገር ሰው አግኝተው አይደለም ወፍ ከሰማይ ያወርዳሉ፡፡ ይዞት የመጣው ደላላ የሻይ ሲጠይቀው የመሳፈሪያውን ሂሳብ ተቀብሎት ላፍ ብሎ ይሆናል፡፡ ብለው የሚያጨቃጭቀውን የያሬድን ሂሳብ ከደረት ሸሚዝ ኪሳቸው አውጥተው ከፈሉለት፡፡
"አጭበርብረውኝ ነው፡፡ እንጅ እኔ እኮ ገንዘቡን ከፍያቸዋለሁ አባት አለ፡፡ እንደ መፀፀት ብሎ፡፡
"ያጭበረበሩህ ባለ መኪናዎቹ አይደሉም፡፡ ዱርዬዎች ናቸው፡፡ አንተም መኪና ውስጥ ሳትገባ መክፈል አልነበረብህም፡፡ ወይም ስትከፍል ደረሰኝ መቀበል ነበረብህ::
"እኔ መቼ አወኩ፡፡ እንደዚህ መሆኑን የት አውቄ፡፡ የእነሱ አጋዥ መስሎኝ ነው፡፡ የከፈልኩት፡፡ መቼ ሰባራ ሳንቲም አቀምሰው ነበር፡፡ ብሎ ስህተቱ የራሱ መሆኑን አውቆ የከፈሉለትን ገንዘብ ሊከፍል ከኪሱ አወጣ፡፡
አባት አመሰግናለሁ ገንዘቡን እንኩ አለ፡፡ በፊቱ ላይ የይቅርታ ምልክት እያሳየ፡፡
ገንዘቡን ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ ተወው ችግር የለውም፡፡ አንተም ተወስዶብህ ነው፡፡ እንጅ አውቀህ አይደለም፡፡ አሁን ያወጣኸውን ገንዘብ መልሰህ ወደ ኪስህ አስገባ እኔ አልቀበልም አሉ አቶ ላንቻ፡፡
አቶ ላንቻ ከድሬደዋ አዳማ እየተመላለሱ የሚነግዱ የታወቁ ቱጃር አልባሳ ነጋዴ ናቸው፡፡ ጨዋታቸው እየሞቀ ሄደ፡፡ አቶ ላንቻ ከተደገፉበት ወንበር ቀና አሉ፡፡
"ስምህን ማን አልከኝ"? አሉት፡፡ መጀመሪያ ነግሯቸው በጭዋታ የተነሳ ዘንግተውት ይሁን ተመስሎባቸው ደግመው መጠየቃቸው፡፡
"ያሬድ እባላለሁ አለ፡፡ ፊቱን ወደ አቶ ላንቻ መለስ አድርጎ፡፡
"አሁን ወዴት ነው የምትሄደው"? ፡፡
"ወደ ድሬ የምሄደው"፡፡
"እዛው ነዋሪ ነህ ወይስ ለስራ ነው የምትሄደው?፡፡
"አይ! ለስራ ነው፡፡ ነገ እመለሳለሁ፡፡ እቤት ከመቀመጥ ብዬ ትንሽ ሳልባጅ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡ ሞልቶ ለማይሞላ ነገር ስንት ገዛኸው ዘጠኝ ፤ ስንት ሸጥከው ዘጠኝ ፤ ትርፉስ ምንድነው? ዘጥ ዘጥ እንደሚባለው የበሰለውን ከማጥፋት ውጭ ድካም ነው፡፡ ውጤት የለውም አላቸው፡፡ ንግግሩ የሚያስቅ ስለነበር ፈገግ አደረጋቸው፡፡
አቶ ላንቻ አለመተዋወቅ እንጅ አልባሳት ከሆነ የምትነግደው እኔ አዳማ ድረስ አመጣልህ ነበር አሉ፡፡
"አልባሳት ይነግዳሉ እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"አዎ፤ ነጋዴ ነኝ፡፡ አሁንም አራግፌ እየተመለስኩ ነው፡፡
"ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ እንዴው የሰው መተዋወቂያው መንገዱ ብዙ ነው አለ ያሬድ፡፡ ያገናኛቸው አጋጣሚ እያስገረመው፡፡
"ድሬ ደንበኛ አለህ የምትረከብበት"? ፡፡
"ደንበኛ እንኳን የለኝም፡፡ የጀመርኩት ቅርብ ጊዜ ስለሆነ ደንበኛ አላበጀሁም፡፡ ከአሸዋ ሜዳ ነው የምገዛው ፡፡
የዛሬ መገናኘታችን ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ አሁን እየደረስን ስለሆነ መነሃርያ ሳንገባ ወርደን አረፍ ብለን እንነጋገራለን" አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
ከመኪና ወርደው ወደ አንድ ሪስቶራንት አመሩ፡፡ አረፍ ብለው የሚጠጣ ለስላሳ አዘዙ፡፡ በመኪና ላይ የጀመሩትን ጭውውታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
"አዳማ ውስጥ የራስዎ ቡቲክ አሎት እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"የራሴ እንኳን ቡቲክ የለኝም፡፡ አዳማ መነሃሪያ አካባቢ ቢያድግልኝ የሚባል የጅምላ አከፋፋይ ሱቅ አጠገብ የተከራየሁት ቡቲክ አለኝ፡፡ እዛ ነው የምሸጠው፡፡ ቦታውን ነገ አብረን ስንሄድ አሳይሃለሁ፡፡ አሁን እንሂድና እዚህ ድሬ ውስጥ ያለኝን ቡቲክ ላሳይህ፡፡ የሚያስፈልግህንም ገዝተህ እኔ በምጭንበት መኪና ጭነህ ነገ አብረን አንሄዳለን፡፡
ያሬድ ያገናኘውን አጋጣሚ እየመረቀ እንዴው ምን ዓይነት ደግ ሰው ነው፡፡ ያጋጠመኝ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ እያለ "አይደህና ነው፡፡ ለእኔም እዚህ ድረስ ከምለፋ ጥሩና መልካም ነው፡፡ እንዴው ውለታዎን ለመክፈል ያብቃኝ" አለ፡፡ ቀለስለስ እያለ፡፡
"አይ! ምንም ማለት አይደለም፡፡ የራሴም ስራ ነው፡፡ አሁን ከአንተ የምጠብቀው ታማኝ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው"፡፡ ብለውት ሊያሳድሩት ወደ ቤታቸው ወሰዱት፡፡
በነጋታው በጥዋት ተነሱ፡፡ በተነጋገሩት መሰረት የሚያስፈልገውን ልብሶች ገዝቶ አብረው ወደ አዳማ ተጓዙ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ደላላው
ያዋጣኝ ይሆን ? ወይስ ያከስረኝ ? ይሆን ? ተጠራጠረ ፤ የአልባሳት ንግዱ ግን ውጤታማ አድርጎታል፡፡ እየተመላለሰ መነገዱን ቀጥሏል፡፡
የባልጪ መኪና ቶሎ ያሬድ ወደ ድሬድዋ ሊሄድ ረፍዶበት ተቻኩሏል፡፡ መኪናው ግን ሳይሞላ መውጣት አልቻም፡፡ አዳማ አርፍዶ ደረሰ፡፡ ወደ ድሬደዋ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦታል፡፡
ተናደደ ፣ ተበሳጨ፡፡ ምነው ዛሬ ባልመጣሁ ኖሯል፡፡ እንደሚረፍድብኝ እያወቅሁ፡፡ ከባልጪ መመለስ ሲኖርብኝ፡፡ ወደ አዳማ መንከርፈፍ ምን ይሉታል? ራሱን እየወቀሰ ከአሰላ መውጫ መነሃሪያ ወጥቶ በስተቀኝ በኩል ወደ ምትገኝ አንድ ሻይ ቤት አመራ፡፡
አንድን ጠቆር ያለ ወጣት ነው፡፡ ቁመተ አጭር ዳክየ፡፡ የተከረከመ ጉቶ ይመስላል፡፡ ፀጉሩ በአቧራ የተለወሰ ፣ የተንጨበረረ ፣ ቁጥርጥር ፀጉራም፡፡
ከመነሃሪያ ውጭ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው የቀረው እያለ ይለፈልፋል፡፡
ቀኝ እግሩን አንስቶ ግራ እግሩን አልደገመም፡፡ ድሬ አንድ ሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ ወደ ፊት መራመዱን ትቶ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ብስጭትና ንዴቱ ለቀቀው፡፡ እየተጣደፈ ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው እያለ ወደ ሚለፈልፈው ደላላ ተጠጋ፡፡ እኔ አለሁ ድሬ አለ፡፡
"ኧረ! ድሬ ነህ ና ተከተለኝ፡፡ አሁን ልንወጣ ነው"፡፡ ብሎት ወደ መኪናው ወሰደው፡፡ ሂሳብ ክፈልና እዚህኛው መኪና ግባ አለው፡፡
ለመሳፈሪያ ብሎ ለይቶ ካስቀመጠው የሱሪ ኪሱ አውጥቶ ከፈለ፡፡ ደረሰኝ ግን አልተቀበለም፡፡ ደላላው ገንዘቡን ተቀብሎት ታጠፈ፡፡
ያሬድ ግባ ወደ ተባለበት አውቶቢስ ገባ፡፡ እውነትም አንድ ሰው ብቻ ነበር የቀረው፡፡ አንድ ተሳፋሪ ቀርቷት የነበረች ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡
እረዳቱ የአውቶቢሱን በር ዘጋ፡፡ ሹፌሩ መኪናውን አስነሳ፡፡ ጉዞው ከአዳማ ወደ ድሬደዋ ተጀመረ፡፡
"ምዕመናን ሂሳብ ወጣ! ወጣ! አድርጉ አለ እረዳቱ፡፡ እየተቀበለ ያሬድ ጋር ደረሰ፡፡
"ለእኔ ደረሰኝ ብቻ ስጠኝ ገንዘቡን ከፍያለሁ አለ ያሬድ፡፡
"ለማነው የከፈልከው አለ እረዳቱ?፡፡
"ሊያሳፍረኝ ይዞኝ ለመጣው ሰውየ ፡፡
"አባት የከፈሉት ሂሳብ ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ አሁን ለእኔ ይክፈሉኝ አለ፡፡ ትህትና በተሞላበት ንግግር፡፡
"አልከፍልም" አለ ያሬድ፡፡
"እባክዎት ይክፈሉኝ" አባት ቢልም ፤ ምንም ቢል ያሬድ ሊሰማ አልቻለም፡፡ ክፈል ፣ ጭቅጭቅና ንትርኩ ተባባሰ፡፡ ሹፌር መኪናውን መንዳቱን አቆመ፡፡ በረዳቱና በያሬድ መሃል ጣልቃ ገባ
"ለምንድ ነው የማከፍለው? በነፃ ተሳፍረህ የምትሄደው የአባትህ ፈረስ አደረግከው አለ ሹፌሩ፡፡ በፊቱ ላይ የደም ስሮቹ ተወጣጠሩ፡፡
"የአባቴ ፈረስ ባይሆንም ገንዘብ ከፍየ ነው የተሳፈርኩት፡፡ ያጭበረበራችሁኝ እናንተ ናችሁ፡፡ በማስፈራራት ደግማችሁ ልታስከፍሉኝ ነው? አልከፍልም፡፡ ወደ ህግ እንሄዳለን እንጅ አለ ያሬድ፡፡
ከመኪናው ውስጥ ጎትተው አወጡት፡፡ ሊደበድቡት ተጋበዙ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ገላገሏቸው፡፡ ክርክሩና ንትርኩ አላቋረጠም፡፡
አቶ ላንቻ ባልቻ የሚባሉ ከያሬድ ጋር አንድ ወንበር ላይ አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጭቅጭቁ አበሳጭቷቸዋል፡፡ ቶሎ ለመድረስ ያሰቡበት ቦታ እየረፈደባቸው ነው፡፡
"ለረዳቱ በቃ! ተወው እኔ እከፍለዋለሁ፡፡ ንትርኩን ተውና ቶሎ ቶሎ ንዳ፡፡ እውነት ይሄ ሰውዬ ሳይከፍልም የተከራከረ አይመስለኝም፡፡ የአዳማ ሞጭላፋ ጩልሌዎች ጨልፈውት ይሆናል፡፡ እንኳን የክፍለ ሃገር ሰው አግኝተው አይደለም ወፍ ከሰማይ ያወርዳሉ፡፡ ይዞት የመጣው ደላላ የሻይ ሲጠይቀው የመሳፈሪያውን ሂሳብ ተቀብሎት ላፍ ብሎ ይሆናል፡፡ ብለው የሚያጨቃጭቀውን የያሬድን ሂሳብ ከደረት ሸሚዝ ኪሳቸው አውጥተው ከፈሉለት፡፡
"አጭበርብረውኝ ነው፡፡ እንጅ እኔ እኮ ገንዘቡን ከፍያቸዋለሁ አባት አለ፡፡ እንደ መፀፀት ብሎ፡፡
"ያጭበረበሩህ ባለ መኪናዎቹ አይደሉም፡፡ ዱርዬዎች ናቸው፡፡ አንተም መኪና ውስጥ ሳትገባ መክፈል አልነበረብህም፡፡ ወይም ስትከፍል ደረሰኝ መቀበል ነበረብህ::
"እኔ መቼ አወኩ፡፡ እንደዚህ መሆኑን የት አውቄ፡፡ የእነሱ አጋዥ መስሎኝ ነው፡፡ የከፈልኩት፡፡ መቼ ሰባራ ሳንቲም አቀምሰው ነበር፡፡ ብሎ ስህተቱ የራሱ መሆኑን አውቆ የከፈሉለትን ገንዘብ ሊከፍል ከኪሱ አወጣ፡፡
አባት አመሰግናለሁ ገንዘቡን እንኩ አለ፡፡ በፊቱ ላይ የይቅርታ ምልክት እያሳየ፡፡
ገንዘቡን ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ ተወው ችግር የለውም፡፡ አንተም ተወስዶብህ ነው፡፡ እንጅ አውቀህ አይደለም፡፡ አሁን ያወጣኸውን ገንዘብ መልሰህ ወደ ኪስህ አስገባ እኔ አልቀበልም አሉ አቶ ላንቻ፡፡
አቶ ላንቻ ከድሬደዋ አዳማ እየተመላለሱ የሚነግዱ የታወቁ ቱጃር አልባሳ ነጋዴ ናቸው፡፡ ጨዋታቸው እየሞቀ ሄደ፡፡ አቶ ላንቻ ከተደገፉበት ወንበር ቀና አሉ፡፡
"ስምህን ማን አልከኝ"? አሉት፡፡ መጀመሪያ ነግሯቸው በጭዋታ የተነሳ ዘንግተውት ይሁን ተመስሎባቸው ደግመው መጠየቃቸው፡፡
"ያሬድ እባላለሁ አለ፡፡ ፊቱን ወደ አቶ ላንቻ መለስ አድርጎ፡፡
"አሁን ወዴት ነው የምትሄደው"? ፡፡
"ወደ ድሬ የምሄደው"፡፡
"እዛው ነዋሪ ነህ ወይስ ለስራ ነው የምትሄደው?፡፡
"አይ! ለስራ ነው፡፡ ነገ እመለሳለሁ፡፡ እቤት ከመቀመጥ ብዬ ትንሽ ሳልባጅ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡ ሞልቶ ለማይሞላ ነገር ስንት ገዛኸው ዘጠኝ ፤ ስንት ሸጥከው ዘጠኝ ፤ ትርፉስ ምንድነው? ዘጥ ዘጥ እንደሚባለው የበሰለውን ከማጥፋት ውጭ ድካም ነው፡፡ ውጤት የለውም አላቸው፡፡ ንግግሩ የሚያስቅ ስለነበር ፈገግ አደረጋቸው፡፡
አቶ ላንቻ አለመተዋወቅ እንጅ አልባሳት ከሆነ የምትነግደው እኔ አዳማ ድረስ አመጣልህ ነበር አሉ፡፡
"አልባሳት ይነግዳሉ እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"አዎ፤ ነጋዴ ነኝ፡፡ አሁንም አራግፌ እየተመለስኩ ነው፡፡
"ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ እንዴው የሰው መተዋወቂያው መንገዱ ብዙ ነው አለ ያሬድ፡፡ ያገናኛቸው አጋጣሚ እያስገረመው፡፡
"ድሬ ደንበኛ አለህ የምትረከብበት"? ፡፡
"ደንበኛ እንኳን የለኝም፡፡ የጀመርኩት ቅርብ ጊዜ ስለሆነ ደንበኛ አላበጀሁም፡፡ ከአሸዋ ሜዳ ነው የምገዛው ፡፡
የዛሬ መገናኘታችን ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ አሁን እየደረስን ስለሆነ መነሃርያ ሳንገባ ወርደን አረፍ ብለን እንነጋገራለን" አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
ከመኪና ወርደው ወደ አንድ ሪስቶራንት አመሩ፡፡ አረፍ ብለው የሚጠጣ ለስላሳ አዘዙ፡፡ በመኪና ላይ የጀመሩትን ጭውውታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
"አዳማ ውስጥ የራስዎ ቡቲክ አሎት እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"የራሴ እንኳን ቡቲክ የለኝም፡፡ አዳማ መነሃሪያ አካባቢ ቢያድግልኝ የሚባል የጅምላ አከፋፋይ ሱቅ አጠገብ የተከራየሁት ቡቲክ አለኝ፡፡ እዛ ነው የምሸጠው፡፡ ቦታውን ነገ አብረን ስንሄድ አሳይሃለሁ፡፡ አሁን እንሂድና እዚህ ድሬ ውስጥ ያለኝን ቡቲክ ላሳይህ፡፡ የሚያስፈልግህንም ገዝተህ እኔ በምጭንበት መኪና ጭነህ ነገ አብረን አንሄዳለን፡፡
ያሬድ ያገናኘውን አጋጣሚ እየመረቀ እንዴው ምን ዓይነት ደግ ሰው ነው፡፡ ያጋጠመኝ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ እያለ "አይደህና ነው፡፡ ለእኔም እዚህ ድረስ ከምለፋ ጥሩና መልካም ነው፡፡ እንዴው ውለታዎን ለመክፈል ያብቃኝ" አለ፡፡ ቀለስለስ እያለ፡፡
"አይ! ምንም ማለት አይደለም፡፡ የራሴም ስራ ነው፡፡ አሁን ከአንተ የምጠብቀው ታማኝ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው"፡፡ ብለውት ሊያሳድሩት ወደ ቤታቸው ወሰዱት፡፡
በነጋታው በጥዋት ተነሱ፡፡ በተነጋገሩት መሰረት የሚያስፈልገውን ልብሶች ገዝቶ አብረው ወደ አዳማ ተጓዙ፡፡
👍64❤10😁1
አቶ ላንቻ ቡቲካቸው ደረሱ፡፡ ከደንበኛቸው ከቢያድግልኝ ጋርም ያሬድን አስተዋወቁት፡፡ ለቀጣይ የሚያስፈልገውን አልባሳት እንደሚያመጡለት ተነጋግረው ያሬድ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ለአይን ያዝ ሲያደርግ እቤቱ ደረሰ፡፡ እግሩን ተጣጥቦ የበጉን ድብዳብ ነጠል አድርጎ ወገቡን በመደብ ላይ ደገፍ አደረገ፡፡
ባለቤቱ አበበች ወጥ እስከ ምትሰራ ድረስ ከስንዴና ከሽንብራ የተቀላቀለ ቆሎ አቀረበችለት፡፡ ከውሃ ሻል የሚል ሰንበትበት ያለም ቅራሬ ሰጠችው፡፡ ከጥሬው ቀጭ ፣ ቀጭ እያደረገ ከቅራሬውም ጎንጨት እያለ ፤ አዳማ ላይ የገጠመውን ሁሉ እያስታወሰ በውስጡ ይገረማል፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ የደከመህ ትመስላለህ ? የሄድክበት አልቀናህም እንዴ ? አለች አበበች፡፡ የወጥ መስሪያ ሽንኩርት እየላጠች፡፡
በውስጡ የሚያብሰለስለውን የገጠመኝ ሃሳብ ተወት አደረገ፡፡
ገበያውስ ቀንቶኛል፡፡ እንዴው የገጠመኝ ነገር እየገረመኝ ነው አላት፡፡
"ደግሞ ምን ገጠመህ"?፡፡
"ባልጪ መኪና ሳይሞላ ቀርቶ ፤ አዳማ ስደርስ ረፍዶ ወደ ድሬ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦኝ ተናድጄ ነበር፡፡ በኋላ፤ አርፍዶ መኪና ኖሯል እሱን አግኝቼ እየተጣደፍኩ ልሳፈር ስል ረዳቱ የመሳፈሪያ ገንዘብ አምጣ
ሲለኝ የመኪናው ባለቤት ነው ብየ ከፈልኩት፡፡ ለካስ ገንዘቡን የተቀበለኝ ዱርየ ኖሯል፡፡ ከዛ ባለመኪናዎቹ ክፈል ፣ አልከፍልም፡፡ ስከራከር አንድ ተሳፋሪ ያጭበረበረኝን አውቀውት ኖሯል፡፡ ተወው ብለው ከፈሉልኝ ፡፡
"አንተ አዲስ አይደለህ ፤ ብትቼኩልስ ለምትከፍለው ሰው አታውቅም እንዴ፡፡ ሆሆይ እግዚአብሔር ደግ ሰው ጥሎልሃል፡፡ እንዴው ሰውዬው ምን አይነት ሰው ናቸው? አለች፡፡
"ሰውዬውስ የተባረኩና ደግ ሰው ከመሆናቸውም የናጠጡ ቱጃር አልባሳት ነጋዴ ናቸው፡፡
"ባለ ሃብት ሆነው ነዋ የከፈሉልህ ፡፡ እኔ እኮ ምን አይነት ሰው ከፈለልህ እያልኩ ነበር፡፡ "
ባለ ሃብት የሆነ እንደሆነ ለማያውቀው ሰው ገንዘቡን ይከፍላል እንዴ"? እንዲያውም እሳቸው ደግና የእግዚአብሔር ሰው በመሆናቸው ነው እንጅ የከፈሉልኝ፡፡ ከአሁን በኋላ ደግሞ ድሬ ድረስ አልሄድም ፡፡
"የትድረስ ነው አምጥተው የሚሸጡት?"፡፡
"አዳማ ድረስ ነው"፡፡ ለእኔም እንደሚያመጡልኝ ተነጋግረን ነው የመጣሁት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...33 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
ለአይን ያዝ ሲያደርግ እቤቱ ደረሰ፡፡ እግሩን ተጣጥቦ የበጉን ድብዳብ ነጠል አድርጎ ወገቡን በመደብ ላይ ደገፍ አደረገ፡፡
ባለቤቱ አበበች ወጥ እስከ ምትሰራ ድረስ ከስንዴና ከሽንብራ የተቀላቀለ ቆሎ አቀረበችለት፡፡ ከውሃ ሻል የሚል ሰንበትበት ያለም ቅራሬ ሰጠችው፡፡ ከጥሬው ቀጭ ፣ ቀጭ እያደረገ ከቅራሬውም ጎንጨት እያለ ፤ አዳማ ላይ የገጠመውን ሁሉ እያስታወሰ በውስጡ ይገረማል፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ የደከመህ ትመስላለህ ? የሄድክበት አልቀናህም እንዴ ? አለች አበበች፡፡ የወጥ መስሪያ ሽንኩርት እየላጠች፡፡
በውስጡ የሚያብሰለስለውን የገጠመኝ ሃሳብ ተወት አደረገ፡፡
ገበያውስ ቀንቶኛል፡፡ እንዴው የገጠመኝ ነገር እየገረመኝ ነው አላት፡፡
"ደግሞ ምን ገጠመህ"?፡፡
"ባልጪ መኪና ሳይሞላ ቀርቶ ፤ አዳማ ስደርስ ረፍዶ ወደ ድሬ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦኝ ተናድጄ ነበር፡፡ በኋላ፤ አርፍዶ መኪና ኖሯል እሱን አግኝቼ እየተጣደፍኩ ልሳፈር ስል ረዳቱ የመሳፈሪያ ገንዘብ አምጣ
ሲለኝ የመኪናው ባለቤት ነው ብየ ከፈልኩት፡፡ ለካስ ገንዘቡን የተቀበለኝ ዱርየ ኖሯል፡፡ ከዛ ባለመኪናዎቹ ክፈል ፣ አልከፍልም፡፡ ስከራከር አንድ ተሳፋሪ ያጭበረበረኝን አውቀውት ኖሯል፡፡ ተወው ብለው ከፈሉልኝ ፡፡
"አንተ አዲስ አይደለህ ፤ ብትቼኩልስ ለምትከፍለው ሰው አታውቅም እንዴ፡፡ ሆሆይ እግዚአብሔር ደግ ሰው ጥሎልሃል፡፡ እንዴው ሰውዬው ምን አይነት ሰው ናቸው? አለች፡፡
"ሰውዬውስ የተባረኩና ደግ ሰው ከመሆናቸውም የናጠጡ ቱጃር አልባሳት ነጋዴ ናቸው፡፡
"ባለ ሃብት ሆነው ነዋ የከፈሉልህ ፡፡ እኔ እኮ ምን አይነት ሰው ከፈለልህ እያልኩ ነበር፡፡ "
ባለ ሃብት የሆነ እንደሆነ ለማያውቀው ሰው ገንዘቡን ይከፍላል እንዴ"? እንዲያውም እሳቸው ደግና የእግዚአብሔር ሰው በመሆናቸው ነው እንጅ የከፈሉልኝ፡፡ ከአሁን በኋላ ደግሞ ድሬ ድረስ አልሄድም ፡፡
"የትድረስ ነው አምጥተው የሚሸጡት?"፡፡
"አዳማ ድረስ ነው"፡፡ ለእኔም እንደሚያመጡልኝ ተነጋግረን ነው የመጣሁት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...33 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍43❤6🔥1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
👍56❤9
የትውልድ ቀየዋን የረሳች ይመስላል፡፡ ለስምንት ዓመት የቆየችበትን የነ አቶ አርምዴን አካባቢ መናገሯ፡፡
ታዲያ እድላዊት የተጠየቀችውንም ፣ ያልተጠየቀችውንም ተናግራ እናትና አባቷ ይሙቱ ይኑሩ ሳታውቅ በውሸት ገድላ ለወ/ሮ ዘነቡ ስትናገር ቅር እንኳን ያላት አትመስልም ነበር፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ በሰሙት ነገር በጣም አዘኑ፡፡ አይዞሽ አሉ፡፡ አቅፈዋት የአይኖቿን እንባ በእጃቸው መዳፍ ጠራረጉላት፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ በድሬደዋ ከተማ ተወልደው ያደጉ ናቸው፡፡ ኑሮአቸው በንግድ ስራ ላይ የተመሰረተ ሆኖ በድሬ ከተማ ውስጥ የናሆም ሆቴል ባለቤት ናቸው፡፡
ሰራተኛ እየፈለጉ ባሉበት ሰዓት በአጋጣሚ በተሳፈሩበት መኪና ላይ ማረፊያዋንና መድረሻዋን የማታውቅ የገጠር መልከ መልካም የጠይም ቆንጆ የሆነች ልጅ በማግኘታቸው ወደር የሌለው ደስታ ፈጥሮላቸዋል፡፡ እድላዊትን የሰጣቸውን አምላክ እያመሰገኑ ወደ ቤታቸው ይዘዋት ገቡ፡፡ የሆቴላቸው አልጋ ልብስ አጣቢ አድርገውም ቀጠሯት፡፡
እድላዊት ስራ በማግኘቷ ተደስታለች፡፡ መድረሻየንና መጠጊያዬን ፈልግልኝ ብላ እያለቀሰች እንደተማፀነችው ፈጣሪዋም ልመናዋን ሳያሳፍራት ሰቷታል፡፡
የተሰጣትን ስራ በትጋት እያከናወነች ሰነባበተች፡፡ በሳምንታት ውስጥ በእናት አባቷ ቤት እያለች የነበረው መልክና ወዘናዋ ተመለሰ፡፡ እያማረባት ከገጠር ልጅ ወደ ከተማ ልጅ ተቀየረች፡፡
ቤተሰቦቿን ሁሉ እረስታ የተደላደለ ሂወት መኖር ባትችልም ከነበራት የተጎሰቋቆለ ህይወት ተላቃ መኖር ጀምራለች፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ በእድላዊት እሩህሩህነት ፣ ታማኝነትና ታዛዥነት እንዲሁም ፤ በስራዋ ላይ ባላት ቅልጥፍና ኮሩባት፡፡ ከልጆቻቸው በላይ አስበልጠው ያምኗት ጀመር፡፡ ቤታቸውንም አደራ ሰተዋት ወደ ፈለጉበት ቦታ ደርሰው ይመለሳሉ፡፡
ታዲያ ሲያገኟት በመከራና በስቃይ ተጎሰቋቁላ የተማረች አይደለም ትምህርት ቤት ያየችም አልመሰለቻቸውም ነበር፡፡
አንድ ቀን በጨዋታ የተነሳ "ለምን ትምህርት አላስተምርሽም አሉዋት?፡፡
"አይ! እትዬ የትምህርት ጉዳይማ አልጨረስኩም እንጅ እስከ ሰባተኛ ተምሬ ነበር አለች፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ ተገርመው እና "እስካሁን ለምን ዝም አልሽኝ ? ካሻሪ አጥቼ የምከራተተው አንችን ከቤት አስቀምጨ ነው ?
በይ....
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...32 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
ታዲያ እድላዊት የተጠየቀችውንም ፣ ያልተጠየቀችውንም ተናግራ እናትና አባቷ ይሙቱ ይኑሩ ሳታውቅ በውሸት ገድላ ለወ/ሮ ዘነቡ ስትናገር ቅር እንኳን ያላት አትመስልም ነበር፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ በሰሙት ነገር በጣም አዘኑ፡፡ አይዞሽ አሉ፡፡ አቅፈዋት የአይኖቿን እንባ በእጃቸው መዳፍ ጠራረጉላት፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ በድሬደዋ ከተማ ተወልደው ያደጉ ናቸው፡፡ ኑሮአቸው በንግድ ስራ ላይ የተመሰረተ ሆኖ በድሬ ከተማ ውስጥ የናሆም ሆቴል ባለቤት ናቸው፡፡
ሰራተኛ እየፈለጉ ባሉበት ሰዓት በአጋጣሚ በተሳፈሩበት መኪና ላይ ማረፊያዋንና መድረሻዋን የማታውቅ የገጠር መልከ መልካም የጠይም ቆንጆ የሆነች ልጅ በማግኘታቸው ወደር የሌለው ደስታ ፈጥሮላቸዋል፡፡ እድላዊትን የሰጣቸውን አምላክ እያመሰገኑ ወደ ቤታቸው ይዘዋት ገቡ፡፡ የሆቴላቸው አልጋ ልብስ አጣቢ አድርገውም ቀጠሯት፡፡
እድላዊት ስራ በማግኘቷ ተደስታለች፡፡ መድረሻየንና መጠጊያዬን ፈልግልኝ ብላ እያለቀሰች እንደተማፀነችው ፈጣሪዋም ልመናዋን ሳያሳፍራት ሰቷታል፡፡
የተሰጣትን ስራ በትጋት እያከናወነች ሰነባበተች፡፡ በሳምንታት ውስጥ በእናት አባቷ ቤት እያለች የነበረው መልክና ወዘናዋ ተመለሰ፡፡ እያማረባት ከገጠር ልጅ ወደ ከተማ ልጅ ተቀየረች፡፡
ቤተሰቦቿን ሁሉ እረስታ የተደላደለ ሂወት መኖር ባትችልም ከነበራት የተጎሰቋቆለ ህይወት ተላቃ መኖር ጀምራለች፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ በእድላዊት እሩህሩህነት ፣ ታማኝነትና ታዛዥነት እንዲሁም ፤ በስራዋ ላይ ባላት ቅልጥፍና ኮሩባት፡፡ ከልጆቻቸው በላይ አስበልጠው ያምኗት ጀመር፡፡ ቤታቸውንም አደራ ሰተዋት ወደ ፈለጉበት ቦታ ደርሰው ይመለሳሉ፡፡
ታዲያ ሲያገኟት በመከራና በስቃይ ተጎሰቋቁላ የተማረች አይደለም ትምህርት ቤት ያየችም አልመሰለቻቸውም ነበር፡፡
አንድ ቀን በጨዋታ የተነሳ "ለምን ትምህርት አላስተምርሽም አሉዋት?፡፡
"አይ! እትዬ የትምህርት ጉዳይማ አልጨረስኩም እንጅ እስከ ሰባተኛ ተምሬ ነበር አለች፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ ተገርመው እና "እስካሁን ለምን ዝም አልሽኝ ? ካሻሪ አጥቼ የምከራተተው አንችን ከቤት አስቀምጨ ነው ?
በይ....
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ የX-Empire ፕሮጀክት...32 ቀን ብቻ ነው የቀረው አዋጭ ነው ጀምሩት
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
👍129❤8👎5🥰4😢2🤔1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እጅግ በጣም ይቅርታ ስልኬ ስለጠፋ እረጅም ጊዜ ታሪኩን ሳለቅ ቀረሁ ወደኋላ መለስ ብለቹ ታሪኩን በማስታወስ ቀጥሉ እንደእግዚአብሔር ፍቃድ ከነገ ጀምሮ ሁለት ክፍል እለቃለሁ እንዲሁም ነገ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ እንጀምራለን የተከፋችሁብኝ አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ🙏
ያሬድ
ከገበያ መጥቶ ደክሞታል፡፡ ገና ሳይመሽ ከመኝታው ላይ ጋደም እንደማለት ብሏል፡፡
"ተመስገንን አብረን እንሄዳለን ብለኸው ነበር እንዴ"? አለች ፤ ባለቤቱ አበበች፡፡
"አዎ ፤ ብዬው ነበር፡፡ ገንዘብ እንዳዘጋጀ ነገረሽ እንዴ"?
"ትላንት አንተን ፈልጎ መጥቶ ነበር፡፡ ሳያገኝህ ሲቀር ለእኔ አጫውቶኛል፡፡ እንሂድ እስከምትለው ነው የሚጠብቀው" ፡፡
"ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ የመነገድ ፍላጎት ካለው አሁን ደግሞ ውሎ ገባ ስለሆነ የምንመጣው ቀን እንኳን ቢመሽም ሁለት መሆኑ አይከፋም፡፡ ከነገ ወዲያ ይዠው እሄዳለሁ"፡፡
ገና በደንብ አልነጋም፡፡ ያሬድም ከመኝታው አልተነሳም፡፡ አበበች አለ ፡፡ ሳይደጋግም በአንዴ የሚሰማ መስሎት፡፡ ነገር ግን የሚሰማው አላገኘም፡፡ አቤት የሚለው አጣ፡፡ ደግሞ ተጣራ፡፡ ያሬድ…..ያሬድ አለ፡፡ አቤት አለች አበበች፡፡ ብቅበይ አለ፡፡ በጥዋት ወደ ያሬድ ጋር የመጣው ተመስገን፡፡
ማነው በጥዋት ብቅበይ የሚለው ብላ ብቅ አለች፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች ? አለ" ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ተመስገን፡፡ አትገባም እንዴ ከብርድ ላይ ፡፡
"ይሁን አልገባም፡፡ ያሬድ የለም እንዴ ? ፡፡
"አለ ፤ ከመኝታውም አልተነሳም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም እንዴ ?
"ኧረ ደህናነኝ፡፡ ለዛ ላጫወትኩሽ ጉዳይ ነበር የመጣሁት ፡፡
"አይ! እሱንማ ከሆነ እኔም ማታ አጫውቸዋለሁ፡፡ ለመነገድ ፍላጎት ካለው ይዠው እሄዳለሁ ብሏል፡፡ ለማንኛውም ግባና አነጋግረው ፡፡
ተመስገን የመጣበትን ጉዳይ እንደተሳካለት አሰበ፡፡ ያሬድን ለማነጋገር ወደ ቤት ገባ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ? ፣ ደሞ ዛሬ በጥዋት አልተነሳህም፡፡ እንቅልፍ ነው ወይስ ድካም ነው?፡፡ ያስተኛህ ፡፡
"ሰላም አደርህ ተመስገን፡፡ ምን የትናንት ገበያ ውልቅልቅ አድርጎኛል፡፡ አሁን በደንብ ነግቷል ማለት ነው እንዴ? አለ፡፡ ከተኛበት መኝታ ተነስቶ እየተንጠራራ፡፡
"ስድስት ሰዓት ሆኖ ነግቷል ትላለህ እንዴ ፤ ለነገሩ ከተማ ለከተማ ስትመላለስ የከተማ ሰው ሆነሃል፡፡ እነኝህ ከተመኞች ሰዓት አስረው ቢይዙም ፤ የሚቆጥሩ መሆናቸውን እንጃ ፤ በየሰዓቱ ነው የሚበሉ
አለ፡፡ ተመስገን እንደማሾፍ ብሎ፡፡
"አይ! ተመስገን እነሱማ በሰዓት የማይበሉበት ጊዜ ስለሌላቸው ነው፡፡ ያለመቁጠር አይደለም፡፡ እንዲያውም እኛ ነን አንዴ ቁርስሠ ፣ አንዴ ምሳ ሰዓት ፣ ደረሰ እያልን ሰዓት የሚቃወመን ይመስል በቀን ሶስቴ ሳይበቃን አራተኛ መክሰስ እያልን የምንመገበው፡
"አይ! መልካም ነው" ብሎ "ለባለፈው ጉዳይ ነበር የመጣሁት" አለ ተመስገን ፡፡
"አበበች ማታ በጨዋታ አንስተን ነግራኛለች፡፡ እና ለመነገድ ፈልገሃል ማለት ነው?፡፡
"የመነገድ ፍላጎት እንኳን ብዙም የለኝም፡፡ እንዴው የዛችን የእህቴ ነገር አንጄቴ አልቆርጥ ብሎኝ ነው፡፡ መቼም እቤት ከመቀመጥ አካባቢንና አገርን ማወቅ አይከፋም፡፡ የእግዚአብሔር ስራም አይታወቅም፡፡ በዛውም እናገኛት ይሆናል"፡፡
"ጥሩ ነው ለማንኛውም ሃሳብህ አይከፋም፡፡ ነገ አብረን ማለድ ብለህ በጥዋት ና፡፡ ውሎ ገባ ስለምንመለስ እንዳይረፍድብን"፡፡
"እሽ በጥዋት እመጣለሁ፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
"በነጋታው በጥዋት ቡና ፈልቶ ተመስገን እየተጠበቀ ነው፡፡ ግን ቶሎ ሊመጣ አልቻለም፡፡ በቃ ቀርቶ ነው ብላ አበበች ቁርስ ልታቀርብ ስትል ተመስገን መጣ፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠው ተቀመጠ፡፡
"ምነው አረፈድህ" አለው ያሬድ
"ምን ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወሰደኝ አድሮ ሊነጋጋ አካባቢ ሸለብ አላደረገኝ መሰለህ ፡፡
"አይ! አንተ ሌሊቱን ሙሉ በሃሳብ ስትሄድ አድረህ ነዋ፡፡ ጥዋት በመነሻህ ሰዓት እንቅልፍ የጣለህ፡፡ በል አሁን የቡና ቁርሱን ያዝና ቡናውን ጠጥተን ቶሎ እንውጣ፡፡ የባልጪ መኪና ሳያመልጠን እንድረስበት፡፡ አንዴ ካመለጠን መመለስ ካልሆነ ሌላ መኪና አናገኝም፡፡
ባለቤቱን በይ እንግዴህ ከብት ሳይበዛ ከብቶቹን ውሃ አጠጫቸው ብሏት ተነስተው ከተመስገን ጋር ጉዞዋቸውን ወደ አዳማ ቀጠሉ፡፡
መኪና እንዳያመልጣቸው እየተጣደፉ ነው፡፡ ከመንገድ ላይ አንድ ጥቁር ሰው ከፊት ለፊታቸው ገጠማቸው፡፡
"ዛሬ ላይቀናን ነው መሰለኝ አለ ተመስገን፡፡ ውስጡ እንደመረበሽ እያለበት፡፡
"ምነው ምን አየህ አለው? ያሬድ፡፡
"ተመስገን የፍጥነት እርምጃውን ገታ አድርጎ ፤ መንገድ ስትሄድ አንድ ሰው ከገጠመህ የምትሄድበት አይቀናህም፡፡ አባቴ ሲናገር ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም እኛ አንድ ሰው ሰለገጠመን ብዬ ነው፡፡
ባያምንበትም ግን ሆዱ እንደመፍራት ብሏል፡፡ "ተው! እባክ ይህ የአንዳንድ ሰው አባባል ነው፡፡ አንተ ደግሞ ያባትህን አትከተል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ያድርገን እንግዴህ አለ፡፡ በፍራቻ ንግግርም ቢሆን፡፡
"እሱማ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው፡፡ እንዴው የሚባለውንና ነው እንጅ ያልኩህ፡፡
ያሬድ ነገሩን ተወት አድርጎ ፤ አሁን ቶሎ ቶሎ ራመድ ራመድ በል፡፡ ያ አቶ ላንቻ ብቻ ሳይቀድመን እንድንደርስበት፡፡
"የማነው አቶ ላንቻ? አለ ተመስገን፡፡
"ለእኔ ከድሬ አዳማ ድረስ አልባሳ የሚያመጡልኝ ናቸው፡፡ መቼም ብታያቸው የተባረኩ እና ደግ ሰው ናቸው፡፡
አሁንም ከሳቸው ተረክበን ነው፡፡ የምንመለሰው ከቀናን"፡፡
"እኔ እኮ ውሎ ገባ ስትመጣ በአየር መምጣት ጀመረ እንዴ ብየ ነበር፡፡ ለካስ አንተ አዳማ ድረስ የሚያመጣልህ ደንበኛ አግኝተህ ኖሯል፡፡እየከነፍህ የምትመጣው"፡፡
"መኪናው ሞልቶ አንድ ሰው ብቻ ቀርቶት ይጠባበቃል፡፡ እየተጣደፉ ደረሱ፡፡ ግን እረዳቱ ከአንድ ሰው ውጭ አልጭንም አላቸው፡፡ ጫነን አልጭንም ፤ ሲከራከሩ አንድ ረፍዶበት የነበር ሰው ረዳቱንም ሳይጠይቅ አልፎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ያሬድ ቢለምንም ፣ ቢማፀንም ሳያሳፍራቸው ጥሏቸው ሄደ፡፡
አላልኩህም፡፡ አንድ ሰው ጥሩ አይደለም ብየህ ነበር አለው ተመስገን፡፡
ጸያሬድ ተመስገን ያለውን የሰማው አይመስልም፡፡ ልቡ ያለው አቶ ላንቻ ጋር ነው፡፡ አንድ የጭነት መኪና ወደ አዳማ ልትወጣ ከመንገድ ላይ ቆማለች፡፡
"ይችን መኪና እንጠይቃት እስቲ ፤ ትጭነን እንደ ሆነ አለ ተመስገን፡፡
"እህል ጭና እያየሃት እንዴት እሽ ብለው ይጭኑናል፡፡ ያጠፋነው እኛ ነን፡፡ በጥዋት መምጣት ሲገባን አርፍደን፡፡ አሁን ያለን አማራጭ ወደ ቤት መመለስ ነው፡፡ ነገ ተመልሰን እንመጣለን፡፡ እንደው
የሚያነድደኝ እምነት ማጉደሌ ነው፡፡ መቼም መኪና አጥቶ ቀረ አይሉኝም፡፡ ሆነ ብሎ ነው እንጅ የሚሉኝ፡፡ እህል ወደ ጫነችው አይሱዚ ተጠጉ፡፡
ፈራ ተባ እያለ ማነህ ወንድም ወደ አዳማ እንደሆነ የምትሄደው መኪና ጥሎን ስለሄደ ነው፡፡ እባክህ ተባበረን ብሎ ሹፌሩን ጠየቀው ያሬድ፡፡
የመኪናው ሹፌር አላመነታም፡፡ "ስንት ናችሁ"? አለ፡፡
"ሁለት ነን አለ፤ ያሬድ፡፡
"ሁለት ሰው ከሆነ አልጭንም"፡፡ አንድ ሰው ከሆነ ጋቢና ግባ አለ፡፡ ባጭር ቃል ሹፌሩ፡፡
"እባክህን ወንድም ተባበረን ስለማንነጣጠል ነው፡፡ የምንሔደውም የታመመ ሰው ለማምጣት ነው፡፡
እንደምንም ተቸገርልን፡፡ ከላይም ቢሆን ተጭነን እንሄዳለን እያለ ሹፌሩን ተማፀነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እጅግ በጣም ይቅርታ ስልኬ ስለጠፋ እረጅም ጊዜ ታሪኩን ሳለቅ ቀረሁ ወደኋላ መለስ ብለቹ ታሪኩን በማስታወስ ቀጥሉ እንደእግዚአብሔር ፍቃድ ከነገ ጀምሮ ሁለት ክፍል እለቃለሁ እንዲሁም ነገ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ እንጀምራለን የተከፋችሁብኝ አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ🙏
ያሬድ
ከገበያ መጥቶ ደክሞታል፡፡ ገና ሳይመሽ ከመኝታው ላይ ጋደም እንደማለት ብሏል፡፡
"ተመስገንን አብረን እንሄዳለን ብለኸው ነበር እንዴ"? አለች ፤ ባለቤቱ አበበች፡፡
"አዎ ፤ ብዬው ነበር፡፡ ገንዘብ እንዳዘጋጀ ነገረሽ እንዴ"?
"ትላንት አንተን ፈልጎ መጥቶ ነበር፡፡ ሳያገኝህ ሲቀር ለእኔ አጫውቶኛል፡፡ እንሂድ እስከምትለው ነው የሚጠብቀው" ፡፡
"ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ የመነገድ ፍላጎት ካለው አሁን ደግሞ ውሎ ገባ ስለሆነ የምንመጣው ቀን እንኳን ቢመሽም ሁለት መሆኑ አይከፋም፡፡ ከነገ ወዲያ ይዠው እሄዳለሁ"፡፡
ገና በደንብ አልነጋም፡፡ ያሬድም ከመኝታው አልተነሳም፡፡ አበበች አለ ፡፡ ሳይደጋግም በአንዴ የሚሰማ መስሎት፡፡ ነገር ግን የሚሰማው አላገኘም፡፡ አቤት የሚለው አጣ፡፡ ደግሞ ተጣራ፡፡ ያሬድ…..ያሬድ አለ፡፡ አቤት አለች አበበች፡፡ ብቅበይ አለ፡፡ በጥዋት ወደ ያሬድ ጋር የመጣው ተመስገን፡፡
ማነው በጥዋት ብቅበይ የሚለው ብላ ብቅ አለች፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች ? አለ" ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ተመስገን፡፡ አትገባም እንዴ ከብርድ ላይ ፡፡
"ይሁን አልገባም፡፡ ያሬድ የለም እንዴ ? ፡፡
"አለ ፤ ከመኝታውም አልተነሳም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም እንዴ ?
"ኧረ ደህናነኝ፡፡ ለዛ ላጫወትኩሽ ጉዳይ ነበር የመጣሁት ፡፡
"አይ! እሱንማ ከሆነ እኔም ማታ አጫውቸዋለሁ፡፡ ለመነገድ ፍላጎት ካለው ይዠው እሄዳለሁ ብሏል፡፡ ለማንኛውም ግባና አነጋግረው ፡፡
ተመስገን የመጣበትን ጉዳይ እንደተሳካለት አሰበ፡፡ ያሬድን ለማነጋገር ወደ ቤት ገባ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ? ፣ ደሞ ዛሬ በጥዋት አልተነሳህም፡፡ እንቅልፍ ነው ወይስ ድካም ነው?፡፡ ያስተኛህ ፡፡
"ሰላም አደርህ ተመስገን፡፡ ምን የትናንት ገበያ ውልቅልቅ አድርጎኛል፡፡ አሁን በደንብ ነግቷል ማለት ነው እንዴ? አለ፡፡ ከተኛበት መኝታ ተነስቶ እየተንጠራራ፡፡
"ስድስት ሰዓት ሆኖ ነግቷል ትላለህ እንዴ ፤ ለነገሩ ከተማ ለከተማ ስትመላለስ የከተማ ሰው ሆነሃል፡፡ እነኝህ ከተመኞች ሰዓት አስረው ቢይዙም ፤ የሚቆጥሩ መሆናቸውን እንጃ ፤ በየሰዓቱ ነው የሚበሉ
አለ፡፡ ተመስገን እንደማሾፍ ብሎ፡፡
"አይ! ተመስገን እነሱማ በሰዓት የማይበሉበት ጊዜ ስለሌላቸው ነው፡፡ ያለመቁጠር አይደለም፡፡ እንዲያውም እኛ ነን አንዴ ቁርስሠ ፣ አንዴ ምሳ ሰዓት ፣ ደረሰ እያልን ሰዓት የሚቃወመን ይመስል በቀን ሶስቴ ሳይበቃን አራተኛ መክሰስ እያልን የምንመገበው፡
"አይ! መልካም ነው" ብሎ "ለባለፈው ጉዳይ ነበር የመጣሁት" አለ ተመስገን ፡፡
"አበበች ማታ በጨዋታ አንስተን ነግራኛለች፡፡ እና ለመነገድ ፈልገሃል ማለት ነው?፡፡
"የመነገድ ፍላጎት እንኳን ብዙም የለኝም፡፡ እንዴው የዛችን የእህቴ ነገር አንጄቴ አልቆርጥ ብሎኝ ነው፡፡ መቼም እቤት ከመቀመጥ አካባቢንና አገርን ማወቅ አይከፋም፡፡ የእግዚአብሔር ስራም አይታወቅም፡፡ በዛውም እናገኛት ይሆናል"፡፡
"ጥሩ ነው ለማንኛውም ሃሳብህ አይከፋም፡፡ ነገ አብረን ማለድ ብለህ በጥዋት ና፡፡ ውሎ ገባ ስለምንመለስ እንዳይረፍድብን"፡፡
"እሽ በጥዋት እመጣለሁ፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
"በነጋታው በጥዋት ቡና ፈልቶ ተመስገን እየተጠበቀ ነው፡፡ ግን ቶሎ ሊመጣ አልቻለም፡፡ በቃ ቀርቶ ነው ብላ አበበች ቁርስ ልታቀርብ ስትል ተመስገን መጣ፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠው ተቀመጠ፡፡
"ምነው አረፈድህ" አለው ያሬድ
"ምን ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወሰደኝ አድሮ ሊነጋጋ አካባቢ ሸለብ አላደረገኝ መሰለህ ፡፡
"አይ! አንተ ሌሊቱን ሙሉ በሃሳብ ስትሄድ አድረህ ነዋ፡፡ ጥዋት በመነሻህ ሰዓት እንቅልፍ የጣለህ፡፡ በል አሁን የቡና ቁርሱን ያዝና ቡናውን ጠጥተን ቶሎ እንውጣ፡፡ የባልጪ መኪና ሳያመልጠን እንድረስበት፡፡ አንዴ ካመለጠን መመለስ ካልሆነ ሌላ መኪና አናገኝም፡፡
ባለቤቱን በይ እንግዴህ ከብት ሳይበዛ ከብቶቹን ውሃ አጠጫቸው ብሏት ተነስተው ከተመስገን ጋር ጉዞዋቸውን ወደ አዳማ ቀጠሉ፡፡
መኪና እንዳያመልጣቸው እየተጣደፉ ነው፡፡ ከመንገድ ላይ አንድ ጥቁር ሰው ከፊት ለፊታቸው ገጠማቸው፡፡
"ዛሬ ላይቀናን ነው መሰለኝ አለ ተመስገን፡፡ ውስጡ እንደመረበሽ እያለበት፡፡
"ምነው ምን አየህ አለው? ያሬድ፡፡
"ተመስገን የፍጥነት እርምጃውን ገታ አድርጎ ፤ መንገድ ስትሄድ አንድ ሰው ከገጠመህ የምትሄድበት አይቀናህም፡፡ አባቴ ሲናገር ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም እኛ አንድ ሰው ሰለገጠመን ብዬ ነው፡፡
ባያምንበትም ግን ሆዱ እንደመፍራት ብሏል፡፡ "ተው! እባክ ይህ የአንዳንድ ሰው አባባል ነው፡፡ አንተ ደግሞ ያባትህን አትከተል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ያድርገን እንግዴህ አለ፡፡ በፍራቻ ንግግርም ቢሆን፡፡
"እሱማ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው፡፡ እንዴው የሚባለውንና ነው እንጅ ያልኩህ፡፡
ያሬድ ነገሩን ተወት አድርጎ ፤ አሁን ቶሎ ቶሎ ራመድ ራመድ በል፡፡ ያ አቶ ላንቻ ብቻ ሳይቀድመን እንድንደርስበት፡፡
"የማነው አቶ ላንቻ? አለ ተመስገን፡፡
"ለእኔ ከድሬ አዳማ ድረስ አልባሳ የሚያመጡልኝ ናቸው፡፡ መቼም ብታያቸው የተባረኩ እና ደግ ሰው ናቸው፡፡
አሁንም ከሳቸው ተረክበን ነው፡፡ የምንመለሰው ከቀናን"፡፡
"እኔ እኮ ውሎ ገባ ስትመጣ በአየር መምጣት ጀመረ እንዴ ብየ ነበር፡፡ ለካስ አንተ አዳማ ድረስ የሚያመጣልህ ደንበኛ አግኝተህ ኖሯል፡፡እየከነፍህ የምትመጣው"፡፡
"መኪናው ሞልቶ አንድ ሰው ብቻ ቀርቶት ይጠባበቃል፡፡ እየተጣደፉ ደረሱ፡፡ ግን እረዳቱ ከአንድ ሰው ውጭ አልጭንም አላቸው፡፡ ጫነን አልጭንም ፤ ሲከራከሩ አንድ ረፍዶበት የነበር ሰው ረዳቱንም ሳይጠይቅ አልፎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ያሬድ ቢለምንም ፣ ቢማፀንም ሳያሳፍራቸው ጥሏቸው ሄደ፡፡
አላልኩህም፡፡ አንድ ሰው ጥሩ አይደለም ብየህ ነበር አለው ተመስገን፡፡
ጸያሬድ ተመስገን ያለውን የሰማው አይመስልም፡፡ ልቡ ያለው አቶ ላንቻ ጋር ነው፡፡ አንድ የጭነት መኪና ወደ አዳማ ልትወጣ ከመንገድ ላይ ቆማለች፡፡
"ይችን መኪና እንጠይቃት እስቲ ፤ ትጭነን እንደ ሆነ አለ ተመስገን፡፡
"እህል ጭና እያየሃት እንዴት እሽ ብለው ይጭኑናል፡፡ ያጠፋነው እኛ ነን፡፡ በጥዋት መምጣት ሲገባን አርፍደን፡፡ አሁን ያለን አማራጭ ወደ ቤት መመለስ ነው፡፡ ነገ ተመልሰን እንመጣለን፡፡ እንደው
የሚያነድደኝ እምነት ማጉደሌ ነው፡፡ መቼም መኪና አጥቶ ቀረ አይሉኝም፡፡ ሆነ ብሎ ነው እንጅ የሚሉኝ፡፡ እህል ወደ ጫነችው አይሱዚ ተጠጉ፡፡
ፈራ ተባ እያለ ማነህ ወንድም ወደ አዳማ እንደሆነ የምትሄደው መኪና ጥሎን ስለሄደ ነው፡፡ እባክህ ተባበረን ብሎ ሹፌሩን ጠየቀው ያሬድ፡፡
የመኪናው ሹፌር አላመነታም፡፡ "ስንት ናችሁ"? አለ፡፡
"ሁለት ነን አለ፤ ያሬድ፡፡
"ሁለት ሰው ከሆነ አልጭንም"፡፡ አንድ ሰው ከሆነ ጋቢና ግባ አለ፡፡ ባጭር ቃል ሹፌሩ፡፡
"እባክህን ወንድም ተባበረን ስለማንነጣጠል ነው፡፡ የምንሔደውም የታመመ ሰው ለማምጣት ነው፡፡
እንደምንም ተቸገርልን፡፡ ከላይም ቢሆን ተጭነን እንሄዳለን እያለ ሹፌሩን ተማፀነው፡፡
👍85❤8👎2🥰1