አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ለኀጥአን_የመጣ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#ክፍል_ሁለት

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


ከስዓታት በኋላ ማታሩ ጆንግ ደረስን ከ ጓደኞቻችን ገብሪላ፣ ካሎኮ እና ካሊሎ ጋር ተገናኘን። ምግብ ገዝተን ከበላን
በኋላ የተሰጣኦ ውድድር መለማመጃ ቦታውን ለማየት እቅድ ያዝን። በነ ካሊድ ቤት ጠባብ ክፍል ውስጥ ትንሽየ አልጋ ላይ አራታችን በአንድ ላይ ተደራርበን አደርን፡፡ በሚቀጥለው ቀን ጅንየር፣ታሎ እና እኔ ቤት ስንቆይ ሌሎቹ ትምህርት ቤት ሄዱ። እስከ ስምንት ስዐት ይቆያሉ ሰንል ቶሎ መጡ። ቶሊ “እንዴት ቶሎ መጣቹህ ?" ብሎ ጠየቃቸው።ገብሪላ አማጺዎች ከተማችን ሞግሚሞን ላይ ጥቃት መስንዝራቸውን ከመምህራን
እንደሰማ ነገረን :: ትምህርት ላልተወሰነ ጊዜ እንደተዘጋ ሲነግረን ደነገጥን እየሰራን የነበረውን አቆምን።

አማጺዎቹ ከስዓት በኋላ የማዕድን ቦታዎችን እንዳጠቁ ከመምህራን ሰማን። የጥይት እሩምታ ህዝቡን ወደ ተለያዩ አቅጣጫ በተነው:: አባቶች ስራቸውን ጥለው ቤታቸውን ለመጠበቅ መጡ። ቤተሰቦቻቸው የት እንደሄዱ አያውቁም።
እናቶች ልጆቻቸውን ፍለጋ እያለቀሱ ወደ ትምህርት ቤት፣ወንዞች እና የውሃ ጉድጓዶች ሮጡ። ልጆች ደግሞ በየ መንገዱ ቤተሰቦቻቸውን ይፈልጋሉ። ተኩሱ ሲባባስ ሰዎች መፈላለጉን
ትተው እግሬ አውጭኝ ሆነ! ከተማውን ለቀው ወጡ።

"መምህራን ይሄ ከተማ ቀጣይ እንደሆነ ነግረውኛል" አለ ገብሪላ ከተቀመጠበት እየተነሳ። ጅንየር ፣ታሉ እና እኔ ቦርሳችንን ይዘን ከሌሎች ጓደኞቻችን ጋር ወደ ባህር ዳርቻ ሄድን፡፡
ብዙ ሰዎች ከማዕድን ቦታዎች ወደ ባህር ዳርቻ ይተማሉ።አንዳንዶቹ የምናውቃቸው ሰዎች ነበሩ ነገር ግን ቤተሰቦቻችን
የት እንዳሉ ሊነግሩን አልቻሉም፡፡ ተኩሱ በጣም ድንገተኛ እና አስደንጋጭ ስለነበር ሁሉም የአካባቢው ሰው በድንገት እንደሽሽ ነበር ነገሩን።

ለሶስት ስዓታት ያህል ቤተሰቦቻችን ይመጣሉ ወይም ያሉበትን የሚያውቅ ሰው ይመጣል ብለን በጭንቀት በወንዙ
ዳርቻ ላይ ቆየን። ነገር ግን ምንም ወሬ የለም፡፡ የውሃ ሽታ ሆኑብን! ቀኑ አንዳች ጉድ ያላየ የተለመደ ቀን ይመስላል።
ፀሐይዋ በነጩ ጉም ላይ ትንሳፈፋለች፣ ወፎች በዛፎች ጣሪያ ላይ ሁነው ይዘምራሉ ዛፎችም በለሆሳስ ንፋስ ይወዛወዛሉ።
ማመን አልቻልኩም! ጦርነቱ በዚህ ፍጥነት ቤታችን ይደርሳል ብየ አልገመትኩም:: በፍጽም! ትናንት ከቤት ስንወጣ አማጺዎቹ ከኛ ቅርብ መሆናቸውን የሚያሳይ አንድም ምልክት
አልነበረም::

"ምንድን ነው የምናድርገው?" ሲል ገብሪላ ጠየቀ፡፡ ለተወሰነ ጊዜ ሁላችንም ዝም አልን። በኋላ ቶሊ "ወደ ቤት እንሂድ፤ ሳይመሽ ቤተሰቦቻችን እንፈልጋቸው" አለ፡፡ ጅንየር እና እኔ ራሳችንን በመነቅነቅ ስምምነታችንን ገለጸን፡፡

ከሶስት ቀናት በፊት አባቴን በዝግታ እየተራመደ ከስራ ሲመለስ አይቸዋልሁ:: ባርኔጣውን በእጆቹ መሐል ይዟል ፤
ረጂም ፊቱ በጋለ ፅሐይ ተመቶ በላብ ተጠምቋል:: በቤቱ ደጃፍ ላይ ነበርኩ:: ካየሁት ቆይቻልሁ። 'ምስጋና ለእንጀራ እናቴ በእኔና በሱ መሃል የነበረውን ግንኙነት አበላሽታዋለች። ያን ቀን
ግን አባቴ ወደ ቤቱ ደረጃ ሲደርስ ፈገግ ብሎ አየኝ። ፊቴን፣ መላ ሰውነቴን አትኩሮ ተመለከተ። የእንጀራ እናቴ ስትመጣ ፊቱን
አዞረ፤ ከዛ ወደ እሷ ተመላከተ። ትንሽ ቆይቶ ወደ ውስጥ ገባ። እንባየን ቋጥሬ ወደ ጁንየር ሮጥኩ። ወደ እናታችን ቤት
ለመሄድ ዝግጅት ላይ ነበርን። በፊት አባታችን የትምህርት ክፍያ በሚከፍልን ጊዜ እናታችንን ከባዕላት በተጨማሪ በየሳምንቱ እንጠይቃት ነበር፡፡ አሁን አባታችን አልከፍልም ስላለ ትምህርት
ቤት የለም ስለዚህ በየሁለት እና ሶስት ቀናት እንጠይቃታለን::

ያን ቀን ከስዓት በኋላ እናታችንን አስቤዛ እየገዛች ገበያ ቦታ አገኘናት:: ደክሟት ፊቷ ከስሉ ዳምኖ ነበር። እኛን ስታየን
ስታቅፈን ግን በቅጸበት ፊቷ በራ። ታናሽ ወንድማችን ኢብራሂም ትምህርት ቤት እንደሆነ እና ስንመለስ እንደምናገኘው
ነገረችን። እጃችንን ይዛ ወደ
ኢብራሂም ትምህርት ቤት መራመድ ጀመርን፡፡

እናታችንን ፊትዋን ወደ እኛ አዙራ "ይቅርታ ልጆች በቂ ገንዝብ ስለሌኝ ነው እናንተን ወደ ትምህርት ቤት ያልመለስኳችሁ። እየጣርኩ ነው።” አለች፡፡ ከዛ ትንሽ ቆይታ
”አባታችሁ እንዴት ነው?” ስትል ጠየቀች::

"ደህና ይመስላል፡፡ ዛሬ አይቸው ነበር።" አልኩ
ጅንየር ምንም አልተናገረም:: ዝም አለ።

እናቴ ጅንየርን ትኩር ብላ አይን አይኑን እያየች” አባትህ ጥሩ ሰው ነው፤ በጣም ይወድሃል። መጥፎ እንጀራ እናቶች
ስለሚገጥሙት ነው” አለች::

ትምህርት ቤት ስንደርስ ትንሹ ወንድሜ ኳስ እየተጫወተ ነበር፡፡ ስምንት አመቱ ነው:: ልክ ሲያየን እየሮጠ መጥቶ ተጠመጠብን፡፡ በቁመት በልጦኝ እንደሆነ ለማወቅ ከእኔ ጋር ለማነጻጸር ሞከረ፡፡ እናቴ ሳቀች:: የትንሹ ወንድሜ ትንሽ ክብ
ፊት በራች፡፡ ሁላችንም ወደ ቤት ሄድን። ትንሹ ወንድሜ እጁን ይዥ ስራመድ ስለ ትምህርት ቤት አወራኝ፤ ማታ ደግሞ
ኳስ ተጫወትን፡፡ እናቴ ሁሉን ነገሯዋን ለኢብራሂም ሰጥታለች፣
ብቻዋን እሱን ትንከባከባለች ። ኢብራሂም አንዳንዴ ስለ አባቱ እንደሚጠይቅ ነገረችን፡፡ አባቱን እንዲያይ የተወሰኑ ቀናቶች ወስዳዋለች። ሁለቱ ሲገናኙ አባቱ ኢብራሂምን ሲያቅፈው ስታይ
ግን ታለቅሳለች። ሁለቱም በጣም ደስተኛ ይሆናሉ ትላለች፡፡በሃሳብ ትወሰዳለች::

ከዛ ጥየቃ ሁለት ቀናት በኋላ ከቤት ወጣን። አሁን ማታሩ ጆንግ ባህር ዳርቻ ላይ ቁመናል። አባቴ ባርኔጣውን በእጆቹ ይዞ ከስራ በሩጫ ሲመለስ በአይነ ሕሊናየ ይታየኛል። እናቴም ስታለቅስ ወደ ትንሽ ወንድሜ ትምህርት ቤት ስትሮጥ በአይነ ህሊናየ ተመላለስ፡ የፍርሃት ስሜት ተቆጣጠረኝ፡፡

ጅንየር፣ታሎ እና እኔ ወደ ጀልባ ዘለን ገባን ፤ በድንገት ጀልባው ሲንቀሳቀስ ለጓደኞቻችን እጆቻችንን አውለበለብን።
ጀልባዋ ከማታሩ ጆንግ ይዛን ወጣች:: በወንዙ ሌላኛው ጫፍ ደርሰን መሬት ስንረግጥ ብዙ ብዙ ሰዎች ሸሽተው እየመጡ ነበር፡፡ መጓዝ ስንጀምር ነጠላ ጫማ ራሱዋ ላይ የተሽከመች ሴትዮ እኛን ሳታየን መናገር ጀመረች" የምትሄድበት ቦታ ብዙ ደም ፈሶበታል። መልካሙ መንፈስ እንኳ ሸሺቷል ”እያለች
አልፋን ሄደች:: በወንዙ ዳር ባለው ጫካ የብዙ ሴቶች ደምጽ ይሰማል። ” ጌታ ሆይ እርዳን” የልጆቻቸውን ስሞች ይጠራሉ፡
የሱፍ፣ጃቡ፣ ፎዳይ..." ልጆች ብቻቸውን ሲጓዙ ፤ በተቀደደ ልብስ አንዳንዶቹ ያለ ውስጥ ሱሪ ”እናቴ” ፣ ”አባቴ” እያሉ
ሲጣሩ ፤ ውሾችም በህዝቡ መሃል ሲሮጡ ፤ ባለቤታቸውን ሲፈልጉ ስናይ ፈራን :: የደም ስሬ ተገታተረ፡፡

ከስድስት ኪሎ ሜትር በኋላ ከአያቴ ሰፈር ካባቲ ደረስን፡፡
ኦና ሁኗል። ከሰፈሩ እስከ ማዶ ያለው ጫካ የተዘረጋው የሰዎች ዱካ ብቻ ይታያል።

ምሽቱ ሲቃረብ ግን ብዙ ሰዎች ከማዕድን ቦታ መምጣት ጀመሩ። የጠንቋዮች ፣ በጉዞ ወላጆቻቸውን በመፈለግ የደከሙ
ና የራባቸው ልጆች ለቅሶ የምሽት ወፎች እና የዶሮዎች ዝማሬ የተካው ይመስላል። በአያቴ ቤት ደጃፍ ተቀምጠን መጠበቅ ማዳመጥ ጀመርን።

ትክክል ነን ግን፧ ወደ ማግቦ መመለስ ጥሩ ሃሳብ ነው ትላላቹህ?” ሲል ጅንየር ጠየቀን። ከመመለሳችን በፊት ግን
ቮልስዋግን ጩህት ሲሰማ ሁሉም ሰው ወደ ጫካው መሮጥ ጀመሩ። እኛም መሮጥ ጀመርን ብዙም ግን አልራቅንም። ልቤ መታ፤ ትንፋሼ ጨመረ፡፡ መኪናው አያቴ ቤት ፊት ለ ፊት ቆመ። አሽከርካሪው አልታጠቀም። ከመኪናው ወጥቶ ደም
መትፋት ጀመረ። እጁ ደም በደም ሁኗል። መትፋቱን ሲያቆም ማልቀስ ጀመረ። አዋቂ ሰው እንደ ህጻን ልጅ ሲያለቅስ
ለመጀመሪያ ጊዜ
👍2
#ለኀጥአን_የመጣ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#ክፍል_ሶስት

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

የምታውቅ ይመስላል።

..ቀጥሎ በጥይት የተበሳሱ ወንዶች እና
ሴቶች መጡ፡፡ አንዳንዶቹ ሰዎች እንደ ቆሰሉ እንኳ አያውቁም ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ራሳቸውን ሳቱ ሌሎቹ ደግሞ አስታወኩ። አቅለሸለሸኝ ራሴም ዞረብኝ መሬት ሲሽከረከር ፤ የሰዎች ድምጸ ሩቅ ሁኖ ይሰማኛል።

በቀኑ መጨረሻ ያየነው ሌላው ጉዳት በጀርባዋ ህጻን ልጅ ያዘለች አንዲት ሴት ናት። ደም በልብሷ ከላይ እስከ ታች
ወርዶ በጀርባዋ መስመር ሰርቷል። ልጆዋ በጥይት ተመቶ ሙቷል። ቁማ ልጅዋን አውርዳ አስቀመጠቻት። በኋላ ወደ
ልጅዋ ቀርባ ወዘወዘቻት። በብዙ ስቃይ እና ድንጋጤ ውስጥ ስለነበረች አለቀሰች።

ጅኒየር፣ታሎ እና እኔ ተያየን ወደ ማታሩ ጆንግ መመለስ እንዳለብን ገባን። ማግቦ ከእንግዲህ ቤታችን እንደማይሆን ወላጆቻችንንም ከዛ ሊሆኑ እንደማይችሉ
ተገነዘብን፡፡ አንዳንድ የቆሰሉ ሰዎች ካባቲ ቀጣይ የአማጺዎች መዳረሻ እንደሚሆን ይናገራሉ። አማጺዎች እንዲያገኙን
አንፈልግም:: በደንብ መራመድ እንኳ ማይችሉ ሰዎች ከካባቲ ለመውጣት የቻሉትን ሁሉ እያረጉ ነው:: ወደ ማታሩ ጆንግ ስንመለስ የዛች ሴትዮዎ እና የልጅዋ ሁኔታ አእምሮየን አስጨነቅው:: ጉዞው ብዙም አልተሰማኝም። ውሃ ጠምቶኝ ጠጥቼ እንኳ ምንም ጥሩ ስሜት ሊሰማኝ አልቻለም፡፡ ያቺ ሴት
ወደመጣችበት መመለስ አልፈልግም ፤ ሁሉም ነገር እንደጠፋ የልጅዋ አይን ይናገራል።
"አንተ ነጌትቭ አስራ ዘጠኝ አመትህ ነው” ይለኝ ነበር ባባ።አባቴ ከ ነጻነት በኋላ በ1961 የሴራሊዎን ሕይወት ምን
እንደምትመስል ስጠይቀው ሁሌም መልሱ ይሄ ነበር፡፡ ምኑ ይገባሃል የሚል ምፀት ያለው መልስ! ከ1808 ዓ/ም ጀምሮ ሴራሊዮን የብሪታንያ ግዛት ነበረች::

ሚልተን ማርጋይ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስቴር በመሆን የሴራሊዮንን ህዝብ ከዚህ አለም በሞት እስከ አረፈበት 1964 ድረስ ሃገሪቱን መርቷል::
ወንድሙ አልበርት ማርጋይ እሱን ተከትሎ እስከ 1967 ማለትም በሲያካ ስቲቨን በምርጫ እስከ ተሸነፍበት ደረስ መምራት ቻለ፡፡ ሲያካ ስቲቨን ወዲያው መፈንቅለ መንግስት ቢያጋጥመውም በ1968 እንደገና ወደ ስልጣን ተመለሰ። ከብዙ
አመታት በኋላ ሃገሪቱ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሃገር እንደሆነች አወጀ:: የሁሉም ህዝቦች ኮንግረስም የሃገሪቱ ብቸኛው ህጋዊ
ፓርቲ ሆነ። የ”ፖለቲካው መበላሸት የሚጀመረው ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነው ይል ነበር አባቴ።ስለዚህ ጦርነቱ ምን እያለ ይሆን?! አዋቂዎች አቢዮታዊ ጦርነት እንደሆነ እና ህዝቡን ከሙሰኛ
መንግስት ነጻ ለማውጣት የ ሚደረግ ጦርነት እንደሆነ ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ የትኛው የነጻነት እንቅስቃሴ ነው ንጹሃንን ህጻናትን የሚገድል? ይህንን የሚመልስ ማንም የለም::ባየሁት ነገር ልቤን ይከብድዋል ያስጨንቀኛል!
የሚታየውን ተራራ ዱሩን ሁሉ ፈራሁ።

በጣም ከመሽ ማታሩ ጆንግ ደረስኩ፡፡ ጅኒየር ና ታሎ ያየነው አስከፊና አስቃቂ ክስተት በሙሉ ለጓደኞቻችንን ነገሩዋቸው። እኔ ግን ያየሁትን ማመን ስላልቻልኩ ዝምታን መረጥኩ። ማታ ማንቀላፋት ስጀምር በህልሜ ጎኔን በጥይት ተመትቼ ቆስዬ ሰዋች ምንም ሳይረዱኝ የራሳቸውን ህይወት ለማትረፍ አልፈውኝ ሲሮጡ አየሁ።

ተንፏቅቄ ወደ ዱር ለመግባት ስሞክር ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ሰው ራሴ ላይ መሳሪያ ደቅኗል። ተኮሰ፡፡ባትቼ ከእንቅልፌ ተነሳሁ፡፡በጥርጣሬ ጎኔን ነካሁ። ፈራሁ! ህልም እና እውነታን መለየት ስላቃተኝ ፈራሁ።

ሁሌም ጥዋት ጎህ ሲቀድ ስለ ቤተሰቦቻችን ወሬ ካለ ለመስማት ወደ ማታሩ ጆንግ ባህር ዳርቻ እንወርዳለን።
ከሳምንት በኋላ ወደ ማታሩ ጆንግ የሚመጡ ስደተኞች ቁጥር ቀነሰ። ስለ ቤተሰቦቻችን ምንም ወሬ የለም። ድጋሚ የውሃ ሽታ ሆኑብን! የመንግስት ወታደሮች በማታሩ ጆንግ ተሰማርተው ኬላዎችን በባህር ዳርቻ እና በከተማው ዋና ዋና አቅጣጫዎች አቁመዋል::

ወታደሮቹ ከባድ መሳሪያዎችን አዘጋጅተው አማጺዎቹን ለመምታት ይጠባበቃሉ። አማጺዎቹ በባህር ዳርቻው በኩል እንደሚመጡ ገምተዋል። ህዝቡ በጊዜ እንዲገባ የስዓት እላፊ ከምሽቱ አንድ ስዐት በኋላ መንግስት አውጇል። ከባድ ምሽት ነበር፤ መተኛት አልቻልንም:: ሁላችንም በጊዜ ተሰባሰብን ከበን
ማውራት ጀመርን፡፡

ይሄ ነገር፦ ይሄ እብደት መቼ ይሆን የሚያበቃው? "በጥቂት ጊዜ ውስጥ የሚያበቃም አይመስለኝም፡፡" አለ ጅኒ የር ”ምን አልባት ለአንድ ና ሁለት ወር ይቆይ ይሆናል።” አለ ታሎ ጣሪያ ጣሪያ እያየ።

ገብሪላ ደግሞ ወታደሮች አመጺዎችን ከማዕድን ቦታ ለማባረር እየገሰገሱ እንደሆነ ሰምቻለሁ አለ። ጦርነቱ ወደ
የፍጻሜው ምዕራፍ ላይ እንዳለ እና ከሶስት ወር በላይ እንደማይቆይ ተማመን፡፡
ጅኒየር፣ታሎ እና እኔ ነገሮችን ለመርሳት ራፕ ሙዚቃ ማደመጥ ጀመርን፡፡ የ ሙዚቃ ካሴቶች እና ልብሶቻችንን ብቻ
ይዘን ነበር ከቤት የወጣነው:: ከቤት ደጃፍ ላይ ተቀምጨ Now That We Found Love ” ፍቅርን አሁን አገኘነው” የሚለውን የሄንሪ ዲ እና ዘ ቦይዝ ሳዳምጥ ትዝ አለኝ ። አይኔን ጨፈንኩ። ካባቲ ያየሁዋቸው አሰቃቂ ነገሮች ሁሉ
በአዕምሮዬ መጡ። ምስሎቹን ከአዕምሮዬ ለማውጣት የድሮውን
በሰላሙን ጊዜ የነበረችውን ካባቲ ማሰብ ጀመርኩ።

በአያቴ መንደር ባንድ በኩል ጥቅጥቅ ያለ ደን ሲኖር በሌላው ደግሞ የቡና እርሻ ነበር፡፡ በጫካው በኩል የሚመጣው ወንዝ ሰፈሩ ዳር፣ በወይራ ዛፎች አደርጎ ወደ ረግረጉ ይገባል። ከረግረጉ በላይ የሙዝ ማሳው እስከዛኛው አድማስ ይታያል። ብዙ ሰው ከቤቱ ጀርባ የማንጎ ዛፎች አለው።

ጥዋት ከጫካው በስተጀርባ ፅሐይ ትወጣለች። መጀመሪያ ጨረሯ በቅጠሎች መሃል ያልፋል። ከዛ አውራ ደሮ ይጮሃል፤ ድንቢጥ ወፎች በዝማሬ አዲስ ቀንን ሲያውጁ ወርቃማ ፅሐይ
ከጫካው ራስ ላይ ጉብ ብላ ትታያለች። ምሽት ላይ ዝንጀሮዎች ወደ ማደሪያቸው ለመመለስ ከዛፍ ዛፍ ሲዘሉ ይታያል። በቡናው ማሳ ደሮዎች ጫጩቶቻቸውን ከጭልፊት ይሸሽጋሉ። ከማሳው
ወዲያ ማዶ ደግሞ የወይን ዛፎች በንፋስ ሲወዛወዙ ይታያል።
አንዳንዴ የወይን ፍሬ ለቃሚ ዛፎች ላይ ወጥቶ ይታያል።
ምሽቱ በዛፎች ውዝዋዜ ድምጽ ( ቀ ቀ ቀ ቀ ) እና በሩዝ መውቀጥ ድምጽ (ድው ዱ ዱ) ታጂቦ ይገባደዳል። ድምጹ በመንደሩ ያስተጋባል። ወፎች በጥንቃቄ እንዲበሩ፣ ዶሮዎች፣እንቁራሪቶች ጉጉቶችም ወደ ማደሪያቸው እንዲመለሱ ያደርጋል። የመንደር ሰዎች ፋኖስ ወይም የተቀጣጣለ እንጨት እያበሩ ከ እርሻ ማሳቸው ይመለሳሉ፡፡

"እንደ ጨረቃ ለመሆን እንትጋ” ይላል አንድ ሽማግሌ ሰውየ ውሃ ሲቀዳ፣ ለአደን ሲሄድ ወይም የወይን ፍሬ ዛፎቹ ላይ ሲቆርጥ። አንድ ቀን አያቴን ምን ማለት እንደሆነ ጠየኳት። አባባሉ ሰዎች ሁሌም ጥሩ እንዲሆኑ እና ለሌሎች መልካም እንዲሆኑ ያስታውሳል። ስዎች የፅሐይን ግለት ፤ ከባድ ዝናብን እና ብርድን ያማርራሉ። ነገር ግን ጨረቃ ስትወጣ
ማንም አያጉረመርምም፡፡ ሁሉም ደስተኛ ነው፤ እንደየራሳቸው ሁኔታ ጨረቃን ያደንቃሉ። ህጻናት ጥላቸውን ያያሉ፤ ሰዎች ተሰባስበው ይጫወታሉ ለሊቱን በጭፈራ ያሳልፋሉ። ጨረቃዋ
ስታበራ ደስታ ይሆናል። ለዛ ነው እንደ ጨረቃ ለመሆን የምንተጋው።
።።
አየሩ ደም ደም እና የተቃጠለ ስጋ በሚሸትበት ከተማ መሐል የዛገ ካሬታ እየገፋሁ ነበር። : ንፋሱ የሲቃ ድምጾችን ያመጣል::
ተመሰቃቅለው በወደቁ ሬሳዎች መካከል ሳልፍ እጃቸውን እና እግራቸውን ያጡ ሰዎች፤ ሆዳቸው ውስጥ ቅልሃ ገብቶ
አንጀታቸው የተዘረገፈ እና በአፍንጫቸው በጆሮቻቸው ደም የፈሰሳቸውን አየሁ። በራሪዎች
👍2🥰1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አራት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ



#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


እንደርስበታለን ብለን ከገመትነው ስዓት በፊት ማታሩ ጆንግ ደረሰን፡፡ ስለ ቤተሰቦቻችን ምንም ዜና የለም። በተስፋ ከመጠበቅ እና ደህንነታቸውን ከመመኘት ውጪ ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም::

አማጺዎች ከ ማታሩ ጆንግ ሃያ ኪሎ ሜትር እና ከዛ በላይ በምትርቀው ሱምብያ ከተማ መሰፈራቸውን ሰማን። ቀጥሎ አማጺዎች ደብዳቤ እንደላኩና ደብዳቤው የነሱም መምጣት፤ ስለ
እኛ እየታገሉ እንደሆነ እና የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እንደሚፈልጉ ያትታል። መልዕክተኛው ወጣት ነው፡፡ ሰውነቱ ላይ የአማጺዎችን ስም እና አጸርሆተ ቃል ማለትም (አአግ
አብዮታዊ የአንድነት ግንባርን ተነቅሷል። ከአውራ ጣቱ ውጪ ሁሉንም ጣቶቹን ቆርጠውበታል። አውራ ጣት በብዙ ሰወች
የተለመደ የፍቅር ምልክት ነበር።

መልዕክቱ እንደደረስ ሰዎች ወደ ጫካ መሸሸግ ጀመሩ። የካሊሎ ቤተሰብ ግን እንድንቆይ እና ስንቅ ይዘን እነሱን
እንድንከተል ጠየቁን። ቆየን፡፡
ያ ምሽት በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ የከተማን ህይወት የሚሰጠው የሰዎች መኖር እና መንፈሳቸው እንደሆነ ተረዳሁ። የሰዎች አለመኖር ከተማውን አስፈሪ አደረገው። ድቅድቅ ጨለማ እና ከባድ ጸጥታ! የዶሮዎች እና የወፎች ዝማሬ
እንኳ የለም። ጨለማ ፈጥኖ መጣ፤ ጨረቃም የለችም። አየሩ ከብዷል፡፡ ተፈጥሮ ራሷ የሚመጣውን የፈራች ትመስላለች።

ሰዎች ለሳምንት ያህል ተሸሸጉ። አማጺዎች ግን አልመጡም።በኋላ ሌላ መልዕክተኛ ላኩ፡፡ መልዕክተኛው ታዋቂ የካቶሊክ ካህነ ነበር፡፡ ከማስፈራራት ውጪ ካህኑን ምንም አላደረጉትም።
ቃሉን ተቀብሎ ህዝቡ ወደ ጫካ ተመልሶ ገባ። አስር ቀናት አለፉ አማጺዎች ግን አልመጡም፡፡ ነዋሪው ወደ ከተማ መመለስ ጀመረ። ትምህርት ቤቶች ተከፈቱ፤ ሰዎች ወደ ዕለት ተዕለት
ኑሯቸው ተመለሱ፡፡ አምስት ቀናት በሰላም አለፉ፡፡

በመጨረሻ አማጺዎች ሲመጡ ቀላል የተኩስ ድምጽ ሰማን፡፡
ጅኒ የር፣ታሉ፣ ካሎኮ፣ ገብሬላ፣ ካሊሎ እና እኔ ቤት ውስጥ ነበረን
"ሰማቹህ?” ብለው ጠየቁ። ወታደሮች ናቸው የተኮሱት ወይስ ሌላ አካል እያልን በማሰብ ደርቀን ቆምን።
ከደቂቃዎች በኋላ ሶስት ጊዜ ተተኮሰ። አሁን ሁላችንም ፈራን።ከተማው ጸጥ ረጭ አለ። ተኩሱ ሲቀጥል። ሁሉም ተደናገጠ።በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ ሰዎች መጮህ እና ወደ ተለያዩ
አቅጣጫዎች መሮጥ ጀመሩ። ሰዎች ተገፋፉ፣ አንዱ በአንዱ ላይ ወደቀ የወደቁ ሰዎችን ረግጦ ያልፋል። እናቶች ልጆቻቸውን አጡ፤ ቤተሰብ ተለያየ፤ የከተማው ነዋሪዎች ለዘመናት
የለፉበትን ጥሪት ትተው ሮጡ። ልቤ በፍጥነት ይመታል።

ወደ ማታሩ ጆንግ ለመግባት ሁለት መንገዶች አሉ።የመኪና መንገድ እና በወንዙ በማቋረጥ :: አማጺዎች ግን በየብስ በኩል እያጠቁ ሲገሰገሱ ሰዎች ወደ ወንዝ እንዲሮጡ ተገደዱ። ብዙ
ሰዎች በፍርሃት ወንዝ ውስጥ ገቡ። እስኪደክማቸው ድረስ ዋኙ:: ወታደሮቹ በቁጥር መበለጣቸውን ሲያውቁ ቀድመው ነበር ከተማውን ለቀው የወጡት :: ህዝብ ሁሉ የተመመበት
አንድ ማምለጫ መንገድ ብቻ ነበር፡፡ ተከተልናቸው። መንገዱ ጭቃ ነበር፡፡ ጭቃ የያዛቸውን አካል ጉደተኞች ማንም
አልረደቸውም፡፡ ማንም ሊረደቸው የሚፈልግ የራሱን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላል፡፡ አማጺዎቹ ወደ ሰው መተኮስ ጀመሩ። ሰው ከተማውን ለቆ እንዲወጣ አልፈለጉም። ነዋሪውን በተለይ
ሴቶችን እና ህጻናትን ምሽግ በማድረግ ከመከላከያ ጥቃት መዳን ይፈልጋሉ፡፡
እንደምንም ግን ወደ ማምለጫው መንገድ ስንዳረስ አማጺዎች ቀጥታ ወደ እኛ መተኮስ ጀመሩ። ሁሉንም የመሳሪያ አይነቶች ተጠቀሙ።ጥይት አዘነቡ፤ ሮኬት ና መትረየስ ተኮሱ ቦምብ ወረወሩ። እኛ ምንም አላመነታነም:: መያዝ የከፋ እንደሚሆን እናውቃለን፡፡ ከተያዝን እንመለመላለን : በጋለ ጩቤ አእግ
ብለው ደስ ያላቸው ቦታ ላይ ይጻፉብናል። ስለዚህ ማምለጥ ግድ ነው። ብዙ ኪሎ ሜትሮችን ሳናርፍ በፍጥነት ሮጥን::
አማጺዎች ተስፋ ቆርጠው ወደ ማታሩ ጆንግ ተመለሱ። እኛ ግን መሮጣችንን ቀጠልን፡፡

ለብዙ ቀናት ስድስታችን ጅኒየር ታሎ ካሎኮ፣ ገብሬላ፣ ካሊ እና እኔ በቀጭን መንገድ ጥቅጥቅ ባለ ጫካ መሃል ተጓዝን፡፡ሁላችንም ሃሳብ ላይ እንመስላለን። ማውራት የለም፤ መሄድ
ብቻ:: ስለ ቤተሰቦቼ ደግሜ ላያቸው እችላለሁ ብየ አሰብኩ፡፡ማልቀስ ፈለኩ በጣም ስለ ራበኝ ግን አቅም አልነበረኝም ::

በተተወ መንደር ውስጥ ባዶ መሬት ላይ ተኛን።በሚቀጥለው ቀን ሙዝ፣ብርቱካን እና ኮኮናት ዛፍ በሚገኝበት መንደር አለፍን፡፡ ሙዙ ጥሬ ስለሆነ ቀቅለን ነበር የበላነው። ከዛ ትንሽ ብርቱካን እና ኮኮናት በላን። በቂ ምግብ ግን ማግኘት
አልቻልንም። ከቀን ቀን ረሃባችን እየተባባሰ መጣ። ስለዚህ ወደ
ማታሩጆንግ ተደብቀን በመግባት ምግብ መግዣ ገንዘብ ማግኘት አለብን፡፡ ከዚህ ውጭ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበረንም።

በመንገዳችን ጸጥ ረጭ ባለ በተከዳ ከተማ ስናልፍ አስክሬን፣የተበላሸ ምግብ ፣ የእንጨት ስራዎች፣ ልብስ እና ሌሎች
እቃዎች በየቦታው ወድቆ አየን። አስክሬን ተቆራርጦ እጅ፣ እግር እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች በየቦታው ወድቋል። ይሄን ሳይ አዞረኝ፤ አቅለሸለሸኝ። የነ ካሊሎ ቤት በከተማ እንዳሉ ሌሎች
ቤቶች በሩ ተሰብሯል ተቃጥሏል። የጥይት ቀዳዳ በበሩ በኩል ሲታይ ስታር ቢራ እና ሲጋራ መጠቅለያ ደግሞ ድጃፍ ላይ ወድቋል።

ገንዘቡን ባስቀመጥኩት ቦታ ሳይነካ አገኘሁት። ገንዘቡን ካልሴ ውስጥ ከትቼ ወደ ረግረጉ ወረድን፡፡ አማጺዎች ባህር ዳርቻው አካባቢ ማማ ላይ ወጥተው ይጠብቁ ስለነበር መንፏቀቅ ነበረብን፡፡ ከመካከላችን አንድ ልጅ ትልቅ ቦርሳ አንግቶ ስለነበር ጠባቂዎች አይትውት ተኩስ ከፈቱ።ከጠባቂዎች እስክንርቅ
ድረስ በፍጥነት ሮጥን።አመሻሽ ላይ ብዙ ሰዎች ያሉበት መንደር ውስጥ ገባን፡፡
ገንዘብ ስለያዝን ምግብ ይሸጡልናል የሚል ተስፋ ነበረን።

ነገር ግን አንዳንዶቹ ለክፉ ጊዜ ምግብ መቆጠብ ስለምንፈልግ አንሸጥም ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ ያለ ምንም ምክንያት አንሸጥም አሉ። ራሳችንን ወቀስን፡፡ የጦርነት ወቅት እንዲህ ተለዋዋጭ
ነው። ማንም አይቆጣጠረውም፡፡ ነገሮችን በፍጥነት መረዳትና
የመትረፌያ መንገዶችን መቀየስ ነበረብን። ያን ምሽት አማራጭ
ስላልነበረን ሰዎች ወደ መኝታ ሲሄዱ ምግብ ሰርቀን በላን::

ምግብ እና ውሃ ሳናገኝ ብዙ ስለቆየን
ጉሮራችን ተንቃቃ፣ ሆድ ቁርጠትም ተሰማን። ከንፈራችን ተጣበቀ መገጣጠሚያችንም ዝሏል። ምግብ የት እንደምናገኝ ግራ ገባን። በመጨረሻ ረሃብ ወደ ማታሩ ጆንግ እንደገና
መለሰን።

የበጋ ወቅት ስለ ነበር ሳር ቅጠሉ ቢጫ ሁኗል። በሳር መሃል እየሄድን ድንገት አማጺዎች መጡብን። ገብሬላ ላይ ሽጉጥ ደቀኑ፤ እኔ ላይ ደግሞ ጩቤ ሰነዘሩ፡ "ደንግጧል" ብሎ ከት ብሎ
ሳቀ፡፡ አልፈን ወደመጣንበት መንደር መለሱን፡፡ አማጺዎቹ እጅጌ ጉርድ ቲሽርት፣ ጂንስ ጃኬት እና ሱሪ ለብሰዋል እና አዲዳስ ጫማም ተጫምተዋል። እጃቸው ላይ ውድ ስዐቶች አስረዋል።
ሁሉም በጉልበት የተቀሙ ወይም የተዘረፍ ናቸው።

ፈራሁ! እጆቼ እና እግሬዎቼ ተንቀጠቀጡ።አማጺዎች ትንሽም እንኳ ለመንቀሳቀስ ከሞከርን እንደሚገሉን ዝተዋል።ከጓደኞቼ እንዱ ወይም ወንድሜ ቢንቀሰቀስ ለማምለጥ ቢሞክርና ቢገሉንስ ብየ ሰግቻለሁ።

በአቅራቢያው ወዳለ መንደር ስንደርስ የመንደሩን ነዎሪዎች ሴቶች ህጻናት ሳይሉ ሁሉንም አሰለፉ። መጀመሪያ ካሊሎ
ቀጥሎ እኔን እና ሌሎች ወንዶችን መረጠው ወደ ፊት እንድንመጣ አዘዙ።
"ጠንካራ ወታደሮችን እንፈልጋለን” በማለት ጅኒየር
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አምስት


#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ


#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


በቡድን መሆናችን እንድንተጋገዝ እና ችግርን በጋራ እንድናልፍ ቢረዳንም ሰዎች እኛን ሲያዩ ይፈሩ ጀመር። በእኛ
እድሜ ያሉ ታዳጊዎች በአማጺዎች ተገደው ይገድሉ ያቆስሉ ነበር። ስለዚህ ሰዎች ቤተሰቦቻቸውን ለመጠበቅ ሲሉ እኛን ለመጉዳት ጥረዋል። እኛም ጥግጥጉን ይዘን መንደሮችን ማለፍ
ጀመርን። የጦርነት አንዱ መዘዝ ይሄ ነው። ሁሉም ሰው መተማመን ያቆማል፣ ጸጉረ ልውጥ ሰው በሙሉ እንደጠላት
ይቆጠራል። የሚያውቁህ ሰዋች እንኳ ሲያቀርቡህ ሲያወሩህ በጥንቃቄ ነው::

በአንድ መንደር ስናልፍ ገብሬላን የምታውቅ ሴትዮ አክስቱ ወደ ሰላሳ ኪሎሜትር የምትርቅ መንደር ውስጥ እንዳለች ነገረችው: አቅጣጫውን ጠቁማን ጉዞ ጀመርን።

የአዝመራ ወቅት እየተቃረበ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ዝናብ ዘንቧል መሬቱ ረስርሷል፡፡ ወፎች በማንጎ ዛፍ ላይ ቤታቸውን ይሰራሉ፡፡ ጠዋት ጠዋት ጤዛ ይታይ ነበር። አጎቴ በዚህ ወቅት
ነው መሞት ምፈልገው እያለ ይቀልድ ነበር። ፀሐይ ቀድማ ወጥታ በሰማያዊው ሰማይ ላይ ትታያለች።

የካማቶር ነዎሪዎች ሁሉም ገበሬ ናቸው። ማገዝ የግድ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከግብርና ጋር ተገናኘን። የመጀመሪያ
ስራችን የነበረው ማሳ ማጽዳት ነበር፡፡ ቅጠላቸው የተቆላለፈ የወይን ዛፎችን መቁረጥ በጣም አስቸጋሪ ነበር። ሶስት ስዓት የሚፈጀውን ሶስት ቀን ቆየንበት።
ከዛ ዘራን።

ለሶስት ወራት ያህል በካማቶር በእርሻ ስራ ላይ ብንቆይም ልለምደው አልቻልኩም። የተመቸኝ ከስዐት እረፍት ላይ ለዋና ወደ ወንዝ የምንወርድበት ጊዜ ብቻ ነበር። ስራው ለፍቶ መና
ነበር። ምክንያቱም አማጺዎች ሲመጡ ትተነው እንሮጣለን ሰብሉ በአረም ይዋጣል ወይም እንስሳት ይበላል::
አንድ የአማጺዎች ጥቃት ግን ይባስ ብሎ ከወንድሜ ጋር አለያየኝ። ትልቅ ወንድሜን ጅኒ የርን ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት
ያን ጊዜ ነበር።

ጥቃቱ የደረሰው በአንድ ለሊት ድንገት ነበር። ስለ አማጺዎች መድረስ ምንም ወሬ አልተሰማም :: ከየት መጡ ሳይባል
መንደራችን ገቡ።

ከምሽቱ ሁለት ስዐት አካባቢ ህዝቡ የቀኑን የመጨረሻ ጸሎት እያደረገ ነበር። ኢማሙ ብዙ እንደሚቆይ ይታወቃል፡፡ በህዝቡ ፊት ለፊት ሁኖ ረዥም የሱራ ጸሎት ያደርሳል። የአማጺዎችን
መግባት ሲሰማ ከኢማሙ በስተቀር ሁሉም መስጊዱን ጥሎ ሄደ። አማጺዎች ኢማሙን ብቻውን አግንተው ህዝቡ በየት
በኩል እንደሄደ ጠየቁት፡፡አልመለሰላቸውም፡፡ እጁን እና እግሩን
አስረው አቃጠሉት።

የአማጺዎች ጥቃት ሲጀምር ጅኒ የር እና ጓደኞቼ ቤት ውስጥ ነበሩ። እኔ ግን ደጃፍላይ ነበርኩ። ድንገት ተኩስ ሲጀምር
ፌቴን ሳላዞር ሩጬ ጫካ ውስጥ ገባሁ።አንድ ዛፍ ስር ብቻየን
አደርኩ። ሲነጋ ካሎኮን አገኘሁት። መንደሩ መሃል ላይ የኢማሙ የተቃጠለ አስክሬን ተጥሏል፤ ቤቶች ተቃጥለዋል
ህይወት የሚባል የለም:: በጥቅጥቁ ደን መኋል ጅኒ የር እና ጓደኞቻችንን ፈለግን
ግን ልናገኛቸው አልቻልንም።
የምናውቃቸው ሰዎች አግኝተን ለሁለት ሳምንታት ያህል ከነሱ ጋር በረግረጉ አካባቢ ተደበቅን። ሁለት ሳምንት ሁለት ወር ሆነብኝ፡፡ ስለእነ ጅኒየር አስባለሁ። አምልጠው ይሆን? ሁሉንም እያጣሁ ነው፦ቤተሰቦቼን፣ጓደኞቼን። በፍርሃት ውስጥ መኖር ሰለቸኝ:: ሞትን የምጠብቅ መስሎ ተሰማኝ። መንደሩ መልቀቅ ሰላም ወደ ሚገኝበት መሄድ እንዳለብኝ ተሰማኝ:: ቆረጥኩ። ካሎኮ ግን ፈራ፤ በረግረጉ መቆየትን መረጠ።

ጠዋት ሁሉንም ተሰናብቼ ወደ ምዕራብ መጓዝ ጀመርኩ።በኪሴ ከያዝኩት ያልበሰለ ብርቱካን ውጭ ሌላ ምንም
አልያዝኩም:: ለስድስት ቀናት ያገኘሁትን እየበላሁ ተጓዝኩ።
በስድስተኛው ቀን ሰው አገኘሁ፡፡ የአንድ ቤተሰብ አባላት እየዋኙ ነበር። ሰላምታ ሰጠኋቸው፡፡ አልመለሱልኝም። ልብሴን አውልቄ ወደ ወንዙ ገባሁ፡፡ " ከየት ነው የመጣሃው ወዴት እየሄድክ ነው?” ሲል ጠየቀኝ።
ከማታሩ ጆንግ ነኝ ወዴት እንደምሄድ ግን አላውቅም” ስል መለስኩለት። ቀጥየ "ወደ ቦንቴ ለመሄድ አቋራጩ መንገድ የቱ
ነው” ስል ጠየቁ፡፡ ቦንቴ ስላማዊ ቦታ ነው ይባላል። በባህሩ በኩል እንድሄድ እና ሰዎችን እንድጠይቅ ነገረኝ።

ብዙ የተቃጠሉ መንደሮችን እያለፍኩ ተጓዝኩ፡፡ በመንደሮቹ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሰዎች ከአዋቂ እስከ ህጻናት አየሁ።አይናቼን ለመጨፈን ሞከርኩ ግን አልቻልኩም። በመጨረሻ ደነዘዝኩ።

ብዙ ስጓዝ ውየ ራሴን ጥቅጥቅ ያለ ጫካ መሃል አገኘሁት።ከቆምኩበት ጫካ
ሰማዩን እንዳላይ በረጃጂም ዛፎች
ቅርንጫፎች እና ቅጠሎች ተጋርድዋል፡ እንዴት እዚህ ጫካ እንደገባሁ እንኳ አላውቅም። ለሊቱ ሲቃረብ ረጂም ቅርንጫፍ ካለው አንድ ዛፍ ላይ ወጥቼ አደርኩ።

በሚቀጥለው ቀን ከጫካው ለመውጣት ወሰንኩ። በጉዞየ በአንድ ትልቅ አለት ላይ የሚወርድ ፏፏቴ አየሁ። በዳርቻው
ትንሽ ለማረፍ ወሰንኩ። ግን ብዙም አልቆየሁም። ወደ ሃሳብ ከምገባ ብየ ጉዞየን ቀጠልኩ። ቀኑን ሙሉ ተጓዝኩ። ዙሬ ዙሬ በመጨረሻ ራሴን ትናንት ማታ ካደርኩብት እዛው ቦታ ላይ
አገኘሁት፡፡ እንደጠፋሁ አመንኩ። ስለዚህ ራሴን ማደላደል አዲሱ ቤቴን ማመቻቸት ጀመርኩ። ቅርንጫፎች ላይ ቅጠሎችን
ጨመርኩ።አካባቢውን ዙሬ ቃኘሁ። ምንም እንኳ ብጠፋ እና ብቻየን ብሆንም ለጊዜው ይሄ ቦታ ሰላማዊ ነው።
የፏፏቴው ጥግ ባልበሰሉ ፍራፍሬዎች ተሸፍኗል። አንዱን ቆርጬ በላሁ። መራራ ነው:: ነገር ግን ረሃብ ያስታግሳል።
ስለዚህ ወደ አስራ ሁለት የሚሆኑ ፍሬዎችን በላሁ። ከተወሰኑ ስዓታት በኋላ ገላየን ለመታጠብ አሰብኩ። ልብሴ ቋሽሽዋል፣የሰውነቴም ሽታ ተቀይሯል። መጀመሪያ በንጹህ ውሃ ቀጥሎ
በእንዶድ ገላየን ታጠብኩ ልብሴንም አጠብኩ።

አስቸጋሪው ነገር ብቸኝነት ነበር። ብቻህን ስትሆን ብዙ ታስባለህ ላቸማሰብ ሞከርኩ ግን አልቻልኩም፡፡ ወደ ጭንቅላቴ የሚመጡትን ሁሉንም ሃሳቦች ለመከላከል ወሰንኩ ብዙውን
ጊዜየን ሃሳብን በመዋጋት ማለትም ስለ ወደፊት ህይወቴ ማሰብ፡
ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ የት ናቸው የሚሉ ሃሳቦችን በመሸሽ አሳልፍ ነበር።
ይሄን ሳደርግ ራሴ ከመቼውም በላይ የጠነከረ መስለኝ። ሃሳቦቹ በህልሜ ይመጣሉ በማለት መተኛት ፈራሁ::

በጣም ትንሽ እያለሁ አባቴ የሚለው አባባል ነበር " በህይወት እስካለህ የተሻለ ቀን እንደሚመጣ እና መልካም ነገር እንደሚሆን ተስፋ አለ። እጣ ፈንታቸው መጥፎ የሆነ ደግ ጊዜ
የማይመጣለቸው ሰዎች ግን ይሞታሉ።”በጉዞየ ስለዚህ አባባል
አስብ ነበር፡፡ እነዚህ ቃላቶች ወደፊት እንድሄድ እንድገፋ አበረቱኝ፡፡

በረሃብ ደክሜ እያዘገምኩ ስሄድ በእኔ የእድሜ ክልል ያሉ ህጻናት አጋጠሙኝ። ስድስት ነበሩ፤ ከስድስቱ ሶስቱ አልሃጂ፣
ሙሳ እና ኬን ማታሩ ጆንግ በሚገኘው ሴንትያል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አብረውኝ ተምረዋል። እጃችንን በመጨባበጥ ሰላም ከተለዋወጥን በኋላ ወደየት እየሄዱ እንደሆነ ጠየቅኳቸው፡፡ በቦንቴ ወረዳ ወደ ምትገኝ የል ወደ ምትባል ሰፈር እየሄዱ እንደሆነ እና የል በ ሴራሌዮን መከላከያ ኃይል የሚጠበቅ
አስተማማኝ ሰላም ያለበት አካባቢ እንደሆነ ነገሩኝ። ተከተልኳቸው::

እንደገና የሰባት ህጻናት ቡድን፡፡ ሰዎች እኛን ሲያዩ ይጮሃሉ ይሮጣሉ። እንደአውሬዎች ተቆጠርን፡፡ ቦታ የሚያመለክተን አቅጣጫ የሚጠቁመን ሰው አልነበረም። ከስድስት ቀናት ጉዞ
በኋላ አንድ ሽማግሌ ሰው አገኘን። የመንደሩ ሰው እኛን ሲያይ ሩጦ እንደጠፋ እሱ ግን መሮጥ እንደማይችል ነገረን። ከየት እንደመጣን እና ወዴት መሄድ እንደምንፈልግ ነገርነው፡፡
ለተወሰኑ ቀናት ከእሱ ጋር
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ስድስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ


#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

የተጠጋጉ ጎጆ ቤቶችን ተመለከትን። ከመንደሩ ስንደርስ ማንም የለም። ከእኛ ተደብቀው ነበር። ብዙም ሳይቆይ አሳ አጥማጆች መጥረቢያ፣ ጦር እና መረብ ይዘው ወጡ። ምንም ማድረግ
አልቻልንም። ባለንበት ደርቀን ቆምን።
እንግዲያውስ "እባካችሁ እኛ ልንጎዳችሁ አልመጣንም፧ መንገደኞች ነን”ብለን ጮህን።አሳ አጥማጆች በሰደፍ መተው ጣሉን፡፡ ከበላያችን ላይ ተቀምጠው ካስሩን በኋላ ወደ አለቃቸው ወሰዱን። ብዙ ጥያቄዎች ጠየቁን። ከየት እንደመጣን፣ የት እንደምንሄድ እና
ለምን ይሄን አቅጣጫ እንደመረጥን ተጠየቅን፡፡ በመጨረሻ እጅ እና እግሮቻችንን ፈተው ከመንደራቸው አባረሩን። ጫማችንን ግን አልሰጡንም::

ብዙ ከተጓዝን በኋላ ነበር አሳ አጥማጆቹ ምን እንደቀጡን የገባን፡፡ ፀሐይ ስትወጣ 120 ዲግሪ ሆነ። ምንም ምንጠጋበት
ዛፍ እንኳ አልነበረም፡፡ ፀሐይዋ አሽዋው ላይ ስታርፍ በጣም ሞቀ፤ ግለት ሆነ። በባዶ እግር አሽዋ ላይ ተራመድን።
እግሮቻችንን ቆሰሉ። ደነዘዝን።በመጨረሻ አንድ ጎጆ ቤት ላይ ደረስን፡፡ ወደ ውስጥ ገብተን ተቀመጥን፡፡ የቤቱ ባለቤት ብዙም
ሳይቆይ መጣ። በሩ ላይ ቆሞ ተመለከተን እና ጉዳታችንን ሲያይ ፊቱን ዙሮ ሄደ፡፡

ከትንሽ ቆይታ በኋላ ሳር ይዞ መጣ። እሳት አያያዘ ከዛ ሳሩን በጥቂቱ እሳቱ እንዲለበለብ ካደረገ በኋላ ሳሩን ወደ እግሮቻችንን አስጠጋው:: ሙቀቱ ስቃያችንን አስታገስልን።ቀጥሎ የተጠበሰ አሳ ሾርባ፣ ሩዝ እና ውሃ ይዞ መጣ እና
ፊታችን ላይ አስቀምጦ እንድንበላ ጠየቀን፡፡ እንደገና ወቶ ሄደ፤
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ተመለሰ። የምንተኛበትን ምንጣፍ አሳየን፤ ከመተኛታችን በፊት እግሮቻችንን የምንቀባው ቅባት ሰጠን።

በሚቀጥለው ቀን ስም አልባው እንግዳ ተቀባይ ሰው ምግብ ይዞልን መጣ። ፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ እየተሻለን እንደሆነና እሱም ደስ እንዳለው ነገረን።

በጎጆው ለሳምንት ቆየን።እንግዳ ተቀባዩ ጥዋት እና ማታ ምግብ ይሰጠናል።ጥርሱ ነጭ በረዶ ይመስላል ከወገብ በላይ ሁሌም ራቁቱን ነው ልብስ አይለብስም።አንድ ቀን ስሙን ጠየቁት።ምን ይጠቅምሀል ብለህ ነው። እንደዚሁ ይሻለናል ለደንነታችን አለኝ።

በሚቀጥለው ቀን አመሻሽ ላይ ወደ ውቅያኖስ ይዞን ወረደ።እግራችንን እንድንነክር ነገረን።ጨዋማ ውሃ ከስቃይ እንደሚያስታግስ እና ከቲታኖስ እንደሚጠብቀን ገገረን።

በሁለት ሳምንት ውስጥ ከህመማችን አገገጀምን።አንድ ጠዋት ግን ሽማግሌ ሴትዮ ከእንቅልፋችን ቀስቅሳ መሄድ እንዳለብን ነገረችኝ።የአስተናጋቻችን እናት ነበረች።መንደሩ ስለኛ እንደሰማና ሊይዙን እየመጡ እንደሆነ ነገረችን።የተጠበሰ አሳ እና ውሃ ሰታን 'ልጆቼ መፍጠን አለባችሁ ጸሎቴ ከናንተ ጋር ነው" አለች።

ፈጥነን ከአሳዳጆቻችን ማምለጥ አልቻልንም አስራ ሁለት ነበሩ። አሸዋ ላይ ጥለው እጆቻችንን አሰሩ።ወደ መንደሩ መልሰው አለቃቸው ፊት አቀረቡን።

እናንተ ህፃናት ትናንሽ ሰይጣናት ሁናችኋል። አሁን ግን ወደተሳሳተ መንደር ነው የመጣችሁት አለ። እንደእናንተ ላለ ሰይጣኖች እዚህ ጋር ይበቃል።

ልብሳችሁን አውልቁ ብሎ አዘዘ አለ ስም አልባው አስተናጋጃችን እና እናቱ በ ህዝብ መሃል ነበሩ። በአለቃው መቆጣት ስለ እኛ ሲሳቀቁ እና ሲከፉ አየሁቸው። ልብሴን
ሲያወልቁ የራፕ ካሴት ከኪሴ ወደቀ። አለቃው ካሴቱን መረመረ እና የካሴት መጫወቻ እንዲመጣ አዘዘ፡፡
መጥቶ ሙዚቃው ተከፈተ። አለቃው ጠራኝ እና እንዴት እንደምንደንስ ማሳየት ጀመርኩ። ሞቴን ሳስብ መዳነስ ከበደኝ፤
ምቱም ጠፋብኝ፡፡ አለቃው ግን መረጋጋት ጀመረ። ልጆች መሆናችንን አወቀ። በድንገት ጓደኞቼ እንዲፈቱ አዘዘ። አለቃው ለህዝቡ ስህተት እንደሆነ እና ልጆች መሆናችንን እና ራሳችንን
ለማትረፍ እንደመጣን ተናገረ::
አለቃው ነጻ እንዳደረገን እና በፍጥነት አካባቢውን ለቀን እንድንወጣ ነገረን።

በጉዞየ ከሚረብሽኝ አንድና ዋናው ነገር ጉዞው የት እና መቼ እንደሚቋጭ አለማወቄ ነው፡፡ ይሄ ጥያቄ አዕምሮየን፣ ሰውነቴን እና ስሜቴን በጉዞየ ሁሉ ሲጎዳ ቆይቷል። በህይወቴ ምን እንደምሰራ ወደ የት እንደማመራ አላውቅም:: በየጊዜው እንደገና እንደምጀምር ይሰማኛል። አሁን የህይወቴ ዋና አላማ መትረፍ
ብቻ ነው። ለትንሽ ጊዜም ቢሆን እራሳችንን በምግብ እና በንጹህ
ውሃ ለማስደስት እንሞክር ነበር። በተለያዩ ስሜቶች ከመዋለል መከፋት ቀላል ነበር፡፡ ወደፊት መግፋት እንዳለብኝ አወቅኩ።
የባሰ አለ ብየ ስላሰብኩ አልተካፋሁም።

ጉዞችን ደመና እንደሽፈናት እና ለመውጣት እንደምትፍጨረጨር ጨረቃ መስሎ ታየኝ፡፡ ጨረቃዋ በመጨረሻ ትወጣለች ለሊቱንም ሙሉ ብርሃንዋን ትሰጣለች::

አንድ ቀን ሰኢዱ ”ብዙ ቀን ሰዎች ሊገድሉን ሲመጡ አይኖቼን ጨፍኜ ሞትን ጠብቄለሁ። እስከአሁን አልሞትኩም::
ሞትን በተቀበልኩ ቁጥር ግን አንድ አካሌ እንደሞተ ይሰማኛል። ከትንሽ ጊዜ በኋላ ሙሉ ለሙሉ እንድምሞት ይሰማኛል። ያኔ
ባዶ ስውነቴ ብቻ አብሮችሁ ይጓዛል። ከአሁኑ በላይ ዝምተኛ ይሆናል" አለ። አይኖቼ እንባን አቀረሩ፤ ግንባሬም ሞቀ። የሰኢዱ ን ቃላቶች እያሰብኩ እስኪነጋ ድረስ መተኛት አልቻልኩም::

ጉዞችን አስቸጋሪ ቢሆንም አንዳንዴ ለትንሽ ደቂቃ ቢሆንም መዝናናት እንሞክራለን። አንድ ቀን አንድ መንደር ስንደርስ ሰዎች ለአደን እየተዘጋጁ ነበር። አብረናቸው እንድናድን ጋበዙን፡፡ ከአደን በኋል ምግብ ለሚያዘጋጁ ሴቶች ውሃ በመቅዳት አገዝን፡፡

ምሽት ላይ ሁሉም መንደርተኛ ወደ መንደሩ ተመለሰ፡፡ምግቡ ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣ፡፡ ለሁሉም በስሃን ታደለ።
ከምግቡ በኋላ ከበሮ መምታት ተጀመረ:: ሁላችንም እጅ ለ እጅ ተያይዘን ክብ ሰርተን በጨረቃ ብርሃን መዳነስ ጀመርን።
በመሃል የት እንደመጣን ስለእኛ ታሪክ እንድናካፍል ተጠየቅን፡፡ቆይቶ ዳንሱ ቀጠለ።

ሲነጋ ውሃ እና መንደርተኛው የሰጠንን የተጠበሰ ስጋ ይዘን ጉዞችንን ቀጠልን፡፡ "የአባቶቻችሁ አምላክ ይከተላቹህ" ብለው ሸኙን።

ፀሐይዋ ስታዘቀዝቅ ወደ አንድ ልዩ መንደር ደረስን። መንደር ለማለት ይከዳል:: አንድ ትልቅ ቤት አንድ ኪሎ ሜትር ራቅ ብሎ ደግሞ ጭስ ቤት ብቻ ነበር የሚገኘው:: አማጺዎች በቀላሉ
ሊይዙት የሚችሉት ሰፈር" ብሎ ጅማህ ሳቀ።

ሰው መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሰፈሩን ሙሉ ዙረን አየነው:: የወይራ ዘይት ሲመረት እንደነበር ምልክቶች አሉ።
ወንዙ ላይ ሳር የበቀለብት ታንኳ አለ። ወደ ትልቁ ቤት ተመልሰን ይዘነው የመጣነውን የተጠበሰ ስጋውን እና ውሃ አስቀመጥን።
ብዙም ሳይቆይ መሸ እና ከጓደኞቼ ጋር ተኛን፡፡ የሊሊቱ አጋማሽ እስከሚደርስ ግን እንቅልፍ አልወሰደኝም። ሴት አያቴን
አስታወስኩ:: "እንደ እሳት እኮ ነው ያደግከው: ስም የወጣልህ ቀን እንደ ትናንት ትዝ ይለኛል" ትላለች :: ሰፊ ድግስ ተደግሶ በግ ዶሮ ታርዶ ከተበላ ከተጠጣ በኋላ ኢማሙ ፊት ቀርቤ "ኢስማኤል ተብሎ ይጠራ እንዳለ እና ታዳሚው እንዳጨበጨበ ከዛም ጭፈራ እልልታ እንደነበረ ትነግረኛለች...

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ሰባት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ


#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


ጥዋት ስንነሳ ስጋው ተበልቶ አገኘን። ማን እንደበላው ግራ ገባን። መጀመሪያ ራስ በራሳችን ተጠቋቁመን ነበር። በኋል ግን ውሻ ሆኖ አገኘነው አልሀጂ በጣም ተናዶ ውሻውን ካልደበደብኩ ብሎ ተከላከልነው፡፡ ውሃችንን ይዘን ጉዞችንን
ቀጠልን፡፡ ቀትር ላይ ያገኘነውን ፍራፍሬ ለመብላት ሞከርን።እስከ ማታ ድረስ በመካከላችን ምንም አይነት ንግግር
አልነበረም። ምሽት ላይ ለማረፍ ወሰን።

አልሃጂ "ውሻውን መግደል ነበረብኝ" አለ።

ለምን? አልኩ እኔ

እኔን ተከትሎ “ምን ትርጉም አለው? የሱ መሞት ምን ያደርግናል" አለ ሞሪባ፡፡
አልሃጂ " ያለንን ብቸኛ ምግብ ነዋ የበላብን። ጥሩ ስጋ ይሆን ነበር።
"አይመስለኝም! ደግሞ ማዘጋጀቱ አስቸጋሪ ይሆን ነበር አልኩ።

ሙሳ ደግሞ ውሻውን ቢገድለው ኖሮ እበላው ነበር አለ። አባቴ ማሌዥያውያን ውሻ እንደሚበሉ ነግሮኛል።አልሃጂ ገድሉት ቢሆን ንሮ በልቼ እሞክረው ነበር። አባቴን እንደገና ሳገኘው የውሻ
ስጋ እንደሚጥም እና እንደማይጥም እነግረው ነበር አለ፡፡ጉዞችንን ማታ ለማድረግ ወሰን፡፡ ቀን ምግብ እንፈልጋለን
ተራ ይዘን እንተኛለን፡፡ ማታ ጨረቃዋ ምትከተለን ይመስላል።ሲነጋ ትጠፋ እና በሚቀጠለው ቀን እንደገና መታ መንገዳችንን ትመራለች።
አንድ ቀትር ላይ ኦና በሆነ መንደር ዉስጥ ምግብ ስንፈልግ ቁራ ከየት እንደመጣ ሳይታወቅ ከሰማይ ወደቀ። አልሞተም ነገር ግን መብረር አልቻለም፡፡ ያልተመደ ነገር ነበር፤ ምግብ ግን ፈልገን ነበር። ላባዋን ስንነጭ ሞሪባ ምን ቀን እንደሆነ ጠየቀን። ማንም ሚያውቅ አልነበረም::

"ዛሬ የባዕል ቀን ነው" አለ ኬን እየሳቀ፡፡ "የፈለጋችሁትን ቀን ልትሰይሙት ትችላላችሁ::"
" የቁራው መውደቅ የእርግማን ምልክት ነው መብላት የለብንም" አለ ሙሳ።

"እንግዲህ የእርግማን ምልክት ከሆነ እኛም እርጉማን ነን፡፡ ስለዚህ በደንብ አድርጌ ነው ምበላው:: የፈለከውን ማድረግ ትችላላህ" አለ ኬን፡፡
ብዙም ሳይቆይ ማታ ሆነ፡፡ ከባድ ጸጥታ! ንፋሱ እና ደመና አንድ የሚጠብቁት ነገር ያለ ይመስል መንቀሳቀሳቸውን
አቆሙ:: ለሊቱ በጣም ጨለማ ነበር። ጫካ ላይ አልነበርንም ጨለማው ግን ለመተያየት አስቸጋሪ ነበር። ሶስት ሰዎች ወደ እኛ ሲመጡ አየን፡፡ በዛፎች መሃል ተደብቀን ማየት ጀመርን።እኛ በመጣንበት አቅጣጫ ሄዱ፡፡ ከተደበቅንበት እየተጠራራን መውጣት ጀመርን። ሰኢድ ግን ሊነሳ አልቻለም። በፍርሃት ደነዘዘ ሊንቀሳቀስ አልቻለም:: በመጨረሻ ኬን ተሸክሞት ድልድዩን ተሻገርን፡፡
ድልድዩን እንደተሻገርን ሰኢድ አስነጠሰ፡፡ ኬን አስቀመጠው እና አስታወከ፡፡ በኋላ " መናፍስት ነበሩ አይደል ማታ ያየናቸው" አለ፡፡
ሁላችንም ተስማማን፡፡

“ራሴን ስቼ ነበር። አሁን ደህና ነኝ እንሂድ" አለ፡፡ እኩለ ቀን ሲሆን አንድ ትልቅ መንደር ደረስን። ገበያ ነበር የሚመስለው:: ሰዎች ያዜማሉ ይጨፍራሉ ልጆች ውርውር
ሲሉ የምግብ ሽታ:: ወደ መንደር ቀስ ብለን ገብተን እንጨት ላይ ተቀመጥን።
ሰዎች አዩን አንዳንዶቹ ከዚህ በፊት የምናውቃቸው ይመስላሉ::
እጃቸውን እያውለበለቡ ሰላም አሉን፡፡ አንድ ሴት ወደ እኛ መጥታ አውቅሃልሁ አለችኝ፡፡ አኔ ግን ላውቃት አልቻልኩም::
ጅኒየር እኔን እየፈለገ መጥቶ እንደነበረ እና እናቴን አባቴን እና ትንሽ ወንድሜን ከሚቀጥለው መንደር እንዳየቻቸው
ነገረችኝ፡፡ ከዛ መንደር ብዙ የማታሩ ጆንግ ሰው አለ እናንተም ዘመዶቻችሁን ልታገኙ ትችላላችህ አለች ወደ ጓደኞቼ ፊትዋን
ዙራ።

ወዲያው ለመሄድ ፈልጌ ነበር ነገር ግን በቀጣዩ ቀን ለመሄድ ተስማማን፡፡ በዛ ላይ ሰኢድ እረፍት ያስፈልገዋል::
ወደ ወንዝ ወርደን ዋኘን ድብብቆሽ ከተጫወትን በኋላ ድስት ሙሉ ሩዝ ሰርቀን በላን፡፡

ያን ምሽት መተኛት አልቻልኩም::

አልሃጂ "ውሾቹ ቀሰቀሱኝ” አለ

እኔ እንኳን ከመጀመሪያው አልተኛሁም አልኩ፡፡

ቤተሰቦችህን ለማየት ጓጉተሃል አይደል አለ አልሃጂ። "እኔም አለ እየሳቀ፡፡ ውሻወቹ ጩሀት ግን አልተለየብሁም?”
ትንሽ ቆይቶ መንደርተኛው ነቃ:: እኔ እና አልሃጂ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀሰቀስና ቸው:: ሰኢድ ሊነሳ አልቻለም:: "ተነስ
መሂድ አለብን" እያልን በጣም አንቀሳቀስነው። ሊነሳ ግን አልቻለም:: እንደገና ራሱን ስቶ ይሆን አልን። አንድ ትልቅ ሰው መጥቶ ውሃ አፈሰሰበት። ሰዒድ አልተንቀሳቀስም። ሰውየዋ
ፊቱን አዙሮ ትንፋሹ አዳመጠ። ቀስ ብሎ " ከዚህ መንደር የምታውቁት ሰው አለ ብሎ ጠየቀን፡፡ አናውቅም ብለን መለስን።
ኬንን ወስዶ በጆሮው አንድ ነገር ነገረው:: ኬን ማልቀስ ጀመረ። ሰዒድ ጥሎን እንደሄደ አወቅን፡፡ ሁሉም ማልቀስ ጀመሩ እኔ ግን ለደቂቃዎች ደንዝዥ ነበር። ኬን እና ትልቁ ሰውየ የመቃብር ሳጥን አምጥተው የስዒድን አስክሬን ሳጥኑ ውስጥ አስገቡ።በነጭ አንሶላ ተጠቅልሎ በእንጨት ሳጥን ውስጥ ከጠረጴዛ ላይ
ተቀመጦ ጸሎት ማድረግ ተጀመረ። ሰሙን እየጠራ ጸሎት ማድረግ ሲጀመር እንባየ ከፊቴ ላይ ኮለል ብሎ መፍሰስ ጀመረ።የስዒድን ትቶን መሄድ ማመን አልቻልኩም፡፡ ራሱን እንደሳተ
እና እንደሚመለስ ለማስብ ስጀምር ወደ መቃብር አስገቡት።እንባየ መሬት ላይ ተንጠባጠበ።

ከቀብር ስነ ስርዐቱ በኋላ ብቻችንን ቀረን። አንድ ነገር እንደሚጠብቅ ሰው ለስዓታት በመቃብሩ ቦታ ተቀመጥን። በጣም ልጆችን ነበርን። ከኬን በስተቀር ከአስራ ሶስት አመት በታች! ኬን ሶስት አመት ይበልጠናል። ምሽቱ ሲቃረብ
ከመቃብር ስፍራው ተንቀሳቀስን።

ሰዒድ ያለው አንድ ነገር ትዝ አለኝ " አንድ አካሌ እንደሞተ ይሰማኛል ::"

ሲነጋ የቀብር ስነ ስርዐቱ እንዲፈጸም የረዱንን አመስገን።ከመካከላቸው አንድ "የት እንዳረፈ ሁሌም ታውቃላችሁ አለ"።
በስምምነት ራሳችንን ነቀነቅን፡፡ ወደዚህ መንደር የመመለስ እድላችን አንስተኛ ነው:: ነገን አናውቅምና። ጓደኛችንን ጥለነው እየሄድን ነው" እናቴ እንደምትለም "የዚህ አለም ጊዚያዊ ሩጫውን ጨረሰ”::

ለሊቱን ሙሉ በጸጥታ ተጓዝን። ለትንሽ ደቂቃ ስናርፍ ሞሪባ ራቅ ብሎ ከተቀመጠ በኋላ ማልቀስ ጀመረ። ራሱን ለመቆጣጠር በቅጠሎች መጫወት ጀመረ።ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ጉዟችንን ቀጠልን።

"መንደሩ ስንደርስ እናቴን ጥብቅ አድርጌ ነው ማቅፋት” አለ አልሃጂ።

ሁላችንም ሳቅን፡፡

ወደ መንደሩ ስንቃረብ ቤተሰቦቻችንን እንደምናገኛቸው ተሰማኝ፡፡ ፈገግታየ አልተቋረጠም። የቡና ዛፎች ደኑን መተካት ጀምረዋል። በቡናው ተቃራኒ መለስተኛ የሙዝ እርሻ አለ፡፡ ከኛ
ተሻግሮ አንድ ሰው ያልበሰለ ሙዝ ሲቆርጥ አገኘነው::

ሰላም ዋሉ?" አለ ኬን።

ሰውየው ጎር ጋስሙ ይባላል። ወንደላጤ ነው:: ሰዎች ትልቅ ሰው አይደል ለምንድን ነው የማያገባው:: የግድየለሽ ኑሮ
የሚኖረው" ይላሉ። ምንም መልስ አይሰጥም::

ጋስሙ ፈገግ አለ። ያዙ አለን ሙዝ።

“አባትህ እና እናትህ ሁሌም ስለ አንተ ያወራሉ ይጸልያሉ” አለ ወደ እኔ ዙሮ።" አሁን ሲያዩህ በጣም ነው ደስ ሚላቸው" አለኝ።መንደሩ ተራራ ላይ ነው አለኝ እና መሮጥ ጀመርኩ። መንገዱ አዙሪት ነበር፡፡ ጫፍ ላይ ስንደርስ ደክሞን ተቀመጥን፡፡

ከተራራው ስወርድ የጥይት ተኩስ ተሰማ።ሰዎች መጮህ ማልቀስ ጀመሩ:: ሙዙን ጥለን በዛፎች መሃል ተሸሸግን።

በመጨረሻ አቆመ ሁሉም ነገር ጸጥ ረጭ አለ። ጋስሙን ወደ መንደሩ መሄድ እንደምፈልግ ስነግረው እጆቼን ያዘኝ፡፡ እጄን አስለቅቄ ወደ ታች ሮጥኩ፡፡ መንደሩ ስደርስ ሁሉም ነገር ተቃጥሏል። የት ጀምሬ እንደምፈልጋቸው
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ስምንት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ


#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

..ለቀናት የተጓዝን ይመስለኛል። ሁለት ስዎች ድንገት ግንባራችን ላይ መሳሪያ ደቅነው ተንቀሳቀሱ እስከ ሚሉን ድረስ
ምንም አላስታውስም:: ከባድ መሳሪያ AK 47፣03 እና HPG ይዘው በሁለት ረድፍ ነዱን:: ፊታቸው በጣም ጥቁር ከመሆኑ የተነሳ ክስል የተቀቡ ነበር ሚመስለው። ቀይ በርበሬ በሚመስሉ
አይኖቻቸው አፈጠጡብን። በመንገዳችን የደንብ ልብሳቸው በደም የተጨማለቀ አራት ሰዎች መሬት ላይ ወድቀዋል። ፊቴን
ለማዞር ስሞክር ራሱን የተመታ ሌላ ሰው ተመለከትኩ።አጥወለወለኝ፡፡ ሁሉም ነገር በዙሪያዬ ሲሽከረከር፤ ሲዞርብኝ አንዱ ወታደር ተመለከተኝ። የውሃ ዕቃውን አውጥቶ ትንሽ ከተጎነጨ በኋላ የቀረውን ፊቴ ላይ ደፋብኝ፡፡

“ትለምደዋለህ ፤ ሁሉም ሰው በመጨረሻ ይለምደዋል” አለ።

የተኩስ ድምፅ ድንገት አካባቢውን አናወጠው። ወታደሮቹ ስድስታችንን ይዘው ተንቀሳቀሱ፡፡ የወታደር ጀልባ ከመተረጊስ ጋር የሚንሳፈፍበት አንድ ወንዝ ደረስን :: በወንዙ ዳርቻ የአስራ
አንድ ፣ አስራ ሁለት አመት የሚሆናቸው ታዳጊ ወታደሮች አስክሬን ወድቋል:: ፊታችን አዙረን ጉዞችንን ቀጠልን። የተኩሱ ድምጸ እየጨመረ መጣ፡፡ ወደ ጀልባው ስንወጣ ተኩሱ ወደ እኛ
ተቃረበ። ሮኬት ይወረውራሉ፤ የወንዙ የላይኛው ክፍል በተኩስ ተናወጠ፡፡ እሳት ላይ እንደተጣደ ወሃ ወንዙ በጥይት ናዳ ፈልቶ ይፈለቀለቃል:: የወታደር ልብስ የለበሰ ሰው ወደ ጀልባዎች እየሮጠ ወደ ወታደሮቹ መተኮስ ጀመረ:: ከእኛ ጀልባ ካሉት ወታደሮች አንዱ ተኩሶ ሰውየውን ጣለው:: ጀልባዎቹ ወደ ታች ሲወርዱ ዘለን ወጣን፡ ወታደሩ ጦር ወደ ሰፈረበት የል ወደ ሚባል መንደር ይዞን መራን። ከአስር ቤቶች በላይ ያሉበት ትልቅ
ሰፈር ነው። አብዛኞቹ ቤቶች በወታደሮቹ የተያዙ ናቸው።ወታደሮቹ እኛ በገባንበት በወንዝ ዳርቻ በኩል ካሉት ዛፎች
በስተቀር በአካባቢው ያሉ ዛፎችን ቆርጠዋል። ከድንገተኛ ጥቃት
ራሳቸውን ለመታደግ እንዳደረጉት አስረዱን::

በመጀመሪያ በዚህ በ የል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ደህንነት ያገኘን መስሎን ነበር። መንደሩ ሞቅ ደመቅ ያለ ሳቅ
እናጨዋታ የሞላበት ነበር፡፡ አዋቂዎች፣ የታጠቁ እና ያልታጠቁ የመንደሩ ሰዎች ስለ አየር ንብረት፣ ስለ አዝመራ እና ስለ አደን ያወራሉ። ስለ ጦርነቱ ግን ምንም ማውራት አይፈልጉም አያወሩም፡፡ በመጀመሪያ ሰዎች ለምን እንደዚህ እንደሚሆኑ አልገባኝም ነበር፡፡ ቀስ በቀስ የሰዎች ፈገግታ ስለ ምንም ነገር
መጨነቅ እንደሌለብኝ እምነት አሳደረብኝ፡፡ የሰፈሩ ቀልብ ግን
ያለ አባት እና እናት በቀሩ ልጆች የደበዘዘ ይመስላል።እድሜቸው ከስድስት እስከ አስራ ስድስት የሚሆኑ ወደ ሰላሳ
የሚጠጉ ልጆች ነበሩ። አንዱ እኔ ነበርኩ። ልጅነታችን ለጊዜው ችግር ይግጠመው ወይም ሙሉ ለ ሙሉ እንሰረቅ አናውቅም።

ተሰርቶ ባላላቀ የጡብ ቤት ውስጥ ከሌሎች ልጆች ጋር ማደር ጀመርን። ወታደሮቹ ከእኛ ራቅ ብሎ ባለ አንድ ትልቅ ቤት ውስጥ ፊልም ያያሉ፣ሙዚቃ ያደምጣሉ፣ ይስቃሉ ማሪዋና ያጨሳሉ
ሽታው ስፈሩን ሁሉ ያዳርስ ነበር። ቀን ቀን ከህዝቡ ጋ ተደባልቀው ምግብ እየሰሩ ያሳልፋሉ። ኬን እና እኔ ውሃ በመቅዳት ስሃን በማጠብ እናግዝ ነበር። ሌሎቹ ጓደኞቻችን ሽንኩርት ከተፋ እና መሰል የማዕድ ቤት ስራዎችን ይረዱ ነበር፡፡ ሙሉ ቀን በስራ መጠመዴን ወደድኩት፥
ወንዝ መውረድ፣ መመለስ እና ስሃን ማጠብ፡፡ ከባድ ራስ ምታት
ከሚያስከትልብኝ ሃሳቦች መራቂያ መንገዱ ይሄ ብቻ ነበር።
እኩለ ቀን ሲሆን ሁሉም ስራ አልቆ ምግብ ይቀርባል። ወላጆች ደጃፍ ላይ ተቀምጠው የልጆቻቸውን ፀጉር ይሰራሉ፣ ሴቶች ይዘፍናሉ ወንዶች ደግሞ ኳስ ይጫወቱ ነበር። ደስታው ጫጫታው ከወንዙ ባሻገር ሳይሰማ አይቀርም። በዚህ መንደር ህይወት በፍርሃት አይኖርም፡፡

የኳስ ጨዋታው በማጊቦ የነበረውን የሊግ ጨዋታ አስታወሰኝ፡፡ የእኔ ቡድን ማለትም እኔ እና የተወሰኑ ጓደኞቼ ያሸነፍንበት የዋንጫ ጨዋታ ትዝ ይለኛል። ወላጆቼ ጨዋታውን ለመመልከት ታድመው ነበር፡፡ ጨዋታው ሲጠናቀቅ እናቴ ኩራት እና ደስታ በተደባለቁበት ስሜት ፊቷ በርቶ ተነስታ አጨበጨበች፡፡ አባቴ ደግሞ እኔ ወዳለሁበት ከመጣ በኋላ ራሴን
አሻሽቶ ቀኝ እጄን ወደ ላይ በማንሳት አሸናፊነቴን አወጀ፡፡ ለጁንየርም ተመሳሳይ አደረገ። እናታችን ቀዝቃዛ ውሃ በኩባያ
አመጣችልን። ደስታው የልብ ምቴን ጨመረ፤ ሰውነቴ በላበት ተጠመቆ ነበር። ከጨዋታው በላይ የአባቴ እና እናቴ ደስተኛ መሆን ደስታየን ጨመረው፡፡

አሁን ግን ራሴን ከጨዋታው አገለልኩ። ከቤቱ ጀርባ ተቀምጨ የራስ ምታቴ እስኪበርድ ድረስ ሰማዩን ስመለከት
ቆየሁ፡፡ የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን እንደሚያሰቃየኝ ለማንም አልተናገርኩም፡፡ የወታደሮቹ ሐኪም ጠዋት ጠዋታ ልጆችን ስብስቦ ጉንፋን እና ሌሎችን በሽታዎች እንደተሰማቸው ጠይቆ ህክምና ይሰጣል፡፡ አንድም ቀን ግን ቅዥት ወይም የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን የሚያስቃየው ልጅ ካለ ብሎ ጠይቆ አያውቅም!ማታ አል ሃጂ፣ ጁማህ፣ ሞሪባ እና ኬን በትናንሽ የአለት
ድንጋዮች ገበጣ ሲጫወቱ ነበር። ሙሳ በሰፈሩ ታዋቂ ለመሆን ብዙም ጊዜ አልፈጀበትም። ልክ እንደ ዛሬው ሙሳ ሁሌም ማታ ማታ ለሰፈሩ ልጆች ተረት ተረት ያወራል። እኔ ግን በቤቱ ጥግ
ላይ ቁጭ ብየ ጥርሴን ነክሼ ስቃየን ውጭ አያቸዋለሁ። በአይነ ህሊናየ የእሳት ነበልባል፤ በመንገዴ ያየሁዋቸው አስቃቂ ነገሮች በጨረፍታ እና የህጻናት እና ሴቶች መራራ ጩኸት ይመጣል።ጭንቅላቴ እንደ ደወል ሲደበደብ በዝምታ አለቅሳለሁ። አንዳንዴ የራስ ምታት በሽታው ማይግሬኔ ሲበርድልኝ ለአፍታ ቢሆንም እንቅልፍ ይወስደኛል። ብዙም ሳልቆይ በቅኝዥት እባንናለሁ።
አንዴ ጭንቅላቴ ላይ በጥይት ሲመታ በህልሜ አየሁ። በደም ተጨመለቄ ወድቄለሁ ሰዎች ግን በጥድፊያ ያልፉኛል። ዉሻ መጥቶ ደሜን ይልሳል። ላባርረው ብፈልግም አቅም አልነበረኝም
መንቀሳቀስም አልቻልኩም። በመጨረሻ የፈራሁትን ነገር ከማድረጉ በፊት ከእንቅልፌ ባነንኩ። ከዛ በኋላ የቀሪውን ለሊት መተኛት አልቻልኩም:: አልቦኝም ነበር።

አንድ ቀን የመንደሩ ሁኔታ ድንገት ተለወጠ። ወጥረት ሆነ የውጥረቱ ምክንያት ባይታወቅም አንድ ከባድ
ነገር እንደሚከተል መገመት ይቻላል። በመንደሩ የሚገኙ ሁሉ ወታደሮች የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ትጥቃቸዉ
አሟልተው ተሰበሰቡ፡፡ “ተጠንቀቅ” “አሳርፍ” “ተጠንቀ “አሳርፍ” :: ከአል ሃጂ ጋር ውሃ ለመቅዳት ወንዝ ስወርድ ነው
የአሰልጣኙን ድምፅ የሰማሁት። ስመለስ ልምምድ አብቅቶ መቶ አለቃ ጃባቲ በወታደሮቹ ፊት ቁሞ ይናገራል። ለምሳ
እስከሚለቀቁ ድረስ ለስዐታት ንግግር አደረገ። መቶ አለቃ በሚናገርበት ወቅት የዕለት ተዕለት ስራችንን እየሰራን ምን
እንደሆነ በልጅ አዕምሮችን ለመረዳት እንሞክር ነበር።

ማታ ወታደሮቹ ጠበንጃዎችን ሲያጸዱ ፤ አልፎ አልፎ ወደ ሰማይ በመተኮስ አሳለፉ። ህጻናት ተኩሱን ሲስሙ ወደ ወላጆች እቅፍ ሮጡ። ወታደሮቹ ገሚሶቹ ሲጋራ ማሪዋና ሲያጨሱ የቀሩት ቁማር ሲጫወቱ እና ፊልም ሲያዩ ለሊቱ ተቃረበ።
መቶ አለቃ ጃባቲ ቤቱ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሐፍ ያነብ ነበር።ቀና ብሎ አያይም። ቢጮሁ ቢያፏጩ ቀና ብሎ አያይም።ያለ ወትሮው ፀጥታ ሲሰፍን ድምጸ ሲጠፋ ግን ቀና ብሎ አካባቢውን ይቃኛል። ወደ እሱ ስመለከት አይናችን ተጋጨ እና ወደ እሱ እንድመጣ ጠራኝ፡፡ ቁመቱ ረጂም፣ ፀጉሩ የሳሳ፣ አይኖቹ ትልልቅ እና ጉንጩ ወፍራም ነበሩ። ዝምተኛ ነገር ግን በዝምታው
👍21
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_ዘጠኝ

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


የሰባት አመት ልጅ እያለሁ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን ለማቅረብ ወደ ከተማ አዳራሽ እሄድ ነበር፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ
አዋቂዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ። ረጂም ጣውላ ወንበር ላይ ተቀምጠው ውይይታቸው ሲያልቅ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን እንዳቀርብ እጠራለሁ። አባቴ ጸጥታ እንዲሰፍን እና
ተውኔቱ እንዲጀምር ደመቅ አርጎ ያነጥሳል። እጁን አጣምሮ ከደማቅ ፈገግታ ጋር ፊት ለፊት ይቀመጥ ነበር። ወንበር ላይ እወጣና ረጂም ዱላ እንደ ሰይፍ በመጠቀም እጀምራለሁ።
ከጅሊየስ ቄሳር “ጓደኞቼ፣ ሮማዊያን፣ የሃገሬ ልጆች እስኪ ጀሮችሁን ስጡኝ፡፡ ብየ እጀምራለሁ። አዋቂዎች የሚወዷቸው
ስለነበሩ ብዙ ጊዜ ማክቤዝ እና ጅሊየስ ቄሳርን ነበር ማቀርበው።የእንግሊዝኛ ቋንቋን የመናገር ችሎታየ የዳበረ እና ጥሩ የሆነ ስለሚመስለኝ በከፍተኛ ጉጉት እና ደስታ ነበር ማቀርበው::

ወታደሮቹ በእኩለ ለሊት ሲገሰግሱ ነቅቼ ነበር። የኮቴቸው ድምጸ በሙሉ መንደሩ አስተጋባ። ቀኑን ሙሉ ጆሮዎየ ላይ
ሲያቃጭልብኝ ዋለ። አስር ወታደሮች ሰፈሩን እንዲጠብቁ ከእኛ ጋር ቀሩ። በየምድብ ቦታቸው ቀኑን ሙሉ ሲጠብቁ ዋሉ። ምሽቱ ፥ሲቃረብ ወታደሮቹ ወደ ሰማይ በመተኮስ እና የመንደሩ ሰዎች
ወደ “ቤት እንዲገቡ” እንዲሸሸጉ በማዘዝ የስዓት እላፊ አወጁ።ያን ምሽት ሙሳ ተረት አላወራም ሞሪባም ከልጆች ጋር ገበጣ አልተጫወተም፡፡ በዝምታ ጀርባችንን ለግድግዳው ሰጠን
ተቀምጠን የተኩስ እሩምታ ሲዘንብ ከርቀት እናዳምጥ ነበር።ለሊቱ እስኪገባደድ የመጨረሻ ስዓት፤ ጨረቃ በጉም መሃል አልፋ ፊቷን በክፍቱ የቤታችን መስኮት እስከምታሳይ እና
በአውራ ዶሮ ጩኅት ለሊቱ እስከሚባረር ድረስ ተኩሱ ቀጠለ።

ፀጠዋት ከፀሐይዋ መውጣት ጋር መመለስ የቻሉ የተወሰኑ ወታደሮች ብቻ ወደ መንደር መጡ። የተወለወለ ኮሬ ጫማቸው በጭቃ ተበላሽቷል። ፈንጠር ፈንጠር ብለው መተማማኛ የመሰላቸውን መሳሪያቸውን አቅፈው ተቀምጠዋል። ብሎኬት ላይ ተቀምጦ የነበረ አንድ ወታደር እጁን በራሱ ላይ ጭኖ
ተርገፈገፈ። ተነስቶ መንደሩን ዙሮ ወደነበረበት ተመለሰ።በተደጋጋሚ እንደዚህ ሲያረግ ቆየ። መቶ አለቃ ጃባቲ ሬዲዮ ላይ መልዕክት ሲያስተላልፍ ከቆየ በኋላ ሬዲዮውን ወረውሮ ወደ ቤቱ ገባ። መንደርተኛው ምንም አላወራም:: ዝም
ብሎ የወረደውን መዓት ታዘበ።

እኩለ ቀን ሲሆን ከሃያ የሚበልጡ ወታደሮች ወደ መንደሯ መጡ። መቶ አለቃ ሲያቸው ማመን አልቻለም ተገረመ ተደሰተ ብዙም ሳይቆይ ቁጥብ ሆነ። ወታደሮቹ ራሳቸዉን እንደገና ካዘጋጁ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ወረዱ። ምንም መደበቅ አላስፈለገም ጦርነቱ ቅርብ ነው። ብዙም ሳይቆይ የተኩስ እሩምታ መስማት ጀመርን። መንደሩን የሚጠብቁት ወታደሮች ወደ ቤት እንድንገባ አዘዙን። ተኩሱ ከወፎችን እና ዶሮዎች ጩኅት ጋር እስከ ምሽት ድረስ ቀጠለ። ለሊት ጥይት ለማምጣት እና ለአጭር ረፍት ጊዜ ወታደሮች እየሮጡ ወደ መንደር መጡ። የቆሰሉ ወታደሮች በፋኑስ የታገዘ ቀላል ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም አብዛኞቹ ይሞታሉ። ወታደሮቹ የሞቱ ጓዶቻቸዉን ወደ መንደር
አያመጡም። ምርኮኛዎችን አሰልፈው ግንባራቸውን በጥይት በመምታት ይገድሉዋቸዋል።

ጦርነቱ ለቀናት ቀጠለ።ወታደሮች ቀስ በቀስ ቁጥራቸው እየቀነሰ ሄደ፡፡ ወታደሮቹ እረፍት አጡ ፤ ኮሽ ካለ የመንደሩ ሰዎች
ላይ ሳይቀር መተኮስ ጀመሩ:: መቶ አለቃዉ የመንደሩን ነዋሪዎች ወደ አደባባይ ወጥተው እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ሰጠ።
“ጫካው ውስጥ ህይወታችንን ሊያጠፉ ዕድላችንን ሊያበላሹ የሚጠብቁ ወታደሮች ተዋግተናቸዋል። በቁጥር ግን ይበልጡናል። መንደሩን በሙሉ ከበው አሉ። ይሄን መንደር እስከሚይዙ ድረስ ተስፋ አልቆርጥም:: የእኛን ምግብ እና መሳሪያ የራሳቸው ማድረግ ይፈልጋሉ።” ብሎ ንግግሩን ገታ አደረገና ቀስ ብሎ እንደገና ቀጠለ። አንዳንዶቻችሁ ከዚህ የምትገኙት ወላጆቻችሁን ቤተሰቦቻችሁን ስለገደሉባችሁ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ አስተማማኝ መጠጊያ መሸሸጊያ ነው ብላችሁ ነው:: እንግዲህ ከዚህ በኋላ
አስተማማኝ አይደለም:: ለዚህ ነው ጠንካራ ወንዶችን ታደጊዎችን የምንፈልገው:: እነዚህን እንድታግዙን የሰፈሩን ሰላም እና ደህንነት እንድንጠብቅ
እንፈልጋለን። መዋጋት ወይም ማገዝ ካልፈለጋችህ ምንም አይደል፡፡ ነገር ግን ቀለብ አይሰፈርላችሁም በመንደሩም መቆየት አትችሉም። መሄድ ትችላላችሁ ከዚህ የምንፈልጋቸው ምግብ
በማብሰል መሳሪያ በማዘጋጀት ጥይት በማቀበል የሚረድን የሚዋጉ ናቸዉ። ለምግብ ማብሰል በቂ ሴቶች አሉ። ስለዚህ ብቁ የሆኑ ታዳጊ ወንዶች እና ወጣቶች ነው እነዚህን አማጺዎች
እንዲዋጉ ምንፈልገው:: አሁን ነው የወላጆቻችሁን ደም የምትመልሱት፤ ሌሎች ልጆችንም ወላጆቻቸውን ከማጣት
ማስቀረት የምትችሉት::” ትንፋሽ ወሰደ። “ ነገ ጠዋት ሁላችሁም ከዚህ ቦታ እንድትሰለፉ ለተለያዩ ስራዎች ሰዎችን
እንመርጣለን።” አደባባዩን ለቆ ሲሄድ ጠባቂዎቹ ተከተሉት።

ለተወሰነ ጊዜ ደርቀን ባለንበት ቁመን ቀረን። ከዛ የስዓት እላፊው ሲቃረብ ወደየ ምኝታ ቦታችን ተበተን። ቤት ውስጥ
ጁማህ፣ አል ሃጂ ሞሪባ፣ ሙሳ እና እኔ ምን ማድረግ እንዳለብን ድምጻችንን ቀንሰን ተወያየን፡፡

“አማጺዎች ከዚህ መንደር የሆነ ማንም ሰው ጠላት ወይም ስላይ ነው ብለው ስለሚገምቱ ሁሉንም ይገድላሉ። ይሄን
ነው ያለው አምሳ አለቃው።” አለ አል ሃጂ የገጠመንን ኣጣብቂኝ ለማስረዳት ሲሞክር። ሌሎቹ ወንዶች ከተጋደሙበት ስጋጃ ተነስተው ውይይቱን ተቀላቀሉ። አል ሃጂ ቀጠለ “የሚሻለው ለጊዜውም ቢሆን ከዚህ መቆየት ነው።” ሌላ ምርጫ
አልነበረንም። መንደሩን ለቆ መሄድ ማለት መሞት ማለት ነው::

“አዳምጡ! ይህ ከመቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው፡፡ ሁላችሁም አሁንኑ ወደ አደባባይ በመውጣት ተሰብሰቡ።” ብሎ በድምጽ ማጉያ ለፈለፈ። ተናግሮ ሳይጨርስ አደባባዩ በሰዎች ሞላ፡፡
ሁሉም ሰው ለደህንነቱ ምን ማድረግ እንዳለበት የሚወስነውን ይህን ጊዜ በጉጉት ይጠብቅ ነበር። ከአዋጁ በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኩሽና ቤቱ ውስጥ ተቀምጬ ነበር። ፊታቸው ባዶ ምንም ስሜት የማይታይበት አይናቸው ግን በሃዘን ገርጥቶ ነበር። አይን ለ አይን ላያቸው ብሞክርም ፊታቸውን አዞሩ። ቁርሴን ለመብላት ብሞክርም ፍርሃት የመብላት ፍላጎቴን ነጥቆኛል።

በሰልፍ መሃል ቦታ ስናገኝ የተኩስ እሩምታ አየሩን ተቆጣጠረው:: ከዚያ ከተኩሱ የሚከብድ ጸጥታ ሆነ።

መቶ አለቃ ለሁሉም ለመታየት ከተደረደረ ጡብ ላይ ወጣ።አጥንት ከሚሰብር ዝምታ በኋላ ወደ ወታደሮቹ እጁን
አመለከተ:: ወታደሮቹ የአንድ ወጣት እና ሌላ ታዳጊ አስክሬን ከፊታችን አስቀመጡ፡፡ የመንደሩ ነዋሪዎች ነበሩ። ልብሳቸው በደም ተጠምቋል አይናቸው እንደተከፈተ ነው፡፡ ሰዎች ፊታቸውን ለማዞር ሲሞክሩ ትንንሽ ልጆች ማልቀስ ጀመሩ።መቶ አለቃው ጉሮሮውን አጥርቶ መናገር ጀመረ፡፡እነዚህን አሰቃቂ አስክሬን በተለይ ልጆች ባሉበት
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስር

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው

...በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።

አንድ ፊሽካ ባንገቱ ላይ ያንጠለጠለ ነገር ግን መለዮ ያልለበስ ወታደር AK-47 ካለበት ሳጥን በማውጣት አንድ አንድ ለሁላችን አደለን። ወደ እኔ ሲደርስ ቀና ብየ ላየው ስላልቻልኩ ራሴን ቀና
አድርጎ ነበር የሰጠኝ። እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር።

“ሁላችሁም በሁለት ነገሮች ትመሳሰላላችሁ” አለ ወታደሩ።
“ስው ቀና ብላችሁ አይን ለአይን ማየት አትችሉም እና መሳሪያ መያዝ ያስፈራችኋል። ራሳችሁ ላይ የተደቀነ ይመስል ትንቀጠቀጣላችሁ። ይሄ መሳሪያ ከእንግዲህ የናንተ ነው።እንዴት መያዝ እንዳለባችሁ ከአሁኑ ተማሩ። ለዛሬ ይበቃል”አለ ወታደሩ።

ያ ለሊት በድንኳኔ መግቢያ ላይ ለተወሰነ ደቂቃ ቆምኩ።ጓደኞቼ መጠው ያወሩኛል ብየ ስጠብቅ ነበር። ማንም ከድንኳኑ
አልወጣም:: እጄን ራሴ ላይ ጭኜ ተቀመጥኩ። የራስ ምታቴ ያን ምሽት ጠፋ።

ከእኔ ጋር ድንኳን የሚጋሩት ሼኩ እና ጆሲያህ ደወል እስከ ሚደወል ንጋት 12 ስዓት ድረስ ተኝተው ነበር።ለስልጠና
መነሳት ነበረብን። ኑ እንሂድ” ብየ ቀስ አድርጌ ልቀሰቅሳቸው ሞከርኩ። ወደ ሌላ ጎናቸው እየተንከባለሉ ከእንቅልፋቸው ሊነሱ አልቻሉም፡፡ ከዛ ሰሌኑን አንስቼ መትቼ አስነሳሁዋቸው።

አዲስ የወታደር ጫማ፣ ሱሪ እና ዝንጉርጉር ቲሸርት ተስጥቶን ልምምዳችን ጀመርን። ሱሪ ስቀይር ወታደሩ ወደ እኔ
መጥቶ አሮጌውን ሱሪ ወደ እሳት ጨመረው። አሮጌው ሱሪ የራፕ ካሴቴን ይዞ ስለነበር ወደ እሳቱ ሩጬ ላተርፈው ሞከርኩ።ካሴቱ ግን መቃጠል ጀምሯል። አይኔ እንባ አቀረረ።

ወደ ጎን ረድፍ ሰርተን እግራችን ከፍተን እጃችንን አጣምረን መጠበቅ ጀመርን። አንዳንድ ወታደሮች ከጦር ሜዳ ተመልሰው የጦር መሳሪያቸውን አስተካከሉ ጥይቶችን በጎናቸው ባለ
ከረጢት ያዙ። አንዳንዶቹ ልብሳቸው እና ፊታቸው ደም ይታይበታል። ቁርሳቸውን በፍጥነት በልተው ተመለሱ::

ሼኩ እና ጆሲያህ ከእኔ ጎን ነበሩ። አንድ ድንኳን መጋራታችን እንደ ትልቅ ወንድም እንዲሰማኝ አድርጓል። በልምምድ መሃል
እኔን ያያሉ፤ ከአሰልጣኝ በላይ እኔ የማደርገውን ያደርጉ ነበር፡፡አሰልጣኙ ራሱን አስር አለቃ ጋዳፊ ብሎ ነበር ያስተዋወቀን ከመቶ አለቃ ጃባቲ እና ከሃምሳ አለቃው ጋር ሲነጻጸር በእድሜ
ያንሳል፤ ራሰ በራ መሆኑ እና ኮስታራ ፊቱ ግን ትልቅ ሰው ያስመስለዋል ::

መጀመሪያ በህንጻው ዙሪያ ለተወሰነ ደቂቃ ሮጥን። ቀጥሎ በዱር ውስጥ አድብቶ መግባት ተማርን። ዛፎ ላይ መውጣት መውረድ፣ ድምጸ ሳናሰማ መንቀሳቀስ እና ተመልሶ ወደ ነበሩበት
ሩጦ መመለስ በተደጋጋሚ ሰራን። አስር አለቃ ጋዳፊ ብዙ አይናገርም:: “መጥፎ አይደለም”፣ “መጥፎ” እና “ፍጥነት” ብቻ
ይል ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ በምልክት ይጠቀማል። ወደ ጫካው ከገባን
በእጃችን እንቅስቃሴ መግባባት እንዳለብን ነገረን። “ቃላት ተናገራችህ ማለት ግንባራችሁን ለጥይት አሳልፋችሁ ሰጣችሁ ማለት ነው” ይላል፡፡ በስልጠና መሃከል ቁርስ እንድንበላ አንድ ደቂቃ ብቻ ይሰጠናል። በመጀመሪያ ቀን ብዙ ሳንበላ ነበር ምግቡ የተነሳው። ከሳምንት በኋላፀ በፍጥነት መብላት ለመድን።
ከስዓት AK-47 ያደለንን አስር አለቃ ፊት ለፊት ገጥመን ተሰለፍን። የእኔ ተራ ሲደርስ አፍጥጦ አየኝ እና ከእንጨት ሳጥን ውስጥ መሳሪያ አውጥቶ ደረቴ ላይ አስታቀፈኝ፡፡ መሳሪያየን
ይዥ ወደ ሰልፉ ተመለስኩ፡፡ እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር፡፡ በእጆቼ
ይዤው እንኳ ላየው ፈራሁ። እኔ ማውቀው በቅርቅሃ ሚስራ የአሻንጉሊት ሽጉጥ ነበር። እኔ እና ጓደኞቼ ከቅርቅሃ ሰርተን በቡና ማሳ ወይም በግንባታ ላይ ባሉ ቤቶች መሃል እንጫወት ነበር። አሁን የዕቃ ዕቃ ጨዋታ አይደለም የእውነት AK-47 ይዘናል። ለጊዜው ያለ ጥይት መሳሪያውን ይዘን መሮጥ መንከባለል ተማርን። ቀጥሎ ወደ ሙዝ ማሳ በመውረድ ሙዙን በሰንጢ መውጋት ጀመርን፡፡ “ሙዙን እንደ ጠላት ተመልከቱት።ወላጃችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን እንደገደሉት አማጺዎች” አስር አለቃ ጮኸ። “ቤተሰቦቻችሁን የገደለን ሰው እንደዚህ ነው ምትወጉት?” እንደዚህ ነው ብሎ እየጮኸ መውጋት ጀመረ።

መጀመሪያ ሆዱን፣ ከዛ አንገቱ ላይ፣ ልቡን” እያለ ቀጠለ። እኛም በንዴት ስሜት ሙዙን መውጋት ቀጠልን:: ምሽት ላይ አልሞ መተኮስ ሰለጠን። ሼኩ እና ጆሲያህ መሳሪያቸውን ለማንሳት
አቅም አልነበራቸውም:: አስር አለቃ ከፍ ያለ ኩርሲ ነገር ሰጣቸው እና ልምምዳቸውን ቀጠሉ። በመጨረሻ መሳሪያ ፈቶ መጠገን እንደይዝጉ ዘይት መቀባት ተማርን፡፡ ያ ምሽት ሁላችንም ደክሞን ስለነበር በቀጥታ ወደ ምኝታችን አመራን።

ሼኩ እና ጆሊያህ ቀን የሰሙትን “አንድ ሁለት” “ፓው ፓው ቡም” ድምጾች በእንቅልፍ ልባቸው ይሉ ነበር።

እሁድ ጠዋት ነበር አስር አለቃ ያን ቀን ስልጠና እንደሌለ እና እንድናርፍ ሲነገረን፡፡ “ሃይማኖተኛ ከሆናችሁ ማለት
ክርስቲያን ከሆናችሁ ዛሬ አምላካችሁን የማምለኪያ ቀን ይሁናችሁ ፤ ምን አልባት ሌላ ጊዜ ላይኖራችሁ ይችላል። ሂዱ”

የወታደር ልብሳችንን እንደለበስን ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣን። ኳስ መጫወት ስንጀምር መቶ አለቃ ከቤቱ ደጃፍ ወጥቶ
ሊቀመጠ ነበር። ጨዋታውን አቁመን ለመቶ አለቃ ሰላምታ ሰጠን። “ጨዋታችሁን ቀጥሉ። አሁን የምፈልገው ወታደሮቹ ኳስ ሲጫወቱ ማየት ነው።” ብሎ ባርጩሜ ላይ ተቀመጦ
ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ን ማንበቡን ቀጠለ ::

ኳስ ጨዋታው ሲበቃን፤ ለመዋኘት ወሰን እና ወደ ወንዝ ወረድን። ፀሐይማ ቀን ነበር፡፡ ወደ ወንዝ ስንወርድ ሰዉነታችን
ላይ የነበረው ላብ እየደረቀ ነበር። ለተወሰኑ ደቂቃዎች ከተንቦጫረቅን በኋላ በሁለት ቡደን ተከፍለን መወዳደር
ጀመርን።

እንሂድ ጓዶች: በዓሉ አብቅቷል።” ብሎ አስር አለቃ ከወንዙ ዳር ሁኖ ጮኸ። ጨዋታውን አቁመን አሱን ተከትለን
ወደ መንደራችን ሄድን።

መንደር እንደደረስን መሳሪያችንን እንድጠግን ትዕዛዝ ተሰጠን። መሳሪያችንን እያጸዳን የወገብ እና የጀርብ ቦርሳ ተሰጠን። ጥይቶችንን የፈለግነውን ያህል እንድንወስድ ተነገረን።
መሸከም ከምንችለው በላይ ከሆነ በፍጥነት መሮጥ እንደማንችል
ነገረን። ከአል ሃጂ እና ከእኔ በስተቀር ሌሎች ደስተኛ ነበሩ።ፀተጨማሪ ልምምድ የሚሄድ ነበር የመሰላቸው። አል ሃጂ መሳርያውን አጥብቆ ያዘ።

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ