#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሶስት
#ትንሣኤ
በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የምርኮኞች ልውውጥ የሚጀመርበት የመጀመሪያው ምዕራፍ......
የድሬዳዋ ከተማ አሸብርቃለች፡፡ ገንደቆሬ፣ ገንደገራዳ፣ መጋላ፣ ከዚራ፣ ለገሀሬ፣ ..... መንደሮች በሙሉ በደስታ ስቀዋል፡፡
በየመንገዱ ግራና ቀኝ ተተክለው ቀዝቃዛና፤ ነፋሻማ አየርን የሚረጩት ዛፎች በደስታ ተውጠው የሚደንሱ ይመስላሉ፡፡ በዚያች ምድር ላይ የተካሄደው ቀውጢ ጦርነት አልፎ፤ ያንን የመሰለ የሰላም አየር መተንፈስ መቻል ዳግማዊ ልደት ነው፡፡
በሐረርጌ ምድር፡፡ በደገሀቡር፣ ቀብሪደሀር፣ መራራሌ፣ በሺላቦ፣
ደቦይን፣ በቆራሄ አሸዋማ ሜዳ፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በካራማራ ተራሮችና በሌሎችም ሺህ ሌሊት ሺህ መአልት የፈሰሰው ደም፣ የተከሰከሰው አጥንት፣ያስገኘው ውጤት፡፡
በዚያን ቀውጢ ሰዓት ላይ ለዳር ድንበር ሲሉ ከጠላት ጋር እየተናነቁ አኩሪ ገድል የፈጸሙት፤ በደማቸው ማህተም፤ በአጥንታቸው ክስካሽ፤ ምድሪቱን ያቀሉት...የመስዋዕትነት ፈርጦች! የሚጠበቁበት ዕለት......
ሰማዩ በዚያን ቀውጢ የጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ አየር ሃይል የተሠራውን አስደናቂ ትርኢትና ተአምር አፍ አውጥቶ ሊናገር፣ የታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ፣ የተዘጋጀ ይመስል አጉረመረመ፡፡ ለሚወዷት እናት አገራቸው ዳር ድንበር ሲሉ የተፋለሙና ልዩ ልዩ ጀብድ ከፈጸሙ በኋላ በጠላት እጅ ወድቀው በባእድ ሀገር በምርኮኝነትና፤ በእስረኝነት ለበርካታ
አመታት ከቆዩ በኋላ በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት ዛሬ ወደሚያፈቅሯትና፤ ወደሚወዷት፤ እናት አገራቸው የሚመለሱበት እለት ስለሆነ፤ እነዚህን ውድ የሀገር አለኝታዎችና፤ ጀግኖች፤በልዩና፤ በደማቅ አቀባበል ፤ ሊቀበል ህዝቡ የአውሮፕላን
ማረፊያውን አካባቢ አጥለቅልቆታል....
ማርሽ የሚያሰማው ሠራዊት በተጠንቀቅ ቆሞ ይጠባበቃል።ባንዲራዎች ይውለበለባሉ፡፡ ህዝቡ ይሯሯጣል፡፡ ይራወጣል። ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ይመለከታል፡፡
አንዳንድ ጊዜ ትላልቅ አሞራዎች ያሳስታሉ፡፡ የሁሉም ልብ ተንጠልጥሏል፡፡ እነማን ይሆኑ?! ሞቱ ተብለው ደረት
የተመታላቸው፣ ተዝካር የተበላላቸው፣ ማን ያውቃል? በህይወት ሊገኙ
ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህ ጦርነት በተካሄደባቸው ብዙ አገሮች በተደጋጋሚ
የታየ ክስተት ነው፡፡
ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ሰማዩ እንደገና በከፍተኛ ድምፅ አጉረመረመ፡፡አውሮፕላኗ በርቀት ታየች፡፡ ከዚያም እየጐላች ፤እየጐላች፤ መጣችና፤በማረፊያው ላይ እየዞረች፤ ማንዣባብ ጀመረች።
የሰው ጩኸት ሁካታ... ግርግር... ትርምሱ...ሌላ ሆኗል፡፡ማርሽ በረጅሙ ይሰማል፡፡ አውሮፕላኗ አዘቀዘቀች..... ከዚያም አኮበኮበችና አረፈች፡፡
ጀግኖች የታደሙባት አውሮፕላን! ለዳር ድንበሯ ሱሉ ደማቸውን ያፈሰሱላትን፣ በእስር የማቀቁላትን፣ ጥለው የወደቁላትን፣ ታስረው የተገረፉላትን፣ የጦር ምርኮኞችን ይዛ ይሄውና አውሮፕላኗ መሬት ላይ አረፈች....
የአውሮፕላኗ በር ተከፍቶ አንድ ረጅም፧ ቀጭን፤ መነጽር ያደረገና በአየር ኃይሉ ውስጥ በጦር ጄት የጠላትን ሃይል ድባቅ
በመምታት በደማቅ ቀለም ታሪክ ያስመዘገበ ምርኮኛ ብቅ አለ፡፡ማርሹ ይሰማል፡፡ እልልታው ቀለጠ!! ግማሹ በሲቃ ያለቅሳል፣ይፈነድቃል፡፡ ምርኮኞቹን ለማየት ሰው በሰው ላይ ይንጠላጠላል፣
ትዕይንቱ ብዙ ነው፡፡ ከዚያም የተዘጋጀውን እቅፍ አበባ ምርኮኛው ተቀበለ፡፡
ምርኮኞቹ ከአውሮፕላኗ እንደወረዱ መሬቷን ይስማሉ። አፈሯን ይልሳሉ፡፡ ያለቅሳሉ፣ ይንከባለላሉ፡፡ የደስታ እንባ... የናፍቆት እንባ... የትዝታ እንባ...
ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት ከአገር፤ ከወገን፣ ከቤተሰብ ጋር ተለያይተው ፤ የብቸኝነትንና የመከራ ኑሮን ሲገፉ ከቆዩ በኋላ፤የሚወዱትንና፤ የሚያፈቅሩትን፤ ህዝብና አገር መቀላቀል ዳግም መወለድ
ነውና፤ ምርኮኞች ዳግም የተወለዱ ያህል በደስታ ሰከሩ። እንደዚያ ዳር ድንበርዋን ሊያስከብሩላት፤ ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው፡ ሳንጃ ለሳንጃ ተሞዣልቀው፡ ጥለው የወደቁላት፡ የውድ ሀገራቸውን ለም አፈር ለማሽተት በመቻላቸው በደስታ የሚሆኑትን አጡ ...ህዝቡም በእልልታና በሆታ የጀግና አቀባበል አደረገላቸው፡፡ ደስ የሚል ከህሊና የማይጠፋ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት......
ለተወሰኑ ቀናቶች በድሬዳዋ ከተማ እረፍት አድርገው ከቆዩና መንፈሳቸው ከተረጋጋ በኋላ፣ በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሊቀላቀሉ የቸኮሉት ቀድመው ተንቀሳቀሱ፡፡
እለተ ቅዳሜ! አዲስ አበባ!! የኢትዮጵያ ዋና ከተማ! ቀዝቃዛ ንፋስ ይነፍስባታል ። በተለይ የባህር ማዶው ዛፍ ለቅዝቃዜው የራሱን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል፡፡
ባቡሩ መንገደኞቹን ጣቢያው አራገፈ፡፡ ግፊያው ለጉድ ነው፡፡ግማሹ ሲመጣ ግማሹ ሲሄድ... የገቢና ወጪ መንገደኞች ምልልስ የማያቋርጥበት አምባ......
ጊዜው ለዐይን ያዝ ማድረግ የጀመረበት ሰዓት ነው፡፡
አንድ ቁመቱ ረዘም ያለ፣ ሰውነቱ በበረሃ ግርፋትና በእስር ስቃይ ምክንያት የተለበለበ ግንድ ቢመስልም፤ በሰላሙ ጊዜ ማራኪ መልክና ቁመና እንደነበረው አሁንም በግልጽ የሚታየው ትክለ ሰውነቱ
ዐቢይ ምስክርነቱን የሚሰጥለት፤ ከሲታ ሰው ከባቡሩ ወረደ፡፡
ደረቱ ሰፋ ያለ፣ ፀጉረ ዞማና ዐይኖቹ ጐላ ጐላ ብለው የሚታዩ ረጅም ሰው ነው፡፡ ሻንጣ አንጠልጥሏል፡፡ ከተሰጠው የኪስ ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ያዋለው ለሁለት ሴቶችና፤ ለአንድ ወንድ የሚሆኑ ልብሶችን በመግዛት ነው፡፡ ከባቡሩ ወርዶ፤ በአምባሳደር ቲያትር በኩል መጥቶ ፤ ወደ ኦርማ ጋራዥ አቀና፡፡ የሚራመደው በደመነፍስ ዐይነት ነው፡፡
በህልም ዓለም የሚራመድ ይመስላል፡፡
እሱ እራሱ የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን ተጠራጥሯል።ግራና ቀኙን በዓይኑ ያማትራል፡፡ ሰዎችን ይቃኛል፡፡ ምናልባት የማውቀው ሰው ካገኘሁ በሚል ግምት ነው፡፡ ግን ማንም የሚያውቀው ሰው አላገኘም፡፡ ድሮ የሚያውቁት ሲያዩት እንኳን፤ በቀላሉ ሊለዩት አይችሉም፡፡ ተለውጧል፡፡ ተጉሳቁሏል፡፡
መንገዶቹ የጠበቡ፣ ቤቶቹም ከምዕተ ዓመት በፊት የነበሩ መስለው ታዩት፡፡ በየመንገዱ ላይ ከሚያያቸው ሰዎች ውስጥ ሶስት ሰዎችን ለማግኘት በናፍቆትና በጉጉት ደጋግሞ ይቃኛል፡፡
የሱ ብርቅዬ፤ ድንቅዬዎች፡፡ ልዩ የህይወቱ ቅመሞች፡፡ የተዳፈነ የናፍቆቱ እምቅ ሊፈነዳ ተቃረበ፡፡ ልቡ ተሸበረ... እየተቃረበ ሲመጣ ልቡ ድው ድው የሚል ድምጽ ሰጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው፡፡
እጅግ አስገራሚ ነው! አስደናቂ
የማይጠበቀው ሰው ፤ እንደዚህ ባልተጠበቀ ሰዓት ከች! ሲል፤ እነሱ
ከአንጀቱ የሚያፈቅራቸው፣ የሚወዳቸው፣ የሚሞትላቸው ቤተሰቦቹ እንዴት ሆነው ይሆን? የሚወዳት ሚስቱ፣ የሚወዳቸው ልጆቹ እንዴት ሆነው ይሆን? ሲለያቸው በነበራቸው ዕድሜ ላይ አስራ አንድ ዓመት ሲጨመርበት የትየለሌ ነው፡፡ ምን መስለው ይሆን?
አቤቱ ፈጣሪ ያንተ ተአምር እንዴት ተወርቶ ያልቅ ይሆን? አደራህን ሁሉንም ለአንድ ቀን እንኳን ቢሆን ዐይናቸውን አይቼው
እንድሞት እርዳኝ፡፡ አንተ ታውቃለህ፡፡
ወባ እንደያዘው ሰው እየተቃረበ መጣ፡፡ ቤቱ ጋ ሲደርስ ሰውነቱ ተንዘፈዘፈበት :: ልቡ በፍጥነት ይመታ ጀመር፡፡
ግቢው ...ያ ...ግቢ የሚወደው ግቢ...እዚያ ውስጥ ያሉት እነ.. መራመድ አልቻለም፡፡ ቆመ፡፡ እንደሀውልት ተገትሮ ቀረ፡፡ ከዚያም ለዘመናት በወስጡ ሲንተከተክ የነበረው እንባ በድንገት ገንፍሉ ወጣ፡፡
ከደስታ ብዛት ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ ቤቱን አየው፡፡ ልጆቹን አቅፎ የሳመበትን፣ ከሚያፈቅራት ባለቤቱ ጋር ደስታን ያሳለፈበትን፣ በመጨረሻም ወደ ጦርነት ሲሄድ ከቤተሰቦቹ ጋር ተላቅሶ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሶስት
#ትንሣኤ
በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት የምርኮኞች ልውውጥ የሚጀመርበት የመጀመሪያው ምዕራፍ......
የድሬዳዋ ከተማ አሸብርቃለች፡፡ ገንደቆሬ፣ ገንደገራዳ፣ መጋላ፣ ከዚራ፣ ለገሀሬ፣ ..... መንደሮች በሙሉ በደስታ ስቀዋል፡፡
በየመንገዱ ግራና ቀኝ ተተክለው ቀዝቃዛና፤ ነፋሻማ አየርን የሚረጩት ዛፎች በደስታ ተውጠው የሚደንሱ ይመስላሉ፡፡ በዚያች ምድር ላይ የተካሄደው ቀውጢ ጦርነት አልፎ፤ ያንን የመሰለ የሰላም አየር መተንፈስ መቻል ዳግማዊ ልደት ነው፡፡
በሐረርጌ ምድር፡፡ በደገሀቡር፣ ቀብሪደሀር፣ መራራሌ፣ በሺላቦ፣
ደቦይን፣ በቆራሄ አሸዋማ ሜዳ፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በካራማራ ተራሮችና በሌሎችም ሺህ ሌሊት ሺህ መአልት የፈሰሰው ደም፣ የተከሰከሰው አጥንት፣ያስገኘው ውጤት፡፡
በዚያን ቀውጢ ሰዓት ላይ ለዳር ድንበር ሲሉ ከጠላት ጋር እየተናነቁ አኩሪ ገድል የፈጸሙት፤ በደማቸው ማህተም፤ በአጥንታቸው ክስካሽ፤ ምድሪቱን ያቀሉት...የመስዋዕትነት ፈርጦች! የሚጠበቁበት ዕለት......
ሰማዩ በዚያን ቀውጢ የጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ አየር ሃይል የተሠራውን አስደናቂ ትርኢትና ተአምር አፍ አውጥቶ ሊናገር፣ የታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ፣ የተዘጋጀ ይመስል አጉረመረመ፡፡ ለሚወዷት እናት አገራቸው ዳር ድንበር ሲሉ የተፋለሙና ልዩ ልዩ ጀብድ ከፈጸሙ በኋላ በጠላት እጅ ወድቀው በባእድ ሀገር በምርኮኝነትና፤ በእስረኝነት ለበርካታ
አመታት ከቆዩ በኋላ በሁለቱ መንግስታት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሰረት ዛሬ ወደሚያፈቅሯትና፤ ወደሚወዷት፤ እናት አገራቸው የሚመለሱበት እለት ስለሆነ፤ እነዚህን ውድ የሀገር አለኝታዎችና፤ ጀግኖች፤በልዩና፤ በደማቅ አቀባበል ፤ ሊቀበል ህዝቡ የአውሮፕላን
ማረፊያውን አካባቢ አጥለቅልቆታል....
ማርሽ የሚያሰማው ሠራዊት በተጠንቀቅ ቆሞ ይጠባበቃል።ባንዲራዎች ይውለበለባሉ፡፡ ህዝቡ ይሯሯጣል፡፡ ይራወጣል። ሰማይ ሰማዩን እያንጋጠጠ ይመለከታል፡፡
አንዳንድ ጊዜ ትላልቅ አሞራዎች ያሳስታሉ፡፡ የሁሉም ልብ ተንጠልጥሏል፡፡ እነማን ይሆኑ?! ሞቱ ተብለው ደረት
የተመታላቸው፣ ተዝካር የተበላላቸው፣ ማን ያውቃል? በህይወት ሊገኙ
ይችሉ ይሆናል፡፡ ይህ ጦርነት በተካሄደባቸው ብዙ አገሮች በተደጋጋሚ
የታየ ክስተት ነው፡፡
ሰዓቱ ደረሰ፡፡ ሰማዩ እንደገና በከፍተኛ ድምፅ አጉረመረመ፡፡አውሮፕላኗ በርቀት ታየች፡፡ ከዚያም እየጐላች ፤እየጐላች፤ መጣችና፤በማረፊያው ላይ እየዞረች፤ ማንዣባብ ጀመረች።
የሰው ጩኸት ሁካታ... ግርግር... ትርምሱ...ሌላ ሆኗል፡፡ማርሽ በረጅሙ ይሰማል፡፡ አውሮፕላኗ አዘቀዘቀች..... ከዚያም አኮበኮበችና አረፈች፡፡
ጀግኖች የታደሙባት አውሮፕላን! ለዳር ድንበሯ ሱሉ ደማቸውን ያፈሰሱላትን፣ በእስር የማቀቁላትን፣ ጥለው የወደቁላትን፣ ታስረው የተገረፉላትን፣ የጦር ምርኮኞችን ይዛ ይሄውና አውሮፕላኗ መሬት ላይ አረፈች....
የአውሮፕላኗ በር ተከፍቶ አንድ ረጅም፧ ቀጭን፤ መነጽር ያደረገና በአየር ኃይሉ ውስጥ በጦር ጄት የጠላትን ሃይል ድባቅ
በመምታት በደማቅ ቀለም ታሪክ ያስመዘገበ ምርኮኛ ብቅ አለ፡፡ማርሹ ይሰማል፡፡ እልልታው ቀለጠ!! ግማሹ በሲቃ ያለቅሳል፣ይፈነድቃል፡፡ ምርኮኞቹን ለማየት ሰው በሰው ላይ ይንጠላጠላል፣
ትዕይንቱ ብዙ ነው፡፡ ከዚያም የተዘጋጀውን እቅፍ አበባ ምርኮኛው ተቀበለ፡፡
ምርኮኞቹ ከአውሮፕላኗ እንደወረዱ መሬቷን ይስማሉ። አፈሯን ይልሳሉ፡፡ ያለቅሳሉ፣ ይንከባለላሉ፡፡ የደስታ እንባ... የናፍቆት እንባ... የትዝታ እንባ...
ላለፉት አስራ አንድ ዓመታት ከአገር፤ ከወገን፣ ከቤተሰብ ጋር ተለያይተው ፤ የብቸኝነትንና የመከራ ኑሮን ሲገፉ ከቆዩ በኋላ፤የሚወዱትንና፤ የሚያፈቅሩትን፤ ህዝብና አገር መቀላቀል ዳግም መወለድ
ነውና፤ ምርኮኞች ዳግም የተወለዱ ያህል በደስታ ሰከሩ። እንደዚያ ዳር ድንበርዋን ሊያስከብሩላት፤ ከጠላት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው፡ ሳንጃ ለሳንጃ ተሞዣልቀው፡ ጥለው የወደቁላት፡ የውድ ሀገራቸውን ለም አፈር ለማሽተት በመቻላቸው በደስታ የሚሆኑትን አጡ ...ህዝቡም በእልልታና በሆታ የጀግና አቀባበል አደረገላቸው፡፡ ደስ የሚል ከህሊና የማይጠፋ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት......
ለተወሰኑ ቀናቶች በድሬዳዋ ከተማ እረፍት አድርገው ከቆዩና መንፈሳቸው ከተረጋጋ በኋላ፣ በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሊቀላቀሉ የቸኮሉት ቀድመው ተንቀሳቀሱ፡፡
እለተ ቅዳሜ! አዲስ አበባ!! የኢትዮጵያ ዋና ከተማ! ቀዝቃዛ ንፋስ ይነፍስባታል ። በተለይ የባህር ማዶው ዛፍ ለቅዝቃዜው የራሱን ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል፡፡
ባቡሩ መንገደኞቹን ጣቢያው አራገፈ፡፡ ግፊያው ለጉድ ነው፡፡ግማሹ ሲመጣ ግማሹ ሲሄድ... የገቢና ወጪ መንገደኞች ምልልስ የማያቋርጥበት አምባ......
ጊዜው ለዐይን ያዝ ማድረግ የጀመረበት ሰዓት ነው፡፡
አንድ ቁመቱ ረዘም ያለ፣ ሰውነቱ በበረሃ ግርፋትና በእስር ስቃይ ምክንያት የተለበለበ ግንድ ቢመስልም፤ በሰላሙ ጊዜ ማራኪ መልክና ቁመና እንደነበረው አሁንም በግልጽ የሚታየው ትክለ ሰውነቱ
ዐቢይ ምስክርነቱን የሚሰጥለት፤ ከሲታ ሰው ከባቡሩ ወረደ፡፡
ደረቱ ሰፋ ያለ፣ ፀጉረ ዞማና ዐይኖቹ ጐላ ጐላ ብለው የሚታዩ ረጅም ሰው ነው፡፡ ሻንጣ አንጠልጥሏል፡፡ ከተሰጠው የኪስ ገንዘብ ውስጥ አብዛኛውን ያዋለው ለሁለት ሴቶችና፤ ለአንድ ወንድ የሚሆኑ ልብሶችን በመግዛት ነው፡፡ ከባቡሩ ወርዶ፤ በአምባሳደር ቲያትር በኩል መጥቶ ፤ ወደ ኦርማ ጋራዥ አቀና፡፡ የሚራመደው በደመነፍስ ዐይነት ነው፡፡
በህልም ዓለም የሚራመድ ይመስላል፡፡
እሱ እራሱ የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን ተጠራጥሯል።ግራና ቀኙን በዓይኑ ያማትራል፡፡ ሰዎችን ይቃኛል፡፡ ምናልባት የማውቀው ሰው ካገኘሁ በሚል ግምት ነው፡፡ ግን ማንም የሚያውቀው ሰው አላገኘም፡፡ ድሮ የሚያውቁት ሲያዩት እንኳን፤ በቀላሉ ሊለዩት አይችሉም፡፡ ተለውጧል፡፡ ተጉሳቁሏል፡፡
መንገዶቹ የጠበቡ፣ ቤቶቹም ከምዕተ ዓመት በፊት የነበሩ መስለው ታዩት፡፡ በየመንገዱ ላይ ከሚያያቸው ሰዎች ውስጥ ሶስት ሰዎችን ለማግኘት በናፍቆትና በጉጉት ደጋግሞ ይቃኛል፡፡
የሱ ብርቅዬ፤ ድንቅዬዎች፡፡ ልዩ የህይወቱ ቅመሞች፡፡ የተዳፈነ የናፍቆቱ እምቅ ሊፈነዳ ተቃረበ፡፡ ልቡ ተሸበረ... እየተቃረበ ሲመጣ ልቡ ድው ድው የሚል ድምጽ ሰጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው፡፡
እጅግ አስገራሚ ነው! አስደናቂ
የማይጠበቀው ሰው ፤ እንደዚህ ባልተጠበቀ ሰዓት ከች! ሲል፤ እነሱ
ከአንጀቱ የሚያፈቅራቸው፣ የሚወዳቸው፣ የሚሞትላቸው ቤተሰቦቹ እንዴት ሆነው ይሆን? የሚወዳት ሚስቱ፣ የሚወዳቸው ልጆቹ እንዴት ሆነው ይሆን? ሲለያቸው በነበራቸው ዕድሜ ላይ አስራ አንድ ዓመት ሲጨመርበት የትየለሌ ነው፡፡ ምን መስለው ይሆን?
አቤቱ ፈጣሪ ያንተ ተአምር እንዴት ተወርቶ ያልቅ ይሆን? አደራህን ሁሉንም ለአንድ ቀን እንኳን ቢሆን ዐይናቸውን አይቼው
እንድሞት እርዳኝ፡፡ አንተ ታውቃለህ፡፡
ወባ እንደያዘው ሰው እየተቃረበ መጣ፡፡ ቤቱ ጋ ሲደርስ ሰውነቱ ተንዘፈዘፈበት :: ልቡ በፍጥነት ይመታ ጀመር፡፡
ግቢው ...ያ ...ግቢ የሚወደው ግቢ...እዚያ ውስጥ ያሉት እነ.. መራመድ አልቻለም፡፡ ቆመ፡፡ እንደሀውልት ተገትሮ ቀረ፡፡ ከዚያም ለዘመናት በወስጡ ሲንተከተክ የነበረው እንባ በድንገት ገንፍሉ ወጣ፡፡
ከደስታ ብዛት ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ ቤቱን አየው፡፡ ልጆቹን አቅፎ የሳመበትን፣ ከሚያፈቅራት ባለቤቱ ጋር ደስታን ያሳለፈበትን፣ በመጨረሻም ወደ ጦርነት ሲሄድ ከቤተሰቦቹ ጋር ተላቅሶ
👍2🔥1
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
፡
፡
...የሴንቸሪ ሲቲ መንገዶች በሙሉ ውር ውር በሚሉ መኪናዎች ቢሞላም የእግረኛ መንገዶቹ ግን ጭር ያሉ ነበሩ ምክንያቱም ብዙውን ጊዜ ሰዎች
በሎስ አንጀለስ በእግራቸው አይሄዱም፤ በተለይ ደግሞ በዝናብ ውስጥ መሄዱ የማይታሰብ ነገር ነው። እርግጥ የሚጠብቃት ሴት አንድ አንዴ
በእግር ትጓዛለች፡፡ “ዛሬስ ምናልባት በእግሯ ወደ ቤቷ መሄድ ብትችልስ?
“በይ ውጭ እኮ ውጭ የት ነው ያለሽው?” እያለ በውስጡ ሲያመላልስ
በድንገት ሴትየዋ ከህንፃው ስትወጣ ልቡ ደነገጠ፡፡ ምክንያቱም አልተዘጋጀም
ነበር፡፡ ልቡ በደንብ እየደለቀም እሷን መመልከት ጀመረ፡፡
ኮቷንም በቀበቶዋ ሸብ አድርጋ እና ራሷን አቀርቅራ በፍጥነት ወደ መንገዱ መሸጋገሪያ የምትሄደውን ሴት እየተመለከተ “እርዱኝ!” እያለ ጮኸ፡፡
በእርግጥ ድምፁ ያን ያክል ይሰማት አይሰማት እርግጠኛ አይደለም።
ቢሆንም ግን ዛሬ ይህቺ ሴት ልትሰማው ይገባል “ኧረ እርዱኝ!” አለ በድጋሚ፡፡
ይሄኔም ሊዛ ፍላንገን ወደ እሱ ዞር አለች ከቆሻሻው መጣያ አጠገብ አንድ ቀጭን ልጅ ይሁን ትልቅ ሰው መሆኑ የማይለይ ሰው አጎንብሶ ቁጢጥ ብሏል፡፡ ወደ እሱ ስትራመድ ስላያትም “እባክሽን 911 ደውይልኝ! ፖሊስ ጥሪልኝ፡፡ የሆነ ሰው በጩቤ ወግቶኛል።” አላት፡፡
እሷም “በእግዚአብሔር ስም” ብላ ስልኳን አወጣች እና እየደወለች ወደ
ልጁ ቀረበች፡፡ “ምን ሆነህ ነው? ደህና ነህ?” ብላ ጠየቀችው። ልጁ አጎንብሶ
ሆዱን በማጠፍ እጁን ሆዱ ላይ አስቀምጦታል፡፡ ኮፍያ ያለው ሹራብ ነው
የለበሰው:: ሹራቡ ላይ የዘነበበት ዝናብም ፊቱን እና ፀጉሩን አርሶታል።
“የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ምን ነበር የፈለጉት?”
“ፖሊስ ይድረስልኝ፡፡” ብላ ሊዛ በማስከተል “ አምቡላንስም ጭምር” አለች እና አናቱን በእጇ እየነካች “አይዞህ እርዳታ እየመጣልን ነው። ምንህን ነው
የተጎዳኸው?” ብላ ጠየቀችው፡፡
ልጁም ፈገግ ብሎ ሲያያት ሊዛ የልጁን ፊት አይታ በጣም ቀፈፋት እና ለማስታወክ ዳዳት ከሹራብ ኮፍያው ሥር ያለው የልጁ ፊት የሰው አይመስልም፡፡ ፊቱ ፍፁም አረንጎዴ ከመሆኑም በላይ አጥንቱ ገጧል። ይባስ
ብሎም ተቆራርጠው የተንጠለጠሉ የበሰበሱ ነገሮች ከፊቱ ተንጠልጥለዋል። ልትጮህ አፍዋን ብትከፍትም አንድም
ሊወጣላት አልቻለም።
911 ላይ የሚያወራት ሰውም “የእኔ እመቤት የት እንዳለሽ ልትነግሪኝ
ትችያለሽ?” ብሎ ጠየቃት። ባለ አረንጎዴው ፊትም በድንጋጤ የተከፈተውን የሊዛን አፍ እየተመለከተ ከሆዱ ስር ስለታም ጩቤ አወጣ እና ሆዷ ላይ ሰመጠጠው። ይሄኔም አየሩን የሚሰነጥቅ የእሪታ ድምፅ ከሊዛ አፍ ሊወጣ በቃ። በድጋሚም ስለቱን ከሆዷ ነቅሎ በጣም በሀይል ሲሰመጥጥባት እጁ ከጩቤው ጋር ተያይዞ ወደ ውስጥ ስለገባ የሆነ የሚሞቅ ርጥበት እጁ ላይ
ተሰማው።
“እባኮትን ያናገሩኝ? ይሰማዎታል? ምንድን ነው የተከሰተው? የት ቦታ
እንደሚገኙ ሊነግሩኝ ይችላሉ?” መሬት ላይ ከእጇ አምልጦ ከወደቀው ስልክ
የሚወጣ የ911 ሰውዬዋ ድምፅ ነው። ዶ/ር ኒኪ ሮበርትስ የX ክላስ
መርሴዲስ መኪና የሌዘር ወንበር ላይ ተለጥጣ የገራጁ በር እስኪከፈት
እየጠበቀች ትገኛለች፡፡ መንገዱ ክፍት ከሆነ በሀያ ደቂቃ ውስጥ ብሬንትውድ
ውስጥ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ትደርሳለች። ምንም እንኳን ረጅም እና
ባዶ የሆነ ህይወት ቤቷ ውስጥ ቢጠብቃትም ቴሌቪዥን በማየት በአንድ
ጠርሙስ አልኮል ባዶ ህይወቷን ትሞላለች:: እንኳን አንድ ምሽት፣ ሁሉ
ነገር ያልፍ አይደል?
ኒኪ መኪና ውስጥ እንዳለች የዛሬው ውሎዋ ላይ ሊዛን በሙሉ ልቧ ስላላደመጠቻት የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቷታል። ታካሚዋን ብትወደውም
ሆነ ብትጠላው ስራዋን በአግባቡ ሰርታ ስላልወጣች በእውነትም ቅር ብሏታል። የገራዥ በር በቀስታ መከፈት እንደጀመረ ኒኪ ወደ በሩ ነዳች እና ከህንፃው ወጥታ ወደ ጠባቡ መንገድ ገባች።
ሊዛ የበሩን መከፈት እና መዘጋት ድምፅን እና የመኪና ሞተር ድምፅ ስትሰማ በነበረበት ጊዜ ከሆዷ እና ከደረቷ ደሟ እንደጎርፍ ይወርድ ነበር።
መሮጥም ሆነ መቆም አልቻለችም:: ማድረግ የምትችለው አንድ ነገር ቢኖር
ጉሮሮዋ እስኪሰነጠቅ ድረስ መጮህ ነበር። በስለት የወጋት ሰው በስለቱ
እጇን፣ ጡቷን እና ጭኗን ጭምር ደግሞ ደጋግሞ ይቆራርጣታል። ቶሎ
ሊገድላት አልፈለገም እና ልክ ድመት የያዘችውን አይጥ እያሰቃየች
እንደምትዝናና ሁሉ እሱም የሚያደርገው ያንን ነበር።
የመኪናው ሞተር ድምፅ እየጨመረ መምጣትን ስትሰማ ግን በተስፋ
ተሞልታ ትንፋሿን ሰበሰበች። ከዚያም በህይወቷ ጮሀ የማታውቀውን
ጩኸት ጮኸች። በጩኸቷ መሀል ላይ ደሟ ጉሮሮዋ ውስጥ ሲንተከተክ
ታውቋታል፡፡ አይኗም ተጎልጉሎ የሚወጣ ሁላ መስሏታል።
የመኪናው መብራት ወደ እነርሱ አቅጣጫ አበራ። ይሄኔም የሚወጋት ሰውዬ እሷን የመውጋት ስራውን አቆመ፡፡ የመኪናው ሞተርም ድምፁ ጠፋ።
ሊዛ ዶ/ር ሮበርትሰን አይታኛለች ከዚህ ነፍሰ ገዳይም ታተርፈኛለች ብላ
እረፍት ተሰማት። ነፍሰ ገዳዩም የያዘውን ጩቤ መሬቱ ላይ ጣለው፡፡ የልብ
ምቷ ቀስ እያለ ሲመታ ይሰማታል፡፡ ባለጩቤው ሰው ግን ጥሏት ሊሮጥ
አልቻለም። የመኪናው በርም ሲከፈት አልሰማችም::
ሁለት... አምስት... አስር ሰኮንዶች አለፉ፡፡ ምንም የተከሰተ ነገር ግን አልነበረም፡፡ “እንዴ... ምንድን ነው ነገሩ?”
የመኪናው ሞተር ድምፅ በድጋሚ ተሰማት፡፡ አይሆንም! ጠባቡን መታጠፊያ የመኪናው መብራት አጥለቀለቀው፡፡
“አይሆንም! አይሆንም! እባክሽን ድረሺልኝ! ስለእግዚአብሔር ብለሽ
ድረሺልኝ!!
የኒኪ ብርማ መርሴዲስ መኪና በጎን በኩል አለፋቸው እና ወደ ዋናው
መንገድ ውስጥ ገባ፡፡የበሰበሱ አጥንታማ እጆችም የሊዛ አንገት ላይ ተጠመጠሙ። ከፊት ለፊቷ አብረቅራቂው የገዳይ ጩቤ በእሷ ደም ጨቅይቶ ይታያታል።
ሊዛ “የት ነበር ያቆምነው?” ብሎ ገዳዩ ሰው እየገለፈጠ የተናገራት ንግግር እና አስቀያሚ ሳቁን ለመጨረሻ ጊዜ ነበር የሰማችው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ታች እንግዳ ማረፊያ ክፍሉ ስለሚጠብቁት ሁለቱ ታጣቂ የግል
ጠባቂዎች እያሰበ ጥሩ ስሜት እንዲሰማው ፈለገ። አልሰራም፡፡ ጥሩ ስሜት አልተሰማውም፡፡ በመቀጠል ደግሞ ቴራፒስቷን ራቁቷን አሰባት። ይሄ
ሳይሻል አይቀርም፡፡ ዶ/ር ኒኪ ሮበርትስ ስሜታዊ ሰው ነች ብሎ ያስባል።
ግራጫ አጭር ቀሚሷን ወደ ላይ ገፋ አድርጎ ዳሌዋን... አሰበ። ቦዲዋ
ተከፍቶ... “ኡፍ ደስ የሚል ነገር ነው...
ካርተር ከእኔ ጋር ነህ?” የሚለው ድምፅ ከሀሳቡ አነቃው። ድምፅዋን ሲሰማ ፊቱ ቀላበት፡፡ በመቀጠል ደግሞ ግራ ተጋባ፤ ለጥቆም ኮስተር አለ፡፡ስኬታማ የኢንቨስትመንት ባንከር፣ ወጣት የተማረ እና በጣም ሀብታም ሰው ነው። ሥራ ቦታው እና ሌሎች ቦታዎች ላይ ሁሉ ካርተር ሰዎችን በትዕዛዝ ቁጭ ብድግ ያስደርጋቸዋል፡፡ የሚፈልገውን ነገርም ሊያሟሉለት የሚራኮቱለት አይነት ሰው ነው። በተለይ ደግሞ ሴቶችን በሙሉ ስልጣን ውስጥ ሆኖ ነው የሚያዛቸው፡፡ አሁን እዚህ ቦታ ላይ ግን ልክ እንደ አንድ
ረባሽ ተማሪ ስሙን ስትጠራው ምቾት አልተሰማውም።
“ትላንት ማታ ምን አየሁ ብለህ እንዳሰብክ ደግመህ ንገረኝ እስቲ” “ሀሳቤ አይደለም! እንዴ እኔ ያየሁትን ነገር አይቼያለሁ። እኔ እብድ አይደለሁም!”
ብሎ ተበሰጫጨ እና ጥቅጥቅ ቡናማ ፀጉሩን ሞነጫጨረው፡፡
“እኔ እንደዛ አላልኩም” ብላ ድምፅዋን በማለስለስ ቀጠለች እና “አንዳንዴ ጤነኛ የሆኑ ሰዎች ሁሉ እንደዚህ አይነት ነገር ሊገጥማቸው ይችላል። እኔ እራሴ አንዳንዴ እንደዚያ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
፡
፡
...የሴንቸሪ ሲቲ መንገዶች በሙሉ ውር ውር በሚሉ መኪናዎች ቢሞላም የእግረኛ መንገዶቹ ግን ጭር ያሉ ነበሩ ምክንያቱም ብዙውን ጊዜ ሰዎች
በሎስ አንጀለስ በእግራቸው አይሄዱም፤ በተለይ ደግሞ በዝናብ ውስጥ መሄዱ የማይታሰብ ነገር ነው። እርግጥ የሚጠብቃት ሴት አንድ አንዴ
በእግር ትጓዛለች፡፡ “ዛሬስ ምናልባት በእግሯ ወደ ቤቷ መሄድ ብትችልስ?
“በይ ውጭ እኮ ውጭ የት ነው ያለሽው?” እያለ በውስጡ ሲያመላልስ
በድንገት ሴትየዋ ከህንፃው ስትወጣ ልቡ ደነገጠ፡፡ ምክንያቱም አልተዘጋጀም
ነበር፡፡ ልቡ በደንብ እየደለቀም እሷን መመልከት ጀመረ፡፡
ኮቷንም በቀበቶዋ ሸብ አድርጋ እና ራሷን አቀርቅራ በፍጥነት ወደ መንገዱ መሸጋገሪያ የምትሄደውን ሴት እየተመለከተ “እርዱኝ!” እያለ ጮኸ፡፡
በእርግጥ ድምፁ ያን ያክል ይሰማት አይሰማት እርግጠኛ አይደለም።
ቢሆንም ግን ዛሬ ይህቺ ሴት ልትሰማው ይገባል “ኧረ እርዱኝ!” አለ በድጋሚ፡፡
ይሄኔም ሊዛ ፍላንገን ወደ እሱ ዞር አለች ከቆሻሻው መጣያ አጠገብ አንድ ቀጭን ልጅ ይሁን ትልቅ ሰው መሆኑ የማይለይ ሰው አጎንብሶ ቁጢጥ ብሏል፡፡ ወደ እሱ ስትራመድ ስላያትም “እባክሽን 911 ደውይልኝ! ፖሊስ ጥሪልኝ፡፡ የሆነ ሰው በጩቤ ወግቶኛል።” አላት፡፡
እሷም “በእግዚአብሔር ስም” ብላ ስልኳን አወጣች እና እየደወለች ወደ
ልጁ ቀረበች፡፡ “ምን ሆነህ ነው? ደህና ነህ?” ብላ ጠየቀችው። ልጁ አጎንብሶ
ሆዱን በማጠፍ እጁን ሆዱ ላይ አስቀምጦታል፡፡ ኮፍያ ያለው ሹራብ ነው
የለበሰው:: ሹራቡ ላይ የዘነበበት ዝናብም ፊቱን እና ፀጉሩን አርሶታል።
“የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ምን ነበር የፈለጉት?”
“ፖሊስ ይድረስልኝ፡፡” ብላ ሊዛ በማስከተል “ አምቡላንስም ጭምር” አለች እና አናቱን በእጇ እየነካች “አይዞህ እርዳታ እየመጣልን ነው። ምንህን ነው
የተጎዳኸው?” ብላ ጠየቀችው፡፡
ልጁም ፈገግ ብሎ ሲያያት ሊዛ የልጁን ፊት አይታ በጣም ቀፈፋት እና ለማስታወክ ዳዳት ከሹራብ ኮፍያው ሥር ያለው የልጁ ፊት የሰው አይመስልም፡፡ ፊቱ ፍፁም አረንጎዴ ከመሆኑም በላይ አጥንቱ ገጧል። ይባስ
ብሎም ተቆራርጠው የተንጠለጠሉ የበሰበሱ ነገሮች ከፊቱ ተንጠልጥለዋል። ልትጮህ አፍዋን ብትከፍትም አንድም
ሊወጣላት አልቻለም።
911 ላይ የሚያወራት ሰውም “የእኔ እመቤት የት እንዳለሽ ልትነግሪኝ
ትችያለሽ?” ብሎ ጠየቃት። ባለ አረንጎዴው ፊትም በድንጋጤ የተከፈተውን የሊዛን አፍ እየተመለከተ ከሆዱ ስር ስለታም ጩቤ አወጣ እና ሆዷ ላይ ሰመጠጠው። ይሄኔም አየሩን የሚሰነጥቅ የእሪታ ድምፅ ከሊዛ አፍ ሊወጣ በቃ። በድጋሚም ስለቱን ከሆዷ ነቅሎ በጣም በሀይል ሲሰመጥጥባት እጁ ከጩቤው ጋር ተያይዞ ወደ ውስጥ ስለገባ የሆነ የሚሞቅ ርጥበት እጁ ላይ
ተሰማው።
“እባኮትን ያናገሩኝ? ይሰማዎታል? ምንድን ነው የተከሰተው? የት ቦታ
እንደሚገኙ ሊነግሩኝ ይችላሉ?” መሬት ላይ ከእጇ አምልጦ ከወደቀው ስልክ
የሚወጣ የ911 ሰውዬዋ ድምፅ ነው። ዶ/ር ኒኪ ሮበርትስ የX ክላስ
መርሴዲስ መኪና የሌዘር ወንበር ላይ ተለጥጣ የገራጁ በር እስኪከፈት
እየጠበቀች ትገኛለች፡፡ መንገዱ ክፍት ከሆነ በሀያ ደቂቃ ውስጥ ብሬንትውድ
ውስጥ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ትደርሳለች። ምንም እንኳን ረጅም እና
ባዶ የሆነ ህይወት ቤቷ ውስጥ ቢጠብቃትም ቴሌቪዥን በማየት በአንድ
ጠርሙስ አልኮል ባዶ ህይወቷን ትሞላለች:: እንኳን አንድ ምሽት፣ ሁሉ
ነገር ያልፍ አይደል?
ኒኪ መኪና ውስጥ እንዳለች የዛሬው ውሎዋ ላይ ሊዛን በሙሉ ልቧ ስላላደመጠቻት የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቷታል። ታካሚዋን ብትወደውም
ሆነ ብትጠላው ስራዋን በአግባቡ ሰርታ ስላልወጣች በእውነትም ቅር ብሏታል። የገራዥ በር በቀስታ መከፈት እንደጀመረ ኒኪ ወደ በሩ ነዳች እና ከህንፃው ወጥታ ወደ ጠባቡ መንገድ ገባች።
ሊዛ የበሩን መከፈት እና መዘጋት ድምፅን እና የመኪና ሞተር ድምፅ ስትሰማ በነበረበት ጊዜ ከሆዷ እና ከደረቷ ደሟ እንደጎርፍ ይወርድ ነበር።
መሮጥም ሆነ መቆም አልቻለችም:: ማድረግ የምትችለው አንድ ነገር ቢኖር
ጉሮሮዋ እስኪሰነጠቅ ድረስ መጮህ ነበር። በስለት የወጋት ሰው በስለቱ
እጇን፣ ጡቷን እና ጭኗን ጭምር ደግሞ ደጋግሞ ይቆራርጣታል። ቶሎ
ሊገድላት አልፈለገም እና ልክ ድመት የያዘችውን አይጥ እያሰቃየች
እንደምትዝናና ሁሉ እሱም የሚያደርገው ያንን ነበር።
የመኪናው ሞተር ድምፅ እየጨመረ መምጣትን ስትሰማ ግን በተስፋ
ተሞልታ ትንፋሿን ሰበሰበች። ከዚያም በህይወቷ ጮሀ የማታውቀውን
ጩኸት ጮኸች። በጩኸቷ መሀል ላይ ደሟ ጉሮሮዋ ውስጥ ሲንተከተክ
ታውቋታል፡፡ አይኗም ተጎልጉሎ የሚወጣ ሁላ መስሏታል።
የመኪናው መብራት ወደ እነርሱ አቅጣጫ አበራ። ይሄኔም የሚወጋት ሰውዬ እሷን የመውጋት ስራውን አቆመ፡፡ የመኪናው ሞተርም ድምፁ ጠፋ።
ሊዛ ዶ/ር ሮበርትሰን አይታኛለች ከዚህ ነፍሰ ገዳይም ታተርፈኛለች ብላ
እረፍት ተሰማት። ነፍሰ ገዳዩም የያዘውን ጩቤ መሬቱ ላይ ጣለው፡፡ የልብ
ምቷ ቀስ እያለ ሲመታ ይሰማታል፡፡ ባለጩቤው ሰው ግን ጥሏት ሊሮጥ
አልቻለም። የመኪናው በርም ሲከፈት አልሰማችም::
ሁለት... አምስት... አስር ሰኮንዶች አለፉ፡፡ ምንም የተከሰተ ነገር ግን አልነበረም፡፡ “እንዴ... ምንድን ነው ነገሩ?”
የመኪናው ሞተር ድምፅ በድጋሚ ተሰማት፡፡ አይሆንም! ጠባቡን መታጠፊያ የመኪናው መብራት አጥለቀለቀው፡፡
“አይሆንም! አይሆንም! እባክሽን ድረሺልኝ! ስለእግዚአብሔር ብለሽ
ድረሺልኝ!!
የኒኪ ብርማ መርሴዲስ መኪና በጎን በኩል አለፋቸው እና ወደ ዋናው
መንገድ ውስጥ ገባ፡፡የበሰበሱ አጥንታማ እጆችም የሊዛ አንገት ላይ ተጠመጠሙ። ከፊት ለፊቷ አብረቅራቂው የገዳይ ጩቤ በእሷ ደም ጨቅይቶ ይታያታል።
ሊዛ “የት ነበር ያቆምነው?” ብሎ ገዳዩ ሰው እየገለፈጠ የተናገራት ንግግር እና አስቀያሚ ሳቁን ለመጨረሻ ጊዜ ነበር የሰማችው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ታች እንግዳ ማረፊያ ክፍሉ ስለሚጠብቁት ሁለቱ ታጣቂ የግል
ጠባቂዎች እያሰበ ጥሩ ስሜት እንዲሰማው ፈለገ። አልሰራም፡፡ ጥሩ ስሜት አልተሰማውም፡፡ በመቀጠል ደግሞ ቴራፒስቷን ራቁቷን አሰባት። ይሄ
ሳይሻል አይቀርም፡፡ ዶ/ር ኒኪ ሮበርትስ ስሜታዊ ሰው ነች ብሎ ያስባል።
ግራጫ አጭር ቀሚሷን ወደ ላይ ገፋ አድርጎ ዳሌዋን... አሰበ። ቦዲዋ
ተከፍቶ... “ኡፍ ደስ የሚል ነገር ነው...
ካርተር ከእኔ ጋር ነህ?” የሚለው ድምፅ ከሀሳቡ አነቃው። ድምፅዋን ሲሰማ ፊቱ ቀላበት፡፡ በመቀጠል ደግሞ ግራ ተጋባ፤ ለጥቆም ኮስተር አለ፡፡ስኬታማ የኢንቨስትመንት ባንከር፣ ወጣት የተማረ እና በጣም ሀብታም ሰው ነው። ሥራ ቦታው እና ሌሎች ቦታዎች ላይ ሁሉ ካርተር ሰዎችን በትዕዛዝ ቁጭ ብድግ ያስደርጋቸዋል፡፡ የሚፈልገውን ነገርም ሊያሟሉለት የሚራኮቱለት አይነት ሰው ነው። በተለይ ደግሞ ሴቶችን በሙሉ ስልጣን ውስጥ ሆኖ ነው የሚያዛቸው፡፡ አሁን እዚህ ቦታ ላይ ግን ልክ እንደ አንድ
ረባሽ ተማሪ ስሙን ስትጠራው ምቾት አልተሰማውም።
“ትላንት ማታ ምን አየሁ ብለህ እንዳሰብክ ደግመህ ንገረኝ እስቲ” “ሀሳቤ አይደለም! እንዴ እኔ ያየሁትን ነገር አይቼያለሁ። እኔ እብድ አይደለሁም!”
ብሎ ተበሰጫጨ እና ጥቅጥቅ ቡናማ ፀጉሩን ሞነጫጨረው፡፡
“እኔ እንደዛ አላልኩም” ብላ ድምፅዋን በማለስለስ ቀጠለች እና “አንዳንዴ ጤነኛ የሆኑ ሰዎች ሁሉ እንደዚህ አይነት ነገር ሊገጥማቸው ይችላል። እኔ እራሴ አንዳንዴ እንደዚያ
❤1👍1
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ዕለቱ የህዳር ወር የመጨረሻው ማክሰኞ ነው የአስቻለው ከንፈሮች ከሔዋን ከንፈሮች ጋር ከተገናኘ ሃምሳ ሁለተኛ ቀን። ሔዋን ቀጠሮ አክብራ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ከአስቻለው ቤት ደረሰች፡፡ አስቻለው ሔዋንን ከወስጥ አድርጎ ቤቱን ሲዘጋ ተሰምቶት የነበረ ደስታ አይረሳም።
በዚያ ዕለት ሔዋንን እንደ እንግዳ ወንበር ላይ ቁጭ በይ አላላትም፣
አንገቷን እቅፍ አድርጎ በቀጥታ ወደ አልጋ ወሰዳት፡፡ አልጋ ላይ ቁጭ ብለው ትንሽ ከተሟሟቁ በኋላ ስሜት በራሱ ሀይል ሲገፋቸው አንገት ለአንገት እንደተቃቀፋ፥ከንፈር ለከንፈር እንደተያያዙ ወደ ኋላ ከንብል አሉ፡፡ ጫማዎቻቸውን አወላልቀው
ወደ መሀል አልጋው ወጡና በሰፊው የፍቅር ሜዳ ላይ ሰፈሩ፡፡
ጉዞው ቀጠለ፡፡ ከንፈሮች በስራ ተጠመዱ፡፡ ዓይኖች ተስለመለሙ ትንፋሽ በረከተ፡፡ ገላጋይ የማያስፈልገው ትንቅንቅ ተጀመረ፣ የአስቻለው ቀኝ እጅ የሔዋንን
አንገት አቅፎ ግራው ደግሞ ሌላ ሥራ ያዘ። ከሔዋን ፀጉር ጀምሮ ማጅራቷን ይጎበኝና በወገቧ ላይ እየተስለክለክ ወደ ዳሌና ጭኖቿ ይወርዳል። ላይ ላዩን እንደ
ወረደ ሁሉ ወስጥ ውስጡን ለመመለስ በማሰብ ቀሚሷን ሰብሰብ እያደረገ ወደ
መሀል ጭኖቿ ጎራ ሊል ይቃጣዋል፡፡ ነገር ግን የሔዋን ጭኖች ወይ ፍንክች!!እንደገና ከላይ ይጀምራል፡፡ ይወርድ ይወርድና በአሰበው መንገድ ለመመሰስ ሲሞክር አሁንም ተቃውሞ ይገጥመዋል፡፡ ለሶስተኛ ጊዜ ሞከረ:: የሔዋን ጭኖች ግን
አልበገር አሉ።
በአራተኛው ጊዜ ከንፈሮችም ድንገት ተላቀቁ:: ሔዋን ወደ ቀልቧ ተመልሳ ኖሮ ድንገት ፍንጥር ብላ በመነሳት አልጋው ላይ ቁጭ አለች። አስቻለውም አልዘገየም፣ ሔዋን በተነሳችበት ቅፅበት እሱም ፍንጥር ብሎ ጭራሽ ከአልጋው ላይ ወደ መሬት ወረደ:: ፊትለፊቷ ቆሞ በነጭ ካኒተራው ላይ ደረቱን እያሻሽ
"ስሜቱ አልገባሽም አይደል ሔዩ" አላት በስሜት ውስጥ ሆኖ
ቅልስልስ እያል፡፡
"ገብቶኛል"
"ታዲያ ለምን ታስጨንቂኛለሽ?"
"እኔም ስለጨነቀኝ፡፡
«እንዴት?"»
«የእናት እደራና የእህት ማስጠንቀቂያ ስላሉበኝ»
“አልገባኝም ሐዩ!
«ና ቁጭ በል ልንገርህ»
አስቻለው ፈጥኖ ከአጠገቧ ቁጭ አለ። በመሀል ሔዋን በሀሳብ ጭልጥ ብሳ ሄደች:: ያኔ በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ከሸዋዬ ጋር ጠዋት ከክብረ መንግሥት ወደ
ዲላ ሊመጡ ሲሉ ማታ በዝግጅት ላይ በነበሩበት ወቅት ሽዋዩ ሔዋንን እፊቷ ቁጭ አድርጋ ከእናቷ ጋር የተነጋገሩት ነገር።
ስሚ እማዬ » ብላ ነበር ሽዋዬ ወሬ የጀመረችው። «ይቺን ሔዋንን
ከአሁኑ ምክሪልኝ:: ዲላ የቡና አገር ነው ሀብታም ሁሉ ሰው በገንዘብ መግዛት ይፈልጋል:: እሷ ደሞ ቆንጆ ስለሆነች በገንዘብ እያታለሉ ትምህርቷን አስትተው ብልግና ሊያስተምሯት ይችላሉ፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ህይወቷ ሊበላሽ ይችላል። እኔም ብሆን እንኳን ብልግና ፈጽማ ፡ የወንድ እጅ ጨበጠች ያሉኝ ዕለት ባለጌሽን አምጥቼ አስረክብሻለሁ።» ብላቸው ነበር፡፡ እናቷ ከተል እንዲህ ዓይነት ብልግና ትፈጥማለች ብዬ አልገምትም::
ያን ያህል ለፍቼ አሳድጌታለሁና
ክብሯን ጠብቃ ወግ ማረግ ታሳየኛለች ብዬ እጠብቃለሁ፡፡ ያ
ሳይሆን ቀርቶ ብልግና ፈጥማ አንቺ ወደኔ ብታመጫት እኔም የዚያኑ ዕለት ገደል ገደል ገብቼ እሞትና ቀብረሽኝ ትመለሻለሽ በማለት ተናግረው ነበር። ሔዋን ይህን የናቷን አደራና የእህቷን የማስጠንቀቂያ ቃል በሀሳቧ እያዳመጠች በነበረችበት ወቅት
«እስቲ ያስጨነቀሽን ነገር ንገሪኝ ሲል አስቻለሁ ከሀሳቧ ቀሰቀሳት፡፡
«ለመኑ ገርል መሆኔን ታውቃለህ?» አለችው ድንግል
መሆኗን ስትገልፅለት፡፡
«ኦ!» አለ አስቻለው ያላሰበው ነገር ሆኖበት።
«አትጠራጠር»። አለችውና ሔዋን እናቷ የጣለችባትን አደራና እህቷ ሸዋዬ የሰጠቻትን ማስጠንቀቂያ በዝርዝር አስረዳችው፡፡
ያ እንደ ብረት ግለ" የነበረ የአስቻለው ሰውነት ድንገት ቅዝትዝ ብርድ! ስንፍናና አለ።
«አደራ የምልህ አስቹ!» ስትል ቀጠለች ሔዋን። «ይህን የፍቅር ጉዳያችንን አንድ ቀን እታ አበባ የሰማች እንደሆነ መግቢያ ቀዳዳ የለኝም፡፡ ስለዚህ ሚስጥራችንን ከታፈሱና ጓደኞችህ" በቀር ሌላ ማንም ስለማያውቅ ሁሉም
በሚስጥር እንዲይዙልን አደራ እንድትላቸው ነው። እለችው::
አስቻለው በሁኔታው ተገርሞ ግንባሩን ይዞ መሬት መሬት ሲያይ ቆየና ድንገት ብድግ ብሎ ሔዋን ፊት በመቆም «እስቲ ወደኔ ነይ ሒዩ!» አላት፡፡
ሔዋንም ቡድግ ብላ በመቆም የአስቻለውን ዓይኖች ማየት ጀመረች፡፡
አስቻለው በሁለት እጆቹ የሔዋን ትክሻና ትክሻ ያዝ አድርጎ ቁልቁል
እየተመለከታት፡ ቃል ልገባ ነው ሐዩ፡»
«ምን ብለህ?»
የበሕይወት እስካለሁ ድረስ ፍጹም አልለይሽም። ከሠርጋችንም በፊት
ምንም አላደርግሽም» አላት፡፡
«እሺ» አለችው ሔዋን፡፡
አንገት ለአንገት ተቃተፉ። ምናልባት በሁለተኛው የህይወት ምዕራፍ ውስጥ እንደ ገቡ ታውቋቸው ሳይሆን አይቀርም ሆዳቸው ባብቶ ሁለቱም ተላቀሱ።
ይህ ዓይነቱ የፍቅር ከመሰራረት ሂደትና በውስጡ ያለው የሔዋን አደራ ነው ዛሬ አስቻለውን የከበደውና መንፈሱን ወጥሮ ነፍሱን ያስጨነቃት። አዎ
ተጨነቀ። ሔዋን በተፈጥሮ ፈሪና ሽቁጥቁጥ መሆኗን ያውቃል፡፡ ዛሬ በሸዋዬ ፊት እንደ ጭብጦ ጭርምትምት ብላ ታየችው:: ችግሩን በምን መላ ሊፈታው
እንደሚችል ግራ ገብቶት ፍዝዝ ትክዝ እንዳለ በዋርካው ምግብ ቤት ለብዙ ጊዜ የእራት ሠዓት ደርሶ ኖሯል። ድንገት ጓደኛው በልሁ በበር በኩል ወደ እሱ ሲያመራ አየወ፡፡ በልሁ ቁመቱ፡፡ ዘለግ ሰውነቱም ፈርጠምጠም ያለ ነው፡፡ ሰፋ ባለ የቀይ ዳማ ፊቱ ላይ በትር ወስሉ የተገተረው አፍንጫው ግርማ ሞገስ
አላብሶታል:: ዓይኑ ጎላ ጎላ ያለና ፈገግ ሲል ጥርሱ የሚያምር ነው:: ከውጭ ሲመጣ አስቻለው ትክዝ ብሉ በርቀት ዓይቶት ኖሮ ቀረብ ብሎ ሲያጤነውም ስሜቱ
መመሳቀሉን በመገንዘብ፡ ምነው ይክተር? ሰላም አይደለህም እንዴ?» አለና ሰላም ብሎት ከአጠገቡ ቁጭ አለ፡፡ አስቻለው ነርስ ስለሆነ ጓደኞቹ ብዙ ጊዜ ይክተር አያሉ በመጥራት ያሾፉበታል፡፡......
💫ይቀጥላል💫
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ዕለቱ የህዳር ወር የመጨረሻው ማክሰኞ ነው የአስቻለው ከንፈሮች ከሔዋን ከንፈሮች ጋር ከተገናኘ ሃምሳ ሁለተኛ ቀን። ሔዋን ቀጠሮ አክብራ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ከአስቻለው ቤት ደረሰች፡፡ አስቻለው ሔዋንን ከወስጥ አድርጎ ቤቱን ሲዘጋ ተሰምቶት የነበረ ደስታ አይረሳም።
በዚያ ዕለት ሔዋንን እንደ እንግዳ ወንበር ላይ ቁጭ በይ አላላትም፣
አንገቷን እቅፍ አድርጎ በቀጥታ ወደ አልጋ ወሰዳት፡፡ አልጋ ላይ ቁጭ ብለው ትንሽ ከተሟሟቁ በኋላ ስሜት በራሱ ሀይል ሲገፋቸው አንገት ለአንገት እንደተቃቀፋ፥ከንፈር ለከንፈር እንደተያያዙ ወደ ኋላ ከንብል አሉ፡፡ ጫማዎቻቸውን አወላልቀው
ወደ መሀል አልጋው ወጡና በሰፊው የፍቅር ሜዳ ላይ ሰፈሩ፡፡
ጉዞው ቀጠለ፡፡ ከንፈሮች በስራ ተጠመዱ፡፡ ዓይኖች ተስለመለሙ ትንፋሽ በረከተ፡፡ ገላጋይ የማያስፈልገው ትንቅንቅ ተጀመረ፣ የአስቻለው ቀኝ እጅ የሔዋንን
አንገት አቅፎ ግራው ደግሞ ሌላ ሥራ ያዘ። ከሔዋን ፀጉር ጀምሮ ማጅራቷን ይጎበኝና በወገቧ ላይ እየተስለክለክ ወደ ዳሌና ጭኖቿ ይወርዳል። ላይ ላዩን እንደ
ወረደ ሁሉ ወስጥ ውስጡን ለመመለስ በማሰብ ቀሚሷን ሰብሰብ እያደረገ ወደ
መሀል ጭኖቿ ጎራ ሊል ይቃጣዋል፡፡ ነገር ግን የሔዋን ጭኖች ወይ ፍንክች!!እንደገና ከላይ ይጀምራል፡፡ ይወርድ ይወርድና በአሰበው መንገድ ለመመሰስ ሲሞክር አሁንም ተቃውሞ ይገጥመዋል፡፡ ለሶስተኛ ጊዜ ሞከረ:: የሔዋን ጭኖች ግን
አልበገር አሉ።
በአራተኛው ጊዜ ከንፈሮችም ድንገት ተላቀቁ:: ሔዋን ወደ ቀልቧ ተመልሳ ኖሮ ድንገት ፍንጥር ብላ በመነሳት አልጋው ላይ ቁጭ አለች። አስቻለውም አልዘገየም፣ ሔዋን በተነሳችበት ቅፅበት እሱም ፍንጥር ብሎ ጭራሽ ከአልጋው ላይ ወደ መሬት ወረደ:: ፊትለፊቷ ቆሞ በነጭ ካኒተራው ላይ ደረቱን እያሻሽ
"ስሜቱ አልገባሽም አይደል ሔዩ" አላት በስሜት ውስጥ ሆኖ
ቅልስልስ እያል፡፡
"ገብቶኛል"
"ታዲያ ለምን ታስጨንቂኛለሽ?"
"እኔም ስለጨነቀኝ፡፡
«እንዴት?"»
«የእናት እደራና የእህት ማስጠንቀቂያ ስላሉበኝ»
“አልገባኝም ሐዩ!
«ና ቁጭ በል ልንገርህ»
አስቻለው ፈጥኖ ከአጠገቧ ቁጭ አለ። በመሀል ሔዋን በሀሳብ ጭልጥ ብሳ ሄደች:: ያኔ በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ከሸዋዬ ጋር ጠዋት ከክብረ መንግሥት ወደ
ዲላ ሊመጡ ሲሉ ማታ በዝግጅት ላይ በነበሩበት ወቅት ሽዋዩ ሔዋንን እፊቷ ቁጭ አድርጋ ከእናቷ ጋር የተነጋገሩት ነገር።
ስሚ እማዬ » ብላ ነበር ሽዋዬ ወሬ የጀመረችው። «ይቺን ሔዋንን
ከአሁኑ ምክሪልኝ:: ዲላ የቡና አገር ነው ሀብታም ሁሉ ሰው በገንዘብ መግዛት ይፈልጋል:: እሷ ደሞ ቆንጆ ስለሆነች በገንዘብ እያታለሉ ትምህርቷን አስትተው ብልግና ሊያስተምሯት ይችላሉ፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ህይወቷ ሊበላሽ ይችላል። እኔም ብሆን እንኳን ብልግና ፈጽማ ፡ የወንድ እጅ ጨበጠች ያሉኝ ዕለት ባለጌሽን አምጥቼ አስረክብሻለሁ።» ብላቸው ነበር፡፡ እናቷ ከተል እንዲህ ዓይነት ብልግና ትፈጥማለች ብዬ አልገምትም::
ያን ያህል ለፍቼ አሳድጌታለሁና
ክብሯን ጠብቃ ወግ ማረግ ታሳየኛለች ብዬ እጠብቃለሁ፡፡ ያ
ሳይሆን ቀርቶ ብልግና ፈጥማ አንቺ ወደኔ ብታመጫት እኔም የዚያኑ ዕለት ገደል ገደል ገብቼ እሞትና ቀብረሽኝ ትመለሻለሽ በማለት ተናግረው ነበር። ሔዋን ይህን የናቷን አደራና የእህቷን የማስጠንቀቂያ ቃል በሀሳቧ እያዳመጠች በነበረችበት ወቅት
«እስቲ ያስጨነቀሽን ነገር ንገሪኝ ሲል አስቻለሁ ከሀሳቧ ቀሰቀሳት፡፡
«ለመኑ ገርል መሆኔን ታውቃለህ?» አለችው ድንግል
መሆኗን ስትገልፅለት፡፡
«ኦ!» አለ አስቻለው ያላሰበው ነገር ሆኖበት።
«አትጠራጠር»። አለችውና ሔዋን እናቷ የጣለችባትን አደራና እህቷ ሸዋዬ የሰጠቻትን ማስጠንቀቂያ በዝርዝር አስረዳችው፡፡
ያ እንደ ብረት ግለ" የነበረ የአስቻለው ሰውነት ድንገት ቅዝትዝ ብርድ! ስንፍናና አለ።
«አደራ የምልህ አስቹ!» ስትል ቀጠለች ሔዋን። «ይህን የፍቅር ጉዳያችንን አንድ ቀን እታ አበባ የሰማች እንደሆነ መግቢያ ቀዳዳ የለኝም፡፡ ስለዚህ ሚስጥራችንን ከታፈሱና ጓደኞችህ" በቀር ሌላ ማንም ስለማያውቅ ሁሉም
በሚስጥር እንዲይዙልን አደራ እንድትላቸው ነው። እለችው::
አስቻለው በሁኔታው ተገርሞ ግንባሩን ይዞ መሬት መሬት ሲያይ ቆየና ድንገት ብድግ ብሎ ሔዋን ፊት በመቆም «እስቲ ወደኔ ነይ ሒዩ!» አላት፡፡
ሔዋንም ቡድግ ብላ በመቆም የአስቻለውን ዓይኖች ማየት ጀመረች፡፡
አስቻለው በሁለት እጆቹ የሔዋን ትክሻና ትክሻ ያዝ አድርጎ ቁልቁል
እየተመለከታት፡ ቃል ልገባ ነው ሐዩ፡»
«ምን ብለህ?»
የበሕይወት እስካለሁ ድረስ ፍጹም አልለይሽም። ከሠርጋችንም በፊት
ምንም አላደርግሽም» አላት፡፡
«እሺ» አለችው ሔዋን፡፡
አንገት ለአንገት ተቃተፉ። ምናልባት በሁለተኛው የህይወት ምዕራፍ ውስጥ እንደ ገቡ ታውቋቸው ሳይሆን አይቀርም ሆዳቸው ባብቶ ሁለቱም ተላቀሱ።
ይህ ዓይነቱ የፍቅር ከመሰራረት ሂደትና በውስጡ ያለው የሔዋን አደራ ነው ዛሬ አስቻለውን የከበደውና መንፈሱን ወጥሮ ነፍሱን ያስጨነቃት። አዎ
ተጨነቀ። ሔዋን በተፈጥሮ ፈሪና ሽቁጥቁጥ መሆኗን ያውቃል፡፡ ዛሬ በሸዋዬ ፊት እንደ ጭብጦ ጭርምትምት ብላ ታየችው:: ችግሩን በምን መላ ሊፈታው
እንደሚችል ግራ ገብቶት ፍዝዝ ትክዝ እንዳለ በዋርካው ምግብ ቤት ለብዙ ጊዜ የእራት ሠዓት ደርሶ ኖሯል። ድንገት ጓደኛው በልሁ በበር በኩል ወደ እሱ ሲያመራ አየወ፡፡ በልሁ ቁመቱ፡፡ ዘለግ ሰውነቱም ፈርጠምጠም ያለ ነው፡፡ ሰፋ ባለ የቀይ ዳማ ፊቱ ላይ በትር ወስሉ የተገተረው አፍንጫው ግርማ ሞገስ
አላብሶታል:: ዓይኑ ጎላ ጎላ ያለና ፈገግ ሲል ጥርሱ የሚያምር ነው:: ከውጭ ሲመጣ አስቻለው ትክዝ ብሉ በርቀት ዓይቶት ኖሮ ቀረብ ብሎ ሲያጤነውም ስሜቱ
መመሳቀሉን በመገንዘብ፡ ምነው ይክተር? ሰላም አይደለህም እንዴ?» አለና ሰላም ብሎት ከአጠገቡ ቁጭ አለ፡፡ አስቻለው ነርስ ስለሆነ ጓደኞቹ ብዙ ጊዜ ይክተር አያሉ በመጥራት ያሾፉበታል፡፡......
💫ይቀጥላል💫
👍4
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...በካፌ ዶርቢቴል በኩል ሳልፍ ሉልሰገድ ከዚያ ወጣ። ቀይ ፊቱ
ደም ለብሷል። ጉልህ ዓይኖቹ ጉድጓዳቸው ውስጥ ይገላበጣሉ። በጣም ተናዷል።
“ምን ሆንክ?» አልኩት
"ይህን ተካ አስታግስልኝ፣ አለዛ አንድ ቀን እገድለዋለሁ» አለኝ
“ምነው?»
"ባገኘኝ ቁጥር ያበሽቀኛል። ላብድ ነው»
«ለምን ሁለተኛ እንዳታናግረኝ አትለውም?»
የተዘረዘሩ ጥቃቅን ጥርሶቹን በተሸነፈ የንዴት ሳቅ እያሳየኝ
ቢያንስ አስር ጊዜ ብየዋለሁ» አለ ሁለተኛ ያናገርከኝ እንደሆነ፣ ወይ ለፖሊስ እነግራለሁ ወይ እገድልሀለሁ ብዬዋለሁ።
ደጋግሜ ደጋግሜ ነግሬዋለሁ፡፡ ሰድቤዋለሁ»
«ታድያስ?»
በሚቀጥለው ጊዜ ሲያገኘኝ ያነጋግረኛል። ትንሽ ካናገረኝ በኋላ
ያበሽቀኛል»
«አታኮርፈውም?»
«አይገባውማ!»
«አሁን ምን ይሻላል?»
«እኔ 'ንጃ፡፡ ይህን ከተማ ለቅቄ ልሂድ መሰለኝ
እየሳቅኩ «እስከዚያው ና ምን የመሰለ ቢራ ላጠጣህ» አልኩና
ባቡር ጣብያው አጠገብ አንዲት ስም የሌላት ካፌ አለች፣ እዚያ
ወሰድኩት። አንድ ቡና አይነት ቢራ አለ፣ ከስኮትላንድ የሚያስመጡት፡፡ ፀሀይ ላይ ቁጭ እንዳልን እሱን ቀመሰና
«ይህን እንዴት አገኘኸው ባክህን? እኔ ሁለተኛ ሌላ ቢራ
አልቀምስም» አለ። ንዴቱን መርሳት ጀምሯል፡፡ ራሱን እየነቀነቀ
«የተካ ዋና ፕሮብሌሙ ምን መሰለህ?» አለኝ «ጥሩ ልጅ ነው::
ከሰው ጋር ተስማምቶ መኖር ይፈልጋል። ግን በሄደበት ሰውን
እንዳበሸቀ ነው:: ወዶ አይደለም። ፍጥረቱ ነው»
«አውቃለሁ። ረስቼ አማንዳ ስትፈልግህ ነበር»
ዝም አለ። ገባኝ
"የፈረንጅ ሴቶች ሲሰለቹ!» አልኩት
«ያንተም ሰልችታሀለች?» አለኝ
«ፈረንጅ አይደለች?»
«አንተስ አትረባም» አለኝ
«ለምን?»
«ያችን የመሰለች ቆንጆ ምኗ ይሰለቻል? ድምፅዋ ብቻ
ይበቃል። በዛ ሰማያዊ አይኗ እያየችህ ያን ፈገግታ ስትሰጥህ
አንድ ፈገግታ እንደሱ ብታጠጣኝ ችዬ ከሷ አልለይም ነበር። በዚያ
ወፍራም ድምፅዋ ሉ ሃኒ ሉ' ብትለኝ ለዘለዓለም እታሰራለሁ»
«ፈገግታውንም ቁልምጫውንም ትሰጥሀለች ከፈለግክ»
«እንዲህም ብልህ'ኮ፣ ፈገግታውና ቁልምጫው ብቻ አይበቃም»
«አንተ ከፈለግክ ሌላውንም ትሰጥሃለች»
«እሱን ተወው! ካንተ ጋር ፍቅር እንደያዛት ያስታውቃል»
« ይመስልሀል» አልኩት
«ትወድሀለች ስልህ!»
«እሺ ይሁን፡፡ ግን አንዳንዴ ስላንተ ጣል የምታረገው ንግግር
አንተም ጠጋ ብትላት እንደማትሸሽህ ያሳያል»
«አዬ? ምን አለች?»
«አይ፣ እሱን አልነግርህም፡፡ ጠጋ ብትላት ራሷ ትነግርሀለች»
«እውነት እንድወስድልህ ትፈልጋለህ?» አለኝ
«አዎን፡፡ ግን ለሀበሾቹ እንዳትነግር»
«ግድ የለህም። እኔ ምልህ የኔን ሸክም ደሞ እንተ ትንሽ
ብትሸከምልኝ። አውቃለሁ አስቀያሚ ነች። ግን ጠጋ ስትላት የደስ ደስ አላት። ደሞ ከዛች ከቆንጆ ጋር ሰንብትህ ወደዚችኛዋ ስትመጣ
ጥሩ ለውጥ ሳይሆን አይቀርም። ሞክር እስቲ»
“አንተ ሞክር"
Shake on It! (ጨብጠኝ)» አለኝ፡፡ ተጨባበጥን
ትንሽ ቆይቶ፣ ራሱን እየነቀነቀ
«አባቶቻችን አሁን የተባባልነውን ቢሰሙ ምንኛ በናቁን!» አለ
እኔና ሉልሰገድ ሚስቶቻችንን እየያዝን አብረን ሲኒማ ገባን፣
አብረን ናይት ክለብ ሄድን። ለመለዋወጥ ሞከርን። አልቻልንም።
እነሱም ጓደኝነት ተያያዙ፡፡ እንደተሸነፍን ገባን
«ገና የፈረንጆቹን ያህል አልሰለጠንንም ባክህ» አለኝ
«እስከመቸም አንሰለጥንም» አልኩት
ሚስት መለዋወጥ ሲያቅተን ጊዜ ታሪክ ተለዋወጥን፡፡ የኔን
እንዴት እንዳገኘኋት ነገርኩት። እሱም ተራውን ነገረኝ። ታሪኩን
ሲጨርስ፣
“እንድ ቀን ምን ሆንኩ መሰለህ?» አለ «ከእራት በኋላ እቤቴ
እንድንገናኝ ተቃጠርን። የቀጠሮው ሰአት ሲደርስ ቤቴ መሄድ
በጣም አስጠላኝ፡፡ ሴት አጥተው ብቻቸውን የሚያድሩትን ጎረምሶች
በጣም ቀናሁባቸው። ቡና ጠጥተህ' ሲኒማ አምሽተህ ቤትህ
መመለስ፣ ፒጃማህን ለብሰህ ጥቅልል ብለህ ብቻህን መተኛት፤ ይሄ በጣም ትልቅ እድል መስሎ ታየኝ! ገደል ትግባ! አልኩና ሲኒማ
ገባሁ። የጀምስ ቦንድ ፊልም ነበር ያየሁት። ሰለላውን፣ ተኩሱን፣
ቦክሱን፣ ድፍረቱን ከምንም አልቆጠርኩለት። ትልቅ ጉብዝና ሆኖ የታየኝ ምን መሰለህ? ይሄ ጄምስ ቦንድ ያሰኘችውን ሴት ተኝቶ፣ ሲበቃው ዘወር ማለት ነው፤ አለቀ በቃ፡፡ እኔ ግን ከአንዲት ሴት
ዘወር ማለት አቅቶኝ እየቀጠርኳት ሲኒማ እገባለሁ፡፡ ራሴን እንዴት
ናቅኩት!
ስለጀምስ ቦንድ እያሰብኩ ወደ ሊቴ ሄድኩ። አኩርፋ
ኣንደምትቆየኝ ስላወቅኩ፣ የምነግራትን ውሸት እያሰላሰልኩ መኝታዬ ገባሁ:: መብራቱን አበራሁ። እንቅልፍ ተኝታለች። መስኮቱ ላይና ወንበሩ ላይ ሸሚዞቼ፣ ካናቴራዎቼ ሙታንታዎቼ፣ እግር ሹራቦቼ
ታጥበው ተሰጥተዋል። የተሰማኝን ልገልፅልህ አልችልም። እፍረት
ነው ይመስለኛል። ድቅቅ አልኩ፡፡ ተሸነፍኩ ልብሴን አውልቄ አልጋ ውስጥ ስገባ ነቃች። የት ቆየህ
አላለችኝም። ዝም ብላ አቀፈችኝ፡፡ አቤት እንዴት ነው ያሳዘነችኝ
ሳለቅስ ምንም ያህል አልቀረኝም
« በነጋታው ከሷ ጋር ዋልኩ፡፡
ስለሷ ማወቅ ፈለግኩ::
ጠያየቅኳት። ነገረችኝ። ያልደረሰባት ግፍ ያለ አይመስለኝም ማለቴ በወንድና በሴት መካከል የሚደረግ ግፍ፡፡ ባሜሪካን አገር የሚደረገው ነገር አንዳንዴ ከኛ አገር ይብሳል። ባስራ ሁለት ኣመቷ ሶስት ጎረምሶች በግድ ያዟትና ጭኗን ከፍተው ሻማ ጨመሩባት።ይህን ምን ትለዋለህ? እስቲ እንደ ሴት ቢበዷት ምን ቸገራቸው ነበር? ባስራ ሰባት አመቷ ደሞ የታላቅ እህቷ ባል በጉልበት ተኛት፡፡
ይህንንስ ስትነግረኝ አለቀሰች። 'ቆንጆንኳ ብሆን ደስ ብየው ነው፣
አላስችል ብሎት ነው ይባላል። ግን ቆንጆ አይደለሁም። ምኔም ደስ አይልም። እንግዲያው ለምን አዋረደኝ? ክፋትንና ጭቆናን የሚስብ አብሮኝ የተፈጠረ አንድ ነገር አለ መሰለኝ አለች
«እውነት ይህን ምን ትለዋለህ» አለ ሉልሰገድ አንድ ሰካራም
አጎት አላት፡፡ እሱ ደሞ አንድ ቀን በግድ ሊተኛት ሞከረ። ታግላ
አመለጠችው:: ግን መሞከሩ እጅግ ጎዳት፡፡ ምን ትለዋለህ ይህን
አይነት እድል? ከዚህ ሁሉ በኋላ ወንዶችን ጨርሳ መሸሽ ነበረባት።
አሷ ግን ተቃራኒ አደረገች፡፡ ለለመናት ሁሉ መስጠት ጀመረች።
እኔ ለዚህ ማስረጃ ላገኝለት አልችልም፡፡ ግን ምናልባት ለሁሉም መስጠት ያው ለማንም እንዳለመስጠት ይቆጠር እንደሆን?
ብቻ ምን ልበልህ? በጭራሽ አምላክ ያጠቃት ልጅ ናት።
ካወቀኝ ወንዶች ሁሉ አንተ ብቻ ነህ እሰካሁን እንደ ሰው የቆጠርከኝ አለችኝና እንደገና ኣለቀሰች፡፡ አልጋው ግርጌ ተንበረከከችና ጉልበቴን አቅፋ
"if you only knew what it means to me i will never be able to repay you never!” never እያለች እንባዋን አወረደችው።«ለኔ ምን ማለት እንደሆነ ባወቅክ! እስከመቸም ውለታህን ልከፍል አልችልም፣ እስከመቸም!»)
ራቁቷን ተንበርክካ ሳለ፣ ነጭ ገላዋ እንዴት ድቡልቡልና
አስቀያሚ እንደሆነ ታየኝ። በጣም አሳዘነችኝ፡፡ እንደዛ እዝኜ
አላውቅም፡፡ አብሪያት አለቀስኩ»
«ምነው አለቀስክ ? ትወደኛለህ እንዴ?' አለችኝ»
«ምንም ምርጫ አልነበረኝም
«አዎን እወድሻለሁ' አልኳት»
«'ምንም ወፍራም ብሆን?»
«'ምንም ወፍራም ብትሆኚ' »
ምንም ርካሽ ብሆን?»
«ምንም ርካሽ ብትሆኚ። ደሞ ርካሽ አይደለሽም፡፡ ተጠቃሽ
ተበደልሽ እንጂ አንቺ ያጠፋሽው ጥፋት የለም። You are a victim
(«ጥቃት የደረሰብሽ ነሽ»)
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...በካፌ ዶርቢቴል በኩል ሳልፍ ሉልሰገድ ከዚያ ወጣ። ቀይ ፊቱ
ደም ለብሷል። ጉልህ ዓይኖቹ ጉድጓዳቸው ውስጥ ይገላበጣሉ። በጣም ተናዷል።
“ምን ሆንክ?» አልኩት
"ይህን ተካ አስታግስልኝ፣ አለዛ አንድ ቀን እገድለዋለሁ» አለኝ
“ምነው?»
"ባገኘኝ ቁጥር ያበሽቀኛል። ላብድ ነው»
«ለምን ሁለተኛ እንዳታናግረኝ አትለውም?»
የተዘረዘሩ ጥቃቅን ጥርሶቹን በተሸነፈ የንዴት ሳቅ እያሳየኝ
ቢያንስ አስር ጊዜ ብየዋለሁ» አለ ሁለተኛ ያናገርከኝ እንደሆነ፣ ወይ ለፖሊስ እነግራለሁ ወይ እገድልሀለሁ ብዬዋለሁ።
ደጋግሜ ደጋግሜ ነግሬዋለሁ፡፡ ሰድቤዋለሁ»
«ታድያስ?»
በሚቀጥለው ጊዜ ሲያገኘኝ ያነጋግረኛል። ትንሽ ካናገረኝ በኋላ
ያበሽቀኛል»
«አታኮርፈውም?»
«አይገባውማ!»
«አሁን ምን ይሻላል?»
«እኔ 'ንጃ፡፡ ይህን ከተማ ለቅቄ ልሂድ መሰለኝ
እየሳቅኩ «እስከዚያው ና ምን የመሰለ ቢራ ላጠጣህ» አልኩና
ባቡር ጣብያው አጠገብ አንዲት ስም የሌላት ካፌ አለች፣ እዚያ
ወሰድኩት። አንድ ቡና አይነት ቢራ አለ፣ ከስኮትላንድ የሚያስመጡት፡፡ ፀሀይ ላይ ቁጭ እንዳልን እሱን ቀመሰና
«ይህን እንዴት አገኘኸው ባክህን? እኔ ሁለተኛ ሌላ ቢራ
አልቀምስም» አለ። ንዴቱን መርሳት ጀምሯል፡፡ ራሱን እየነቀነቀ
«የተካ ዋና ፕሮብሌሙ ምን መሰለህ?» አለኝ «ጥሩ ልጅ ነው::
ከሰው ጋር ተስማምቶ መኖር ይፈልጋል። ግን በሄደበት ሰውን
እንዳበሸቀ ነው:: ወዶ አይደለም። ፍጥረቱ ነው»
«አውቃለሁ። ረስቼ አማንዳ ስትፈልግህ ነበር»
ዝም አለ። ገባኝ
"የፈረንጅ ሴቶች ሲሰለቹ!» አልኩት
«ያንተም ሰልችታሀለች?» አለኝ
«ፈረንጅ አይደለች?»
«አንተስ አትረባም» አለኝ
«ለምን?»
«ያችን የመሰለች ቆንጆ ምኗ ይሰለቻል? ድምፅዋ ብቻ
ይበቃል። በዛ ሰማያዊ አይኗ እያየችህ ያን ፈገግታ ስትሰጥህ
አንድ ፈገግታ እንደሱ ብታጠጣኝ ችዬ ከሷ አልለይም ነበር። በዚያ
ወፍራም ድምፅዋ ሉ ሃኒ ሉ' ብትለኝ ለዘለዓለም እታሰራለሁ»
«ፈገግታውንም ቁልምጫውንም ትሰጥሀለች ከፈለግክ»
«እንዲህም ብልህ'ኮ፣ ፈገግታውና ቁልምጫው ብቻ አይበቃም»
«አንተ ከፈለግክ ሌላውንም ትሰጥሃለች»
«እሱን ተወው! ካንተ ጋር ፍቅር እንደያዛት ያስታውቃል»
« ይመስልሀል» አልኩት
«ትወድሀለች ስልህ!»
«እሺ ይሁን፡፡ ግን አንዳንዴ ስላንተ ጣል የምታረገው ንግግር
አንተም ጠጋ ብትላት እንደማትሸሽህ ያሳያል»
«አዬ? ምን አለች?»
«አይ፣ እሱን አልነግርህም፡፡ ጠጋ ብትላት ራሷ ትነግርሀለች»
«እውነት እንድወስድልህ ትፈልጋለህ?» አለኝ
«አዎን፡፡ ግን ለሀበሾቹ እንዳትነግር»
«ግድ የለህም። እኔ ምልህ የኔን ሸክም ደሞ እንተ ትንሽ
ብትሸከምልኝ። አውቃለሁ አስቀያሚ ነች። ግን ጠጋ ስትላት የደስ ደስ አላት። ደሞ ከዛች ከቆንጆ ጋር ሰንብትህ ወደዚችኛዋ ስትመጣ
ጥሩ ለውጥ ሳይሆን አይቀርም። ሞክር እስቲ»
“አንተ ሞክር"
Shake on It! (ጨብጠኝ)» አለኝ፡፡ ተጨባበጥን
ትንሽ ቆይቶ፣ ራሱን እየነቀነቀ
«አባቶቻችን አሁን የተባባልነውን ቢሰሙ ምንኛ በናቁን!» አለ
እኔና ሉልሰገድ ሚስቶቻችንን እየያዝን አብረን ሲኒማ ገባን፣
አብረን ናይት ክለብ ሄድን። ለመለዋወጥ ሞከርን። አልቻልንም።
እነሱም ጓደኝነት ተያያዙ፡፡ እንደተሸነፍን ገባን
«ገና የፈረንጆቹን ያህል አልሰለጠንንም ባክህ» አለኝ
«እስከመቸም አንሰለጥንም» አልኩት
ሚስት መለዋወጥ ሲያቅተን ጊዜ ታሪክ ተለዋወጥን፡፡ የኔን
እንዴት እንዳገኘኋት ነገርኩት። እሱም ተራውን ነገረኝ። ታሪኩን
ሲጨርስ፣
“እንድ ቀን ምን ሆንኩ መሰለህ?» አለ «ከእራት በኋላ እቤቴ
እንድንገናኝ ተቃጠርን። የቀጠሮው ሰአት ሲደርስ ቤቴ መሄድ
በጣም አስጠላኝ፡፡ ሴት አጥተው ብቻቸውን የሚያድሩትን ጎረምሶች
በጣም ቀናሁባቸው። ቡና ጠጥተህ' ሲኒማ አምሽተህ ቤትህ
መመለስ፣ ፒጃማህን ለብሰህ ጥቅልል ብለህ ብቻህን መተኛት፤ ይሄ በጣም ትልቅ እድል መስሎ ታየኝ! ገደል ትግባ! አልኩና ሲኒማ
ገባሁ። የጀምስ ቦንድ ፊልም ነበር ያየሁት። ሰለላውን፣ ተኩሱን፣
ቦክሱን፣ ድፍረቱን ከምንም አልቆጠርኩለት። ትልቅ ጉብዝና ሆኖ የታየኝ ምን መሰለህ? ይሄ ጄምስ ቦንድ ያሰኘችውን ሴት ተኝቶ፣ ሲበቃው ዘወር ማለት ነው፤ አለቀ በቃ፡፡ እኔ ግን ከአንዲት ሴት
ዘወር ማለት አቅቶኝ እየቀጠርኳት ሲኒማ እገባለሁ፡፡ ራሴን እንዴት
ናቅኩት!
ስለጀምስ ቦንድ እያሰብኩ ወደ ሊቴ ሄድኩ። አኩርፋ
ኣንደምትቆየኝ ስላወቅኩ፣ የምነግራትን ውሸት እያሰላሰልኩ መኝታዬ ገባሁ:: መብራቱን አበራሁ። እንቅልፍ ተኝታለች። መስኮቱ ላይና ወንበሩ ላይ ሸሚዞቼ፣ ካናቴራዎቼ ሙታንታዎቼ፣ እግር ሹራቦቼ
ታጥበው ተሰጥተዋል። የተሰማኝን ልገልፅልህ አልችልም። እፍረት
ነው ይመስለኛል። ድቅቅ አልኩ፡፡ ተሸነፍኩ ልብሴን አውልቄ አልጋ ውስጥ ስገባ ነቃች። የት ቆየህ
አላለችኝም። ዝም ብላ አቀፈችኝ፡፡ አቤት እንዴት ነው ያሳዘነችኝ
ሳለቅስ ምንም ያህል አልቀረኝም
« በነጋታው ከሷ ጋር ዋልኩ፡፡
ስለሷ ማወቅ ፈለግኩ::
ጠያየቅኳት። ነገረችኝ። ያልደረሰባት ግፍ ያለ አይመስለኝም ማለቴ በወንድና በሴት መካከል የሚደረግ ግፍ፡፡ ባሜሪካን አገር የሚደረገው ነገር አንዳንዴ ከኛ አገር ይብሳል። ባስራ ሁለት ኣመቷ ሶስት ጎረምሶች በግድ ያዟትና ጭኗን ከፍተው ሻማ ጨመሩባት።ይህን ምን ትለዋለህ? እስቲ እንደ ሴት ቢበዷት ምን ቸገራቸው ነበር? ባስራ ሰባት አመቷ ደሞ የታላቅ እህቷ ባል በጉልበት ተኛት፡፡
ይህንንስ ስትነግረኝ አለቀሰች። 'ቆንጆንኳ ብሆን ደስ ብየው ነው፣
አላስችል ብሎት ነው ይባላል። ግን ቆንጆ አይደለሁም። ምኔም ደስ አይልም። እንግዲያው ለምን አዋረደኝ? ክፋትንና ጭቆናን የሚስብ አብሮኝ የተፈጠረ አንድ ነገር አለ መሰለኝ አለች
«እውነት ይህን ምን ትለዋለህ» አለ ሉልሰገድ አንድ ሰካራም
አጎት አላት፡፡ እሱ ደሞ አንድ ቀን በግድ ሊተኛት ሞከረ። ታግላ
አመለጠችው:: ግን መሞከሩ እጅግ ጎዳት፡፡ ምን ትለዋለህ ይህን
አይነት እድል? ከዚህ ሁሉ በኋላ ወንዶችን ጨርሳ መሸሽ ነበረባት።
አሷ ግን ተቃራኒ አደረገች፡፡ ለለመናት ሁሉ መስጠት ጀመረች።
እኔ ለዚህ ማስረጃ ላገኝለት አልችልም፡፡ ግን ምናልባት ለሁሉም መስጠት ያው ለማንም እንዳለመስጠት ይቆጠር እንደሆን?
ብቻ ምን ልበልህ? በጭራሽ አምላክ ያጠቃት ልጅ ናት።
ካወቀኝ ወንዶች ሁሉ አንተ ብቻ ነህ እሰካሁን እንደ ሰው የቆጠርከኝ አለችኝና እንደገና ኣለቀሰች፡፡ አልጋው ግርጌ ተንበረከከችና ጉልበቴን አቅፋ
"if you only knew what it means to me i will never be able to repay you never!” never እያለች እንባዋን አወረደችው።«ለኔ ምን ማለት እንደሆነ ባወቅክ! እስከመቸም ውለታህን ልከፍል አልችልም፣ እስከመቸም!»)
ራቁቷን ተንበርክካ ሳለ፣ ነጭ ገላዋ እንዴት ድቡልቡልና
አስቀያሚ እንደሆነ ታየኝ። በጣም አሳዘነችኝ፡፡ እንደዛ እዝኜ
አላውቅም፡፡ አብሪያት አለቀስኩ»
«ምነው አለቀስክ ? ትወደኛለህ እንዴ?' አለችኝ»
«ምንም ምርጫ አልነበረኝም
«አዎን እወድሻለሁ' አልኳት»
«'ምንም ወፍራም ብሆን?»
«'ምንም ወፍራም ብትሆኚ' »
ምንም ርካሽ ብሆን?»
«ምንም ርካሽ ብትሆኚ። ደሞ ርካሽ አይደለሽም፡፡ ተጠቃሽ
ተበደልሽ እንጂ አንቺ ያጠፋሽው ጥፋት የለም። You are a victim
(«ጥቃት የደረሰብሽ ነሽ»)
👍26😢2🤔1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከዚያ ቤት የነበረ ሰው ሁሉ እንቅልፍ ወሰደው::
እኩለ ሌሊት ላይ ዣን ቫልዣ ነቃ::
ዣን ቫልዣ ገጠሬ ሲሆን የተወለደው ብሬ በመባል ከታወቀ ደሃ ቤተሰብ ነው። በልጅነቱ ትምህርት ቤት ገብቶ የመማር እድል ባለማግኘቱ መሐይም ነው ከአደገ በኋላ ከተማ ውስጥ በአትክልተኝነት ሥራ ጀመረ
ዣን ቫልዣ በተፈጥሮው ለሰው አሳቢ እንጂ አዛኝ አልነበረም፡፡ ቤተሰቦቹ በልጅነቱ ነው የሞቱት:: እናቱ የሞቱት ታምመው ሲሆን አባቱ ከዛፍ ላይ ወድቀው ነው:: አባቱም እንደ እርሱ አትክልተኛ ስለነበሩ ዛፍ ለመከርከም
ከትልቅ ዛፍ ላይ ወጥተው ሳለ በድንገት ወድቀው ነው ሕይወታቸው ያለፈው:: ከቤተሰቡ መካከል በሕይወት የቀረች ከእርሱ ሌላ አንዲት እህት
ነበረችው:: የእህቱ ባል ሰባት ልጆች ጥሎባት ይጠፋል፡፡ ዣን ቫልዣን ያስጠጋችው እህቱ ስትሆን ባልዋ እስከጠፋ ድረስ ተንከባክባ ነበር ያሳደገችው::
ባልዬው ሲሞት የትልቁ ልጃቸው እድሜ ስምንት ዓመት ሲሆን የመጨረሻው ልጅ እድሜ አንድ ዐመት ነበር፡፡ ዣን ቫልዣ በዚያን ጊዜ 25 ዓመቱ ነበር::
እርሱ በተራው የልጆቹን አባት ተክቶ እህቱንና ልጆችዋን ይረዳ ጀመር::የወጣትነት ዘመኑን አዳጋችና አድካሚ ግን ብዙ ገቢ በማያስገኝ ሥራ ላይ ነበር ያሳለፈው:: በጊዜ ማጣትና ድኅነት ምክንያት በአፍላ ዘመኑ የከንፈር ወዳጅ እንኳን አልነበረውም:: እንዲያውም ከነአካቴው ለፍቅር ጊዜ
አልነበረውም ማለት ይቻላል፡፡
ማታ ማታ ከመሸ በኋላ ከቤቱ ተመልሶ ቃል ሳይናገር ያገኘውን
ይበላል፡፡ አንዳንድ ቀን ያቸን የምስኪን እራቱን ሲበላ እህቱ ከቀረበለት ምግብ ጥቂቱን እንደገና እየወሰደች ለልጆችዋ ትሰጥበታለች:: ይህ ሲሆን
በረጅም ፀጉሩ ፊቱን ሸፍኖ በዝምታ የተረፈችውን ይበላል:: ምንም ነገር እንዳልሆነ በመቁጠር ራሱን ለማታለል ይሞክራል:: ምርጫም አልነበረውም::
ዛፍ በሚገረዝበት ወራት በቀን እስከ 18 ሱስ ያገኛል:: ሥራ ሳይመርጥ ያገኘውን ይሠራል። እህቱም ትሠራለች:: ቢሆንም ራሳቸውን ያልቻለ ሰባት ልጆችን ማሳደግ ቀላል አልነበረም:: ገንዘቡ ስላልበቃቸው ቤተሰቡ
ችግር ቀስ በቀስ እያለ የሚያሳድደው አሳዛኝ ቤተሰብ ሆነ
የአንድ ዘመን ክረምት በጣም የከፋ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ዣን ቫልዣ ሥራ አ፣ልነበረውም:: በዚህ የተነሣ ቤተሰቡ የሚላስ ወይም የሚቀመስ ነገር ያጣል:: አንድ ቀን እሑድ ማታ የአንድ ዳቦ መጋገሪያ ቤት ባለቤት ሊተኛ ሲል የዳቦ ቤቱ መስታወት ሲሰበር ይሰማል፡፡ የሰውዬው መኖሪያ ቅጥር
ግቢው ውስጥ ስለነበር በጊዜ በመድረሱ በተሰበረወ መስታወት በኩል አንድ ሰው እጁን አሾልኮ ዳቦ ሲሰርቅ ያየዋል:: ሌባው ዳቦውን ይዞ ሮጠ፡፡የዳቦ ቤቱ መስታወት የሰበረው በቡጢ ስለነበር እጁ ይደማል:: ስለዚህ
ዳቦው የተወሰደው በሌባ ለመሆነ ሌላ ማስረጃ አላስፈለገም:: ሌባ
ሰውዬ ዣን ቫልገ ነበር፡፡
ይህ የሆነው በ1795 ዓ.ም መጨረሻ ነው:: ዣን ቫልዣ የተዘጋ ቤት ጨለማን ተገን በማድረግ ሰብሮ ለመስረቅ በመሞከሩ «ወንጀለኛ ነው» ተብሎ ተፈረደበት:: ብያኔው ለአምስት ዓመታት በባርነት የመርከብ ቀዛፊ
ሆኖ እንዲሠራ ነበር፡፡
ዣን ቫልዣ አንገቱ በብረት ሰንሰለት ታስሮ ቱሉን ወደተባለ እስር
ቤት ተወሰደ:: ጉዞው ሃያ ሰባት ቀን ወሰደበት፡፡ የተጓዘው በእንስሳ በሚጎተት ጋሪ ነበር፡፡ ከተወሰነለት ሥፍራ እንደደረሰ ጥብቆ አለበሱት:: ያለፈው ታሪኩ ፤ ስሙ እንኳን ሳይቀር ተለወጠ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ስሙ ዣን ቫልዣ ሳይሆን ቁጥር 24 ሺህ 601 ሆነ::
ከዚያ በኋላ እህቱ ምን ሆነች? ሰባት ልጆችዋስ ምን ደረሱ? ስለዚህ ጉዳይ ራሱን ያስጨነቀ አልነበረም:: ጥቂት የዛፍ ቅርንጫፎች ከትልቅ ዛፍ
ግንድ ሲቆረጥ ማነው ስለቅርንጫፎቹ የሚጨነቀው?
አራተኛ ዓመቱን ሲያገባድድ ዣን ቫልዣ ከእስር ቤት አምልጦ
ነፃነቱን የማግኘት እድል አጋጠመው:: ከእንደዚያ ባለ አስፈሪ ቦታ ያለ ሰዎች ዘወትር እንደሚተባበሩ ሁሉ የእርሱም የሥራ ጓደኞች ረድተውት
አመለጠ፡፡ ለሁለት ቀናት በየጥሻውና በእርሻ ቦታ እየተሽሎከሎከ ቆየ፡፡
በሁለተኛው ቀን ግን ወደማታ እንደገና ተያዘ፡፡ ለ36 ሰዓት ያህል እህል አልቀመሰም:: እንቅልፍም አልተኛም:: ለማምለጥ በመሞከሩ የእሥራት ዘመኑን በሦስት ዓመት ፍርድ ቤቱ አራዘመበት:: በጠቅላላው ስምንት ዓመት ሆነበት ማለት ነው:: በስድስተኛው ዓመት እንደገና ለማምለጥ
ሞክሮ ሳይሳካለት ቀረ:: ማታ ስም ሲጠራ 'አቤት' ሳይል በመቅረቱ
ጥሩምባ ተነፋ፡፡ ማታውኑ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ከመርከብ ስር ተሸሽጎ አገኙት፡፡ ዘበኛው ሊይዘው ሲል ተናነቀው፡፡ ወንጀሉ እጥፍ ሆነ፡፡ ለማምለጥ
በመሞከሩና ዘበኛ በመተናነቁ ለዚህ ጥፋቱ አምስት ዓመት ተፈረደበት::
አሥራ ሦስት ዓመት ሆነ፡፡ በአሥረኛው ዓመት እንደገና ለማምለጥ ሞክሮ አሁንም ሳይሳካለት ቀረ:: ለዚህም ሙከራው ሦስት ዓመት ተፈረደበት::አሥራ ስድስት ዓመት! በመጨረሻም በአሥራ ሦስተኛ ዓመቱ ይመስለኛል
እንደገና ለማምለጥ ሙከራ አድርጎ ከአራት ሰዓት በኋላ እንደገና ተያዘ፡፡
ለአራት ሰዓት ከእስር ቤት በመጥፋቱ አሁንም አራት ዐመት ተፈረደበት:: ሃያ ዓመት! ዳቦ በመሰረቁ ከእስር ቤት የገባው በ1796 ዓ.ም ሲሆን ከአሥራ
ዘጠኝ ዓመት እሥራት በኋላ ግን ለማምለጥ ቻለ፡፡
መርከብ ቀዛፊዎች ከሚታሰሩበት ሲገባ እየተንቀጠቀጠና እያለቀሰ
ነበር:: ያን ሥፍራ ሲለቅ ግን ልቡ ደንድኖ ነበር የወጣው:: ከዚያ ሲገባ ተስፋ ቆርጦ ነበር የገባው፧ ሲወጣ ግን ተስፋ ቢስ ብቻ ሳይሆን ጨካኝም ሆኖ ነው የወጣው::
ታዲያ የዚህ ነፍስ ሕይወት ምን ይሆን!
ታሪኩን ለማውሳት እንሞክር እስቲ፡፡ የሰውዬው ችግር በሕብረተሰቡ የተፈጠረ ስለሆነ ይኸው ሕብረተሰብ እነዚህን ነገሮች አጢኖ መመልከት
ይኖርበታል፡፡
ቀደም ሲል እንዳልነው ዣን ቫልዣ አላዋቂ ነው:: ግን ደደብ አይደለም:: በተፈጥሮው ጭምት ነው:: ሰንኳላው እድሉ ደግሞ በይበልጥ እንዲጨምትና
እንዲያስተውል ገፋፍቶታል፡፡ ሲገረፍ፤ በሰንሰለት ሲጠፈር፤ ጨለማ ቤት ሲታሰር ሰውነቱ በድካም ብዛት ዝሏል፡፡ የሌሊት ቁር ሲያቆራምደው፤ የቀን ፀሐይ ሲያወራጨው፤ እንዲሁም ከእንጨት ላይ ተኝቶ ዘወትር
ከአሳብ ውስጥ እየዋኘ ከኅሊናው ጋር ሲሟገት የኖረ ሰው ነው::
ራሱን እንደ ፍርድ ቤት ስለቆጠረ ምርመራውን በመጀመሪያ ከራሱ
ይጀምራል:: ያለ አግባብ የተቀጣ የዋህና ቀና ሰው አለመሆኑን ኅሊናው ያውቃል:: ሕገ ወጥ ተግባር መፈጸሙን አይክድም፡፡ ምናልባት ያንን አንድ ዳቦ ቢለምን ኖሮ አይነፈግም ነበር ይሆናል፡፡ አዛኝ ወይም አሠሪ እስኪያገኝ
ድረስ ደግሞ መታገስ ነበረበት፡፡ ለእነዚያ የትም በትኖአቸው ለቀረው ምስኪኖችም ይኸው ይበጅ ነበር፡፡ ስለዚህ የፈጸመው ተግባር የሞኝ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ አንድ አርቆ ለማየት የማይችል ድሃ ዓለምን በጉልበት
አሸንፋለሁ ብሉ ቢጋፈጥ ወይም ችግሮችን በሌብነት እወጣለሁ ብሎ ቢታለል ስህተተኛነቱን ገሃድ ያወጣል፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከዚያ ቤት የነበረ ሰው ሁሉ እንቅልፍ ወሰደው::
እኩለ ሌሊት ላይ ዣን ቫልዣ ነቃ::
ዣን ቫልዣ ገጠሬ ሲሆን የተወለደው ብሬ በመባል ከታወቀ ደሃ ቤተሰብ ነው። በልጅነቱ ትምህርት ቤት ገብቶ የመማር እድል ባለማግኘቱ መሐይም ነው ከአደገ በኋላ ከተማ ውስጥ በአትክልተኝነት ሥራ ጀመረ
ዣን ቫልዣ በተፈጥሮው ለሰው አሳቢ እንጂ አዛኝ አልነበረም፡፡ ቤተሰቦቹ በልጅነቱ ነው የሞቱት:: እናቱ የሞቱት ታምመው ሲሆን አባቱ ከዛፍ ላይ ወድቀው ነው:: አባቱም እንደ እርሱ አትክልተኛ ስለነበሩ ዛፍ ለመከርከም
ከትልቅ ዛፍ ላይ ወጥተው ሳለ በድንገት ወድቀው ነው ሕይወታቸው ያለፈው:: ከቤተሰቡ መካከል በሕይወት የቀረች ከእርሱ ሌላ አንዲት እህት
ነበረችው:: የእህቱ ባል ሰባት ልጆች ጥሎባት ይጠፋል፡፡ ዣን ቫልዣን ያስጠጋችው እህቱ ስትሆን ባልዋ እስከጠፋ ድረስ ተንከባክባ ነበር ያሳደገችው::
ባልዬው ሲሞት የትልቁ ልጃቸው እድሜ ስምንት ዓመት ሲሆን የመጨረሻው ልጅ እድሜ አንድ ዐመት ነበር፡፡ ዣን ቫልዣ በዚያን ጊዜ 25 ዓመቱ ነበር::
እርሱ በተራው የልጆቹን አባት ተክቶ እህቱንና ልጆችዋን ይረዳ ጀመር::የወጣትነት ዘመኑን አዳጋችና አድካሚ ግን ብዙ ገቢ በማያስገኝ ሥራ ላይ ነበር ያሳለፈው:: በጊዜ ማጣትና ድኅነት ምክንያት በአፍላ ዘመኑ የከንፈር ወዳጅ እንኳን አልነበረውም:: እንዲያውም ከነአካቴው ለፍቅር ጊዜ
አልነበረውም ማለት ይቻላል፡፡
ማታ ማታ ከመሸ በኋላ ከቤቱ ተመልሶ ቃል ሳይናገር ያገኘውን
ይበላል፡፡ አንዳንድ ቀን ያቸን የምስኪን እራቱን ሲበላ እህቱ ከቀረበለት ምግብ ጥቂቱን እንደገና እየወሰደች ለልጆችዋ ትሰጥበታለች:: ይህ ሲሆን
በረጅም ፀጉሩ ፊቱን ሸፍኖ በዝምታ የተረፈችውን ይበላል:: ምንም ነገር እንዳልሆነ በመቁጠር ራሱን ለማታለል ይሞክራል:: ምርጫም አልነበረውም::
ዛፍ በሚገረዝበት ወራት በቀን እስከ 18 ሱስ ያገኛል:: ሥራ ሳይመርጥ ያገኘውን ይሠራል። እህቱም ትሠራለች:: ቢሆንም ራሳቸውን ያልቻለ ሰባት ልጆችን ማሳደግ ቀላል አልነበረም:: ገንዘቡ ስላልበቃቸው ቤተሰቡ
ችግር ቀስ በቀስ እያለ የሚያሳድደው አሳዛኝ ቤተሰብ ሆነ
የአንድ ዘመን ክረምት በጣም የከፋ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ዣን ቫልዣ ሥራ አ፣ልነበረውም:: በዚህ የተነሣ ቤተሰቡ የሚላስ ወይም የሚቀመስ ነገር ያጣል:: አንድ ቀን እሑድ ማታ የአንድ ዳቦ መጋገሪያ ቤት ባለቤት ሊተኛ ሲል የዳቦ ቤቱ መስታወት ሲሰበር ይሰማል፡፡ የሰውዬው መኖሪያ ቅጥር
ግቢው ውስጥ ስለነበር በጊዜ በመድረሱ በተሰበረወ መስታወት በኩል አንድ ሰው እጁን አሾልኮ ዳቦ ሲሰርቅ ያየዋል:: ሌባው ዳቦውን ይዞ ሮጠ፡፡የዳቦ ቤቱ መስታወት የሰበረው በቡጢ ስለነበር እጁ ይደማል:: ስለዚህ
ዳቦው የተወሰደው በሌባ ለመሆነ ሌላ ማስረጃ አላስፈለገም:: ሌባ
ሰውዬ ዣን ቫልገ ነበር፡፡
ይህ የሆነው በ1795 ዓ.ም መጨረሻ ነው:: ዣን ቫልዣ የተዘጋ ቤት ጨለማን ተገን በማድረግ ሰብሮ ለመስረቅ በመሞከሩ «ወንጀለኛ ነው» ተብሎ ተፈረደበት:: ብያኔው ለአምስት ዓመታት በባርነት የመርከብ ቀዛፊ
ሆኖ እንዲሠራ ነበር፡፡
ዣን ቫልዣ አንገቱ በብረት ሰንሰለት ታስሮ ቱሉን ወደተባለ እስር
ቤት ተወሰደ:: ጉዞው ሃያ ሰባት ቀን ወሰደበት፡፡ የተጓዘው በእንስሳ በሚጎተት ጋሪ ነበር፡፡ ከተወሰነለት ሥፍራ እንደደረሰ ጥብቆ አለበሱት:: ያለፈው ታሪኩ ፤ ስሙ እንኳን ሳይቀር ተለወጠ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ስሙ ዣን ቫልዣ ሳይሆን ቁጥር 24 ሺህ 601 ሆነ::
ከዚያ በኋላ እህቱ ምን ሆነች? ሰባት ልጆችዋስ ምን ደረሱ? ስለዚህ ጉዳይ ራሱን ያስጨነቀ አልነበረም:: ጥቂት የዛፍ ቅርንጫፎች ከትልቅ ዛፍ
ግንድ ሲቆረጥ ማነው ስለቅርንጫፎቹ የሚጨነቀው?
አራተኛ ዓመቱን ሲያገባድድ ዣን ቫልዣ ከእስር ቤት አምልጦ
ነፃነቱን የማግኘት እድል አጋጠመው:: ከእንደዚያ ባለ አስፈሪ ቦታ ያለ ሰዎች ዘወትር እንደሚተባበሩ ሁሉ የእርሱም የሥራ ጓደኞች ረድተውት
አመለጠ፡፡ ለሁለት ቀናት በየጥሻውና በእርሻ ቦታ እየተሽሎከሎከ ቆየ፡፡
በሁለተኛው ቀን ግን ወደማታ እንደገና ተያዘ፡፡ ለ36 ሰዓት ያህል እህል አልቀመሰም:: እንቅልፍም አልተኛም:: ለማምለጥ በመሞከሩ የእሥራት ዘመኑን በሦስት ዓመት ፍርድ ቤቱ አራዘመበት:: በጠቅላላው ስምንት ዓመት ሆነበት ማለት ነው:: በስድስተኛው ዓመት እንደገና ለማምለጥ
ሞክሮ ሳይሳካለት ቀረ:: ማታ ስም ሲጠራ 'አቤት' ሳይል በመቅረቱ
ጥሩምባ ተነፋ፡፡ ማታውኑ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ከመርከብ ስር ተሸሽጎ አገኙት፡፡ ዘበኛው ሊይዘው ሲል ተናነቀው፡፡ ወንጀሉ እጥፍ ሆነ፡፡ ለማምለጥ
በመሞከሩና ዘበኛ በመተናነቁ ለዚህ ጥፋቱ አምስት ዓመት ተፈረደበት::
አሥራ ሦስት ዓመት ሆነ፡፡ በአሥረኛው ዓመት እንደገና ለማምለጥ ሞክሮ አሁንም ሳይሳካለት ቀረ:: ለዚህም ሙከራው ሦስት ዓመት ተፈረደበት::አሥራ ስድስት ዓመት! በመጨረሻም በአሥራ ሦስተኛ ዓመቱ ይመስለኛል
እንደገና ለማምለጥ ሙከራ አድርጎ ከአራት ሰዓት በኋላ እንደገና ተያዘ፡፡
ለአራት ሰዓት ከእስር ቤት በመጥፋቱ አሁንም አራት ዐመት ተፈረደበት:: ሃያ ዓመት! ዳቦ በመሰረቁ ከእስር ቤት የገባው በ1796 ዓ.ም ሲሆን ከአሥራ
ዘጠኝ ዓመት እሥራት በኋላ ግን ለማምለጥ ቻለ፡፡
መርከብ ቀዛፊዎች ከሚታሰሩበት ሲገባ እየተንቀጠቀጠና እያለቀሰ
ነበር:: ያን ሥፍራ ሲለቅ ግን ልቡ ደንድኖ ነበር የወጣው:: ከዚያ ሲገባ ተስፋ ቆርጦ ነበር የገባው፧ ሲወጣ ግን ተስፋ ቢስ ብቻ ሳይሆን ጨካኝም ሆኖ ነው የወጣው::
ታዲያ የዚህ ነፍስ ሕይወት ምን ይሆን!
ታሪኩን ለማውሳት እንሞክር እስቲ፡፡ የሰውዬው ችግር በሕብረተሰቡ የተፈጠረ ስለሆነ ይኸው ሕብረተሰብ እነዚህን ነገሮች አጢኖ መመልከት
ይኖርበታል፡፡
ቀደም ሲል እንዳልነው ዣን ቫልዣ አላዋቂ ነው:: ግን ደደብ አይደለም:: በተፈጥሮው ጭምት ነው:: ሰንኳላው እድሉ ደግሞ በይበልጥ እንዲጨምትና
እንዲያስተውል ገፋፍቶታል፡፡ ሲገረፍ፤ በሰንሰለት ሲጠፈር፤ ጨለማ ቤት ሲታሰር ሰውነቱ በድካም ብዛት ዝሏል፡፡ የሌሊት ቁር ሲያቆራምደው፤ የቀን ፀሐይ ሲያወራጨው፤ እንዲሁም ከእንጨት ላይ ተኝቶ ዘወትር
ከአሳብ ውስጥ እየዋኘ ከኅሊናው ጋር ሲሟገት የኖረ ሰው ነው::
ራሱን እንደ ፍርድ ቤት ስለቆጠረ ምርመራውን በመጀመሪያ ከራሱ
ይጀምራል:: ያለ አግባብ የተቀጣ የዋህና ቀና ሰው አለመሆኑን ኅሊናው ያውቃል:: ሕገ ወጥ ተግባር መፈጸሙን አይክድም፡፡ ምናልባት ያንን አንድ ዳቦ ቢለምን ኖሮ አይነፈግም ነበር ይሆናል፡፡ አዛኝ ወይም አሠሪ እስኪያገኝ
ድረስ ደግሞ መታገስ ነበረበት፡፡ ለእነዚያ የትም በትኖአቸው ለቀረው ምስኪኖችም ይኸው ይበጅ ነበር፡፡ ስለዚህ የፈጸመው ተግባር የሞኝ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ አንድ አርቆ ለማየት የማይችል ድሃ ዓለምን በጉልበት
አሸንፋለሁ ብሉ ቢጋፈጥ ወይም ችግሮችን በሌብነት እወጣለሁ ብሎ ቢታለል ስህተተኛነቱን ገሃድ ያወጣል፡፡
👍21❤3
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...“ሃያ ሳምንት!” አልሁኝ፣ ከአፋቸው ነጥቄ፡፡ ሳይታወቀኝ ደረቅ ቁጣ አንቆኛል፡፡ በእኔም ብሶ ደግሞ እንደ አሮጌ ቆርቆሮ ነው የጮህኩት። “ሃያ ሳምንት ከአራት ቀን!” አልኋቸው፣ የባሰ እየተንኳኳሁ። የባልቻ ያላ
ኃጢአቱ መጠርጠር ሁሉ ግድ አልሰጠኝም። ወንበሩን ወደ ኋላ
አሽቀነጠርሁና፣ እየተቆናጠርሁ ወደ በሩ ሄድሁኝ፡፡ በሩን በኃይል በርግጄ ከከፈትሁ በኋላ፣ ግው አድርጌ ዘግቼባቸው ወጣሁ። ምን እየሆንሁ እንደሆነ እንኳን እነሱ ለኔም አልታወቀኝም፡፡
መኪናዬ ዉስጥ ገብቼ እንዴት አድርጌ በየት በኩል እንደ ነዳሁት
አላስታውሰውም፡፡ እንዲሁ ብዥ እንዳለብኝ ወደ ራሴ ቤት የሚወስድ በመሰለኝ መንገድ የእውር ድንብሬን እያሽከረከርሁ ነበር፡፡ ገና ትንሽ እንደ ነዳሁ፣ ሁሉም ነገር ሰለቸኝ፡፡ ጠነባኝ፡፡
ይበልጥ ድቅድቅ ብሎ ጨለመብኝ፡፡ እንደ ምንም ዳር ይዤ አረፍ አልሁና ወደ ልቡናዬ
ለመመለስ ረዥም ጸሎት አደረስሁ፡፡ ሻል እንዳለኝ፣ የተሻለ ቦታ ተከሰተልኝ፡፡ የእናቴ ቤት!
የመኪናዬን መሪ በግራ በኩል ጠመዘዝሁት እና ወደ እመዋ ቤት
የሚወስደዉን መንገድ ተያያዝሁት። እግዚአብሔር ከክፉ አደጋ ጠብቆኝ በደህና ደረስሁ እንጂ፣ አኳኋኔ እንኳን አያድርስ ነበር። ወደ እመዋ ቤት ደርሼ ስገባ ግን ማንንም አላገኘሁም፡፡ ባዶዉ ቤት ሊዉጠኝ አፉን አ ብሎ
ከፍቶ ጠበቀኝ፡፡ ይኼ ሰፊ ቤት አሁንም አሁንም እንባዉን እስከማዉቅለት ድረስ አዛጋብኝ፡፡ እንደ ገና ደግሞ ሊያስገባኝ የቀፈፈውም መሰለኝ፡፡ እንደ
ምንም ወደ ዉስጥ ብዘልቅም፣ በዚህ ቀትር እንደ እኩለ ሌሊት ነው የጨላለመብኝ፡፡ እግሬን እየጎተትሁ ግራ ቀኝ ከተቅበዘበዝሁ በኋላ፤
ለሳሎኑ ወደሚቀርበዉ ክፍል ገብቼ አልጋዉ ላይ ወደቅሁበት።
ጥቅልል ብዬ መተኛት ነበር የሚሻለኝ፡፡ እንቅልፍ ግን ከየት አባቱ ይምጣልኝ? ነገሩ ሁሉ ተደበላልቆብኛል፡፡ እህል የሚባል ለመጨረሻ ጊዜ የቀመስሁት ትናንትና ማታ ነው:: ግን አሁንም አልራበኝም። ለነገሩ፣ እንደ ሥራዬ ቢሆንማ፣ እንኳንስ እመዋ ቤት ይቅርና እመዋ የረገጠችው
አፈር ላይ እንኳን የመተኛት ሞራሉ የለኝም፡፡ በዚያም ላይ ይኼ አልጋ
ጠዋት ከእመዋ ጋር በታዕካ ነገሥት ገዳም ቆይቼ ስወጣ መንገዴ ላይ ቆመዉ እህቱ አይደለችም ብለዉ የተወራረዱበት፣ የወንድሜ የጃሪም አልጋ ነዉ።
ሁሉንም ነገር ማፈር ጀምሬያለሁ።
የአባቴ ነፍስ እንዴት ትጠየፈኝ ይሆን? የየዋኋ እናቴ አምላክስ እንዴት ይጠላኝ ይሆን? እያልሁ ተበጠበጥሁ። ይኼ አልበቃ ብሎኝ፣ ከአንድ መቶ አርባ አራት ቀናት በፊት የተፈጠረው ነገር ሁሉ በዓይነ ኅሊናዬ እየተመላለሰ ዕረፍት የሚባል ነገር ከለከለኝ፡፡ ላለማስታወስ ከራሴ ጋር
ብዙ ብቦቃቀስም፣ አለማስታወስ ግን አልቻልሁም፡፡ ዕለቷ ከነቅጽበቷ ሳትቀር መጥታ የሚከብድ ጥላዋን ጥላብኝ ዓይነ ልቡናዬ ላይ ቁጭ አለችብኝ፡፡
ትዝ አለኝ።
ዕለቷ እሁድ ነበረች። በዚያች ዕለት፣ አመሻሽ ላይ እንደ ልማዴ ክራሬን ይዤ ወደ አንድ ምዕራባዊ የአዲስ አበባ ዳገታማ ሥፍራ ላይ ወጥቻለሁ። ልክ እንደ ሁልጊዜው፣ ከሚወዱኝ የቀረ ሰው አልነበረም። ጠይም ወይ ቀይ፣ ያገባ ወይ ያላገባ፣ ወንድ ወይ ሴት፣ የወለደ ወይ ያልወለደ፣ አማኝ
ወይ ከሃዲ ሳይቀር ግልብጥ ብሎ ከቦኛል። አንዳንዱ መልኬ ጠርቶት፣ አንዳንዱ ድምፄ ናፍቆት፣ አንዳንዱ ደግሞ ሌላ ሰው ተከትሎ መጥቷል። አለባበሴም ፀሐያማ ነበር።
አስታዉሳለሁ።
ዉቧ ጀንበር ሄድሁ ሄድሁ ብላለች፡፡
ሲጀመር ለፀሐይ ምንም አይወጣላት። ለኔ ደግሞ ምንም ሲሆን፣ ከዚህ ሰዓት ሌላ ዉበቷ ደምቆ አይታየኝም። በአድማሱ ላይ እግሮቿን ከፋፍታ፣ ደልቀቅ ብላ የምትታየኝ ሲመሻሽ ብቻ ነው፡፡ ነፃነቷስ! ራሷን ወደ ታች
በምድር ላይ፣ እግሯን ደግሞ ወደ ላይ በሰማዩ ትሰቅለዋለች። መዘቅዘቋን ተከትሎ፣ ስስ ፀሐያማ ቀሚሷ ገለብ ቢልም፣ ሐፍረተ እንትኗን ግን አናይባትም፡፡ የእኔን ጉጉት እያየች ነዉ መሰለኝ፣ ፈገግ ትልብኛለች።ፈገግታዋ ደግሞ በማንም ቆዳ ላይ አይደርስም፡፡ ይኼ ራሷ ለራሷ የሰጠችው የፍስሐ ጊዜዋ ይመስለኛል። ባትሞት ትታመም፣ ሥጋ
የሚባል ግን አይኖራት ይሆን?
በዚሁ ዕለትም ከጀንበሯ ፈገግታ ፊት ለፊት ሆኜ የግራ እጆቼን ጣቶች በክራሬ አዉታሮች ላይ ዘርግቻለሁ። ከዚያም ምዕራብ ምዕራቡን እያየሁ፣
ለስለስ አድርጌ መግረፍ ጀመርሁ።
ደገኛዉ መጽሐፍ
ባሪያዎችህም ጭምር፣
ኢትዮጵያን ይሏታል
ጌታ ያንተ ሀገር።
እንግዲያዉ ጌታዬ፤
አልሟገትህም
ሀገሬን ወደ ጫፍ ሲገፉት ብትል ዝም፣
ባገርህ ነኝና ካንተ አይብስብኝም።
ድምፄን ጨመር አድርጌ እንደ ገና አንጎራጎርሁ።
ጌታ በናትህ መልሰው፣
እረ ጌታ በማርያም መልሰው
የጀግናዬ ን ልብ እንደ ሰው።
ይኼንን ብዬ፣ ያለ ልማዴ እንደ አጋጣሚ ቀና ብል፣ ከመካከላቸው አንድ ወጣት ሹልክ ብሎ ሲሄድ አየሁት። የከበበኝን ሰዉ ሁሉ ከምንም ሳልቆጥር በረቃቅሼዉ ብድግ ብዬ ተከተልሁት። ይኼን ልጅ ነው ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ
ነፍስ የተያየሁት፡፡ ይኼን ልጅ
እስከማውቀው ድረስ ዕለት በዕለት የምቆጨው መነኩሴ ባለመሆኔ ነበር።በተለይም ልጅ እያለሁ ካህኑን አባቴን ተከትዬ ለመሳለም ወደ ገዳም በምሄድ ጊዜ፣ ለደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡ ከዛሬ ነገ ገዳም ገብቼ በአመክሮ እጀምራለሁ እያልሁ ቀን እቆጥራለሁ። አባቴ እና እናቴ እንኳን ከእኔ የሕይወት መስመር በቀር የሚያከራክራቸው ጉዳይ መኖሩን አላዉቅም። አባቴ ሁልጊዜም ቢሆን ዉብርስቴ መንኩሳ እስከ እመምኔትነት ደርሳ ሳታሳየኝ አልሙት» የሚል ነበር ጸሎቱ ሁሉ። እናቴ ደግሞ በተቃራኒዉ ልጄ ማለፊያ ትዳር ገብታ ዓይኗን በዓይኗ ሳታሳየኝ
አትግደለኝ ባይ ናት። እንዲያዉ ድከሙ ቢላቸዉ ነዉ እንጂ፣ እመዋ ሆኖላት አባቴን እንዴትም ብላ ብታሳምነዉ እንኳን፣ የእኔ ዝንባሌ ግን የአባቴ ምርጫ ነበር። እማሆይነት። ቢሆንልኝ ብዬ የምመኘዉን የምንኩስና ስም ሁሉ ለራሴ አዉጥቼ አዉቃለሁ። አብዝቼ የተለማመድሁት ሕይወትም ምንኩስናን ነዉ። እጅግ በጣም የምቀናባቸው ሰዎች፣ በአርምሞ ዉስጥ ያሉ መነኮሳት ብቻ ናቸዉ።
በሕልሜም በዉኔም የሚታየኝ ብቸኛ ቦታ በጽዶች እና በዝግባዎች የተከበበ ጸጥ ያለ ገዳም ነበር።
ይኼን ልጅ ካወቅሁት በኋላ፣ ሕልሜን በሌላ ሕልም አስለወጠኝ። እሸቴ
ይባላል።
እሸቴ!
ቆዳው ሞኛሞኝ፣ አእምሮው ግን እሳታማ የሆነለት ልጅ ነው። ወይ
ጭንቅላት! አወይ መታደል! ባልወደው ነበር የሚደንቀኝ። አነጋገሩ የጅል፣ ንግግሩ ግን የንጉሥ የሆነለት ልጅ ነዉ። እንኳን እሱ እናቱም ጭምር ለልብ የሚደርሱ የሙቀት ወንዛወንዝ ናቸው።
ጭልጥ አልሁለታ!
በዚሁ በሲራክ-፯ ጀማሪ አባል ሳለሁ፣ የመጀመሪያ ተልእኮ የተሰጠኝ የእሸቴ ጉዳይ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም ስሙን እና ዝናውን በሩቁ ከመስማት በቀር ትውውቁ አልነበረንም። ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁትም ያኔ የእሱን ጉዳይ ተልእኮዬ አድርጌ የተቀበልሁ ጊዜ ነው። በዚያን ጊዜ እሱ የአዲስ አበባ ኑሮ በአፍንጫዬ ይውጣ ብሎ፤ የት ይደርስበታል
የሚባልበትን የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን እርግፍ አድርጎ ጥሎት አልዩ አምባ ወደምትባል ጥንታዊት ትንሽ ከተማ ከሸክላ ሠሪ እናቱ ጋር መኖር ጀምሯል፡፡ ሲራክ-፯ ደግሞ የእሸቴን የአእምሮ ያውቀዋልና፤ ይኼን የመሰለ ልጅ ባክኖ ከሚቀር ልጠቀምበት ብሎ ወሰነ።
የእኔ ተልእኮም እሱን ለሲራክ፯ አባልነት መመልመል እና ማብቃት
ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...“ሃያ ሳምንት!” አልሁኝ፣ ከአፋቸው ነጥቄ፡፡ ሳይታወቀኝ ደረቅ ቁጣ አንቆኛል፡፡ በእኔም ብሶ ደግሞ እንደ አሮጌ ቆርቆሮ ነው የጮህኩት። “ሃያ ሳምንት ከአራት ቀን!” አልኋቸው፣ የባሰ እየተንኳኳሁ። የባልቻ ያላ
ኃጢአቱ መጠርጠር ሁሉ ግድ አልሰጠኝም። ወንበሩን ወደ ኋላ
አሽቀነጠርሁና፣ እየተቆናጠርሁ ወደ በሩ ሄድሁኝ፡፡ በሩን በኃይል በርግጄ ከከፈትሁ በኋላ፣ ግው አድርጌ ዘግቼባቸው ወጣሁ። ምን እየሆንሁ እንደሆነ እንኳን እነሱ ለኔም አልታወቀኝም፡፡
መኪናዬ ዉስጥ ገብቼ እንዴት አድርጌ በየት በኩል እንደ ነዳሁት
አላስታውሰውም፡፡ እንዲሁ ብዥ እንዳለብኝ ወደ ራሴ ቤት የሚወስድ በመሰለኝ መንገድ የእውር ድንብሬን እያሽከረከርሁ ነበር፡፡ ገና ትንሽ እንደ ነዳሁ፣ ሁሉም ነገር ሰለቸኝ፡፡ ጠነባኝ፡፡
ይበልጥ ድቅድቅ ብሎ ጨለመብኝ፡፡ እንደ ምንም ዳር ይዤ አረፍ አልሁና ወደ ልቡናዬ
ለመመለስ ረዥም ጸሎት አደረስሁ፡፡ ሻል እንዳለኝ፣ የተሻለ ቦታ ተከሰተልኝ፡፡ የእናቴ ቤት!
የመኪናዬን መሪ በግራ በኩል ጠመዘዝሁት እና ወደ እመዋ ቤት
የሚወስደዉን መንገድ ተያያዝሁት። እግዚአብሔር ከክፉ አደጋ ጠብቆኝ በደህና ደረስሁ እንጂ፣ አኳኋኔ እንኳን አያድርስ ነበር። ወደ እመዋ ቤት ደርሼ ስገባ ግን ማንንም አላገኘሁም፡፡ ባዶዉ ቤት ሊዉጠኝ አፉን አ ብሎ
ከፍቶ ጠበቀኝ፡፡ ይኼ ሰፊ ቤት አሁንም አሁንም እንባዉን እስከማዉቅለት ድረስ አዛጋብኝ፡፡ እንደ ገና ደግሞ ሊያስገባኝ የቀፈፈውም መሰለኝ፡፡ እንደ
ምንም ወደ ዉስጥ ብዘልቅም፣ በዚህ ቀትር እንደ እኩለ ሌሊት ነው የጨላለመብኝ፡፡ እግሬን እየጎተትሁ ግራ ቀኝ ከተቅበዘበዝሁ በኋላ፤
ለሳሎኑ ወደሚቀርበዉ ክፍል ገብቼ አልጋዉ ላይ ወደቅሁበት።
ጥቅልል ብዬ መተኛት ነበር የሚሻለኝ፡፡ እንቅልፍ ግን ከየት አባቱ ይምጣልኝ? ነገሩ ሁሉ ተደበላልቆብኛል፡፡ እህል የሚባል ለመጨረሻ ጊዜ የቀመስሁት ትናንትና ማታ ነው:: ግን አሁንም አልራበኝም። ለነገሩ፣ እንደ ሥራዬ ቢሆንማ፣ እንኳንስ እመዋ ቤት ይቅርና እመዋ የረገጠችው
አፈር ላይ እንኳን የመተኛት ሞራሉ የለኝም፡፡ በዚያም ላይ ይኼ አልጋ
ጠዋት ከእመዋ ጋር በታዕካ ነገሥት ገዳም ቆይቼ ስወጣ መንገዴ ላይ ቆመዉ እህቱ አይደለችም ብለዉ የተወራረዱበት፣ የወንድሜ የጃሪም አልጋ ነዉ።
ሁሉንም ነገር ማፈር ጀምሬያለሁ።
የአባቴ ነፍስ እንዴት ትጠየፈኝ ይሆን? የየዋኋ እናቴ አምላክስ እንዴት ይጠላኝ ይሆን? እያልሁ ተበጠበጥሁ። ይኼ አልበቃ ብሎኝ፣ ከአንድ መቶ አርባ አራት ቀናት በፊት የተፈጠረው ነገር ሁሉ በዓይነ ኅሊናዬ እየተመላለሰ ዕረፍት የሚባል ነገር ከለከለኝ፡፡ ላለማስታወስ ከራሴ ጋር
ብዙ ብቦቃቀስም፣ አለማስታወስ ግን አልቻልሁም፡፡ ዕለቷ ከነቅጽበቷ ሳትቀር መጥታ የሚከብድ ጥላዋን ጥላብኝ ዓይነ ልቡናዬ ላይ ቁጭ አለችብኝ፡፡
ትዝ አለኝ።
ዕለቷ እሁድ ነበረች። በዚያች ዕለት፣ አመሻሽ ላይ እንደ ልማዴ ክራሬን ይዤ ወደ አንድ ምዕራባዊ የአዲስ አበባ ዳገታማ ሥፍራ ላይ ወጥቻለሁ። ልክ እንደ ሁልጊዜው፣ ከሚወዱኝ የቀረ ሰው አልነበረም። ጠይም ወይ ቀይ፣ ያገባ ወይ ያላገባ፣ ወንድ ወይ ሴት፣ የወለደ ወይ ያልወለደ፣ አማኝ
ወይ ከሃዲ ሳይቀር ግልብጥ ብሎ ከቦኛል። አንዳንዱ መልኬ ጠርቶት፣ አንዳንዱ ድምፄ ናፍቆት፣ አንዳንዱ ደግሞ ሌላ ሰው ተከትሎ መጥቷል። አለባበሴም ፀሐያማ ነበር።
አስታዉሳለሁ።
ዉቧ ጀንበር ሄድሁ ሄድሁ ብላለች፡፡
ሲጀመር ለፀሐይ ምንም አይወጣላት። ለኔ ደግሞ ምንም ሲሆን፣ ከዚህ ሰዓት ሌላ ዉበቷ ደምቆ አይታየኝም። በአድማሱ ላይ እግሮቿን ከፋፍታ፣ ደልቀቅ ብላ የምትታየኝ ሲመሻሽ ብቻ ነው፡፡ ነፃነቷስ! ራሷን ወደ ታች
በምድር ላይ፣ እግሯን ደግሞ ወደ ላይ በሰማዩ ትሰቅለዋለች። መዘቅዘቋን ተከትሎ፣ ስስ ፀሐያማ ቀሚሷ ገለብ ቢልም፣ ሐፍረተ እንትኗን ግን አናይባትም፡፡ የእኔን ጉጉት እያየች ነዉ መሰለኝ፣ ፈገግ ትልብኛለች።ፈገግታዋ ደግሞ በማንም ቆዳ ላይ አይደርስም፡፡ ይኼ ራሷ ለራሷ የሰጠችው የፍስሐ ጊዜዋ ይመስለኛል። ባትሞት ትታመም፣ ሥጋ
የሚባል ግን አይኖራት ይሆን?
በዚሁ ዕለትም ከጀንበሯ ፈገግታ ፊት ለፊት ሆኜ የግራ እጆቼን ጣቶች በክራሬ አዉታሮች ላይ ዘርግቻለሁ። ከዚያም ምዕራብ ምዕራቡን እያየሁ፣
ለስለስ አድርጌ መግረፍ ጀመርሁ።
ደገኛዉ መጽሐፍ
ባሪያዎችህም ጭምር፣
ኢትዮጵያን ይሏታል
ጌታ ያንተ ሀገር።
እንግዲያዉ ጌታዬ፤
አልሟገትህም
ሀገሬን ወደ ጫፍ ሲገፉት ብትል ዝም፣
ባገርህ ነኝና ካንተ አይብስብኝም።
ድምፄን ጨመር አድርጌ እንደ ገና አንጎራጎርሁ።
ጌታ በናትህ መልሰው፣
እረ ጌታ በማርያም መልሰው
የጀግናዬ ን ልብ እንደ ሰው።
ይኼንን ብዬ፣ ያለ ልማዴ እንደ አጋጣሚ ቀና ብል፣ ከመካከላቸው አንድ ወጣት ሹልክ ብሎ ሲሄድ አየሁት። የከበበኝን ሰዉ ሁሉ ከምንም ሳልቆጥር በረቃቅሼዉ ብድግ ብዬ ተከተልሁት። ይኼን ልጅ ነው ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ
ነፍስ የተያየሁት፡፡ ይኼን ልጅ
እስከማውቀው ድረስ ዕለት በዕለት የምቆጨው መነኩሴ ባለመሆኔ ነበር።በተለይም ልጅ እያለሁ ካህኑን አባቴን ተከትዬ ለመሳለም ወደ ገዳም በምሄድ ጊዜ፣ ለደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡ ከዛሬ ነገ ገዳም ገብቼ በአመክሮ እጀምራለሁ እያልሁ ቀን እቆጥራለሁ። አባቴ እና እናቴ እንኳን ከእኔ የሕይወት መስመር በቀር የሚያከራክራቸው ጉዳይ መኖሩን አላዉቅም። አባቴ ሁልጊዜም ቢሆን ዉብርስቴ መንኩሳ እስከ እመምኔትነት ደርሳ ሳታሳየኝ አልሙት» የሚል ነበር ጸሎቱ ሁሉ። እናቴ ደግሞ በተቃራኒዉ ልጄ ማለፊያ ትዳር ገብታ ዓይኗን በዓይኗ ሳታሳየኝ
አትግደለኝ ባይ ናት። እንዲያዉ ድከሙ ቢላቸዉ ነዉ እንጂ፣ እመዋ ሆኖላት አባቴን እንዴትም ብላ ብታሳምነዉ እንኳን፣ የእኔ ዝንባሌ ግን የአባቴ ምርጫ ነበር። እማሆይነት። ቢሆንልኝ ብዬ የምመኘዉን የምንኩስና ስም ሁሉ ለራሴ አዉጥቼ አዉቃለሁ። አብዝቼ የተለማመድሁት ሕይወትም ምንኩስናን ነዉ። እጅግ በጣም የምቀናባቸው ሰዎች፣ በአርምሞ ዉስጥ ያሉ መነኮሳት ብቻ ናቸዉ።
በሕልሜም በዉኔም የሚታየኝ ብቸኛ ቦታ በጽዶች እና በዝግባዎች የተከበበ ጸጥ ያለ ገዳም ነበር።
ይኼን ልጅ ካወቅሁት በኋላ፣ ሕልሜን በሌላ ሕልም አስለወጠኝ። እሸቴ
ይባላል።
እሸቴ!
ቆዳው ሞኛሞኝ፣ አእምሮው ግን እሳታማ የሆነለት ልጅ ነው። ወይ
ጭንቅላት! አወይ መታደል! ባልወደው ነበር የሚደንቀኝ። አነጋገሩ የጅል፣ ንግግሩ ግን የንጉሥ የሆነለት ልጅ ነዉ። እንኳን እሱ እናቱም ጭምር ለልብ የሚደርሱ የሙቀት ወንዛወንዝ ናቸው።
ጭልጥ አልሁለታ!
በዚሁ በሲራክ-፯ ጀማሪ አባል ሳለሁ፣ የመጀመሪያ ተልእኮ የተሰጠኝ የእሸቴ ጉዳይ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም ስሙን እና ዝናውን በሩቁ ከመስማት በቀር ትውውቁ አልነበረንም። ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁትም ያኔ የእሱን ጉዳይ ተልእኮዬ አድርጌ የተቀበልሁ ጊዜ ነው። በዚያን ጊዜ እሱ የአዲስ አበባ ኑሮ በአፍንጫዬ ይውጣ ብሎ፤ የት ይደርስበታል
የሚባልበትን የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን እርግፍ አድርጎ ጥሎት አልዩ አምባ ወደምትባል ጥንታዊት ትንሽ ከተማ ከሸክላ ሠሪ እናቱ ጋር መኖር ጀምሯል፡፡ ሲራክ-፯ ደግሞ የእሸቴን የአእምሮ ያውቀዋልና፤ ይኼን የመሰለ ልጅ ባክኖ ከሚቀር ልጠቀምበት ብሎ ወሰነ።
የእኔ ተልእኮም እሱን ለሲራክ፯ አባልነት መመልመል እና ማብቃት
ነበር።
👍27❤2😁1
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
..እውነትም ገራሚ ልጅ አይደለም? ገና ስሙን ነግሮኝ እየተዋወቀኝ ለመስለው ለእኔ ያለ ሐፍረት እንዲህ ከመሀሉ ጀምሮ መናዘዙ አይገርምም? ቅሌቴ የሚለዉን ነገር የመናገሪያ አመጣዉ? እንዴት ሆነለት? በጣም ደነቀኝ፡፡ እኔ እሱን ብሆንስ?አይደለም ለሌላ ሰው ልነግረው ይቅርና፣ ራሴንም እንደማልክደው እርግጠኛ አይደለሁም። እሸቴ የተለየ ሰዉ መሆኑን አመንሁ። ገራገር ነው። በዚያም ላይ በግልጽነቱ ላይ ወሰን አጣሁበት። ይኼን ሰው
ከማድነቅ በቀር አማራጭ የለኝም።
“ስለ ለምንድን ነው ግን የነገርሁሽ?” አለ፣ እንደ ማፈርም እንደ መሳቅም ብሎ።
“እንጃ” አልሁት፣ ባይነግረኝ እንደማለቅስ እያወቅሁት። በእኔ ቤት ለእሱ ግድ የሌለኝ መምሰሌ ነዉ። ዉሸት! ለምን ሆነና ስንትና ስንት ኪሎ ሜትሮች አቆራርጬ፣ እዚህ አልዩ አምባ የመጣሁት? ለእሱ ብዬ እኮ ነዉ። የገዛ ታሪኩን ከራሱ አፍ ለመስማት፡፡ ደካማ ጎኑን ለማወቅና የሲራክ ፯ አባል ለማድረግ ነዉ እዚህ ድረስ መምጫ ምክንያቴ፡፡ ቢሆንም
ግን እንደማዉቀዉ ሊያዉቅብኝ አይገባም፡፡ ስለዚህ የባሰ ፊት ነሳሁት።
“ቅቅቅቅቅቅ ቅሌታም ነኝ አይደል?”
“ነህ እንዴ?”
“ይኼን ያወቁ የግቢ ልጆች ምን ብለው ቅጽል ስም እንዳወጡልኝ
ታዉቂያለሽ?”
“ግቢ...?” አልሁት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኮምፒዉተር ሳይንስ
ተማሪ እንደነበር ጠንቅቄ የማላውቅ ይመስል። እንኳንስ ይቺን፣ ስለሚያዘወትረዉ የካልሲ ቀለም ሳይቀር ተነግሮኛል። ግቢ ነበርህ እንዴ?” አልሁት አሁንም፣ ስለሱ ምንም እንደማላዉቅ መስየ።
“አዎ”
“እሺ፣ ምን አሉህ?”
“ዎዎዎዎ ዎከር”
“ዎከር?”
«ሂያጅ ማለታቸዉ እንደሆነ። ያያያያ ያው የቀላዋጭ መጠሪያው
እንደዚያ አይደል? እኔ ከዚያ በፊት ለማንም ሐሜት ደንታ የለኝም ባይ
ነበርሁ። ይኸኔ ግን ተሰማኝ። አመመኝ። በጣም አፈርሁ። ራሴን መናቅ ሁሉ ጀመርሁ። ተማሪ አስጠላኝ። አስተማሪ አስጠላኝ። ዩኒቨርስቲ አስጠላኝ። መማር ጠላሁ። በበበ በቃ ሁሉ ነገር ጉሮሮዬ ላይ መጣ።
የጀመርሁትን በጅምር ትቸው ወጣሁ። ከዚያ ሁሉም ነገር በአፍንጫዬ ይውጣ ብዬ ወደ እናቴ መጣሁ እልሻለሁ” አለና፣ ኧሁሁ ብሎ በረዥሙ ሲተነፍስ፣ ወዠቦ ያለፈ ነበር የመሰለኝ። ቅዝዝ ብዬ አየሁት፡፡ አዘንሁለት። ሰነባብቼ እንዲያዉም ሲራክ፤ ከሰጠኝ ተልእኮዬ ጎን ለጎን
ለእሱ ማዘኑንም ለራሴ እየደረብሁበት መጣሁ፡፡ ይባስ ብዬ ራሴን ሳታልለው ደግሞ «እሸቴ እኮ የእኔ እርዳታ ያስፈልገዋል ማለት ጀመርሁ። አዝኜ ሞትኋ! እኔ ማነኝና ለእሽቴ አዝናለሁ? ዉሽት።
የምንኩስና ምኞቴን የሚያስረሳ ቦታ በልቤ ዉስጥ ጠርጌ ማስረከቤን ላለማመን የፈጠርኋት መሸንገያዬ ናት። መከጀሌን ከውርደት ብቆጥረው
እንጂ አሸንፎኛል። በቃ ገዳም የሚለዉ የልጅነት ምኞቴ ቀረና ትዳር ያሰኘኝ ጀመር። መነኩሴነት ቀረ እና ሚስትነት በዓይን በዓይኔ ዞረ። በእርግጥ እሱ ብቻ ሳይሆን እኔም አሸንፌዋለሁ። ማኅበሩን ጨምሮ ጠላሁት ያለውን ነገር ሁሉ አስወድጀዋለሁ። ልክ እንደ ተላክሁት ሄጄ አምጥቼዋለሁ። ማምጣት ብቻ ሳይሆን የሲራክ-፯ አባል ማድረግ ችያለሁ። ያዉም ተራ ሳይሆን፣ እንደ ዓይን የሚቆጠር መኩሪያ አባል።
ተልእኮዬን በፍጽምና ተወጥቼዋለሁ።
ከዚያ በኋላ አፍ አዉጥተን ፍቅረኛሞች ነን ባንባባልም፣ ያዉ ሆነናል። በበኩሌ ልቤን ሰጥቼዋለሁ፡፡ ስለ እሱ ሞኝነት እና ጉብዝና መስማቱ ሱስ ሆኖብኛል፡፡ እሱም ቢሆን አይቶኝ እና እንጉርጉሮዬን ሰምቶ አይጠግብም፡፡ነገር ግን ገና ማንም ያወቀብን አይመስለኝም፡፡ ምናልባት፣ ባልቻ እና
የእሽቴ እናት ጥርጣሬው ይኖራቸው ይሆናል እንዳይታወቅብን የተለየ ጥንቃቄ አድርገን ሳይሆን እኔ ክራሬን ይዤ
ወደ አደባባይ ስወጣ ብዙ ወጣት ግልብጥ ብሎ እንደሚያጅበኝ የታወቀ በመሆኑ ይመስለኛል
በሲራክ ፯ ማዕከልም ቢሆን ከብዙዎች ጋር ጥሩ ቀረቤታ ስላለን፣ የእሽቱን የተለየ አያስመስለውም። ወይ
እኔን በእንዲህ ያለ ነገር
የሚጠረጥረኝ አይኖር ይሆናል፡፡ በተለይ ቤተሰቦቼ ሴትና ወንድ እንኳ ለይቼ ማወቅ የሚሆንልኝ አይመስላቸዉም፡፡ እንዲያውም አንደኛዋ እህቴን ልነግራት ስሞክር፤ አንቺ እንኳን እንደ እሸቴ ላለ ዘሟች ይቅርና ለጳጳስ ልጅም አትደነግጭት ብላኛለች፡፡ ጳጳስ ልጅ እንደማይወልድ ጠፍቷት ሳይሆን ምን ያህል እኔን በእንዲህ ዓይነት መንገድ
እንደማትገምተኝ ስታሳምነኝ ነው።
አላወቀችኝማ፣ ለእሽቴ ስል የማይተወዉን ሕልሜን እንደ ተዉሁት።
“እኔ ምልህ እሸቴ” አልሁት፣ በዚያች ጎደሎ ምሽት በእኔ ቤት እራት በልተን ከመጨረሳችን። ቀደም ብሎ፣ አመሻሹ ላይ ከጀንበሯ ፊት ክራር ይዤ ሳለሁ፣ እኔን ከብቦ እንጉርጉሮዬን በስስት የሚያዳምጠኝን ሰዉ
ሁሉ ከምንም ሳልቆጥር ረግጬ፤ እሱን ተከትዬዉ ቀጥታ ወደኔ ቤት
ነበር እራት እንብላ ብዬ የወሰድሁት።
“ትናንት” አልሁት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን ለመቅመስ እጄን ወደ
ብርጭቆዉ እየሰደድሁ። አልኮል የሚባል ነገር በአፌ ዞሮ ስለማያውቅ፣ ምን ምን እንደሚል መቅመሱ ሳያጓጓኝ አልቀረም።
“ትትትትት-ትናንት ምን?”
አንድ ነገር ብጠይቅህ ሳትደብቅ ትነግረኛለህ እ?”
“ካካካ ካንቺ መደበቁ ሆኖልኝ እኔ?”
“አዉቃለሁ፣ አትደብቀኝም”
“ስስስ-ስለኔ ላንቺ ምንድነዉ ያልነገርሁሽ ዉቤዋ?”
“ትናንትና በዚህ ሰዓት የት ነበርህ?” አልሁት ዓይን ዓይኑን እያየሁ፣ ቁርጥ አድርጌ፡፡
“ትትትት ትናንትና?” አለ፣ ደም እንደሚጎነጭ ዝግንን ብሎት የወይኑን ብርጭቆ ወደ አፉ እያስጠጋ።
“የት ነበርህ?”
እንደ ትኩስ ቡና በፍራቻ ፉት ያለዉን ወይን በአፉ እንደ ያዘዉ ለረዥም ጊዜ ጣሪያ ጣሪያዉን አየ። እኔም ልቤ ለምላሹ እንደ ተንጠለጠለች፣ በዝምታ ጠበቅሁት። የጠረጠርሁት ነገር አለ። መቼም ዐመል በዋዛ
አይለቅምና፣ ምናልባት ወደ ሴተኛ አዳሪዎች መሄዱን የተወዉ
አልመስልሽ ስላለኝ ነዉ አጠያየቄ፡፡ ቢሆንም፣ ከእሱ ጋር ያለዉን እዉነት መስማት አለብኝ፡፡ እኔን እንደማይዋሸኝ ደግሞ አዉቃለሁ። እንኳንስ እንዲህ እየተቁለጨለጭሁ ጠይቄው ይቅርና፣ ድሮዉንም ግልጽነቱን
ማንም እንደ እሱ አልታደለዉ። የት ነበርሁ ይለኝ ይሆን?
“እእእ አልሆነልኝማ” ብሎኝ አረፈዉ፣ እንባ በዓይኑ ጢም እያለበት፡፡
እንደ ፈራሁት!
“ምን ማለት ነዉ አልሆነልኝም ማለት?”
“በቃ ሄጄ ነበር። እሱን አይደል የምትጠይቂኝ? ትናንትና በዚህ ሠዐት ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ ነበርሁ”
“እኮ ምን ልትሆን!?”
“አአአ አልቻልሁም። ምን ጎትቶ እንደሚወስደኝም አላውቀው። ምኑ ሽዉ እንደሚያደርገኝ ሁሉ እንጃለቴን። ግን ትናንትም ሴተኛ አዳሪዎች ጋ ሄጄ ነበር። አቅቶኛል እኔ”
እየየ ብለን ተላቀስን። እንባዬ እየወረደም ንዴት ተናንቆኛል። እየቆየማ ጥርሴ ሁሉ ተፋጨብኝ። ይኸኔ በንክሻ ብዘለዝለዉ ሁሉ የልቤ አይደርስም። ለንዴቴ ማብረጃ አጣሁለት።
“ደግሞ አታፍርም? ጀብዱ እንደ ፈጸመ ሰዉ ጉድህን ስትናገር ሐፍረት የሚባል የለህም!?”
“ብዋሽሽ የባሰ አታዝኝብኝም ነበር?”
“ዋሽተህ መሞከር ነበራ! ሁልጊዜ አንድ ዓይነት መልስ አያሳፍርህም? ሁልጊዜ ‹አቃተኝ ስትለኝ አታፍርም!? ጨክነዉ ከተዉት እንኳን ዝሙት
ሌላዉስ ይቀር የለም እንዴ!?
ሁልጊዜ አንጀቴን የምትበላው
ይመስልሃል? ቆይ ጅል ነዉ እንዴ የምመስልህ!?”
ሌላ መልስ አጣ። ደግሞ ምናባቱንስ ይመልስልኛል?
“ልንገርህ አይደል? አንተ መቼም አያልፍልህም! መቼም አትለወጥም!”
“አሳፈርሁሽ አይደል?”
“ነገርሁህ። ተንፏቀህ ተልከስክሰህ ትቀራታለህ እንጂ፣ መቼም
አትለወጥም!”
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
..እውነትም ገራሚ ልጅ አይደለም? ገና ስሙን ነግሮኝ እየተዋወቀኝ ለመስለው ለእኔ ያለ ሐፍረት እንዲህ ከመሀሉ ጀምሮ መናዘዙ አይገርምም? ቅሌቴ የሚለዉን ነገር የመናገሪያ አመጣዉ? እንዴት ሆነለት? በጣም ደነቀኝ፡፡ እኔ እሱን ብሆንስ?አይደለም ለሌላ ሰው ልነግረው ይቅርና፣ ራሴንም እንደማልክደው እርግጠኛ አይደለሁም። እሸቴ የተለየ ሰዉ መሆኑን አመንሁ። ገራገር ነው። በዚያም ላይ በግልጽነቱ ላይ ወሰን አጣሁበት። ይኼን ሰው
ከማድነቅ በቀር አማራጭ የለኝም።
“ስለ ለምንድን ነው ግን የነገርሁሽ?” አለ፣ እንደ ማፈርም እንደ መሳቅም ብሎ።
“እንጃ” አልሁት፣ ባይነግረኝ እንደማለቅስ እያወቅሁት። በእኔ ቤት ለእሱ ግድ የሌለኝ መምሰሌ ነዉ። ዉሸት! ለምን ሆነና ስንትና ስንት ኪሎ ሜትሮች አቆራርጬ፣ እዚህ አልዩ አምባ የመጣሁት? ለእሱ ብዬ እኮ ነዉ። የገዛ ታሪኩን ከራሱ አፍ ለመስማት፡፡ ደካማ ጎኑን ለማወቅና የሲራክ ፯ አባል ለማድረግ ነዉ እዚህ ድረስ መምጫ ምክንያቴ፡፡ ቢሆንም
ግን እንደማዉቀዉ ሊያዉቅብኝ አይገባም፡፡ ስለዚህ የባሰ ፊት ነሳሁት።
“ቅቅቅቅቅቅ ቅሌታም ነኝ አይደል?”
“ነህ እንዴ?”
“ይኼን ያወቁ የግቢ ልጆች ምን ብለው ቅጽል ስም እንዳወጡልኝ
ታዉቂያለሽ?”
“ግቢ...?” አልሁት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኮምፒዉተር ሳይንስ
ተማሪ እንደነበር ጠንቅቄ የማላውቅ ይመስል። እንኳንስ ይቺን፣ ስለሚያዘወትረዉ የካልሲ ቀለም ሳይቀር ተነግሮኛል። ግቢ ነበርህ እንዴ?” አልሁት አሁንም፣ ስለሱ ምንም እንደማላዉቅ መስየ።
“አዎ”
“እሺ፣ ምን አሉህ?”
“ዎዎዎዎ ዎከር”
“ዎከር?”
«ሂያጅ ማለታቸዉ እንደሆነ። ያያያያ ያው የቀላዋጭ መጠሪያው
እንደዚያ አይደል? እኔ ከዚያ በፊት ለማንም ሐሜት ደንታ የለኝም ባይ
ነበርሁ። ይኸኔ ግን ተሰማኝ። አመመኝ። በጣም አፈርሁ። ራሴን መናቅ ሁሉ ጀመርሁ። ተማሪ አስጠላኝ። አስተማሪ አስጠላኝ። ዩኒቨርስቲ አስጠላኝ። መማር ጠላሁ። በበበ በቃ ሁሉ ነገር ጉሮሮዬ ላይ መጣ።
የጀመርሁትን በጅምር ትቸው ወጣሁ። ከዚያ ሁሉም ነገር በአፍንጫዬ ይውጣ ብዬ ወደ እናቴ መጣሁ እልሻለሁ” አለና፣ ኧሁሁ ብሎ በረዥሙ ሲተነፍስ፣ ወዠቦ ያለፈ ነበር የመሰለኝ። ቅዝዝ ብዬ አየሁት፡፡ አዘንሁለት። ሰነባብቼ እንዲያዉም ሲራክ፤ ከሰጠኝ ተልእኮዬ ጎን ለጎን
ለእሱ ማዘኑንም ለራሴ እየደረብሁበት መጣሁ፡፡ ይባስ ብዬ ራሴን ሳታልለው ደግሞ «እሸቴ እኮ የእኔ እርዳታ ያስፈልገዋል ማለት ጀመርሁ። አዝኜ ሞትኋ! እኔ ማነኝና ለእሽቴ አዝናለሁ? ዉሽት።
የምንኩስና ምኞቴን የሚያስረሳ ቦታ በልቤ ዉስጥ ጠርጌ ማስረከቤን ላለማመን የፈጠርኋት መሸንገያዬ ናት። መከጀሌን ከውርደት ብቆጥረው
እንጂ አሸንፎኛል። በቃ ገዳም የሚለዉ የልጅነት ምኞቴ ቀረና ትዳር ያሰኘኝ ጀመር። መነኩሴነት ቀረ እና ሚስትነት በዓይን በዓይኔ ዞረ። በእርግጥ እሱ ብቻ ሳይሆን እኔም አሸንፌዋለሁ። ማኅበሩን ጨምሮ ጠላሁት ያለውን ነገር ሁሉ አስወድጀዋለሁ። ልክ እንደ ተላክሁት ሄጄ አምጥቼዋለሁ። ማምጣት ብቻ ሳይሆን የሲራክ-፯ አባል ማድረግ ችያለሁ። ያዉም ተራ ሳይሆን፣ እንደ ዓይን የሚቆጠር መኩሪያ አባል።
ተልእኮዬን በፍጽምና ተወጥቼዋለሁ።
ከዚያ በኋላ አፍ አዉጥተን ፍቅረኛሞች ነን ባንባባልም፣ ያዉ ሆነናል። በበኩሌ ልቤን ሰጥቼዋለሁ፡፡ ስለ እሱ ሞኝነት እና ጉብዝና መስማቱ ሱስ ሆኖብኛል፡፡ እሱም ቢሆን አይቶኝ እና እንጉርጉሮዬን ሰምቶ አይጠግብም፡፡ነገር ግን ገና ማንም ያወቀብን አይመስለኝም፡፡ ምናልባት፣ ባልቻ እና
የእሽቴ እናት ጥርጣሬው ይኖራቸው ይሆናል እንዳይታወቅብን የተለየ ጥንቃቄ አድርገን ሳይሆን እኔ ክራሬን ይዤ
ወደ አደባባይ ስወጣ ብዙ ወጣት ግልብጥ ብሎ እንደሚያጅበኝ የታወቀ በመሆኑ ይመስለኛል
በሲራክ ፯ ማዕከልም ቢሆን ከብዙዎች ጋር ጥሩ ቀረቤታ ስላለን፣ የእሽቱን የተለየ አያስመስለውም። ወይ
እኔን በእንዲህ ያለ ነገር
የሚጠረጥረኝ አይኖር ይሆናል፡፡ በተለይ ቤተሰቦቼ ሴትና ወንድ እንኳ ለይቼ ማወቅ የሚሆንልኝ አይመስላቸዉም፡፡ እንዲያውም አንደኛዋ እህቴን ልነግራት ስሞክር፤ አንቺ እንኳን እንደ እሸቴ ላለ ዘሟች ይቅርና ለጳጳስ ልጅም አትደነግጭት ብላኛለች፡፡ ጳጳስ ልጅ እንደማይወልድ ጠፍቷት ሳይሆን ምን ያህል እኔን በእንዲህ ዓይነት መንገድ
እንደማትገምተኝ ስታሳምነኝ ነው።
አላወቀችኝማ፣ ለእሽቴ ስል የማይተወዉን ሕልሜን እንደ ተዉሁት።
“እኔ ምልህ እሸቴ” አልሁት፣ በዚያች ጎደሎ ምሽት በእኔ ቤት እራት በልተን ከመጨረሳችን። ቀደም ብሎ፣ አመሻሹ ላይ ከጀንበሯ ፊት ክራር ይዤ ሳለሁ፣ እኔን ከብቦ እንጉርጉሮዬን በስስት የሚያዳምጠኝን ሰዉ
ሁሉ ከምንም ሳልቆጥር ረግጬ፤ እሱን ተከትዬዉ ቀጥታ ወደኔ ቤት
ነበር እራት እንብላ ብዬ የወሰድሁት።
“ትናንት” አልሁት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን ለመቅመስ እጄን ወደ
ብርጭቆዉ እየሰደድሁ። አልኮል የሚባል ነገር በአፌ ዞሮ ስለማያውቅ፣ ምን ምን እንደሚል መቅመሱ ሳያጓጓኝ አልቀረም።
“ትትትትት-ትናንት ምን?”
አንድ ነገር ብጠይቅህ ሳትደብቅ ትነግረኛለህ እ?”
“ካካካ ካንቺ መደበቁ ሆኖልኝ እኔ?”
“አዉቃለሁ፣ አትደብቀኝም”
“ስስስ-ስለኔ ላንቺ ምንድነዉ ያልነገርሁሽ ዉቤዋ?”
“ትናንትና በዚህ ሰዓት የት ነበርህ?” አልሁት ዓይን ዓይኑን እያየሁ፣ ቁርጥ አድርጌ፡፡
“ትትትት ትናንትና?” አለ፣ ደም እንደሚጎነጭ ዝግንን ብሎት የወይኑን ብርጭቆ ወደ አፉ እያስጠጋ።
“የት ነበርህ?”
እንደ ትኩስ ቡና በፍራቻ ፉት ያለዉን ወይን በአፉ እንደ ያዘዉ ለረዥም ጊዜ ጣሪያ ጣሪያዉን አየ። እኔም ልቤ ለምላሹ እንደ ተንጠለጠለች፣ በዝምታ ጠበቅሁት። የጠረጠርሁት ነገር አለ። መቼም ዐመል በዋዛ
አይለቅምና፣ ምናልባት ወደ ሴተኛ አዳሪዎች መሄዱን የተወዉ
አልመስልሽ ስላለኝ ነዉ አጠያየቄ፡፡ ቢሆንም፣ ከእሱ ጋር ያለዉን እዉነት መስማት አለብኝ፡፡ እኔን እንደማይዋሸኝ ደግሞ አዉቃለሁ። እንኳንስ እንዲህ እየተቁለጨለጭሁ ጠይቄው ይቅርና፣ ድሮዉንም ግልጽነቱን
ማንም እንደ እሱ አልታደለዉ። የት ነበርሁ ይለኝ ይሆን?
“እእእ አልሆነልኝማ” ብሎኝ አረፈዉ፣ እንባ በዓይኑ ጢም እያለበት፡፡
እንደ ፈራሁት!
“ምን ማለት ነዉ አልሆነልኝም ማለት?”
“በቃ ሄጄ ነበር። እሱን አይደል የምትጠይቂኝ? ትናንትና በዚህ ሠዐት ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ ነበርሁ”
“እኮ ምን ልትሆን!?”
“አአአ አልቻልሁም። ምን ጎትቶ እንደሚወስደኝም አላውቀው። ምኑ ሽዉ እንደሚያደርገኝ ሁሉ እንጃለቴን። ግን ትናንትም ሴተኛ አዳሪዎች ጋ ሄጄ ነበር። አቅቶኛል እኔ”
እየየ ብለን ተላቀስን። እንባዬ እየወረደም ንዴት ተናንቆኛል። እየቆየማ ጥርሴ ሁሉ ተፋጨብኝ። ይኸኔ በንክሻ ብዘለዝለዉ ሁሉ የልቤ አይደርስም። ለንዴቴ ማብረጃ አጣሁለት።
“ደግሞ አታፍርም? ጀብዱ እንደ ፈጸመ ሰዉ ጉድህን ስትናገር ሐፍረት የሚባል የለህም!?”
“ብዋሽሽ የባሰ አታዝኝብኝም ነበር?”
“ዋሽተህ መሞከር ነበራ! ሁልጊዜ አንድ ዓይነት መልስ አያሳፍርህም? ሁልጊዜ ‹አቃተኝ ስትለኝ አታፍርም!? ጨክነዉ ከተዉት እንኳን ዝሙት
ሌላዉስ ይቀር የለም እንዴ!?
ሁልጊዜ አንጀቴን የምትበላው
ይመስልሃል? ቆይ ጅል ነዉ እንዴ የምመስልህ!?”
ሌላ መልስ አጣ። ደግሞ ምናባቱንስ ይመልስልኛል?
“ልንገርህ አይደል? አንተ መቼም አያልፍልህም! መቼም አትለወጥም!”
“አሳፈርሁሽ አይደል?”
“ነገርሁህ። ተንፏቀህ ተልከስክሰህ ትቀራታለህ እንጂ፣ መቼም
አትለወጥም!”
👍43❤2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
....እኔ እንደተሰማኝ ሊሰማቸው የማይገባ ስለሆነ መንትዮቹ እንዴት እንደሆኑ ለማወቅ ዞሬ ተመለከትኩ።አንድ መልካም ሰው ወደ ወጥ ቤት ወስዷቸው
ከመተኛታቸው በፊት ቀለል ያለ ምግብ እያዘጋጀላቸው ነበር። አይኔ ከክሪስቶፈር አይን ጋር ተጋጨ ልክ እንደኔ በዚህ ቅዠት ውስጥ እንደተያዘ ያስታውቃል። ፊቱ የገረጣና የደነገጠ ይመስላል። አይኖቹ ሀዘን አጥልቶባቸው ጠቁረዋል።
አንደኛው ፖሊስ ወደ መኪናው ተመልሶ የታሰሩ ነገሮች ይዞ መጣና በጥንቃቄ ጠረጴዛ ላይ ዘረገፋቸው አባቴ ኪሱ ውስጥ የሚያስቀምጣቸው ነገሮች
ነበሩ እናታችን ለገና በስጦታ የሰጠችው የኪስ ቦርሳ፣ የማስታወሻ ደብተሩ፣ የእጁን ሰዓትና የጋብቻ ቀለበቱን ስመለከት በቆምኩበት ደረቅኩ። ሁሉም ነገር ጠቁሯል። በጭስና በእሳት አርሯል።
በመጨረሻ የመጡት የመኪናው የእቃ ማስቀመጫ ሲመታ ከሻንጣው ውስጥ የተበተኑት የአባቴ ልብሶችና ለኮሪና ኬሪ የተገዙላቸው ባለቀለም አሻንጉሊቶች ነበሩ። ባለ ቀይ ፊቱ ፖሊስ ሲናገር ሁሉም የተገኙት መንገዱ ላይ ተበትነው ነበር።
እነዚያን ልብሶች አውቃቸዋለሁ: እነዚያን ሸሚዞች፣ ከረባቶችና ካልሲዎች...ሁሉንም አውቃቸዋለሁ ከልብሶቹ መሀል ላለፈው ልደቱ ሰጥቼው የነበረው ከረባት ነበረበት።
“አስከሬኑ የእሱ መሆኑን የሚለይልን አንድ ሰው እንፈልጋለን፡” አለ ፖሊሱ።
አሁን በእርግጠኝነት አወቅኩ እውነት ነው: አባታችን… በራሱ የልደት ቀን እንኳን ሳይቀር ስጦታ ይዞልን የሚመጣው አባታችን ሞቷል!!
ከዚያ ክፍል ሮጬ ወጣሁ! ልቤን ከሚያደሙትና እስከዛሬ ከተሰሙኝ ህመሞች ሁሉ በከፋ ሁኔታ ካሳመሙኝ ከተዘረገፉት ዕቃዎች ሸሽቼ ሮጥኩ። ከቤት
ወጥቼ ከጀርባ ያለው የአትክልት ቦታ ሄድኩና አሮጌውን የማፕል ዛፍ በጡጫ ቀጠቀጥኩት እስኪያመኝና እጄ ደም በደም እስኪሆን ድረስ ቀጠቀጥኩት።
ከዚያ ሳሩ ላይ ዘጭ ብዬ ወድቄ አምርሬ አነባሁ በህይወት መቆየት ይገባው ስለነበረው አባቴ አለቀስኩ። ያለ እርሱ ህይወታችንን ለምንገፋው ለእኛ አነባሁ እናም ምን ያህል መልካም አባት እንደሆነና እንደነበረ የማወቅ
እድል ላላገኙት መንታ እህትና ወንድሜ አለቀስኩ። እምባዬ አልቆ አይኖቼ አብጠው ደም መስለው እየቆጠቆጡኝ ባለሁበት ቅፅበት የእግር ኮቴ ወደኔ ሲመጣ ሰማሁ። እናቴ ነበረች:
ሳሩ ላይ አጠገቤ ተቀመጠችና እጄን በእጆቿ ያዘች ሰማዩ ላይ ግማሽ ጨረቃ በሚሊየን በሚቆጠሩ ከዋክብት ታጅባ ወጥታለች አዲስ ከተወለደው ከፀደዩ ሽታ ጋር ንፋሱ ደስ የሚል ነበር። በመካከላችን የነበረው ዝምታ ማብቂያ የሌለው በሚመስል ሁኔታ ለረጅም ደቂቃዎች ቀጠለ፡ በመጨረሻ እናቴ “ካቲ አባትሽ ከላይ ከሰማይ ሆኖ እያየሽ ነው፡ ጎበዝ እንድትሆኚ እንደሚፈልግ
ታውቂያለሽ አይደል?” አለችኝ።
“አልሞተም እማዬ!” ላለማመን ፈለግኩ።
“እዚህ ቦታ ብዙ ቆይተሻል። ምናልባት አላስተዋልሽ ይሆናል እንጂ አራት ሰዓት ሆኗል። አንድ ሰው የአባትሽን አስከሬን መለየት ነበረበት ለዚህ ደግሞ
ጂም ጆንስተን እንደሚሄድ ነገሮኝ ነበር። እኔ ግን ራሴ ማየት ስፈለግኩ ሄጄ አየሁት። አየሽ እኔም ለማመን ከብዶኝ ነበር አባትሽ ሞቷል ካቲ። ክሪስቶፈር አልጋው ላይ ሆኖ እያለቀሰ ነው፡ መንትዮቹ ተኝተዋል። መሞት
ምን እንደሆነ ገና በደንብ አልገባቸውም:”
አቅፋኝ ጭንቅላቴን ትከሻዋ ላይ አሳረፈችው።
ከዚያ ተነሳችና ከእሷ ጋር እንድነሳ ክንዷን ወገቤ ላይ አድርጋ እየጎተተችኝ “ነይ… እንደዚህ አዝነሽ ብቻሽን መሆንሽ ጥሩ አይደለም: ሀዘንሽን ውስጥሽ
ከምትቀብሪው ይልቅ ሀዘንሽን ከሚጋሩሽ ሰዎች ጋር መሆን የተሻለ ነው:"
ይህንን ስትነግረኝ አንዲት ዘለላ እምባ እንኳን አይኖቿ ላይ አልነበረም ነገር ግን በውስጧ እያለቀሰችና እየጮኸች እንደሆነ ከድምጽዋና አይኖቿ ላይ
ከሚታየው ጥልቅ ሀዘን መናገር ይቻላል።
ከአባታችን ሞት ጋር ተያይዞ ቀኖቻችንን ቅዠት ያጠላባቸው ጀመር᎓ እናቴን ያለማቋረጥ አተኩሬ እያየኋት ለእንደዚህ አይነት ነገር አስቀድማ ልታዘጋጀን
ይገባ እንደነበር አሰብኩ የሆነ ነገር በሞት ማጣት ምን እንደሚመስል
እንድናውቅ የራሳችን የሆነ ውሻ ወይም ድመት እንዲኖረን ፈቅዳልን
አታውቅም ያንን ብታደርግ ኖሮ ድንገት ሲሞቱብን ሞት ምን ማለት
እንደሆነ በጥቂቱም ቢሆን ማወቅ እንችል የነበረ ይመስለኛል የሆነ ሰው፣ትልቅ ስው፣ መልከ መልካሞችም፣ ወጣቶችም፣ በጣም አስፈላጊ ሰዎችም
ሊሞቱ እንደሚችሉ ሊያስጠነቅቀን ይገባ ነበር።
ዕጣ ፋንታ በሆነ ቀዳዳ ውስጥ እየጎተታት ቀጭንና ስስ ላደረጋት እናት እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር ሊባል ይችላል? መናገር ወይም መብላት ወይም ፀጉሯን ማበጠር ወይም ሳጥኗን የሞሉትን የሚያማምሩ ልብሶች መልበስ ለማትፈልግ ሴት እንዴት እንዲህ አይነት ነገር በግልፅ መናገር
ይቻላል? ሌላው ቀርቶ እኛ የሚያስፈልገንን ነገር እንኳ ማየት አትችልም ነበር። ደጋግ የጎረቤቶቻችን ሴቶች መጥተው የሚወስዱን መሆናቸው
ቤታቸው ያዘጋጁትን ምግብ የሚያመጡልን መሆኑ መልካም ሆኖልን ነበር ቤታችንም በአበቦችና ጎረቤቶች ሰርተው በሚያመጡት ምግብ የተሞላ ነበር።
አባታችንን የሚወዱት፣ የሚያደንቁትና የሚያከብሩት ብዙ ሰዎች ሁለ ይመጡ ስለነበር አባታችን ይህን ያህል ታዋቂ በመሆኑ ተገረምኩ። ሆኖም
የሆነ ሰው እንዴት እንደሞተ ጠይቆ ስንት ጥቅም የሌለው መሞት ያለበት ለማህበረሰቡ ሸክም የሆነ ሰው እያለ እንደሱ አይነት ወጣት መሞቱ አሳዛኝ
ነገር እንደሆነ በተናገረ ቁጥር ሞቱ ይበልጥ ያሳምመኝ ነበር።
ከሰማኋቸው ነገሮች የተነሳ ዕጣ ፋንታ የሚባለው ነገር ክፉና ለሚወደድና ለሚፈለግ ሰው እንኳን ክብር የሌለው አሰቃቂ ነገር እንደሆነ አወቅኩ።
የፀደይ ቀናት እያለፉ ወደ በጋ ተጠጋ። ምንም ያህል ለቅሶውን ለማስተናገድ ቢሞhርም ሀዘን እየደበዘዘ የሚመጣበት የራሱ መንገድ አለው። እናም
በህይወት ውስጥ በጣም ተወዳጅ የነበረ ሰው ሳይቀር የደበዘዘና ከትኩረታችን ወጣ ያለ ጥላ እየሆነ ይመጣል።
አንድ ቀን እናታችን ፈገግ ማለት እንዴት እንደሆነ የረሳች በሚመስል ሁኔታ ፊቷ ተከፍቶ ተቀምጣ ነበር ሀዘኗን ላስረሳት በመጣር “እማዬ… አባታችን
በህይወት እንዳለ ቁጠሪውና ለሌላ የስራ ጉዞ እንደሄደና እንደሚመለስ፣ ከዚያ "
በበሩ ገብቶ ልክ ድሮ እንደሚያደርገው ተጣርቶ “የሚወደኝ መጥቶ ይሳመኝ
ሲል አይታይሽም? እማዬ ለሁላችንም እንደዚህ ብናስብ ይሻለናል ሁላችንም የሆነ እኛ የማናየው ቦታ እየኖረ እንደሆነና ድንገት እንደሚመጣ መጠበቅ እንችላለን" አልኳት።
“አይሆንም ካቲ፣ እውነቱን መቀበል አለብሽ፡ በማስመሰል ውስጥ መደበቂያ መፈለግ የለብሽም ሰምተሸኛል? አባትሽ ሞቷል። ነፍሱ ወደ መንግስተሰማይ ሄዳለች እናም በአንቺ እድሜ ማንም ሰው ከሰማይ ተመልሶ እንደማይመጣ
መረዳት አለብሽ፡ እኛ ካለእሱ የምንችለውን እናደርጋለን፡ ያ ማለት ግን እውነታን ባለመጋፈጥ ማምለጥ ማለት አይደለም” አለችኝ በቁጣ።
ከዚያ ከተቀመጠችበት ወንበር ላይ ተነስታ ቁርስ ለመስራት ከማቀዝቀዣው ውስጥ የሆኑ ነገሮች ስታወጣ አየኋት።
እንደገና እንዳትቆጣኝ እየተጠነቀቅኩ “እማዬ ካለሱ የምትችይ ይመስልሻል?
አልኳት።
“በህይወት እንድንቆይ የቻልኩትን ሁሉ አደርጋለሁ” አለች ስሜት በማይሰጥ ድምፅ።
“አሁን እንደ ወይዘሮ ጆንስተን ስራ መሄድ አለብሽ ማለት ነው?”
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
....እኔ እንደተሰማኝ ሊሰማቸው የማይገባ ስለሆነ መንትዮቹ እንዴት እንደሆኑ ለማወቅ ዞሬ ተመለከትኩ።አንድ መልካም ሰው ወደ ወጥ ቤት ወስዷቸው
ከመተኛታቸው በፊት ቀለል ያለ ምግብ እያዘጋጀላቸው ነበር። አይኔ ከክሪስቶፈር አይን ጋር ተጋጨ ልክ እንደኔ በዚህ ቅዠት ውስጥ እንደተያዘ ያስታውቃል። ፊቱ የገረጣና የደነገጠ ይመስላል። አይኖቹ ሀዘን አጥልቶባቸው ጠቁረዋል።
አንደኛው ፖሊስ ወደ መኪናው ተመልሶ የታሰሩ ነገሮች ይዞ መጣና በጥንቃቄ ጠረጴዛ ላይ ዘረገፋቸው አባቴ ኪሱ ውስጥ የሚያስቀምጣቸው ነገሮች
ነበሩ እናታችን ለገና በስጦታ የሰጠችው የኪስ ቦርሳ፣ የማስታወሻ ደብተሩ፣ የእጁን ሰዓትና የጋብቻ ቀለበቱን ስመለከት በቆምኩበት ደረቅኩ። ሁሉም ነገር ጠቁሯል። በጭስና በእሳት አርሯል።
በመጨረሻ የመጡት የመኪናው የእቃ ማስቀመጫ ሲመታ ከሻንጣው ውስጥ የተበተኑት የአባቴ ልብሶችና ለኮሪና ኬሪ የተገዙላቸው ባለቀለም አሻንጉሊቶች ነበሩ። ባለ ቀይ ፊቱ ፖሊስ ሲናገር ሁሉም የተገኙት መንገዱ ላይ ተበትነው ነበር።
እነዚያን ልብሶች አውቃቸዋለሁ: እነዚያን ሸሚዞች፣ ከረባቶችና ካልሲዎች...ሁሉንም አውቃቸዋለሁ ከልብሶቹ መሀል ላለፈው ልደቱ ሰጥቼው የነበረው ከረባት ነበረበት።
“አስከሬኑ የእሱ መሆኑን የሚለይልን አንድ ሰው እንፈልጋለን፡” አለ ፖሊሱ።
አሁን በእርግጠኝነት አወቅኩ እውነት ነው: አባታችን… በራሱ የልደት ቀን እንኳን ሳይቀር ስጦታ ይዞልን የሚመጣው አባታችን ሞቷል!!
ከዚያ ክፍል ሮጬ ወጣሁ! ልቤን ከሚያደሙትና እስከዛሬ ከተሰሙኝ ህመሞች ሁሉ በከፋ ሁኔታ ካሳመሙኝ ከተዘረገፉት ዕቃዎች ሸሽቼ ሮጥኩ። ከቤት
ወጥቼ ከጀርባ ያለው የአትክልት ቦታ ሄድኩና አሮጌውን የማፕል ዛፍ በጡጫ ቀጠቀጥኩት እስኪያመኝና እጄ ደም በደም እስኪሆን ድረስ ቀጠቀጥኩት።
ከዚያ ሳሩ ላይ ዘጭ ብዬ ወድቄ አምርሬ አነባሁ በህይወት መቆየት ይገባው ስለነበረው አባቴ አለቀስኩ። ያለ እርሱ ህይወታችንን ለምንገፋው ለእኛ አነባሁ እናም ምን ያህል መልካም አባት እንደሆነና እንደነበረ የማወቅ
እድል ላላገኙት መንታ እህትና ወንድሜ አለቀስኩ። እምባዬ አልቆ አይኖቼ አብጠው ደም መስለው እየቆጠቆጡኝ ባለሁበት ቅፅበት የእግር ኮቴ ወደኔ ሲመጣ ሰማሁ። እናቴ ነበረች:
ሳሩ ላይ አጠገቤ ተቀመጠችና እጄን በእጆቿ ያዘች ሰማዩ ላይ ግማሽ ጨረቃ በሚሊየን በሚቆጠሩ ከዋክብት ታጅባ ወጥታለች አዲስ ከተወለደው ከፀደዩ ሽታ ጋር ንፋሱ ደስ የሚል ነበር። በመካከላችን የነበረው ዝምታ ማብቂያ የሌለው በሚመስል ሁኔታ ለረጅም ደቂቃዎች ቀጠለ፡ በመጨረሻ እናቴ “ካቲ አባትሽ ከላይ ከሰማይ ሆኖ እያየሽ ነው፡ ጎበዝ እንድትሆኚ እንደሚፈልግ
ታውቂያለሽ አይደል?” አለችኝ።
“አልሞተም እማዬ!” ላለማመን ፈለግኩ።
“እዚህ ቦታ ብዙ ቆይተሻል። ምናልባት አላስተዋልሽ ይሆናል እንጂ አራት ሰዓት ሆኗል። አንድ ሰው የአባትሽን አስከሬን መለየት ነበረበት ለዚህ ደግሞ
ጂም ጆንስተን እንደሚሄድ ነገሮኝ ነበር። እኔ ግን ራሴ ማየት ስፈለግኩ ሄጄ አየሁት። አየሽ እኔም ለማመን ከብዶኝ ነበር አባትሽ ሞቷል ካቲ። ክሪስቶፈር አልጋው ላይ ሆኖ እያለቀሰ ነው፡ መንትዮቹ ተኝተዋል። መሞት
ምን እንደሆነ ገና በደንብ አልገባቸውም:”
አቅፋኝ ጭንቅላቴን ትከሻዋ ላይ አሳረፈችው።
ከዚያ ተነሳችና ከእሷ ጋር እንድነሳ ክንዷን ወገቤ ላይ አድርጋ እየጎተተችኝ “ነይ… እንደዚህ አዝነሽ ብቻሽን መሆንሽ ጥሩ አይደለም: ሀዘንሽን ውስጥሽ
ከምትቀብሪው ይልቅ ሀዘንሽን ከሚጋሩሽ ሰዎች ጋር መሆን የተሻለ ነው:"
ይህንን ስትነግረኝ አንዲት ዘለላ እምባ እንኳን አይኖቿ ላይ አልነበረም ነገር ግን በውስጧ እያለቀሰችና እየጮኸች እንደሆነ ከድምጽዋና አይኖቿ ላይ
ከሚታየው ጥልቅ ሀዘን መናገር ይቻላል።
ከአባታችን ሞት ጋር ተያይዞ ቀኖቻችንን ቅዠት ያጠላባቸው ጀመር᎓ እናቴን ያለማቋረጥ አተኩሬ እያየኋት ለእንደዚህ አይነት ነገር አስቀድማ ልታዘጋጀን
ይገባ እንደነበር አሰብኩ የሆነ ነገር በሞት ማጣት ምን እንደሚመስል
እንድናውቅ የራሳችን የሆነ ውሻ ወይም ድመት እንዲኖረን ፈቅዳልን
አታውቅም ያንን ብታደርግ ኖሮ ድንገት ሲሞቱብን ሞት ምን ማለት
እንደሆነ በጥቂቱም ቢሆን ማወቅ እንችል የነበረ ይመስለኛል የሆነ ሰው፣ትልቅ ስው፣ መልከ መልካሞችም፣ ወጣቶችም፣ በጣም አስፈላጊ ሰዎችም
ሊሞቱ እንደሚችሉ ሊያስጠነቅቀን ይገባ ነበር።
ዕጣ ፋንታ በሆነ ቀዳዳ ውስጥ እየጎተታት ቀጭንና ስስ ላደረጋት እናት እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር ሊባል ይችላል? መናገር ወይም መብላት ወይም ፀጉሯን ማበጠር ወይም ሳጥኗን የሞሉትን የሚያማምሩ ልብሶች መልበስ ለማትፈልግ ሴት እንዴት እንዲህ አይነት ነገር በግልፅ መናገር
ይቻላል? ሌላው ቀርቶ እኛ የሚያስፈልገንን ነገር እንኳ ማየት አትችልም ነበር። ደጋግ የጎረቤቶቻችን ሴቶች መጥተው የሚወስዱን መሆናቸው
ቤታቸው ያዘጋጁትን ምግብ የሚያመጡልን መሆኑ መልካም ሆኖልን ነበር ቤታችንም በአበቦችና ጎረቤቶች ሰርተው በሚያመጡት ምግብ የተሞላ ነበር።
አባታችንን የሚወዱት፣ የሚያደንቁትና የሚያከብሩት ብዙ ሰዎች ሁለ ይመጡ ስለነበር አባታችን ይህን ያህል ታዋቂ በመሆኑ ተገረምኩ። ሆኖም
የሆነ ሰው እንዴት እንደሞተ ጠይቆ ስንት ጥቅም የሌለው መሞት ያለበት ለማህበረሰቡ ሸክም የሆነ ሰው እያለ እንደሱ አይነት ወጣት መሞቱ አሳዛኝ
ነገር እንደሆነ በተናገረ ቁጥር ሞቱ ይበልጥ ያሳምመኝ ነበር።
ከሰማኋቸው ነገሮች የተነሳ ዕጣ ፋንታ የሚባለው ነገር ክፉና ለሚወደድና ለሚፈለግ ሰው እንኳን ክብር የሌለው አሰቃቂ ነገር እንደሆነ አወቅኩ።
የፀደይ ቀናት እያለፉ ወደ በጋ ተጠጋ። ምንም ያህል ለቅሶውን ለማስተናገድ ቢሞhርም ሀዘን እየደበዘዘ የሚመጣበት የራሱ መንገድ አለው። እናም
በህይወት ውስጥ በጣም ተወዳጅ የነበረ ሰው ሳይቀር የደበዘዘና ከትኩረታችን ወጣ ያለ ጥላ እየሆነ ይመጣል።
አንድ ቀን እናታችን ፈገግ ማለት እንዴት እንደሆነ የረሳች በሚመስል ሁኔታ ፊቷ ተከፍቶ ተቀምጣ ነበር ሀዘኗን ላስረሳት በመጣር “እማዬ… አባታችን
በህይወት እንዳለ ቁጠሪውና ለሌላ የስራ ጉዞ እንደሄደና እንደሚመለስ፣ ከዚያ "
በበሩ ገብቶ ልክ ድሮ እንደሚያደርገው ተጣርቶ “የሚወደኝ መጥቶ ይሳመኝ
ሲል አይታይሽም? እማዬ ለሁላችንም እንደዚህ ብናስብ ይሻለናል ሁላችንም የሆነ እኛ የማናየው ቦታ እየኖረ እንደሆነና ድንገት እንደሚመጣ መጠበቅ እንችላለን" አልኳት።
“አይሆንም ካቲ፣ እውነቱን መቀበል አለብሽ፡ በማስመሰል ውስጥ መደበቂያ መፈለግ የለብሽም ሰምተሸኛል? አባትሽ ሞቷል። ነፍሱ ወደ መንግስተሰማይ ሄዳለች እናም በአንቺ እድሜ ማንም ሰው ከሰማይ ተመልሶ እንደማይመጣ
መረዳት አለብሽ፡ እኛ ካለእሱ የምንችለውን እናደርጋለን፡ ያ ማለት ግን እውነታን ባለመጋፈጥ ማምለጥ ማለት አይደለም” አለችኝ በቁጣ።
ከዚያ ከተቀመጠችበት ወንበር ላይ ተነስታ ቁርስ ለመስራት ከማቀዝቀዣው ውስጥ የሆኑ ነገሮች ስታወጣ አየኋት።
እንደገና እንዳትቆጣኝ እየተጠነቀቅኩ “እማዬ ካለሱ የምትችይ ይመስልሻል?
አልኳት።
“በህይወት እንድንቆይ የቻልኩትን ሁሉ አደርጋለሁ” አለች ስሜት በማይሰጥ ድምፅ።
“አሁን እንደ ወይዘሮ ጆንስተን ስራ መሄድ አለብሽ ማለት ነው?”
👍34❤5👏3👎1