አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#በክፍለማርያም

..ፍቃዱ የሚወጣዉን ሰዉ ተመለከተዉ
ፍፁም የጀመረዉን አጋምሶ ፍቃዱ እስካሁን ስለጠፋሁበት ተመልሶ ይሆናል በማለት ለጥቂት ደቂቃ ስለተቀመጠ እግሩን እያስነከሰዉ በክራንቹ እየተመረኮዘ ሰበር ሰካ እያለ ሲወጣ
ፍቃዱ ከቅድሙ ሰዉዬ ጋር ቆሞ እያወራ ፊት ለፊት ተፋጠጡ።

ቤዛዊት በሽታዋ እያገረሸ እየተብከነከነች ብቻዋን እያወራች ወደ ፍፁም ቤት አምርታ አለመኖሩ ስታረጋግጥ አከራዩ ጋር ሄዳ

"የት ነዉ የሄደዉ?"

ለእሳቸዉ የማይጠየቅ ጥያቄ አይኖቿን እያጉረጠረጠች ጠየቀቻቸዉ
"እኔ ምን አዉቃለዉ የሚሄድበትን ነግሮኝ አይሄድ"
ሲሉ አኩዋሀኗ ያላማራቸዉ የፍፁም አከራይ መለሱላት
"እሺ እኔን የምትመስል ቁመት ብቻ የምትበልጠኝ ሴት መጥታ ነበር"
አጉረጠረጠችባቸዉ
የፍፁም ቤት አከራይ በልባቸዉ ምኗ ለካፊ ናት እያሉ
"የኔ እመቤት ማንም የመጣ ሰዉ አላየሁም አቶ ፍፁም ግን ብቻዉን ጠዋት ሲወጣ ተገናኝተን ነበር"
ይህን ሲሏት ትንሽ ተረጋጋች ከእህቴ ጋር ነዉ ስትል የነበረዉን ትታ እየከነፈች ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።

ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ደርሳ ከመግባቷ በፊት ለአፍታ ፍፁምን አሰበችዉ
"የት ሄዶ ይሆን ምን ገጠመዉ"
አይምሮዋ ግን አልተረጋጋም በቆመችበት ቦታ አንፑላንስ ድምፁን እያሰማ በአጠገቧ ሲያልፍ ጩሀቱ ስለቀፈፋት በእጆቿ ጆሮወቿን ደፍና ለደቂቃ ቆመች
መኪናዉ አልፎ ጩሀቱ እየቀነሰ ሲመጣ ተስፋ በመቁረጥ ስሜት አስፓልቱ ዳር ዝርፍጥ ብላ ተቀምጣ በአይኖቿ የፍፁምን መምጣት ትጠባበቃለች።

እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊት መጣሁ ብላ መጥፋት አሳስቧቸዉ ወደ ዉጪ ወጣ ሲሉ መንገድ ዳር ተቀምጣ አይኖቿ ሲንከራተቱ ስላዩዋት ደረታቸዉን እየደቁ እየደገፉ ወደ ቤት ለማስገባት የቤዛዊትን ሰዉነት መጎተት ጀመሩ።

"አይመጣም ቀረ..."

እያለቻቸዉ እየተሳበች እየተጎተተች ተነስታ የእማማ ስንቅነሽን ቀሚስ ጨምድዳ ይዛ እየቆመች
በታመመ አይምሮዋ የቅድሙን ቃል ደገመችላቸዉ

"አይመጣም ቀረ..."

እማማ ስንቅነሽም በዝምታ ወደ ቤት እንድትገባላቸዉ እየጎተቷት
ቅድም ያለፈዉ አንፑላንስ ተመልሶ እየጮሀ አለፈ በአሁኑ ግን ጆሮወቿን አልያዘችም በድንገት ግትር ብላ ቆማ
"ያ ዉ ያዉና መጣ"
የቀኝ እጇን የመጠቆምያ ጣት ወደ ታች ወደሚወርዱ ብዛት ያላቸዉ ሰወች ቀስራ
ፍፁም እያነከሰ በሁለት ፖሊሶች ተከቦ ከጀርባቸዉ ወሬ አድማቂ ሰዉ አጅቦት አንገቱን ደፍቶ እየተራመደ ነዉ መሬት መሬቱን እያየ ሸንከል ሸግከል እያለ ይራመዳል ፖሊሶቹ እንዲፈጥን ኮሌታዉን ይዘዉ ይጎትቱታል
ፍፁምን ካጀቡት ሰወች መሀከል
"ገድሎታል አረ አልሞተም"
እየተባባሉ ይከራከራሉ
ቤዛዊት እማማ ስንቅነሽ እጅ ላይ አይኖቿ ፍዝዝ ብለዉ በድን ሆና ቆማለች መናገር አቁማለች የምትሰማም አትመስልም የአይኖቿ ብሌኖች ብቻ በቀስታ ይንከዋለላሉ።

(ከደቂቃወች በፊት)
ፍፁም ፊት ለፊቱ የቆመዉን ፍቃዱን ሲያየዉ እያዘነ አይቶ እንዳላየዉ መስሎ ሊያልፈዉ ሲል ፍቃዱ ከጀርባዉ ደርሶበት
"የት ለመድረስ ነዉ የምታነክሰዉ"
ይለዋል በንቀት እግር እግሩን እያየ
ፍፁም መልስ ሳይሰጠዉ መራመዱን ሲቀጥል ፍቃዱ ደግሞ ደርሶበት እየሳቀ
"ቤዛዊትን መቼም አታገኛትም የኔ ናት አንተ ዉሻ እያዋራሁክ ደሞ የምን ንቀት ነዉ ጥለሀኝ የምትሄደዉ..."
ፍፁም መታገስ አልቻለም ክራንቹን ወደ ሰማይ አንስቶ ፍቃዱ ላይ ሳያቋርጥ ማሳረፍ ጀመረ።

ሳያስበዉ በእልህ ፍቃዱን ክፉኛ ስለመታዉ መቆም ያቃተዉ ፍቃዱ ተዝለፍልፎ ወደቀ።

💫ይቀጥላል💫

ምዕራፍ #1 በዚህ ተጠናቋል ምዕራፍ #2 በቅርቡ እንጀምራለን እስከዛው በሌሎች ጣፋጭ ድርሰቶች እንቀጥላለን እስካሁን በሄደው ድርሰት ላይ ያሎትን አስተያየት አድርሱን

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...“ እንዲያው ምን ምን ይላት ይሆን?እኔ እሱ ለሴት ልጅ የሚያወራውን ነገር ለመስማት እጓጓለሁ " ግን አንተ ባል
ከው ዐይነት አገጣጥሞኝ አያውቅም ። ”

“አጅሬ ምኑ ሞኝ ነው ላንተ የሚታየው ?!እሷን ሲያገኛት ቦታው ጭር የሚልበትን ጊዜ ጠብቆ ነው ።

“ ወይ ጉድ ! መቼም ፍቅር የማያሸንፈው ልብ የለም ”አለ እስክንድር በልቡ ። ስለ ድብርት የበለጠ ለማወቅ ጓጉቶ ነበር ። ሆኖም ጨዋታው በተዘዋዋሪም ቢሆን አንዳንድ የአቤልን ድርጊቶች እንደሚንካ ስለ ገመተ አርዕስቱን ለመለወጥ ፈለገ ሳምሶንም ይህንን ሁሉ ልብ ሳይል እንደ መጣለት ነበር የሚጫወተው ። እስክንድር ግን የአቤል ስሜት
እየተለዋወጠ እንደ መጣ በሥርቆት ከገጽታው ላይ አንብቦአል ድብርት የሴት ጓደኛውን ለማግኘት ጭር ያለ ጊዜ
መጠበቁ የአቤልን ስሜት ክፉኛ ነክቶታል እሱም ትዕግሥትን ለማየት የሚጠቀምባቸውን ጊዜያቶች ያውቃል ።

ስማኝ ላምሶን ! ግን ለምንድነው አንተ ብዙ ጊዜ ድብርትን የምትለክፈው ? ” በማለት እስክንድር አርዕስቱን አሸጋገረው
“ ለተንኮል አይደለም ። ግን የሚነፋነፍ ሰው መልከፍ እንዲሁ ደስ ይለኛል ። እንዴት ብዬ ላስረዳህ ? ለምሳሌ
ቀርቦ መናከስ የማይደፍር ውሻ በሩቁ እያፈገፈገ ሲጮህብህ እልሁን ለማስጨራረስ በዱላ እንደምትተናኮለው ዐይነት ነው ። ብቻ እንዲሁ ስለክፈው ደስ ይለኛል እንጂ ለድብርት መጥፎ አመለካከት የለኝም ለየት ያለ ተፈጥሮ ስላለው ያስገርመኛል ” አለና አሳላፊዋን ለመጥራት ጠረጴዛውን ጠበጠበ።

“ አቤት ! ምን ልታዘዝ? ” እያለች አንገቷ በንቅሳት የተዥጎረጎረ ሴት ከፊታቸው መጥታ ቆመች ።

“ ቢራ ድገሚን ሦስት ቢራ ! ” አላት ሳምሶን በዚያው ቁጡ ድምፁ

“ እኔ ይብቃኝ ! ” አለ አቤል "

“ አትቀልድ እባክህ ። አንቺ እኔ የማዝሽን አምጪ!” አለና ሳምሶን አሳላፊዋ ላይ ጮኸባት ።

"ጥርስሽን እንዳያወልቅ ” አለና እስክንድር በልቡ ሳቀ ።

“ እኔኮ ያንተም ተፈጥሮ ያስገርመኛል ” አለው እስክንድር ሳምሶንን
“ እንዴት ?”
“ አሁን ሚስተር ሆርስ ከአቤል ጋር ከታረቀ በኋላ ለምን ትዝትበታለህ ?”

“ አዎ ! የማታውቀው ነገር አለ እስክንድር እየዛትክ የምትተው ከሆነ ዛቻው ሲደጋገም ሰው ይንቅሃል ።ወንድ ከሆንክ አንዴ ማቅመስ አለብህ ። እንዲያውም አንተን ብዬ ነው እንጂ እሱን ልጅ አንድቀን ብሰብረው ደስይለኛል ። ከፈለገ የገዛ ጥርሱን ከመሬት አሰለቅመዋለሁ ።

“ጡንቻህን ፈትነኝ እያለ ያስቸግሃል መሰለኝ” አለና እስክንድር እየሣቀ ከእሱ መልስ ሳይጠብቅ ፡ “ ብቻ ያለንበትንም ጊዜ አትዘንጋ : ሀያኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነን ” አለው ።

“ እና ? ” የብሽቀት ድምፅ ነበር ።

“ እናማ ስፖርተኝነትህን እወድልሃለሁ ። ይህችን በጡንቻ መመካትህን ግን ...

“ እንግዲህ አትልከፈኝ ፡ ልጠጣበት ! ” አለና ቢራውን ተጎነጨ

ሳምሶን ሌላ ሰው እንዲህ ቢናገረውም ካልተደባደበ በዋዛ እይላቀቁም ነበር ። ለእስክንድር ያለው ክብር ግን ብዙ ዓመት ከቆየ የልጅነት የአስተሳሰብ ተጽዕኖ የመጣ ነው ። የሠፈር ልጆች እንደ መሆናቸው መጠን ሳምሶን ስለ እስክንድር ብዙ ነገር ያውቃል ። እሱ ገና ልጅነቱን ሳይጨርስ እስክንድር በሠፈራቸው ውስጥ ስመ ጥር ጎረምሳ
ነበር ። እንዲህ እንዳሁኑ ከመስከኑ በፊት እናቱ በእስክንድር ያላዩት አበሳ የለም ። ከለውጡ በፊት ጸብ አሽትቶ ነበር
የሚፈልገው ። እስር ቤትን ቤቱ አድርጎት ነበር ። አንዴ ጸበኞቹ በቡድን ሆነው ከደበደቡት በኋላ ሆዱ ላይ በጩቤ
ወግተውት ለጥቂት ነው ከምት የተረፈው ከለውጡ በኋላ ደግሞ በወቅቱ በተፈጠሩት የፖለቲካ ድርጅቶች ሳቢያ
ያልቀመሰው፡ አበሳ የለም ። ችኩል ነበር ። ሰው አይገራውም ፣ ያየሁት አይለፈኝ የሚል ስሜት ያሸንፈዋል ።
የጀብደኝነት ስሜት ያጠቃዋል ። ትኩስ ኃያልነቱ፡ መንፈሱን ያቅበጠብጠዋል ። አሁን ግን በዕድሜም በብስለትም ሰክኖ
እንኳን ለራሰ ሌሎችንም ይመክራል ። ከአፍላነት ቅብጥብጥነት ጊዜው ይዞ የመጣውና አሁንም ያልተወው ነገር ቢኖር
የሲጋራ ሱስ ብቻ ነው። ይህ ሁሉ ሁኔታ በሳምሶን ላይ የሚኖረው ተጽእኖ ቀላል አይደለም። በፀጉሩ ኪንኪነት እየለከፈው ከእስክንድር ጋር መቃለድ የጀመረው እንኳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው።

አቤል እባክህ ተጫወት ይሄንን ተወው
አለ ሳምሶን እስክንድርን በመንቀፍ አይነት

“ እየሰማኋችሁ “ኮ ነው ? ” አለ አቤል በጨዋታቸው ውስጥ የቆየ ለመምሰል ጥርሱን በውሸት ብልጭ አደረገ።

ሐሳቡ በከፌል ወደ እነ ትእግስት ዘምቶ ነበረ። ፈተና ከጨረሰች በኋሳ ወዴት ትሔድ ይሆን ? አርፎ መተኛት ወይስ
ዙረት መውጣት ? እያለ ሲያሰላስል ነው የቆየው።ሁለተኛውን ጠርሙስ ቢራ ግማሽ አድርሶታል ። ከቻቻታው ጋር
ቢራው ሞቅ አድርጎት ውስጥ ውስጡን እየሰከረ መምጣቱ ይሰማው ነበር። የመጠጣት ልምድ ስለሌለው ጭንቅላቱ ቶሎ መረታት ጀምሯል ። ድፍረትም ተሰማው ማንንም ያለመፍራት ሃይነት ስሜት !

“ ለምን ሙዚቃውን አይቀይሩልንም ? ” ሲል ድምፁን አሰማ ። የእንግሊዝኛ ሙዚቃ ነበር አዳራሹን የሚነቀንቀው፤“ ማስቀየር እንችላለን ። የማን ክር ይደረግ ? ” አሉ እስክንድርና ሳምሶን በአንድ ድምፅ አቤል ከዝምታ ወደ
ተሳትፎ መምጣቱ ደስ አሰኝቶአቸው ነበር

•የ... የመልካሙ ተበጀ ክር ቢሆን
ይሻላል” አለ አቤል በተሰባበረ ድምፅ

እስክንድርም ሆነ ሳምሶን በፍጥነት የጠረጠሩት ነገር አልነበረም ። አሳላፊዋን ጠርተው ክሩ እንዲቀየር አዘዟዋት።

ባለቤትየዋ እሷ የመረጠችው ዘፈን ካልሆን እሺ አትልም ግን ልሞክርላችሁ ” አለች አሳላፊዋ ።

“ ንገሪያት ! ለምን እሺ አትልም ? ” አለና ሳምሶን አፈጠጠበት እሷ ዘፈኑን ልታዝዝ ስትሔድ አቤል ቀድሞ በልቡ
ያንጐራጉር ጀመር።

አረ መላ ምቱ ወዳጅ ዘመዶቼ
ዐይናፋር ሆኛለሁ ፡ ዐይናፋር አይቼ
ሰሳምታ አልሰጠኋት አላነጋገርኳት
በዐይን ብቻ እያየሁ አንድ ዓመት ወደድኳት።

ልቡ ይህን እያዜመ፥ ጆሮው የሚሰማው ግን ሌላ ሙዚቃ ነበር ቢጠብቅ ፥ ቢጠብቅ የተለወጠ ነገር የለም ጥቂት
ቆይታ አሳላፊዋ ተመልሳ መጣች።

የመልካሙ ክር የለም ብላለች ባለቤትየዋ ! ”

አቤል በሽቆ “ ገደል ግቢ በያት ! ” ከማለቱ ዐይኑ እንባ አቀረረ ። የሰው ስሜት የማይጠበቅበት ዓለም ! ባለቡና ቤቶች ፍቅረኛውን የሚያስታውስበትን ዘፈን አይከፍቱለትም "መምህራን ትምህርት ምን ያህል እንዳስጠላው አይረዱለትም ። ወላጆቹ ልጃቸው ከድህነት ቀንበር እንዲያላቅቃቸው
ይመኛሉ እንጂ እሱ ያለበትን ችግር አያውቁለትም ። ጓደኞቹ ብቸኝነቱን አይፈቅዱለትም ።

“ እሷ ከሙዚቃዋ ጋር ገደል ትግባ ! አንቺ ቢራ ድግሚን ” አላት ሳምሶን በሽቆ ።

“ኧረ ይብቃን ! ሰዓቱም መሽቷል የካምፓስ ፖሊሶች አያስገቡንም ” አለ እንክንርድ ኪሱን እየዳበሰ ።

አምጪልን እባክሽ እንጠጣው ዛሬ ካምፓስ ማን ይገባል? ” አለ ሳምሶን በሞቅታ ስሜት ።

“በይ እንግዲያው አንቺንም እንጋብዝሽ የምትጠጪውን ነገር ይዘሽ ነይ ” አላትና እስክንድር ፡ ወደ ሳምሶን ዘወር ብሎ ፥ “ ከጠጣን አይቀር መሐላችን አንዲት አንስታይ ስትኖር ይሻላል” አለው ። ከሳምሶን ሁኔታ ገንዘብ እንደያዘ
ገምቶ ነበር "

እቤል ምንም አስተያየት አልሰጠም ። የያዘውን ቢራም አልጨረሰም ። ከዚያ በላይ መጠጣት አልፈለገም ። ሆኖም
አልተከላከለም ። ሕይወትን የመሰልቸት ዐይነት ነበር የሚሰማው ። ለምንም ነገር ያለመጨነቅ ። ስካር ማለት ይሄ ይሆን እንዴ?
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ።
ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች። ናፍቆቷን ሙሉውን ሌሊት አቅፋት በመተኛት ተወጣች፡፡
አሁን ሁሉንም ጣጣዋን ጨርሳለች፡፡ ዕቅዷን ልትፈጽም ሰዓቱ እየደረሰ ነው፡፡ በሌሊት ተነስታ ልብሷን ለባብሳ ጨረሰችና፣ ከፔርሙስ ትንሽ አጥሚት ቀድታ ካጠጣቻት በኋላ፤ “ወደ ቤት ልሂድ እማ!” ብላ ለመሄደ ተነሳች፡፡
ደግማ፤ ደጋግማ፤ ጉንጮቿን አገላብጣ ሳመቻትና፤ ወጣች፡፡ስትወጣ መንፈሷ ሁሉ ጠንካራ ነበር፡፡ ፍርሀት ጓዙን ጠቅልሎ ነው የሄደው፡፡ ቤት ደርሳ ያንን ትናንትና በፍቅር ስታሽሞነሙነው የዋለችውን የአባቷን ቅርስ ሸፋፍና፤ በቦርሳዋ ይዛ፤ ወደ መርካቶ ገሰገሰች፡፡
እዚያ እፍልሚያው ቦታ ስትደርስ ከታክሲ ወረደችና ራቅ ብላ ዓይኖቿን በሱቁ ላይ ተክላ ትጠባበቅ ጀመር፡፡
ልቧ ድው! ድው፤ ይላል፡፡ እልህና ሲቃ ይተናነቋታል፡፡ እንዷ ደቂቃ አቤት ርዝመቷ! አውሬው ወጥመዱ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ በንቃት መጠባበቋን ቀጠለች፡፡
አንዳንድ ሱቆች መከፈት ጀምረዋል፡፡ እምብዛም ሰው አይታይም፡፡ መርካቶ ትንሽ ሞቅ ሲል እንደዚያ እንደማይተራመስ ሁሉ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያስገርም ነው፡፡
ነጠላዋን ተሸፋፍና፣ መንገደኛ መስላ፧ አንድ ጥግ ላይ ተቀመጠችና፤ ግዳይዋን መጠባበቁን ተያያዘችው፡፡ በእርግጥም ስለቸኮለች ነው መሰል በጣም ቀድማ ነበር የመጣችው፡፡
ገንዘብ በገፍ እየገባለት የመጣው ጎረምሳ በንግዱ ላይ ትኩረቱን እየጣለ ሄዶ ነበር፡፡ አበራን ወደዚያ ካባረረ በኋላ ትርፉን ለግሉ ማግበስበስ ጀምሯል።
ገንዘብ ሲቀምሱት ይጣፍጣል፡፡ በላይ በላዩ ያስመኛል። እህል ሲጠግቡት ያስገሳል፡፡ሲበዛም ያስጠላል፡፡ ገንዘብ የሚጠግብ ሆድ ግን የለም፡፡ ግሳትም የለው፡፡ በላይ በላዩ ጨምሩልኝ፣ ጨምሩልኝ፣ የሚያሰኝ፣ እየበሉት የሚርብ ነገር ቢኖር ገንዘብ ነው፡፡
እንደሻው የራሱ የሆነውን፤ እንደፈለገው የሚያዝበትን ገንዘብ ሲያገኝ፤ እንደጠላት ገንዘብ ማውደም ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ ሱቁን በማደራጀት ሀብታም መሆን ስለፈለገ፣ ቆጣቢና ትጉህ ሠራተኛ ሆኗል።
ዛሬ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ገበያ ሊሻማ መጣና የሱቁን በር ከፈተ፡፡ ሙሉ ጂንስ ለብሷል፡፡ ከላይ ጥቁር ክብ ባርኔጣ አድርጓል፡፡
አንገቱ ላይ አጠር ያለች ወፍራም ሻርፕ ጠምጥሞ ነበር፡፡
የሱቁን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ መዝለቁን ስታይ ትህትና ተዘጋጀች፡፡ እሷም ጂንስ ሱሪ ነው የለበሰችው፡፡
ቀስ ብላ ቀኝ እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰደደችና፣ ማጥበቂያውን አላላች፡፡ ሽጉጡ ላግዳጁ ዝግጁ ሆነ፡፡ አሁንም ቀስ ብላ ጨበጠቸው፡፡ እጇ የተንቀጠቀጠ መሰላት፡፡
“አይዞሽ ትህትና ጠንከር በይ” አለች ለራሷ፡፡ “የመጨረሻው ሰዓት የድል ሰዓት ደርሷል፡፡ የመጨረሻውን የድል ሰዓት ባትወጪው አበቃልሽ!” አለችና ራሷን አደፋፈረች፡፡
ይህ የመጨረሻው መክሸፍ የሌለበት እርምጃ ነው፡፡ በእውነትም ጠንከር አለች፡፡ ልቧ በትክክል መምታት ጀመረ፡፡ ሰውነቷ መራራ ደም ሲረጭ ተሰማት፡፡ የቀድሞ ባህሪዋ ከውስጧ ጥርግርግ ብሎ ወጣና፤ አዲስ የቆራጥነት፣ የደፋርነትና፤ የጭካኔ ባህሪይ ተላበሰች፡፡
“አምላኬ በደሌን አንተ ይቅር በለኝ፡፡ ነፍሴን ተቀበላት!” አለችና የሽጉጡን ምላጭ እንደያዘች እየተንደረደረች ወደ ሱቁ ሩጫዋን ቀጠለች፡፡
ሱቁ በር ላይ ስትደርስ እንደሻው በሚያየው ነገር ተደናግጦ፣ ዐይኖቹ ተበልጥጠው፣ አፉ ተከፍቶ እንደቀረ ትንፋሽ ከማውጣቱ በፊት
ሽጉጡን ላጥ አድርጋ አወጣችው፡፡
ንግግር የለ፣ ግርግር የለ፣ ፋታ ሳትሰጠው በቀጥታ እርምጃውን ወሰደች፡፡
ዷ! ዷ! ዷ! ዷ! አምስት የቆጠረች መሰላት፡፡ አራንቱን ጥይቶች ካንጣጣችበት በኋላ፣ ተንገዳግዶ መውደቁን ስታረጋግጥ፧ ሽጉጡን
ወደራሷ አዙራ አፍዋ ውስጥ አስገባቸው፡፡
ሰው መሯሯጥ ጀመረ፡፡ ለሚተራመሰው ሰው ቦታ ሳትሰጥ፤
እርምጃዋን በራሷ ላይ ወሰደች፡፡ ምላጩን ሳበቸው፡፡ ዷ! ዷ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ የተባዘተ ጥጥ በመሰለው ደመና ተዥጐርጉሯል።
ጨረሯን የፈነጠቀችው ፀሐይ ያንን የደመና ቁልል እየናደችው ስትመጣ፤
ሰዓሊው በሸራ ላይ በብሩሹ የፈነጠቀው ንድፍ እየመሰለ ሄደ፡፡ ከዚያም ሙሉ ለሙሉ ደመናው ተገፈፈና፤ ጥርት ያለ ሰማይ ታየ፡፡
የሰው ልጅ የውስጥ ስሜቱ ሲጐዳ፣ ሲከፋው፣ ሲጨንቀው፤ ልክ ሰማዩ በደመና እንደሚያኮርፈው ሁሉ፤ ይህንን መጥፎ የውስጥ ስሜቱን በጨፈገገ ገጽታው ይገልጸዋል፡፡ በሆነ ባልሆነው ሆደ ባሻነት ያጠቃዋል፡፡
እነሆ ልቡ ከአምስት ዓመታት በላይ ከፍቅር ተገልሎ የቆየው ሻምበል ብሩክ ትህትናን ካገኘበት እለት ጀምሮ መንፈሱ ታድሶ!
የወደፊት የትዳር ህይወቱን በቅርብ ርቀት አሻግሮ መመልከት ሲጀምር፤ በእንጭጩ ተቀጨ፡፡
ትህትና ፍቅሯን ብቻ ሳይሆን፤ ያንን ደስተኛነቱን ጭምር በልቡ ውስጥ ገድላበት ነው የሄደችው፡፡
ድምጿን ለመስማት ይፈልጋል፣ ወዲያውኑ ደግሞ ከነመፈጠሯ እንዲረሳት ይመኛል፡፡ ትናፍቀዋለች፤ የሠራችው በደል ፊቱ ላይ ድቅን
ይልበታል፡፡ በቅናት ይቃጠላል፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ ብሩኬ.... ብሩኬ....
ብሩኬ.... የሚለው ያ ለስላሳ ድምጿ፣ ያ ለስላሳ ሰውነቷ ያ ለስላሳ ባህሪዋ፤ ይታወሰዋል፡፡
በፊት የነበረችው ትህትና እንዴት የምትወደድ ልጅ ነበረች? ለምን ፈጣሪ አሳይቶ ነሳው? ምነው እሱ ለፍቅር አልታደለ? ሁል ጊዜ መጨነቅ?
“ምነው የዚያን ዕለት ባልተገናኘን ኖሮ” የሚል ሃሣብ መጣበት፡፡ ሆኖም በመገናኘታቸው አንድ መልካም ሥራ መስራቱ ያስደስተዋል፡፡
አጋር ያልነበራት እናቷን መርዳት መቻሉ እርካታን ይሰጠዋል።
ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም፡፡ እንዲሉ፣ እሷ ትበድለው እንጂ፤ እሱ ከበደል ይልቅ መልካም ሥራን የሠራ ተበዳይ መሆኑ ሲታወሰው፤ “ይሁን እስቲ ሁሉ ነገር ከፈጣሪ ይገኛል” ይልና
ይጽናናል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ የሰሞኑ ሁኔታው የተለየ ነበር፡፡ ናፍቆቷ ነፍሱን ሊያወጣው ደርሷል፡፡
በውስጡ ፍቅርና ጥላቻ ነግሰውበታል፡፡ እንዳይጠላት ይወዳታል፣ እንዳይወዳት ደግሞ የሠራችው ሥራ...እንዳንድ ጊዜ ያ አለቃቀሷ፤ እዚያ እላዩ ላይ ተጠምጥማ እየተንሰቀሰቀች የተናገረችው ንግግር፣ ትዝ ይለውና፤ “ምን ነበረበት ይቅር ብላት ኖሮ? ግብዝ ነኝ” በማለት እራሱን
ይኮንናል፡፡ ወዲያው ደግሞ የሻክረና ጥርጣሬ የገባው ልብ ተመልሶ ልብ
ላይሆን፡፡ የነቃ ብርሌ ተመልሶ ዕቃ ላይሆን፣ አጉል ሙጥኝ አለማለቱን
ይወደውና..
እንኳንም በጊዜ አቋረጥን” የሚል ስሜት ይሰማዋል፡፡በጠዋቱ መ/ቤቱ እንደደረሰ ወደ ቢሮ ከመግባቱ በፊት ጫማውን
ሊያስጠርግ ሄደ፡፡ሰማዩን አየው፡፡ ከቤት ሲወጣ በደመና የተሸፈነ ነበር፡፡ አሁን
ግን ጥርት ብሏል፡፡ የሱ ስሜት ግን እንደሰማዩ አልጠራም፡፡ ፊቱ ጨፍግጓል፡፡ ጫማውን አስጠርጐ ወደ መሥሪያ ቤቱ ግቢ ሲዘልቅ......
“እንደምን አደርክ ሻምበል መልዕክት አለህ” አዳሪው ፖሊስ ከኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ፖስታ አቀበለው፡፡
ሻምበል ፖስታውን ተቀብሎ ተመለከተው፡፡ የላኪው ሥም
የለበትም፡፡
የአደራ ደብዳቤነቱን እንጂ ከማን እንደተላከ አይገልጽም፡፡
“ማን ነው የሰጠህ?” ሲል ፖሊሱን ጠየቀው፡፡ ስሟን እንዳልነገረችው ገለፀለት፡፡ በቀጥታ ወደ ቢሮው ሄደ፡፡
የቢሮውን መስኮት ከፈተው፡፡ ንፁህ አየር ገባ፡፡ ከዚያም
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....አፓርትመንቷ ጋ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ እጥፍ ብሎ ከአንድ ትንሽ ሻይ ቤት ገባና በሩ አጠገብ ካለ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሻይ አዘዘ፡፡ ጥንቃቄ ያስፈልጋል እርጋታ፡፡ ባሻገር የሚታየው የአፓርትመንቱ ቅጥር ግቢ አለቅጥ ጭር ብሏል፡፡ የወትሮው ግርግር ወጪና ገቢ አይታይም፡፡ ከአፓርትመንቱ ስር መኪናዎች በስርኣት ተደርድረው ቆመዋል፡፡ ለወትሮው ሲሯሯጠ የሚታዩ ሲጫወቱ የሚገኙ የአፓርትመንቱ ነዋሪዎች ልጆች በግቢው አይታዩም፡፡በር ላይ ብቻ እኛው የድሮው ሽማግሌ ዘበኛ አፈርማ ካፖርታቸውን ደርበው ከዘበኛዋ ቤት ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለው ያንጎላጃሉ፡፡

ይህ ነው ብሎ ምክንያት ሳይሰጠውም ፍርሃት ገባው፡፡ ፀጥታ ተራ ነገር አይደለም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሙሉ ፀጥታ አደጋ ከመድረሱ በፊት የሚያንዣብብ ማዘናጊያና አደጋው ከደረሰ በኋላ ድንጋጤን ደርቦ የሚንጠለጠል ግግርት ነው፡፡ ጥፍሩን መቆረጣጠም ጀመረ። ጭንቅላቱ ግራና ቀኝ ቆሞ ይሟገት ጀመር፡፡

ሰዓቱን ተመለከተ አሥራ ሁለት ከሃያ፡፡

ዝም ብዬ ነውኮ ይልቅ ብሎ ገብቼ እይቻት ብወጣ ይሻላል...ግን በአካባቢው የአውሬው አይን ቢኖርስ ስገባ ቢያየኝስ?ወዲያው ቢከቡኝስ ታዲያ እስከመቼ እዚህ ተቀምጨ እቆያለሁ?! ስልክ ደውዩ
ወንድሟን «ውጣ» ብለውስ ከአፓርትመንቱ እራቅ እንዲል ነግሬው
ባነጋግረውስ ምን ዋጋ አለው? ገብቼ ካላየኋትማ ለምንስ መጣሁ? ብገባ
ይሻላል... አዎ አይቻት ቶሉ እወጣለሁ… በአካባቢው ካሉ ግን ያለጥርጥር
እንደ ጅግራ ነው ክንፌን ብለው የሚጥሉኝ…ምን ዘዴ መፍጠር ይሻላል?

ጭንቅላቱን አፋጨው፡፡ አካባቢው እየጨለመ መጣ፡፡ የመንገድ
መብራቶች ቦግ ቦግ ቢሉም ደቂቃዎች በሄዱ ቁጥር ይበልጥ የሚደምቀውን
ጨለማ መታገል ማሸነፍ መግፈፍ እያቃታቸው መጠ፡፡ ናትናኤል ያለበትን
ክፍል ቃኘው፡፡ ትንሿ የሻይ ቤት ንጽህና የሌላት ናት፡፡ . በውስጧ የተሰበሰቡትም ሰዎች እሱው?እንዳጠለቀው በህይት የተጨማለቀ የጋራዥ ቱታ ቆሻሻ ልብስ የለበሱ ቀዝቅተኛ ኑሮ የሚገፉ፤ የሚጎትቱ እንደሆነ “ ያስታውቃሉ፡፡ ሰዓቱን ድጋሚ ተመለከተ፡፡ አስራ ሁለት ተኩል፡፡
በተቀመጠበት እንዳለ አሻግሮ የአፓርትመቱን መግቢያ በር ቃኘው፡፡ በሩቅ በድንግዝግዝ አንድ ሰው ይታየዋል፡፡ የበሩን አንድ ወገን መቃን ተደግፎ ቆሟል ሰውየወ:: ናትናኤል አትካር ተመለከተው፤ ካፖርት ለብሶ
አንገተዬውን ቀልብሶ የቆመውን ሰው ግን ሊለየው አልቻለም፡፡

'ብስራት ይሆን? መሆን አለበት። አሰበ፡፡
ተነስቶ ወደ አፓርትመንቱ መሄድ ግን ፈራ፡፡ ድጋሚ ዞር አለና እሱ ከተቀመጠበት ስፍራ ፈንጠር ብሎ ሁለት ክንዶቹን ጠረጴዛ ላይ ተክሎ
ጉንጭጮቹን በሁለት መዳፎቹ ደግፎ የተቀመጠ ጎረምሳ ላይ አተኮረ፡፡ አንድ
ዘዴ መጣለት:: ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ ወጣቱ ተጠጋ፡፡

“ሰላም...ልቀመጥ?” አለ ከወጣቱ ጠረጴዛ ዙሪያ ከተደረደሩት ሦስት
ወንበሮች አንዱን ያዝ ኣድርጎ፡፡

ወጣቱ ጉንጮቹን ዘሁለት መዳፎቹ ውስጥ ሳያወጣ አይኑን ብቻ
አቅንቶ ተመለከተው::

“ተቀመጥ:: አለ ወጣቱ ግድ እንደሌለው ለማሳየት ትከሻውን ከፍ ዝቅ አድርጎ፡፡

“እንድ የምትሰራልኝ ስራ ነበር፡፡ በቂ ገንዘብ እከፍልሃለሁ፡፡” አለ ናትናኤል ከኪሱ ቦርሳወን አውጥቶ ሁለት የአስር ብር ኖቶች እየመዘዘ፡፡

ከፊት ለፊቱ የተቀመጠው ወጣት ቀያዮቹን ኖቶች ሲመለከት ጉንጮቹን ለቀቅ አደረገና ቀና አለ፡፡ የደረበው ረጅም አሮጌ ኮት አንገትዬው ነትቧል፤ ከውስጥ ሸሚዞ በሽቅጧል፡፡

“ትስማማለህ?”
“ምንድነው የምሰራልህ? የሚደበደብ ሰው ከሆነ እርሳው፡፡” አለ ወጣቱ አገጩ ላይ ችፍርግ ብሎ የበቀለውን የቆሽሽ ጺም እያከከ፡፡

“አይደለም፡፡” አለ ናትናኤል ወደፊት ጠጋ ብሎ “እየው ያ ፎቅ ይታይሃል? በሩ ላይ የቆመው ሰውዬ ይታይሃል?”
ወጣቱ በ'አዎንታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡

“…ቀጥ ብለህ ወደ ሰውየው ትሄድና አጠገቡ ልትደርስ ጥቂት
እርምጃዎች ሲቀርህ ናትናኤል ይፈልግሃል። ተከተለኝ በለውና ድንገት
ፊትህን መልሰህ እየሮጥክ ከግቢው ወጥተህ ትመጣለህ፡፡”

“እናስ.. ከዛ በኋላስ?”
“በቃ::”
“እንዴት በቃ? እለ ወጣቱ ፊቱ ጥርጣሬ ለብሶ:: “እዛች ደርሼ ስለተመለስኩ ነው ይህን የምትሰጠኝ?” ወጣቱ፡፡ ዓይኖቹን በሁለቱ፡ የአስር ብር ኖቶች ላይ አነጣጠራቸው፡፡

“አዎ::"
“ምንም ሳልሰራ?”
“አዎ፡፡”
“አትቀልድ፡፡ ነገር አለው፡፡” አለ ጎረምሳው ወደ አንድ ወገን እየሳቀ፡፡

“ምንም ነገር የለውም፡፡”

ወጣቱ ኣይኖቸን አጥብቦ ናትናኤልን ሊያጠናው ሞከረ::
“ለምን እራስህ አትሄድም?"
“ትፈልጋለህ አትፈልግም?” አለ ናትናኤል ሁለቱን የአስር ብር ኖቶች ወደፊት እየገፋ::

ወጣቱ፡ ከራሱ ጋር ክርክር የገጠመ መሰለ፡፡ ናትናኤል ድንገት ትቶት ሲነሳ ፈጠን ብሎ አብሮት ተነሳ፡፡

“እሺ አምጣ፡፡ ፀጥ ብዬ ገብቼ ናትናኤል ያጠራሃል ብዬው ፀጥ ብዬ መወጣት ነው… እይደል?”

“እየሮጥክ ነው የምትወጣው፤ ፀጥ ብለህ አያደለም:: ልክ ከሰውየው እንደምትሸሽ ዓይነት እየሮጥክ፡፡” ናትናኤል ቆፍጠን አለ ሃያ ብር
የያዘውን ቀኝ እጁን ወደኋላ ሰብስቦ፡፡

“እሺ ኣምጣ…. እሮጣለሁ፡፡” አለ ወጣቱ እጁን ወደ ብሩ ዘርግቶ፡፡
“ደርስህ ስትመለስ…. መሮጥሀን ካየሁ በኋላ፡፡” ናትናኤል ፈርጠም አላ::

“እሺ ግማሹን ስጠኝ::”
“ደርሰህ ስትመለስ መሉው ያንተ ነው፡፡”
ወጣቱ ከሻይ ቤቷ ወጥቶ ወደ አፓርትመንቱ ሲያመራ ናትናኤል
ተከትሎት ወጣና የመኪና መንገዱን ተሻግሮ ከለላ ይዞ የሚሆነውን
ይከታተል ጀመር፡፡

የሚጠባበቁት ሰዎች ካሉ ወደ አፓርትመንቱ ሲገባ ሊይዘት ወጥመድ ያጠመዱ ካሉ። ወጥመዳቸው በወጣቱ ላይ እንደሚወነጨፍ እርግጠኛ ነበር፡፡

ወጣቱ የአፓርትመንቱን የአጥር ግቢ በር አልፎ ሲገባ ሽማግሌው ዘበኛ ከእንቅልፋቸው አልነቁም:: ወጣቱ እጆቹን የኮት ከሶቹ ውስጥ ከትቶ በእርጋታ አፓርትመንቱ በር ላይ ወደቆመው ሰው አመራ፡፡ ሰውዬውጋ ለመድረስ በግምት አአስር እርምጃዎች ሲቀሩት ድንገት ቆም አለና ናትናኤል እንዳዘዘው መልዕክቱን ተንፍሶ ፊቱን መልሶ ሮጥ ከማለቱ፡ ግራና ቀኝ ቆመው የነበሩ መኪናዎች በሮች እየተበረገዱ አራት ሰዎች ዱብ ዱብ አሉ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን አፍጥጦ ቀረ፡፡ በሁኔታው የተደናገጠው ወጣት
ለማምለጥ ቢሞክርም ከአጥር ግቢው በር ከመድረሱ በፊት ይዘው እፍስፍጥ
አድርገው ከአንደኛዋ መኪና ውስጥ ከተቱት፡፡

ለደቂቃዎች ናትናኤል ካለበት ሳይንቀሳቀስ ተጠባበቀ፡፡ ወዲያው
የመኪናዋ በር ተከፈተና በሁለት በኩል የወጣቱን ክንዶች የልጨመደዱ ሁለት
ሰዎችና ሌሎች ተጨጨማሪ ሶስት ሰዎች ወደ አፓርትመንቱ፡ ግቢ በር ያጣደፉ ጀመር፡፡ ከአፓርትመንቱ፡ ግቢ ሲወጡ ናትናኤል ወደ ኋላ አፈገፈገና ጥሩ ከለላ ይዞ በሩቁ በአይኑ ያስተውላቸው ጀመር::

አምስቱ ሰዎች ወጣቱን ከበው ወደ ሻይ ቤቷ ተጣደፉ፡፡ ከሻይ ቤቷ ደጃፍ፡ እንደደረሱ ሀለቱ ልጁን አስቀድመን ከተል ብለው ሲገቡ ሁለቱ፡፡ በሻይ ቤቷ ጓሮ ዞሩ፡፡ የተቀረው አምስተኛው እፊት ለፊት ጀርባውን ግድግዳው ላያ ለጥፎ ቀኝ እጁን ከኮቱ፡ ስር ብብቱ ስር ከቶ ቆመ::

ናትናኤል ሰውየው ከኮቱ ስር የጨበጠው ምን እንደሆነ ሲረዳ አብርሃም ታወሰው፡፡ ሻይ ቤቷ ውስጥ የቡት ሰዎች ከውስጥ ሲያጡት ወጥተው አካበቢውን ሊያስሱ እንደሚችሉ ሲረዳ ፈጠን ብሎ ከተደበቀበት ወጣና ሽቅብ በሩጫ ተፈተለኩ ታክሲ ተራ ደርሶ ለገሃር ብሎ ታክሲው ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ሁሉ ሁለት ሦስቴ እየተገላመጠ ተመለከተ፡፡ ከጀርባው የተከተለው ሰው ግን አልነበረም፡፡ ወደኋላ መመለስ
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...ኪም ቾይ ላና ግሬይ ከዶክተር ሮበርትስ ቢሮ ስትወጣ እንዳየቻት ኮምፒውተሯ ላይ እየተየበች እንደሆነ ማስመሰል ጀመረች።

በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ በኒሮ ሳይንስ ዲግሪዋን የያዘችው ኪም ቾይ የኒኪ ረዳት ሆና የትሬይን ቦታ ተክታ በመሥራት ላይ ትገኛለች፡፡ ኪም በጣም ጎበዝ እና ቆንጆ ናት፡፡ ለስላሳ የእስያ ቆዳ፣ ጎላ ጎላ ያሉ ዓይኖች እና ጥቁር ሀር የመሰለ ፀጉር አላት፡፡

ወግ አጥባቂ በሆነ የቻይና ቤተሰብ ውስጥ ስላደገችም የቀድሞ ታዋቂ
የቴሌቪዥን ተዋናይዋን ስታያት በጣም ነው የደነገጠችው።

“ሚሲስ ግሬይ ሌላ የቀጠሮ ጊዜ ልያዝልሽ?” ብላም ኪም ልቧ በጣም
እየመታባት ጠየቀቻት፡፡ ከዚህ በፊት ከታዋቂ ሰው ጋር በአካል ተገናኝታ
ስለማታውቅ ነበር ልቧ መምታቱ። ይኼ የትርፍ ጊዜ ስራዋ ብዙ ታዋቂ
ሰዎችን በአካል እንድታይ አድርጓታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ላይብረሪ ውስጥ
ከመንቀዋለል እዚህ መዋሏ በጣም ደስ የሚል ነገር ነው የሚፈጥርላት።

ላና ዞር ብላ ከዴስኩ ጀርባ የምትገኘውን ቀጭን ቆንጆ የእስያ ደም ያላትን ልጅም ስትመለከት ኃይለኛ ቅናት ጉሮሮዋን አነቃት፡፡ የራሷ የዶክተሯ አልበቃ ብሏት በየሳምንቱ ዶክተሯን ስታገኛት በእሷ ሕይወት እና ቁንጅና ማስቀናቷ አልበቃ አላት እና አሁን ደግሞ በጣም ቆንጆ ወጣትን ለቢሮዋ ቀጠረች።

'ይህን ነገር አውቃ ነው የምታደርገው?' ብላ ላና እያሰበች 'ለራሴ ያለኝን
ግምት ልታንኮታኩተው ትፈልጋለች ፤ ስለዚህም ይህንን የወደቀውን ለራሴ
ያለኝን ግምት ለማስተካከል ብዬ ወደ እሷ ስመላለስ እንግዲህ እሷ 300
ዶላሯን ላጥ ታደርጋለች ማለት ነው፡፡ ማን ይታመናል በዚህ ጊዜ ዶክተሯ ይህን አታደርግም አይባልም፡፡

ላናም ወደ ኪም ዴስክ ቀረበች እና ጎንበስ ብላ በተቆጣ ድምፅ “እኔ ሌላ ቀጠሮ መያዝ ብፈልግ እነግርሽ አልነበር እንዴ?” ብላ ጠየቀቻት፡፡

ኪምም በላና ምላሽ በጣም ደንግጣ ግራ ተጋባች፡፡ “ምናልባት የሐኪሟ ደምበኞች ሳይናገሩኝ ማናገር አይጠበቅብኝ ይሆን? ብላም አሰበች እኛ
“ይቅርታ ሚስስ ግሬይ እኔ ያሰብኩት...” አለቻት፡፡

ላናም በጣም ተናድዳ ወደ ዴስኩ ሄደችና ኪም ላይ አይኗን አጉረጥርጣ
“እኔ ቀጠሮ ስፈልግ እጠይቅሻለሁ። እንዲያውም ከዚህ በኋላ እዚህ አልመጣም” ብላት እየተቆናጠረች በሩን በሀይል ዘግታ ከእንግዳ መቀበያው
ክፍል ወጣች፡፡

የበሩን በሀይል መዘጋትን የሰማችው ኒኪም ከቢሮዋ ወጥታ የእንግዳ
መቀበያ ክፍሉ ውስጥ ስትገባ ረዳቷ ኪም ቾይን አይኗ እምባ አቅርሮ ተመለከተቻት፡፡

“ይቅርታ ዶክተር እኔ ላናን ሳላበሳጫት አልቀርም። ግን እኮ ቀጠሮ ልያዝልሽ ነው እንጂ ሌላ ምንም ነገር አላልኳትም፡፡”

“አይዞሽ እሷ ሁሌም እንደዚህ ናት” ብላ ኒኪ አፅናናቻት።

“ግን እኮ ሁለተኛ እዚህ አልመጣም ብላለች። ይቅርታ ሥራሽን አበላሽሁብሽ መሰለኝ” ብላ ኪም ቾይ ማልቀስ ጀመረች፡፡

“ኧረ አታልቅሺ፡፡ ታያለሽ በሚቀጥለው ሳምንት እራሷ ትመጣለች። አሁን ተረጋጊ፡ ሌላው ደግሞ ካርተር በርክሌይ እንደመጣ አስገቢው” አለቻት፡፡

ኒኪ ወደ ቢሮዋ ተመልሳ ወንበር ላይ ቁጭ ካለች በኋላ ባሏ በሕይወት
እያለ ያለማመዳትን የትንፋሽ ልምምድ ማድረግ ጀመረች።

አየር በኃይል ወደ ውስጥ ሳቢ የሚለው የባሏ ድምፅ በውስጧ ይሰማታል፡፡ ከዚያም ወረቀቶችሽን እየነጠልሽ እንደምታስቀምጪ ሁሉ
ሃሳቦችሽንም አንድ በአንድ በየተራ እየነጠልሽ አስቀምጪያቸው።

አየር በኃይል ወደ ውስጥ ሳበች እና የመጀመሪያውን ሃሳቧን ማሰብ ጀመረች ላናን ላግዛት አልቻልኩም፡፡ እሷ ሁሌም ወጣት ሴቶችን ባየች ቁጥር ንዴቷ እየጨመረ ነው የሚመጣው፡፡ ምናልባት ወደ ሌላ ቴራፒስት ልልካት ይገባል፡፡ ቴራፒስት ብቻ ሳይሆን ሳይካትሪስትም ሳያስፈልጋት አይቀርም፡፡ ግን እንዴት ልልካት እችላለሁ?'

ለሁለተኛ ጊዜ አየር በጣም ወደ ውስጥ ሳበች እና ስለእሷ ማሰብ ጀመረች፡፡ እኔ ጥሩ ቴራፒስትም ጥሩ ሚስትም አይደለሁም፡፡ ምክንያቱም ጥሩ ሚስት ብሆን ኖሮ ለባሌ አርግዤለት ልጅ እወልድለት ነበር፡፡ እሱም ሌላ ሰው ጋር ባልሄደ ነበር፡፡' ብላ አሰበች፡፡ በመቀጠልም “አሁን ስለራሴ
ሳይሆን ስለታካሚዎቼ ነው ማሰብ የሚገባኝ እያለች ሃሳቧን ልትጀምር
ስትል ቢሮዋ ግርግዳ ላይ ያለው የተረኛ ታካሚውን መምጣት የሚገልጸው
መብራት ብልጭ ድርግም ሲል ካርተር እንደመጣ አወቀች፡፡ ከወንበሯ
ተነስታም የቢሮዋን በር ከፈተች::

ኮሪደሩ ላይ ካርተር አንድ እግሩ በጀሶ ታስሮ እና በአንደኛው ወንበር መደገፊያም ላይም ሁለት ክራንቾቹን አስቀምጧል፡፡ የቢሮውን መከፈት እንዳየም በፍጥነት ሁለቱን ክራንቾቹን በግራና በቀኝ በኩል እየተደገፈ ወደ ቢሮው ውስጥ ገባ፡፡ ኒኪ በሩን ዘግታ ካርተር ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ምን ሆነህ ነው?” ብላ አስባለት ጠየቀችው፡፡

ፊቱ ላይ ላቡ ችፍ ብሎ ጠብታዎች ግንባሩ ላይ ሠርቷል፡፡ ጥርሱም
እየተንቀጫቀጨ ነው።

“በጥይት መተውኝ ነው!” አላት እና በፍርሃት ዓይን ያያት ጀመር፡፡

“በእግዚአብሔር ስም ማን ነው የመታህ? መቼ ነው ይኼ ነገር የተከሰተው?”

“ምናልባት አላማርኳቸው ይሆናል፡፡ ግን እነዚያ ሁሌም ስነግርሽ የነበሩት የሜክሲኮ ወሮበሎች ናቸው፡፡ ከዚህ ቀደም ቤቴ ገብተው የማስፈራሪያ ነገር መኝታ ቤቴ ውስጥ አስቀምጠው ነበር፡፡”

“ይህንን ደግሞ ፖሊሶች ጋር አመልክቼ ነበር፡፡ እነርሱ ግን እኔ ፈጥሬ የተናገርኩት ይመስል አላመኑኝም” አላት፡፡

ኒኪ ይህንን ስትሰማ ደነገጠች፡፡ ምክንያቱም እሷ ቤትም የሆነ ሰው
ከመኝታ ቤቷ ውስጥ የሚገኘውን የእሷና የባሏን የሠርግ ፎቶ እንደተወሰደባት ለፖሊሶች ብትነግርም እነርሱ ግን ችላ ያሉትን ነገር አስታወሰች፡፡

“እነርሱ እንደዚህ ቢያስቡም አያገባኝም፡፡ እናታቸውን... እኔ እውነታውን በደንብ ነው የማውቀው፡፡ በጥይት የተመታሁት ባለፈው ቅዳሜ ከክለብ ስወጣ ሌሊት ላይ ነው፡፡ በግምት ከሌሊቱ 7፡30 ላይ፡፡ ምናልባትም ይከታተሉን ስለነበር ያለሁበትን ቦታ አውቀውታል፡፡ እኔ ከክለቡ ወጥቼ መኪናዬን ፓርክ ያደረገው ሰው መኪናዬን እስኪያመጣልኝ ድረስ
እየጠበቅሁት ነበር፡፡ ይኼኔም አንድ መኪና ከአጠገቤ ቆመ እና ሁለት ሰዎች
ወጡ፡፡ አንደኛው ቅልጥሜ ላይ በጥይት ከመታኝ በኋላ መኪና ውስጥ
ገብተው መሬት ላይ ጥለውኝ ሄዱ፡፡”
ካርተር የደረሰበትን ነገር በፍጥነት ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ አሁንም
የደረሰበትን ነገር እያስታወሰ ጥርሱን ሲያንቀጫቅጭ ኒኪ ተመለከተችው፡፡

“በጥይት ሲመቱህ በአካባቢው ላይ ማንም አልነበረም?” ብላ ጠየቀችው፡፡
ካርተርም ጭንቅላቱን በአሉታ ወዝውዞ “ማንም አልነበረም ብቻዬን ነበርኩኝ፡ መኪናዬን ያቆመው ልጅም መኪናዬን ካቆመበት ቦታ ሊያመጣ ሄዶ ነበር፡፡ እሱ መኪናዬን ይዞ በመጣ ጊዜ እኔ መሬት ላይ ወድቄ ደሜን እያዘራሁ ከመሆኔም በላይ ራሴንም በመሳት ላይ ነበርኩኝ”

“መልካም” አለች ኒኪ፡፡ እንደሰው የነገራትን ነገር ማመን ይኖርባታል።
ምክንያቱም እሷን ለማሳመን ብሎ እግሩን በጀሶ እንደማያጅል ይገባታል፡፡
ምናልባት እንኳን የነገራት ነገር ውሽት ቢሆን እንኳን የራሱን ቅልጥም
በሽጉጥ መትቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ይህንን ለምን ያደርጋል? አትኩሮት
ፍለጋ ነው? ካርተር ደግሞ በዚህ መልኩ በሽታው ብሶበታል ብላ ኒኪ አታምንም፡፡ ምክንያቱም የባንክ ሥራውን በአግባቡ እየሰራ መሆኑን ታውቃለች

ስለሜክሲካኖቹ የወሮበሎች ቡድን በየጊዜው የሚያወራትን ነገር
ተጨባጭነት ባለው ምክንያት ሳያረጋግጥላት በጥይት ቅልጥሙን መቱት የሚለውን
👍2
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል


...ጋሻዬነህ ጌታነህ ይባላል» ብላ ጸጥ አለች። ከወዲህም ከወዲያም ከጣራውም ከወለሉም ላይ ድምፅ ስደት ገባ።

ከማን የተወለደ? የመቼው? የት የነበረ? ብላ የተሰደደውን ድምፅ መለሰችው:: ነገሩ በመፋፋሙና ጥያቄው በመድራቱ የመጣው ይምጣ ብዩ ዐይኔን ጨፍኜ ገባሁ፡፡

ምንም ሳልናር ተቀመጥኩ፡፡ ጋሻይነህ እናቴ እግሮች መካከል ቆሟል።
የውብነሽ ከእናቴ ፊት ለፊት ቆማ የአቤቱታ መልስ የሚጠባበቅ ድኃ መስላለች።እናቴ ዘወር ብላ ካየችኝ በኋላ ለዛ ባጣ ፈገግታ ገረመመችኝ፡፡ «የጌታነህማ ልጅ ከሆነ እሱው ራሱ ይናገር፣ ይኸው መጣ! አንቺ ምን ታጎበጉቢያለሽ» አለችና ዐይኖቿን ወደ ጋሻዬነህ መለሰቻቸው:: አቀረቀርኩ፡፡ ከንፈሮቼ ተጣበቁ፡፡

ያመጣኸውን ብታመጣ በደስታ እቀበልልሃለሁ፣ እፈጽምልሃለሁ ብለሽ
የአቦን ስም ጠርተሽ ምለሻል:: አሁን ወዲያ ወዲህ እንዳትይ! በዚህ ወጥቶ በዚያ ወርዶ ብሎ ነገር የለም፡፡ ታሪኩንና ሁኔታን ሁሉ ቀስ በቀስ ነገና ከነገ ወዲያ
እንዘረዝርልሻለን፡፡ አሁን ግን ምንም ምንም ሳትይ ይህን የአተር ክክ የመሰለ ልጅ ደስ ብሎሽ ተቀበይን፡፡ የሚያኮራና የሚያስደስት ነው:: ከዛሬ ስድስት ዓመት
በፊት የተወለደ የጌታነህ ልጅ ነው» ብላ በሙሉ ልብ ተዝናንታ ተቀመጠች፡፡
ከተሽከምኩት የሐሳብ ቀንበር ላይ ትንሽ ተጎርዶ ወደቀ፡፡ ደቂቃዎች ተውዘገዘጉ፡፡

እናቴ በሐሳብ ላይ እንዳለች ጋሻዬነህ ከእግሮቿ መኻል ሹልክ ብሎ ወጣና ትከሻዬን ይዞ ከጐኔ ቆመ:: ጉልህ መልስና ድንቅ ምስክርነት ነበር፡፡

እናቴ ወደ ጎን ዘወር ብላ ስታይ ሰርቀው ከሚመለከቷት ዐይኖቼ ጋር ተጋጨች፡፡ የእኔዎቹ ተሰበሩ፡፡ ፍርሃት ሳይሆን ትሕትና ሰበራቸው።

«ይሁና! አበጀህ! ደግ አረክ! ታዲያ ምን ኣለበት እንኳን ወንድ ልጅና፣ሴትም ልጅ ወልዳ ትመጣለች ! ቀና በል! የምን ማቀርቀር ነው:: ያንበሳ ግልገል
የመሰለ ልጅ ነው ያመጣኸው! እኔ እናትህ ባልምል ባልገዘትስ አንተን ልጄን
አሳፍርሃለሁ እንዴ? ደስ የሚል እንጂ የሚያሳፍር አይደለም፡፡ ያኔዬስ ቢሆን
መላውን አጥቼውና የሴት ነገር ሆኖ ተበሳጭቼ ነው እንጂ የኋላ ኋላ ሳልጠጣትና ሳያንገበግበኝ ቀርቶ መሰለህ: ሽንፍላችን ስስ ነው:: አንችልም! አንኳን አንድ ሁለትና ሦስት ቢሆንሳ? እስከ ዛሬ ድረስ ደብቀሽኝ በመኖርሀ ግን ቀስ ብለን እንወቃቀስበታለን» ብላ ጋሻዬነህን ወስዳ አገላብጣ ሳመችው። የደስታና የርኅራኄ እንባ ዐይኖቿ ላይ ተንቀዋለለ።

ጨምደድ ባለው ፊቷ ላይ የኃፍረትና የጸጸት ስስ ፈገግታ ታየ። አምጣ አምጣ እንደ ተገላገለች ነፍሰ ጡር እኔም የሐሳቤን እትብት አስቆርጡ አፎይ
አልኩ፡፡

«አቤት እኔ! ይኸስ እውነትም እልል በይ የሚያሰኝ ነው፡፡ በል አንተ ትልቁ ልጅ
ደግሞ ሳመኝ፡፡ ምንስ ቢሆን ከጥጃይቱ በፊት እናቲቱ” ይሉ የለ፡፡ ከዚህ የበለጠ
ዓለም የት ይገኛል» ብላ ከመናገሯ እመር ብዬ ሄጀ ተሳሳምን፡፡ የውብነሽ በደስታ
ተፍነከነከች፡፡ ደሜ የፈንጠዚያ ግልቢያ ጋለበ። ዐይኖቼ በእናቴ በኩል የሚደረገውን የተስፋና የጉጉት ውጤት አፍጥጠው ተመለከቱ። በእናቴ የፍቅር
ሚዛን ላይ የዱሮው ጌታነህ ለመሆን ተቃረብኩ፡፡ ወንዙን ላደነቀ ምንጩን
ማሳየት አስፈላጊ በመሆኑ የጋሻዬነህን ምንጭ ማሳየት አስፈላጊ ነው፡፡

ተመስገን! ተመስገን! ክብርህ ይስፋ! እንኳን ለዚህ ያበቃኸኝ! ኖረህ ኖረህ ይህን የመሰለ ልጅ ይዘህልኝ ስትመጣ ምን ከፍቶኝ! አቦዬም ስለታቸውን አገኙ፡፡ ትንሽም ቅር የሚለኝ እንደ ወንድሞችህና እኅቶችህ ወግ ማረግ...አረ ምን አባቱ! ይሁን! ዞሮ ዞሮ ለዚሁ አይደል?» አለችና ከሕሊናዋ ጋር ለመግባባት አስተያየቷን መለወጥ ሞከረች፡፡ እንደ ወንድሞቼና እህቶቼ እንድሆንላት ስትመኝ የነበረው ምኞቷና ፍላጎቷ ሁሉ በዚህ ባልጠበቀችው ሁኔታና ኢጋጣሚ ከሰመ፡፡

«ደስ አለሽ? እኛማ በጣም ፈርተንና ተጨንቀን ነበር፡፡ እንዲህ በቀላሉ
ይቀናናል፣ እንዲህ ባለ ሁኔታ ይሳካልናል ብለን በፍፁም አላሰብንም ነበር?» ብላ
የእናቴን ኃይለኛነትና ትፈሪነት ለማስገንዘብ ሞከረች፡፡ እግረ መንገዷንም የእናቴ ስሜት ወደ እኛ እንዲያዘነብል ማጎሳመሷ ነበር፡፡

«እስኪ ተይኝ ልጀ! የዛሬዋን ደስታዩን ዝግ ብለን ልባችንን አስፍተን እንጫወታለን፡፡ ጌታነህ እንበሳ ከነነፍሱ ይዞልኝ መጥቷል» ካለች በኋላ ጋሻዬነህን
ለየውብነሽ ሰጥታ ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ሄደች። እኔና የውብነሽ በደስታ
ተቃቅፈን ተሳሳምን። ጋሻዬነህንም ለሁለት ኣንሥተን «አንተ ዕድለኛ» ብለን
በየአቅጣጫችን ያለውን ጉንጩን ስመን ወደየነበርንበት ቦታ ተመልሰን
ተቀመጥን። ሰው በደስታ ይፈነዳ ሲሆን ያለጥርጥር እፈነዳ ነበር። አንዲት
ሠራተኛ የእጅ ውሃ አምጥታ እንዳስታጠበችን እናታችን ገባች። ይኽነዩ ነበር የቀድሞው የየወዲያነሽ ሕይወት ትዝ ያለኝና መንፈሴ ስለ ባለቤቴ
የተሠቃየው:: በሌሎች ሁለት ሠራተኞች ደግሞ ምግብና መጠጥ በየተራ ቀረበ።
«የቤታችንን የሲሳይ ርጥበት አሳምሬ ስለማውቀው በቀረበው መስተንግዶ
አልተደነቅሁም፡፡
እህል ብቻ ሳይሆን የደስታ እንክብክብ ጎረስኩ፡፡ ባልገመትኩት አኳኋን ወኔና ብርታት አካበትኩ፡፡ አዲስ የኑሮ ተስፋ ከፊት ለፊቴ ተዘረጋ፡፡ አጋጣሚና
ድል የሚባለው ይኸ ይሆን? እስከ ማለት ደረስኩ፡፡ እናቴ ወደ እፏ ከላከችው
ይልቅ ለእኔና ለጋሻዬነህ ያጎረሰችን ይበልጣል። የጣቶቿ ጫፎች ከንፈሮቼን
እየነኩ ሲመለሱ የእናትነቷን ውድ ፍቅር እያቀበሉኝ ተመለሱ።

ጋሻዬነህ አካባቢውን ስለተለማመደው ያ በግርታ መጦ የነበረው ፊቱ እጥፍ ፈገግታ አንዠረገገ። ገበታው ከፍ ኣለ። የአዲሱ ግንኙነት ማዕድ ግን በሰፊው ቀጠለ። እናቴ ብርጭቆዋ ውስጥ የነበረችውን ጠላዋን ተጎንጭታ
ጉሮሮዋን ካራሰች በኋላ እናንተ ግን ምስጥ ናችሁ፣ ልባችሁ አይገኝም፡፡
የገረመኝ ደግሞ ሆን ብላችሁ አባታችሁ በሌለበት ቀን መምጣታችሁ ነው::
የናንተን ብልጠት ማን ያገኘዋል» አለችና ተንኮል የሌለበት ሣቅ ሣቀች፡፡

«ከአባታችን ይልቅ አንቺን በመጀመሪያ ብንጠይቅና ብናሸንፍ፣ አንቺ
ካየሽው በኋላ የምትይንን ለማወቅ ብለን ነው:: በተለይ የዛሬዋን ቀን ጠብቀን
የመጣነው» ብላ የውብነሽ በጠላዋ ውስጥ የምትታየውን የገዛ ፊቷን ምስል
ለማየት አንገቷን ወደ ብርጭቆው አሰገገችው።

«ኧረ ለመሆኑ አንቺ ይኸ ልጅ መወለዱን የሰማሽውና ያወቅሽው መቼ ነው?» ብላ መገረሟን በሚገልጽ ስሜት ጠየቀቻት። የውብነሽ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ «አጅሬ መች እንዲህ የዋዛ ሰው ነውና! እኔም ያየሁት አሁን በቅርቡ ነው:: ያም ሆነ ይህ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ የቀረውን ተይኝ» በማለት ወቀሳ የቦረቦረው ድጋፍ አደረገችልኝ። የጋሻዬነህ እናት ማንነት እና ስሟ ተጠቅሶ ባለመነገሩ በውስጤ የሚፈራገጠውን ጭንቀቴን አጠቃልዬ አልገደልኩም፡፡

«ኧረ ለመሆኑ እናቱ ማን ትባላለች? የማን ልጅ ትሆን? አልነገራችሁኝም እኮ?» ብላ ሁለታችንንም. በየተራ አየችን፡፡ እኔና የውብነሽ ተፋጠጥን! ይህን ለጊዜው በምሥራችነት የማይነገር ታላቅ ጉዳይ ማን ያርዳ?
የውብነሽ መልስ ለመስጠት አልዘገየችም፡፡ «የእናቱ ጉዳይ ግልጽም
??ስውርም ነው:: ከዚህ ቤት ይጀምርና ወደ ሌላ ሰፊ ሥፍራ ይጓዛል። ዳቦውን
ገምጦ ምጣዱን መጥላት አይገባም፡፡ የዚህ ልጅ እናት አንቺ እንደምትመኘው
የማንም ትልቅ ሰው ልጅ አይደለችም፡፡ በደፈናው የሰው ልጅ ነች፡፡ እስከ አሁን
ድረስ ፈርተናል ፣ተጨንቀናል፣ ከእንግዲህ ግን በቃ! የዚህ ልጅ እናት የመከራ
እሳት የለበለባት፡ የሥቃይ ቀንበር የተጫናት፣ የሰው ፊት እንደ እሳት ነበልባል
👍31👏1
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


....የዓመቱ መጨረሻ ስለሆነ ትምህርት ቤቷ የወላጆች ቀን በአሏን በማክበር ላይ ትገኛለች። ዘይኑ እንደተለመደው በደረጃ ከክፍሏ አንደኛ ወጥታ ወደ ስድስተኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ለአምስት አመታት ከጓደኞቿ ጋር የቦረቀችበትን ትምርት ቤት የመሰነባበቻዋ ዕለት ነበር። ሽልማቷን ብትቀበልም አይኖችዋ እምባ መቋጠራቸውን አልተዉም፡፡ እናቷም ረዳቻት።አብራት አለቀሰች፡፡ የጎበዝ ልጅ እናት መሆን እንዴት ደስ ይላል? ግራ
ቀኟ ለተቀመጡት ወላጆች የሷ ልጅ መሆኗን በኩራት ገለፀችላቸው::
“ጎሽ የተባረከች ልጅ እንጀራ ይውጣላት። ሴት ልጅ እንደዚህ ስትሆን መታደል ነው” በማለት አደነቁላት፡፡
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ከመስተንግዶው ጋር መሳ ለመሳ ሲጓዝ ቆየ።ዘይኑ የትምህርት ቤት ሰርተፊኬቷን አወጣች። መጪው መስከረም ነው፡፡ የመስከረም ወር ሳሩ ቅጠሉ ለምልሞ የሚታይበት አዲሱ ዓመት አዲስ
ተስፋን ይዞ የሚመጣበት የዘመን መለወጫ በመሆኑ ወዳድ
ዘመዱ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ የሚባባልባት ተወዳጅ ወር ናት፡፡ መስከረም "በአበባ አየሽወይ" የህፃናት ጣፋጭ ጣዕመ ዜማ የምታሽበርቅ ወር....

እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ፣
በአበቦች መሀል አሽብርቀሽ..
እየተባለች የምትወደስ የአዲሱ አመት መክፈቻ በር ዘይኑም ከሰፈሯ ልጆች ጋር በአዲስ ልብስ አምራና ተውባ "አበባ አየሽ ወይን" ትጫወታለች።
ባልንጀሮቼ ቁሙ በተራ፣
እንጨት ሰብሬ ቤት እስክሰራ፣
እንኳን ቤትና የለኝም አጥር፣
ከደጅ አድራለሁ ኮከብ ስቆጥር።
ኮከብ ቆጥሬ ስገባ ቤቴ፣
ትቆጣኛለች እንጀራ እናቴ...
በአንድ አውራጅ እየተቀባበሉ የሚፈነድቁባት የመስከረም ወር መጣች፡፡ ዘይኑ ይቺን በናፍቆት የምትጠብቃት "የአበባ አየሽወይ" በዓልን ሳታከብር ወደ ወንድሟ እንድትሄድ እናቷ ስለወሰነች የትምህር ቤት ጣጣዋን
ሁሉ ጨርሳ የአዲስ አበባ ተጓዥ መንገደኛ ሆነች፡፡ የምትነሳበት ቀን
ተቆርጦ ወንድሟ እንዲጠብቃት ተነገረው። በዚሁ መሠረት አቶ አለሙ ይዘዋት ሊሄዱ ተነሱ... በዚህ ጊዜ እናትና ልጅ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው ተላቀሱ፡፡ ልጀቿን ወደ አዲስ አበባ ሸኝታ የጨረሰችው እናት ብቻዋን ልትቀር እጅግ የምታፈቅራት ሴት ልጅዋን መሸኘት ግዴታዋን ሆነ።

"በሄድሽበት ሁሉ እንደ ማር እንደ ወተት ጣፍጪ። አንድ ቀን እንኳ
እንደ ትንሽ ልጅ ተሳስታ ሰው ሳታስቀይም ሁሉን እሺ እንዳለች ለሁሉ እንደታዘዘች" ሊሸሿት የመጡት በሙሉ አድናቆታቸውን እየገለፁ እሷንም እንደ ወንድሟ መረቋት፡፡
እናት ከዐይኖችዋ ያለማቋረጥ የሚፈስ እንባዋን በነጠላዋ ጫፍ ቶሎ ቶሎ እያበሰች ልትሸኛቸው አብራ ተነሳች። አውቶቡሱ ረጅም ጡሩምባውን አሰማ፡፡ "ፑም! ጥም! ፓም! ፓም!እረም!.. እረም!” አለና በጢስ ማውጫው በኩል ጥቁር ጥጥ የመሰለ ወፍራም ጢስ ትጉልል አድርጎ
አስወጣ፡፡ ያንን የመኪናውን አሸባሪ ተዘጋጁ! ተዘጋጁ! የሚለውን ድምፅ ስትሰማ እንደ አዲስ ልቧ ሽብር ሽብር አለባት። አንጀቷ ተላወሰ፡፡ጣፋጫ ትንሽዋ ዘይኑ ልትሄድ ነው፡፡

በሉ እንግዲህ ጋሼ ዓለሙ እሱ ፈጣሪ ይከተላችሁ በደህና ግቡ...”ልጇን እቅፍ አድርጋ ለመጨረሻ ጊዜ ስማ ተሰናበተቻቸው። አቶ ዓለሙ
በቶሎ ብለው ዘይኑን እጅዋን ያዙና ወደ መኪናው ገቡ፡፡ ዘይኑም እንባዋን እያፈሰሰች በመስታወቱ ፊቷን ብቅ አደረገችና እናቷን አይን አይኗን አየቻት። ከዚያም ትንሿን እጅዋን አውለበለበችላት...
ቻዎ! ቻዎ! ባይ! ባይ! እማምዬ..” መኪናው ተንቀሳቀሰ፡፡ እናት ወገቧ
እየተንቀጠቀጠ እግሯ እየተብረከረከ ስለተቸገረች በቆመችበት ቦታ ላይ ቁጢጥ አለች።
"ምነው አመመሽ እንዴ?" አሉ ጎረቤቷ ወይዘሮ ተዋበች። መልስ አልሰጠቻቸውም፡፡ መናገር አቃታት።
"በይ በርቺ ከንግዲህ አንቺም ወደዚያው ወደነሱ መጠቃለልሽ አይቀርም፡፡ እስከዚያው ድረስ ግን ብቸኝነቱን ጠንከር ብለሽ መቋቋም አለብሽ አውቶቡሱ እየተመዘገዘገ ጉዞውን ወደ ፊት ቀጠለ... ዳገት ቁልቁለቱን
ጋራ ሽንተረሩን ጫካና ሜዳውን እያቆራረጠ ወደ ፊት ተወነጨፈ
የባሌ ደን መቼም ለጉድ ነው፡፡ ዘይኑ የደኑን ውበት እያደነቀች አሻግራ የምታያቸው ዛፎች ሁሉ እየተነሱ የሚፈርጡ እየመሰላት
እየተገረመች ሰብስቤ ዋሻ ደረሱ፡፡ ሰብስቤ ዋሻን ቁልቁል ስትመለከተው ፍርሀት ፍርሀት አላት። እዚያ ግድም ሰማይ ተገምሶ የወደቀ ይመስላል። ከላይ ወደ ታች የሆነ ነገር ቢወረወር መሬት ለመድረስ ሳምንት የሚፈጅበት ይመስላል። መኪናው ወደ ፊት ነጎደ

"ሙጨዮ በረከቴ ኢጀ በዳ ሲንላለን! የተባረክሽ ልጅ ክፉ ዐይን አይይሽ.."እያሉ የሚመርቋት የሚወዷት ጎረቤቶቿ ትዝታ ከእናቷ ትዝታ ጋር በዐይኖቿ ላይ እየተንቀዋለለ የተራራውንና የሜዳውን ግልቢያ አሻግራ
ስትመለከት እየተደነቀች ወደ አዲስ አበባ ወደ ወንድም ጋሻዋ ከነፈች…..መኪናው በየመንገዱ ላይ እየቆመ ሸንኮራ አገዳ፣ ብርቱካን፣ ሙዝ፣ፓፓያ ለመሽጥ የሚሮጡ ልጆችን እያስተናገደ ተሳፋሪው በመስታወቱ አንገቱን ብቅ እያደረገ እየገዛ እየተቋደሰ ጉዞው ቀጠለ...

"ይህችን! ይህችን ጣፋጭ ብርቱካን! መንደሪን!. . ሙዝ አለ ሙዝ! አለ ሙዝ! ሽንኮራ ጣፋጭ ሸንኮራ አገዲ!" ሁሉም የሚሸጡትን እያወደሱ ከጣዕሙ የበለጠ በቃላት እያጣፈጡ ለመሸጥ ይሯሯጣሉ። መኪናው
በዚህ ሁኔታ ሲጓዝ ውሎ ሻሽመኔ ከተማ ደረሰ፡፡ አቶ አለሙ ዘይኑን
ይዘው ምሳ ለመብላት ወደ ኢየሩሳሌም ሆቴል ገቡ። ሆቴሉ በተስተናጋጅ እንግዶች ተጣቧል፡፡ አስተናጋጆችም ወዲያና ወዲህ ይሯሯጣሉ።
“ሄይ! ምነው ቶሎ በል እንጂ! ለአዳር አልመጣንምኮ?!"
“ምነው ባክህ ገና እያረዳችሁ ነው እንዴ? የበሰለ ወጥ ጨልፎ ለማምጣት እስከዚህ ድረስ?!.
“ከኛ በኋላ የገባው ስንቱ ተሸኘ በናታችሁ? ስማ ወንድም! መኪና ጥሎን ይሄዳልኮ ያንተን ሩጫ ለማየት አልመጣንም " ከሁሉም የሚሰነዘራውን ወቀሳ የሚስማው አስተናጋጅ.."እሺ ጌታዬ ይደርሳል አሁኑኑ አመጣለሁ" ለዘገየበት ይቅርታ ጠይቆ ይከንፋል። ደግሞ ይሮጣል.እሺ! እሺ! ማለቱ ተመጋቢውን ከንዴቱ ትንሽ መለስ ያደርገዋል። የተባረከ አስተናጋጅ በመሆኑ እንጂ እንደ ሌሎቹ ቢሆን ኖሮ ያንን ሁሉ ወቀሳና ዘለፋ
በትዕግስት አያሳልፈውም ነበር፡፡ ደንበኛን ላበሳጩበት ደመወዝ የሚከፈላቸው የሚመስላቸውን ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ ለስድብ የሚጋበዙም ሞልተዋል፡፡ይሄኛው ግን ፍፁም የተለየ ነው፡፡ ዘይኑ የአቶ አለሙን ጉልበት ተደግፋ የተመጋቢዎቹን ሁኔታ“ የአስተናጋጆቹን ሩጫ ስትመለከት
ደስ አላት። አይታው የማታውቀው ድራማ ነበር፡፡ ዘይኑና አቶ አለሙ
ተራቸው ደርሶ አስተናጋጁ ያመጣላቸውን ምግብ ከበሉና ለስላሳቸውን ጠጥተው ጥቂት እረፍት ከወሰዱ በኋላ መኪናው ለመንቀሳቀስ ጥሩምባውን አሰማ፡፡ በጊዜ የተጠናቀቀው በፍጥነት ብድግ እያለ ሲወጣ የዘገየው ደግሞ ሁለቴና ሶስቴ ይመላለስበት የነበረውን በአንድ ጉርሻ እያጠቃ በፍአጥነት ተነሳ ፡፡ ከዚያም ጉዞው ቀጥሎ ሞጆ ከተማ ደረሱ፡፡

“እንግዲህ አዲስ አበባ ልንገባ ደርስናል ወንድም ጋሼሽን ልታገኝው ትንሽ ነው የቀረሽ፡፡ ደስ ይበልሽ!” አሏት፡፡ ዘይኑ ፊቷ ፈካ ።
👍2
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

...ሔዋን ግን ወዲያው ሀሳብ ውስጥ ገባች። ዓይኖ ሰማይ ላይ ተተከሉ ልቧ አድማስ ተሻግሮ ሄደ። አጠገቧ ያሉትን እናቷ ረሳቻቸው። በሆዷ እያወራች ከንፈሯቿም ይንቀሳቀሱ ጀመር።

«እሙዬ» ሲሉ እናቷ አሁንም ከሃሳቧ ቀሰቀሷት::
«አቤት እማ»
«አኪሙ የነገረሽን ረሳሽው? ብዙ ማሰብና መጨነቅ እኮ ይቺን ልብሽን ታባብስብሻለች ብሎሽ ነበር። እኔም ስታስቢ ሳይሽ እሰጋለሁ። ታድያ አንዳንዴ እንኳን ቀልብሽን ሰብሰብ አድርገሽ ሀሳብሽን መርሳት ብትሞክሪ ምን አለበት የኔ ልጅ? አሏት በሀዘን አስተያየት መልከት እያሏት::

«አይዞሽ እማ! አትጨነቂ ብዙም አላስብ። አልጨነቅም!» አለቻቸው አንገቷን ወደ መሬት ደፋ አድርጋ።
«አየየ…እሙዬ! ሁኔታሽንማ እያየሁት አይደል! መጨነቄማ
ምን ይቀራል ብለሽ የኔ ልጅ?»
አሏት በትካዜ አነጋገር።
ተይ እማ፡ እንደዚህማ ከሆነ እኔም የባሰ እጨነቅብሻለሁ! ባይሆን እኔም ማሰቤን እተዋለሁ። አንቺም እትጨነቂብኝ፡፡» አለቻቸው ዓይን ዓይናቸውን እያየች።
«እባክሽ እሙዬ እባክሽ! እንደው በአጠባሁሽ ጡት ገዝቼሻለሁና ይህን ሃሳብና ትካዜ የሚባል ነገር እርግፍ አድርገሽ ተይልኝ! የኔ ልጅ እባክሽ» አሏት እናቷ አይናቸው እንባ እስኪአቀር ድረስ ጭንቅ እያላቸው።
«ተይ እማ! በጡትሽማ አትገዝችኝ ጡትሽ እኮ ለኔ የአንቺነትሽ መገለጫ ነው የእኔነቴ መሰረት ነው። ጡትሽ እኮ ስጋና ደሜ ነው ለዚያውም አስተዳደጌን እንደነገርሽኝ ለዚያን ያህል ዓመት የጠባሁት፡፡ ስለዚህ እማ! ግዝትሽን አወርጅልኝ ድንገት ተሳስቼ ሀሳብ ውስጥ የገባሁ እንደሆነ ግዝት መተላለፌ ሲሰማኝ ይበልጥኑ እጨነቅብሻለሁ እማ! አሁኑኑ ግዝትሽን አንሺልኝ እባክሽ የኔ እናት » ስትል እጆቿን እያርገበገበች ተማፀኘቻቸው።
«እሺ የኔ ልጅ፣አወርጄልሻለሁ ::" አሏት እንባቸው ከዓይናቸው ላይ እየወረደ።
«እወድሻለው እማ!» አለችና ሄዋንም እንባዋን ከዓይኗ ላይ
ትጠርግ ጀመር፡፡ ለአፍታ ያህል በመሀላቸው ፀጥታ ሰፈነ።
«ግን እሙዬ!» ሲሉ እንደገና ጠሯት።
«አቤት እማ!»
«እንደው ለዛ ልጅ ደብዳቤ ፅፈሽለት ታውቅያለሽ?» ሲሉ ጠየቋት ወደ ዛሬዋ ዋና ጉዳያቸው
ጠጋ ጠጋ ለማለት ፈልገው፡፡
«ለማን ለአስቻለው?»
«እ»
«የት ብዬ እማ! አድራሻውን ባውቅማ ኖሮ ደብዳቤ ከመጻፍ ይልቅ…» ብላ ንግግሯን ቆም ስታደርግ እናቷ ቀጠሉ።
«አዎ የኔ ልጅ! ሀሳብሽ ገብቶኛል፡፡ እንኳን አንቺ እኔ ራሴ ብርርር ብዬ
ሄጄ የሆነውን ነገር እጠይቀው ነበር፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፣ የሄደበት አገር አጉል አጉል ሆነ፣ ምን ማድረግ እችላላሁ የኔ ልጅ!?» አሏት በሀሳብ ከጎኗ መሆናቸውን ለማረጋገጥ።

«ኤርትራ ትሄጂ ነበር እማ?»
«ለምን አልሄድ እሙዬ ለምን አልለፋ ለምን አልንክራተስ እኔ
እኮ ነገሩኝ ሁሉን ገብቶኛል። ሁሉን ነገር በእነኛ ወርቆች ዓይን አደል ያየሁት» አሉ ታፈሡን በልሁንና መርእድን በማስታወስ። ቀጠሉና «ያየሁት የልጁ ወትግራፍስ ቢሆን በቀላሉ የሚረሳኝ ሆኖ ነው? ባልወልደውም ልጄ ይመስለኛል። እንደ ወለላ የረጋ መሆኑን አውቄዋለሁ!» አሏትና እንባቸውን ከዓይናቸው ላይ ጥርግ አረጉት፡፡

በዚህ ጊዜ ሔዋን ያ ሽዋዬ ለአባትና ለእናቷ የጻፈችባት ደብዳቤ አላት።በዚያ ምክንያት በእሷም ሆነ በአስቻለው ላይ አድሮ የነብረ ስጋት ታሰባትና
ዋይ ዋይ! አለች በሆዷ። ምነው ይኸን የእናቴን ሀሳብ አውቄው ቢሆን አስቹ።

ያኔ እንዲያ እየተጨነኩ ሳስጨንቅህ! እንዲያ እያለቀስኩ ሳስለቅስህ ያን ያህል ስለኔ ስትጨነቅና ስትጠበብ ኖረህ ዛሬ እናተረ ለአንተ ያላትን እምነትና ግምት አውቀኸው ቢሆን ኖሮ ምንኛ ደስ ባለህ ነበር? የቆሰለ መንፈስህ እንዴት በሻረልህ ነበር?
ግን ምን ዋጋ አለው? ያ ሁሉ ሲሆን ቆየና የዛሬው እድልህ እንዲህ ሆኖ ቀረ አስቹ?
የ'ኔ ሆድ ምን ላርግህ! የኔ ፍቅር እንዴት ልሁንልህ፡ በማለት ውስጥ
ውስጧን ስታስብና ስትብሰለሰል ቆየችና ድንገት ለቅሶ ፈንቅሏት እህህህ ….» በማለት ተንሰፈሰፈች።
«አንቺ እሙዬ» አሉና እናቷ ድንግጥ ብለው ከመቀመጬቸው በመነሳት ወደ እሷ ሮጡ።

«እማ ተይኝ!» አለች ሔዋን ፊቷን በጭኖቿ ላይ ድፍት አድርጋ እየተንሰቀሰቀች።

«እባክሽ እሙዬ እባክሽ የኔ ልጅ እባክሽ! አረ እንደው እባክሽ?» በማለት አንገቷን እቅፍ አድርገው እሳቸውም እያለቀሱ ይለምኗት ጀመር፡፡
ሔዋን ግን እሺ አላለችም። «እንቺ የማታውቂው ብዙ ነገር በሆዴ አለ እኮ እማ! » አለች አሁንም እያለቀሰች፡፡ በዚያው ቀጠለችና አስቻለው እኮ አብሮኝ የቆየው እያለቀሰ ነው እማ ትቶኝም የሄደው እያዘነ ነው እማ አስቻለው እኮ እኔን ሲል ያላየው መከራ የለም እማዬ! ያልቀመስዉ አበሳ የለም እኮ ወደ ኤርትራ እንዲሄድ ያደረኩት እኔ እራሴ ነኝ እማ! በዚያ ላይ የሄደበት አገር ጦርነት ነው።
የዋይታና የኡኡታ ምድር ነው፡፡ አስቻለው እኮ የሚታየኝ በዚህ ሀሉ የስው ልጅ አበሳና መከራ ውስጥ ሆኖ ነው።አስቻለው ሁል ጊዜ ሲደማ ይታየኛል ሁልጊዜ ሲቆስል ይሰማኛል፡፡ አንዳንዴማ ሞቶ ሬሳው በአውሬ ሲጎተት ይታየኛል፡፡
ስቃዩ መከራው ሁሉ በእዝነ-ልቦናዬ ውስጥ አልጠፋ አለ እማ! ታዲያ እንዴት ላድርግ እማ? እንዴት ልሁነው እማ እንዴትስ አይጨንቀኝ እንዴትስ አይጥበበኝ እማ!» አለችና እሁንም «እህህህ…» በማለት በለቅሶ ተንሰፈሰፈች።

«እሱን ማሪያም ትጠብቀዋለች የኔ ልጅ እመዬ እባክሽ አታልቅሽብኝ፤
እባክሽ በአጠባሁሽ ጡት! እሙዬ አሁን ዝም በይ በቃ ተይው የኔ ልጅ» በማለት እናቷ እየተርገበገቡ ለመኗት
ሔዋን ግን ለቅሶዋ ሊበርድ እንባዋ ሊቆም አልቻለም፤ አሁንም እያለቀሰች «እት አበባ እኮ፣ እት-አበባ እኮ..» ብላ ልትቀጥል ስትል ነገሩን ተወት አደረገችው፡፡ አንደበተ ቁጥቧ ሔዋን የቱንም ያህል ያስከፋቻት ቢሆን ሽዋዬን
በእናቷ ፊት መውቀስ አልፈለገችም፡፡ ብቻ እንጀቷ እስከሚሰፈሰፍ ድረስ አሁንም
በለቅሶ ተንሰቀሰቀች።
እናቷ ግን ገብቷቸዋል፡፡ «እሷን ተያት እውዬ! ያቺን አረመኔ ተያት የኔ ልጄ ያችን ጨካኝ ተያት እሙ
እኔ ገብቶኝ የለ! ተረድቼው የለ!
እባክሽ የን ልጅ ማልቀሱ አይጠቅምም።እባክሽ ዝም በይልኝ!» ሲሉ ተማፀኗት እሳቸውም እያለቀሱ።

«እ...እሺ እማ፣ ዝ..ዝም እላለሁ ቁጭ በይ!» አለቻቸው ድምጿ፤ በሲቃ እየተቆራረጠና በእንባ የራሰ ፊቷን በመጠራረግ።
የሔዋን እናት እያለቀሱ አጠገቧ ቁጭ አሉና ዓይን ዓይኗን ያዩት ጀመር። ከትንሽ ቆይታ በኋሳ ሔዋን በረድ እያላች መጣች። ለአፍታ ያህል ፀጥታ ሰፈነ ግን ደሞ ሔዋን ሀሳብ ውሰጥ ገባች ያን የሰሜን ኢትዮጽያ ክፍል በሃሳብ ትዳስሰው ጀመር ወደዚያ ለመሄድ እንዳታስብ እንኳ እንቅፋት የሆናትን ስለ አካባቢው ያላትን ግንዛቤ ሁሉ ታሰላስል ጀመር።
አዎ፤ ያ ሰሜን ኢትዮጵያ! የጥንት ስልጣኔ መነሻ፤ የውጭ ወራሪዎች መግቢያ መውጫ! በዘመናቱ አንገታቸውን ብቅ እያረጉ ሲሰልሱት የኖረና እያወደሙም ቢሆን የወደሙበት የዘመናት የጦር አውድማ! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፣የውጭ ወራሪዎች በፈጠሩት መዘዝ ወንድም ከወንድሙ እየተጋጨ አንተም ተው አንተም ተው' የሚል ጠፍቶ የእርስ በእርስ መጨራረሻ ሆኖ የቀረ የደም መሬት ያ
👍71
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....ከንስሐ ስትወጣ መቅሰፍት ተከተላት። እሷና ኢያሱ በነገሡ በአስራ ስድስተኛ ዓመታቸው ላይ አንድ ጠዋት ምንትዋብ ወደ ጸሎት ቤት ልትሄድ ስትዘጋጅ፣ አንደኛዋ ደንገጡሯ መጥታ፣ “ኧረ እቴጌ ሰማይ ምድሩ ዕርድ መስሏል” አለቻት፣ ቢጫ ስለለበሰው ሰማይና መሬት።

“እንዴት?”

“እንዲህ ዕርድ ሲመስል በነገታው አንበጣ ይወራል አሉ። ደሞም
ንፋስ እየነፈሰ ነው፣ ሰማዩም ደመና አዝሏል። ሁለቱም ነገሩን
ያባብሱታል።”

ፈጠን ብላ ወደ መስኮቱ ሄደች ምንትዋብ። እውነትም የጐንደር
ሰማይ ቢጫ ሆኗል። አፏን በእጇ ይዛ፣ “ምን ጉድ ነው? ምን ይሻላል?” አለች።

“እግዚኦ ማለት ነው እንጂ ሌላ ምን አለ?” አለች፣ ደንገጡሯ።

ኢያሱ መቸም ይሰማል... ይነግሩታል ኣለች ምንትዋብ፣ ለራሷ።

ካህናቱ በፍጥነት ጸሎት እንዲይዙ መልዕክት ላከችባቸው። ጸሎት
ቤቷ ለመሄድ ወጥታ ተመልሳ እልፍኟ ተቀመጠች። ሰማይና ምድሩ እንደዛ ሆኖ ስታየው አስፈራት።

በማግሥቱ የአንበጣ መንጋ ሰማዩን አለበሰው። የአንድ ቀን ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀናት በመቆየቱ ቤተመንግሥትም ጐንደርም ተጨነቁ፤ተጠበቡ። ሕዝቡ፣ “እግዚኦ” አለ። ታላቅ መቅሰፍት እንደመጣ አመነ።
ምሽት ላይ ሳይቀር አንበጦች ሰማዩን አንለቅ አሉ። ከባድ ዝናብና
ንፋስ ወረራውን አባባሱት።
ውሎ አድሮም ሰብል ተበላሽ። እየቆየ ሲሄድ ጐንደር ትልቅ ችግር
ላይ ስትወድቅ፣ ሕዝቧንና እንስሳዋን ረሐብ አጠወለገው፤ በሽታ አጣደፈው። ቀናትና ወራት እያለፉ ሲመጡ ቀባሪ እስኪጠፋ ሙታን በየወደቁበት ቀሩ። የተረፉት ከነገሥታቱ ጀምሮ በኃይለኛ ጉንፋን ተያዙ። እንዲህ እያለ ሁለት ዓመት አለፈ።
ሰዉ ካደረሰበት ጉዳት ገና ሳያገግም፣ ተምች በመመለሱ ችግር ብቻ ሳይሆን፣ ከቀድሞው የበለጠ ረሐብ ገባ።

ጌታችን ወርዶ ከባሕር፣
ኣዳምን ዋና ሊያስተምር፣
አፋፍ ላይ ሁነን ብናየው፣
እያጣ አለቀ ሰው።

ተብሎ እንደተገጠመው ሁሉ ጐንደርን ጨምሮ በደጋም በቆላም ሰው አለቀ። ከቤተመንግሥት የተቻለውን ያህል የእህል እርዳታ ቢደረግ እያደር ዐቅም አነሰ። የቻለ ጐንደርና አካባቢዋን ጥሎ ተሰደደ ::መሬቱን፣ ንብረቱንና ደብሩን ጥሎ መሄድ ያልሆነለት ለረሐብና ለበሽታ ተጋለጠ።

ጐንደሬዎች የሕይወት ምልክቱ ከፊታቸው ላይ ጠፍቶ ባዶው ላይ
አፈጠጡ። ከንፈራቸው ሐሩርና ውርጭ የመታው ይመስል ከስሞ፣
ቆዳቸው ተሰነጣጥቆ፣ የአንገታቸው ቆዳ ተንጠልጥሎ፣ የጉንጫቸው አጥንት አፈንግጦ፣ የሰለሉ እጆችና እግሮቻቸውን ማንሳት ተስኗቸው በረሐብ፣ በጥምና በበሽታ ተንጠራወዙ።

መከራ በሰዎች ገጽታ ላይ ግዘፍ ነሥቶ ታየ።

ለእናት፣ ለአባትና ለልጅ ቀባሪ የሚሆን ዐቅም ጠፍቶ ጐንደሬዎች
ዐይናቸው ቦዞ፣ እንባቸው ደርቆ፣ እጅና እግራቸው ዝሎ ተቀመጡ።
ትናንት ስቀው፣ ወደው፣ ጠልተው ከቶውንም በልተው የማያውቁ
መሰሉ። ዛሬ ተስፋቸውን ተነጥቀው ከሞት ጋር ተፋጠጡ። ነገ የእነሱ እንዳልሆነች አውቀው እጃቸውን ለሞት ሰጡ።

ሞት፣ ያ የሰው ልጅ የቁም ቅዠት አላስደነግጥ አለ። እንደተራ
ነገር ተቆጠረ። ጐንደሬዎች የሚዘክራቸው መላዕክትና ቅዱሳን ሁሉ ወዴት እንደሄዱ ጠየቁ። የእግዚአብሔርንም መኖሪያ አጠያየቁ። እንደ ዳዊት፣ “ጆሮን የፈጠረ አይሰማምን? ዐይንን የፈጠረ አያይምን?” ብለው
አቤቱታ አስገቡ። ሕጻናት ጡት አፋቸው እንደሸጎጡ እናቶቻቸው
እቅፍ ውስጥ ለዘላለም አሽለቡ።

ጐንደር ጉልበቷ ዛለ።

“ግዝየ ምንድነው?”

1748 ዓ.ም ለምንትዋብ ሆነ ለሃገሪቱ ጥሩ ዓመት አልሆን አለ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በጽኑ ታመመ። እናቴ ትጨነቃለች ብሎ
መታመሙን ደበቀ። ለሀያ አምስት ዓመታት ከእናቱ ጋር በስምምነት፣
በምክክርና በሰላም የገዛው ዳግማዊ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሐሙስ ሰኔ 21 ቀን ዐረፈ። የሕመሙ መንስኤ ባይታወቅም፣ የግራዝማች ኢያሱ እኅት የወንድሟን ደም ለመበቀል መርዝ አብልታው ነው የሚል ወሬ
ጐንደር ውስጥ ተዛመተ፡፡

አሳዛኙ ዜና ለምንትዋብ ደረሳት። ስትበር ልጂጋ ሄደች።
የምትሳሳለት ልጇ በሞት ተለይቷታል። ጉልበቷ ከዳት፤ መቀነቷን ፈታች። ጮኸች። አበደች። “ወዮልኝ ልጄ! ወዮልኝ ውዱ ልቼ! የዐይኖቼ ብርሃን! የልቤ ደስታ! ወዮልኝ ልጄ” እያለች ደረቷን ደቃች፣እየወደቀች ተነሳች፣ ፀጉሯን ነጨች፤ ፊቷን ቧጠጠች።

“የላስታን ዓቀባት ያለፈረስ ያለበቅሎ የወጣህ፣ እንዴት ታሰረ
እግርህ። አገር አንድ ለማረግ እንዳልጣርኸው፣ ጫካ ገብተህ አድነህ እንዳልመጣህ፣ ኸነብር ኻንበሳ ጋር ተጋፍጠህ እንዳላሸነፍህ፣ አሁን ማን እግርህን በገመድ አሰረህ?” እያለች አነባች።

ራሷን እስከመሳት ደረሰች።

“ያ እንደ አንበሳ ሚያስገመግመው ድምፅህ የት ጠፋ? ምን ነበር
እመምህ? መታመመህን ያልነገርኸኝ ምን ሁነህ ነው? ያላንተ ማን አለኝ? የአባትህ ዐደራ ነህ። አንተ ለኔ አባቴ፣ እናቴ፣ እህቴ፣ ወንድሜ፣ ጋሻ መከታዬ፣ ክብሬ፣ ሁሉ ነገሬ ነህ። አሁን ምን ይበጀኛል ልዤ? ኸንግድህ እንዴት ልኖር ነው? እንድህ አልጋ ላይ ተኝተህ ኸማይህ ሞቶ መቀበር ይሻለኝ ነበረ” እያለች ጮኸች።

ወዳጅ፣ ዘመድ፣ መኳንንትና ሌሎችም ለመያዝ አቃታቸው።
“ጠንካራው ማንነትሽ የት ኸደ? እርጋታሽ... አስተዋይነትሽ የት ኸደ? አሁንም ይች አገር ባንቺ ዠርባ ላይ ናት። እንምከር... ሁሉንም ነገር በቅጡ እናርገው” ሲሉ ተማጸኗት።

እሷ ግን መጽናናት አልሆነላትም።

“ማነው እንዳንተ ኸንጉሥ የተገኘ ዠግና ወንድ ልዥ፣ ለጠላቶቹ
ማይመለስ፣ ክንዱ ማይዝል? እንዳንተ ይቅር ባይ፣ ማነው እንዳንተ በሃይማኖቱ ጽኑ? ለድኻ ሚራራ፣ ሚዘክር፣ ማነው? እንዳተ የድኻውን ሮሮ ሰሚ፣ ማነው እንዳንተ ፍርድ ጎደለ፣ ደኻ ተበደለ ብሎ ውነት ፈራጅ? ማነው እንዳንተ አገር ወዳጅ? እንዳተ የናቱን ምክር ሰሚ፣ ማነው? እንዳንተ ታላቆቹን ኣክባሪ፣ ማነው? እንዳንተ ሸጋ ማነው?
እንዳንተ ጥርሰ መልካም፣ እንዳንተ ዕንቁ፣ እንዳንተ ወርቅ ማነው?
አሁን ምን ላርግ? የት ልኸድ? የት ልግባ? ቀድሞ በሕይወትህ
አስደስትኸኝ፣ አሁን በሞትህ አነደድኸኝ” እያለች ዋይታዋ ማባሪያ ኣጣ።

በአጎቷ በደጅአዝማች እሸቴ ራስቢትወደድ ወልደልዑልን
አስጠራች። ወልደልዑል ሲሰማ ሲሮጥ መጣ፤ አበደ፤ ጨርቁን ጣለ።እንደ እሱ የኢያሱን መሞት ያልሰሙ መኳንንት መጉረፍ ሲጀምሩ፣ እንደገና ዋይታና ሰቆቃ ሆነ። ጩኸትና ዋይታ ከዳር እዳር አስተጋባ።

ጩኸቱና ዋይታው ወህኒ አምባ ከመድረሱ ቀደም ብሎ እልፍኝ
አስከልካዮች የብርሃን ሰገድ ኢያሱ አስከሬን ያለበትን ቤተመንግሥት ቆለፉ። ወልደልዑል በአስቸኳይ መደረግ ወዳለበት ነገር ትኩረቱን
አደረገ ምንትዋብን፣ “እቴ ብርሃን ሞገሳ ሆይ፣ ብርሃን ሰገድ
ልዥሽ በሕይወት ሳለ ምን ነግሮሽ ነበር? መንበረ መንግሥቱን ማን
እንደሚወርስ አልነገረሽም? ኸሦስቱ ልዦቹ ከአቤቶ አፅቁ፣ ከአቤቶ ኃይሉና ከአቤቶ ዋዩ መኻል የትኛው ይንገሥ አለ? የነገረሽ ኻለ እባክሽ ንገሪን” ሲል ወተወታት።

“ኸመቤት ውቢት የተወለደው አቤቶ ዋዩ በእኔ መንበረ መንግሥት ይቀመጥ። ዮዳኤ የሰባት ዓመቱን ኢዮአስን እንዳነገሠው እናንተም
ልጄን ኢዮአስን አንግሡት፤ እኔንም አባቴን በካፋንም ሊተካ ይችላል።
ምወደው እሱን ነው” ብሏል፣ አለቻቸው ሲቃ እየተናነቃት።

ወልደልዑል፣ የቅርብ ዘመዶችና የቅርብ መኳንንት በር ዘግተውና
በነፍጥ አስጠብቀው መከሩ። አቤቶ ዋዩ ወይንም ኢዮአስ ገና የሰባት ዓመት ልጅ ነበርና፣ “እቴጌ በነበረችበት ሥልጣን ትቀጥል” ብለው ወሰኑ።
👍14👏1