#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....የማለዳዋ የጥር ወር ፀሐይ በመሬት ወለል አካባቢ ከየሚዳው! ከየተራራው፣ ከየዛፉ፣ ከየቤቱ፣ ከየጉራንጉሩ ቀዝቃዛ አየር ጋር ትንቅንቅ ገጥማለች። ተፈጥሮ ራሷን በራሷ የምታስተካክልበትና የምትለዋውጥበት ተፈራራቂ ኃይል ስላላት ቀዝቃዛው አየሩ ቀስ በቀስ ተረታ። ለውጥ የተፃራሪ ኃይሎች የግብግብ ውጤት ነው::
በእኔ ሕይወት ውስጥ ግን ጎልቶ የሚጠቀስ ለውጥ ባለመገኘቱ ሕሊናዩ
እየቀዘቀዘ ከመሔድ በቀር የብርታት ለውጥ አልታየብኝም፡፡ ከመኝታዬ ተነሥቼ
ልብሴን ስለባብስ ሰውነቴ ቀነቀነኝ፡፡ እውነተኛዎቹ የሐሳቤ ቅንቅኖች ግን አንጎሌ ውስጥ ይርመሰመሳሉ። የሥራ ቀን ነበር፡፡
መንገዱ የሚያልቅልኝ ስላልመስለኝ ቀደም ብዬ ተነሣሁ፡፡ ወደ ሕጋዊ ፍርድ ቤት ሳይሆን ወደ ግፈኞች የመከራ ሽንጎ የምገሠግሥ መሰለኝ፡፡ ከአራት ኪሎ እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለውን ርቀት በሁለት ታክሲ አጠቃለልኩት፡፡
ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ጸሐፊዎች፣ ነገረ ፈጆችና ወኪሎች፣ ተሟጋቾችና አማላጆች፣ “ጫማ ጠራጊዎችና ሥራ ፈቶች፣ እንደየ ኑሮ ደረጃቸው ለብሰው ተራ በተራ ሁለትና ሦስት እየሆኑ በመምጣት የፍርድ ቤቱን አካባቢ የበጋ ወራት ገብያ
አስመሰሉት፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች የለበሱት ነጠላና ጋቢ በጣም ከመቆሸሹ የተነሣ
ዳግመኛ ታጥቦ የሚነጣ አይመስልም፡፡ ጥለቱ የተንዘለዘለ፣ ዐልፎ ዐልፎ አይጥ
የበላው ይመስል የተቀዳደደ፣ እንደ አረጀ ሻሽ አለቅጥ የሳሳ ልብስ፣ በተለያየ
የጨርቅ ዐይነት የተጣጣፈ ኮትና ሱሪ፣ ከታጠበ ብዙ ዓመታት ዐልፈውት እድፉ
እንደ ማሰሻ የተላከከበት ሱፍ ኮት፣ ከተወለወለ ወራት ያለፉትና የቆዳው ቀለም የተገጣጠባ ከወደ አፍንጫው በእንቅፋት አልቆ ቀዳዳው የደረቀ የዓሣ አፍ የመሰለ፡ ከወደ ተረከዙ ወይም ከወደ ጎኑ ባንድ ወገን ተበልቶ የተንጋደደ ጫማ፣
በፀሐይ ሐሩርና በውርጭ፣ በአቧራና በእንክርት ቀለሙ ጠፍቶ የነተበ ባርኔጣ፣
የለበሱ ያደረጉና የደፉ ሰዎች በተስፋ መቁረጥ ስሜት እዚህም እዚያም
ቆመዋል፡፡ ለአያሌ ወራትና ዓመታት የተንገላቱና የተጎሳቆሉ ባለጉዳዮች ናቸው::በረሃብና በጥማት በርዛትና በንዴት በመጎዳታቸው አብዛኛዎቹ ውርጭ ላይ ያደረ አንጋሬ ይመስላሉ፡፡ ሕይወታቸው በትካዜ በመሞላቱ የገጽታቸው ፈገግታ ደርቋል፡፡
ወዛቸው እንደ ቅቤ ቅል የሚቅለጠለጥ ፊታቸው በዶሮ ጮማ እንደተወለወለ የወይራ በትር የሚያበራ፣ ቦርጫቸው የመንፈቅ ርጉዝ መስሎ ሱሪያቸው መታጠቂያው ላይ የሪቅ አፍ የሚያህል፣ አለባበሳቸው ሁሉ በጣም ያማረና የተዋበ ደንደሳሞች፣ በየደቂቃው በሚረባና በማይረባው ሁሉ የሚሥቁ በጣም መሠሪ ሰዎች ከየቢጤዎቻቸው ጋር ሰብሰብ ከምችት ብለው አፍ ለአፍ
ገጥመው ያወራሉ። የያዙት የሰነዶች መያዣ ኮሮጆ እንደ ባለቤቶቹ የፀዳ ሲሆን
የልፋት እንክርት አልነካውም፡፡ የተሰበሰበውን ሰው በዝርዝር ሲያዩት እያንዳንዱ ብቻውን ቆሞ እጁን እያወራጨ ከራሱ ጋር ይሟገታል።
አብዛኛው ጨርቅ ለባሽ በሌላ ሰው ወረቀት እያስነበበ ይኽ ልክ ነው
የለም ይኽ ሐሰት ነው! ለዚህ በቂ ነቃሽ አለኝ! ያያት የቅድመ አያቴ ነው ይግባኝ እላለሁ፡ ከዳኛው ጋር ተዋውለው ነው። ወላዲተ አምላክን!” እያለ እሰጥ
አገባ ይላል። ሁሉም ከሕይወት ወዲያ ማዶ በውሸት ዓለም ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እንጂ በርግጠኛ ሕይወት በእውነተኛ ዓለም የሚኖሩ አልመሰሉኝም
የመጥፎ ነገር ጥቀርሻ በጥብጠው የጋቱኝ ይመስል አእምሮዩ ተጨነቀ፡፡
የማያቋርጠው የጊዜ ጎርፍ እየጋፈረ መጓዙን ቀጠለ። ደቂቃ የደቂቃ ርካብ ረግጣ እየተፈናጠጠች ላትመለስ ትጋልባለች።
ጎነ ረጂሙ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ግዙፍ ሕንፃ ታላቅ የመከራ ተራራ መስሎ ፊት ለፊት ተገትሯል። የማደርገውን ጥንቃቄ አሟልቼ አካባቢዬን ገልመጥ እያልኩ እያየሁ መለስ ቀለስ አልኩ፡፡ ጭንቀቴና ጥበቴ እንደ ሐምሌ ጥቁር ደመና ከብዶ አንጎሌ ውስጥ አንዣሰሰ። በውስጤ የነበረው ሥጋት በድኃ ገበሬዎች አዋሳኝ እንዳለ የከበርቴ እርሻ መስፋቱን ቀጠለ። ረፈደ።
በወታደሮች ታጅበው በእግራቸውና በመኪና የመጡ አያሌ እስረኞች
በተለየ ቦታ ሰብሰብ አጀብ ብለው ቆሙ። ገር ገጭ ገጭ ገጭ፣ ሲጢጢጢጢጢ !
ካካካካካኪ! የሚል ድምፅ የምታሰማ ቮልስዋገን መጥታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ጉልላት ነው። የየወዲያነሽ ቀነ ቀጠሮ በመሆኑ እኔና እርሱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት
ለመገናኘት ተነጋግረን ነበር። ድክምክም ባለ እንቅስቃሴ የመኪናይቱን ቋቋቲያም
“በር ከፍቶ ወጣና ጨበጠኝ፡፡
ለአራት ሰዓት ሩብ ጉዳይ እኮ ሆኗል እስካሁን አላመጧትም እንዴ?»
አለኝ፡፡ ከንፈሬ ተጣብቆና ምላሴ አልላወስ ብሎ ቢያስቸግረኝም የለም እስካሁን አላመጧትም» ብዬ ዝም አልኩ። ውካታ በበዛበት አካባቢ ጥቂት ዝም ብለን ቆምን። ትላንት ማምሻዬን ሦስት ባለሙያ ጠበቆች አነጋግሬ ነበር። ሁሉም የሰጡኝ መልስ በጣም ተቀራራቢ ነበር፡፡ ቢበዛ አምስት ዓመት” አሉኝ። እንተስ ምን ይመስልሃል?» ብሎ ዐይኔን ማየት ጀመረ።
«እኔ ምን ዐውቃለሁ፡፡ ማንም ቢሆን ከራሱ ላይ ይልቅ በሌላው ላይ
መፍረድ ይቀልለዋል። የፍርድ ሰጪዎቹን ማንነት ስታየው ግን አምስት ዓመት
የሚበዛ አይመስልም፡፡ ቢሆንም ለእኔና ለእርሷ እያንዳንዱ ደቂቃ የሕይወታችን
ማሻከሪያ ክፍለ ጊዜ መሆኗ ነው» ብዬ ዝም አልኩ፡፡
«መቼም ቢሆን» አለ ጉልላት ወደድክም ጠላህም ምን ጊዜም ቢሆን ሕግ አለ። በሕጉም የሚጠቀሙና ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁ አሉ። አህያና ጅብ
ባንድ ላይ ሕግ አያረፉም፡፡ ለጨቋኝና ለተጨቋት በአንድ ጊዜ በእኩልነት
የሚያገለግል ሕግ የለም፣ አልነበረምም፡፡ ሕግ ስለተፃፈ ብቻ ሕጋዊ አሠራር አለ
ማለት አይቻልም። እኔና አንተ ባለንበት ሥርዓተ ማኅበር ውስጥ እጀግ በጣም
አያሌ ባለሥልጣኖችና አጫፋሪዎቻቸው በልዩ ልዩ የእሠራር ስልትና ሥልጣን
ፈጠር ከለላ ከሕግ በላይ የሆኑበትና የሚሆኑበት ሁኔታ እንዳለ መዘንጋት
የለበትም፡፡ ስለሆነም ሕግ በትክክለኛው መንገድ በሥራ ላይ እስካልዋለ ድረስ
የሌለ ያህል ነው፡፡ ይህ ጉዳይ በስፋት የሚያነጋግግር ስለሆነ አሁን ከመጣንበት
ጉዳይ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የለውም። ወደ መጣንበት ጉዳይ እንመለስ፡፡
ስለዚህ በሚሰጠው ፍርድ እንዳትገረም፡፡ የበዛ ወይም ያነሰ ሊሆን ይሆናል» ብሎ
ወደፊት ተራመደ፡፡ ርምጃዬን ከርምጃው ጋር አስተካክዩ ተከተልኩት።
ከእኛ ትንሽ ራቅ ብሎ አንድ ብረት ሽፍን ባለ ጥቁር ሰሌዳ አረንጓዴ መኪና ቆሟል፡፡ ጉልላት መኪናውን አሻግሮ እየተመለከተ «ለምንድን ነው አልመጣችም ያልከኝ? ያ እኮ ነው የወህኒ ቤቱ መኪና» ብሎ ጥሎኝ ሔደ፡፡
አልተከተልኩትም፡፡
መኪናው ውስጥ ከተቀመጠው ሰው ጋር ምን እንደተባባሉ ባይሰማም ጉልላት ትንሽ ራቅ ብሎ ተነጋገሩ። ወዲያው ወደ እኔ ዞር ብሉ ና ቶሉ በሚል አኳኋን ጠቀሰኝ እና ሄድኩ፡፡ እስረኞቹ ወደሚገኙበት አካባቢ እንደ ደረስን ዐይኔ
ያካባቢው የብርሃን መጠን ያነሣት ይመስል የውበት ሃያ መስኮቶቿ ተሸጎሩ።
አጠርጠር ያሉና በሰፊ የካኪ ጨርቅ ስልቻ ውስጥ የቆሙ የሚመስሉ
የወህኒ ቤት ሴት ወታደሮች እያንዳንዳቸው አጠር ያለ ዱላ ይዘው ቆመዋል። በአቅራቢያቸው አምስት ሴቶች ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። የትካዜ እሳት ያነኮታቸው ይመስላሉ። ንዳድ እንደ ተነሣበት ሰው መላ ሰውነቴ ጋየ፡፡
የሕይወቴ ክፋይ የሆነችውና የማፈቅራት የወዲያነሽ አንገቷን ሰበር አድርጋና ጀርባዋን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥታ መሬት ትቆረቁራለች። ጉልላት ከሴቷ ወታደር ትንሽ ራቅ ብሎ በትሕትና እጅ ነሣ ራመድ ብዬ ከጎኑ ቆመኩ
በተከዘ ፊቱ ላይ ለማስደሰት የሚፍጨረጨር ፈገግታ እያሳየ «ከነዚህ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....የማለዳዋ የጥር ወር ፀሐይ በመሬት ወለል አካባቢ ከየሚዳው! ከየተራራው፣ ከየዛፉ፣ ከየቤቱ፣ ከየጉራንጉሩ ቀዝቃዛ አየር ጋር ትንቅንቅ ገጥማለች። ተፈጥሮ ራሷን በራሷ የምታስተካክልበትና የምትለዋውጥበት ተፈራራቂ ኃይል ስላላት ቀዝቃዛው አየሩ ቀስ በቀስ ተረታ። ለውጥ የተፃራሪ ኃይሎች የግብግብ ውጤት ነው::
በእኔ ሕይወት ውስጥ ግን ጎልቶ የሚጠቀስ ለውጥ ባለመገኘቱ ሕሊናዩ
እየቀዘቀዘ ከመሔድ በቀር የብርታት ለውጥ አልታየብኝም፡፡ ከመኝታዬ ተነሥቼ
ልብሴን ስለባብስ ሰውነቴ ቀነቀነኝ፡፡ እውነተኛዎቹ የሐሳቤ ቅንቅኖች ግን አንጎሌ ውስጥ ይርመሰመሳሉ። የሥራ ቀን ነበር፡፡
መንገዱ የሚያልቅልኝ ስላልመስለኝ ቀደም ብዬ ተነሣሁ፡፡ ወደ ሕጋዊ ፍርድ ቤት ሳይሆን ወደ ግፈኞች የመከራ ሽንጎ የምገሠግሥ መሰለኝ፡፡ ከአራት ኪሎ እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለውን ርቀት በሁለት ታክሲ አጠቃለልኩት፡፡
ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ጸሐፊዎች፣ ነገረ ፈጆችና ወኪሎች፣ ተሟጋቾችና አማላጆች፣ “ጫማ ጠራጊዎችና ሥራ ፈቶች፣ እንደየ ኑሮ ደረጃቸው ለብሰው ተራ በተራ ሁለትና ሦስት እየሆኑ በመምጣት የፍርድ ቤቱን አካባቢ የበጋ ወራት ገብያ
አስመሰሉት፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች የለበሱት ነጠላና ጋቢ በጣም ከመቆሸሹ የተነሣ
ዳግመኛ ታጥቦ የሚነጣ አይመስልም፡፡ ጥለቱ የተንዘለዘለ፣ ዐልፎ ዐልፎ አይጥ
የበላው ይመስል የተቀዳደደ፣ እንደ አረጀ ሻሽ አለቅጥ የሳሳ ልብስ፣ በተለያየ
የጨርቅ ዐይነት የተጣጣፈ ኮትና ሱሪ፣ ከታጠበ ብዙ ዓመታት ዐልፈውት እድፉ
እንደ ማሰሻ የተላከከበት ሱፍ ኮት፣ ከተወለወለ ወራት ያለፉትና የቆዳው ቀለም የተገጣጠባ ከወደ አፍንጫው በእንቅፋት አልቆ ቀዳዳው የደረቀ የዓሣ አፍ የመሰለ፡ ከወደ ተረከዙ ወይም ከወደ ጎኑ ባንድ ወገን ተበልቶ የተንጋደደ ጫማ፣
በፀሐይ ሐሩርና በውርጭ፣ በአቧራና በእንክርት ቀለሙ ጠፍቶ የነተበ ባርኔጣ፣
የለበሱ ያደረጉና የደፉ ሰዎች በተስፋ መቁረጥ ስሜት እዚህም እዚያም
ቆመዋል፡፡ ለአያሌ ወራትና ዓመታት የተንገላቱና የተጎሳቆሉ ባለጉዳዮች ናቸው::በረሃብና በጥማት በርዛትና በንዴት በመጎዳታቸው አብዛኛዎቹ ውርጭ ላይ ያደረ አንጋሬ ይመስላሉ፡፡ ሕይወታቸው በትካዜ በመሞላቱ የገጽታቸው ፈገግታ ደርቋል፡፡
ወዛቸው እንደ ቅቤ ቅል የሚቅለጠለጥ ፊታቸው በዶሮ ጮማ እንደተወለወለ የወይራ በትር የሚያበራ፣ ቦርጫቸው የመንፈቅ ርጉዝ መስሎ ሱሪያቸው መታጠቂያው ላይ የሪቅ አፍ የሚያህል፣ አለባበሳቸው ሁሉ በጣም ያማረና የተዋበ ደንደሳሞች፣ በየደቂቃው በሚረባና በማይረባው ሁሉ የሚሥቁ በጣም መሠሪ ሰዎች ከየቢጤዎቻቸው ጋር ሰብሰብ ከምችት ብለው አፍ ለአፍ
ገጥመው ያወራሉ። የያዙት የሰነዶች መያዣ ኮሮጆ እንደ ባለቤቶቹ የፀዳ ሲሆን
የልፋት እንክርት አልነካውም፡፡ የተሰበሰበውን ሰው በዝርዝር ሲያዩት እያንዳንዱ ብቻውን ቆሞ እጁን እያወራጨ ከራሱ ጋር ይሟገታል።
አብዛኛው ጨርቅ ለባሽ በሌላ ሰው ወረቀት እያስነበበ ይኽ ልክ ነው
የለም ይኽ ሐሰት ነው! ለዚህ በቂ ነቃሽ አለኝ! ያያት የቅድመ አያቴ ነው ይግባኝ እላለሁ፡ ከዳኛው ጋር ተዋውለው ነው። ወላዲተ አምላክን!” እያለ እሰጥ
አገባ ይላል። ሁሉም ከሕይወት ወዲያ ማዶ በውሸት ዓለም ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እንጂ በርግጠኛ ሕይወት በእውነተኛ ዓለም የሚኖሩ አልመሰሉኝም
የመጥፎ ነገር ጥቀርሻ በጥብጠው የጋቱኝ ይመስል አእምሮዩ ተጨነቀ፡፡
የማያቋርጠው የጊዜ ጎርፍ እየጋፈረ መጓዙን ቀጠለ። ደቂቃ የደቂቃ ርካብ ረግጣ እየተፈናጠጠች ላትመለስ ትጋልባለች።
ጎነ ረጂሙ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ግዙፍ ሕንፃ ታላቅ የመከራ ተራራ መስሎ ፊት ለፊት ተገትሯል። የማደርገውን ጥንቃቄ አሟልቼ አካባቢዬን ገልመጥ እያልኩ እያየሁ መለስ ቀለስ አልኩ፡፡ ጭንቀቴና ጥበቴ እንደ ሐምሌ ጥቁር ደመና ከብዶ አንጎሌ ውስጥ አንዣሰሰ። በውስጤ የነበረው ሥጋት በድኃ ገበሬዎች አዋሳኝ እንዳለ የከበርቴ እርሻ መስፋቱን ቀጠለ። ረፈደ።
በወታደሮች ታጅበው በእግራቸውና በመኪና የመጡ አያሌ እስረኞች
በተለየ ቦታ ሰብሰብ አጀብ ብለው ቆሙ። ገር ገጭ ገጭ ገጭ፣ ሲጢጢጢጢጢ !
ካካካካካኪ! የሚል ድምፅ የምታሰማ ቮልስዋገን መጥታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ጉልላት ነው። የየወዲያነሽ ቀነ ቀጠሮ በመሆኑ እኔና እርሱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት
ለመገናኘት ተነጋግረን ነበር። ድክምክም ባለ እንቅስቃሴ የመኪናይቱን ቋቋቲያም
“በር ከፍቶ ወጣና ጨበጠኝ፡፡
ለአራት ሰዓት ሩብ ጉዳይ እኮ ሆኗል እስካሁን አላመጧትም እንዴ?»
አለኝ፡፡ ከንፈሬ ተጣብቆና ምላሴ አልላወስ ብሎ ቢያስቸግረኝም የለም እስካሁን አላመጧትም» ብዬ ዝም አልኩ። ውካታ በበዛበት አካባቢ ጥቂት ዝም ብለን ቆምን። ትላንት ማምሻዬን ሦስት ባለሙያ ጠበቆች አነጋግሬ ነበር። ሁሉም የሰጡኝ መልስ በጣም ተቀራራቢ ነበር፡፡ ቢበዛ አምስት ዓመት” አሉኝ። እንተስ ምን ይመስልሃል?» ብሎ ዐይኔን ማየት ጀመረ።
«እኔ ምን ዐውቃለሁ፡፡ ማንም ቢሆን ከራሱ ላይ ይልቅ በሌላው ላይ
መፍረድ ይቀልለዋል። የፍርድ ሰጪዎቹን ማንነት ስታየው ግን አምስት ዓመት
የሚበዛ አይመስልም፡፡ ቢሆንም ለእኔና ለእርሷ እያንዳንዱ ደቂቃ የሕይወታችን
ማሻከሪያ ክፍለ ጊዜ መሆኗ ነው» ብዬ ዝም አልኩ፡፡
«መቼም ቢሆን» አለ ጉልላት ወደድክም ጠላህም ምን ጊዜም ቢሆን ሕግ አለ። በሕጉም የሚጠቀሙና ጥቅማቸውን የሚያስጠብቁ አሉ። አህያና ጅብ
ባንድ ላይ ሕግ አያረፉም፡፡ ለጨቋኝና ለተጨቋት በአንድ ጊዜ በእኩልነት
የሚያገለግል ሕግ የለም፣ አልነበረምም፡፡ ሕግ ስለተፃፈ ብቻ ሕጋዊ አሠራር አለ
ማለት አይቻልም። እኔና አንተ ባለንበት ሥርዓተ ማኅበር ውስጥ እጀግ በጣም
አያሌ ባለሥልጣኖችና አጫፋሪዎቻቸው በልዩ ልዩ የእሠራር ስልትና ሥልጣን
ፈጠር ከለላ ከሕግ በላይ የሆኑበትና የሚሆኑበት ሁኔታ እንዳለ መዘንጋት
የለበትም፡፡ ስለሆነም ሕግ በትክክለኛው መንገድ በሥራ ላይ እስካልዋለ ድረስ
የሌለ ያህል ነው፡፡ ይህ ጉዳይ በስፋት የሚያነጋግግር ስለሆነ አሁን ከመጣንበት
ጉዳይ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የለውም። ወደ መጣንበት ጉዳይ እንመለስ፡፡
ስለዚህ በሚሰጠው ፍርድ እንዳትገረም፡፡ የበዛ ወይም ያነሰ ሊሆን ይሆናል» ብሎ
ወደፊት ተራመደ፡፡ ርምጃዬን ከርምጃው ጋር አስተካክዩ ተከተልኩት።
ከእኛ ትንሽ ራቅ ብሎ አንድ ብረት ሽፍን ባለ ጥቁር ሰሌዳ አረንጓዴ መኪና ቆሟል፡፡ ጉልላት መኪናውን አሻግሮ እየተመለከተ «ለምንድን ነው አልመጣችም ያልከኝ? ያ እኮ ነው የወህኒ ቤቱ መኪና» ብሎ ጥሎኝ ሔደ፡፡
አልተከተልኩትም፡፡
መኪናው ውስጥ ከተቀመጠው ሰው ጋር ምን እንደተባባሉ ባይሰማም ጉልላት ትንሽ ራቅ ብሎ ተነጋገሩ። ወዲያው ወደ እኔ ዞር ብሉ ና ቶሉ በሚል አኳኋን ጠቀሰኝ እና ሄድኩ፡፡ እስረኞቹ ወደሚገኙበት አካባቢ እንደ ደረስን ዐይኔ
ያካባቢው የብርሃን መጠን ያነሣት ይመስል የውበት ሃያ መስኮቶቿ ተሸጎሩ።
አጠርጠር ያሉና በሰፊ የካኪ ጨርቅ ስልቻ ውስጥ የቆሙ የሚመስሉ
የወህኒ ቤት ሴት ወታደሮች እያንዳንዳቸው አጠር ያለ ዱላ ይዘው ቆመዋል። በአቅራቢያቸው አምስት ሴቶች ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። የትካዜ እሳት ያነኮታቸው ይመስላሉ። ንዳድ እንደ ተነሣበት ሰው መላ ሰውነቴ ጋየ፡፡
የሕይወቴ ክፋይ የሆነችውና የማፈቅራት የወዲያነሽ አንገቷን ሰበር አድርጋና ጀርባዋን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥታ መሬት ትቆረቁራለች። ጉልላት ከሴቷ ወታደር ትንሽ ራቅ ብሎ በትሕትና እጅ ነሣ ራመድ ብዬ ከጎኑ ቆመኩ
በተከዘ ፊቱ ላይ ለማስደሰት የሚፍጨረጨር ፈገግታ እያሳየ «ከነዚህ
👍3❤1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«ስለ ልጅሽ አታስቢ አንቺንም በሚገባ እረዳሻለሁ። አየሽ አእምሮዩ ባንዲት ተስፋ ብቻ ትደሰታለች። ይኸውም ካንቺ ጋር እንደገና እንገናኛለን የሚለው ተስፋ ነው» ብያት ሳልወድ በግድ ዝም አልኩ።
ምላሴ ተቆልፋ እምቢ ባትለኝ ኖሮ በውስጤ የማግበሰበሰው ሐሳብስ ስፍር
ቁጥር አልነበረውም። በብስጭት ከመለብለብ ብዬ ጥያቸው ገለል አልኩ።
ጉልላትም ካሦስት ደቂቃ በኋላ ተለይቷት መጣ፡፡ የእሱን መኪና እንደ ተደገፈን
ብዙ ደቂቃዎች ዐለፉ። እንሒድ ተባብለን ወደ ፍርድ ቤቱ በር አካባቢ ተጠጋን፡፡
አንድ ወፈር ያለ ድምፅ «የወዲያአሉሽ አሸናፊ!» ብሎ ተጣራ፡፡ ለፈተና
እንዳልተዘጋጀ ሰነፍ ተማሪ ተርበተበትኩ፡፡ ሮጥ ሮጥ ብለን ሴቷን ወታደር
ደረስንባትና ስንተኛ ችሎት ነው የምትቀርበው?» ብለን ጠየቅናት።
«አንደኛ ወንጀል ችሎት» ብላ የወደያነሽን ለዕርድ እንደሚነዳ ሠንጋ ነዳቻት። በረዶ የመታኝ ያህል ተንዘፈዘፍኩ፡፡ ወደ ፍርድ ቤቱ ለመግባት ከባለጉዳዮችና ከአቸፍቻፊዎች ጋር ተደባልቄ ዘለቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ራመድ እንዳልኩ፣ ልክ ከፊት ለፊቴ ድንገተኛ መብረቅ የወደቀ ይመስል አካላቴ በታላቅ ድንጋጤ ተተረተረ። ወዲያም ወዲህ ሳላይ ቀንዷን እንደ ተመታች ላም ወደ ኋላ ተመለስኩ፡፡ ተከታትለው የሚይዙኝ ይመስል ሽሽቴን ቀጠልኩ፡፡ የምገባበት ጨነቀኝ፣ ተቅበዘበዝኩ፡፡ መሬት ተሰንጥቃ
ብትውጠኝ ባልጠላሁ ነበር። መለስ ብዬ ብመለከት የጉልላትም ፊት ቡን ብሏል፡፡
ጭንቅላቴን ይዤ አፈሩ ላይ ተጎለትኩ፡፡ መላ ሰውነቴን አሳከከኝ። ዐይኔ ውስጥ
አሽዋ የገባበት ይመስል ቆረቆረኝ፡፡ ዙሪያው ጨለመብኝ። አተነፋፈሴ ፈጠነ፡፡
የእጮኛውን ሞት እንዳረዱነት ወጣት መላ አካላቴ በውስጣዊ የኃዘን ማረሻ
ታርሶ ተበረቃቀሰ፡፡
«የወዲያነሽ ስንት ዓመት ይፈረድባት ይሆን?» እያልኩ ከእግር እስከ ራሴ በፍርሃትና በሥጋት ማጥ ውስጥ ተዘፈቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ገና ረገጥ ስናደርግ እኔንና ጉልላትን ያስበረገገን ግን
ከሦስቱ ዳኞች አንዱ ያውም የመኻል ዳኛው የእኔው አባት ባሻ ያየህይራድ
መሆኑ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም እንደዚያ ያለ ድንጋጤ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡
አቀርቅሮ የክስ ፋይል ይመለከት ስለነበር አላየኝም፡፡ እነዚያ በሕይወቴ ውስጥ
ዕድሜ እየሆኑ የተቆጠሩት አስደንጋጭ ደቂቃዎች እንደ ማንኛውም ደቂቃ
ዐለፉ፡፡ በዚያ ቅፅበት በእእምሮዬ ውስጥ የጎረፈውን የስጋት ሽብር በተግባር
ለቀመሰው እንጂ በወሬ ለሚሰማው ክብደት የለውም፡፡
አቃቤ ሕጉ በየወዲያነሽ ላይ የሚያቀርበውን ክስና አባቴ ከሁለቱ ዳኞች ጋር ሆኖ የሚሰጠውን የቅጣት ፍርድ ፊት ለፊት ለማየትና ለመስማት ባለመቻሌ ምን ጊዜም የማልበቀለው ጉዳት አጨቀየኝ።
የየወዲያነሽ ሰውነት በጣም በመኮስመኑና ስሟም በመጠኑ ተለውጦ
የወዲያ አሉሽ በመባሏ አባቴ ሊያውቃት አይችልም፡፡ አለባበሷና አንገተ
ሰባራነቷ እንደሚያዛልቅ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ጭንቅላቴን ይዤ እንዳቀረቀርኩና
ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ጉልላትም እንደ ማማ ተገትሮ እንደ ቆመ ግማሽ ሰዓት
ያህል ነጎደ። ወዴት እንደሚሔድ ባላውቅም የእግሩ ኮቴ ድምፅ ከወደ ኋላዬ እየራቀ ሄደ። አሁንም ጥቂት ደቂቃዎች ዐለፉ፡፡ እፎይታ ሳይሆን የመከራ ነዲድ በውስጤ ተግፈጠፈጠ።
የአባቴን ጠቅላላ የሕሊናና የአካል አቋም ከልጅነት እስከ ዕውቀት የማውቀውን ያህል እያሰላሰልኩ ከፊት ለፊቴ አቆምኩት፡፡ እርሱ በሚያነብበው
የሃይማኖት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ የሚነገርለት ሰው በላው ሰው ሰባ ስምንት
ሰዎች በልቷል እየተባለ ይነገራል። አባቴም በላዔ ሰብ እየተባለ የሚነገርለትን የክፉ ሰው አምሳል መስሎ ታየኝ።
እሱም እንደ ሰው በላው ሰው የሰው አካል አወራርዶና ግጦ የሰው ሥጋ ባይበላም ሰው በላ ነው:: የሰውን ሕይወት በማጥፋትና የሰውን ሕሊና በመግደል
መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ ስለ እውነተኛ ርትእና ፍትሕ እየተናገረ
ከሓሰተኞች ጎን ቆሞ ፍርድ ያዛባል፡፡ ከሐቅ ጋር ለቆመ ድሃ ሳይሆን ከሐሰትና
ከክህደት ጋር ጡት ለተጣቡ ባለጊዜና ባለ ገንዘብ ይፈርዳል። ስለዚህም «ሰው
በላ» ነው፡፡
ስለ ድሀ መጨቆንና መበደል ሲያወራ ማንም የሚስተካከለው አይመስልም፡፡ የየአካላችን ደም ስለየሕሊናችን ቅንነትና መሠሪነት መስካሪ ቢሆን ኖሮ ከአባቴ ኣካል የሚንጠፈጠፍ ደም ምንኛ ባጋለጠው!
ከጥቅምና ከኑሮው ላይ ቅንጣት ታህል የሚነካ ሰው ከመጣ፡ አንዷ ሰው
በላው ሰው የሰው አካል ዘነጣጥሎ ባይበላም ነገር ሽርቦና ጉንጉኖ ዓመት ሳይተኩስ ጥርኝ ዐፈር ያደርገዋል።
«ጨርቅ ለባሽ፣ አጥንተርካሽ በማለት የሚጸየፋቸውን ሰዎች ስለ ስምና
ክብሩ ብሉ ያንገላታቸውን ድሆች ሳስታውስ አባቴ እንደዚያ እንደ ታሪኩ ሰው
በቀጥታ የሰው ሥጋ ሳይሆን የሰው ሕይወት በልቷል። ስለ ሰው ችግርና ሥቃይ ፍጹም ደንታ የለሹ አባቴ፣ ማንም ቢንገላታና በጊሳቆል የቁጫጭ ሞት ያህል አያሳዝነውም፡፡ በአባቴና በመሰሎቹ አካባቢ ግዙፍ በደል በድሉ፣ በእጅ አዙር ሰው አስገድሉ፣ ከድሆችና ከከልታሞች ዲቃላ ደቅሎ ምስጢርን መቅ መጨመር የመሠሪነት ሳይሆን «የትልቅ ሰውነት» መለዮ ነው:: ለዚህ ዐይነቱ ደባ የሹም ምልመላ ቢካሔድ አባቴ ያላንዳች ቀዳሚ በትራሹመቱን ይጨብጣል።
«እሳቸው የሞቱ ዕለት ስንቱ ዲቃላ ከየሥርቻ ስርኩቻው ይጎለጎል ይሆን?» በማለት ውስጥ ውስጡንና የሚያማው ብዙ ነው:: እንደ ሰው ሐሜትማ ከሆነ ከልዩ ልዩ ሴቶች ተወልደው በአባቴ የተካዱትን እኀት ወንድሞቼን በግምት ሳሰላስል፣ አባቴ ከሰው በላው ብሶ ታየኝ። በተለይም ጠለቅ ብሎ ሥር ከፍ ብሎ ግንድ የለሽ» እያለ ሌሎችን በማኮሰስ የራሱን የዘር ሐረግ ሲያሳምር ታየኝና አስተሳሰቡን ሁሉ ተፀየፍኩት፡፡
ጉልላት ተመልሶ ከፊት ለፊቴ ቆመ፡፡ በእጆቹ ጎትቶ አስነሣኝ፡፡ በፊቱ ላይ አደናጋሪ ፈገግታ እየታየ «የምሥራች ጌታነህ!» አለኝ፡፡
በዚያች አስጨናቂ ጊዜ ውስጥ አንዳችም የምሥራች ይገኛል ብዬ ስላልጠረጠርኩ ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ ቀጠል አደረገና «ምነው ዝም አልክ? የወዲያነሽ እኮ ተፈረደባት። የምሥራች ያልኩህ ግን እጅዋ ከተያዘበት ቀን አንሥቶ አምስት ዓመት እንድትታሠር ስለተፈረደባት ነው:: 'የፈረዱብኝ የጌታነህ አባትና አብረዋቸው ያሉት ናቸው” አለችኝ፡፡ የቅጣቱን ውሳኔ ግን በንባብ ያሰሙት ያንተ አባት ናቸው አለች፡ በስሜ መለወጥና በመጎሳቆሌ
አላወቁኝም በማለቷ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አለቀ። በፍርሃት የሚጠብቁት ሥቃይ
ካለፈ እፎይታ ነው» ብሎ ከሚተናነቀው ምስቅልቅል ሲቃ ጋር ዝምታውን ቀጠለ።
ከፍርዱ በኋላ የወዲያነሽ ወደ ነበረችበት አካባቢ አብረን ሄድን፡፡ ያ የዐይኗ ቋንቋ የሆነው እንባዋ ገነፈለ። ሴቷ ወታደር ትካዜያችንን አይታ አዘነች፡፡ እኔና ጉልላት እንደገና ጠጋ ብለን ለማነጋገር አዲስ ፈቃድ አልጠየቅንም፡፡
«አይዞሽ! ብዙ ጊዜ አይደለም፡፡ በወህኒ ቤት ውስጥም ሆነ እስራትሽን ጨርሰሽ ስትወጪ የእኔ ነሽ። እኔም ያንቺ እንጂ የማንም የሌላ እይደለሁም፡፡ የልብሽ አዳራሽ በዚህ እውነተኛ በሆነ የቃል ኪዳን ተስፋ ይሞላ። ይህን በላይሽ ላይ የጫንኩትን የመከራ ቀንበር አብሬሽ እሸከመዋለሁ፡፡ በመጨረሻም አብረን
እንሰባብረዋለን፡፡ ያጠቆርኩትን ሕይወትሽን በአዲስ የኑሮ ብርሃን እንዲደሞቅ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ» ብዬ የልቤን ፅላት ሰጠኋት። አፏ ባይናገርም ልቧ ተቀብሉኛል፡፡ ያደረግሁት ንግግር ተፅፎ የተጠና እንጂ እዚያው ተቀናብሮ የተነገረ ስለማይመስል እኔኑ መልሶ ገረመኝ፡፡
መለስ ብዩ ለሴቷ ወታደር ምናምን ጨበጥ እደረኩላት፡፡ የማይፈቀድ
ነገር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....«ስለ ልጅሽ አታስቢ አንቺንም በሚገባ እረዳሻለሁ። አየሽ አእምሮዩ ባንዲት ተስፋ ብቻ ትደሰታለች። ይኸውም ካንቺ ጋር እንደገና እንገናኛለን የሚለው ተስፋ ነው» ብያት ሳልወድ በግድ ዝም አልኩ።
ምላሴ ተቆልፋ እምቢ ባትለኝ ኖሮ በውስጤ የማግበሰበሰው ሐሳብስ ስፍር
ቁጥር አልነበረውም። በብስጭት ከመለብለብ ብዬ ጥያቸው ገለል አልኩ።
ጉልላትም ካሦስት ደቂቃ በኋላ ተለይቷት መጣ፡፡ የእሱን መኪና እንደ ተደገፈን
ብዙ ደቂቃዎች ዐለፉ። እንሒድ ተባብለን ወደ ፍርድ ቤቱ በር አካባቢ ተጠጋን፡፡
አንድ ወፈር ያለ ድምፅ «የወዲያአሉሽ አሸናፊ!» ብሎ ተጣራ፡፡ ለፈተና
እንዳልተዘጋጀ ሰነፍ ተማሪ ተርበተበትኩ፡፡ ሮጥ ሮጥ ብለን ሴቷን ወታደር
ደረስንባትና ስንተኛ ችሎት ነው የምትቀርበው?» ብለን ጠየቅናት።
«አንደኛ ወንጀል ችሎት» ብላ የወደያነሽን ለዕርድ እንደሚነዳ ሠንጋ ነዳቻት። በረዶ የመታኝ ያህል ተንዘፈዘፍኩ፡፡ ወደ ፍርድ ቤቱ ለመግባት ከባለጉዳዮችና ከአቸፍቻፊዎች ጋር ተደባልቄ ዘለቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ራመድ እንዳልኩ፣ ልክ ከፊት ለፊቴ ድንገተኛ መብረቅ የወደቀ ይመስል አካላቴ በታላቅ ድንጋጤ ተተረተረ። ወዲያም ወዲህ ሳላይ ቀንዷን እንደ ተመታች ላም ወደ ኋላ ተመለስኩ፡፡ ተከታትለው የሚይዙኝ ይመስል ሽሽቴን ቀጠልኩ፡፡ የምገባበት ጨነቀኝ፣ ተቅበዘበዝኩ፡፡ መሬት ተሰንጥቃ
ብትውጠኝ ባልጠላሁ ነበር። መለስ ብዬ ብመለከት የጉልላትም ፊት ቡን ብሏል፡፡
ጭንቅላቴን ይዤ አፈሩ ላይ ተጎለትኩ፡፡ መላ ሰውነቴን አሳከከኝ። ዐይኔ ውስጥ
አሽዋ የገባበት ይመስል ቆረቆረኝ፡፡ ዙሪያው ጨለመብኝ። አተነፋፈሴ ፈጠነ፡፡
የእጮኛውን ሞት እንዳረዱነት ወጣት መላ አካላቴ በውስጣዊ የኃዘን ማረሻ
ታርሶ ተበረቃቀሰ፡፡
«የወዲያነሽ ስንት ዓመት ይፈረድባት ይሆን?» እያልኩ ከእግር እስከ ራሴ በፍርሃትና በሥጋት ማጥ ውስጥ ተዘፈቅሁ፡፡
የፍርድ ቤቱን ደፍ ገና ረገጥ ስናደርግ እኔንና ጉልላትን ያስበረገገን ግን
ከሦስቱ ዳኞች አንዱ ያውም የመኻል ዳኛው የእኔው አባት ባሻ ያየህይራድ
መሆኑ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም እንደዚያ ያለ ድንጋጤ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡
አቀርቅሮ የክስ ፋይል ይመለከት ስለነበር አላየኝም፡፡ እነዚያ በሕይወቴ ውስጥ
ዕድሜ እየሆኑ የተቆጠሩት አስደንጋጭ ደቂቃዎች እንደ ማንኛውም ደቂቃ
ዐለፉ፡፡ በዚያ ቅፅበት በእእምሮዬ ውስጥ የጎረፈውን የስጋት ሽብር በተግባር
ለቀመሰው እንጂ በወሬ ለሚሰማው ክብደት የለውም፡፡
አቃቤ ሕጉ በየወዲያነሽ ላይ የሚያቀርበውን ክስና አባቴ ከሁለቱ ዳኞች ጋር ሆኖ የሚሰጠውን የቅጣት ፍርድ ፊት ለፊት ለማየትና ለመስማት ባለመቻሌ ምን ጊዜም የማልበቀለው ጉዳት አጨቀየኝ።
የየወዲያነሽ ሰውነት በጣም በመኮስመኑና ስሟም በመጠኑ ተለውጦ
የወዲያ አሉሽ በመባሏ አባቴ ሊያውቃት አይችልም፡፡ አለባበሷና አንገተ
ሰባራነቷ እንደሚያዛልቅ ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ጭንቅላቴን ይዤ እንዳቀረቀርኩና
ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ጉልላትም እንደ ማማ ተገትሮ እንደ ቆመ ግማሽ ሰዓት
ያህል ነጎደ። ወዴት እንደሚሔድ ባላውቅም የእግሩ ኮቴ ድምፅ ከወደ ኋላዬ እየራቀ ሄደ። አሁንም ጥቂት ደቂቃዎች ዐለፉ፡፡ እፎይታ ሳይሆን የመከራ ነዲድ በውስጤ ተግፈጠፈጠ።
የአባቴን ጠቅላላ የሕሊናና የአካል አቋም ከልጅነት እስከ ዕውቀት የማውቀውን ያህል እያሰላሰልኩ ከፊት ለፊቴ አቆምኩት፡፡ እርሱ በሚያነብበው
የሃይማኖት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ የሚነገርለት ሰው በላው ሰው ሰባ ስምንት
ሰዎች በልቷል እየተባለ ይነገራል። አባቴም በላዔ ሰብ እየተባለ የሚነገርለትን የክፉ ሰው አምሳል መስሎ ታየኝ።
እሱም እንደ ሰው በላው ሰው የሰው አካል አወራርዶና ግጦ የሰው ሥጋ ባይበላም ሰው በላ ነው:: የሰውን ሕይወት በማጥፋትና የሰውን ሕሊና በመግደል
መካከል ምንም ልዩነት የለም፡፡ ስለ እውነተኛ ርትእና ፍትሕ እየተናገረ
ከሓሰተኞች ጎን ቆሞ ፍርድ ያዛባል፡፡ ከሐቅ ጋር ለቆመ ድሃ ሳይሆን ከሐሰትና
ከክህደት ጋር ጡት ለተጣቡ ባለጊዜና ባለ ገንዘብ ይፈርዳል። ስለዚህም «ሰው
በላ» ነው፡፡
ስለ ድሀ መጨቆንና መበደል ሲያወራ ማንም የሚስተካከለው አይመስልም፡፡ የየአካላችን ደም ስለየሕሊናችን ቅንነትና መሠሪነት መስካሪ ቢሆን ኖሮ ከአባቴ ኣካል የሚንጠፈጠፍ ደም ምንኛ ባጋለጠው!
ከጥቅምና ከኑሮው ላይ ቅንጣት ታህል የሚነካ ሰው ከመጣ፡ አንዷ ሰው
በላው ሰው የሰው አካል ዘነጣጥሎ ባይበላም ነገር ሽርቦና ጉንጉኖ ዓመት ሳይተኩስ ጥርኝ ዐፈር ያደርገዋል።
«ጨርቅ ለባሽ፣ አጥንተርካሽ በማለት የሚጸየፋቸውን ሰዎች ስለ ስምና
ክብሩ ብሉ ያንገላታቸውን ድሆች ሳስታውስ አባቴ እንደዚያ እንደ ታሪኩ ሰው
በቀጥታ የሰው ሥጋ ሳይሆን የሰው ሕይወት በልቷል። ስለ ሰው ችግርና ሥቃይ ፍጹም ደንታ የለሹ አባቴ፣ ማንም ቢንገላታና በጊሳቆል የቁጫጭ ሞት ያህል አያሳዝነውም፡፡ በአባቴና በመሰሎቹ አካባቢ ግዙፍ በደል በድሉ፣ በእጅ አዙር ሰው አስገድሉ፣ ከድሆችና ከከልታሞች ዲቃላ ደቅሎ ምስጢርን መቅ መጨመር የመሠሪነት ሳይሆን «የትልቅ ሰውነት» መለዮ ነው:: ለዚህ ዐይነቱ ደባ የሹም ምልመላ ቢካሔድ አባቴ ያላንዳች ቀዳሚ በትራሹመቱን ይጨብጣል።
«እሳቸው የሞቱ ዕለት ስንቱ ዲቃላ ከየሥርቻ ስርኩቻው ይጎለጎል ይሆን?» በማለት ውስጥ ውስጡንና የሚያማው ብዙ ነው:: እንደ ሰው ሐሜትማ ከሆነ ከልዩ ልዩ ሴቶች ተወልደው በአባቴ የተካዱትን እኀት ወንድሞቼን በግምት ሳሰላስል፣ አባቴ ከሰው በላው ብሶ ታየኝ። በተለይም ጠለቅ ብሎ ሥር ከፍ ብሎ ግንድ የለሽ» እያለ ሌሎችን በማኮሰስ የራሱን የዘር ሐረግ ሲያሳምር ታየኝና አስተሳሰቡን ሁሉ ተፀየፍኩት፡፡
ጉልላት ተመልሶ ከፊት ለፊቴ ቆመ፡፡ በእጆቹ ጎትቶ አስነሣኝ፡፡ በፊቱ ላይ አደናጋሪ ፈገግታ እየታየ «የምሥራች ጌታነህ!» አለኝ፡፡
በዚያች አስጨናቂ ጊዜ ውስጥ አንዳችም የምሥራች ይገኛል ብዬ ስላልጠረጠርኩ ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ ቀጠል አደረገና «ምነው ዝም አልክ? የወዲያነሽ እኮ ተፈረደባት። የምሥራች ያልኩህ ግን እጅዋ ከተያዘበት ቀን አንሥቶ አምስት ዓመት እንድትታሠር ስለተፈረደባት ነው:: 'የፈረዱብኝ የጌታነህ አባትና አብረዋቸው ያሉት ናቸው” አለችኝ፡፡ የቅጣቱን ውሳኔ ግን በንባብ ያሰሙት ያንተ አባት ናቸው አለች፡ በስሜ መለወጥና በመጎሳቆሌ
አላወቁኝም በማለቷ በጣም ተደስቻለሁ፡፡ አለቀ። በፍርሃት የሚጠብቁት ሥቃይ
ካለፈ እፎይታ ነው» ብሎ ከሚተናነቀው ምስቅልቅል ሲቃ ጋር ዝምታውን ቀጠለ።
ከፍርዱ በኋላ የወዲያነሽ ወደ ነበረችበት አካባቢ አብረን ሄድን፡፡ ያ የዐይኗ ቋንቋ የሆነው እንባዋ ገነፈለ። ሴቷ ወታደር ትካዜያችንን አይታ አዘነች፡፡ እኔና ጉልላት እንደገና ጠጋ ብለን ለማነጋገር አዲስ ፈቃድ አልጠየቅንም፡፡
«አይዞሽ! ብዙ ጊዜ አይደለም፡፡ በወህኒ ቤት ውስጥም ሆነ እስራትሽን ጨርሰሽ ስትወጪ የእኔ ነሽ። እኔም ያንቺ እንጂ የማንም የሌላ እይደለሁም፡፡ የልብሽ አዳራሽ በዚህ እውነተኛ በሆነ የቃል ኪዳን ተስፋ ይሞላ። ይህን በላይሽ ላይ የጫንኩትን የመከራ ቀንበር አብሬሽ እሸከመዋለሁ፡፡ በመጨረሻም አብረን
እንሰባብረዋለን፡፡ ያጠቆርኩትን ሕይወትሽን በአዲስ የኑሮ ብርሃን እንዲደሞቅ እስከ መጨረሻው እታገላለሁ» ብዬ የልቤን ፅላት ሰጠኋት። አፏ ባይናገርም ልቧ ተቀብሉኛል፡፡ ያደረግሁት ንግግር ተፅፎ የተጠና እንጂ እዚያው ተቀናብሮ የተነገረ ስለማይመስል እኔኑ መልሶ ገረመኝ፡፡
መለስ ብዩ ለሴቷ ወታደር ምናምን ጨበጥ እደረኩላት፡፡ የማይፈቀድ
ነገር
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....ከቤተሰቦቼ ጋር የነበረኝ ግንኙነት እምብዛም ሳያፈነግጥና ሳይቀርብ፣
ሳይጥምና ሳይሆመጥጥ ቀጠለ የወዲያነሽ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደ አንድ የደስታ ቀን ፈጥኖ ዐለፈ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከሰዓት በኋላ ከአንድ ጓደኛዬ
የተዋስኩትን መቅረፀ ትርዒት (ካሜራ ወይም ፎቶ ማንሻ ይዤ ወደ ዕጓላ
ማውታ ሄድኩ
ከዚያ ቀደም ሲል ከወሰድኩለት ልብሶች መካከል ጥሩዋን ልብስ አልብሽ አነሣሁትና እንዴት እንደሚደርሳት ቀደም ብዪ ጨርሼ ስለነበር በሳምንቱ እሑድ
የልጇን ፎቶ ይዤ በጉልላት መኪና ወህኒ ቤት ሄድኩ። እንደ ተለመደው !
፣አስጠራኋት፡፡ የአጥሩን አግዳሚ ዕንጨት ተደግፋ ጥቂት አወራራን ድንገት !ሳታስበው ፎቶግራፉን ከኪሴ መዥረጥ አደረግሁና «በይ እስኪ በቃሽ እዪና ጥገቢው፡ ነጋ ጠባ፣ ልጄ! ልጄ ስትይ!...» ብዬ በወታደሪቱ ኣስተላላፊነት
አቀበልኳት፡፡ የወረቀቱን ግራ ቀኝ ጠርዝ በሁለት እጆቿ ይዛ ትኩር ብላ
ተመለከተችው:: ፊቷ ላይ ስታሸበሽብ የቆየችው ኮስማና ፈገግታ ደብዛዋ ጠፋ።
ወዲያው ብርሃኗ በጥቅጥቅ ጭጋግ እንደ ፈዘዘ ጨረቃ ፈዘዘች። እንባዋ
በዐይኖቿ ዙሪያ ግጥም አለ፡፡ አቀረቀረች። በሰንበሌጥ ላይ እየተንኳላላች እንደምትወርድ ጠፈጠፍ እንባዋ ጉንጯን ሳይነካ ከትንሿ ወረቀት ላይ ተንጠባጠበ።
ከሩኅሩኅ የእናትነቷ ባሕሪ የመነጨ የፍቅር ኩልልታ ስለነበር ለመጪው
ጊዜ የሚቀመጥ የትዝታ ጥሪት አስቀመጥኩ፡፡ ደግማ ደጋግማ ሥዕሉን ሳመች።እምብዛም ነገሬ ሳትለኝና እህ! ብላ ሳታዳምጠኝ ተሰናብቻት ተመለስኩ።
ከሌላ ስድስት ወር በኋላ የወዲ ያነሽ ሁለት ዓመት ሞላት።
እሑድ ከሰዓት በኋላ ነበር፡፡ የዕለቱን ጋዜጣ እያነበብኩ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ውስጥ ተቀምጬ ሳለሁ የውብነሽ አጠገቤ ተቀመጠች። የያዘችውን
የአማርኛ ሰዋሰው መጽሐፍ እንደተገለጠ አጭሯ ክብ ጠረጴዛ ላይ ዘረጋችው።
ዐይኔ ተወርውራ የጊዜ ተውሳከ ግሥ የሚለውን ርዕስ አየች። ለነገርና
ለወሬ ማነሣሻ ይሆነኝ ዘንድ «ይልቅስ የአኳኋንና የሁኔታን ተውሳከ ግሥ
አታጠኚም» ብዬ መጽሐፉ ውስጥ የማነበው ያለኝ ይመስል አገላብጬ
አስቀመጥኩት። «እኔ የጊዜ ተውሳከ ግሥ አልዘለቅ ብሎኛል። አንተ ደግሞ
ሌላውን ትለኛልሀ» አለችና እጄ ላይ የነበረውን ጋዜጣ ወስዳ የመጀመሪያን ገጽ አርእስቶች በለሆሳስ አነበበች፡፡
«ሥራ አለብሽ እንዴ የውቢ? ከሌለብሽ አንድ ቦታ ደረስ ብለን እንምጣ» ብዬ ጸጉሬን አሻሸሁት፡፡ ጋዜጣውን አጣጥፋ አስቀመጠችው:: «እሺ እንሂድ፡፡ ይህን ማታም ቢሆን ልፈጽመው እችላለሁ» ብላ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች።
«ምንም እንኳ ለጊዜው አሳዛኝ መስሎ እንደሚታይሽ ባውቅም የኋላ ኋላ
ግን ያስደስትሽ ይሆናል» ብዩ ኩራትን ለመግለጽ በሚያስችል ወፍራም ደርባባ
ድምፅ ተናገርኩ። ካንተ ጋር ከሆንኩ ምን ያሳዝነኛል? በመጨረሻ የሚያስደስተኝ
ነገር ሁሉ ደስ ይለኛል፡፡ እንሂድ ካልክ ልብሴን ልቀያይርና እንሂድ» ብላ ተነሣች፡፡ እንዲሁ ገባ እንዳለች ዘርፈጥ ብላ የተቀመጠችበት ቀሚሷ ከበስተኋላዋ
ልሙጥነቱ ጠፍቶ ወደ ልዩ ልዩ አቅጣጫ የተሰበጣጠረ ጭምድ መስመሮች
ሠርቷል። ልብሷን ለመቀያየር ወደ መኝታ ቤት ስትገባ እኔም ጸጉሬን ለማበጠር
ወደ ክፍሌ ገባሁ፡፡
የልብሴን መስተካከል በመስተዋት ከተመለከትኩ በኋላ ጸጉሬን በደረቁ
እበጥሬው ወጣሁ፡፡ ደረጃውን ወርጀ እንደ ጨረስኩ ደረሰችብኝ።
ምንም እንኳ ወዴት እንደምንሄድ ባታውቅም «የምንሔድበት ቦታ ብዙ
ሰዎች አለበት እንዴ?» ብላ ጠየቀችኝ፡፡ «ማንም የለም። የምንሄደው አንድ እሳዛኝ
ሰው ለማየት ነው» ብዬ አለባበስና አረማመዷን እያየሁ መንገድ ገባን፡፡ ደማም ወጣትነቷና እንስታዊ ውብ ቅርጺ ማራኪነት ሰጥቷታል፡፡ ፈገግ ስትል ፍልቅቅ የሚሉት ነጫጭ ውብ ጥርሶቿ ከደም ግባቷ ጋር የአተር አበባ አስመስለዋታል፡፡
እግረ መንገዳችንን ልዩ ልዩ የሚባሉ ነገሮች ገዛሁላት። ዐሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ደረስን፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት
አስከትዩ በመሄዴ ያ ዘወትር ብቻዬን ስመላለስ የሚያየኝ ዘበኛ የውብነሽን
በማየቱ የመገረም ፈገግታ ታየበት።
አብዛኛውን ጊዜ ከቤቱ ታዛ አካባቢ ከብዙ ከልጆች ጋር ተቀምጦ ሲጫወት ከሩቁ የማውቀው በልብሱ ስለነበር ሜዳው መኻል ቆም እያልኩ የቢቶቹን የፊት ዙሪያ ተመለከትኩ፡፡ ብዙ ልጆች ጨዋታቸውንና ልፊያቸውን እየተዉ አዩን፡፡ ወደ መኝታ ክፍሉ ይዣት ገባሁ። እሱኑ ከሚያካክሉ ሁለት ልጆች ጋር ወለሉ ላይ ተቀምጦ እየተኮላተፈ ይጫወታል። ሁለቱ ልጆች መለስ ብለው ካዩን በኋላ ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዐይኖች ግን እኔ ላይ
ተተከሉ፡፡ ጎንበስ ብዪ አነሣሁት፡፡
አባባና እማማ የሚባሉ ቃላት የማያውቀው፣ የወላጅ ፍቅር ያልቀመሰው
ልጄ እንደ ወፍ ዘራሽ የመስክ አበባ ያምራል። ለምን ወደ ዕጓለ ማውታ እንደ
መጣች ግራ የገባት የውብነሽ በመጠኑ ደንገጥ አለች፡፡ ወደ እርስዋ ዞሬ ትከሻዋን
ቸብ ካደረግሁዋት በኋላ እስኪ ይህን ልጅ ተመልከችው የውብነሽ ቆንጆ ልጅ
አይደለም እንዴ? ብዬ ጠየቅኋት። እ..ብላ ዝም አለች።
ሰውነቷ በጥርጣሬና በሐሳብ የተጠመደ መሰለ፡ ድንገት ከእንቅልፏ ነቅታ ባጋጣሚ ያየችው ይመስል ሁለት እጆቿን ዘርግታ «እውይ እማምዬ ማማሩ! ደስ ማለቱ?» ብላ ከእጁ ላይ ወስዳ ታቀፈችው፡፡
በፊቱ ላይ አንዳችም ሌላ ለውጥ ሳይታይና ፈገግታው ሳይቀንስ ዝርግፍ
ብሉ ወደ እርሷ በመሄዱ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እንዲያውም እዚያች ጠባብ ደረቷ
ላይ ልጥቅ አለ፡፡ ነገር ግን ልጄን ለመጀመሪያ ጊዜ ያቺ የማፈቅራትና
የምንሰፈሰፍላት የወዲያዬ ሳትሆን እኅቴ አቅፋው በማየቴ በፋይዳ የለሽ ጥላቻ
ተናደድኩ፡፡ ጉንጮቹን ሳም ሳም ካደረገች በኋላ ፊቷን ወደ እኔ መለስ አድርጋ
<<የማን ልጅ ነው ?» ብላ በጓጓ ስሜት ጠየቀችኝ። የምናገረው እውነተኛና ርግጠኛ እንዲመስል ለመመለስ የማሰላሰያ ጊዜ አልወሰድኩም፡፡ «አንቺ የማታውቂው አንድ ጓደኛ ነበረኝ፡፡ የዚህ ልጅ አባት ማለቴ ነው። ትዝ እይልሽም ይሆናል እንጂ እኛም ቤት አንድ ሁለት ቀን ያህል መጥቶ ነበር» ካልኩ በኋላ የነገሩን
ድምጥማጥ ይበልጥ ለማጥፋት «ነገር ግን ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሞቷል፡፡ ልጁ ግን ለጊዜው አሳዳጊ ዘመድ በማጣቱ
ይኸው እዚህ በምታይው ሁኔታ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ልጅ አባት በጣም
ግሩም ሰው ስለ ነበር እሱን በማሰብና ለልጁ በማዘን ብቻ አልፎ አልፎ ብቅ
እያልኩ እጠይቀዋለሁ፡፡ ጉልላትም አንዳንድ ቀን እየመጣ ያየዋል» ብዬ ዋሸኋት፡፡ግንባሩን ሁለት ጊዜ ያህል ስማ ውብ ዐይኖቹን ባንጸባራቂ ሸጋ ዐይኖቿ ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው::
«ምነው አንተም እንዲህ የሚያምርና የሚያስጐመዥ ልጅ በነበረህ» ብላ
እንደ ወይን እሽት የሚያስጐመዡትን ጉንጮቹን ሳመቻቸው:: ንግግሯ ለጊዜው
ረግቶና በርዶ የቆየውን የሕሊናዬን ባሕር በብስጭት ማዕበል አረሰው፡፡
“ምናልባት ሚስት ባገባ ማስቴን በርግዝናዋ ወራት ከቤት አታባርሯት
እንደሆነ ነዋ እንዲህ ያለ ልጅ ማግኘት የሚቻለው» ብዩ በሽሙጥ መለስኩላት።
ድንገተኛው የንግግሬ ይዘት ፊቷን አስቀጨመው:: ልጁን ከሰጠችኝ በኋላ
አንገቷን ስብራ አቀረቀረች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ ከወለሉ ላይ ቃላት
እየለቃቀመች ትናገር ይመስል ወለሉን እያየች «ያ ያለፈው ሁሉ ሌላ ጉዳይ
ነው፡፡ የማይገናኙ ነገሮች አታገናኝ እኔን ምን አድርጊ ትለኛለህ? አንተ ከእኔ
የበለጠ ብልህ መሆንህን ዐውቃለሁ አባታችን ቢሰማ ኖሮ በአንተና በእርሱ
መካከል ትልቅ ጠብና ማለቂያ የሌለው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
....ከቤተሰቦቼ ጋር የነበረኝ ግንኙነት እምብዛም ሳያፈነግጥና ሳይቀርብ፣
ሳይጥምና ሳይሆመጥጥ ቀጠለ የወዲያነሽ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደ አንድ የደስታ ቀን ፈጥኖ ዐለፈ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከሰዓት በኋላ ከአንድ ጓደኛዬ
የተዋስኩትን መቅረፀ ትርዒት (ካሜራ ወይም ፎቶ ማንሻ ይዤ ወደ ዕጓላ
ማውታ ሄድኩ
ከዚያ ቀደም ሲል ከወሰድኩለት ልብሶች መካከል ጥሩዋን ልብስ አልብሽ አነሣሁትና እንዴት እንደሚደርሳት ቀደም ብዪ ጨርሼ ስለነበር በሳምንቱ እሑድ
የልጇን ፎቶ ይዤ በጉልላት መኪና ወህኒ ቤት ሄድኩ። እንደ ተለመደው !
፣አስጠራኋት፡፡ የአጥሩን አግዳሚ ዕንጨት ተደግፋ ጥቂት አወራራን ድንገት !ሳታስበው ፎቶግራፉን ከኪሴ መዥረጥ አደረግሁና «በይ እስኪ በቃሽ እዪና ጥገቢው፡ ነጋ ጠባ፣ ልጄ! ልጄ ስትይ!...» ብዬ በወታደሪቱ ኣስተላላፊነት
አቀበልኳት፡፡ የወረቀቱን ግራ ቀኝ ጠርዝ በሁለት እጆቿ ይዛ ትኩር ብላ
ተመለከተችው:: ፊቷ ላይ ስታሸበሽብ የቆየችው ኮስማና ፈገግታ ደብዛዋ ጠፋ።
ወዲያው ብርሃኗ በጥቅጥቅ ጭጋግ እንደ ፈዘዘ ጨረቃ ፈዘዘች። እንባዋ
በዐይኖቿ ዙሪያ ግጥም አለ፡፡ አቀረቀረች። በሰንበሌጥ ላይ እየተንኳላላች እንደምትወርድ ጠፈጠፍ እንባዋ ጉንጯን ሳይነካ ከትንሿ ወረቀት ላይ ተንጠባጠበ።
ከሩኅሩኅ የእናትነቷ ባሕሪ የመነጨ የፍቅር ኩልልታ ስለነበር ለመጪው
ጊዜ የሚቀመጥ የትዝታ ጥሪት አስቀመጥኩ፡፡ ደግማ ደጋግማ ሥዕሉን ሳመች።እምብዛም ነገሬ ሳትለኝና እህ! ብላ ሳታዳምጠኝ ተሰናብቻት ተመለስኩ።
ከሌላ ስድስት ወር በኋላ የወዲ ያነሽ ሁለት ዓመት ሞላት።
እሑድ ከሰዓት በኋላ ነበር፡፡ የዕለቱን ጋዜጣ እያነበብኩ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ውስጥ ተቀምጬ ሳለሁ የውብነሽ አጠገቤ ተቀመጠች። የያዘችውን
የአማርኛ ሰዋሰው መጽሐፍ እንደተገለጠ አጭሯ ክብ ጠረጴዛ ላይ ዘረጋችው።
ዐይኔ ተወርውራ የጊዜ ተውሳከ ግሥ የሚለውን ርዕስ አየች። ለነገርና
ለወሬ ማነሣሻ ይሆነኝ ዘንድ «ይልቅስ የአኳኋንና የሁኔታን ተውሳከ ግሥ
አታጠኚም» ብዬ መጽሐፉ ውስጥ የማነበው ያለኝ ይመስል አገላብጬ
አስቀመጥኩት። «እኔ የጊዜ ተውሳከ ግሥ አልዘለቅ ብሎኛል። አንተ ደግሞ
ሌላውን ትለኛልሀ» አለችና እጄ ላይ የነበረውን ጋዜጣ ወስዳ የመጀመሪያን ገጽ አርእስቶች በለሆሳስ አነበበች፡፡
«ሥራ አለብሽ እንዴ የውቢ? ከሌለብሽ አንድ ቦታ ደረስ ብለን እንምጣ» ብዬ ጸጉሬን አሻሸሁት፡፡ ጋዜጣውን አጣጥፋ አስቀመጠችው:: «እሺ እንሂድ፡፡ ይህን ማታም ቢሆን ልፈጽመው እችላለሁ» ብላ ከንፈሯን በምላሷ እያራሰች።
«ምንም እንኳ ለጊዜው አሳዛኝ መስሎ እንደሚታይሽ ባውቅም የኋላ ኋላ
ግን ያስደስትሽ ይሆናል» ብዩ ኩራትን ለመግለጽ በሚያስችል ወፍራም ደርባባ
ድምፅ ተናገርኩ። ካንተ ጋር ከሆንኩ ምን ያሳዝነኛል? በመጨረሻ የሚያስደስተኝ
ነገር ሁሉ ደስ ይለኛል፡፡ እንሂድ ካልክ ልብሴን ልቀያይርና እንሂድ» ብላ ተነሣች፡፡ እንዲሁ ገባ እንዳለች ዘርፈጥ ብላ የተቀመጠችበት ቀሚሷ ከበስተኋላዋ
ልሙጥነቱ ጠፍቶ ወደ ልዩ ልዩ አቅጣጫ የተሰበጣጠረ ጭምድ መስመሮች
ሠርቷል። ልብሷን ለመቀያየር ወደ መኝታ ቤት ስትገባ እኔም ጸጉሬን ለማበጠር
ወደ ክፍሌ ገባሁ፡፡
የልብሴን መስተካከል በመስተዋት ከተመለከትኩ በኋላ ጸጉሬን በደረቁ
እበጥሬው ወጣሁ፡፡ ደረጃውን ወርጀ እንደ ጨረስኩ ደረሰችብኝ።
ምንም እንኳ ወዴት እንደምንሄድ ባታውቅም «የምንሔድበት ቦታ ብዙ
ሰዎች አለበት እንዴ?» ብላ ጠየቀችኝ፡፡ «ማንም የለም። የምንሄደው አንድ እሳዛኝ
ሰው ለማየት ነው» ብዬ አለባበስና አረማመዷን እያየሁ መንገድ ገባን፡፡ ደማም ወጣትነቷና እንስታዊ ውብ ቅርጺ ማራኪነት ሰጥቷታል፡፡ ፈገግ ስትል ፍልቅቅ የሚሉት ነጫጭ ውብ ጥርሶቿ ከደም ግባቷ ጋር የአተር አበባ አስመስለዋታል፡፡
እግረ መንገዳችንን ልዩ ልዩ የሚባሉ ነገሮች ገዛሁላት። ዐሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ደረስን፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት
አስከትዩ በመሄዴ ያ ዘወትር ብቻዬን ስመላለስ የሚያየኝ ዘበኛ የውብነሽን
በማየቱ የመገረም ፈገግታ ታየበት።
አብዛኛውን ጊዜ ከቤቱ ታዛ አካባቢ ከብዙ ከልጆች ጋር ተቀምጦ ሲጫወት ከሩቁ የማውቀው በልብሱ ስለነበር ሜዳው መኻል ቆም እያልኩ የቢቶቹን የፊት ዙሪያ ተመለከትኩ፡፡ ብዙ ልጆች ጨዋታቸውንና ልፊያቸውን እየተዉ አዩን፡፡ ወደ መኝታ ክፍሉ ይዣት ገባሁ። እሱኑ ከሚያካክሉ ሁለት ልጆች ጋር ወለሉ ላይ ተቀምጦ እየተኮላተፈ ይጫወታል። ሁለቱ ልጆች መለስ ብለው ካዩን በኋላ ጨዋታቸውን ቀጠሉ፡፡ የእኔ ልጅ ዐይኖች ግን እኔ ላይ
ተተከሉ፡፡ ጎንበስ ብዪ አነሣሁት፡፡
አባባና እማማ የሚባሉ ቃላት የማያውቀው፣ የወላጅ ፍቅር ያልቀመሰው
ልጄ እንደ ወፍ ዘራሽ የመስክ አበባ ያምራል። ለምን ወደ ዕጓለ ማውታ እንደ
መጣች ግራ የገባት የውብነሽ በመጠኑ ደንገጥ አለች፡፡ ወደ እርስዋ ዞሬ ትከሻዋን
ቸብ ካደረግሁዋት በኋላ እስኪ ይህን ልጅ ተመልከችው የውብነሽ ቆንጆ ልጅ
አይደለም እንዴ? ብዬ ጠየቅኋት። እ..ብላ ዝም አለች።
ሰውነቷ በጥርጣሬና በሐሳብ የተጠመደ መሰለ፡ ድንገት ከእንቅልፏ ነቅታ ባጋጣሚ ያየችው ይመስል ሁለት እጆቿን ዘርግታ «እውይ እማምዬ ማማሩ! ደስ ማለቱ?» ብላ ከእጁ ላይ ወስዳ ታቀፈችው፡፡
በፊቱ ላይ አንዳችም ሌላ ለውጥ ሳይታይና ፈገግታው ሳይቀንስ ዝርግፍ
ብሉ ወደ እርሷ በመሄዱ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እንዲያውም እዚያች ጠባብ ደረቷ
ላይ ልጥቅ አለ፡፡ ነገር ግን ልጄን ለመጀመሪያ ጊዜ ያቺ የማፈቅራትና
የምንሰፈሰፍላት የወዲያዬ ሳትሆን እኅቴ አቅፋው በማየቴ በፋይዳ የለሽ ጥላቻ
ተናደድኩ፡፡ ጉንጮቹን ሳም ሳም ካደረገች በኋላ ፊቷን ወደ እኔ መለስ አድርጋ
<<የማን ልጅ ነው ?» ብላ በጓጓ ስሜት ጠየቀችኝ። የምናገረው እውነተኛና ርግጠኛ እንዲመስል ለመመለስ የማሰላሰያ ጊዜ አልወሰድኩም፡፡ «አንቺ የማታውቂው አንድ ጓደኛ ነበረኝ፡፡ የዚህ ልጅ አባት ማለቴ ነው። ትዝ እይልሽም ይሆናል እንጂ እኛም ቤት አንድ ሁለት ቀን ያህል መጥቶ ነበር» ካልኩ በኋላ የነገሩን
ድምጥማጥ ይበልጥ ለማጥፋት «ነገር ግን ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሞቷል፡፡ ልጁ ግን ለጊዜው አሳዳጊ ዘመድ በማጣቱ
ይኸው እዚህ በምታይው ሁኔታ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ልጅ አባት በጣም
ግሩም ሰው ስለ ነበር እሱን በማሰብና ለልጁ በማዘን ብቻ አልፎ አልፎ ብቅ
እያልኩ እጠይቀዋለሁ፡፡ ጉልላትም አንዳንድ ቀን እየመጣ ያየዋል» ብዬ ዋሸኋት፡፡ግንባሩን ሁለት ጊዜ ያህል ስማ ውብ ዐይኖቹን ባንጸባራቂ ሸጋ ዐይኖቿ ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው::
«ምነው አንተም እንዲህ የሚያምርና የሚያስጐመዥ ልጅ በነበረህ» ብላ
እንደ ወይን እሽት የሚያስጐመዡትን ጉንጮቹን ሳመቻቸው:: ንግግሯ ለጊዜው
ረግቶና በርዶ የቆየውን የሕሊናዬን ባሕር በብስጭት ማዕበል አረሰው፡፡
“ምናልባት ሚስት ባገባ ማስቴን በርግዝናዋ ወራት ከቤት አታባርሯት
እንደሆነ ነዋ እንዲህ ያለ ልጅ ማግኘት የሚቻለው» ብዩ በሽሙጥ መለስኩላት።
ድንገተኛው የንግግሬ ይዘት ፊቷን አስቀጨመው:: ልጁን ከሰጠችኝ በኋላ
አንገቷን ስብራ አቀረቀረች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ ከወለሉ ላይ ቃላት
እየለቃቀመች ትናገር ይመስል ወለሉን እያየች «ያ ያለፈው ሁሉ ሌላ ጉዳይ
ነው፡፡ የማይገናኙ ነገሮች አታገናኝ እኔን ምን አድርጊ ትለኛለህ? አንተ ከእኔ
የበለጠ ብልህ መሆንህን ዐውቃለሁ አባታችን ቢሰማ ኖሮ በአንተና በእርሱ
መካከል ትልቅ ጠብና ማለቂያ የሌለው
👍4
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...የካቲት ነበር፣ የመጀመሪያዉ እሑድ። ከዚያ ቀደም እንደማደርገው ልዩ ልዩ ነገሮች ይዤላት ወህኒ ቤት ሄድኩ። የወዲያነሽን ለማስጠራት ዐይኔ
እየዋተተ ጠሪ ስፈልግ ከስድስት ዓመታት በፊት በነበራት የፈገግታ ዐይነት ፊቷ
ፈክቶ ሣቅ ሣቅ እያለች «አንተ ጌታነህ! » ብላ ጠራችኝ፡፡ የአሁኑ ፈገግታዋ
ከቀድሞው የሚለየው ፊቷ ከሲታ ሆኖ በመገርጣቱ ብቻ ነው፡፡ ለምን ከአንጀቷ
ፈገግ እንዳለች የምከንያቱ መነሾ ጠፋኝ፡፡ ለወትሮው የወዲያነሽን የማገኛት
እያስጠራሁ ነበር፡፡ የዚያን ዕለት ግን ቀደም ብላ መጥታ ስትጠብቀኝ በመድረሴ ለውጡ ግራ ገባኝ፡፡
ምንም እንኳን ፈገግታዋና ሣቋ ደስ ቢያሰኘኝም ለጊዜው ደስታዬን አምቄ «ደኅና ነሽ ወይ? ደኅና ሰነበትሽ ወይ?» አልኳት። የደስታ ሲቃ እየተናነቃት አይታ የማትጠግበኝ ይመስል ዓይኖቿ ቃበዙ፡፡ አጥሩን ዘላ የምትወጣ መሰለች፡፡
አጥሩ ግን የሥቃይ ሕግ ግድግዳ እንጂ ተራ እንጨት አልነበረም፡፡አፏን ሁለትና ሦስት ጊዜ ከፍታ መልሳ ገጠመችው:: የወሰድኩላትን ጥቂት ዕቃና ምግብ በወታደሯ አማካይነት እንዲደርሳት አደረግሁ፡፡ በማስቀመጥ ፈንታ
ዐቅፋው ቆመች፡፡ የደነገጥን ይመስል
ዝም ተባባልን፡፡ የታቀፈችው ዕቃ
አምልጧት እግሯ ሥር ዱብ አለ፡፡ ተሰባሪ ነገር ስላልነበረበት አልደነገጥኩም፡፡
እዚያው እንዳለ ጎንበስ ብላ እግሮቿ መኻል አስገብታ እጣብቃ ይዛው ቆመች።
ባላት አካላዊ ሁኔታ ላይ ፈገግታዋ የመጨረሻውን ደረጃ ያዘ፡፡
«ጌታነህ» ብላ በዚያች ውብ የሴታ ሴት ድምጺ ከጠራችኝ በኋላ «ነገ ሮብ እኮ» ብላ ዝም እለች፡፡ ከበፊቱ በበለጠ ጥንቃቄ አቆብቁቤና አፍጥጬ
ተመለከትኳት። ዝግ ብላ ምራቋን ዋጠችና «ሮብ እኮሮብ እኮ ትለቀቂያለሽ'
ትፈቺያለሽ ተባልኩ» ብላ በዐይኖቿ ዙሪያ እንባ ከተረ፡፡ የሰማሁት ነገር እውነት
ስላልመሰለኝ ድንገተኛ የደስታ እና የድንጋጤ ሲቃ ያዘኝ፡፡ «ምን?! ምን
አልሽ?!» አልኩና ነፋስ እንዳስጎነበሳት ለጋ ቅርንጫፍ አንገቴን ወደፊት
አሰገግሁ።
«ሮብ ትለቀቂያለሽ ብለውኛል ነው የምልህ» ብላ ጥርሶቿን እንደ ፈለቀቀች ከነፈገግታዋ ዝም አለች፡፡ ዘልዬ በአንገቷ ዙሪያ እንዳልጠመጠምባትና ጮቤ እየዘለልሁ ደስታዬን እንዳልገልጽ በመካከላችን የተጋረጠው ዐፅሙ የገጠጠ አጥር የመከራ ገረገራ ሆኖ አገደኝ፡፡ የምይዝ የምጨብጠው ጠፋኝ። የደስታ ዕብደት አበድኩ፡፡ አዲስ የሕይወት ብርሃን ፏ አለ፡፡ የሰማይን ሰማያዊ ውብ ጣራ አንጋጥጬ ተመለከትኩ፡፡ በውብ የመስክ አበቦች መካከል እየተዘዋወረች ያሻትን አበባ እንደምትቀስም ንብ ሕሊናዬ ባስፈለጋት የደስታ ዐይነት መካከል
እያማረጠች ቦረቀች።
አምስቱ የሥቃይ ዓመታት እንደ አንድ ረዘም ያለ አስፈሪና አስደንጋጭ ሕልም አለፉ። የደስታ ዘለላዎች እየተሸመጠጡ የሚታደለ ተጨባጭ ነገሮች ቢሆኑ ኖሮ በዚያች ሰዓት ውስጥ ለአያሌ ሰዎች እተርፍ ነበር። በደስታ የሚንከባለሉትንና ብዙ ነገር ለማየት የጓጉትን ዐይኖቿን እየተመለከትኩ በይ እንግዲህ መሔዴ ነው፣ ለጉልላትም ልንገረው:: ሮብ ጧት ከሁለት ሰዓት ጀምሮ ካጥር ውጪ እጠብቅሻለሁ» አልኳት፡፡
«ሮብ ዕለት መጥተህ ወዴት ትወስደኛለህ? ከእንግዲህ ወዲያ ደግሞ
አንተን ላስቸግር ነው?» ብላ ተከዘች፡፡
የማያወላውል ዓላማና ግቤን ስለማውቅ በጊዜያዊ ትካዜዋ አልተበሳጨሁም፡፡
ለ ሮብ ዕለተ ጉዳይ የማውቅው እኔ ነኝ፡፡ ጉዳዩን ሁሉ ለእኔ ተይው:: አሁን ግን
ደኅና ዋይ! እንደ ልቤ ልፈንድቅበት!» ብያት ለመጀመሪያ ጊዜ በርግጠኛ ተስፋ
ተሰናብቻት መንገድ ገባሁ፡፡
ከዕለቱ የደስታ ማሕበል የተወለዱ አስደሳች ትርዒቶች በአንጎሌ ውስጥ
እያሸበሸቡ በመደዳ ከነፉ::
ወዲያ ወዲህ ሳልል በቀጥታ ወደ ጉልላት ቤት አመራሁ። የተሣፈርኩባት መኪና በጣም ያዘገመች ስለ መሰለኝ «ቶሎ ቶሎ በል ጃል» እያልኩ በተደጋጋሚ ወተወትኩ፡፡
ጉልላት «መቼ አነሱኝና · ይበቁኛል፣ ከብዙ ደረቅ ጥቂት ርጥብ ይበልጣል» የሚላቸውን የግቢውን አባቦችና አትክልቶች ዐልፌ ወደ ቤት ገባሁ።
እንግዳ መቀበያ ክፍላቸው ውስጥ ጉልላትና እናቱ ወይዘሮ አማከለች ጐን
ለጐን ተቀምጠው ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ እንዴት ሰላምታ ሰጥቻቸው እንደ
ተቀመጥኩ አላስታውስም፡፡ ከእናትዬው ጋር ያደረግሁት «የእንደምን ሰነበቱ?
ሰላምታ በምን አኳኋን እንደ ተፈጸመች ሃች አምና የታየ ሕልምን ያህል እንኳ
አትታወሰኝም፡፡
«ጌታነህ» አሉ ከተቀመጡበት እየተነሡ «እስኪ አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ይሁን ተጫወቱ » ብለው ወደ ውጪ ወጡ። እንዴት ብዬ እንደምጀምር ስለጰ ጠፋኝ ሁለት ጊዜ ሀይኔን ጨፈንኩ፡፡ አልከሠትልህ ስላለኝ ድንገት ተነሣሁ።
ጸጉሬን ካወዲያ ወዲህ አሽቼ መነጨርኩት፡፡ የፍርሃቴ ሸክም ከጭንቅላቴ ላይ ዘጭ ብሎ የወደቀልኝ ይመስል የምሥራች ጉልላት!» አልኩት።
አንጋጦ ዐይን ዐይኔን እያዬ «ምሥር ብላ! ምን አገኘህ?» ብሎ ለመስማት ተጣደፈ። በሕይወቴ ውስጥ ትልቁ ደስታ ሊጀመር፣ ነባሩ የትግላችን ምዕራፍ የፊታችን ሮብ ሲዘጋ ሌላው ደግሞ ወዲያው ይከፈታል!» ብዬ እንደገና አዲስ ብርታት በመጨመር የፊታችን ሮብ የወዲያነሽ ትፈታለች!» አልኩት ጮክ ብዩ።
«እስኪ ሙት በለኝ!» ብሎ አንገቴ ላይ ተጠመጠመ። ለብዙ ዓመታት
እንደ ተለያዩ ጓደኛሞች ተሳሳምን፡፡ ጉልላት በደስታ ባሕር ውስጥ ተዘፍቆ
ውስጣዊ ስሜቱን በይፋ ገለጠ፡፡ ትከሻዩን ያዝ እንዳደረገ ግራና ቀኝ ተቀመጥን።
ፈገግታ በፊቱ ላይ እስክስ አለች። «አየህ እኔና አንተ ባለፈው ቅዳሜ የተሳሳትነው አንድ ነገር ነበር። እጅዋ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ የሚለውን የፍርድ ውሳኔ ዘንግተነዋል። የሰባት ወር ጊዜ ሲጠቃለል ሙሉ አምስት ዓመት
ይሆናል ማለት ነው» ካልኩ በኋላ ጣራ ግድግዳውን በጠቅላላ የቤቱን ዙሪያ
ተመለከትኩት፡፡ «እንግዲህ እኔ እንኳን ደስ ያለህ ነው ወይስ እንኳን ደስ ያለሽ
የምለው?» አለና በደስታ የፈዘዘ አእምሮዬን ለማንቃት ትከሻዬን ይዞ ነቀነቀኝ፡፡
«እኔን አይደለም እርሷን መሆን አለበት፡፡ የእኔማ ጉዳይ ገና ምኑ ተነካና! ገና ብዙ ፈተናና ተከታታይ ችግር ይጠብቀኛል። እሷንና ቤተሰቦቼን ለማገናኘት ወይም ዘላቂ መብትና የእኩልነት ሕልውናዋን ለማረጋገጥ ከመጪው ሮብ ጀምሮ አንድ ትልቅ ተጋድሎና ጦርነት እጀምራለሁ፡፡ የወዲያነሽ ሙሉ የሕሊና ነጻነት እስከምትጎናጸፍ ድረስ እታገላለሁ፡፡ በተመሳሳይ የሕሊና ባርነት ውስጥ የሚገኙ እልፍ አዕላፍ ሰዎች ስላሉ ብቻችንን አይደለንም፡፡ ያም ሆነ ይህ
ከወላጆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ግን ከሮብ ጀምሮ ከዋናው ግንድ ላይ ተሰብራ
በልጧ ብቻ የተንጠለጠለች ቅርንጫፍ እምሳያ መሆኑ ነው» ብዬ መለስኩለት፡፡
በንግግሬ ውስጥ ያለውን የሐሳብ ይዘት እያሰላሰለ ጥቂት ዝም ስላለ «ብዙ ጊዜ
ቢፈጅም አንድ ቀን ድል እንደማደርግ አውቃለሁ፡፡ ይህን አስፈሪ መሳይ ያረጀ
አፍራሽ የልማድ ድልድይ እንዴት ኣድርጌ እንደማልፈውና እንደምሻገረው ካሁኑ
ጭንቅ ጥብብ ብሎኛል። የምፈራውና የሚያርበተብተኝ ምን እንደሆነ አሣምረህ
ታውቀዋለህ፡፡ ፍርሃቴ በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ግን የወዲያነሽን ለመከራ አሳልፈ መስጠቴ ነው» ብዪ እንደ ጨረስኩ ወደ ጉዳዩ ዝርዝር ክርክርና ፍሬ ነገር ገባን።
ያን ዕለት ከሰዓት በኋላ ወደ ዕጓለ ማውታ ሳልሄድ ቀረሁ። ከቤቱ ውስጥ ወበቅ ደጁ ይሻል ይሆናል በማለት ከቤት ከወጣን በኋላ ግራና ቀኝ ቆም እንዳልን
«እንግዲህ የወዲያነሽ ነገ ሮብ መፈታቷ ነው:: ከወህኒ ቤት እንደ ወጣች ከእኔ
ሌላ ምንም መግቢያና መጠጊያ የላትም፡፡ ስለዚህ ነገም ይሁን ከነገ ወዲያ ባፋጣኝ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...የካቲት ነበር፣ የመጀመሪያዉ እሑድ። ከዚያ ቀደም እንደማደርገው ልዩ ልዩ ነገሮች ይዤላት ወህኒ ቤት ሄድኩ። የወዲያነሽን ለማስጠራት ዐይኔ
እየዋተተ ጠሪ ስፈልግ ከስድስት ዓመታት በፊት በነበራት የፈገግታ ዐይነት ፊቷ
ፈክቶ ሣቅ ሣቅ እያለች «አንተ ጌታነህ! » ብላ ጠራችኝ፡፡ የአሁኑ ፈገግታዋ
ከቀድሞው የሚለየው ፊቷ ከሲታ ሆኖ በመገርጣቱ ብቻ ነው፡፡ ለምን ከአንጀቷ
ፈገግ እንዳለች የምከንያቱ መነሾ ጠፋኝ፡፡ ለወትሮው የወዲያነሽን የማገኛት
እያስጠራሁ ነበር፡፡ የዚያን ዕለት ግን ቀደም ብላ መጥታ ስትጠብቀኝ በመድረሴ ለውጡ ግራ ገባኝ፡፡
ምንም እንኳን ፈገግታዋና ሣቋ ደስ ቢያሰኘኝም ለጊዜው ደስታዬን አምቄ «ደኅና ነሽ ወይ? ደኅና ሰነበትሽ ወይ?» አልኳት። የደስታ ሲቃ እየተናነቃት አይታ የማትጠግበኝ ይመስል ዓይኖቿ ቃበዙ፡፡ አጥሩን ዘላ የምትወጣ መሰለች፡፡
አጥሩ ግን የሥቃይ ሕግ ግድግዳ እንጂ ተራ እንጨት አልነበረም፡፡አፏን ሁለትና ሦስት ጊዜ ከፍታ መልሳ ገጠመችው:: የወሰድኩላትን ጥቂት ዕቃና ምግብ በወታደሯ አማካይነት እንዲደርሳት አደረግሁ፡፡ በማስቀመጥ ፈንታ
ዐቅፋው ቆመች፡፡ የደነገጥን ይመስል
ዝም ተባባልን፡፡ የታቀፈችው ዕቃ
አምልጧት እግሯ ሥር ዱብ አለ፡፡ ተሰባሪ ነገር ስላልነበረበት አልደነገጥኩም፡፡
እዚያው እንዳለ ጎንበስ ብላ እግሮቿ መኻል አስገብታ እጣብቃ ይዛው ቆመች።
ባላት አካላዊ ሁኔታ ላይ ፈገግታዋ የመጨረሻውን ደረጃ ያዘ፡፡
«ጌታነህ» ብላ በዚያች ውብ የሴታ ሴት ድምጺ ከጠራችኝ በኋላ «ነገ ሮብ እኮ» ብላ ዝም እለች፡፡ ከበፊቱ በበለጠ ጥንቃቄ አቆብቁቤና አፍጥጬ
ተመለከትኳት። ዝግ ብላ ምራቋን ዋጠችና «ሮብ እኮሮብ እኮ ትለቀቂያለሽ'
ትፈቺያለሽ ተባልኩ» ብላ በዐይኖቿ ዙሪያ እንባ ከተረ፡፡ የሰማሁት ነገር እውነት
ስላልመሰለኝ ድንገተኛ የደስታ እና የድንጋጤ ሲቃ ያዘኝ፡፡ «ምን?! ምን
አልሽ?!» አልኩና ነፋስ እንዳስጎነበሳት ለጋ ቅርንጫፍ አንገቴን ወደፊት
አሰገግሁ።
«ሮብ ትለቀቂያለሽ ብለውኛል ነው የምልህ» ብላ ጥርሶቿን እንደ ፈለቀቀች ከነፈገግታዋ ዝም አለች፡፡ ዘልዬ በአንገቷ ዙሪያ እንዳልጠመጠምባትና ጮቤ እየዘለልሁ ደስታዬን እንዳልገልጽ በመካከላችን የተጋረጠው ዐፅሙ የገጠጠ አጥር የመከራ ገረገራ ሆኖ አገደኝ፡፡ የምይዝ የምጨብጠው ጠፋኝ። የደስታ ዕብደት አበድኩ፡፡ አዲስ የሕይወት ብርሃን ፏ አለ፡፡ የሰማይን ሰማያዊ ውብ ጣራ አንጋጥጬ ተመለከትኩ፡፡ በውብ የመስክ አበቦች መካከል እየተዘዋወረች ያሻትን አበባ እንደምትቀስም ንብ ሕሊናዬ ባስፈለጋት የደስታ ዐይነት መካከል
እያማረጠች ቦረቀች።
አምስቱ የሥቃይ ዓመታት እንደ አንድ ረዘም ያለ አስፈሪና አስደንጋጭ ሕልም አለፉ። የደስታ ዘለላዎች እየተሸመጠጡ የሚታደለ ተጨባጭ ነገሮች ቢሆኑ ኖሮ በዚያች ሰዓት ውስጥ ለአያሌ ሰዎች እተርፍ ነበር። በደስታ የሚንከባለሉትንና ብዙ ነገር ለማየት የጓጉትን ዐይኖቿን እየተመለከትኩ በይ እንግዲህ መሔዴ ነው፣ ለጉልላትም ልንገረው:: ሮብ ጧት ከሁለት ሰዓት ጀምሮ ካጥር ውጪ እጠብቅሻለሁ» አልኳት፡፡
«ሮብ ዕለት መጥተህ ወዴት ትወስደኛለህ? ከእንግዲህ ወዲያ ደግሞ
አንተን ላስቸግር ነው?» ብላ ተከዘች፡፡
የማያወላውል ዓላማና ግቤን ስለማውቅ በጊዜያዊ ትካዜዋ አልተበሳጨሁም፡፡
ለ ሮብ ዕለተ ጉዳይ የማውቅው እኔ ነኝ፡፡ ጉዳዩን ሁሉ ለእኔ ተይው:: አሁን ግን
ደኅና ዋይ! እንደ ልቤ ልፈንድቅበት!» ብያት ለመጀመሪያ ጊዜ በርግጠኛ ተስፋ
ተሰናብቻት መንገድ ገባሁ፡፡
ከዕለቱ የደስታ ማሕበል የተወለዱ አስደሳች ትርዒቶች በአንጎሌ ውስጥ
እያሸበሸቡ በመደዳ ከነፉ::
ወዲያ ወዲህ ሳልል በቀጥታ ወደ ጉልላት ቤት አመራሁ። የተሣፈርኩባት መኪና በጣም ያዘገመች ስለ መሰለኝ «ቶሎ ቶሎ በል ጃል» እያልኩ በተደጋጋሚ ወተወትኩ፡፡
ጉልላት «መቼ አነሱኝና · ይበቁኛል፣ ከብዙ ደረቅ ጥቂት ርጥብ ይበልጣል» የሚላቸውን የግቢውን አባቦችና አትክልቶች ዐልፌ ወደ ቤት ገባሁ።
እንግዳ መቀበያ ክፍላቸው ውስጥ ጉልላትና እናቱ ወይዘሮ አማከለች ጐን
ለጐን ተቀምጠው ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ እንዴት ሰላምታ ሰጥቻቸው እንደ
ተቀመጥኩ አላስታውስም፡፡ ከእናትዬው ጋር ያደረግሁት «የእንደምን ሰነበቱ?
ሰላምታ በምን አኳኋን እንደ ተፈጸመች ሃች አምና የታየ ሕልምን ያህል እንኳ
አትታወሰኝም፡፡
«ጌታነህ» አሉ ከተቀመጡበት እየተነሡ «እስኪ አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ይሁን ተጫወቱ » ብለው ወደ ውጪ ወጡ። እንዴት ብዬ እንደምጀምር ስለጰ ጠፋኝ ሁለት ጊዜ ሀይኔን ጨፈንኩ፡፡ አልከሠትልህ ስላለኝ ድንገት ተነሣሁ።
ጸጉሬን ካወዲያ ወዲህ አሽቼ መነጨርኩት፡፡ የፍርሃቴ ሸክም ከጭንቅላቴ ላይ ዘጭ ብሎ የወደቀልኝ ይመስል የምሥራች ጉልላት!» አልኩት።
አንጋጦ ዐይን ዐይኔን እያዬ «ምሥር ብላ! ምን አገኘህ?» ብሎ ለመስማት ተጣደፈ። በሕይወቴ ውስጥ ትልቁ ደስታ ሊጀመር፣ ነባሩ የትግላችን ምዕራፍ የፊታችን ሮብ ሲዘጋ ሌላው ደግሞ ወዲያው ይከፈታል!» ብዬ እንደገና አዲስ ብርታት በመጨመር የፊታችን ሮብ የወዲያነሽ ትፈታለች!» አልኩት ጮክ ብዩ።
«እስኪ ሙት በለኝ!» ብሎ አንገቴ ላይ ተጠመጠመ። ለብዙ ዓመታት
እንደ ተለያዩ ጓደኛሞች ተሳሳምን፡፡ ጉልላት በደስታ ባሕር ውስጥ ተዘፍቆ
ውስጣዊ ስሜቱን በይፋ ገለጠ፡፡ ትከሻዩን ያዝ እንዳደረገ ግራና ቀኝ ተቀመጥን።
ፈገግታ በፊቱ ላይ እስክስ አለች። «አየህ እኔና አንተ ባለፈው ቅዳሜ የተሳሳትነው አንድ ነገር ነበር። እጅዋ ከተያዘበት ዕለት ጀምሮ የሚለውን የፍርድ ውሳኔ ዘንግተነዋል። የሰባት ወር ጊዜ ሲጠቃለል ሙሉ አምስት ዓመት
ይሆናል ማለት ነው» ካልኩ በኋላ ጣራ ግድግዳውን በጠቅላላ የቤቱን ዙሪያ
ተመለከትኩት፡፡ «እንግዲህ እኔ እንኳን ደስ ያለህ ነው ወይስ እንኳን ደስ ያለሽ
የምለው?» አለና በደስታ የፈዘዘ አእምሮዬን ለማንቃት ትከሻዬን ይዞ ነቀነቀኝ፡፡
«እኔን አይደለም እርሷን መሆን አለበት፡፡ የእኔማ ጉዳይ ገና ምኑ ተነካና! ገና ብዙ ፈተናና ተከታታይ ችግር ይጠብቀኛል። እሷንና ቤተሰቦቼን ለማገናኘት ወይም ዘላቂ መብትና የእኩልነት ሕልውናዋን ለማረጋገጥ ከመጪው ሮብ ጀምሮ አንድ ትልቅ ተጋድሎና ጦርነት እጀምራለሁ፡፡ የወዲያነሽ ሙሉ የሕሊና ነጻነት እስከምትጎናጸፍ ድረስ እታገላለሁ፡፡ በተመሳሳይ የሕሊና ባርነት ውስጥ የሚገኙ እልፍ አዕላፍ ሰዎች ስላሉ ብቻችንን አይደለንም፡፡ ያም ሆነ ይህ
ከወላጆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ግን ከሮብ ጀምሮ ከዋናው ግንድ ላይ ተሰብራ
በልጧ ብቻ የተንጠለጠለች ቅርንጫፍ እምሳያ መሆኑ ነው» ብዬ መለስኩለት፡፡
በንግግሬ ውስጥ ያለውን የሐሳብ ይዘት እያሰላሰለ ጥቂት ዝም ስላለ «ብዙ ጊዜ
ቢፈጅም አንድ ቀን ድል እንደማደርግ አውቃለሁ፡፡ ይህን አስፈሪ መሳይ ያረጀ
አፍራሽ የልማድ ድልድይ እንዴት ኣድርጌ እንደማልፈውና እንደምሻገረው ካሁኑ
ጭንቅ ጥብብ ብሎኛል። የምፈራውና የሚያርበተብተኝ ምን እንደሆነ አሣምረህ
ታውቀዋለህ፡፡ ፍርሃቴ በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ ግን የወዲያነሽን ለመከራ አሳልፈ መስጠቴ ነው» ብዪ እንደ ጨረስኩ ወደ ጉዳዩ ዝርዝር ክርክርና ፍሬ ነገር ገባን።
ያን ዕለት ከሰዓት በኋላ ወደ ዕጓለ ማውታ ሳልሄድ ቀረሁ። ከቤቱ ውስጥ ወበቅ ደጁ ይሻል ይሆናል በማለት ከቤት ከወጣን በኋላ ግራና ቀኝ ቆም እንዳልን
«እንግዲህ የወዲያነሽ ነገ ሮብ መፈታቷ ነው:: ከወህኒ ቤት እንደ ወጣች ከእኔ
ሌላ ምንም መግቢያና መጠጊያ የላትም፡፡ ስለዚህ ነገም ይሁን ከነገ ወዲያ ባፋጣኝ
👍2
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጉልላት ከመንቃቱ በፊት ለዐሥራ ሁለት ሰዓት ኻያ አምስት ጉዳይ እንደሆነ ልብሴን ለባበስኩ፡፡ የማክሰኛ ውሱን ዕድሜ ከማለቋ በፊት ወደ ውጪ
ወጣሁ፡፡ ምሥራቃዊው አድማስ ቀይ ሽንብራ መስሏል፡፡ ቆሜ አካባቢዩን
ስመለከት ንጣትና ቅላት ተጋጩ፡፡ የአዲሱ ዛሬና የአሮጌው ትላንትና የመጨረሻ
ግብ ግብ ነበር! አሽናፊውን በመለየት ላይ ሳለሁ አዲሷ ሮብ ተማጠች። ዐሥራ
ሁለት ሰዓት ማለቂያ ላይ እንደ ተወለደች አዕዋፍ የዕለቱን የመጨረሻ የእልልታ
ድምፅ አሰሙ፡፡ ምንጊዜም ለዘላለም የማትመለሰዋን ሮብ በፍርሃትና በጉጉት
ተቀበልኳት፡፡ ፊቴን ታጥቤና ጸጉሬን አበጥሬ እንደ ጨረስኩ ጉልላት ነቃ፡፡
ልብሱን ለባብሶና ተጣጥቦ ሲጨርስ ልክ ሁለት ሰዓት ደፈነ። እያንዳንዷ የሰውነቴ
ጡንቻ፣ ተባርኮ ሕይወቱ በማለፍ ላይ እንዳለ ወጠጤ ተፈራገጠች፡፡ የተዘጋጀ
ወይም ሊዘጋጅ የሚችል ቁርስ ስላልነበረን በባዶ አፋችን ከቤት ወጣን፡፡
የሰዓቴ የደቂቃ ዘንግ ኻያ ደቂቃ ጨመረ። ጉልላት ጠንቀቅ ባለ ስሜት
«እኔ አሁን አደርስህና ሠራተኛ ለማምጣት እመለሳለሁ። የቤት ሠራተኛ ያስፈልጋል። ሥራ ቦታ አሁኑኑ ስለምመለስ የቤቱን ቁልፍ ስጠኝ ብሎ ወሰደ።የሕሊና ምጥ ያዘኝ፡፡ የግልግሌ ደቂቃ እየተቃረበች ብትመጣም ሙሉ እፎይታ ለማግኘት ገና የትናየት ይቀረኛል፡፡ ልክ ለሦስት ሰዓት ኻያ ጉዳይ ሲሆን በጉልላት ቮልስዋገን ወህኒ ቤት ደረስን። «እኔ አሁኑኑ ከሥራ እመለሳለሁ! ሁሉንም ነገር አሰናድቼ እጠብቅሃለሁ:: አይዞህ በርታ! አእምሮዋ በድንጋጤና በጥርጣሬ እንዳይታመስ ከአሁኑ ደቂቃ ጀምረህ ሙሉ ረዳቷና አለኝታዋ መሆንህን በተግባር ግለጽላት፡፡ በል እንግዲህ አብሬህ ከምቆይ ይልቅ ሄጄ የማከናውነው ይበልጣልና ልሒድ!» ብሎ መኪናውን ሲያስነሣ በሩን ከፍቼ
ወጣሁ፡፡
ከውጪ በመስኮቱ በኩል «እምብዛም አትጨነቅ የወዲያነሽን ባለኝ ነገር
ብቻ ተሰናድቼ እንድቀበላት እንጂ በጭንቀት ተከብቤ እንዳስተናግዳት አልሻም፡፡ያም ሆነ ይህ ሁሉንም ታውቀዋለህና ሂድ» አልኩት፡፡ መኪናውን ጠምዝዞ ሔደ።ከወህኒ ቤቱ ትልቅ የብረት በር አጠገብ ያለውን ግንብ ተደግፌ የጊዜን ፍጥነት እታዘብ ጀመር፡፡ እያንዳንዷ ደቂቃ የአንድ ሰዓት ያህል የርዝማኔ ቆይታ በማድረግ ላይ ያለች መሰለኝ። እጄ ላይ ያሰርኳት ሰዓት የጊዜን የፍሰሰት ሕግ መለወጥ ትችል ይመስል ደጋግሜ ኣየኋት።
አይቻልም እንጂ የሚቻለኝ ቢሆን ኖሮ ተሽከርካሪዋን ዓለም በቡጢ ነርቼ
ካላት ፍጥነት በላይ እንድትሾር የማድረግ ከንቱ ፍላጎት ነበረኝ፡፡ የጊዜና የስሜት
ቁርኝት ገረመኝ፡፡ ጊዜ በአእምሯችን የስሜት ፍላጎት መጠን ሲያጥርና ሲረዝም ተሰማኝ፡፡ ሆኖም ስለ ሕልም ማለም ምን ይጠቅማል? በዚያች ቀን አንድ ሰዓት ስድሳ ካልኢቶች ብቻ መሆኗ አጠራጠረኝ፡፡ የቢሮ ውስጥ ጣጣ እስኪፈጸምና የሕይወቴ ክፋይ በሩን አልፋ እንደ ንጋት ጮራ ብቅ እስከምትል' ከአንድ ሰዓት በላይ መጠባበቅ ነበረብኝ፡፡
የናፍቆት የትዝታ፣ የደስታና የአዲስ ሕይወት ስሜት አቅበጠበጠኝ። ድንጋዩ ጠጠሩ' ሣር ቅጠሉ' ግንቡ' ከሩቅ የሚታዩት ዛፎች፣ አላፈ እግዳሚው ሁሉ ደስታ ፈጣሪ ትርዒቶች ሆኑ፡፡ አንጎሌ በደስታ እና በኃዘን በሽብር እና በተስፋ ጥንስስ ተዥጎረጎረ። በአንድ በማላውቀው አስደሳችና ሸንተራራማ ለምላሚ ውስጥ ያለሁ መሰለኝ። በቅኔው ሲኦል ወርዶ በደስታና በኃዘን እንደባዘነው ባለቅኔ እኔም ወህኒ ቤት በር ላይ ተቀምጩ የወዲያነሽን በመጠባበቅ ደስታና ኃዘንን እያፈራረቅሁ ገመጥኩ። ከጊዜ ጋር ተፋጠጥን። የእኔ ልብ በጉጉትና በጥድፊያ ተጠምዳ ድው…ድው እንደምትል ሁሉ፣ የወዲያነሽም
ካጥሩ ወዲያ ባለው ምድራዊ ሲኦል ውስጥ እንደ እኔው እንደምትሆን ታወቀኝ፡፡ የጊዜ ሕግ ሆነና ግማሽ ሰዓት ዐለፈ፡፡
በሕይወቴ ውስጥ ትልቁ የኑሮ ፍሥሓ መረዋ ተደወለ። ግዙፉ የብረት በር ገርገጭ አለ፡፡ የሰውነቴ ውስጣዊ እንቅስቃሴ አብሮ ተንገራገጨ። የት
እንዳለሁና ምን እንደማደርግ ማወቅ ተሳነኝ፡፡ በሩ እንደገና ሲጢጢጢጢጢ
የሚል ቀጭን የብረት ፍጭት ድምፅ አሰማ፡፡ እንደ አይጥ መንጋ የጮኸው በር
ተርገፈገፈ የተጠበቀ የትግል ምዕራፍ! በሩ ወለል ብሎ ተከፈተ! ሁለት ወንዶችና ኣዲት ቀጠን ብላ ቁመቷ ዘለግ፣ መልኳ ጠቆር ያለ ሴት በሩን ዐልፈው ወጡ፡፡ አዎ ውዲቱ የሕይወቴ ግርማ ሞገስ የወህኒ ቤቱን በር ዐልፋ ወጣች! ሕይወት ውብ ዝማሬ ዘመረች አዝማቿን ተቀበልኩ፡፡
«የወዲያነሽ! የወዲያ! እዚህ ነኝ! መጥቻለሁ!» ብዬ ጠራኋት፡፡ እኔ ወደሷ፣ እሷ ወደ እኔ ገሠገሥን፡፡ እጆቿን ዘርግታ ስትጠመጠምብኝ የፍቅራችን
ዳግማዊ ትንሣኤ ሆነ!! የሰውነቷ ጠረን ውሃ ያርከፈከፉበት ዐፈር ዐፈር ይላል። በእጅዎ የያዘቻት ቁራጭ ወረቀት ጫማዩን መታ አድርጋ ከእግሬ ሥር ወደቀች።አብረዋት የተለቀቁት ሁለት ወንዶች መለስ ብለው እንኳ ሳያዩን ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ በደስታ የተዝለፈለፈው አካላቴ አልንቀሳቀስ አለኝ፡፡ ዐሥር የማይሞሉ እርምጃዎች እንደ ተራመድን ከመንገድ ዳር ለምለም ሣር ላይ ተቀመጥን።
እይቼ አልጠግባት አልኩ፡፡ የወዲያነሽ እይታ ስላልጠገበችኝና የናፍቆቷም ከርስ
ስላልሞላች እንደገና ተሳሳምን፡፡ ዐይኖቿን አሻሽቻቸው:: እጆቿ ሲነሡ እንባዋ
ተዘረገፈ፡፡ ወደ ወህኒ ቤት ከወሰድኩላት ልብሶች መካከል አንድም ይዛ አልወጣችም። ቀኝ እጄን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጌ በትዝታ ተመለከትኳት።
የአንገቷና የደረቷ አካባቢ ቀሚሷም ጭምር በጭቅቅት ተበልቷል፡፡ ፊቷ ጠቆር ብሎ ከመክሳቱ በስተቀር ልዩ ለውጥ አይታይበትም፡፡ ዐይኖቿ ፈዘዝ ብለው ቀልተዋል፡፡ ቆዳ ጫማዋ በቀለም እጦት ተላልጧል። አንጀቴ እርር በማለቱ
ከንፈሬን በንዴት ነከስኩት፡፡ ትንሽ አዘገምን፡፡ ዳሩ ግን የየወዲያነሽ እግር
በመቀያየዱ በታክሲ ተሳፈርን፡፡
ከእስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ትንሽ እልፍ ብለን ድልድዩ ጋ ሳይደርስ ወረድን፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ የምታሻቅበውን አጭር አቀበት እጅ ለእጅ ተያይዘን ወጣናት፡፡ የወዲያነሽ እጅዋን ከእጄ ኣላቅቃ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር በር ሄደች። ተከተልኳት። በብረቱ በር ላይ ያለውን የብረት መስቀል በግንባሯ እየገጨች «አንተ ታውቅልኛለህ ጌታዬ! ለዚህ ያበቃኸኝ ጌታ ተመስገን! አንተው ሁነኝ» ብላ በሻከረ ድምፅ ተናገረች፡፡ ወዴት እንደምወስዳት ስለማታውቅ ዝም ብላ ተከተለችኝ፡፡ የአዲሱ ቤታችን በር ወለል ብሎ ተከፍቷል፡፡ ከማድ ቤት
የሚወጣው ጢስ በመስኮትና በመዝጊያው በኩል እንደ ሐምሌ ጉም ዝግ እያለ ይትጎለጎላል።
በኑሮ ተጐሳቁላ በእስራት የማቀቀችውን የወዲያነሽን ባለፉት ሁለት ቀናት የእኔ ባልኩትና ዛሬ ደግሞ በሁለታችን ውሕደት የእኛ ወደምለው ቤት ይዣት ስገባ በረጂሙ ትግሌ ውስጥ አነስተኛ ድል አድራጊነት ተሰማኝ፡፡
እንዲት ቀጠን ረዘም ያሉ ቀይ ሴትዮ ቀሚሳቸውን በቀኝ እጃቸው ከፍ
ሰብሰብ እያደረጉና የአዘኔታ ገጽታ እያሳዩ መጣችሁ? እሰየው እሰይ! በሉ ግቡ!
ግቡ!» ብለው እኛን እኛን እያዩ ቆሙ። «ኧረ በእግዚአብሔር ምነው ምነው?
በሉ ተቀመጡ! » ብዬ እንዲቀመጡ አደረግሁ፡፡ የወዲያነሽም ባቀረብኩላት
ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ሴትዮዋ ትንሽ ከእኛ ፈንጠር ብለው ስኒ በረከቦትና
የሚሰክን ጀበና አጠገባቸው አለ፡፡
ቀበርቾ፣ ዕጣን፣ ደረቅ የሎሚ ልጣጭ፣
መዝጊያው ሥር ጊርጊራ ላይ ይጨሳሉ፡፡ ሽታው አብሮ አደጌ ሽታ በመሆኑ ደስ
አለኝ፡፡
«እሱም እዚሁ ከቤት ውስጥ ነው ሲሠራና ዕቃውን ሲያስተካክል የዋለው: እሁን እመጣለሁ ብሎ ነው ወጣ ያለው፣ እንዲህ ቶሎ የምትመጣም አልመሰለው» አሉና ጀበናይቱን አነሱ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጉልላት ከመንቃቱ በፊት ለዐሥራ ሁለት ሰዓት ኻያ አምስት ጉዳይ እንደሆነ ልብሴን ለባበስኩ፡፡ የማክሰኛ ውሱን ዕድሜ ከማለቋ በፊት ወደ ውጪ
ወጣሁ፡፡ ምሥራቃዊው አድማስ ቀይ ሽንብራ መስሏል፡፡ ቆሜ አካባቢዩን
ስመለከት ንጣትና ቅላት ተጋጩ፡፡ የአዲሱ ዛሬና የአሮጌው ትላንትና የመጨረሻ
ግብ ግብ ነበር! አሽናፊውን በመለየት ላይ ሳለሁ አዲሷ ሮብ ተማጠች። ዐሥራ
ሁለት ሰዓት ማለቂያ ላይ እንደ ተወለደች አዕዋፍ የዕለቱን የመጨረሻ የእልልታ
ድምፅ አሰሙ፡፡ ምንጊዜም ለዘላለም የማትመለሰዋን ሮብ በፍርሃትና በጉጉት
ተቀበልኳት፡፡ ፊቴን ታጥቤና ጸጉሬን አበጥሬ እንደ ጨረስኩ ጉልላት ነቃ፡፡
ልብሱን ለባብሶና ተጣጥቦ ሲጨርስ ልክ ሁለት ሰዓት ደፈነ። እያንዳንዷ የሰውነቴ
ጡንቻ፣ ተባርኮ ሕይወቱ በማለፍ ላይ እንዳለ ወጠጤ ተፈራገጠች፡፡ የተዘጋጀ
ወይም ሊዘጋጅ የሚችል ቁርስ ስላልነበረን በባዶ አፋችን ከቤት ወጣን፡፡
የሰዓቴ የደቂቃ ዘንግ ኻያ ደቂቃ ጨመረ። ጉልላት ጠንቀቅ ባለ ስሜት
«እኔ አሁን አደርስህና ሠራተኛ ለማምጣት እመለሳለሁ። የቤት ሠራተኛ ያስፈልጋል። ሥራ ቦታ አሁኑኑ ስለምመለስ የቤቱን ቁልፍ ስጠኝ ብሎ ወሰደ።የሕሊና ምጥ ያዘኝ፡፡ የግልግሌ ደቂቃ እየተቃረበች ብትመጣም ሙሉ እፎይታ ለማግኘት ገና የትናየት ይቀረኛል፡፡ ልክ ለሦስት ሰዓት ኻያ ጉዳይ ሲሆን በጉልላት ቮልስዋገን ወህኒ ቤት ደረስን። «እኔ አሁኑኑ ከሥራ እመለሳለሁ! ሁሉንም ነገር አሰናድቼ እጠብቅሃለሁ:: አይዞህ በርታ! አእምሮዋ በድንጋጤና በጥርጣሬ እንዳይታመስ ከአሁኑ ደቂቃ ጀምረህ ሙሉ ረዳቷና አለኝታዋ መሆንህን በተግባር ግለጽላት፡፡ በል እንግዲህ አብሬህ ከምቆይ ይልቅ ሄጄ የማከናውነው ይበልጣልና ልሒድ!» ብሎ መኪናውን ሲያስነሣ በሩን ከፍቼ
ወጣሁ፡፡
ከውጪ በመስኮቱ በኩል «እምብዛም አትጨነቅ የወዲያነሽን ባለኝ ነገር
ብቻ ተሰናድቼ እንድቀበላት እንጂ በጭንቀት ተከብቤ እንዳስተናግዳት አልሻም፡፡ያም ሆነ ይህ ሁሉንም ታውቀዋለህና ሂድ» አልኩት፡፡ መኪናውን ጠምዝዞ ሔደ።ከወህኒ ቤቱ ትልቅ የብረት በር አጠገብ ያለውን ግንብ ተደግፌ የጊዜን ፍጥነት እታዘብ ጀመር፡፡ እያንዳንዷ ደቂቃ የአንድ ሰዓት ያህል የርዝማኔ ቆይታ በማድረግ ላይ ያለች መሰለኝ። እጄ ላይ ያሰርኳት ሰዓት የጊዜን የፍሰሰት ሕግ መለወጥ ትችል ይመስል ደጋግሜ ኣየኋት።
አይቻልም እንጂ የሚቻለኝ ቢሆን ኖሮ ተሽከርካሪዋን ዓለም በቡጢ ነርቼ
ካላት ፍጥነት በላይ እንድትሾር የማድረግ ከንቱ ፍላጎት ነበረኝ፡፡ የጊዜና የስሜት
ቁርኝት ገረመኝ፡፡ ጊዜ በአእምሯችን የስሜት ፍላጎት መጠን ሲያጥርና ሲረዝም ተሰማኝ፡፡ ሆኖም ስለ ሕልም ማለም ምን ይጠቅማል? በዚያች ቀን አንድ ሰዓት ስድሳ ካልኢቶች ብቻ መሆኗ አጠራጠረኝ፡፡ የቢሮ ውስጥ ጣጣ እስኪፈጸምና የሕይወቴ ክፋይ በሩን አልፋ እንደ ንጋት ጮራ ብቅ እስከምትል' ከአንድ ሰዓት በላይ መጠባበቅ ነበረብኝ፡፡
የናፍቆት የትዝታ፣ የደስታና የአዲስ ሕይወት ስሜት አቅበጠበጠኝ። ድንጋዩ ጠጠሩ' ሣር ቅጠሉ' ግንቡ' ከሩቅ የሚታዩት ዛፎች፣ አላፈ እግዳሚው ሁሉ ደስታ ፈጣሪ ትርዒቶች ሆኑ፡፡ አንጎሌ በደስታ እና በኃዘን በሽብር እና በተስፋ ጥንስስ ተዥጎረጎረ። በአንድ በማላውቀው አስደሳችና ሸንተራራማ ለምላሚ ውስጥ ያለሁ መሰለኝ። በቅኔው ሲኦል ወርዶ በደስታና በኃዘን እንደባዘነው ባለቅኔ እኔም ወህኒ ቤት በር ላይ ተቀምጩ የወዲያነሽን በመጠባበቅ ደስታና ኃዘንን እያፈራረቅሁ ገመጥኩ። ከጊዜ ጋር ተፋጠጥን። የእኔ ልብ በጉጉትና በጥድፊያ ተጠምዳ ድው…ድው እንደምትል ሁሉ፣ የወዲያነሽም
ካጥሩ ወዲያ ባለው ምድራዊ ሲኦል ውስጥ እንደ እኔው እንደምትሆን ታወቀኝ፡፡ የጊዜ ሕግ ሆነና ግማሽ ሰዓት ዐለፈ፡፡
በሕይወቴ ውስጥ ትልቁ የኑሮ ፍሥሓ መረዋ ተደወለ። ግዙፉ የብረት በር ገርገጭ አለ፡፡ የሰውነቴ ውስጣዊ እንቅስቃሴ አብሮ ተንገራገጨ። የት
እንዳለሁና ምን እንደማደርግ ማወቅ ተሳነኝ፡፡ በሩ እንደገና ሲጢጢጢጢጢ
የሚል ቀጭን የብረት ፍጭት ድምፅ አሰማ፡፡ እንደ አይጥ መንጋ የጮኸው በር
ተርገፈገፈ የተጠበቀ የትግል ምዕራፍ! በሩ ወለል ብሎ ተከፈተ! ሁለት ወንዶችና ኣዲት ቀጠን ብላ ቁመቷ ዘለግ፣ መልኳ ጠቆር ያለ ሴት በሩን ዐልፈው ወጡ፡፡ አዎ ውዲቱ የሕይወቴ ግርማ ሞገስ የወህኒ ቤቱን በር ዐልፋ ወጣች! ሕይወት ውብ ዝማሬ ዘመረች አዝማቿን ተቀበልኩ፡፡
«የወዲያነሽ! የወዲያ! እዚህ ነኝ! መጥቻለሁ!» ብዬ ጠራኋት፡፡ እኔ ወደሷ፣ እሷ ወደ እኔ ገሠገሥን፡፡ እጆቿን ዘርግታ ስትጠመጠምብኝ የፍቅራችን
ዳግማዊ ትንሣኤ ሆነ!! የሰውነቷ ጠረን ውሃ ያርከፈከፉበት ዐፈር ዐፈር ይላል። በእጅዎ የያዘቻት ቁራጭ ወረቀት ጫማዩን መታ አድርጋ ከእግሬ ሥር ወደቀች።አብረዋት የተለቀቁት ሁለት ወንዶች መለስ ብለው እንኳ ሳያዩን ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ በደስታ የተዝለፈለፈው አካላቴ አልንቀሳቀስ አለኝ፡፡ ዐሥር የማይሞሉ እርምጃዎች እንደ ተራመድን ከመንገድ ዳር ለምለም ሣር ላይ ተቀመጥን።
እይቼ አልጠግባት አልኩ፡፡ የወዲያነሽ እይታ ስላልጠገበችኝና የናፍቆቷም ከርስ
ስላልሞላች እንደገና ተሳሳምን፡፡ ዐይኖቿን አሻሽቻቸው:: እጆቿ ሲነሡ እንባዋ
ተዘረገፈ፡፡ ወደ ወህኒ ቤት ከወሰድኩላት ልብሶች መካከል አንድም ይዛ አልወጣችም። ቀኝ እጄን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጌ በትዝታ ተመለከትኳት።
የአንገቷና የደረቷ አካባቢ ቀሚሷም ጭምር በጭቅቅት ተበልቷል፡፡ ፊቷ ጠቆር ብሎ ከመክሳቱ በስተቀር ልዩ ለውጥ አይታይበትም፡፡ ዐይኖቿ ፈዘዝ ብለው ቀልተዋል፡፡ ቆዳ ጫማዋ በቀለም እጦት ተላልጧል። አንጀቴ እርር በማለቱ
ከንፈሬን በንዴት ነከስኩት፡፡ ትንሽ አዘገምን፡፡ ዳሩ ግን የየወዲያነሽ እግር
በመቀያየዱ በታክሲ ተሳፈርን፡፡
ከእስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ትንሽ እልፍ ብለን ድልድዩ ጋ ሳይደርስ ወረድን፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ የምታሻቅበውን አጭር አቀበት እጅ ለእጅ ተያይዘን ወጣናት፡፡ የወዲያነሽ እጅዋን ከእጄ ኣላቅቃ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር በር ሄደች። ተከተልኳት። በብረቱ በር ላይ ያለውን የብረት መስቀል በግንባሯ እየገጨች «አንተ ታውቅልኛለህ ጌታዬ! ለዚህ ያበቃኸኝ ጌታ ተመስገን! አንተው ሁነኝ» ብላ በሻከረ ድምፅ ተናገረች፡፡ ወዴት እንደምወስዳት ስለማታውቅ ዝም ብላ ተከተለችኝ፡፡ የአዲሱ ቤታችን በር ወለል ብሎ ተከፍቷል፡፡ ከማድ ቤት
የሚወጣው ጢስ በመስኮትና በመዝጊያው በኩል እንደ ሐምሌ ጉም ዝግ እያለ ይትጎለጎላል።
በኑሮ ተጐሳቁላ በእስራት የማቀቀችውን የወዲያነሽን ባለፉት ሁለት ቀናት የእኔ ባልኩትና ዛሬ ደግሞ በሁለታችን ውሕደት የእኛ ወደምለው ቤት ይዣት ስገባ በረጂሙ ትግሌ ውስጥ አነስተኛ ድል አድራጊነት ተሰማኝ፡፡
እንዲት ቀጠን ረዘም ያሉ ቀይ ሴትዮ ቀሚሳቸውን በቀኝ እጃቸው ከፍ
ሰብሰብ እያደረጉና የአዘኔታ ገጽታ እያሳዩ መጣችሁ? እሰየው እሰይ! በሉ ግቡ!
ግቡ!» ብለው እኛን እኛን እያዩ ቆሙ። «ኧረ በእግዚአብሔር ምነው ምነው?
በሉ ተቀመጡ! » ብዬ እንዲቀመጡ አደረግሁ፡፡ የወዲያነሽም ባቀረብኩላት
ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ሴትዮዋ ትንሽ ከእኛ ፈንጠር ብለው ስኒ በረከቦትና
የሚሰክን ጀበና አጠገባቸው አለ፡፡
ቀበርቾ፣ ዕጣን፣ ደረቅ የሎሚ ልጣጭ፣
መዝጊያው ሥር ጊርጊራ ላይ ይጨሳሉ፡፡ ሽታው አብሮ አደጌ ሽታ በመሆኑ ደስ
አለኝ፡፡
«እሱም እዚሁ ከቤት ውስጥ ነው ሲሠራና ዕቃውን ሲያስተካክል የዋለው: እሁን እመጣለሁ ብሎ ነው ወጣ ያለው፣ እንዲህ ቶሎ የምትመጣም አልመሰለው» አሉና ጀበናይቱን አነሱ
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ለቤት ወጪ እያልኩ ከምሰጣት ገንዘብ ላይ እያብቃቃች ልዩ ልዩ ተጨማሪ የማድ ቤት ቁሳቁሶች ገዛች፡፡ ዕቃዎቹ ሳይሆኑ ቁጠባዋ አስደሰተኝ።
የወዲያነሽ' ዛሬ የማድረው ወላጆቼ ቤት ነው፡፡ ስለዚህ እንዳትሠጊ ትፈሪያለሽ እንዴ?» ብያት በምሄድበት ጊዜ «ለእኔ ብለህ እኮ ተሠቃየህ ወይ አበሳህ» በማለት ራሷን ታማርራለች፡፡
ከዋል አደር የወህኒ ቤቱን ሕይወቷን እየረሳች አዲሱን ኑሮ ተላመደች::
ፈገግታዋ" ለዛና ጨዋታዋ ቀስ በቀስ ጎረፈ፡፡ እኔ ግን ወላጆቼ እንዳሰቡትና
እንደ ተመኙት ሳይሆን፣ ማንም ሳያውቅና ሳይሰማ፣ ጠላ ሳይጠመቅ፣ ጠጅና
ፍሪዳ ሳይጣል፣ ድንኳን ሳይተከል፣ ዕልልታና ሆታው ሳይቀልጥ፣ ጉልበት ስማ ሳልመረቅ፣ ከአንዱ የመከራ ጊዜ ጓደኛዬ በስተቀር ሚዜ ሳልመርጥና
ሳልመለምል፣ ሞላ ጎደለ ብዬ ሳልማስን፣ የእኔ ናት ብዬ ያመንኩባትንና ሕሊናዬ
ሙሉ በሙሉ የተቀበላትን የወዲያነሽን የኑሮ ጓደኛዪ ኣድርጌ ጎጆ ወጣሁ፡፡
ወደዱም ጠሉም የወዲያነሽ የሕይወቴ ምሰሶ ሆና በይፋ ብቅ የምትልበት ብሩህ
ቀን መምጣቱ አይቀርም፡፡
የተከራየነው የጉልላት አጎት ቤት አርጀትጀት ያለ በመሆኑ ግድግዳው
ላይ የተለጠፉት የአዲስ ዘመንና የሰንደቅ ዓላማችን ጋዜጦች ተገሽላልጠው ፀሐይ
እንዳጠቃው የሙዝ ቅጠል ዐልፎ ዐልፎ ተሽመልምለዋል። ምርጊቱ ላይ ተለጥፈው የተጋደሙት የጤፍ ጭዶች ይታያሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የወዲያነሽ
አብራኝ ስላለችና አብሬያት ስላለሁ ያለሁትና ያለችው በፍቅር ውብ እልፍኝ
ውስጥ ነው፡፡ ከፋ ሲለኝና ሐሳብ ሲያስጨንቀኝ ግን «የሕይወት ጥቀርሻ» ማለቴ አይቀረም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ጉልላትና የወዲያነሽ ባንድ ላይ ተቀምጠውም ሆነ ቆመው ሲያወሩ ደስ ይላሉ። የናቴ ልጅ እንኳ እንደ ጋሼ ጉልላት አይሆንልኝም፣ ጋሼ ጉልላት! ጋሼ ጉልላት ያንጀት ናቸው» ትላለች፡፡
ዓርብ ማታ ነበር፡፡ የወዲያነሽ ከተፈታች 17 ቀን ሆኗታል፡፡ ጉልላት ጀምሮልኝ የነበረውን ሐሳብ «ያም ሆነ ይህ ያለፈው ሁሉ ዐልፏል። የመጪውን ጊዜ ኑሮ ለማስተካከል ከባድ ጥረት ያስፈልጋል» አለና ዝም አለ። ዝም የማለትም
አመል አለበት። ይህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ሐሳቡን እያሰላሰልኩና እየሸነሸንኩ
በማሰብ በቆምኩባት መሬት ላይ የተተከልኩ ይመስል ውልፍት ሳልል ብዙ
ደቂቃዎች ቆየሁ፡፡ የሰበሰቡን አራት ማዕዘን አግዳሚ ዕንጨት እንደያዝኩ ትንሽ ቀና ብል ምሥራቃዊውን የበጋ ሰማይ ባዘቶ የሚመስል ደመና እዚህና እዚያ ጉች ጉች ብለውበታል። በውስጡ በሚከናወነው የአየር ግፊት ሜክንያት ደመናው ተለዋዋጭ ቅርፆች እየሰራ ወደ ምእራብ ተጓዘ።ደመናው ወደ ምእራብ በገሠገሠ ቁጥር የተለያየ ውበትና መጠን ያላቸው ከወክብት ወደ ምስራቅ የሚጓዙ ይመስላሉ ደመናው ጥርግ ብሎ ከሄደ በኋላ ግን እንደ ነባር አቀማመጣቸው በየነበሩበት ቀጥ ብለው ይቀራሉ።የእኔም ሐሳብ ይጓዝ ይክነፍ ይመጥቅ ይውዘገዘግና አንዲት ተራ የሐሳብ ድንበር ሳያገኝ ቀጥ ይላል።
የእናቱን ጡት እያነፈነፈ እንደሚፈልግ የውሻ ቡችላ ሐሳብ ሲያነፈፍ የቆየው ጉልላት እንግዲህ» ብሉ ንግግሩን ጀመር ሲያደርግ ወደ እርሱ መለስ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። በሕይወት ውስጥ ባሉት የኑሮ ጐዳናዎች በምትጓዝበት ጊዜ የሚያጋጥሙህን ፈተናዎችና ትግሎች ሁሉ ሳትሸሽና ሳታመነታ መታገል ይገባሃል፡፡ በዕንባዋ የሚረጥቡት ዐይኖቿ ያሳዝኑኛል፡፡ሥቃይዋ ይመረኛል' ማለት በቂ አይደለም፡፡ ማዘን ቢሉህ ማዘን አይምሰልህ።አንድ ምጽዋት ሰጪ ሃይማኖተኛ የሰማይ በር ያስከፍትልኛል ለሠራሁት ኃጢአት መደምሰሻ ይሆንልኛል ብሎ ለአንድ ለማኝ ቁራሽ ሲሰጥ ያዝናል፤ ያን በማድረጉ የራሱን የማይታይ ሥውር ጥቅም ጨመረ እንጂ ለማኙን ከራሱ
ጋር አላስተካከለውም፡፡ አድርግም ቢባል እሺ አይልም፡፡ አንተ ግን ከዚህ የተለየህ
ሁን። አሁን በምትኖርበት ኅብረተሰብ ውስጥ የመልካም ኑሮዋ ጀንበር
እንድትወጣና እንድትጠልቅ የምታደርጋት አንተ መሆንህን ዕወቅ።
«እኔም ራሲ ማን መሆኔን ለማወቅ የምችለውና ምግባሬን አሻግሬ
በማየት እኔነቴን ለማወቅ የምበቃው የአንተን የትግል አረማመድና ውጤት
እየተመለከትኩ ነው» ብሎ በእኔ ላይ ሙሉ እምነትና ተስፋ እንዳለው ለማረጋገጥ ረጋ ባለ ሁኔታ ምራቁን ውጦ ዝም እለ፡፡ እንደገና ከወደ ምሥራቅ የመጣው ደመና የከዋክብቱን ብርሃን እየጋረደው ሲሄድ አካባቢያችን ግራጫ ጨለማ አለበሰው።
በየወዲያነሽ ሕይወት ላይ የደረሰውን የመጥፎ ልማድ ውጤት ሁሉ በማስወገድ ሌላ አዲስ ትርጉምና ይዞታ እንዲያገኝ ለማድረግ የገባሁትን የተግባር ቃል አሳጥፈውም፡፡ መሸከም የሚገባኝን ቀንበር ከዛሬ ጀምሬ እሸከማለሁ፡፡ ሆኖም
ድል ማድረግ አለብህ ማለት ሳይሆን የሚጠብቀኝን ተቃውሞና የቤተሰብ መራር አንካሰላንትያ እንድታውቅልኝ ያስፈልጋል” አልኩና እንደ አዲስ ትክል የቤት ምሰሶ ቀጥ ብዬ ቆምኩ፡፡
ጉልላት ራሱን እየነቀነቀ ወደ ቤት ገባ፡፡ ተከትዬው ገባሁና አጠገቡ ተቀመጥኩ፡፡ የወዲያነሽ የጣደችው ሻይ እየተንተከተከ እንፋሎቱ አየር ውስጥ እየገባ ይዋጣል፡፡ እሷ እንገቷን ደፍታ በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ የሻይ ስኒ ታጥባለች፡፡
አሮጊቷ ሠራተኛ ትንሽ ራቅ ብለው ጉልበታቸውን ኣቅፈው ያንጎላጃሉ፡፡
በጣም ጫን ሲላቸው ለሰስተኛ ንፋስ እንደምታወዛውዛት መቃ ወደ ጎን ወይንም ወደ ፊት ጠንቀስ ይሉና ደንገጥ ብለው ቀና ሲሉ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ብልጭ ብለው ይከደናሉ፡፡ ሻዩ ተቀድቶ ቀረበልን፡፡
ጉልላት እንፋሎቱ እየተነነ የሚወጣውን ሻይ እየተመለከተ «እኔ እኮ የምልህ» ብሎ ንግግር ጀመረ የሁለታችን ጠንካራ ፍቅርና አንድነት ብዙ ነገር መጀመርና መፈጸም የሚችል መሆን አለበት፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እብራችሁ
መታገልና የሚያጋጥማችሁ የጋራ መሰናክል ሁሉ ሽንጣችሁን ገትራችሁ
መቋቋም እንጂ መሽሽና ያላግባብ ማፈግፈግ የእናንተ ድርሻ መሆን የለበትም፡፡
በተለይም አንተ እሷን እያጠናከር ክና ሳትነጠል ለአዲስ ዘላቂ ግብ
የሚገሠግሥ እውነተኛ ዓላማ እንዳለሁ አሳይ። አንተ በኑሮህ እና በትምህርትህ
ምክንያት የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ አለህ፡፡ ምሳሌዩ ቅር እንዳያሰኝህ እጂ
ቀላዋጭ የሚቀላውጠው የአስቀልዋጩን ያህል ስለሌለው ወይም በግልጽ በሥውር ስለ ተነጠቀ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ አግዛት፣ አብራህ ትሠለፋለች::
ዓርማህን በፅናት ለመትከል ካልተጣጣርህና አካባቢህንም ለመለወጥ እምነትህን ካላስፋፋህ የጥንቱ ልማድ እንደ ክፉ አውሬ አሳዶ ይበላሃል። የበሰለ ሕሊና ያለው ሰው የምትሰኘውም ብዙዎችን ላስቸገረ ከባድ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ስትል ከራስህ አልፈህ በተግባር የሚተባበሩህን መልካም ሰዎች በማፍራት ለዘላቂ መፍትሔ ስትታገል ነው፡፡ የዚህን የአሁኑን ሕይወት ቅርፅና ይዘት መለወጥ ያስፈልጋል። አሮጌውንና ለሕዝብ የማይጠቅመውን ነገር ሁሉ እያፈራረሱ በአዲስ የአኗኗር ስልት መተካት ይገባል፡፡ ግን አፈጻጸሙ እንደ አወራሩ ቀላል አይደለም» ብሎ በንግግሩ መኻል በረድ ያለችውን ሻይ መጠጣት ጀመረ፡፡
የወዲያነሽ ጉልላት ስለ እኔና ስለ እርሷ እንደ ተናገረ ስለ ገባት የመጨነቅ ሁኔታ ፊቷን ወረረው:: በስኒው ውስጥ የቀረችውን ሻይ ጨለጠና
የወዲያነሽን አሻግሮ እያየ «አንቺም ከእንግዲህ ወዲህ ነቃ ነቃ በይ! ይኸ ዐይን እስኪያብጥ እያለቀሱ አጉል መተከዝ በፍፁም አይጠቅማችሁም፡፡ ምንም እንኳ እንዳንቺ ወህኒ ቤት ገብተን ባንታሰርም እኛም ያንችኑ ያህል ከውጪ ሆነን ተሠቃይተናል። ሐሞትሽን ኮስተር አድርገሽ ለመታገል ከበረታሽ መልካሟ
የቤትሽ እመቤት አንቺ ብቻ ነሽ» ብሎ ጠበል እንዳልጠቀመው በሽተኛ ሻይ
እንዳስሞላለት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ለቤት ወጪ እያልኩ ከምሰጣት ገንዘብ ላይ እያብቃቃች ልዩ ልዩ ተጨማሪ የማድ ቤት ቁሳቁሶች ገዛች፡፡ ዕቃዎቹ ሳይሆኑ ቁጠባዋ አስደሰተኝ።
የወዲያነሽ' ዛሬ የማድረው ወላጆቼ ቤት ነው፡፡ ስለዚህ እንዳትሠጊ ትፈሪያለሽ እንዴ?» ብያት በምሄድበት ጊዜ «ለእኔ ብለህ እኮ ተሠቃየህ ወይ አበሳህ» በማለት ራሷን ታማርራለች፡፡
ከዋል አደር የወህኒ ቤቱን ሕይወቷን እየረሳች አዲሱን ኑሮ ተላመደች::
ፈገግታዋ" ለዛና ጨዋታዋ ቀስ በቀስ ጎረፈ፡፡ እኔ ግን ወላጆቼ እንዳሰቡትና
እንደ ተመኙት ሳይሆን፣ ማንም ሳያውቅና ሳይሰማ፣ ጠላ ሳይጠመቅ፣ ጠጅና
ፍሪዳ ሳይጣል፣ ድንኳን ሳይተከል፣ ዕልልታና ሆታው ሳይቀልጥ፣ ጉልበት ስማ ሳልመረቅ፣ ከአንዱ የመከራ ጊዜ ጓደኛዬ በስተቀር ሚዜ ሳልመርጥና
ሳልመለምል፣ ሞላ ጎደለ ብዬ ሳልማስን፣ የእኔ ናት ብዬ ያመንኩባትንና ሕሊናዬ
ሙሉ በሙሉ የተቀበላትን የወዲያነሽን የኑሮ ጓደኛዪ ኣድርጌ ጎጆ ወጣሁ፡፡
ወደዱም ጠሉም የወዲያነሽ የሕይወቴ ምሰሶ ሆና በይፋ ብቅ የምትልበት ብሩህ
ቀን መምጣቱ አይቀርም፡፡
የተከራየነው የጉልላት አጎት ቤት አርጀትጀት ያለ በመሆኑ ግድግዳው
ላይ የተለጠፉት የአዲስ ዘመንና የሰንደቅ ዓላማችን ጋዜጦች ተገሽላልጠው ፀሐይ
እንዳጠቃው የሙዝ ቅጠል ዐልፎ ዐልፎ ተሽመልምለዋል። ምርጊቱ ላይ ተለጥፈው የተጋደሙት የጤፍ ጭዶች ይታያሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ የወዲያነሽ
አብራኝ ስላለችና አብሬያት ስላለሁ ያለሁትና ያለችው በፍቅር ውብ እልፍኝ
ውስጥ ነው፡፡ ከፋ ሲለኝና ሐሳብ ሲያስጨንቀኝ ግን «የሕይወት ጥቀርሻ» ማለቴ አይቀረም፡፡
ምንጊዜም ቢሆን ጉልላትና የወዲያነሽ ባንድ ላይ ተቀምጠውም ሆነ ቆመው ሲያወሩ ደስ ይላሉ። የናቴ ልጅ እንኳ እንደ ጋሼ ጉልላት አይሆንልኝም፣ ጋሼ ጉልላት! ጋሼ ጉልላት ያንጀት ናቸው» ትላለች፡፡
ዓርብ ማታ ነበር፡፡ የወዲያነሽ ከተፈታች 17 ቀን ሆኗታል፡፡ ጉልላት ጀምሮልኝ የነበረውን ሐሳብ «ያም ሆነ ይህ ያለፈው ሁሉ ዐልፏል። የመጪውን ጊዜ ኑሮ ለማስተካከል ከባድ ጥረት ያስፈልጋል» አለና ዝም አለ። ዝም የማለትም
አመል አለበት። ይህን ተናግሮ እንደ ጨረሰ ሐሳቡን እያሰላሰልኩና እየሸነሸንኩ
በማሰብ በቆምኩባት መሬት ላይ የተተከልኩ ይመስል ውልፍት ሳልል ብዙ
ደቂቃዎች ቆየሁ፡፡ የሰበሰቡን አራት ማዕዘን አግዳሚ ዕንጨት እንደያዝኩ ትንሽ ቀና ብል ምሥራቃዊውን የበጋ ሰማይ ባዘቶ የሚመስል ደመና እዚህና እዚያ ጉች ጉች ብለውበታል። በውስጡ በሚከናወነው የአየር ግፊት ሜክንያት ደመናው ተለዋዋጭ ቅርፆች እየሰራ ወደ ምእራብ ተጓዘ።ደመናው ወደ ምእራብ በገሠገሠ ቁጥር የተለያየ ውበትና መጠን ያላቸው ከወክብት ወደ ምስራቅ የሚጓዙ ይመስላሉ ደመናው ጥርግ ብሎ ከሄደ በኋላ ግን እንደ ነባር አቀማመጣቸው በየነበሩበት ቀጥ ብለው ይቀራሉ።የእኔም ሐሳብ ይጓዝ ይክነፍ ይመጥቅ ይውዘገዘግና አንዲት ተራ የሐሳብ ድንበር ሳያገኝ ቀጥ ይላል።
የእናቱን ጡት እያነፈነፈ እንደሚፈልግ የውሻ ቡችላ ሐሳብ ሲያነፈፍ የቆየው ጉልላት እንግዲህ» ብሉ ንግግሩን ጀመር ሲያደርግ ወደ እርሱ መለስ ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ። በሕይወት ውስጥ ባሉት የኑሮ ጐዳናዎች በምትጓዝበት ጊዜ የሚያጋጥሙህን ፈተናዎችና ትግሎች ሁሉ ሳትሸሽና ሳታመነታ መታገል ይገባሃል፡፡ በዕንባዋ የሚረጥቡት ዐይኖቿ ያሳዝኑኛል፡፡ሥቃይዋ ይመረኛል' ማለት በቂ አይደለም፡፡ ማዘን ቢሉህ ማዘን አይምሰልህ።አንድ ምጽዋት ሰጪ ሃይማኖተኛ የሰማይ በር ያስከፍትልኛል ለሠራሁት ኃጢአት መደምሰሻ ይሆንልኛል ብሎ ለአንድ ለማኝ ቁራሽ ሲሰጥ ያዝናል፤ ያን በማድረጉ የራሱን የማይታይ ሥውር ጥቅም ጨመረ እንጂ ለማኙን ከራሱ
ጋር አላስተካከለውም፡፡ አድርግም ቢባል እሺ አይልም፡፡ አንተ ግን ከዚህ የተለየህ
ሁን። አሁን በምትኖርበት ኅብረተሰብ ውስጥ የመልካም ኑሮዋ ጀንበር
እንድትወጣና እንድትጠልቅ የምታደርጋት አንተ መሆንህን ዕወቅ።
«እኔም ራሲ ማን መሆኔን ለማወቅ የምችለውና ምግባሬን አሻግሬ
በማየት እኔነቴን ለማወቅ የምበቃው የአንተን የትግል አረማመድና ውጤት
እየተመለከትኩ ነው» ብሎ በእኔ ላይ ሙሉ እምነትና ተስፋ እንዳለው ለማረጋገጥ ረጋ ባለ ሁኔታ ምራቁን ውጦ ዝም እለ፡፡ እንደገና ከወደ ምሥራቅ የመጣው ደመና የከዋክብቱን ብርሃን እየጋረደው ሲሄድ አካባቢያችን ግራጫ ጨለማ አለበሰው።
በየወዲያነሽ ሕይወት ላይ የደረሰውን የመጥፎ ልማድ ውጤት ሁሉ በማስወገድ ሌላ አዲስ ትርጉምና ይዞታ እንዲያገኝ ለማድረግ የገባሁትን የተግባር ቃል አሳጥፈውም፡፡ መሸከም የሚገባኝን ቀንበር ከዛሬ ጀምሬ እሸከማለሁ፡፡ ሆኖም
ድል ማድረግ አለብህ ማለት ሳይሆን የሚጠብቀኝን ተቃውሞና የቤተሰብ መራር አንካሰላንትያ እንድታውቅልኝ ያስፈልጋል” አልኩና እንደ አዲስ ትክል የቤት ምሰሶ ቀጥ ብዬ ቆምኩ፡፡
ጉልላት ራሱን እየነቀነቀ ወደ ቤት ገባ፡፡ ተከትዬው ገባሁና አጠገቡ ተቀመጥኩ፡፡ የወዲያነሽ የጣደችው ሻይ እየተንተከተከ እንፋሎቱ አየር ውስጥ እየገባ ይዋጣል፡፡ እሷ እንገቷን ደፍታ በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ የሻይ ስኒ ታጥባለች፡፡
አሮጊቷ ሠራተኛ ትንሽ ራቅ ብለው ጉልበታቸውን ኣቅፈው ያንጎላጃሉ፡፡
በጣም ጫን ሲላቸው ለሰስተኛ ንፋስ እንደምታወዛውዛት መቃ ወደ ጎን ወይንም ወደ ፊት ጠንቀስ ይሉና ደንገጥ ብለው ቀና ሲሉ ትናንሽ ዐይኖቻቸው ብልጭ ብለው ይከደናሉ፡፡ ሻዩ ተቀድቶ ቀረበልን፡፡
ጉልላት እንፋሎቱ እየተነነ የሚወጣውን ሻይ እየተመለከተ «እኔ እኮ የምልህ» ብሎ ንግግር ጀመረ የሁለታችን ጠንካራ ፍቅርና አንድነት ብዙ ነገር መጀመርና መፈጸም የሚችል መሆን አለበት፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እብራችሁ
መታገልና የሚያጋጥማችሁ የጋራ መሰናክል ሁሉ ሽንጣችሁን ገትራችሁ
መቋቋም እንጂ መሽሽና ያላግባብ ማፈግፈግ የእናንተ ድርሻ መሆን የለበትም፡፡
በተለይም አንተ እሷን እያጠናከር ክና ሳትነጠል ለአዲስ ዘላቂ ግብ
የሚገሠግሥ እውነተኛ ዓላማ እንዳለሁ አሳይ። አንተ በኑሮህ እና በትምህርትህ
ምክንያት የተሻለ ዕውቀትና ችሎታ አለህ፡፡ ምሳሌዩ ቅር እንዳያሰኝህ እጂ
ቀላዋጭ የሚቀላውጠው የአስቀልዋጩን ያህል ስለሌለው ወይም በግልጽ በሥውር ስለ ተነጠቀ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ አግዛት፣ አብራህ ትሠለፋለች::
ዓርማህን በፅናት ለመትከል ካልተጣጣርህና አካባቢህንም ለመለወጥ እምነትህን ካላስፋፋህ የጥንቱ ልማድ እንደ ክፉ አውሬ አሳዶ ይበላሃል። የበሰለ ሕሊና ያለው ሰው የምትሰኘውም ብዙዎችን ላስቸገረ ከባድ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ስትል ከራስህ አልፈህ በተግባር የሚተባበሩህን መልካም ሰዎች በማፍራት ለዘላቂ መፍትሔ ስትታገል ነው፡፡ የዚህን የአሁኑን ሕይወት ቅርፅና ይዘት መለወጥ ያስፈልጋል። አሮጌውንና ለሕዝብ የማይጠቅመውን ነገር ሁሉ እያፈራረሱ በአዲስ የአኗኗር ስልት መተካት ይገባል፡፡ ግን አፈጻጸሙ እንደ አወራሩ ቀላል አይደለም» ብሎ በንግግሩ መኻል በረድ ያለችውን ሻይ መጠጣት ጀመረ፡፡
የወዲያነሽ ጉልላት ስለ እኔና ስለ እርሷ እንደ ተናገረ ስለ ገባት የመጨነቅ ሁኔታ ፊቷን ወረረው:: በስኒው ውስጥ የቀረችውን ሻይ ጨለጠና
የወዲያነሽን አሻግሮ እያየ «አንቺም ከእንግዲህ ወዲህ ነቃ ነቃ በይ! ይኸ ዐይን እስኪያብጥ እያለቀሱ አጉል መተከዝ በፍፁም አይጠቅማችሁም፡፡ ምንም እንኳ እንዳንቺ ወህኒ ቤት ገብተን ባንታሰርም እኛም ያንችኑ ያህል ከውጪ ሆነን ተሠቃይተናል። ሐሞትሽን ኮስተር አድርገሽ ለመታገል ከበረታሽ መልካሟ
የቤትሽ እመቤት አንቺ ብቻ ነሽ» ብሎ ጠበል እንዳልጠቀመው በሽተኛ ሻይ
እንዳስሞላለት
👍4
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....የውስጤን ሥቃይና የሕሊናዬን ሰፊ ጠባሳ ጠልቀው ያላዩ የቅርብ
ዘመዶቻችን «ዛሬማ ተበላሽቶ፣ የሱ ነገር እንዲህ ሆኖ ቀረ፡፡ ያየህይራድን የመሰለ
አንበሳ አባት እያለው ወግ ማዕረግ ያለማየቱ...» እያሉ ያጉመተምታሉ፡፡ ከቤት
ውጪ ማደሬ ያለ ማቋረጥ በመዘውተሩ ሁኔታውን መላው ቤተሰብ ከዳር እስከ
ዳር ዐወቀ፡፡ ደግማ ደጋግማ እናቴ እያፈረች፣ እኅቴ በተለይም የእናቴ
ምስጢረኛና የቅርብ ጓደኛ ወይዘሮ አማረች መኝታ ቤት ድረስ እየገቡ፣ ተው
ደግም አይደል የትልቅ ሰውና የጨዋ ልጅ እንዲህ አይደለም፡፡ እናትህ ብታለቅስ
ታደርስብሃለች» እያሉ ለወጉ ያህል ገሠጹኝ፡፡
እኔን የምመክራትና የምዳኛት ወደ ፊትም ሆነ ወደ ኋላ የማስኪዳት እኔው ራሴ ብቻ በመሆኔ የእነርሱን ምክር ሁሉ እንደሚያልፍ የበረዶ ውሽንፍር
ቆጠርኩት። በጠቅላላ መጻሕፍቶቼንና ልብሶቼን ውስጥ ውስጡን አንድ በአንድ
እግዥ ጨረስኩ፡፡ ከሁለትና ከሦስት ቀን አዳር በኋላ ወደ ወላጆቼ ቤት ስገባ ዘና
ብሎ የሚያናግረኝ ሰው አልነበረም፡፡
አባቴም ከቤት ውጪ በተደጋጋሚ ማደሬንና እንደ እናቴም አባባል «መዛተሌን» ቀስ በቀስ ሰማ።
«አግባ! ትዳር ንብረት ያዝ፣ እንደ ማንም የባለጌ ልጅ ሰፈር ለሰፈር
እትልከስከስ፣ ጎጆ ያስከብራል፣ ትዳር ግርማ ሞገስ ነው ያልኩህ ለዚህ ብዬ ነበር፡፡ያለበለዚያ ግን አካለ መጠን ከደረሰ ጐረምሳ ጋር ምን ያታግለኛል» ብሎ
ከነከተቴው ችላ አለኝ፡፡
ዋል አደር ብሎም «አደጋ ብቻ እንዳያገኘው እንጂ ልቡ መለስ
ሲልለትና ያበጠው ልቡ ሲሟሽሽ እንዳረጀች ውሻ ክትት ይላል» አለና ይብሱኑ ስለ እኔ የነበረውን 'አለና የለም ወይ?” እርግፍ አድርጎ ተወ፡፡
የሐሳቤ ተፃራሪ የሆነው አባቴ እንደ አህያ ሬሳ ቢጠላኝም ቅር አላለኝ፡፡ እኔ ግን «ይህ ነው ለሰው ልጅ የሚሰጠው ታላቅ የመኖር ጸጋ ብዬ ከጥላቻው ውስጥ ብርታትና እፎይታ የተሸለምኩ መሰለኝ።
ወደ ወላጆቼ ቤት ባሰኘን ጊዜ ገብቼ ባስፈለገኝ ሰዓት ውልቅ ማለት
ለመድኩ፡፡ እንደ ምኞቴ ሳልዘጋጅና ሳላስበው፣ የኑሮዬንም አዝማሚያ በሚገባ ሳላቅድ ድንገት ባለትዳር በመሆኔ ኑሮ በመጠኑ ተደናገረኝ። ሆኖም ትዳራችን የተመሠረተው በጽኑ ፍቅር ላይ በመሆኑ ፍላጎቴና ጉጉቴ ሁሉ ነጋ ጠባ
ለመሻሻልና አስደሳች ለውጥ ለማግኘት ሆነ። ወትሮ በቀላሉ ደንግጦ ይበረግግ
የነበረው አእምሮዬ የድፍረትና የወኔ ካፈያ ተርከፈከፈበት።
የየወዲያነሽን ቀኝ እጅ ያዝ አደርግና «ዛሬ ምን ያስፈልገናል?» ስላት ዐይን ዐይኔን እያየች እና የኮቴን አዝራሮች በጣቶቿ እየጠራረገች «ካለህማ....ያህል ይበቃኛል» ብላ ገንዘብ ስትጠይቀኝ የትዳርን አያያዝና አመራር ቀስ በቀስ
ለመድነው። በየወዲያነሽ በኩል የተቸገርኩበት ጉዳይ ቢኖር፡ ስትተኛም ይሁን ስትነሣ ስትበላም ይሁን ስትጠጣ አረ ተው ጌታነህ፡ ኧረ ተው! እረ ተው
ልጄን አሳየኝ? ሞቶም እንደሆነ ቁርጡን ንገረኝ ባይኖር ነው እንጂ ቢኖርግ
መቼ እንዲህ ዝም ትለኝ ነበር?» እያለች ስለምትጨቀጭቀኝ ነበር፡፡ ምንም እንኳ
አንዳንድ ነገርን አገላብጠው የማያዩ ቀባጣሪዎች «ጨካኝ አረመኔ ነች» እያሉ
እንደሚያሟትና ወደ ፊትም እንደሚያባጥሏት እያሰብኩ ለጊዜው ብበሳጭም እኔ ከማንም ይበልጥ የእኔዋን እና ቅኗን የወዲያነሽን አሳምሬ ስለማውቃት አባባላቸው ሁሉ ከወሬ እንኳ የነፈሰበት ተራ ወሬ ነው ብዬ እንደ ቤት ጉድፍ ጠራርጌ ጣልኩት።
ያን በማሕፀኗ ዘጠኝ ወር ሙሉ ተሽክማ በስንት የኑሮ ሥቃይ እና ውጣ ውረድ የወለደችውን ልጅዋንና አካሏን ለማየት እያለቀሰች ብታስቸግረኝም
የእናትነት ወጓ በመሆኑ ምንም ቅር አላለኝም፡፡
አንድ ቀን እሑድ ጥዋት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን ሳላስበውና
የሚያጋጥመኝን ሳልጠራጠር ከኪሴ እንድ ትንሽ ሰማያዊ ማኅደር አወጣሁ፡፡
በውስጡ የነበሩትን ልዩ ልዩ ሥዕሎች ተራ በተራ ስመለከት የወዲያነሽም
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል አድርጋ ትመለከት ነበር፡፡ የልጃችንን ሥዕል ኣየት
እንዳደረገች «ይኸውና» ብላ ባስደንጋጭ ሁኔታ ጮኸች፡፡ ከእጄ ላይ መንጭቃ
ደረቷ ላይ ለጠፈችው።
እነዚያ በእንባ ተኮትኩተው ያደጉት ዐይኖቿ የእንባ ኩልልታ እንጠፈጠፉ፡፡ ሥዕሉን ጠረጴዛው ላይ ወርውራ እግሬ ላይ ዘፍ አለች፡፡ እግሬን ባላት ጠቅላላ ኃይል ቁልቁል ጨምድዳ ስለ ያዘችው ጎትቼ ማላቀቅ አቃተኝ።
«ብዙ ሥቃይና መከራ ያየሁበት፣ ተንገላትቼ የተንከራተትኩበት የበኸር
ልጂ ነውና አለበት ድረስ ወስደሀ እሳየኝ፡፡ እናት አባትሀም ቤት ከሆነ ከሩቅ
ልየው:: ዐይኑን አይቼና ኣንድ ጊዜ ስሜው ልሙት!» ብላ ጫፈ ድልዱሙን
ጥቁር ጫማዩን ዕንባ አርከፈከፈችበት። የምይዘውና የምለቀው ጠፋኝ፡፡ ቁርጡን
ለማወቅ ቆርጣ መነሣቷን ስላወቅሁ ኣበይ ተነሽ ልብስሽን ቀያይሪና እንሂድ!
እይተሽው ለመመለስ እንጂ ይዘነው መምጣት አንችልም» አልኳት። እግሬን
ሳትለቅ አሻቅባ እያየች «እኔም ይዤው ልምጣ አልልም፣ ዐይኑን ብቻ አንድ ጊዜ
ልየው፣ በሕይወት መኖሩን ብቻ ልይ!» ብላ የልቧን አውጥታ ተናገረች።
በጉንጫ ላይ የሚንኳለለው ትኩስ እንባ የልቤን የፍቅር ወለል ቦረቦረው።ተነሥታ ወደ ጓዳ ስትገባ አረማመዷ እንኳ አሳዘነኝ። የባዕድ ሀላፊ አግዳሚ ያህል
እንኳ የማይተዋወቀችን እናትና ልጅ እንዴት አድርጌ እንደማስተዋውቅ ጭንቅ
ጥብብ አለኝ፡፡ እማምዬ እያለ በእናቱ ክንዶች ላይ ያልተዘናከተን' አልቅሶ
ያልተባበለን ሕፃን፣ ዐይኑ አይቶ ሕሊናው ያልመዘገባትን፣ አልቅሶም ይሁን በማቅ
ተንከትክቶ ዕቅፏ ላይ ያልተዘረገፈን ልጅ እንዴት አድርጌ እማማዬ እማማ
ለማሰኘት እንደምችል አጀማመሩም ሆነ አፈጻጸሙ ስማይን መቆንጠር መስሎ
በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ልብሷን ቀይራ ብቅ አለች፡፡ ኣጭር ዞማ ጸጉሯ በሚያምር ሐምራዊ ሻሽ ሽብ ተደርጓል፡፡ ኣጠገቤ መጥታ ቆም ካለች በኋላ በል አታጓጓኝ ይኸው መጣሁ! እንሂድ! » ብላ አሰፈሰፈች፡፡
የረሳችውን ሕፃን፡ ልጅሽ ይኸ ነው ብዬ ሳሳያት፣ ኣቅፋው በደስታ ስታለቅስ እና የልጁም በሁኔታው መደናገጥ ገና ከሩቁ አሽቆጠቆጠኝ፡፡
«የምንሄድበት ቦታ እኮ በጣም ሩቅ ነው» አልኳት፡፡ ግድ የለህም ስለ መንገዱ ሰማይ ጥግ ይድረስ፣ እንሂድ ብቻ' » ብላ ቆርጣ መነሳቷን ወደ በሩ በመራመድ ገለጸች፡፡ ከአስራ አምስት ደቂቃ ጉዞ በኋላ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ግቢ ደረስን። ለሁለተኛ ጊዜ ከሴት ጋር ያዩኝ የድርጅቱ ዘበኞችና ሌሉች ሠራተኞች እርስ በርሳቸው በመተያየት ተጎሻሽሙብኝ፡፡
ሕፃናቱ ሁሉ ልዩ ልዩ ቅርዕና መልክ ያላቸው መጫወቻዎችና አሻንጉሊቶች ይዘው በምድረ ግቢው ሜዳ ላይ እንደ እውድማ ዳር ጥሬ ፈስሰዋል፡፡ ኳስ እያንከባለለ የሚጫወተውን፣ ጅዋጅዌ የሚገፈትረውን፣ ወለሉ ላይ
በተሽከርካሪዎቿ እየተገፋች የምትሽከረከር መኪና ይዞ ራን ራን ጵጵ! ቢብ! የሚለውን፣ ሜዳ መኻል እየተሯሯጡ ድብብቆሽ የሚጫወቱትን ሁሉ አየናቸው::
ለጊዜው ልጃችንን ስላጣሁት ዐመዴ ቡን አለ፡፡ እጄን ኮት ኪሴ ውስጥ
ወሽቄ ከቤት እንደ ወጣን የገዛሁለትን ከረሜላ ማሻሸት ጀመርኩ፡፡ የየወዲያነሽ
ዐይኖች በተስፋ ብርሃን ተከበቡ። የናፍቆት ጎተራቸው አፉን ከፈተ። የጉጉቷ ጥም ተንሰፈሰፈ። ዐይኖቿን ቅርብና ሩቅ ድረስ እየላከች ኣየች፡፡ ሰውነቷ የሚንቀጠቀጥ መሰለ። ውሪ ብጤ ሩጭሩጭ እያለ ባጠገቧ ባለፈ ቁጥር ዐይኖቿ እግሮቹን ተከትለው ይጓዙና በዚያው ፈዝዘው ይቀራሉ፡፡
በመኻሉ አንድ አጠር ጠበብ ያለች ነጭ ሱሪ የታጠቀና ዐመድማ ሹራብ
የደረበ ድምቡል ያለ የሚያምር ልጅ ዝንጉርጉር ቢራቢሮ በግራ እጁ ይዞ
እያንደፋደፈና እፍ እያለባት ከፊት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....የውስጤን ሥቃይና የሕሊናዬን ሰፊ ጠባሳ ጠልቀው ያላዩ የቅርብ
ዘመዶቻችን «ዛሬማ ተበላሽቶ፣ የሱ ነገር እንዲህ ሆኖ ቀረ፡፡ ያየህይራድን የመሰለ
አንበሳ አባት እያለው ወግ ማዕረግ ያለማየቱ...» እያሉ ያጉመተምታሉ፡፡ ከቤት
ውጪ ማደሬ ያለ ማቋረጥ በመዘውተሩ ሁኔታውን መላው ቤተሰብ ከዳር እስከ
ዳር ዐወቀ፡፡ ደግማ ደጋግማ እናቴ እያፈረች፣ እኅቴ በተለይም የእናቴ
ምስጢረኛና የቅርብ ጓደኛ ወይዘሮ አማረች መኝታ ቤት ድረስ እየገቡ፣ ተው
ደግም አይደል የትልቅ ሰውና የጨዋ ልጅ እንዲህ አይደለም፡፡ እናትህ ብታለቅስ
ታደርስብሃለች» እያሉ ለወጉ ያህል ገሠጹኝ፡፡
እኔን የምመክራትና የምዳኛት ወደ ፊትም ሆነ ወደ ኋላ የማስኪዳት እኔው ራሴ ብቻ በመሆኔ የእነርሱን ምክር ሁሉ እንደሚያልፍ የበረዶ ውሽንፍር
ቆጠርኩት። በጠቅላላ መጻሕፍቶቼንና ልብሶቼን ውስጥ ውስጡን አንድ በአንድ
እግዥ ጨረስኩ፡፡ ከሁለትና ከሦስት ቀን አዳር በኋላ ወደ ወላጆቼ ቤት ስገባ ዘና
ብሎ የሚያናግረኝ ሰው አልነበረም፡፡
አባቴም ከቤት ውጪ በተደጋጋሚ ማደሬንና እንደ እናቴም አባባል «መዛተሌን» ቀስ በቀስ ሰማ።
«አግባ! ትዳር ንብረት ያዝ፣ እንደ ማንም የባለጌ ልጅ ሰፈር ለሰፈር
እትልከስከስ፣ ጎጆ ያስከብራል፣ ትዳር ግርማ ሞገስ ነው ያልኩህ ለዚህ ብዬ ነበር፡፡ያለበለዚያ ግን አካለ መጠን ከደረሰ ጐረምሳ ጋር ምን ያታግለኛል» ብሎ
ከነከተቴው ችላ አለኝ፡፡
ዋል አደር ብሎም «አደጋ ብቻ እንዳያገኘው እንጂ ልቡ መለስ
ሲልለትና ያበጠው ልቡ ሲሟሽሽ እንዳረጀች ውሻ ክትት ይላል» አለና ይብሱኑ ስለ እኔ የነበረውን 'አለና የለም ወይ?” እርግፍ አድርጎ ተወ፡፡
የሐሳቤ ተፃራሪ የሆነው አባቴ እንደ አህያ ሬሳ ቢጠላኝም ቅር አላለኝ፡፡ እኔ ግን «ይህ ነው ለሰው ልጅ የሚሰጠው ታላቅ የመኖር ጸጋ ብዬ ከጥላቻው ውስጥ ብርታትና እፎይታ የተሸለምኩ መሰለኝ።
ወደ ወላጆቼ ቤት ባሰኘን ጊዜ ገብቼ ባስፈለገኝ ሰዓት ውልቅ ማለት
ለመድኩ፡፡ እንደ ምኞቴ ሳልዘጋጅና ሳላስበው፣ የኑሮዬንም አዝማሚያ በሚገባ ሳላቅድ ድንገት ባለትዳር በመሆኔ ኑሮ በመጠኑ ተደናገረኝ። ሆኖም ትዳራችን የተመሠረተው በጽኑ ፍቅር ላይ በመሆኑ ፍላጎቴና ጉጉቴ ሁሉ ነጋ ጠባ
ለመሻሻልና አስደሳች ለውጥ ለማግኘት ሆነ። ወትሮ በቀላሉ ደንግጦ ይበረግግ
የነበረው አእምሮዬ የድፍረትና የወኔ ካፈያ ተርከፈከፈበት።
የየወዲያነሽን ቀኝ እጅ ያዝ አደርግና «ዛሬ ምን ያስፈልገናል?» ስላት ዐይን ዐይኔን እያየች እና የኮቴን አዝራሮች በጣቶቿ እየጠራረገች «ካለህማ....ያህል ይበቃኛል» ብላ ገንዘብ ስትጠይቀኝ የትዳርን አያያዝና አመራር ቀስ በቀስ
ለመድነው። በየወዲያነሽ በኩል የተቸገርኩበት ጉዳይ ቢኖር፡ ስትተኛም ይሁን ስትነሣ ስትበላም ይሁን ስትጠጣ አረ ተው ጌታነህ፡ ኧረ ተው! እረ ተው
ልጄን አሳየኝ? ሞቶም እንደሆነ ቁርጡን ንገረኝ ባይኖር ነው እንጂ ቢኖርግ
መቼ እንዲህ ዝም ትለኝ ነበር?» እያለች ስለምትጨቀጭቀኝ ነበር፡፡ ምንም እንኳ
አንዳንድ ነገርን አገላብጠው የማያዩ ቀባጣሪዎች «ጨካኝ አረመኔ ነች» እያሉ
እንደሚያሟትና ወደ ፊትም እንደሚያባጥሏት እያሰብኩ ለጊዜው ብበሳጭም እኔ ከማንም ይበልጥ የእኔዋን እና ቅኗን የወዲያነሽን አሳምሬ ስለማውቃት አባባላቸው ሁሉ ከወሬ እንኳ የነፈሰበት ተራ ወሬ ነው ብዬ እንደ ቤት ጉድፍ ጠራርጌ ጣልኩት።
ያን በማሕፀኗ ዘጠኝ ወር ሙሉ ተሽክማ በስንት የኑሮ ሥቃይ እና ውጣ ውረድ የወለደችውን ልጅዋንና አካሏን ለማየት እያለቀሰች ብታስቸግረኝም
የእናትነት ወጓ በመሆኑ ምንም ቅር አላለኝም፡፡
አንድ ቀን እሑድ ጥዋት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን ሳላስበውና
የሚያጋጥመኝን ሳልጠራጠር ከኪሴ እንድ ትንሽ ሰማያዊ ማኅደር አወጣሁ፡፡
በውስጡ የነበሩትን ልዩ ልዩ ሥዕሎች ተራ በተራ ስመለከት የወዲያነሽም
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል አድርጋ ትመለከት ነበር፡፡ የልጃችንን ሥዕል ኣየት
እንዳደረገች «ይኸውና» ብላ ባስደንጋጭ ሁኔታ ጮኸች፡፡ ከእጄ ላይ መንጭቃ
ደረቷ ላይ ለጠፈችው።
እነዚያ በእንባ ተኮትኩተው ያደጉት ዐይኖቿ የእንባ ኩልልታ እንጠፈጠፉ፡፡ ሥዕሉን ጠረጴዛው ላይ ወርውራ እግሬ ላይ ዘፍ አለች፡፡ እግሬን ባላት ጠቅላላ ኃይል ቁልቁል ጨምድዳ ስለ ያዘችው ጎትቼ ማላቀቅ አቃተኝ።
«ብዙ ሥቃይና መከራ ያየሁበት፣ ተንገላትቼ የተንከራተትኩበት የበኸር
ልጂ ነውና አለበት ድረስ ወስደሀ እሳየኝ፡፡ እናት አባትሀም ቤት ከሆነ ከሩቅ
ልየው:: ዐይኑን አይቼና ኣንድ ጊዜ ስሜው ልሙት!» ብላ ጫፈ ድልዱሙን
ጥቁር ጫማዩን ዕንባ አርከፈከፈችበት። የምይዘውና የምለቀው ጠፋኝ፡፡ ቁርጡን
ለማወቅ ቆርጣ መነሣቷን ስላወቅሁ ኣበይ ተነሽ ልብስሽን ቀያይሪና እንሂድ!
እይተሽው ለመመለስ እንጂ ይዘነው መምጣት አንችልም» አልኳት። እግሬን
ሳትለቅ አሻቅባ እያየች «እኔም ይዤው ልምጣ አልልም፣ ዐይኑን ብቻ አንድ ጊዜ
ልየው፣ በሕይወት መኖሩን ብቻ ልይ!» ብላ የልቧን አውጥታ ተናገረች።
በጉንጫ ላይ የሚንኳለለው ትኩስ እንባ የልቤን የፍቅር ወለል ቦረቦረው።ተነሥታ ወደ ጓዳ ስትገባ አረማመዷ እንኳ አሳዘነኝ። የባዕድ ሀላፊ አግዳሚ ያህል
እንኳ የማይተዋወቀችን እናትና ልጅ እንዴት አድርጌ እንደማስተዋውቅ ጭንቅ
ጥብብ አለኝ፡፡ እማምዬ እያለ በእናቱ ክንዶች ላይ ያልተዘናከተን' አልቅሶ
ያልተባበለን ሕፃን፣ ዐይኑ አይቶ ሕሊናው ያልመዘገባትን፣ አልቅሶም ይሁን በማቅ
ተንከትክቶ ዕቅፏ ላይ ያልተዘረገፈን ልጅ እንዴት አድርጌ እማማዬ እማማ
ለማሰኘት እንደምችል አጀማመሩም ሆነ አፈጻጸሙ ስማይን መቆንጠር መስሎ
በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ልብሷን ቀይራ ብቅ አለች፡፡ ኣጭር ዞማ ጸጉሯ በሚያምር ሐምራዊ ሻሽ ሽብ ተደርጓል፡፡ ኣጠገቤ መጥታ ቆም ካለች በኋላ በል አታጓጓኝ ይኸው መጣሁ! እንሂድ! » ብላ አሰፈሰፈች፡፡
የረሳችውን ሕፃን፡ ልጅሽ ይኸ ነው ብዬ ሳሳያት፣ ኣቅፋው በደስታ ስታለቅስ እና የልጁም በሁኔታው መደናገጥ ገና ከሩቁ አሽቆጠቆጠኝ፡፡
«የምንሄድበት ቦታ እኮ በጣም ሩቅ ነው» አልኳት፡፡ ግድ የለህም ስለ መንገዱ ሰማይ ጥግ ይድረስ፣ እንሂድ ብቻ' » ብላ ቆርጣ መነሳቷን ወደ በሩ በመራመድ ገለጸች፡፡ ከአስራ አምስት ደቂቃ ጉዞ በኋላ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ግቢ ደረስን። ለሁለተኛ ጊዜ ከሴት ጋር ያዩኝ የድርጅቱ ዘበኞችና ሌሉች ሠራተኞች እርስ በርሳቸው በመተያየት ተጎሻሽሙብኝ፡፡
ሕፃናቱ ሁሉ ልዩ ልዩ ቅርዕና መልክ ያላቸው መጫወቻዎችና አሻንጉሊቶች ይዘው በምድረ ግቢው ሜዳ ላይ እንደ እውድማ ዳር ጥሬ ፈስሰዋል፡፡ ኳስ እያንከባለለ የሚጫወተውን፣ ጅዋጅዌ የሚገፈትረውን፣ ወለሉ ላይ
በተሽከርካሪዎቿ እየተገፋች የምትሽከረከር መኪና ይዞ ራን ራን ጵጵ! ቢብ! የሚለውን፣ ሜዳ መኻል እየተሯሯጡ ድብብቆሽ የሚጫወቱትን ሁሉ አየናቸው::
ለጊዜው ልጃችንን ስላጣሁት ዐመዴ ቡን አለ፡፡ እጄን ኮት ኪሴ ውስጥ
ወሽቄ ከቤት እንደ ወጣን የገዛሁለትን ከረሜላ ማሻሸት ጀመርኩ፡፡ የየወዲያነሽ
ዐይኖች በተስፋ ብርሃን ተከበቡ። የናፍቆት ጎተራቸው አፉን ከፈተ። የጉጉቷ ጥም ተንሰፈሰፈ። ዐይኖቿን ቅርብና ሩቅ ድረስ እየላከች ኣየች፡፡ ሰውነቷ የሚንቀጠቀጥ መሰለ። ውሪ ብጤ ሩጭሩጭ እያለ ባጠገቧ ባለፈ ቁጥር ዐይኖቿ እግሮቹን ተከትለው ይጓዙና በዚያው ፈዝዘው ይቀራሉ፡፡
በመኻሉ አንድ አጠር ጠበብ ያለች ነጭ ሱሪ የታጠቀና ዐመድማ ሹራብ
የደረበ ድምቡል ያለ የሚያምር ልጅ ዝንጉርጉር ቢራቢሮ በግራ እጁ ይዞ
እያንደፋደፈና እፍ እያለባት ከፊት
👍3
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አሮጊቷ ሠራተኛችን ነጋ ጠባ እየታመሙ መውደቅ መነሣት ስለ
በዛባቸው «እስኪ በጠበሉም በምኑም ልሞካክረው» ብለው ከሔዱ ወሩ ተጋመሰ::በእርሳቸው እግር እንዲት ልጅ እግር ሠራተኛ ተካን፡ የወዲያነሽም ያሳለፈችው ችግርና መከራ ቁጣና ግልምጫ ረሃብና እርዛት ሁሉ ከአእምሮዋ ላይ የማይደመሰስና የማይረሳ የኑሮ ትምህርት አስጠንቷታል። በዚሁ የተነሣ አዲሷን ሠራተኛችንን በርኅራኄና በደግነት ታያታለች። በትምህርትም ረገድ ከቀን ወደ
ቀን በመበርታቷ በእርሷ ላይ ያለኝ ተስፋ እንደ አበባ እምቡጥ በየጊዜው ይፈነዳ
ጀመር። የደመወዜ ከፍ ማለት የቤታችንን ዕቃዎች በአዳዲስ ምርጥ ቁሳቁሶች
ለመተካት ረዳ፡፡ ለውጥ የኑሮ መስተዋት ነው። የየወዲያነሽ መልክና ውበትም
የቀድሞ ደረጃውን ሊይዝ ስንዝር ታህል ቀረው፡፡ በክርክርና በውይይት
እንድትመራና እንድታምን ያደረግሁት ጥረት ከጊዜው ሁኔታ ጋር እየተቀራረበ
የሚራመድ የልፋት ውጤት እስገኘልኝ። ጸጉሯ እንገቷ ላይ እየተገማሸረ
የቀሚሷን እንገትያ መዳሰስ ጀመረ፡፡ ዕድሜዋ ኻያ ሰባት ገደማ በመድረሱ
ደርባባና ጐዝጉዝ ያለች ወጣት ሆነች፡፡ እንዲያውም በምኗም በምኗም በከፍተኛ
ምቾትና ድሎት ካደገችው እኅቴ ይልቅ የእኔዋ የወዲያነሽ በእጅጉ ላቀች፡፡
የውብነሽ የንግድ ሥራ ትምህርቷን ጨርሳ ከንግድ ትምህርት ቤት
ከተመረቀች ሦስት ወር ዐለፋት፡፡ ነገር ግን መስከረም ሲጠባ ሥራ ትጀምሪያለሽ
ተብላ ቦዝና ከረመች፡፡ አባቴ ከግሼን ማርያም በተመለሰ በሳምንቱ በደኅና ደሞዝ ሥራ ጀመረች።
አንድ ቀን እሑድ ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ ላይ እኔና የወዲያነሽ በእግራችን ወደ አፍንጮ በር ስናዘግም ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ደረስን።
በቤተ ክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረትና አካባቢ እጅግ በጣም ብዙ ሕዝብ ተሰብስቧል።
በሕዝቡ መኻል እየተጋፋን ወደ ሰሜን አቅጣጫ ስንጓዝ የኅዳር ማርያም መሆኗ
ትዝ አለኝ፡፡ ሕዝቡ እየተግተለተላ ወዲያ ወዲህ ሲሔድ ድንጋዩ የተፈነቀለበት
ቁጫጭ መስሏል፡፡ የወዲያነሽ ግንባሩን በጥንግ እንደ ተመታ ገነኛ ቀጥ ብላ
ቆመች፡፡ የቀኝ እጀን ይዛ ወደ ኋላ እየጎተተች «ጌትዬ ጉድፈላልህ! የዛሬን
አውጣኝ! » ስትል ትንፋሿ በድንጋጤ ወደ ውስጥ ሠረገ፡፡
ከወደፊታችን አንዳች አደጋ የመጣ መስሉኝ አፍጥጬ ተመለከትኩ፡፡
አገር አማን ነበር፡፡ ለካስ ነገሩ ወዲህ ኖሯል፡፡ ከፊት ለፊታችን ትንሽ ራቅ ብሎ
አንድ ቀጠን ረዘም ብለው ጥቁር ሱፍ የለበሱና አሽከር ያስከተሉ የቀይ ዳግ
አዛውንት ወደ እኛ ሲመጡ አየሁ። አባቴ ነው።
የወዲያነሽ እጅ በዱላ የተመታ ይመስል ተዝለፈለፈ። የበደነ አካል የያዝኩ መሰለኝ፡፡ እጅዋን ለቅቄ ወደ ጎን ገፋኋት። አልራቀችም፡፡ ከአባቴ በስተጀርባ እናቴና እኅቴ አንዲት ነባር ሠራተኛ አስከትለው ይከተላሉ፡፡የወዲያነሽ ትንሽ ፈንጠር ብላ በግራ ጎናቸው ዐልፋ ሄደች። በከዘራ በጥፊና በክርን ደብድበው ካባረሯት ወዲህ እናቴንና እህቴን ስታያቸው የመጀመሪያ የመጀመርያ ጊዜዋ ነበር።
ሁለት እጆቼን ወደኋላዩ አድርጌ ልምጥ ብዬ እጅ ነሳሁ፡፡ እሱ ግን ሌላም እላለ። «እንተ ከሃዲ! ወይኔ ያየህ ይራድ! የማታ ማታ እንዲህ ታደርገኝ?
በቁሜ ቀብረኸኝ ትሄድ? አዝኘብሃለሁና ወላዲተ አምላክ በዕለተ ቀኗ ትመስክር
አይቀናህም!! እንዲሁ አውታታ ሆነህ ትቀራለህ! በል ሒድ!» አለና ከእግር
እስከ ራሴ በጥላቻ ግርምሞኝ ሄደ፡፡
ከአባቴ በስተጀርባ ቆማ የነበረችው እናቴ ዐይኔን ከማየት ብላ ከሠራተኛዋ ጋር ታወራ ነበር። ነጭ ጋቢ የለበሰችው የውብነሽ በፍርሃት ዐይኗን እያቁለጨለጨች ጨበጥ አድርጋኝ ወደ እነርሱ ተመለሰች፡፡ ሆድና ጀርባ ሆነን
እነርሱ ወደ ደቡብ እኛ ወደ ሰሜን ተጓዝን፡፡ የወዲያነሽ ምን አሉህ?' እንኳ ብላ አልጠየቀችኝም፡፡ እኔም አላነሣሁላትም፡፡ የወጣንበትን ጉዳይ ፈጽመን ወደ ልጃትን ዘንድ ሄድን፡፡
ከዚያ ቀደም በወሰድንለት የመላያ እርሳሶች እየተጠቀመ በአንድ መስመር አልባ ወረቀት ላይ የምታምር ሰማያዊ አበባ ሥሉ ቅጠሎቿን አረንጓዴ ቀለም እየቀባ ሲያሳምራት ቀስ ብለን ከበስተጀርባው ቆመን አየን።እኔና የወዲያነሽ እርስ በርሳችን ተያየን፡፡ ፊቱን ወደ ምዕራብ አዙሮ በመቀመጡ ለመጥለቅ የጥቂት ጊዜ ጉዞ ብቻ የቀራት ፀሐይ ብርሃኗን በስላች ለቃ በነጩ ወረቀት ላይ ደማቅ ቦግታ ፈጥራለች። ዐይኖቹ እንዳይጎዱ ሠጋሁ፡፡ ከበላዩ እንደ ታቦት ድባብ ጉፍ ብሉ ቅርንጫፎቹን በቅጠሎች ፤ያሳመረው የባሕር ማዶ ተክል ለሰስ ባለው የምሽት ነፋስ ይወዛወዛል።ከበስተጀርባችን ባላው መሬት ላይ ያረፈው የዛፍ ጥላ በውዝዋዜ እየተመራ በቅርንጫፎቹና በቅጠላ ቅጠሎቹ ሥዕል ይሥላል። አንድ ሉክ ገለጠ። አራት ረዘም ረዘም ያሉ የተሰናሰሉ ተራሮች በተጉበጠበጡ መስመሮች ተያይዘው ቡናና ጥቁር ቀለም ተቀብተዋል፡፡ ዕጫፍ ጫፋቸው ላይ ሁለት ሁለትና አልፎ ልፎም ሦስት ዛፎች ጉች ጉች ብለዋል። ከተራሮቹ እግር አንሥቶ እስከ ወረቀቱ የታች ጠርዝ ድረስ አረንጓዴና ቀይ፣ ቢጫና ሰማያዊ መስመር
ከወዲያ ወዲህ ተመሳቅለው ጭራሮ መሰል ውስብስብ መረብ ጥረዋል።
ከየተራራው መኻል ላይ ደግሞ እየተጥመዘመዙ የሚወርዱ ደማቅ ሰማያዊ መስመሮች አሽቆልቁለዋል። ጅረቶች መሆናቸው ነው፡፡
እኔና እርሷ ደረቁ ፀደይ አፈር ላይ እግሮቻችንን ዘርግተን ተቀመጥን። ጋሻዬነህ በሁለታችን መኻል ፊቱን ወደ እኛ አዘሮ በመቀመጡ ሁለታችንም በወሬና በጥያቄ ተሻማነው። ዐልፎ ዐልፎ ኮልተፍ ይላል፡፡ ፀሐይ ያላትን ሙቀትና ብርሃን ዘክዝካ የጨረሰች ይመስል ቀስ በቀስ ሙቀትና ብርሃን እየነፈገች ከተራራው በስተጀርባ ተሰወረች። ዳግማኛ የማትመለሰዋ ቀንም አብራ ለዘልዓለም ጠለቀች። ሕፃናቱና ከፍ ከፍ ያሉት ልጆች ሁሉ ወደ መኝታ ክፍላቸው የሚዝብት ጊዜ በመድረሱ ልጆች ሁሉ ሊገቡ ነው፡ልሂድ እኔም» ብሎ በየተራ አየን። ያመጣንለትን ዕቃ በቀኝ እጁ ዐቅፎ
የሥዕል ደብተሩንና እርሳሶቹን በግራ እጁ ጨብጦ ተነሣ፡፡ እኛም ጉንጩን
ስመን ተለየነው:: ከዚያን ዕለት ወዲህ ስለ ልጃችን ጉዳይ ሐሳብ ገባን፡፡ከእኛው ጋር ቢሆን ለአስተዳደጉ እንደሚበጅ ስንወያይበት ሰነበትንና ከእጓለ
ማውታ ልናወጣው ተስማምተን ዝግጅቶች ጀመርን።
በዚህ መኻል የዘመዶቼን ሁኔታ ለማወቅ ስለ ጓጓሁ እስኪ የሚባለውን ልስማ በማለት ከሩቅ ዘመዶቼ ውስጥ ጠንቃቃውን መርጬ አንድ ቀን ወደ
ቤት ይዤው መጣሁ፡፡ እንግዳዩ እንግዳዋ በመሆኑ አንጀት በሚያርስ አኳኋን ተቀብላ አስተናገደችው፡፡ ለመሄድ ሲነሣም የእንግዳ ወጉ ሁነኛ ጥቂት ልሸኝህ ብዩው አብረን ወጣን፡፡ ሳይታወቀን ብዙ ተጓዝን፡፡ በጨዋታችን መኻል«መቼም ስለዚህ ጉዳይ ወላጆችህ ምንም አልሰሙ፣ ሰምተዋል እንዴ?» ብሎ ጠየቀኝ፡፡
ለካስ አንድ ቀን እነጉልላት ቤት በእንግድነት እንደተቀመጠ እኔና
ጉልላት ስንነጋገር አንዳንድ የቃላት ፍንጣሪ ወሬ ሰምቶ ኖሯል። «አዎ እስከ
ዛሬ ድረስ አልሰሙም ያም ሆነ ይህ መስማታቸው አይቀርም የእኔ ውሳኔ ግን
አይለወጥም» ብዬ ሐተታ ሳላበዛ ዝም አልኩ፡፡ “ታዲያ ነገ ጧት አባትህ
ባድራጎትህ ተናደውና ተበሳጭተው ከዚህ ሁሉ ሀብት ንብረታቸው ላይ ቢነቅሉህስ?» አለኝ፡፡ “ይኸ ቀላል ጉዳይ ነው። ሁልጊዜ ሰዎች ሸምጥጠው ያወረዱትን ፍሬ መመገብ የለብኝም፡፡ እኔም በድርሻዬ መሽምጠጥና የመሽምጠጥን ልፋት ማየትና መቅመስ አለብኝ፡፡ ዛሬ ተወዝፈ ነገ በሚወረስ ነገር አልተማመንም፡፡ እሱ ያፈራውን ንብረትና ሀብት ያህል እኔም በዘዴና በቆራጥነት ከሠራ አገኘዋለሁ። ከዚያ በኋላ እኔም በፈንታዩ አውራሽ ሆንኩ ማለት ነው፡፡ ይህ ነው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አሮጊቷ ሠራተኛችን ነጋ ጠባ እየታመሙ መውደቅ መነሣት ስለ
በዛባቸው «እስኪ በጠበሉም በምኑም ልሞካክረው» ብለው ከሔዱ ወሩ ተጋመሰ::በእርሳቸው እግር እንዲት ልጅ እግር ሠራተኛ ተካን፡ የወዲያነሽም ያሳለፈችው ችግርና መከራ ቁጣና ግልምጫ ረሃብና እርዛት ሁሉ ከአእምሮዋ ላይ የማይደመሰስና የማይረሳ የኑሮ ትምህርት አስጠንቷታል። በዚሁ የተነሣ አዲሷን ሠራተኛችንን በርኅራኄና በደግነት ታያታለች። በትምህርትም ረገድ ከቀን ወደ
ቀን በመበርታቷ በእርሷ ላይ ያለኝ ተስፋ እንደ አበባ እምቡጥ በየጊዜው ይፈነዳ
ጀመር። የደመወዜ ከፍ ማለት የቤታችንን ዕቃዎች በአዳዲስ ምርጥ ቁሳቁሶች
ለመተካት ረዳ፡፡ ለውጥ የኑሮ መስተዋት ነው። የየወዲያነሽ መልክና ውበትም
የቀድሞ ደረጃውን ሊይዝ ስንዝር ታህል ቀረው፡፡ በክርክርና በውይይት
እንድትመራና እንድታምን ያደረግሁት ጥረት ከጊዜው ሁኔታ ጋር እየተቀራረበ
የሚራመድ የልፋት ውጤት እስገኘልኝ። ጸጉሯ እንገቷ ላይ እየተገማሸረ
የቀሚሷን እንገትያ መዳሰስ ጀመረ፡፡ ዕድሜዋ ኻያ ሰባት ገደማ በመድረሱ
ደርባባና ጐዝጉዝ ያለች ወጣት ሆነች፡፡ እንዲያውም በምኗም በምኗም በከፍተኛ
ምቾትና ድሎት ካደገችው እኅቴ ይልቅ የእኔዋ የወዲያነሽ በእጅጉ ላቀች፡፡
የውብነሽ የንግድ ሥራ ትምህርቷን ጨርሳ ከንግድ ትምህርት ቤት
ከተመረቀች ሦስት ወር ዐለፋት፡፡ ነገር ግን መስከረም ሲጠባ ሥራ ትጀምሪያለሽ
ተብላ ቦዝና ከረመች፡፡ አባቴ ከግሼን ማርያም በተመለሰ በሳምንቱ በደኅና ደሞዝ ሥራ ጀመረች።
አንድ ቀን እሑድ ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ ላይ እኔና የወዲያነሽ በእግራችን ወደ አፍንጮ በር ስናዘግም ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ደረስን።
በቤተ ክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረትና አካባቢ እጅግ በጣም ብዙ ሕዝብ ተሰብስቧል።
በሕዝቡ መኻል እየተጋፋን ወደ ሰሜን አቅጣጫ ስንጓዝ የኅዳር ማርያም መሆኗ
ትዝ አለኝ፡፡ ሕዝቡ እየተግተለተላ ወዲያ ወዲህ ሲሔድ ድንጋዩ የተፈነቀለበት
ቁጫጭ መስሏል፡፡ የወዲያነሽ ግንባሩን በጥንግ እንደ ተመታ ገነኛ ቀጥ ብላ
ቆመች፡፡ የቀኝ እጀን ይዛ ወደ ኋላ እየጎተተች «ጌትዬ ጉድፈላልህ! የዛሬን
አውጣኝ! » ስትል ትንፋሿ በድንጋጤ ወደ ውስጥ ሠረገ፡፡
ከወደፊታችን አንዳች አደጋ የመጣ መስሉኝ አፍጥጬ ተመለከትኩ፡፡
አገር አማን ነበር፡፡ ለካስ ነገሩ ወዲህ ኖሯል፡፡ ከፊት ለፊታችን ትንሽ ራቅ ብሎ
አንድ ቀጠን ረዘም ብለው ጥቁር ሱፍ የለበሱና አሽከር ያስከተሉ የቀይ ዳግ
አዛውንት ወደ እኛ ሲመጡ አየሁ። አባቴ ነው።
የወዲያነሽ እጅ በዱላ የተመታ ይመስል ተዝለፈለፈ። የበደነ አካል የያዝኩ መሰለኝ፡፡ እጅዋን ለቅቄ ወደ ጎን ገፋኋት። አልራቀችም፡፡ ከአባቴ በስተጀርባ እናቴና እኅቴ አንዲት ነባር ሠራተኛ አስከትለው ይከተላሉ፡፡የወዲያነሽ ትንሽ ፈንጠር ብላ በግራ ጎናቸው ዐልፋ ሄደች። በከዘራ በጥፊና በክርን ደብድበው ካባረሯት ወዲህ እናቴንና እህቴን ስታያቸው የመጀመሪያ የመጀመርያ ጊዜዋ ነበር።
ሁለት እጆቼን ወደኋላዩ አድርጌ ልምጥ ብዬ እጅ ነሳሁ፡፡ እሱ ግን ሌላም እላለ። «እንተ ከሃዲ! ወይኔ ያየህ ይራድ! የማታ ማታ እንዲህ ታደርገኝ?
በቁሜ ቀብረኸኝ ትሄድ? አዝኘብሃለሁና ወላዲተ አምላክ በዕለተ ቀኗ ትመስክር
አይቀናህም!! እንዲሁ አውታታ ሆነህ ትቀራለህ! በል ሒድ!» አለና ከእግር
እስከ ራሴ በጥላቻ ግርምሞኝ ሄደ፡፡
ከአባቴ በስተጀርባ ቆማ የነበረችው እናቴ ዐይኔን ከማየት ብላ ከሠራተኛዋ ጋር ታወራ ነበር። ነጭ ጋቢ የለበሰችው የውብነሽ በፍርሃት ዐይኗን እያቁለጨለጨች ጨበጥ አድርጋኝ ወደ እነርሱ ተመለሰች፡፡ ሆድና ጀርባ ሆነን
እነርሱ ወደ ደቡብ እኛ ወደ ሰሜን ተጓዝን፡፡ የወዲያነሽ ምን አሉህ?' እንኳ ብላ አልጠየቀችኝም፡፡ እኔም አላነሣሁላትም፡፡ የወጣንበትን ጉዳይ ፈጽመን ወደ ልጃትን ዘንድ ሄድን፡፡
ከዚያ ቀደም በወሰድንለት የመላያ እርሳሶች እየተጠቀመ በአንድ መስመር አልባ ወረቀት ላይ የምታምር ሰማያዊ አበባ ሥሉ ቅጠሎቿን አረንጓዴ ቀለም እየቀባ ሲያሳምራት ቀስ ብለን ከበስተጀርባው ቆመን አየን።እኔና የወዲያነሽ እርስ በርሳችን ተያየን፡፡ ፊቱን ወደ ምዕራብ አዙሮ በመቀመጡ ለመጥለቅ የጥቂት ጊዜ ጉዞ ብቻ የቀራት ፀሐይ ብርሃኗን በስላች ለቃ በነጩ ወረቀት ላይ ደማቅ ቦግታ ፈጥራለች። ዐይኖቹ እንዳይጎዱ ሠጋሁ፡፡ ከበላዩ እንደ ታቦት ድባብ ጉፍ ብሉ ቅርንጫፎቹን በቅጠሎች ፤ያሳመረው የባሕር ማዶ ተክል ለሰስ ባለው የምሽት ነፋስ ይወዛወዛል።ከበስተጀርባችን ባላው መሬት ላይ ያረፈው የዛፍ ጥላ በውዝዋዜ እየተመራ በቅርንጫፎቹና በቅጠላ ቅጠሎቹ ሥዕል ይሥላል። አንድ ሉክ ገለጠ። አራት ረዘም ረዘም ያሉ የተሰናሰሉ ተራሮች በተጉበጠበጡ መስመሮች ተያይዘው ቡናና ጥቁር ቀለም ተቀብተዋል፡፡ ዕጫፍ ጫፋቸው ላይ ሁለት ሁለትና አልፎ ልፎም ሦስት ዛፎች ጉች ጉች ብለዋል። ከተራሮቹ እግር አንሥቶ እስከ ወረቀቱ የታች ጠርዝ ድረስ አረንጓዴና ቀይ፣ ቢጫና ሰማያዊ መስመር
ከወዲያ ወዲህ ተመሳቅለው ጭራሮ መሰል ውስብስብ መረብ ጥረዋል።
ከየተራራው መኻል ላይ ደግሞ እየተጥመዘመዙ የሚወርዱ ደማቅ ሰማያዊ መስመሮች አሽቆልቁለዋል። ጅረቶች መሆናቸው ነው፡፡
እኔና እርሷ ደረቁ ፀደይ አፈር ላይ እግሮቻችንን ዘርግተን ተቀመጥን። ጋሻዬነህ በሁለታችን መኻል ፊቱን ወደ እኛ አዘሮ በመቀመጡ ሁለታችንም በወሬና በጥያቄ ተሻማነው። ዐልፎ ዐልፎ ኮልተፍ ይላል፡፡ ፀሐይ ያላትን ሙቀትና ብርሃን ዘክዝካ የጨረሰች ይመስል ቀስ በቀስ ሙቀትና ብርሃን እየነፈገች ከተራራው በስተጀርባ ተሰወረች። ዳግማኛ የማትመለሰዋ ቀንም አብራ ለዘልዓለም ጠለቀች። ሕፃናቱና ከፍ ከፍ ያሉት ልጆች ሁሉ ወደ መኝታ ክፍላቸው የሚዝብት ጊዜ በመድረሱ ልጆች ሁሉ ሊገቡ ነው፡ልሂድ እኔም» ብሎ በየተራ አየን። ያመጣንለትን ዕቃ በቀኝ እጁ ዐቅፎ
የሥዕል ደብተሩንና እርሳሶቹን በግራ እጁ ጨብጦ ተነሣ፡፡ እኛም ጉንጩን
ስመን ተለየነው:: ከዚያን ዕለት ወዲህ ስለ ልጃችን ጉዳይ ሐሳብ ገባን፡፡ከእኛው ጋር ቢሆን ለአስተዳደጉ እንደሚበጅ ስንወያይበት ሰነበትንና ከእጓለ
ማውታ ልናወጣው ተስማምተን ዝግጅቶች ጀመርን።
በዚህ መኻል የዘመዶቼን ሁኔታ ለማወቅ ስለ ጓጓሁ እስኪ የሚባለውን ልስማ በማለት ከሩቅ ዘመዶቼ ውስጥ ጠንቃቃውን መርጬ አንድ ቀን ወደ
ቤት ይዤው መጣሁ፡፡ እንግዳዩ እንግዳዋ በመሆኑ አንጀት በሚያርስ አኳኋን ተቀብላ አስተናገደችው፡፡ ለመሄድ ሲነሣም የእንግዳ ወጉ ሁነኛ ጥቂት ልሸኝህ ብዩው አብረን ወጣን፡፡ ሳይታወቀን ብዙ ተጓዝን፡፡ በጨዋታችን መኻል«መቼም ስለዚህ ጉዳይ ወላጆችህ ምንም አልሰሙ፣ ሰምተዋል እንዴ?» ብሎ ጠየቀኝ፡፡
ለካስ አንድ ቀን እነጉልላት ቤት በእንግድነት እንደተቀመጠ እኔና
ጉልላት ስንነጋገር አንዳንድ የቃላት ፍንጣሪ ወሬ ሰምቶ ኖሯል። «አዎ እስከ
ዛሬ ድረስ አልሰሙም ያም ሆነ ይህ መስማታቸው አይቀርም የእኔ ውሳኔ ግን
አይለወጥም» ብዬ ሐተታ ሳላበዛ ዝም አልኩ፡፡ “ታዲያ ነገ ጧት አባትህ
ባድራጎትህ ተናደውና ተበሳጭተው ከዚህ ሁሉ ሀብት ንብረታቸው ላይ ቢነቅሉህስ?» አለኝ፡፡ “ይኸ ቀላል ጉዳይ ነው። ሁልጊዜ ሰዎች ሸምጥጠው ያወረዱትን ፍሬ መመገብ የለብኝም፡፡ እኔም በድርሻዬ መሽምጠጥና የመሽምጠጥን ልፋት ማየትና መቅመስ አለብኝ፡፡ ዛሬ ተወዝፈ ነገ በሚወረስ ነገር አልተማመንም፡፡ እሱ ያፈራውን ንብረትና ሀብት ያህል እኔም በዘዴና በቆራጥነት ከሠራ አገኘዋለሁ። ከዚያ በኋላ እኔም በፈንታዩ አውራሽ ሆንኩ ማለት ነው፡፡ ይህ ነው
👍3❤1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ያች በየጊዜው የምትጠገነውና የማያዘልቅ የገንዘብ መፍጃ ዕድሳት
የሚደረግላት የጉልላት ቮልስዋገን እየተንገጫገጨች መንቆርሰሷ አልቀረም፡፡
አውላላ ሜዳ ላይ ታጋልጠኛለች በማለት ሆዱን ቅር ያለው ዕለት በታክሲና በእግሩ መሔድ ይቀናዋል። አንዳንድ ቀን ተገፍታም ይሁን በበርቺ በርቺ
ተንቀሳቅሳ መሽከርከሯ ስለማይቀር እየተንገራገጨችም ቢሆን ይነዳታል፡፡
መንገድ ላይ ቀጥ ባለች ቁጥር ደግሞ ከየትም ለቃቅሞ ያገዛቸውን ልዩ ልዩ
መፍቻዎች፣ የብረታ ብረት ቅባት ካጠገበ አሮጊ ከረጢት ውስጥ ይዘከዝክና
ለማጠባበቅ ወደ ሞተሯ ይገሠግሣል። ምን ያደርጋል ታዲያ! ያን ውስብስብና
ቁልፍልፍ የብረት ቁልል ሲያይ “አሁን ደግሞ የትኛው ይሆን? ምን ዐይነት
ፍርጃ ነው! » ይልና አንዱን መፍቻ ወርውሮ እንቺ ቅመሽ ይላታል። በዚያው
ደግሞ ሌላ ዕቃ ይቀለጠምና ከናካቴው እንደ አበያ በሬ ለጥ ትላለች፡፡
ከተማዉ ውስጥ ያሉት ሽቃዮች የተሰናከለች ተሽከርካሪ አነፍንፈው ማግኘት ይችሉ ይመስል ወዲያውኑ እንደ ጉንዳን ይከቧታል። እሺ ካለች አለች፡
አለበለዚያም በምንጭሯ አስጎትቶም ይሁን ከወደ ጅራቷ አስጠምዞ አንዱ ጋ
አስጠግቷት ይሔዳል። ለገፉለትም ሆነ ለሳቡለት ሰዎች ስለት እንዳለበት ሰው
የሚሰጠውን ሰጥቶና ኣንጀቱን አሳርሮ በእግሩ ሲንገላወድ የነቀሉት ጭሰኛ
ይመስላል፡፡
እንድ ሰሞን ጥርሱን ነክሶ ስላሳደሳት የመኪና ወጉ ደርሷት ደኅና ስትሽከረከር ሰነበተች። እሱም ሠጋር በቅሉ ላይ እንደ ተቀመጠ የዱሮ መኳንንት ውስጧ ገብቶ ጉብ ይላል፡፡ የወዲያነሽ ጋር ሽርሽር ለመሔድ አስበን ስለ ነበር መኪናውን እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፡፡ 'ውሰድ አለ ቃሉን
ሠፈር አድርጎ በደኅንነቷ እየተመካ፡፡ «በዚህ ሰሞን ውቃቢ ቀርቧታል፡፡
እንዳጋጣሚ ግን በመሏ መጥቶ እንዱ ጋ ቀጥ ብላ ጉድ ካደረገችህ የራስህ
ጉዳይ ነው የለሁበትም!» ብሉኝ ቅዳሜ ማታ ወሰድኳት።
እኔና የወዲያነሽ ከንጋቱ አስራ አንድ ሰዓት እንደሆነ ለሁለታችን የሚበቃ ጥቂት ለስላሳ መጠጥና ምግብ ጭነን ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ጎጃም መንገድ ሰማንያ አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ተጓዝንባት፡፡ ምንም እንከንና ጉድለት ሳያጋጥመን ካሰብነው ቦታ እስክንደርስ ድረስ መኪናይቱን እያቆምኩ ባሻገር የሚታዩትን ተራሮችና ኮረብቶች ለጥ ያሉ ለምለም ሜዳዎችና የሽልጥልጥ ሸንተራራማ ገደሉች እያየን፡፡ ምቹ ቦታና መዝናኛ ነው ብዬ ከገመትኩት ሥፍራ ላይ እንደ ደረስኩ የመንገዱን ዳር አስይዤ አቆምኳት፡፡ያ ብዙ ቦታ ላይ በንዝረት የሚገጫገጨው ልል የብረታ ብረት ክፍል ጊዜያዊ ጸጥታ አገኘ። የመኪናይቱ ሙቀት ቀስ በቀስ ቀነሰ። የውስጧ ሞቃት አየር
በመስኮት በኩል በሚገባው ቀዝቃዛ አየር የተገፋ ቦታ ይለቃል፡፡ የመኪናይቱ
ፊት ወደ ሰሜን በመዞሩ በስተምሥራቅ በኩል ባለው መስኮት በከፍተኛ
ፍጥነት እየተግለበለበ የሚገባው አየር በትይዩው መስኮት እየተዥጎደጎደ
ይፈተለካል። የመኪናይቱ መሪ በስተግራ በኩል በመሆኑ የወዲያነሽን እየዳበሰ
የሚመጣው አየር ከላይዋ ላይ የለሰለሰ የሽቶ መዓዛ ያመጣና አወድወድ አድርጎኝ ይከተለባል። ባለፈው አየር እግር የሚተካው አየር ይክሰኛል። በእኔ በኩል ያለውን በር ከፍቼ እግሬን ወደ ውጪ ዘርግቼ ራሴን በየወዲያነሽ ጭን
ላይ አሳረፍኩት፡፡ አንጋጥጬ ስመለከታት አዘቅዝቃ አየችኝ፡፡ አዝራሮቼ በተከፈቱበት በኩል ቀኝ እጅዋን አሾልካ ደረቴን ስትደባብሰኝ የፍቅራዊ ደስታ ሰመመን አጥለቀለቀኝ፡፡ ጋደም እንዳልኩ ዐይኖቼ ተንገረገቡ፡፡ ዐሥራ አምስት ደቂቃ ያህል ቀ-ም እንዳደረግሁ ወደ ከተማ በሚያዘግም የጭነት መኪና ድምፅ ባንኜ ነቃሁ፡፡ ጥቂት ምዕራፎች ወደፊት ነዳሁ።
እንደገና ከመንገድ ገለል አድርጌ አቆምኳት። ሠላሳ ርምጃዎች ያህል
ወጣ ብዬ ስለ ነበር አንዳንድ አጫጭር ቁጥቋጦዎች በመኪናይቱ ተቀለጣጠሙ ጎማው የተሽከረከረባቸው በዚያው ሲቀሩ በመኪናይቱ ሆድ የተለመሰሉት ግን በመጠኑ ጎበጥበጥ ብለው ቀኑ፡፡ ከፊት ለፊታችን ጥቅጥቅ ያለ አጋምና ብሳና ድግጣና ምሥርች ዐልፎ ዐልፎ ኮርች በቅሉ አካባቢውን አይደፈር መሳይ ግርማ አልብሶታል። ወደ ዱሩ የምታስኬደው ቀጭን መንገድ ባረንጓዴ ወረቀት ላይ የተሰመረች ግራጫ መስመር ትመስላለች፡፡በዚቹ መንገድ በኩል ይዣት ልግባ ይሆን ይቅርብኝ እያልኩ ሳመነታ'
ስፈራና ስጠራጠር ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡
አንድ ውሳኔ ለመወሰን ጫካውን አፍጥጬ ስመለከት ጥቂት ራቅ
ብሎ አንድ አፈርቻና ሦስት አራት ያህል ዝንጉርጉር እንስሳት ከጫካው ውስጥ ተከታትለው ብቅ አሉ፡፡
ለጊዜው ልብ ብዬ ባለማየቴ ደንገጥ አልኩና «ምንድናቸው?» አልኩ።
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል ያደረገችው የወዲያነሽ «ፍየሉች ናቸው» አለችኝ፡፡
«እኔስ ሌላ ነገር መስለውኝ» ብዩ ነገሩን ወዲያ ወዲህ እምታታሁ፡፡ ደግነቱ
ስሜቴን ስላላወቀችብኝ ዝም አለች። ጥሎ አይጥሌ ሲረዳኝ አንድ እረኛ ብዙ
ፍየሎች እያንጋጋ ከጫካው ውስጥ ብቅ አለ፡፡ ከመኪና ወጥተን የየወዲያነሽን
እጅ ያዝ አድርጌ እንደቆምኩ እረኛው አጠገባችን ደረሰ። ደረቱ ላይ ሰፋ-ሰፋ
ያለ ኪሶች ያለባት የአቡጀዲ እጀ ጠባብ ለብሷል። የሁለቱም ኪሶቹ አፍ አደፍደፍ ብሎ ጠቁሯል። ሁለት ፍየሎች ተነጥለው ወደ ሌላ አቅጣጫ ስለሄዱ እነሱን ለመመለስ ነይ እሪያ!» ብሎ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ልብሱ ከበስተኋላው ቂጡ ላይ ድልህ የነካው ጋቢ መስሏል።
ከጉልበቱ በታች ያለው ሙጭርጭር በደረቀ ጭራሮ የተጠረገ የረገጥ ቤት መስሏል፡፡ በግራ ብብቱ ቀጠን ያለች ብትር አጣብቆ ይዟል። ዋሽንቱን በእጁ ውስጥ እያንከባለለ ያሻሻታል። ፍየሎቹ እየቀነጣጠቡ በአጠገባችን አለፉ፡፡ እረኛውም ከኋላ ከኋላቸው ከተፍ አለ። ልብሱ ላይ ዐልፎ ዐልፎ ጨጎጊት ተጣብቋል። አጋም ሲቃቅምበት የዋለው ከንፈሩ ጠቋቀሯል። እንኩታ ሲቸችግ የዋለ መስሏል።
ለስለስ ባለ ድምፅ "አንተ ልጅ ና እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ አልኩት፡፡ ነባር ፍርሃት ሳይሆን የጥርጣሬ ፍርሃት በፊቱ ላይ እየታየ በዝግታ መጥቶ ቆመ ወደ ጫካው እያመላከትኩት በዚ ጫካ ውስጥ መንገድ አለ እንዴ?ብዬ ጠየኩት? 'አዎ' ብሎ ባጭሩ መለሰልኝ፡፡
«እንግዲያውማ እዚ ቅርቡ መናፈስ ይቻላል፣ አስቸገሩኝ አትበለኝና አንድ ነገር ልለምንህ ነው? ይህን የመብል የመጠጡን ነገር ተወው፡ ነጭ
ሺልንግም እጨምርልሃለሁ ይቺን መኪና ትጠብቅልኛለህ አልኩት።
«ፍየሎቼን ማን ያግድልኛል?» ብሎ መለሰልኝ፡፡ ጓደኛም የለህ እንዴ?
ካለህ ፍየሎቻችሁን ተራ በተራ እየመለሳቹ መኪና ትጠብቁልኛላችሁ» ከማለቴ ጓደኛስ አለኝ» አለኝ፡፡ “ሒድ በል ጥራውና ና » ብዬ በትሕትና አዘዝኩት፡፡ በቀጭኗ መንገድ ወደ ጫካው ወስተ ሄደ፡፡ ወደ ጉድጓድ እንደሚገባ ሰው ጭንቅላቱ ቁልቁል ስለ ወረደች አካባቢው ተዳፋት
እንደሆነ ገባኝ፡፡ ከየወዲያነሽ ጋር የሚረባ ወሬ እንኳ ሳናወራ ጥጆችና ጊደሮች
እየነዱ ከተፍ አሉ፡፡ በመጀመሪያዉ ልጅና በሁለተኛው ልጅ መካከል ትንሽ
የመልክ ልዩነት እንጂ በአለባበስና በአረማመድ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ሁለተኛ
ልጅ ፊቱ ሰልከክ ብላ መጠጥ ያለች ነች፡፡ አፍንጫው ሰልካካ ፀጉሩ ጥቁር
ለስላሳ ነው፡፡ ቆሸሽ ባለችው የእጀ ጠባቡ ኪሶች ኣካባባና እጅጌዎቹ ላይ ልዩ
ልዩ አዝራሮች ተተክለዋል። ሁለቱም ግራና ቀኝ ቆመው እንጠብቅላችኋልን አሉ፡፡
«እንግዲህ አደራችሁን ስመለስ የማደርግላችሁን አታውቁትም አልኩና መኪናይቱን ከፍቼ ምግብና መጠጥ የያዘውን መጠነኛ የእቃ ሻንጣ
አወጣሁ፡፡
ደስ እንዲላቸውኛ በሚያጓጓ ተስፋ እንዲጠብቁልኝ በማሰብ ሁለት
ሁለት ዳቦና አንዳንድ ብርቱካን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ያች በየጊዜው የምትጠገነውና የማያዘልቅ የገንዘብ መፍጃ ዕድሳት
የሚደረግላት የጉልላት ቮልስዋገን እየተንገጫገጨች መንቆርሰሷ አልቀረም፡፡
አውላላ ሜዳ ላይ ታጋልጠኛለች በማለት ሆዱን ቅር ያለው ዕለት በታክሲና በእግሩ መሔድ ይቀናዋል። አንዳንድ ቀን ተገፍታም ይሁን በበርቺ በርቺ
ተንቀሳቅሳ መሽከርከሯ ስለማይቀር እየተንገራገጨችም ቢሆን ይነዳታል፡፡
መንገድ ላይ ቀጥ ባለች ቁጥር ደግሞ ከየትም ለቃቅሞ ያገዛቸውን ልዩ ልዩ
መፍቻዎች፣ የብረታ ብረት ቅባት ካጠገበ አሮጊ ከረጢት ውስጥ ይዘከዝክና
ለማጠባበቅ ወደ ሞተሯ ይገሠግሣል። ምን ያደርጋል ታዲያ! ያን ውስብስብና
ቁልፍልፍ የብረት ቁልል ሲያይ “አሁን ደግሞ የትኛው ይሆን? ምን ዐይነት
ፍርጃ ነው! » ይልና አንዱን መፍቻ ወርውሮ እንቺ ቅመሽ ይላታል። በዚያው
ደግሞ ሌላ ዕቃ ይቀለጠምና ከናካቴው እንደ አበያ በሬ ለጥ ትላለች፡፡
ከተማዉ ውስጥ ያሉት ሽቃዮች የተሰናከለች ተሽከርካሪ አነፍንፈው ማግኘት ይችሉ ይመስል ወዲያውኑ እንደ ጉንዳን ይከቧታል። እሺ ካለች አለች፡
አለበለዚያም በምንጭሯ አስጎትቶም ይሁን ከወደ ጅራቷ አስጠምዞ አንዱ ጋ
አስጠግቷት ይሔዳል። ለገፉለትም ሆነ ለሳቡለት ሰዎች ስለት እንዳለበት ሰው
የሚሰጠውን ሰጥቶና ኣንጀቱን አሳርሮ በእግሩ ሲንገላወድ የነቀሉት ጭሰኛ
ይመስላል፡፡
እንድ ሰሞን ጥርሱን ነክሶ ስላሳደሳት የመኪና ወጉ ደርሷት ደኅና ስትሽከረከር ሰነበተች። እሱም ሠጋር በቅሉ ላይ እንደ ተቀመጠ የዱሮ መኳንንት ውስጧ ገብቶ ጉብ ይላል፡፡ የወዲያነሽ ጋር ሽርሽር ለመሔድ አስበን ስለ ነበር መኪናውን እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፡፡ 'ውሰድ አለ ቃሉን
ሠፈር አድርጎ በደኅንነቷ እየተመካ፡፡ «በዚህ ሰሞን ውቃቢ ቀርቧታል፡፡
እንዳጋጣሚ ግን በመሏ መጥቶ እንዱ ጋ ቀጥ ብላ ጉድ ካደረገችህ የራስህ
ጉዳይ ነው የለሁበትም!» ብሉኝ ቅዳሜ ማታ ወሰድኳት።
እኔና የወዲያነሽ ከንጋቱ አስራ አንድ ሰዓት እንደሆነ ለሁለታችን የሚበቃ ጥቂት ለስላሳ መጠጥና ምግብ ጭነን ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ጎጃም መንገድ ሰማንያ አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ተጓዝንባት፡፡ ምንም እንከንና ጉድለት ሳያጋጥመን ካሰብነው ቦታ እስክንደርስ ድረስ መኪናይቱን እያቆምኩ ባሻገር የሚታዩትን ተራሮችና ኮረብቶች ለጥ ያሉ ለምለም ሜዳዎችና የሽልጥልጥ ሸንተራራማ ገደሉች እያየን፡፡ ምቹ ቦታና መዝናኛ ነው ብዬ ከገመትኩት ሥፍራ ላይ እንደ ደረስኩ የመንገዱን ዳር አስይዤ አቆምኳት፡፡ያ ብዙ ቦታ ላይ በንዝረት የሚገጫገጨው ልል የብረታ ብረት ክፍል ጊዜያዊ ጸጥታ አገኘ። የመኪናይቱ ሙቀት ቀስ በቀስ ቀነሰ። የውስጧ ሞቃት አየር
በመስኮት በኩል በሚገባው ቀዝቃዛ አየር የተገፋ ቦታ ይለቃል፡፡ የመኪናይቱ
ፊት ወደ ሰሜን በመዞሩ በስተምሥራቅ በኩል ባለው መስኮት በከፍተኛ
ፍጥነት እየተግለበለበ የሚገባው አየር በትይዩው መስኮት እየተዥጎደጎደ
ይፈተለካል። የመኪናይቱ መሪ በስተግራ በኩል በመሆኑ የወዲያነሽን እየዳበሰ
የሚመጣው አየር ከላይዋ ላይ የለሰለሰ የሽቶ መዓዛ ያመጣና አወድወድ አድርጎኝ ይከተለባል። ባለፈው አየር እግር የሚተካው አየር ይክሰኛል። በእኔ በኩል ያለውን በር ከፍቼ እግሬን ወደ ውጪ ዘርግቼ ራሴን በየወዲያነሽ ጭን
ላይ አሳረፍኩት፡፡ አንጋጥጬ ስመለከታት አዘቅዝቃ አየችኝ፡፡ አዝራሮቼ በተከፈቱበት በኩል ቀኝ እጅዋን አሾልካ ደረቴን ስትደባብሰኝ የፍቅራዊ ደስታ ሰመመን አጥለቀለቀኝ፡፡ ጋደም እንዳልኩ ዐይኖቼ ተንገረገቡ፡፡ ዐሥራ አምስት ደቂቃ ያህል ቀ-ም እንዳደረግሁ ወደ ከተማ በሚያዘግም የጭነት መኪና ድምፅ ባንኜ ነቃሁ፡፡ ጥቂት ምዕራፎች ወደፊት ነዳሁ።
እንደገና ከመንገድ ገለል አድርጌ አቆምኳት። ሠላሳ ርምጃዎች ያህል
ወጣ ብዬ ስለ ነበር አንዳንድ አጫጭር ቁጥቋጦዎች በመኪናይቱ ተቀለጣጠሙ ጎማው የተሽከረከረባቸው በዚያው ሲቀሩ በመኪናይቱ ሆድ የተለመሰሉት ግን በመጠኑ ጎበጥበጥ ብለው ቀኑ፡፡ ከፊት ለፊታችን ጥቅጥቅ ያለ አጋምና ብሳና ድግጣና ምሥርች ዐልፎ ዐልፎ ኮርች በቅሉ አካባቢውን አይደፈር መሳይ ግርማ አልብሶታል። ወደ ዱሩ የምታስኬደው ቀጭን መንገድ ባረንጓዴ ወረቀት ላይ የተሰመረች ግራጫ መስመር ትመስላለች፡፡በዚቹ መንገድ በኩል ይዣት ልግባ ይሆን ይቅርብኝ እያልኩ ሳመነታ'
ስፈራና ስጠራጠር ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡
አንድ ውሳኔ ለመወሰን ጫካውን አፍጥጬ ስመለከት ጥቂት ራቅ
ብሎ አንድ አፈርቻና ሦስት አራት ያህል ዝንጉርጉር እንስሳት ከጫካው ውስጥ ተከታትለው ብቅ አሉ፡፡
ለጊዜው ልብ ብዬ ባለማየቴ ደንገጥ አልኩና «ምንድናቸው?» አልኩ።
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል ያደረገችው የወዲያነሽ «ፍየሉች ናቸው» አለችኝ፡፡
«እኔስ ሌላ ነገር መስለውኝ» ብዩ ነገሩን ወዲያ ወዲህ እምታታሁ፡፡ ደግነቱ
ስሜቴን ስላላወቀችብኝ ዝም አለች። ጥሎ አይጥሌ ሲረዳኝ አንድ እረኛ ብዙ
ፍየሎች እያንጋጋ ከጫካው ውስጥ ብቅ አለ፡፡ ከመኪና ወጥተን የየወዲያነሽን
እጅ ያዝ አድርጌ እንደቆምኩ እረኛው አጠገባችን ደረሰ። ደረቱ ላይ ሰፋ-ሰፋ
ያለ ኪሶች ያለባት የአቡጀዲ እጀ ጠባብ ለብሷል። የሁለቱም ኪሶቹ አፍ አደፍደፍ ብሎ ጠቁሯል። ሁለት ፍየሎች ተነጥለው ወደ ሌላ አቅጣጫ ስለሄዱ እነሱን ለመመለስ ነይ እሪያ!» ብሎ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ልብሱ ከበስተኋላው ቂጡ ላይ ድልህ የነካው ጋቢ መስሏል።
ከጉልበቱ በታች ያለው ሙጭርጭር በደረቀ ጭራሮ የተጠረገ የረገጥ ቤት መስሏል፡፡ በግራ ብብቱ ቀጠን ያለች ብትር አጣብቆ ይዟል። ዋሽንቱን በእጁ ውስጥ እያንከባለለ ያሻሻታል። ፍየሎቹ እየቀነጣጠቡ በአጠገባችን አለፉ፡፡ እረኛውም ከኋላ ከኋላቸው ከተፍ አለ። ልብሱ ላይ ዐልፎ ዐልፎ ጨጎጊት ተጣብቋል። አጋም ሲቃቅምበት የዋለው ከንፈሩ ጠቋቀሯል። እንኩታ ሲቸችግ የዋለ መስሏል።
ለስለስ ባለ ድምፅ "አንተ ልጅ ና እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ አልኩት፡፡ ነባር ፍርሃት ሳይሆን የጥርጣሬ ፍርሃት በፊቱ ላይ እየታየ በዝግታ መጥቶ ቆመ ወደ ጫካው እያመላከትኩት በዚ ጫካ ውስጥ መንገድ አለ እንዴ?ብዬ ጠየኩት? 'አዎ' ብሎ ባጭሩ መለሰልኝ፡፡
«እንግዲያውማ እዚ ቅርቡ መናፈስ ይቻላል፣ አስቸገሩኝ አትበለኝና አንድ ነገር ልለምንህ ነው? ይህን የመብል የመጠጡን ነገር ተወው፡ ነጭ
ሺልንግም እጨምርልሃለሁ ይቺን መኪና ትጠብቅልኛለህ አልኩት።
«ፍየሎቼን ማን ያግድልኛል?» ብሎ መለሰልኝ፡፡ ጓደኛም የለህ እንዴ?
ካለህ ፍየሎቻችሁን ተራ በተራ እየመለሳቹ መኪና ትጠብቁልኛላችሁ» ከማለቴ ጓደኛስ አለኝ» አለኝ፡፡ “ሒድ በል ጥራውና ና » ብዬ በትሕትና አዘዝኩት፡፡ በቀጭኗ መንገድ ወደ ጫካው ወስተ ሄደ፡፡ ወደ ጉድጓድ እንደሚገባ ሰው ጭንቅላቱ ቁልቁል ስለ ወረደች አካባቢው ተዳፋት
እንደሆነ ገባኝ፡፡ ከየወዲያነሽ ጋር የሚረባ ወሬ እንኳ ሳናወራ ጥጆችና ጊደሮች
እየነዱ ከተፍ አሉ፡፡ በመጀመሪያዉ ልጅና በሁለተኛው ልጅ መካከል ትንሽ
የመልክ ልዩነት እንጂ በአለባበስና በአረማመድ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ሁለተኛ
ልጅ ፊቱ ሰልከክ ብላ መጠጥ ያለች ነች፡፡ አፍንጫው ሰልካካ ፀጉሩ ጥቁር
ለስላሳ ነው፡፡ ቆሸሽ ባለችው የእጀ ጠባቡ ኪሶች ኣካባባና እጅጌዎቹ ላይ ልዩ
ልዩ አዝራሮች ተተክለዋል። ሁለቱም ግራና ቀኝ ቆመው እንጠብቅላችኋልን አሉ፡፡
«እንግዲህ አደራችሁን ስመለስ የማደርግላችሁን አታውቁትም አልኩና መኪናይቱን ከፍቼ ምግብና መጠጥ የያዘውን መጠነኛ የእቃ ሻንጣ
አወጣሁ፡፡
ደስ እንዲላቸውኛ በሚያጓጓ ተስፋ እንዲጠብቁልኝ በማሰብ ሁለት
ሁለት ዳቦና አንዳንድ ብርቱካን
👍2
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...እንደ ረጂም ነጭ ጭራ የዕንጨት ሽበት ያንጠለጠሉ ዛፎች በብዛት ይታያሉ፡፡ የማዶውን ትቼ አጠገቤ ስመለከት ትልልቅ ጐለጐሎች የሞተች
የእባብ ራስ (ትል) ጉማጅ አግኝተው ከፊትና ከኋላ በመተጋገዝ እያንከባለሉና
እየገፉ ሲወስዷት አየሁ። ሕይወት እና ኑሮ የከባድ ትግል ውጤት ናቸው::የቦታው ቁልቁለታማ ስበት ከጉልበታቸው በላይ በማየሉ አምልጣቸው ተንከባለለች፡፡ የት እንዳረፈችና እንደገባች ስላጧት ተቅነዘነዙ። እንደ ፈሪ መርዶ ነጋሪ ዙሪያውን ዞሩ። በፍለጋ ብዛት አገኟት፡፡
ተፈጥሮ ለታካች ከማዕዷ አታጎርስምና እንደገና በትግል ይዘዋት መንገድ ቀጠሉ ፍጻሜያቸውን ለማወቅ በዐይኖቼ ተከተልኳቸው:: በአንዲት ሰፊ ደረቅ ቅጠል ሥር ከነግዳያቸው ተሸጎጡ፡፡ የእንሱ ጉዳይ በዚያው አከተመ።
የየወዲያነሽ አእምሮ ምን እንደሚያስብና እንደሚያሰላስል ባላውቅም አካባቢውን በፈገግታ ትመለከተዋለች። ድንገት ሳታስበው ክንዷን ሳብ አድርጌ
«የወዲያ! ይኸ አካባቢ ደስ አይልም እንዴ? አልኳት፡፡ በአድናቂ ስሜት ፈገገ
አለች።
ሻንጣውን ከጐኗ ሳብ አድርጋ ትውስብሳቢውን ተረተረችው:: አምስት
ብርቱካኖች አውጥታ እንደ ምፅዋት መቀበያ ሰጣ በተን ባለው ነጠላዋ ላይ
አስቀመጠች:: እናት ነች የልብ ከውቃ:: መላጥ ጀመርኩ፡፡ እሷም ተያያዘችው:: እርሷ ገና ልጣ ሳታጋምስ እኔ ለእሷ ሦስት ጊዜ ለራሴ ሁለቴ ጎረስኩ፡፡ አንዷን የብርቱካን ፍንካች አፌ ውስጥ እያንከላወስኩ «የወዲያ ደስ አላለሽም መሰል ይህ አካባቢ?» ብዬ እንደገና ጠየቅኋት። በጠይሙ ፊቷ ላይ
ፈገግታዋ እየተዘናከተ «እንዴት ብዬ ልንገርህ?» ብላ በእጅዋ የያዘቻትን
ፍንካች ሰለከከች። እኔ ሁለተኛዬን በልቼ ልጨርስ ስል እርሷ ሁለተኛይቱን
ልጣ ፈረካከሰቻት። «እንካ እስኪ ይቺን ቅመሳት ጌትዬ?» አለችኝ።
“አ!” ብዬ ተቀበልኳት። ከእጅዋ ላይ ተጨማሪ ጣዕም ፈልቆ ብርቱካኑ ውስጥ የገባ ይመስል ያጎረሰችኝ ጣፈጠኝ። ስውጥ አይታ ደገመችኝ። ቁልቁል ሸኘኋት፡፡ በድጋሚ ስትዘረጋ «ተይ ተይ በቃኝ! አንቺ ጉረሻት» አልኳት። እጅዋን እንደ ዘረጋች «ይቺን ብቻ ጌትዬ ስሞትልህ?» ስትለኝ ካንገት በላይ እየተግደረደርኩ ተቀበልኳት። ሆዴ ብቻ ሳይሆን ሕሊናዬም ጠገበች፡፡ ደመናኑን በረጅም መጥረጊያ ሙልጭ አድርገው የጠረጉት ይመስል ሰማዩ ጸጥ ያለ ባሕር መስሏል። ምንም እንኳ በሰማዩ ላይ ደመና ባይታይ ፀሐይዋን ለማየት የቻልነው ገላጣው ቦታ ላይ በመቀመጣችን ነበር፡፡
እኩለ ቀን ሊሞላ አንድ ሰዓት ብቻ ቀርቶታል። ኃይለኛውን የበጋ ሐሩር የቀነሰልን ግን ከአካባቢው የሚነፍሰው የለስላሳ አየር ሽውታ ነበር፡፡
ከነበርንበት ሥፍራ ተነሥተን ጥቂት ርምጃዎች ወደ ጎን አለፍ ብለን ከአንድ
ቁጥቋጦ ሥር ተቀመጥን፡፡ የቁጥቋጦው ቅጠል የላይ ገጽ በጣም ደማቅ አረንጓዴ ሆኖ ወበቅ እንዳቃጠለው የከበርቴ ፊት
በስተጀርባው ግን ግርጣት ያይልባታል።
ወዛም እንደ ቀድሞ ገዳይ ጎፈሬ የተቸመቸመው ድፍን አረንጓዴ ቅጠሏና
ደርበብ ያለው ቁመቷ ታይቶ የማይጠገብ የውበት ፀጋ አልብሷታል፡፡
የወዲያነሽ አንዷን ጎበጥ ብላ መሬት ለመንካት አንድ ክንድ ያህል የማይቀራትን ቅርንጫፍ እንደ ተቀመጠች ተንጠራርታ ሳበቻትና ለጋ ጫፉን ቀለጠመቻት፡፡ በቀኝ እጅዋ ይዛ ግራ እጅዋ ላይ ስትጠበጥባት ጥቂት ቅጠሎች ረገፉ፡፡
አንዷን በጥቃ ተስተካክለው በሰቀሉት ጥርሶቿ እየነካከሰች በሳቻት።
ቅጠሊቱን ከእጅዋ ላይ መንጭቄ ወረወርኩና «ምን ዐይነቷ ናት እባካችሁ?
እስኪ አሁን ምኑን አውቀሽው ነው? ምናልባትስ መርዘኛ ቅጠል ቢሆን?»
አልኩና ከአንጀት ያልመጣ ቁጣ ተቆጣሁ፡፡ ሣቅ ብላ ትንሿን ጣቴን ያዘችና
«መጥፎ ቅጠል መሰለህ እንዴ? እኔ እኮ ዱሮውንም ቢሆን አውቀዋለሁ፡፡
አንተ አታውቀውም መስል? ደደሆ እኮ ነው:: ምን ያደርጋታል ብለህ ነው?
አለችኝ።
አለማወቄን ለመሰወር ያህል ነው እንዴ? እኔ እኮ ከረሳሁት ቆይቻለሁ» አልኳት ቀድሞዉንም ቢሆን የማላውቀውን ቅጠል፡፡ እንደማላውቀው አውቃብኛለች፡፡ አሁንም ያንኑ ቅጠል በጥሳ በጥርሷ
ወጋጋችው። እኔም ለመቅመስ ያህል አራት አምስቱን ቅጠል አጎርኩት።
ምራቄ ከአፌ ውስጥ በመዘውር ተቀድቶ የተወሰደ ይመስል አፌ ኩበት ሆነ፡፡
ምላሴ ደረቀች። ላንቃዬ እንደ ተወቀረ ወፍጮ ሞዠቀኝ። ውስጥ ውስጡን
ጉዴ ፈላ፡፡ እንዳይታወቅብኝ ወሬም የለ ምንም የለ፣ ዝም አልኩ፡፡ዳግመኛ ሌላ ቅርንጫፍ ጎትቼ እመጣለሁ ብላ ስትንጠራራ ጠርዙ ጉልበቷ ላይ ያደረው ቀሚሷ እስከ ጭኗ ተስቦ አሻቀበ፡፡ የወንድነት ንቁ ፍላጎቴ በጠይሙ ውብ ገላዋ ዙሪያ ተንከራተተ፡፡ እጄን ዘርግቼ ለስላሳ ገላዋን ዳበስኩት፡፡ መላ ሰውነቴ ብው ብሎ ጋለ፡፡ ከተቀመጥኩበት ተነሣሁ የወዲያነሽንም አፈፍ ኣድርጌ አስነሣኋት። እኔ ወደ ምዕራብ እርሷ ወደ
ምሥራቅ እያየን ፊት ለፊት ቆምን፡፡ ትከሻዋን ይዤ ደረቴን ወደ ደረቷ
አስጠጋሁት። አቀፈችኝ፡፡ አቀፍኳት። ከልብ ተሳሳምን።
ነፋስ እንደ መነጫጨረው የድርቆሽ ክምር ጸጉሯን በታተንኩት፡፡ ያ ከጥቂት ወራት በፊት አንገቷ ላይ ደርሶ የነበረው ጸጉሯ አድጎ ትከሻዋን ያስሳል፡፡ ጫፍ ጫፉ ተቆልምሞ በመጥመዝመዝ እጆቹን ሽቅብ እንደ ዘረጋ ባሕታዊ ወደ ላይ አንጋጧል። ከከንፈሯ ወረድ ብዩ ያን ካፊያ እንደ መታው ጓሚያ እንኮይ የተውለከለከውን አንገቷን ባፍና በአገጬ አድፈጠፈጥኩት።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ከቁጥቋጦይቱ ውስጥ ወጣን፡፡ አካባቢውን ለማየት ስለ ፈለግን አንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ወጥተን መንገድ ፈለግን፡፡ የወዲያነሽ የለበሰችው ገብስማ ቀሚስና የደረበችው ቢጫ ሹራብ፣ የአካባቢው ዕፅዋት ልምላሜ፣ ምግብ የያዝንበት ቀይ ሻንጣ፣ የታጠቅሁት ሰማያዊ ሱሪና የለበስኩት ሽንብራማ ኮት፣ ባንድነት ሆነው የውበት ሽማ በመዘርጋት በቅልቅል ኀብረ ቀለማቸው አእምሮዬን ስላረኩት ታላቅ ሰብኣዊ ኩራት ተሰማኝ፡፡ ሹራቧንና ነጠላዋን አጣጥፌ ሻንጣ ውስጥ ከጨመርኩ በኋላ ቁልቁለቱን ተያያዝነው:: በጫካው ውስጥ ለውስጥ የሚያስኬደው መንገድ ቡችሎች እንደ ጎተቱት አንጀት የተጥመዘመዘ በመሆኑ በረጂሙ አግድም እንሔድና እንደ ገና ደግሞ ተመልሰን ከነበርንበት ቦታ ግርጌ እንደርሳለን፡፡ልዩነቱ ትንሽ ዝቅ ማለታችን ብቻ ነበር። አንዲት አፈመለከት ቅርፅ ያላት ትንሽ ቢጫ የሐረግ አበባ አገኘሁና ቀጥፌ ዘረጋሁላት፡፡ እጅዋ በድካም እንደ
መዝለፍለፍ እየቃጣው ተቀበለችኝ። መለስ ብዪ «የወዲያ! ያቺ ፀሐይና ይኸ
ቁልቁለት አዛሉሽ መሰል?» አልኳት። «ብዙ ሄጄ ስለማላውቅ ነው መሰል»
ብላ ደማ ፈገግታ አሳየች፡፡
ጥቂት ዝቅ እንዳልን ጆሮዎቼ የመልካም ተስፋ ድምፅ ሰሙ:: ለእኔም ለእርሷም አንጀት የሚያርስ እፎይታ ነበር። ከፊት ለፊታችን ከወደ ጋራው ጥግ ካሉት ትላልቅ የድንጋይ ቋጥኞች ሥር በከፍተኛ ፍጥነት እየተውዘገዘገች የምትወርድ ፏፏቴ ኣየን፡፡
በፏፏቴው ዳርና ዳር ያለው አለት በጥቁርና ጓያ መስል መልኩ
በጣም ይማርካል። ከወንዚቱ ዳርቻ የበቀሉት ዛፎች ቅርንጫፎቻቸው እንደ
ደጋን ጎብጦ ቅጠሎቻቸው ወራጅዋ ውሃ ውስጥ ተዘፍቆ በውሃይቱ ግፊት
ከወዲያ ወዲሀ ይነቃነቃሉ፡፡ ከሸለቆው ውስጥ የትኛው ቦታ ላይ እንደምትመነጭ አይታይም። ኩልል ብሎ የጠራው ውሃ የድንጋዩን መልክ ተጋርቶታል። ወራጂቱ ውሃ ድምፅ ሳታሰማ ጥቂት አግድመት ታገድምና ጥግ ይዞ ጠርብ የመሰለ ድንጋይ ሲያጋጥማት ፏፏቴ ቢጤ ፈጥራ ትፈጠረቃለች።
በፏፏቴው ማረፊያ ዙሪያ የእንዶድ አሪፋ የመሰሉ ነጭ የውሃ ንፍሥሪ ኳሶች ይንሳፈፋሉ፡፡ የጥበትና የስፋታቸው መጠን የተለያየ ቢሆንም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...እንደ ረጂም ነጭ ጭራ የዕንጨት ሽበት ያንጠለጠሉ ዛፎች በብዛት ይታያሉ፡፡ የማዶውን ትቼ አጠገቤ ስመለከት ትልልቅ ጐለጐሎች የሞተች
የእባብ ራስ (ትል) ጉማጅ አግኝተው ከፊትና ከኋላ በመተጋገዝ እያንከባለሉና
እየገፉ ሲወስዷት አየሁ። ሕይወት እና ኑሮ የከባድ ትግል ውጤት ናቸው::የቦታው ቁልቁለታማ ስበት ከጉልበታቸው በላይ በማየሉ አምልጣቸው ተንከባለለች፡፡ የት እንዳረፈችና እንደገባች ስላጧት ተቅነዘነዙ። እንደ ፈሪ መርዶ ነጋሪ ዙሪያውን ዞሩ። በፍለጋ ብዛት አገኟት፡፡
ተፈጥሮ ለታካች ከማዕዷ አታጎርስምና እንደገና በትግል ይዘዋት መንገድ ቀጠሉ ፍጻሜያቸውን ለማወቅ በዐይኖቼ ተከተልኳቸው:: በአንዲት ሰፊ ደረቅ ቅጠል ሥር ከነግዳያቸው ተሸጎጡ፡፡ የእንሱ ጉዳይ በዚያው አከተመ።
የየወዲያነሽ አእምሮ ምን እንደሚያስብና እንደሚያሰላስል ባላውቅም አካባቢውን በፈገግታ ትመለከተዋለች። ድንገት ሳታስበው ክንዷን ሳብ አድርጌ
«የወዲያ! ይኸ አካባቢ ደስ አይልም እንዴ? አልኳት፡፡ በአድናቂ ስሜት ፈገገ
አለች።
ሻንጣውን ከጐኗ ሳብ አድርጋ ትውስብሳቢውን ተረተረችው:: አምስት
ብርቱካኖች አውጥታ እንደ ምፅዋት መቀበያ ሰጣ በተን ባለው ነጠላዋ ላይ
አስቀመጠች:: እናት ነች የልብ ከውቃ:: መላጥ ጀመርኩ፡፡ እሷም ተያያዘችው:: እርሷ ገና ልጣ ሳታጋምስ እኔ ለእሷ ሦስት ጊዜ ለራሴ ሁለቴ ጎረስኩ፡፡ አንዷን የብርቱካን ፍንካች አፌ ውስጥ እያንከላወስኩ «የወዲያ ደስ አላለሽም መሰል ይህ አካባቢ?» ብዬ እንደገና ጠየቅኋት። በጠይሙ ፊቷ ላይ
ፈገግታዋ እየተዘናከተ «እንዴት ብዬ ልንገርህ?» ብላ በእጅዋ የያዘቻትን
ፍንካች ሰለከከች። እኔ ሁለተኛዬን በልቼ ልጨርስ ስል እርሷ ሁለተኛይቱን
ልጣ ፈረካከሰቻት። «እንካ እስኪ ይቺን ቅመሳት ጌትዬ?» አለችኝ።
“አ!” ብዬ ተቀበልኳት። ከእጅዋ ላይ ተጨማሪ ጣዕም ፈልቆ ብርቱካኑ ውስጥ የገባ ይመስል ያጎረሰችኝ ጣፈጠኝ። ስውጥ አይታ ደገመችኝ። ቁልቁል ሸኘኋት፡፡ በድጋሚ ስትዘረጋ «ተይ ተይ በቃኝ! አንቺ ጉረሻት» አልኳት። እጅዋን እንደ ዘረጋች «ይቺን ብቻ ጌትዬ ስሞትልህ?» ስትለኝ ካንገት በላይ እየተግደረደርኩ ተቀበልኳት። ሆዴ ብቻ ሳይሆን ሕሊናዬም ጠገበች፡፡ ደመናኑን በረጅም መጥረጊያ ሙልጭ አድርገው የጠረጉት ይመስል ሰማዩ ጸጥ ያለ ባሕር መስሏል። ምንም እንኳ በሰማዩ ላይ ደመና ባይታይ ፀሐይዋን ለማየት የቻልነው ገላጣው ቦታ ላይ በመቀመጣችን ነበር፡፡
እኩለ ቀን ሊሞላ አንድ ሰዓት ብቻ ቀርቶታል። ኃይለኛውን የበጋ ሐሩር የቀነሰልን ግን ከአካባቢው የሚነፍሰው የለስላሳ አየር ሽውታ ነበር፡፡
ከነበርንበት ሥፍራ ተነሥተን ጥቂት ርምጃዎች ወደ ጎን አለፍ ብለን ከአንድ
ቁጥቋጦ ሥር ተቀመጥን፡፡ የቁጥቋጦው ቅጠል የላይ ገጽ በጣም ደማቅ አረንጓዴ ሆኖ ወበቅ እንዳቃጠለው የከበርቴ ፊት
በስተጀርባው ግን ግርጣት ያይልባታል።
ወዛም እንደ ቀድሞ ገዳይ ጎፈሬ የተቸመቸመው ድፍን አረንጓዴ ቅጠሏና
ደርበብ ያለው ቁመቷ ታይቶ የማይጠገብ የውበት ፀጋ አልብሷታል፡፡
የወዲያነሽ አንዷን ጎበጥ ብላ መሬት ለመንካት አንድ ክንድ ያህል የማይቀራትን ቅርንጫፍ እንደ ተቀመጠች ተንጠራርታ ሳበቻትና ለጋ ጫፉን ቀለጠመቻት፡፡ በቀኝ እጅዋ ይዛ ግራ እጅዋ ላይ ስትጠበጥባት ጥቂት ቅጠሎች ረገፉ፡፡
አንዷን በጥቃ ተስተካክለው በሰቀሉት ጥርሶቿ እየነካከሰች በሳቻት።
ቅጠሊቱን ከእጅዋ ላይ መንጭቄ ወረወርኩና «ምን ዐይነቷ ናት እባካችሁ?
እስኪ አሁን ምኑን አውቀሽው ነው? ምናልባትስ መርዘኛ ቅጠል ቢሆን?»
አልኩና ከአንጀት ያልመጣ ቁጣ ተቆጣሁ፡፡ ሣቅ ብላ ትንሿን ጣቴን ያዘችና
«መጥፎ ቅጠል መሰለህ እንዴ? እኔ እኮ ዱሮውንም ቢሆን አውቀዋለሁ፡፡
አንተ አታውቀውም መስል? ደደሆ እኮ ነው:: ምን ያደርጋታል ብለህ ነው?
አለችኝ።
አለማወቄን ለመሰወር ያህል ነው እንዴ? እኔ እኮ ከረሳሁት ቆይቻለሁ» አልኳት ቀድሞዉንም ቢሆን የማላውቀውን ቅጠል፡፡ እንደማላውቀው አውቃብኛለች፡፡ አሁንም ያንኑ ቅጠል በጥሳ በጥርሷ
ወጋጋችው። እኔም ለመቅመስ ያህል አራት አምስቱን ቅጠል አጎርኩት።
ምራቄ ከአፌ ውስጥ በመዘውር ተቀድቶ የተወሰደ ይመስል አፌ ኩበት ሆነ፡፡
ምላሴ ደረቀች። ላንቃዬ እንደ ተወቀረ ወፍጮ ሞዠቀኝ። ውስጥ ውስጡን
ጉዴ ፈላ፡፡ እንዳይታወቅብኝ ወሬም የለ ምንም የለ፣ ዝም አልኩ፡፡ዳግመኛ ሌላ ቅርንጫፍ ጎትቼ እመጣለሁ ብላ ስትንጠራራ ጠርዙ ጉልበቷ ላይ ያደረው ቀሚሷ እስከ ጭኗ ተስቦ አሻቀበ፡፡ የወንድነት ንቁ ፍላጎቴ በጠይሙ ውብ ገላዋ ዙሪያ ተንከራተተ፡፡ እጄን ዘርግቼ ለስላሳ ገላዋን ዳበስኩት፡፡ መላ ሰውነቴ ብው ብሎ ጋለ፡፡ ከተቀመጥኩበት ተነሣሁ የወዲያነሽንም አፈፍ ኣድርጌ አስነሣኋት። እኔ ወደ ምዕራብ እርሷ ወደ
ምሥራቅ እያየን ፊት ለፊት ቆምን፡፡ ትከሻዋን ይዤ ደረቴን ወደ ደረቷ
አስጠጋሁት። አቀፈችኝ፡፡ አቀፍኳት። ከልብ ተሳሳምን።
ነፋስ እንደ መነጫጨረው የድርቆሽ ክምር ጸጉሯን በታተንኩት፡፡ ያ ከጥቂት ወራት በፊት አንገቷ ላይ ደርሶ የነበረው ጸጉሯ አድጎ ትከሻዋን ያስሳል፡፡ ጫፍ ጫፉ ተቆልምሞ በመጥመዝመዝ እጆቹን ሽቅብ እንደ ዘረጋ ባሕታዊ ወደ ላይ አንጋጧል። ከከንፈሯ ወረድ ብዩ ያን ካፊያ እንደ መታው ጓሚያ እንኮይ የተውለከለከውን አንገቷን ባፍና በአገጬ አድፈጠፈጥኩት።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ከቁጥቋጦይቱ ውስጥ ወጣን፡፡ አካባቢውን ለማየት ስለ ፈለግን አንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ወጥተን መንገድ ፈለግን፡፡ የወዲያነሽ የለበሰችው ገብስማ ቀሚስና የደረበችው ቢጫ ሹራብ፣ የአካባቢው ዕፅዋት ልምላሜ፣ ምግብ የያዝንበት ቀይ ሻንጣ፣ የታጠቅሁት ሰማያዊ ሱሪና የለበስኩት ሽንብራማ ኮት፣ ባንድነት ሆነው የውበት ሽማ በመዘርጋት በቅልቅል ኀብረ ቀለማቸው አእምሮዬን ስላረኩት ታላቅ ሰብኣዊ ኩራት ተሰማኝ፡፡ ሹራቧንና ነጠላዋን አጣጥፌ ሻንጣ ውስጥ ከጨመርኩ በኋላ ቁልቁለቱን ተያያዝነው:: በጫካው ውስጥ ለውስጥ የሚያስኬደው መንገድ ቡችሎች እንደ ጎተቱት አንጀት የተጥመዘመዘ በመሆኑ በረጂሙ አግድም እንሔድና እንደ ገና ደግሞ ተመልሰን ከነበርንበት ቦታ ግርጌ እንደርሳለን፡፡ልዩነቱ ትንሽ ዝቅ ማለታችን ብቻ ነበር። አንዲት አፈመለከት ቅርፅ ያላት ትንሽ ቢጫ የሐረግ አበባ አገኘሁና ቀጥፌ ዘረጋሁላት፡፡ እጅዋ በድካም እንደ
መዝለፍለፍ እየቃጣው ተቀበለችኝ። መለስ ብዪ «የወዲያ! ያቺ ፀሐይና ይኸ
ቁልቁለት አዛሉሽ መሰል?» አልኳት። «ብዙ ሄጄ ስለማላውቅ ነው መሰል»
ብላ ደማ ፈገግታ አሳየች፡፡
ጥቂት ዝቅ እንዳልን ጆሮዎቼ የመልካም ተስፋ ድምፅ ሰሙ:: ለእኔም ለእርሷም አንጀት የሚያርስ እፎይታ ነበር። ከፊት ለፊታችን ከወደ ጋራው ጥግ ካሉት ትላልቅ የድንጋይ ቋጥኞች ሥር በከፍተኛ ፍጥነት እየተውዘገዘገች የምትወርድ ፏፏቴ ኣየን፡፡
በፏፏቴው ዳርና ዳር ያለው አለት በጥቁርና ጓያ መስል መልኩ
በጣም ይማርካል። ከወንዚቱ ዳርቻ የበቀሉት ዛፎች ቅርንጫፎቻቸው እንደ
ደጋን ጎብጦ ቅጠሎቻቸው ወራጅዋ ውሃ ውስጥ ተዘፍቆ በውሃይቱ ግፊት
ከወዲያ ወዲሀ ይነቃነቃሉ፡፡ ከሸለቆው ውስጥ የትኛው ቦታ ላይ እንደምትመነጭ አይታይም። ኩልል ብሎ የጠራው ውሃ የድንጋዩን መልክ ተጋርቶታል። ወራጂቱ ውሃ ድምፅ ሳታሰማ ጥቂት አግድመት ታገድምና ጥግ ይዞ ጠርብ የመሰለ ድንጋይ ሲያጋጥማት ፏፏቴ ቢጤ ፈጥራ ትፈጠረቃለች።
በፏፏቴው ማረፊያ ዙሪያ የእንዶድ አሪፋ የመሰሉ ነጭ የውሃ ንፍሥሪ ኳሶች ይንሳፈፋሉ፡፡ የጥበትና የስፋታቸው መጠን የተለያየ ቢሆንም
👍4❤2😁1
A:
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....እሑድ ከሰዓት በኋላ.….ስለ ለጎ ሐይቅ ከተማና አካባቢዋ ኣንድ ባንድ ካወራችልኝ በኋላ የሕሊናዋን ትዝታ ወደ ደሲ መልሳ ስለ በርበሬ ገንዳ ሙጋድ፣ ዳውዶ ገራዶ፣ ሆጤ፤ ሶሳ፣ አዘዋ ገደል ሰኞ ገበያ…. ነገረችኝ፡፡ «ቆየኝ ደግሞ ሥራዬን ጨርሼ ልምጣና አወራልሃለሁ» ብላ ካልጋው ጫፍ ላይ ሸርተት ብላ ሔደች፡፡ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ሥራዋን አጠናቃ ከተፍ አለች::ነጣ ያለ ቦላሌና ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሼ አልጋው ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ
የጋሻዬነህን ሥዕል አንጋጥጬ ስመለከት ደረሰች፡፡ ሲሠውረኝ አላየችብኝም፡፡
ትከሻዬ ሥር ጣል አድርጌ ተኛሁበት፡፡ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ በሆዴ
ላይ እጂን አሻግራ በመመርኮዝ ከደረቷ ዘንበል አለች፡፡ ትከሻዋ ላይ የነበረችው ባለ አረንጓዴ ጥለት ያንገት ልብስ ተንሸራተተችና የተዘረጋችውን እጅዋን ሸፈነቻት፡፡ ከደረቴ በታች የሆዴ አካባቢ በድንኳን ውስጥ ያላ ነጭ አግዳሚ መቀጫ መሰለ፡፡
ያን በሆዴ ላይ ዐልፎ አልጋው ላይ እንደ ካስማ የተተከለውን እጅዋን በቀኝ እጄ እያሻሽሁ ምናልባት ቅር ይላት ይሆን? በማለት ስፈራ ስቸር ከቆየሁ በኋላ የወዲያ፣ አንድ ነገር ብጠይቅሽ ቅር ይልሻል?» አልኳት፡፡ አሽቆልቁላ ዐይን ዐይኔን ትክ ብላ እያየች ምንስ ነገር ብትጠይቀኝ ምን ብዬ እቀየማለሁ? ስል ጠይቀኝ ልንገርህ? ብላ አቀማመጡዋን አመቻቸች።
ለሁለት ደቂቃ ያህል ውስጥ ውስጡን ሐሳቢን አንቀረቀብኩ፡፡ እንግዲህ
ያለችውን ትበል አልኩና «የወዲያ! ለምን አስታወስከኝ ኣትበይና፣ እናትና
አባትሽ ሲሞቱ የስንት ዓመት ልጅ ነበርሽ?» አልኳት። ፈገግታዋን የቅሬታ
ደም ስለ በረዘው ፊቷ ፈዞ የክረምት ዋዜማ መሰለ፡ ውስጥ ውስጡን ራሴን
«ጌታነህ! የተዳፈነ የኅዘን ረመጥ ጫርክ፣ ያንቀላፋ ኀዘን ቀሰቀስክ» ብዩ ወቀስኩ፡፡ ደቂቃዎች ሠገሩ። ትንሽ ፈነከነክ ብላ «ምነው ምን ነካሀና ኖረሀ ኖረህ ጠየቅኸኝ?» ብላ ፊቷን የትካዜ ዐመድ ነሰነሰችበት፡፡ ካኣሁን አሁን ትጀምራለች በማለት አሰፍስፌ ጠበቅሁ፡፡ ያን እንደ አተር እምቡጥ እበጥ ብሎ የቆየ የታች ከንፈሯን በላይኛው ውብ ጥርሷ ረመጠጠችው። አንድ ጊዜ
አፈትልኮ የተነገረን ሐሳብ መልሶ መዋጥ የማይቻል በመሆኑ ችሎታዩ ከዝምታ ሊያልፍ አልቻለም። እየር ስትስብና ስታስወጣ ከፍና ዝቅ የሚለውን
ደረቷን በመመልከት ላይ እንዳለ «አባቴ ሲሞት አንዲት ፍሬ ልጅ ነበርኩ
አሉ፡፡ ትንሽ ትንሽ እንደ ሕልም ትዝ ይለኛል፡፡ እናቴም አባትሽ ከልጆቹ
ሁሉ አንቺን ይወድሽ ነበር፡፡ ሳይንት እሚባል አገር ካሉት ዘመዶቹ መኻል
የሚወዳትን አክስቱን ስለምትመስዪ የእርሷ ነገር ሆነበትና 'የወዲያነሽ የወዲያ
ሰው ብሎ ስም አወጣልሽና የወዲያዬ የወዲያነሽ አልንሽ ብላ ነገረችኝ። ልጅ
ስለ ነበርኩ ሁሉንም ኣላስታውስም እንጂ አባቴ ብዙ ጊዜ ታሞና ማቆ ማቆ
ነው የሞተው። የሞተ ዕለት ሰዎች ሁሉ ሲያለቅሱ አይቼ እኔም ትንሽ
አልቅሻለሁ፡፡ ሞት ምን እንደሆነ ስለማላውቅ ሄዶ የሚመለስ እንጂ በዚያው የሚቀር አይመስለኝም ነበር፡፡ ሬሳውን በአልጋ ይዘው ከቤት ሲወጡ ምንም ስላልመሰለኝ ጉድሮዬን እያዘናፈልኩ ከመንደሩ ልጆች ጋር እቦርቅ ነበር፡፡
ታናሽ እኅቴ እማዋይሽ ክርስትና የተነሣች ዕለት መጥተው የነበሩት ቄሶች ራሱ የቀብሩም ዕለት መጥተው ስለነበር ለደስታ የመጡ እንጂ ለሌላ ነገር
የመጡ አልመሰለኝም። እያደር ግን ዋል አደር ስል ዕንጨት ለቀማም ይሁን
ዋርማ ይዤ ጅረት ስወርድ ጓደኛቼ እንደ ቀልድ 'አንቺዬ ማሳዘኗ' አንድ ቀን እኮ የሞቱት የዚች አባት ናቸው” እያሉ ሲያንሾካሽኩ እየሰማሁ ግራ ግብት ይለኝ ነበር። አባቴ ከሞተ በኋላ እዚያው አገር ቤት ከእናቴና ከእኅት ወንድሞቼ ጋር ቆየሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን የእናቴ ታላቅ እኅት ከአገር ቤት ወደ ከተማ ይዛኝ መጥታ ትምህርት ቤት አስገባችኝ ብላ ዝም ስላለች ያ በኀዘን ጉም ተሸፍኖ የቆየው ዐይኔ ቦግ ብሎ ወደ የወዲያነሽ ዐይኖች ተወረወረ፡፡እንባዋ እንደ አሸንዳ ጠፈጠፍ እየተንከባለለ በጉንጯ ላይ ተንኳለለ፡፡ ልብሴ ላይ የተንጠባጠበውን ዕንባዋን ደረቁ ሸሚዜ እንደ ግንቦት አፈር ጠጣው፡ የደቀነችውን ወሬ ለመጨረስ እንባዋን ካባበሰች በኋላ «አሁንም ቢሆን እነዚያ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ትዝ ይሉኛል። እነ የሻረግ፣ ዘነበች፡ አሚናት፡
ይመር፣ አያሌው፣ ገበያነሽ፣ ሰኢድ ኧረ ስንቱ ስንቱ... እክስቴ ከልጆቹ ሁሉ እኔን መርጣ የወሰደችኝ የረጋች ልጅ ነች፣ ደስ ትለኛለች» ብላ ነበር። ሁለት ሦስት ጊዜ ላግባ ባይ መጥቶ ሲጠይቅ ቆይ እስኪ ጥቂት ተምራ ነው ነፍስ ትወቅ» ብላ እምቢ አለቻቸው፡፡
እኔና እርሷ ብቻችንን ተቀምጠን በምናወራበት ጊዜ ግን፡ ያም የሸማኔ ልጅ ነው፣ ያኛው መናጢ ዘረ ድሃ ነው፣ የዚያኛውም እናት ዘር ማንዘሯ ሸክላ ሠሪ ነው የጠዳ የጨዋ ልጅ እስኪመጣ ሰጥ ብለሽ ትምርትሽን ተማሪ» ትለኝ ነበር፡፡ አክስቴ ከምላሷና ከንዝንኳ በስተቀር ሆዷ ባዶ ነው::ባልዋ አይዋ ዘለቀ አንድ ሲናገሩ ሁለትና ሦስት ነበር የምትመልስላቸው:: ችለው ችለው አንድ ቀን የተነሡ ለታ ግን ቀሽልደው ቀሽልደው ሲለቋት ውሃ ውስጥ የገባች አይጥ ትሆናለች። እሷ ታዲያ የሳቸውን እልክ በኔ ላይ ነበር የምትወጣው::
«አንቺ መድረሻ ቢስ ግንባረ ነጭ» ብላ ከጀመረች በርበሬ ሳታጥነኝና በጥርሷ ሳትበተብተኝ እንገላገልም፡፡ «አፈር ብይ! አፈር ያስበላሽ! ያባትሽን ቀን ይስጥሽ» ስትለኝ ግን አይመኙ ነገር ያስመኘኝ ነበር። ለጎ-ሐይቅ በሔድኩ በአራተኛው ዓመት አገር ቤት ወረርሽኝ ገባ ተባለና እናቴ በጠና ታመመች።ያኔውኑ ትምህርት ቤት በመዘጋቱ ካልሔድኩ ብዬ አገር አመስኩ፡፡ ቢሉኝ ቢፈጥሩኝ እዚያቹ ከናቴ
ጋር እሞታታለሁ እንጂ እይደረግም ብዬ
አስቸገርኩ፡፡ በማይረባው ነገር ሁሉ ካክስቴ ጋር መነታረኩ መሮኝ ስለ ነበር
ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከፊቷ ገለል ብዬ እፎይ ማለት ፈልጌ ነበር። ወሬ
አበዛሁብህ መሰል? ላሳጥርልህ፣ እናቴ ቡሄ በዋላ ልክ በሳምንቱ ሞተች። ያን
እለት የሆንኩትን አኳኋን ግን ባትሰማው ይሻላል። እናቴ ፀሐይነሽ አማረ ትባል ነበር። ከዘመዶቻችን ጋር ዕርባዋን አውጥቼ ትምህርት ቤት የተከፈተ
በሳምንቱ ከዚያቹ ከአክስቴ ጋር ወደ ከተማ ተመለስኩ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ወደ
አገር ቤት አልተመለስኩም» ብላ ጋደም አለች፡፡ ያ የቀድሞ ውበታዋም ርዝማኔውን ሊይዝ ጥቂት የቀረው የሴትነቷ ግርማ የሆነው ዞማ ጸጉሯ በአንገቷ ዙሪያ በተንተን ብሎ ተነሰነሰ። ድንገት
ቀና ብላ እግሯን ኮርምታ ተቀመጠች፡፡ «አልጨረስኩልህም እኮ» ብላ
ቀጠለች። በበኩሌ የሕይወቷ ምሬት አንገፍግፎኝ ነበር፡፡» ያክስቴ ባል ዘኃ
ነጋዴ ነበሩ። ከደሴ ዘኃ ያመጡና፣ ከሐይቅ ደግሞ አንጋሬና ቆዳ ይዘው
ይመለሳሉ። የኋላ ኋላ ግን ደሴ መሬት ገዝተው ቤት ስለሠሩና ንብረት ስላበጁ ሁላችንም ወደዚያው ሄድን። ደሴ ወይዘሮ ስሒን ትምህርት ቤት አምስተኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ያነዩ ገና ዐሥራ አራት ዓመቴ ነበር፡፡ አክስቴ ውሃ ቀጠነ፣ ጪስ በነነ፣ እያለች ስለምትነዛነዝ ይብስ እሳትና ጭድ ሆንን። እልህ ማብረጃ አረገችኝ፡፡ ስወጣም ስገባም ስድብና ዱላ ሆነ፡፡
ለጊዜውም ቢሆን ሌላ የሚያስጠጋኝና የምገባበት ዘመድ ስላልነበረኝ ያለችውን ብትል ታግሼ ዝም አልኩ፡፡ እንደ ምንም ብዬ ተፍጨርጭሬ ሰባተኛ ክፍል እንደ ገባሁ ከነከተቴው ሒጂልኝ! ውጪልኝ! ዐይንሽን ላፈር! ማለት አመጣች። ንግግሯ ሁሉ አንገሸገሸኝ፡፡ የዓመቱ ትምህርት ባሳር በመከራ ካለቀልኝ በኋላ ብሞትም ልሙት ብዩ ቆርጬ ተነሣሁ አንድ ቀን
ጎረቤታችን የነበሩ አንድ የጦር
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....እሑድ ከሰዓት በኋላ.….ስለ ለጎ ሐይቅ ከተማና አካባቢዋ ኣንድ ባንድ ካወራችልኝ በኋላ የሕሊናዋን ትዝታ ወደ ደሲ መልሳ ስለ በርበሬ ገንዳ ሙጋድ፣ ዳውዶ ገራዶ፣ ሆጤ፤ ሶሳ፣ አዘዋ ገደል ሰኞ ገበያ…. ነገረችኝ፡፡ «ቆየኝ ደግሞ ሥራዬን ጨርሼ ልምጣና አወራልሃለሁ» ብላ ካልጋው ጫፍ ላይ ሸርተት ብላ ሔደች፡፡ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ሥራዋን አጠናቃ ከተፍ አለች::ነጣ ያለ ቦላሌና ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሼ አልጋው ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ
የጋሻዬነህን ሥዕል አንጋጥጬ ስመለከት ደረሰች፡፡ ሲሠውረኝ አላየችብኝም፡፡
ትከሻዬ ሥር ጣል አድርጌ ተኛሁበት፡፡ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ በሆዴ
ላይ እጂን አሻግራ በመመርኮዝ ከደረቷ ዘንበል አለች፡፡ ትከሻዋ ላይ የነበረችው ባለ አረንጓዴ ጥለት ያንገት ልብስ ተንሸራተተችና የተዘረጋችውን እጅዋን ሸፈነቻት፡፡ ከደረቴ በታች የሆዴ አካባቢ በድንኳን ውስጥ ያላ ነጭ አግዳሚ መቀጫ መሰለ፡፡
ያን በሆዴ ላይ ዐልፎ አልጋው ላይ እንደ ካስማ የተተከለውን እጅዋን በቀኝ እጄ እያሻሽሁ ምናልባት ቅር ይላት ይሆን? በማለት ስፈራ ስቸር ከቆየሁ በኋላ የወዲያ፣ አንድ ነገር ብጠይቅሽ ቅር ይልሻል?» አልኳት፡፡ አሽቆልቁላ ዐይን ዐይኔን ትክ ብላ እያየች ምንስ ነገር ብትጠይቀኝ ምን ብዬ እቀየማለሁ? ስል ጠይቀኝ ልንገርህ? ብላ አቀማመጡዋን አመቻቸች።
ለሁለት ደቂቃ ያህል ውስጥ ውስጡን ሐሳቢን አንቀረቀብኩ፡፡ እንግዲህ
ያለችውን ትበል አልኩና «የወዲያ! ለምን አስታወስከኝ ኣትበይና፣ እናትና
አባትሽ ሲሞቱ የስንት ዓመት ልጅ ነበርሽ?» አልኳት። ፈገግታዋን የቅሬታ
ደም ስለ በረዘው ፊቷ ፈዞ የክረምት ዋዜማ መሰለ፡ ውስጥ ውስጡን ራሴን
«ጌታነህ! የተዳፈነ የኅዘን ረመጥ ጫርክ፣ ያንቀላፋ ኀዘን ቀሰቀስክ» ብዩ ወቀስኩ፡፡ ደቂቃዎች ሠገሩ። ትንሽ ፈነከነክ ብላ «ምነው ምን ነካሀና ኖረሀ ኖረህ ጠየቅኸኝ?» ብላ ፊቷን የትካዜ ዐመድ ነሰነሰችበት፡፡ ካኣሁን አሁን ትጀምራለች በማለት አሰፍስፌ ጠበቅሁ፡፡ ያን እንደ አተር እምቡጥ እበጥ ብሎ የቆየ የታች ከንፈሯን በላይኛው ውብ ጥርሷ ረመጠጠችው። አንድ ጊዜ
አፈትልኮ የተነገረን ሐሳብ መልሶ መዋጥ የማይቻል በመሆኑ ችሎታዩ ከዝምታ ሊያልፍ አልቻለም። እየር ስትስብና ስታስወጣ ከፍና ዝቅ የሚለውን
ደረቷን በመመልከት ላይ እንዳለ «አባቴ ሲሞት አንዲት ፍሬ ልጅ ነበርኩ
አሉ፡፡ ትንሽ ትንሽ እንደ ሕልም ትዝ ይለኛል፡፡ እናቴም አባትሽ ከልጆቹ
ሁሉ አንቺን ይወድሽ ነበር፡፡ ሳይንት እሚባል አገር ካሉት ዘመዶቹ መኻል
የሚወዳትን አክስቱን ስለምትመስዪ የእርሷ ነገር ሆነበትና 'የወዲያነሽ የወዲያ
ሰው ብሎ ስም አወጣልሽና የወዲያዬ የወዲያነሽ አልንሽ ብላ ነገረችኝ። ልጅ
ስለ ነበርኩ ሁሉንም ኣላስታውስም እንጂ አባቴ ብዙ ጊዜ ታሞና ማቆ ማቆ
ነው የሞተው። የሞተ ዕለት ሰዎች ሁሉ ሲያለቅሱ አይቼ እኔም ትንሽ
አልቅሻለሁ፡፡ ሞት ምን እንደሆነ ስለማላውቅ ሄዶ የሚመለስ እንጂ በዚያው የሚቀር አይመስለኝም ነበር፡፡ ሬሳውን በአልጋ ይዘው ከቤት ሲወጡ ምንም ስላልመሰለኝ ጉድሮዬን እያዘናፈልኩ ከመንደሩ ልጆች ጋር እቦርቅ ነበር፡፡
ታናሽ እኅቴ እማዋይሽ ክርስትና የተነሣች ዕለት መጥተው የነበሩት ቄሶች ራሱ የቀብሩም ዕለት መጥተው ስለነበር ለደስታ የመጡ እንጂ ለሌላ ነገር
የመጡ አልመሰለኝም። እያደር ግን ዋል አደር ስል ዕንጨት ለቀማም ይሁን
ዋርማ ይዤ ጅረት ስወርድ ጓደኛቼ እንደ ቀልድ 'አንቺዬ ማሳዘኗ' አንድ ቀን እኮ የሞቱት የዚች አባት ናቸው” እያሉ ሲያንሾካሽኩ እየሰማሁ ግራ ግብት ይለኝ ነበር። አባቴ ከሞተ በኋላ እዚያው አገር ቤት ከእናቴና ከእኅት ወንድሞቼ ጋር ቆየሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን የእናቴ ታላቅ እኅት ከአገር ቤት ወደ ከተማ ይዛኝ መጥታ ትምህርት ቤት አስገባችኝ ብላ ዝም ስላለች ያ በኀዘን ጉም ተሸፍኖ የቆየው ዐይኔ ቦግ ብሎ ወደ የወዲያነሽ ዐይኖች ተወረወረ፡፡እንባዋ እንደ አሸንዳ ጠፈጠፍ እየተንከባለለ በጉንጯ ላይ ተንኳለለ፡፡ ልብሴ ላይ የተንጠባጠበውን ዕንባዋን ደረቁ ሸሚዜ እንደ ግንቦት አፈር ጠጣው፡ የደቀነችውን ወሬ ለመጨረስ እንባዋን ካባበሰች በኋላ «አሁንም ቢሆን እነዚያ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ትዝ ይሉኛል። እነ የሻረግ፣ ዘነበች፡ አሚናት፡
ይመር፣ አያሌው፣ ገበያነሽ፣ ሰኢድ ኧረ ስንቱ ስንቱ... እክስቴ ከልጆቹ ሁሉ እኔን መርጣ የወሰደችኝ የረጋች ልጅ ነች፣ ደስ ትለኛለች» ብላ ነበር። ሁለት ሦስት ጊዜ ላግባ ባይ መጥቶ ሲጠይቅ ቆይ እስኪ ጥቂት ተምራ ነው ነፍስ ትወቅ» ብላ እምቢ አለቻቸው፡፡
እኔና እርሷ ብቻችንን ተቀምጠን በምናወራበት ጊዜ ግን፡ ያም የሸማኔ ልጅ ነው፣ ያኛው መናጢ ዘረ ድሃ ነው፣ የዚያኛውም እናት ዘር ማንዘሯ ሸክላ ሠሪ ነው የጠዳ የጨዋ ልጅ እስኪመጣ ሰጥ ብለሽ ትምርትሽን ተማሪ» ትለኝ ነበር፡፡ አክስቴ ከምላሷና ከንዝንኳ በስተቀር ሆዷ ባዶ ነው::ባልዋ አይዋ ዘለቀ አንድ ሲናገሩ ሁለትና ሦስት ነበር የምትመልስላቸው:: ችለው ችለው አንድ ቀን የተነሡ ለታ ግን ቀሽልደው ቀሽልደው ሲለቋት ውሃ ውስጥ የገባች አይጥ ትሆናለች። እሷ ታዲያ የሳቸውን እልክ በኔ ላይ ነበር የምትወጣው::
«አንቺ መድረሻ ቢስ ግንባረ ነጭ» ብላ ከጀመረች በርበሬ ሳታጥነኝና በጥርሷ ሳትበተብተኝ እንገላገልም፡፡ «አፈር ብይ! አፈር ያስበላሽ! ያባትሽን ቀን ይስጥሽ» ስትለኝ ግን አይመኙ ነገር ያስመኘኝ ነበር። ለጎ-ሐይቅ በሔድኩ በአራተኛው ዓመት አገር ቤት ወረርሽኝ ገባ ተባለና እናቴ በጠና ታመመች።ያኔውኑ ትምህርት ቤት በመዘጋቱ ካልሔድኩ ብዬ አገር አመስኩ፡፡ ቢሉኝ ቢፈጥሩኝ እዚያቹ ከናቴ
ጋር እሞታታለሁ እንጂ እይደረግም ብዬ
አስቸገርኩ፡፡ በማይረባው ነገር ሁሉ ካክስቴ ጋር መነታረኩ መሮኝ ስለ ነበር
ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከፊቷ ገለል ብዬ እፎይ ማለት ፈልጌ ነበር። ወሬ
አበዛሁብህ መሰል? ላሳጥርልህ፣ እናቴ ቡሄ በዋላ ልክ በሳምንቱ ሞተች። ያን
እለት የሆንኩትን አኳኋን ግን ባትሰማው ይሻላል። እናቴ ፀሐይነሽ አማረ ትባል ነበር። ከዘመዶቻችን ጋር ዕርባዋን አውጥቼ ትምህርት ቤት የተከፈተ
በሳምንቱ ከዚያቹ ከአክስቴ ጋር ወደ ከተማ ተመለስኩ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ወደ
አገር ቤት አልተመለስኩም» ብላ ጋደም አለች፡፡ ያ የቀድሞ ውበታዋም ርዝማኔውን ሊይዝ ጥቂት የቀረው የሴትነቷ ግርማ የሆነው ዞማ ጸጉሯ በአንገቷ ዙሪያ በተንተን ብሎ ተነሰነሰ። ድንገት
ቀና ብላ እግሯን ኮርምታ ተቀመጠች፡፡ «አልጨረስኩልህም እኮ» ብላ
ቀጠለች። በበኩሌ የሕይወቷ ምሬት አንገፍግፎኝ ነበር፡፡» ያክስቴ ባል ዘኃ
ነጋዴ ነበሩ። ከደሴ ዘኃ ያመጡና፣ ከሐይቅ ደግሞ አንጋሬና ቆዳ ይዘው
ይመለሳሉ። የኋላ ኋላ ግን ደሴ መሬት ገዝተው ቤት ስለሠሩና ንብረት ስላበጁ ሁላችንም ወደዚያው ሄድን። ደሴ ወይዘሮ ስሒን ትምህርት ቤት አምስተኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ያነዩ ገና ዐሥራ አራት ዓመቴ ነበር፡፡ አክስቴ ውሃ ቀጠነ፣ ጪስ በነነ፣ እያለች ስለምትነዛነዝ ይብስ እሳትና ጭድ ሆንን። እልህ ማብረጃ አረገችኝ፡፡ ስወጣም ስገባም ስድብና ዱላ ሆነ፡፡
ለጊዜውም ቢሆን ሌላ የሚያስጠጋኝና የምገባበት ዘመድ ስላልነበረኝ ያለችውን ብትል ታግሼ ዝም አልኩ፡፡ እንደ ምንም ብዬ ተፍጨርጭሬ ሰባተኛ ክፍል እንደ ገባሁ ከነከተቴው ሒጂልኝ! ውጪልኝ! ዐይንሽን ላፈር! ማለት አመጣች። ንግግሯ ሁሉ አንገሸገሸኝ፡፡ የዓመቱ ትምህርት ባሳር በመከራ ካለቀልኝ በኋላ ብሞትም ልሙት ብዩ ቆርጬ ተነሣሁ አንድ ቀን
ጎረቤታችን የነበሩ አንድ የጦር
👍7
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
በሐሰት ተገንብቶ በተለበጠ አካባቢ ሁሉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ተገንጥሉ ልዩ ትክክለኛ አካባቢ ለመፍጠር ከፍ ያለ ችግር ያጋጥመዋል።ሁሉም በየበኩሉ የየራሱን የኑሮ ማሳ እያዳበረ በሚያርስበትና በሚያዘምርበት
ትክክለኛ ዓላማና ግብ ማምራት እንጂ፣ ይኸ እንዲህ ነው፣ ያኛው እንዲያ
አካባቢ፣ የራስን ዶማ እና መሣሪያ ይዞ በመቀላቀል ቀስ በቀስ ወደሚመኙት
ነው እያሉ መጃጃል ወደፊት መራመድ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ ነው:: ልክ
ያልሆነው ነገር ሁሉ ወለል ብሎ ቢታየኝም በግል ስክበው የሰነበትኩት
አስተሳሰብ ለጊዜውም ቢሆን በአካባቢዬ አሮጌ ልማድ ተዋጠ።
ባለሁበት ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ተርፎታል፣ ሞልቶታል፣ እየተባለ ነገር ግን ዝቅ ብሎ መታየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለምና የአካባቢን አስተያየትና ግምት ለመለወጥ ሲባል የሚደረግ ልዩ ልዩ ጥረት አንድም ፈጽሞ መውደቂያ ወይም ለጊዜው ቀጥ ብሎ መቆሚያ ሊሆን ይችላል፡፡ ግላዊ ስምና ክብርን ለመጠበቅና ለማስከበር ሲባል የሚደረግ የስግብግብነት ውጣ ውረድ ሁሉ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ የሥቃይ ሸክም ነው::
በግል ሀብት ጥሪት ፍላጎት የቆሰለና የበለዘ ሕሊናን ለማንጻትና ለማዳን የሚደረግ ጥረት መሪርና አድካሚ ነው:: ከቤተሰቦቼ የሚደርስብኝን ትችትና የወጪ ገቢ ሐሜት ለመከላከል ያህል የሕሊናዬን ዓላማ ቅንጣት ታህል ችላ ብዪ ሕይወት ኣልባ ተራ ስሜን ለማዳን ስል አንዲት የተለየች የሐሳብና የተግባር ዘመቻ ጀመርኩ። ሌሎችን ለመምሰልና ላይ ላዩን እኩል ሆኜ ለመታየት ስል አንዲት ባገልግሎት ላይ ከዋለች አራት ዓመት ያህል ያለፋት ቮልስዋገን መኪና ከስንት የደላላ ንትርክ በኋላ ገዛሁ፡፡ በክፍያው ላይ እኔና ጉልላት ተረባረብንበት፡፡ የጠንቃቃ ሰው ንብረት ስለ ነበረች በየጊዜው በመሰናከል አላስቸገረችኝም፡፡
ኑሮዬን መለስ ብዬ እያየሁ «የሕይወት ቀላል ፍቺ ይህች ትሆን? ወይስ ራስን የማታለያ ስሕተት» እያልኩ ማሰብ አዲሱ ልማዱ ሆነ፡፡ መስሎ መታየትና በጉራ ተኮፍሶ መወጣጠርን ከዚህም ከዚያም ቀሠምኩ፡፡ አንዳንድ ቀን ያን መበስበሱ እየታወቀ ቀለም እንደተቀባ ግንድ ላይ ላዩን ያሽበረቀ አስመሳይ ኑሮዬን መለስ ብዬ ሳየው ጎምዛዛ ኀዘን ይስማኝና በረጅሙ እተክዛለሁ። በሳምንት አንድና ሁለት ቀን እያመሽሁ መግባትና ሳይበዛም
መጠጥ መጎንጨትን ኣዘወተርኩ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከጧቱ ሁለት ሰዓት የወጣሁ ጥምብዝ ብዬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ገባሁ።
የወዲያነሽ ያጋጠማትን ያልታሰበ ችግር ችላ «አይ ጌትዩ! ስንቱን ለፈለፍከው ! መንጋት አበይለው ነጋ» አለችኝ ሰክሬ በገባሁ ማግሥት አብረን ቁርስ ስንበላ፡፡ ከዚያ በመጥፎ ልማዳዊ እምነት ተበክሎ ካደገው ልቦናዩ ምን አስነዋሪ ነገር ወጥቶ ይሆን በማለት በጣም ሠጋሁ፡፡ ከጎኔ ተነሥታ በስተጀርባዬ ቆመች፡፡ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ሁሉ ፊት ለፊቴ ባለው የቁም ሳጥን መስታዋት እመለከት ነበር። እሷም ይህችኑ ብልሃቴን ደርሳበት ኖሮ በመስተዋቲቱ ውስጥ ስታየኝ ዐይን ለዐይን ተጋጨን። የያዝኩትን
የእንቁላል ጥብስ ለመጉረስ አፈን ከፈት ላደርግ ሣቄ አመለጠኝና ተንከተከትኩ፡፡ እጄን ስባ ጎረሰችብኝ፡፡ 'ጌትዬ” አለችኝ ጉርሻዩን ቀምታ የልቧን ካደረሰች በኋላ፡፡ «ይኸው ዛሬ አምስተኛህ መሆኑ ነው መሰል ካንተ አላውቅምና ለምኑም ለምኑም ቢሆን ጥሩ አይደለም። ጌታነህ ሰክሮ እንዲህ አለ መባል ደግሞ አንዳች የሚያህል ነውር ነው። በዚያ ላይ ውርደቱ? ቅሌቱ... ጌትዬ አፈር ስበላልህ! ባንዲት እንጨት ስሔድ አትጠጣ፡ መቼም
ይኸን ጉድህን ጋሼ ጉልላት ኣልሰማም እንጂ ቢሰማማ....» ብላ አዘኔታና
ምክሯን አደባልቃ ከነገረችኝ በኋላ የተዳፈረችኝ ስለ መሰላት ሳይታወቃት
ትከሻዬን በግንባሯ ጠረግ ጠረግ እድርጋ ልትሸሽ ስትል እጅዋን ይዤ
አስቀረኋት፡፡
«ለመሆኑ ክፉ ነገር ተናገርኩ እንዴ? ሆድ ያባውን... የሚሉት ነገር ነበረበት?... አልኳት።
«የተናገርከው ሁሉ ምኑም አልገባኝ። እነዚያኑ ቤተሰቦችህን ስትሰድብና ስታጥላላ ነው ያደርከው:: እኔንም አይዞሽ በርቺ ድሉ ያንቺ ነው፤ ያባትሽ ስም አሸናፊ ነው እንቺም አሸናፊ ትሆኛለሽ እያልክ
ስታጫውተኝ አመሽህ» ብላ እጅዋን ነጥቃኝ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
የገዛ ስሕተቴን ለማስተባበል ሳይሆን ለማመኻንት ያህል ከጓዳ መለስ
እንዳለች «ትላንትም በል በል ብለው፣ አጠጥተውኝ ነው እንጂ ከእንግዲህ
ወዲህ መጠጥ በረበት ኣልዞርም» አልኳትና ወደ ሥራዬ ሄድኩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሌሊቱ አብዛኛውን ክፍል በሐሳብ ስገላበጥ አሳለፍኩት፡፡ እሑድ ጧት ከቁርስ በኋላ ሽር አልኩ። ሰበሰቡ ላይ ቆም ብዬ የወዲያነሽን ጠራኋት።
ከወደ ውስጥ ከተፍ አለች፡፡ የምትለውን ለመስማት ያህል 'አይቆርጡን አይፈልጡን ነይ እስኪ ወላጆቼ ቤት ይዤሽ ልሂድ? እኔ እያለሁ ምንም
እትሆኚ» አልኳት፡፡
ከልቤ ስለ መሰላት ክው ብላ ደነገጠች፡፡ «እንዲህ ንገረኝና ይለይልኝ
እንጂ! እጄን ይዘህ አስገድለኛ! እንኳንስ ካንተ ጋር አብሬ እዚያች ቤት
ገብቼላቸውና መንገድ ላይ ያዩን ይሆን እያልኩ አካላቴ ይበጠቃል። ምን
ቅብጥ ልጄ! ይልቅስ ሂድ ይቅናህ!» ብላ በእርሷ አስተሳሰብ የልቧን ተናግሬ
እንዳበቃች መንገድ ገባሁ፡፡ ጠምዛዛው መንገድ ከዐይኗ እስከ ሰወረኝ ድረስ
የአጥር ግቢውን በር ተደግፋ በዐይኖቿ ሸንችኝ፡፡ መኪናዬን ከቀበና ድልድይ
በላይ አቁሜ በእግር ቀጠልኩ። የወላጆቼን ቤት ከረገጥኩ ሦስት ወር ያህል አልፎኝ ስለ ነበር በዱሮው ዘበኛ በአቶ በየነ ምትክ ሌላ ሰው ተቀጥረዋል።
አጠር ብለው ከወደ ዐይናቸው ላም ያሉ ጸጉረ ገብስማ ሽማግሌ ናቸው::
አያውቁኝም። ለመግባት ፍቃድ ጠየቅሁ። ደረታቸውን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥተው
ማንን ነው የምትፈልገው? ጌቶችና አሜቴ እንደሁ ቤተስኪያን ሊስሙ እንደ
ኤዱ አልተመለሱም፡፡ ቆየት ብለህ ተመልሰሀ ናና ነግሬልህ ትገባለህ» ብለው ፊታቸውን አዙረው ችላ አሉኝ፡፡ ቸልታቸው ስላበሳጨኝ ልጃቸውስ የለችም
እንዴ? እሷም ካለች ያው ነው» ብዬ ጠየቅኋቸው፡፡ በጥፊ የመታኋቸው ያህል
ብው ብለው ተናደዱ፡፡ «እንዴ! እንዴ! መች አበድኩና! አንተ ስለ እኔ
እንጀራ ምንቸገረህ! የዋዛ ቤት መስሎሃል! እዚች ቦታም አያውሉኝ!» አሉና ነገሩኝ፡፡ ቀባጥሬም ሆነ ማንነቴን አስረድቼ መግባት ስላልፈለግሁ ደጅ ደጁን እያልኩ ለመቆየት ወሰንኩ፡፡ በዚያው አካባቢ መለስ ቀለስ ስል የውብነሽ ባዘቶ የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሳ ስትመጣ አየኋት።አመጣጧ በእኔው ኣቅጣጫ ስለ ነበር ቆሜ ጠበቅኋት። ከሩቅ የጀመረው ፈገግታዋ አጠገቤ ስትደርስ ተራውን ለውብ ጥርሶቿ ለቀቀ፡፡ ከጋቢው ሥር እጅዋን ብቅ አድርጋ ጨበጠችኝ፡፡ ስሜቷን ለመሸንገል ያህል ሳምኳት፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ሽማግሌው ኣጠገብ ደረስን፡፡ ቀና ብለው ከእግር እስከ ራሴ አዩኝ። ይኸ ደግሞ የማን ነው? በሚል አስተያየት እየገረመሙኝ አልፈናቸው ገባን፡፡
በምድረ ግቢው ያሉት አበቦችና አትክልቶች በጣም ያማሩ መሰለኝ፡፡
ከየውብነሽ ጋር እያወራሁ ዐይኖቼ ካትክልቶቸ ላይ አልተነቀሉም፡፡ እነዚያ
ምን ጊዜም ሌላ መሄጂያና መግቢያ የሌላቸው የሚመስሉት ነባር ሠራተኞች
ናፍቆትን በሚገልጽ ፈገግታ እጅ ነሡኝ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ዛሬ የጌቶች
ልጅ ከየት መጡ?” እንደሚሉ ታወቀኝ፡፡ አንደኛዋ ሠራተኛ እማማ ወለተሩፋኤልማ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ እኔ ግን ገና ከልጅነቴ ጀምሮ አልወዳቸውም ነበር፡፡ ኣብሮ ከመኖር ብዛት የተነሣ
እናትና አባቴ እንደ "ገረድ አያዩዋቸውም፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
በሐሰት ተገንብቶ በተለበጠ አካባቢ ሁሉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ተገንጥሉ ልዩ ትክክለኛ አካባቢ ለመፍጠር ከፍ ያለ ችግር ያጋጥመዋል።ሁሉም በየበኩሉ የየራሱን የኑሮ ማሳ እያዳበረ በሚያርስበትና በሚያዘምርበት
ትክክለኛ ዓላማና ግብ ማምራት እንጂ፣ ይኸ እንዲህ ነው፣ ያኛው እንዲያ
አካባቢ፣ የራስን ዶማ እና መሣሪያ ይዞ በመቀላቀል ቀስ በቀስ ወደሚመኙት
ነው እያሉ መጃጃል ወደፊት መራመድ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ ነው:: ልክ
ያልሆነው ነገር ሁሉ ወለል ብሎ ቢታየኝም በግል ስክበው የሰነበትኩት
አስተሳሰብ ለጊዜውም ቢሆን በአካባቢዬ አሮጌ ልማድ ተዋጠ።
ባለሁበት ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ተርፎታል፣ ሞልቶታል፣ እየተባለ ነገር ግን ዝቅ ብሎ መታየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለምና የአካባቢን አስተያየትና ግምት ለመለወጥ ሲባል የሚደረግ ልዩ ልዩ ጥረት አንድም ፈጽሞ መውደቂያ ወይም ለጊዜው ቀጥ ብሎ መቆሚያ ሊሆን ይችላል፡፡ ግላዊ ስምና ክብርን ለመጠበቅና ለማስከበር ሲባል የሚደረግ የስግብግብነት ውጣ ውረድ ሁሉ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ የሥቃይ ሸክም ነው::
በግል ሀብት ጥሪት ፍላጎት የቆሰለና የበለዘ ሕሊናን ለማንጻትና ለማዳን የሚደረግ ጥረት መሪርና አድካሚ ነው:: ከቤተሰቦቼ የሚደርስብኝን ትችትና የወጪ ገቢ ሐሜት ለመከላከል ያህል የሕሊናዬን ዓላማ ቅንጣት ታህል ችላ ብዪ ሕይወት ኣልባ ተራ ስሜን ለማዳን ስል አንዲት የተለየች የሐሳብና የተግባር ዘመቻ ጀመርኩ። ሌሎችን ለመምሰልና ላይ ላዩን እኩል ሆኜ ለመታየት ስል አንዲት ባገልግሎት ላይ ከዋለች አራት ዓመት ያህል ያለፋት ቮልስዋገን መኪና ከስንት የደላላ ንትርክ በኋላ ገዛሁ፡፡ በክፍያው ላይ እኔና ጉልላት ተረባረብንበት፡፡ የጠንቃቃ ሰው ንብረት ስለ ነበረች በየጊዜው በመሰናከል አላስቸገረችኝም፡፡
ኑሮዬን መለስ ብዬ እያየሁ «የሕይወት ቀላል ፍቺ ይህች ትሆን? ወይስ ራስን የማታለያ ስሕተት» እያልኩ ማሰብ አዲሱ ልማዱ ሆነ፡፡ መስሎ መታየትና በጉራ ተኮፍሶ መወጣጠርን ከዚህም ከዚያም ቀሠምኩ፡፡ አንዳንድ ቀን ያን መበስበሱ እየታወቀ ቀለም እንደተቀባ ግንድ ላይ ላዩን ያሽበረቀ አስመሳይ ኑሮዬን መለስ ብዬ ሳየው ጎምዛዛ ኀዘን ይስማኝና በረጅሙ እተክዛለሁ። በሳምንት አንድና ሁለት ቀን እያመሽሁ መግባትና ሳይበዛም
መጠጥ መጎንጨትን ኣዘወተርኩ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከጧቱ ሁለት ሰዓት የወጣሁ ጥምብዝ ብዬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ገባሁ።
የወዲያነሽ ያጋጠማትን ያልታሰበ ችግር ችላ «አይ ጌትዩ! ስንቱን ለፈለፍከው ! መንጋት አበይለው ነጋ» አለችኝ ሰክሬ በገባሁ ማግሥት አብረን ቁርስ ስንበላ፡፡ ከዚያ በመጥፎ ልማዳዊ እምነት ተበክሎ ካደገው ልቦናዩ ምን አስነዋሪ ነገር ወጥቶ ይሆን በማለት በጣም ሠጋሁ፡፡ ከጎኔ ተነሥታ በስተጀርባዬ ቆመች፡፡ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ሁሉ ፊት ለፊቴ ባለው የቁም ሳጥን መስታዋት እመለከት ነበር። እሷም ይህችኑ ብልሃቴን ደርሳበት ኖሮ በመስተዋቲቱ ውስጥ ስታየኝ ዐይን ለዐይን ተጋጨን። የያዝኩትን
የእንቁላል ጥብስ ለመጉረስ አፈን ከፈት ላደርግ ሣቄ አመለጠኝና ተንከተከትኩ፡፡ እጄን ስባ ጎረሰችብኝ፡፡ 'ጌትዬ” አለችኝ ጉርሻዩን ቀምታ የልቧን ካደረሰች በኋላ፡፡ «ይኸው ዛሬ አምስተኛህ መሆኑ ነው መሰል ካንተ አላውቅምና ለምኑም ለምኑም ቢሆን ጥሩ አይደለም። ጌታነህ ሰክሮ እንዲህ አለ መባል ደግሞ አንዳች የሚያህል ነውር ነው። በዚያ ላይ ውርደቱ? ቅሌቱ... ጌትዬ አፈር ስበላልህ! ባንዲት እንጨት ስሔድ አትጠጣ፡ መቼም
ይኸን ጉድህን ጋሼ ጉልላት ኣልሰማም እንጂ ቢሰማማ....» ብላ አዘኔታና
ምክሯን አደባልቃ ከነገረችኝ በኋላ የተዳፈረችኝ ስለ መሰላት ሳይታወቃት
ትከሻዬን በግንባሯ ጠረግ ጠረግ እድርጋ ልትሸሽ ስትል እጅዋን ይዤ
አስቀረኋት፡፡
«ለመሆኑ ክፉ ነገር ተናገርኩ እንዴ? ሆድ ያባውን... የሚሉት ነገር ነበረበት?... አልኳት።
«የተናገርከው ሁሉ ምኑም አልገባኝ። እነዚያኑ ቤተሰቦችህን ስትሰድብና ስታጥላላ ነው ያደርከው:: እኔንም አይዞሽ በርቺ ድሉ ያንቺ ነው፤ ያባትሽ ስም አሸናፊ ነው እንቺም አሸናፊ ትሆኛለሽ እያልክ
ስታጫውተኝ አመሽህ» ብላ እጅዋን ነጥቃኝ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
የገዛ ስሕተቴን ለማስተባበል ሳይሆን ለማመኻንት ያህል ከጓዳ መለስ
እንዳለች «ትላንትም በል በል ብለው፣ አጠጥተውኝ ነው እንጂ ከእንግዲህ
ወዲህ መጠጥ በረበት ኣልዞርም» አልኳትና ወደ ሥራዬ ሄድኩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሌሊቱ አብዛኛውን ክፍል በሐሳብ ስገላበጥ አሳለፍኩት፡፡ እሑድ ጧት ከቁርስ በኋላ ሽር አልኩ። ሰበሰቡ ላይ ቆም ብዬ የወዲያነሽን ጠራኋት።
ከወደ ውስጥ ከተፍ አለች፡፡ የምትለውን ለመስማት ያህል 'አይቆርጡን አይፈልጡን ነይ እስኪ ወላጆቼ ቤት ይዤሽ ልሂድ? እኔ እያለሁ ምንም
እትሆኚ» አልኳት፡፡
ከልቤ ስለ መሰላት ክው ብላ ደነገጠች፡፡ «እንዲህ ንገረኝና ይለይልኝ
እንጂ! እጄን ይዘህ አስገድለኛ! እንኳንስ ካንተ ጋር አብሬ እዚያች ቤት
ገብቼላቸውና መንገድ ላይ ያዩን ይሆን እያልኩ አካላቴ ይበጠቃል። ምን
ቅብጥ ልጄ! ይልቅስ ሂድ ይቅናህ!» ብላ በእርሷ አስተሳሰብ የልቧን ተናግሬ
እንዳበቃች መንገድ ገባሁ፡፡ ጠምዛዛው መንገድ ከዐይኗ እስከ ሰወረኝ ድረስ
የአጥር ግቢውን በር ተደግፋ በዐይኖቿ ሸንችኝ፡፡ መኪናዬን ከቀበና ድልድይ
በላይ አቁሜ በእግር ቀጠልኩ። የወላጆቼን ቤት ከረገጥኩ ሦስት ወር ያህል አልፎኝ ስለ ነበር በዱሮው ዘበኛ በአቶ በየነ ምትክ ሌላ ሰው ተቀጥረዋል።
አጠር ብለው ከወደ ዐይናቸው ላም ያሉ ጸጉረ ገብስማ ሽማግሌ ናቸው::
አያውቁኝም። ለመግባት ፍቃድ ጠየቅሁ። ደረታቸውን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥተው
ማንን ነው የምትፈልገው? ጌቶችና አሜቴ እንደሁ ቤተስኪያን ሊስሙ እንደ
ኤዱ አልተመለሱም፡፡ ቆየት ብለህ ተመልሰሀ ናና ነግሬልህ ትገባለህ» ብለው ፊታቸውን አዙረው ችላ አሉኝ፡፡ ቸልታቸው ስላበሳጨኝ ልጃቸውስ የለችም
እንዴ? እሷም ካለች ያው ነው» ብዬ ጠየቅኋቸው፡፡ በጥፊ የመታኋቸው ያህል
ብው ብለው ተናደዱ፡፡ «እንዴ! እንዴ! መች አበድኩና! አንተ ስለ እኔ
እንጀራ ምንቸገረህ! የዋዛ ቤት መስሎሃል! እዚች ቦታም አያውሉኝ!» አሉና ነገሩኝ፡፡ ቀባጥሬም ሆነ ማንነቴን አስረድቼ መግባት ስላልፈለግሁ ደጅ ደጁን እያልኩ ለመቆየት ወሰንኩ፡፡ በዚያው አካባቢ መለስ ቀለስ ስል የውብነሽ ባዘቶ የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሳ ስትመጣ አየኋት።አመጣጧ በእኔው ኣቅጣጫ ስለ ነበር ቆሜ ጠበቅኋት። ከሩቅ የጀመረው ፈገግታዋ አጠገቤ ስትደርስ ተራውን ለውብ ጥርሶቿ ለቀቀ፡፡ ከጋቢው ሥር እጅዋን ብቅ አድርጋ ጨበጠችኝ፡፡ ስሜቷን ለመሸንገል ያህል ሳምኳት፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ሽማግሌው ኣጠገብ ደረስን፡፡ ቀና ብለው ከእግር እስከ ራሴ አዩኝ። ይኸ ደግሞ የማን ነው? በሚል አስተያየት እየገረመሙኝ አልፈናቸው ገባን፡፡
በምድረ ግቢው ያሉት አበቦችና አትክልቶች በጣም ያማሩ መሰለኝ፡፡
ከየውብነሽ ጋር እያወራሁ ዐይኖቼ ካትክልቶቸ ላይ አልተነቀሉም፡፡ እነዚያ
ምን ጊዜም ሌላ መሄጂያና መግቢያ የሌላቸው የሚመስሉት ነባር ሠራተኞች
ናፍቆትን በሚገልጽ ፈገግታ እጅ ነሡኝ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ዛሬ የጌቶች
ልጅ ከየት መጡ?” እንደሚሉ ታወቀኝ፡፡ አንደኛዋ ሠራተኛ እማማ ወለተሩፋኤልማ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ እኔ ግን ገና ከልጅነቴ ጀምሮ አልወዳቸውም ነበር፡፡ ኣብሮ ከመኖር ብዛት የተነሣ
እናትና አባቴ እንደ "ገረድ አያዩዋቸውም፡፡
👍4