#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍቃዱ የሚወጣዉን ሰዉ ተመለከተዉ
ፍፁም የጀመረዉን አጋምሶ ፍቃዱ እስካሁን ስለጠፋሁበት ተመልሶ ይሆናል በማለት ለጥቂት ደቂቃ ስለተቀመጠ እግሩን እያስነከሰዉ በክራንቹ እየተመረኮዘ ሰበር ሰካ እያለ ሲወጣ
ፍቃዱ ከቅድሙ ሰዉዬ ጋር ቆሞ እያወራ ፊት ለፊት ተፋጠጡ።
ቤዛዊት በሽታዋ እያገረሸ እየተብከነከነች ብቻዋን እያወራች ወደ ፍፁም ቤት አምርታ አለመኖሩ ስታረጋግጥ አከራዩ ጋር ሄዳ
"የት ነዉ የሄደዉ?"
ለእሳቸዉ የማይጠየቅ ጥያቄ አይኖቿን እያጉረጠረጠች ጠየቀቻቸዉ
"እኔ ምን አዉቃለዉ የሚሄድበትን ነግሮኝ አይሄድ"
ሲሉ አኩዋሀኗ ያላማራቸዉ የፍፁም አከራይ መለሱላት
"እሺ እኔን የምትመስል ቁመት ብቻ የምትበልጠኝ ሴት መጥታ ነበር"
አጉረጠረጠችባቸዉ
የፍፁም ቤት አከራይ በልባቸዉ ምኗ ለካፊ ናት እያሉ
"የኔ እመቤት ማንም የመጣ ሰዉ አላየሁም አቶ ፍፁም ግን ብቻዉን ጠዋት ሲወጣ ተገናኝተን ነበር"
ይህን ሲሏት ትንሽ ተረጋጋች ከእህቴ ጋር ነዉ ስትል የነበረዉን ትታ እየከነፈች ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ደርሳ ከመግባቷ በፊት ለአፍታ ፍፁምን አሰበችዉ
"የት ሄዶ ይሆን ምን ገጠመዉ"
አይምሮዋ ግን አልተረጋጋም በቆመችበት ቦታ አንፑላንስ ድምፁን እያሰማ በአጠገቧ ሲያልፍ ጩሀቱ ስለቀፈፋት በእጆቿ ጆሮወቿን ደፍና ለደቂቃ ቆመች
መኪናዉ አልፎ ጩሀቱ እየቀነሰ ሲመጣ ተስፋ በመቁረጥ ስሜት አስፓልቱ ዳር ዝርፍጥ ብላ ተቀምጣ በአይኖቿ የፍፁምን መምጣት ትጠባበቃለች።
እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊት መጣሁ ብላ መጥፋት አሳስቧቸዉ ወደ ዉጪ ወጣ ሲሉ መንገድ ዳር ተቀምጣ አይኖቿ ሲንከራተቱ ስላዩዋት ደረታቸዉን እየደቁ እየደገፉ ወደ ቤት ለማስገባት የቤዛዊትን ሰዉነት መጎተት ጀመሩ።
"አይመጣም ቀረ..."
እያለቻቸዉ እየተሳበች እየተጎተተች ተነስታ የእማማ ስንቅነሽን ቀሚስ ጨምድዳ ይዛ እየቆመች
በታመመ አይምሮዋ የቅድሙን ቃል ደገመችላቸዉ
"አይመጣም ቀረ..."
እማማ ስንቅነሽም በዝምታ ወደ ቤት እንድትገባላቸዉ እየጎተቷት
ቅድም ያለፈዉ አንፑላንስ ተመልሶ እየጮሀ አለፈ በአሁኑ ግን ጆሮወቿን አልያዘችም በድንገት ግትር ብላ ቆማ
"ያ ዉ ያዉና መጣ"
የቀኝ እጇን የመጠቆምያ ጣት ወደ ታች ወደሚወርዱ ብዛት ያላቸዉ ሰወች ቀስራ
ፍፁም እያነከሰ በሁለት ፖሊሶች ተከቦ ከጀርባቸዉ ወሬ አድማቂ ሰዉ አጅቦት አንገቱን ደፍቶ እየተራመደ ነዉ መሬት መሬቱን እያየ ሸንከል ሸግከል እያለ ይራመዳል ፖሊሶቹ እንዲፈጥን ኮሌታዉን ይዘዉ ይጎትቱታል
ፍፁምን ካጀቡት ሰወች መሀከል
"ገድሎታል አረ አልሞተም"
እየተባባሉ ይከራከራሉ
ቤዛዊት እማማ ስንቅነሽ እጅ ላይ አይኖቿ ፍዝዝ ብለዉ በድን ሆና ቆማለች መናገር አቁማለች የምትሰማም አትመስልም የአይኖቿ ብሌኖች ብቻ በቀስታ ይንከዋለላሉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ፍፁም ፊት ለፊቱ የቆመዉን ፍቃዱን ሲያየዉ እያዘነ አይቶ እንዳላየዉ መስሎ ሊያልፈዉ ሲል ፍቃዱ ከጀርባዉ ደርሶበት
"የት ለመድረስ ነዉ የምታነክሰዉ"
ይለዋል በንቀት እግር እግሩን እያየ
ፍፁም መልስ ሳይሰጠዉ መራመዱን ሲቀጥል ፍቃዱ ደግሞ ደርሶበት እየሳቀ
"ቤዛዊትን መቼም አታገኛትም የኔ ናት አንተ ዉሻ እያዋራሁክ ደሞ የምን ንቀት ነዉ ጥለሀኝ የምትሄደዉ..."
ፍፁም መታገስ አልቻለም ክራንቹን ወደ ሰማይ አንስቶ ፍቃዱ ላይ ሳያቋርጥ ማሳረፍ ጀመረ።
ሳያስበዉ በእልህ ፍቃዱን ክፉኛ ስለመታዉ መቆም ያቃተዉ ፍቃዱ ተዝለፍልፎ ወደቀ።
💫ይቀጥላል💫
ምዕራፍ #1 በዚህ ተጠናቋል ምዕራፍ #2 በቅርቡ እንጀምራለን እስከዛው በሌሎች ጣፋጭ ድርሰቶች እንቀጥላለን እስካሁን በሄደው ድርሰት ላይ ያሎትን አስተያየት አድርሱን
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍቃዱ የሚወጣዉን ሰዉ ተመለከተዉ
ፍፁም የጀመረዉን አጋምሶ ፍቃዱ እስካሁን ስለጠፋሁበት ተመልሶ ይሆናል በማለት ለጥቂት ደቂቃ ስለተቀመጠ እግሩን እያስነከሰዉ በክራንቹ እየተመረኮዘ ሰበር ሰካ እያለ ሲወጣ
ፍቃዱ ከቅድሙ ሰዉዬ ጋር ቆሞ እያወራ ፊት ለፊት ተፋጠጡ።
ቤዛዊት በሽታዋ እያገረሸ እየተብከነከነች ብቻዋን እያወራች ወደ ፍፁም ቤት አምርታ አለመኖሩ ስታረጋግጥ አከራዩ ጋር ሄዳ
"የት ነዉ የሄደዉ?"
ለእሳቸዉ የማይጠየቅ ጥያቄ አይኖቿን እያጉረጠረጠች ጠየቀቻቸዉ
"እኔ ምን አዉቃለዉ የሚሄድበትን ነግሮኝ አይሄድ"
ሲሉ አኩዋሀኗ ያላማራቸዉ የፍፁም አከራይ መለሱላት
"እሺ እኔን የምትመስል ቁመት ብቻ የምትበልጠኝ ሴት መጥታ ነበር"
አጉረጠረጠችባቸዉ
የፍፁም ቤት አከራይ በልባቸዉ ምኗ ለካፊ ናት እያሉ
"የኔ እመቤት ማንም የመጣ ሰዉ አላየሁም አቶ ፍፁም ግን ብቻዉን ጠዋት ሲወጣ ተገናኝተን ነበር"
ይህን ሲሏት ትንሽ ተረጋጋች ከእህቴ ጋር ነዉ ስትል የነበረዉን ትታ እየከነፈች ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ደርሳ ከመግባቷ በፊት ለአፍታ ፍፁምን አሰበችዉ
"የት ሄዶ ይሆን ምን ገጠመዉ"
አይምሮዋ ግን አልተረጋጋም በቆመችበት ቦታ አንፑላንስ ድምፁን እያሰማ በአጠገቧ ሲያልፍ ጩሀቱ ስለቀፈፋት በእጆቿ ጆሮወቿን ደፍና ለደቂቃ ቆመች
መኪናዉ አልፎ ጩሀቱ እየቀነሰ ሲመጣ ተስፋ በመቁረጥ ስሜት አስፓልቱ ዳር ዝርፍጥ ብላ ተቀምጣ በአይኖቿ የፍፁምን መምጣት ትጠባበቃለች።
እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊት መጣሁ ብላ መጥፋት አሳስቧቸዉ ወደ ዉጪ ወጣ ሲሉ መንገድ ዳር ተቀምጣ አይኖቿ ሲንከራተቱ ስላዩዋት ደረታቸዉን እየደቁ እየደገፉ ወደ ቤት ለማስገባት የቤዛዊትን ሰዉነት መጎተት ጀመሩ።
"አይመጣም ቀረ..."
እያለቻቸዉ እየተሳበች እየተጎተተች ተነስታ የእማማ ስንቅነሽን ቀሚስ ጨምድዳ ይዛ እየቆመች
በታመመ አይምሮዋ የቅድሙን ቃል ደገመችላቸዉ
"አይመጣም ቀረ..."
እማማ ስንቅነሽም በዝምታ ወደ ቤት እንድትገባላቸዉ እየጎተቷት
ቅድም ያለፈዉ አንፑላንስ ተመልሶ እየጮሀ አለፈ በአሁኑ ግን ጆሮወቿን አልያዘችም በድንገት ግትር ብላ ቆማ
"ያ ዉ ያዉና መጣ"
የቀኝ እጇን የመጠቆምያ ጣት ወደ ታች ወደሚወርዱ ብዛት ያላቸዉ ሰወች ቀስራ
ፍፁም እያነከሰ በሁለት ፖሊሶች ተከቦ ከጀርባቸዉ ወሬ አድማቂ ሰዉ አጅቦት አንገቱን ደፍቶ እየተራመደ ነዉ መሬት መሬቱን እያየ ሸንከል ሸግከል እያለ ይራመዳል ፖሊሶቹ እንዲፈጥን ኮሌታዉን ይዘዉ ይጎትቱታል
ፍፁምን ካጀቡት ሰወች መሀከል
"ገድሎታል አረ አልሞተም"
እየተባባሉ ይከራከራሉ
ቤዛዊት እማማ ስንቅነሽ እጅ ላይ አይኖቿ ፍዝዝ ብለዉ በድን ሆና ቆማለች መናገር አቁማለች የምትሰማም አትመስልም የአይኖቿ ብሌኖች ብቻ በቀስታ ይንከዋለላሉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ፍፁም ፊት ለፊቱ የቆመዉን ፍቃዱን ሲያየዉ እያዘነ አይቶ እንዳላየዉ መስሎ ሊያልፈዉ ሲል ፍቃዱ ከጀርባዉ ደርሶበት
"የት ለመድረስ ነዉ የምታነክሰዉ"
ይለዋል በንቀት እግር እግሩን እያየ
ፍፁም መልስ ሳይሰጠዉ መራመዱን ሲቀጥል ፍቃዱ ደግሞ ደርሶበት እየሳቀ
"ቤዛዊትን መቼም አታገኛትም የኔ ናት አንተ ዉሻ እያዋራሁክ ደሞ የምን ንቀት ነዉ ጥለሀኝ የምትሄደዉ..."
ፍፁም መታገስ አልቻለም ክራንቹን ወደ ሰማይ አንስቶ ፍቃዱ ላይ ሳያቋርጥ ማሳረፍ ጀመረ።
ሳያስበዉ በእልህ ፍቃዱን ክፉኛ ስለመታዉ መቆም ያቃተዉ ፍቃዱ ተዝለፍልፎ ወደቀ።
💫ይቀጥላል💫
ምዕራፍ #1 በዚህ ተጠናቋል ምዕራፍ #2 በቅርቡ እንጀምራለን እስከዛው በሌሎች ጣፋጭ ድርሰቶች እንቀጥላለን እስካሁን በሄደው ድርሰት ላይ ያሎትን አስተያየት አድርሱን
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ያልተቋጨ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በክፍለማርያም
የእረፍት ሰአት እንደተደወለ ግቢዉ በተማሪወች ጫጫታ ተሞላ እሮጠዉ ያልጠገቡ ህፃናት ከወዲህ ወድያ ይሯሯጣሉ ትንሽ የሚሻሉት ደግሞ ጥጋቸዉን ይዘዉ ጨዋታ ይጫወታሉ
በእድሜ እና ክፍል ከፍ ያሉት ተማሪዎች ሁሉም በየራሱ ሀሳብ ተዉጦ ገሚሱ ቆሞ ገሚሱ ተቀምጦ ያስባል የሚያወራም አለ።
ትንሳኤ ከጉዋደኛው ዮናስ አጠገብ ቢቀመጥም ሀሳቡ ያለዉ ግን ህሊና ጋር ነዉ አይኖቹን በማይታየዉ አየር ላይ ተክሎ እያሰበ ቆይቶ ፊቱ ላይ የጀግንነት የድፍረት ወኔ እየታየ
"የመጣው ይምጣ ዛሬማ እነግራታለሁ"
አለ እጁን ጨምድድ እያረገ
"እስቲ እናያለን"
ጉዋደኛዉ ዮናስ ትንሳኤን በሚያሳዝን አስተያየት እያየዉ
ይሄ ለመጀመርያ ግዜ አደለማ
እንደዚህ ሲለዉ ከአንዴም ሁለት ሶስቴ ትንሳኤ የወደዳትን ያፈቀራትን ህሊናን በድፍረት ዛሬ የልቤን እነግራታለሁ ብሎ እንደዛሬዉ ይፎክር እና ልክ ህሊና ከጉዋደኞቿ ጋር በእነሱ በኩል ስታልፍ ምንም እንዳልተፈጠረ አንገቱን ደፍቶ ላብ በላብ ሆኖ ያሳልፋታል መጨረሻም ጉዋደኛዉ ዮናስ
"አይ አንተ አፍቃሪ"
እያለ ሲስቅበት ይዉላል
"ዛሬ ግን የመጨረሻ ነው ወደድኩሽ እንጂ ሌላ ምንም አልላት ታየኛለህ አሁን"
አለ ትንሳኤ የህሊናን መምጣት በጉጉት እየጠበቀ
ህሊና ከጉዋደኞቿ ጋር እያወራች ወደ እነ ትንሳኤ አቅጣጫ እየመጣች ነዉ
ዮናስ የጉዋደኛዉን የትንሳኤን ድፍረት ለማየት እና መልሷን ለመስማት ከትንሳኤ ጎን ጥቂት ፈንጠር ብሎ ቆሞዋል
ህሊና ቀስ እያለች እየተራመደች በትንሳኤ አጠገብ ስታልፍ ደፍሮ እንደማያዋራት የገመተዉ ዮናስ
"አዋራት ምን ያስፈራሀል!"
ይለዋል ድፍረት ለመስጠት ይመስል የትንሳኤን ትከሻ በእጆቹ ነካ ነካ እያደረገ
"ዛሬ ይቅር ነገ ልንገራት"
አለና ትንሳኤ ከሩጫ ባልተናነሰ እርምጃ ወደ ክፍል ተመልሶ ገባ ዮናስም እየሳቀ ተከተለዉ።
ትንሳኤ 18 አመት ከሞላው ወር አይሞላዉም ከቤት ወጥቶ የማያዉቅ ልጅ ነበር የእናቱ ህይወት ካለፈ በኋላ ግን አባቱ ሌላ ፀባይ ስላመጣ እሱንም ችላ ስላለዉ ወጣ ወጣ ማለት ጀምሯል ማንም የሚቆጣጠረዉ የሚናገረዉ
ሰው የለም ቢሆንም በትምህርቱ ጎበዝ ነዉ ጭንቅላቱ ፈጣን ነገሮችን ቶሎ የመቀበል ችሎታ አላቸዉ።
ከትምህርት ቤት ሲለቀቁ ትንሳኤ እና ዮናስ በጠዋቱ ጉዳይ እያወሩ ከትምህርት ቤቱ እየወጡ
ነው
"የኛ ደፋር እኔ እኮ የሚያስቀኝ አሁን ዛሬ እነግራታለሁ እያልክ የምትምለዉ ነገር ነው "
ሲል ዮናስ ትንሳኤን ገፍተር እያረገዉ እየቀለደበት
ትንሳኤ በአይምሮዉ ወደ ኋላ ሄዶ አስታወሰ የሆነ ቀንም አዋራታለሁ ብሎ ምሎ ተገዝቶ ህሊና አጠገቡ ስትደርስ አደለም መናገር መላ ሰዉነቱም የሚሰሩም አይመስሉም
በሩቁ እየሰረቀ ያያታል እንጂ አይን ካይን እንዲገጣጠሙ እራሱ አይፈልግም እንደሚፈራት አስታዉሶ
እሱም ትንሽ እንደመሳቅ አለና
"ለምን አሁን ወደ ቤት ስትወጣ አላናግራትም"
ትከሻው ላይ ያነገበዉን ቦርሳ ወደ ዮናስ እንዲይዝለት እየሰጠዉ
"የማታረገዉን አረ አታስቀኝ አርፈን ወደ ቤት እንሂድ እርቦኛል"
ዮናስ አልይዝም አለዉ ቦርሳዉን
"እንደዉም አሁን ብነግራት ጥሩ ነዉ ምክንያቱም ነገ ቅዳሚ ከነገ ወድያ እሁድ አንተያይም አላፍራትም እስዋም አስባበት መልሷን ትነግረኛለች "
ትንሳኤ ይሄን ሲል ዮናስ አዘነለት በልቡ ምን አይነት ፍቅር ቢይዘዉ ነዉ እያለ
ከትምህርት ቤቱ መዉጫ በር ፊት ለፊት ቆመዉ የህሊናን መዉጣት በአይናቸዉ እየፈለጉ ነዉ
ትንሳኤ አይኖቹን ወደ ትምህርት ቤቱ ህንፃ ሲወረዉር ህሊና በደረጃ እየወረደች ተመለከታት አይኖቹ ፈዘዉ እያያት ነዉ በድንገት እሷም አየችዉ ተያዩ አይኖቹን ሰበር አድርጎ ድጋሜ አያት አሁንም እያየችዉ ነዉ የልብ ልብ ተሰማዉ
"ትዉረድ ብቻ ማን እንደሆንኩ አሳይሀለዉ "
ፊቱን አበስ አበስ አፍንጫውን ነካ አርጎ በተጠንቀቅ ቆመ
ዮናስ ዝግ ባለድምፅ
"አሁን ካልነገርካት እኔ እነግርልሀለዉ አለው "
ትንሳኤ ደረቱን ነፋ እያደረገ
"እኔ ምን ሆኜ ነዉ አንተ የምትነግርልኝ"
አለና ደፈር ብሎ ከደረጃዉ ወርዳ ወደ መዉጫዉ በር ወደ ምትመጣዋ ህሊና መራመድ ጀመረ.....0
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በክፍለማርያም
የእረፍት ሰአት እንደተደወለ ግቢዉ በተማሪወች ጫጫታ ተሞላ እሮጠዉ ያልጠገቡ ህፃናት ከወዲህ ወድያ ይሯሯጣሉ ትንሽ የሚሻሉት ደግሞ ጥጋቸዉን ይዘዉ ጨዋታ ይጫወታሉ
በእድሜ እና ክፍል ከፍ ያሉት ተማሪዎች ሁሉም በየራሱ ሀሳብ ተዉጦ ገሚሱ ቆሞ ገሚሱ ተቀምጦ ያስባል የሚያወራም አለ።
ትንሳኤ ከጉዋደኛው ዮናስ አጠገብ ቢቀመጥም ሀሳቡ ያለዉ ግን ህሊና ጋር ነዉ አይኖቹን በማይታየዉ አየር ላይ ተክሎ እያሰበ ቆይቶ ፊቱ ላይ የጀግንነት የድፍረት ወኔ እየታየ
"የመጣው ይምጣ ዛሬማ እነግራታለሁ"
አለ እጁን ጨምድድ እያረገ
"እስቲ እናያለን"
ጉዋደኛዉ ዮናስ ትንሳኤን በሚያሳዝን አስተያየት እያየዉ
ይሄ ለመጀመርያ ግዜ አደለማ
እንደዚህ ሲለዉ ከአንዴም ሁለት ሶስቴ ትንሳኤ የወደዳትን ያፈቀራትን ህሊናን በድፍረት ዛሬ የልቤን እነግራታለሁ ብሎ እንደዛሬዉ ይፎክር እና ልክ ህሊና ከጉዋደኞቿ ጋር በእነሱ በኩል ስታልፍ ምንም እንዳልተፈጠረ አንገቱን ደፍቶ ላብ በላብ ሆኖ ያሳልፋታል መጨረሻም ጉዋደኛዉ ዮናስ
"አይ አንተ አፍቃሪ"
እያለ ሲስቅበት ይዉላል
"ዛሬ ግን የመጨረሻ ነው ወደድኩሽ እንጂ ሌላ ምንም አልላት ታየኛለህ አሁን"
አለ ትንሳኤ የህሊናን መምጣት በጉጉት እየጠበቀ
ህሊና ከጉዋደኞቿ ጋር እያወራች ወደ እነ ትንሳኤ አቅጣጫ እየመጣች ነዉ
ዮናስ የጉዋደኛዉን የትንሳኤን ድፍረት ለማየት እና መልሷን ለመስማት ከትንሳኤ ጎን ጥቂት ፈንጠር ብሎ ቆሞዋል
ህሊና ቀስ እያለች እየተራመደች በትንሳኤ አጠገብ ስታልፍ ደፍሮ እንደማያዋራት የገመተዉ ዮናስ
"አዋራት ምን ያስፈራሀል!"
ይለዋል ድፍረት ለመስጠት ይመስል የትንሳኤን ትከሻ በእጆቹ ነካ ነካ እያደረገ
"ዛሬ ይቅር ነገ ልንገራት"
አለና ትንሳኤ ከሩጫ ባልተናነሰ እርምጃ ወደ ክፍል ተመልሶ ገባ ዮናስም እየሳቀ ተከተለዉ።
ትንሳኤ 18 አመት ከሞላው ወር አይሞላዉም ከቤት ወጥቶ የማያዉቅ ልጅ ነበር የእናቱ ህይወት ካለፈ በኋላ ግን አባቱ ሌላ ፀባይ ስላመጣ እሱንም ችላ ስላለዉ ወጣ ወጣ ማለት ጀምሯል ማንም የሚቆጣጠረዉ የሚናገረዉ
ሰው የለም ቢሆንም በትምህርቱ ጎበዝ ነዉ ጭንቅላቱ ፈጣን ነገሮችን ቶሎ የመቀበል ችሎታ አላቸዉ።
ከትምህርት ቤት ሲለቀቁ ትንሳኤ እና ዮናስ በጠዋቱ ጉዳይ እያወሩ ከትምህርት ቤቱ እየወጡ
ነው
"የኛ ደፋር እኔ እኮ የሚያስቀኝ አሁን ዛሬ እነግራታለሁ እያልክ የምትምለዉ ነገር ነው "
ሲል ዮናስ ትንሳኤን ገፍተር እያረገዉ እየቀለደበት
ትንሳኤ በአይምሮዉ ወደ ኋላ ሄዶ አስታወሰ የሆነ ቀንም አዋራታለሁ ብሎ ምሎ ተገዝቶ ህሊና አጠገቡ ስትደርስ አደለም መናገር መላ ሰዉነቱም የሚሰሩም አይመስሉም
በሩቁ እየሰረቀ ያያታል እንጂ አይን ካይን እንዲገጣጠሙ እራሱ አይፈልግም እንደሚፈራት አስታዉሶ
እሱም ትንሽ እንደመሳቅ አለና
"ለምን አሁን ወደ ቤት ስትወጣ አላናግራትም"
ትከሻው ላይ ያነገበዉን ቦርሳ ወደ ዮናስ እንዲይዝለት እየሰጠዉ
"የማታረገዉን አረ አታስቀኝ አርፈን ወደ ቤት እንሂድ እርቦኛል"
ዮናስ አልይዝም አለዉ ቦርሳዉን
"እንደዉም አሁን ብነግራት ጥሩ ነዉ ምክንያቱም ነገ ቅዳሚ ከነገ ወድያ እሁድ አንተያይም አላፍራትም እስዋም አስባበት መልሷን ትነግረኛለች "
ትንሳኤ ይሄን ሲል ዮናስ አዘነለት በልቡ ምን አይነት ፍቅር ቢይዘዉ ነዉ እያለ
ከትምህርት ቤቱ መዉጫ በር ፊት ለፊት ቆመዉ የህሊናን መዉጣት በአይናቸዉ እየፈለጉ ነዉ
ትንሳኤ አይኖቹን ወደ ትምህርት ቤቱ ህንፃ ሲወረዉር ህሊና በደረጃ እየወረደች ተመለከታት አይኖቹ ፈዘዉ እያያት ነዉ በድንገት እሷም አየችዉ ተያዩ አይኖቹን ሰበር አድርጎ ድጋሜ አያት አሁንም እያየችዉ ነዉ የልብ ልብ ተሰማዉ
"ትዉረድ ብቻ ማን እንደሆንኩ አሳይሀለዉ "
ፊቱን አበስ አበስ አፍንጫውን ነካ አርጎ በተጠንቀቅ ቆመ
ዮናስ ዝግ ባለድምፅ
"አሁን ካልነገርካት እኔ እነግርልሀለዉ አለው "
ትንሳኤ ደረቱን ነፋ እያደረገ
"እኔ ምን ሆኜ ነዉ አንተ የምትነግርልኝ"
አለና ደፈር ብሎ ከደረጃዉ ወርዳ ወደ መዉጫዉ በር ወደ ምትመጣዋ ህሊና መራመድ ጀመረ.....0
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ያልተቋጨ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በክፍለማርያም
ወደ ህሊና አመራ ትንሳኤ ከደረጃ እየወረደች ወደሱ ትይዩ እየመጣችዉ ያለችውን ህሊናን ሲያያት ፊቱ እየቀላና ድንብርብሩ እየወጣ በር ላይ እየጠበቀዉ ወዳለዉ ጉዋደኛዉ ጋር ደርሶ
"ባክህ ፈራሁዋት አፍቃሪዉ ምናምን እያልክ ደሞ እንዳትሰድበኝ"
እያለ ቦርሳዉን ከጉዋደኛዉ ተቀብሎ ወደ ቤቱ አመራ።
ቅዳሜ እና እሁድን በጠዋት እየተነሳ ለሰኞ የፍቅር ጥያቄ ለማቅረብ እና እስዋ ፊት ሲደርስ ወንዳወንድ ለመምሰል ፑሽ አፕ ፑል አፕ በተጨማሪም ቤቱ ዉስጥ በስንሚንቶ በሰራዉ ክብደት ስፖርት ሲሰራ ፍርሀቱን ለማስወገድ እንደ እብድ መስታወት ፊት ቆሞ ሲለፈልፍ ሰኞ ደረሰ።
እንደወትሮዉ የህሊና ክፍል ከትንሳኤ ክፍል ቀጥሎ ስለሆነ ባንዲራ ተሰቅሎ ተማሪ ወደየ ክፍሉ ከገባ በኋላ አይኗን ሳያይ መዋል ስለማያስችለዉ ቀስ እያለ እየተራመደ ወደሱ ክፍል ከመግባቱ በፊት የህሊናን ክፍል በር አሻግሮ በአይኑ ህሊናን መፈለግ ጀመረ።
የቀረች መስሎት ሊበሳጭ ነበር ነገር ግን ፊቷን አዙራ ወሬ እያወራች ስለነበር ነዉ።
መጥታለች በርቀት ሲመለከታት ደስ አለዉ ደስታው በምንም የማይተካ ነበር ፈገግ እያለ በልቡ ስላያት ተመስጌን መጥታለች እያለ ወደሱ ክፍል ሲገባ ጉዋደኞቹ በሳቅ ተቀበሉት
ከዮናስ ጎን የተቀመጠዉ እዮብ በትንሳኤ አፍቅሮ እንደዚህ መሆን አይስቅበትም ምን አልባት እሱም ከሌላ ፍቅር ሊኖርበት ይችላል ዮናስም ቢሆን በሀሪዉ ሆኖ የትንሳኤ ሁኔታ ስለሚገርመዉ ይስቅበታል እንጂ ጨክኖበት አልነበረም።
የህሊና ጉዋደኞች እነ ትንሳኤ ክፍል ስላሉ ሁሌ ህሊና ምሳ ለመብላት እነሱጋር ትመጣለች ትንሳኤም መጀመርያ በህሊና ፍቅር የወደቀዉ እሷ ስትመላለስ አይቷት ነዉ
ቀኑን ያስታዉሰዋል ምሳ ስዓት ላይ አሸናፊ የሚባሉ አብሮት አንድ ዴስክ ላይ የሚቀመጥ ተማሪ በስልኩ ሙዚቃ ከፍቶ ነበር
"ለምን አየኝ አለች ሳያት እሷን ብቻ
መዉደዴን ስነግራት አርጋዉ የጥላቻ.."
እያለ የሚቀጥል የመስፍን በቀለን ዘፈን ህሊና ቦርሳ አንግባ በምን እንደምትስቅ ባያዉቅም አነስአነስ ያሉ ነጭ ጥርሶቿን እያሳየች ወደነትንሳኤ ክፍል ገባች።
ወደ ክፍሉ ብቻ አደለም የገባችዉ እንደሙዚቃዉ በልቡ ግጥምና ዜማዋ ሳቋና ሁሉነገሯ ልቡ ዉስጥ ገባ።
ዛሬም ምሳ ስዓት ሲደወል ጉዋደኞቹ
"እንዉጣ"
ቢሉትም በልቡ ያሰበዉ ነገር ስለነበር
"አልወጣም የምፅፈዉ ነገር አለ"
ሲላቸዉ ጉዋደኞቹ ጥለዉት ወጡ
ትንሳኤ ጠዋት ቁርስ በልቶ ከቤቱ ስላልወጣ ሆዱ የርሀብ ጥያቄ እያሰማ ነበር
ህሊና ወደ ጉዋደኞቿ ክፍል ስትገባ ትንሳኤ ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ በረንዳ ወጥቷ በልታ እስክትጨርስ ሠንጎማለል ጀመረ።
እርቦታል ቤቱ ቅርብ ስለነበር ሄዶ መብላት ይችላል ነገር ግን ልቡ ዉስጥ ያለዉን ለመናገር ቻል አርጎ ከአሁን አሁን በልተዉ ጨረሱ እያለ በአይኑም ለማረጋገጥ እያያቸዉ ቆይቶ በልታ ጨርሳ እጇን ታጥባ እንደጨረሰች።
ለመጥራት ፈልጎ እንዴት መጥራት እንዳለበት ግራ ገብቶት ለጉዋደኞቹ እንደለመደዉ በቅርብ እርቀት ላይ ሆና አፉዋጨላት ደፋር ደፋር እያጫወተዉ ነበር።
ህሊና ዞራ እያየችዉ እኔን ነዉ ለማለት ሌባ ጣቷን ወደ ደረቷ አስጠግታ ስታሳየዉ አዎ ለማለት አንገቱን ከላይ ወደታች እየነቀነቀ በእጆቹ ጠራት
"አንዴ መጣሁ"
አለችዉና ወደ ጉዋደኞቿ ተመለሰች
ትንሳኤ ፍርሀት አይን አዉጥቶ ሂድ ሂድ ቢለዉም ቅዳሜና እሁድ የለፋበት ስፖርት ጥቂት ወኔ ሰጥቶት ደረቱን ነፍቶ ጠበቃት አጠገቡ ህሊና
"አቤት"
ብላ ስትጠጋዉ ግን ተንፍሶ ጥቂት ዝም አለና
እጁን እየዘረጋ
"ትንሳኤ"
አላት ስሙን ለመናገር እየፈለገ
"ህሊና"
ብላዉ የሚነግራትን ለመስማት አይን አይኑን አየችዉ
ትንሳኤ አይኗን እያየ በልቡ
"አቤት ሲያምር ደሞ የሆነ የሚያሳዝን ነገር አላት "
ብሎ በድንጋጤ ሊያዋራት አፉን ከፈተ
"ካየሁሽ ቀን ጀምሮ እወድሻለሁ"
የማይባል ነገር አለ
መሸወዱ አመታት አልፎ ነዉ የገባዉ እንዴት አዉርተሀት በደንብ እንኳን አይታህ የማታዉቅ ሴትን እንደዚህ ይባላል
💫ይቀጥላል 💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በክፍለማርያም
ወደ ህሊና አመራ ትንሳኤ ከደረጃ እየወረደች ወደሱ ትይዩ እየመጣችዉ ያለችውን ህሊናን ሲያያት ፊቱ እየቀላና ድንብርብሩ እየወጣ በር ላይ እየጠበቀዉ ወዳለዉ ጉዋደኛዉ ጋር ደርሶ
"ባክህ ፈራሁዋት አፍቃሪዉ ምናምን እያልክ ደሞ እንዳትሰድበኝ"
እያለ ቦርሳዉን ከጉዋደኛዉ ተቀብሎ ወደ ቤቱ አመራ።
ቅዳሜ እና እሁድን በጠዋት እየተነሳ ለሰኞ የፍቅር ጥያቄ ለማቅረብ እና እስዋ ፊት ሲደርስ ወንዳወንድ ለመምሰል ፑሽ አፕ ፑል አፕ በተጨማሪም ቤቱ ዉስጥ በስንሚንቶ በሰራዉ ክብደት ስፖርት ሲሰራ ፍርሀቱን ለማስወገድ እንደ እብድ መስታወት ፊት ቆሞ ሲለፈልፍ ሰኞ ደረሰ።
እንደወትሮዉ የህሊና ክፍል ከትንሳኤ ክፍል ቀጥሎ ስለሆነ ባንዲራ ተሰቅሎ ተማሪ ወደየ ክፍሉ ከገባ በኋላ አይኗን ሳያይ መዋል ስለማያስችለዉ ቀስ እያለ እየተራመደ ወደሱ ክፍል ከመግባቱ በፊት የህሊናን ክፍል በር አሻግሮ በአይኑ ህሊናን መፈለግ ጀመረ።
የቀረች መስሎት ሊበሳጭ ነበር ነገር ግን ፊቷን አዙራ ወሬ እያወራች ስለነበር ነዉ።
መጥታለች በርቀት ሲመለከታት ደስ አለዉ ደስታው በምንም የማይተካ ነበር ፈገግ እያለ በልቡ ስላያት ተመስጌን መጥታለች እያለ ወደሱ ክፍል ሲገባ ጉዋደኞቹ በሳቅ ተቀበሉት
ከዮናስ ጎን የተቀመጠዉ እዮብ በትንሳኤ አፍቅሮ እንደዚህ መሆን አይስቅበትም ምን አልባት እሱም ከሌላ ፍቅር ሊኖርበት ይችላል ዮናስም ቢሆን በሀሪዉ ሆኖ የትንሳኤ ሁኔታ ስለሚገርመዉ ይስቅበታል እንጂ ጨክኖበት አልነበረም።
የህሊና ጉዋደኞች እነ ትንሳኤ ክፍል ስላሉ ሁሌ ህሊና ምሳ ለመብላት እነሱጋር ትመጣለች ትንሳኤም መጀመርያ በህሊና ፍቅር የወደቀዉ እሷ ስትመላለስ አይቷት ነዉ
ቀኑን ያስታዉሰዋል ምሳ ስዓት ላይ አሸናፊ የሚባሉ አብሮት አንድ ዴስክ ላይ የሚቀመጥ ተማሪ በስልኩ ሙዚቃ ከፍቶ ነበር
"ለምን አየኝ አለች ሳያት እሷን ብቻ
መዉደዴን ስነግራት አርጋዉ የጥላቻ.."
እያለ የሚቀጥል የመስፍን በቀለን ዘፈን ህሊና ቦርሳ አንግባ በምን እንደምትስቅ ባያዉቅም አነስአነስ ያሉ ነጭ ጥርሶቿን እያሳየች ወደነትንሳኤ ክፍል ገባች።
ወደ ክፍሉ ብቻ አደለም የገባችዉ እንደሙዚቃዉ በልቡ ግጥምና ዜማዋ ሳቋና ሁሉነገሯ ልቡ ዉስጥ ገባ።
ዛሬም ምሳ ስዓት ሲደወል ጉዋደኞቹ
"እንዉጣ"
ቢሉትም በልቡ ያሰበዉ ነገር ስለነበር
"አልወጣም የምፅፈዉ ነገር አለ"
ሲላቸዉ ጉዋደኞቹ ጥለዉት ወጡ
ትንሳኤ ጠዋት ቁርስ በልቶ ከቤቱ ስላልወጣ ሆዱ የርሀብ ጥያቄ እያሰማ ነበር
ህሊና ወደ ጉዋደኞቿ ክፍል ስትገባ ትንሳኤ ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ በረንዳ ወጥቷ በልታ እስክትጨርስ ሠንጎማለል ጀመረ።
እርቦታል ቤቱ ቅርብ ስለነበር ሄዶ መብላት ይችላል ነገር ግን ልቡ ዉስጥ ያለዉን ለመናገር ቻል አርጎ ከአሁን አሁን በልተዉ ጨረሱ እያለ በአይኑም ለማረጋገጥ እያያቸዉ ቆይቶ በልታ ጨርሳ እጇን ታጥባ እንደጨረሰች።
ለመጥራት ፈልጎ እንዴት መጥራት እንዳለበት ግራ ገብቶት ለጉዋደኞቹ እንደለመደዉ በቅርብ እርቀት ላይ ሆና አፉዋጨላት ደፋር ደፋር እያጫወተዉ ነበር።
ህሊና ዞራ እያየችዉ እኔን ነዉ ለማለት ሌባ ጣቷን ወደ ደረቷ አስጠግታ ስታሳየዉ አዎ ለማለት አንገቱን ከላይ ወደታች እየነቀነቀ በእጆቹ ጠራት
"አንዴ መጣሁ"
አለችዉና ወደ ጉዋደኞቿ ተመለሰች
ትንሳኤ ፍርሀት አይን አዉጥቶ ሂድ ሂድ ቢለዉም ቅዳሜና እሁድ የለፋበት ስፖርት ጥቂት ወኔ ሰጥቶት ደረቱን ነፍቶ ጠበቃት አጠገቡ ህሊና
"አቤት"
ብላ ስትጠጋዉ ግን ተንፍሶ ጥቂት ዝም አለና
እጁን እየዘረጋ
"ትንሳኤ"
አላት ስሙን ለመናገር እየፈለገ
"ህሊና"
ብላዉ የሚነግራትን ለመስማት አይን አይኑን አየችዉ
ትንሳኤ አይኗን እያየ በልቡ
"አቤት ሲያምር ደሞ የሆነ የሚያሳዝን ነገር አላት "
ብሎ በድንጋጤ ሊያዋራት አፉን ከፈተ
"ካየሁሽ ቀን ጀምሮ እወድሻለሁ"
የማይባል ነገር አለ
መሸወዱ አመታት አልፎ ነዉ የገባዉ እንዴት አዉርተሀት በደንብ እንኳን አይታህ የማታዉቅ ሴትን እንደዚህ ይባላል
💫ይቀጥላል 💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1👍1
#ያልተቋጨ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...እንዴት ይባላል
ህሊና ደንገጥ ብላ አየችዉ እብድም ሳይመስላይ አይቀርም ፊቷ ላይ የመደንገጥ እና የመገረም የሚመስል ድባብ ይታይባታል ቶሎ ለመራቅ አስባ አፏ ላይ የመጣላትን
"ጉዋደኛ አለኝ"
ብላዉ ጥላዉ ወደ ጉዋደኞቿ ገባች።
የዛን ለት ወድያዉ እሷ ጥላዉ ስትገባ ደብተሩን እንኳን ሳይዝ እየተበሳጨ እየተመናቀረ ከትምህርት ቤቱ ግቢ ወጣ
ግራ የተጋባ ስሜት መናገሩ የልቡን መተንፈሱ ቢቀለዉም የመለሰችለት መልስ ያሳየችዉ ፊት ግን አስከፍቶታል
አፍቃሪ የሚጠብቀዉ እንደልቡ ፍላጎት ህልሙ ተሳክቶ ማየት ነዉ
ህይወት ግን ወጥንቅጧ የበዛ ስለሆነ አንዳንዴ በአንድ ወገን ያለ ፍቅር ለብቻዉ እንደሻማ በርቶ ይቀልጣል እንጂ አይሰምርም
መንገድ ላይ እየተሪመደ አንድ መንገድ ዳር የተቀመጠ ሲጋራ የሚያጨስ ከትንሳኤ እድሜ የሚበልጥ ልጅ
"ና" ብሎ ጠራዉ
ትንሳኤ እየተወዛገበ
"አቤት" እያለ ተጠጋዉ
"ስንት ብር ይዘሀል "
እያለ ልጁ ቆመ
ትንሳኤ ለራሱ ከባድ የፍቅር ረመጥ ዉስጥ ነዉ አደለም የማንም ጉልበተኛ ነኝ ባይ
"ና ያለህን አምጣ" ብሎት
ትንሳኤ ሳያንገራግር ወደ ልጁ ቦክስ ሰደደ ልጁም ወደ ትንሳኤ የመልስ ምት ላከ ገላጋይ ባይገባ ሁለቱም ይጎዳዱ ነበር። ትንሳኤን ሲያገላግሉ የያዙት ሰወች
"ምን አይነት ልብ ነዉ ያለህ ከታላቅህ ጋር ትጣላለህ"
እያሉ ሲመክለሩት የልብ ልብ ተሰምቶት ድጋሜ ካልተጣላሁ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ቢልም ጉልቤ ለመሆን የሞከረዉ ልጅ ግረግሩ እና የትንሳኤ ፉከራ ስላልጣመዉ ከአካባቢዉ ተሰወረ።
በነጋታዉ ትንሳኤ ወደ ክፍል እንደገባ ዮናስ በፈገግታ ተቀበለዉ
"ጀግናችን ወሬ አይደበቅም ስታዋራት ሰው አይቶካል ምን ተፈጠረ ጭዌዉን እንደወረደ"
ሲለዉ ሌሎች ጉዋደኞቹም በተሰበሰቡበት ትንሳኤ የተፈጠረዉን በሙሉ ነገራቸዉ ዮናስ ተበሳጨ
"አረ አፍቃሪዉ ተበልተሀል የሆነ በሙድ አትገባላትም ነበር ዝም ብለህ እወድሻለሁ አረ አይነፌክስ"
ትንሳኤ ላይ የእዉነት ወረደበት ተናዶ
ለትንሳኤ መልካም ስለሚያስብ ነበር
ምክንያቱም ሲጨነቅ ስለሷ ሲያስብ የእዉነት እንደወደዳት አስተዉሎታል
ትንሳኤም ግልፅ ስለሚያወራ ቀንም ማታም ስለሷ ቢያወራ ስለማይጠግብ ሁሉንም ስሜቱን ሳይደብቅ ይነግራቸዉ ስለነበረ ነዉ
በተቃራኒዉ እዮብ
"ዋናዉ ማዋራትህ ነዉ አንበሳ እኔኮ ትመቺኛለሽ"
ሲል በእጁ የትንሳኤን ትከሻ ከነካ በኃላ
"በቅርቡ የሆነ ብር አገኛለሁ እጋብዝሀለዉ ጭንቀትህንም ትረሳለህ"
ሲል አከለበት
ታሪኩ እንዲህ እያለ ቀጠለ ትንሳኤ እወድሻለሁ ካላት በኋላ ህሊና ገና ከሩቁ ትንሳኤን ካየችዉ መሸሽ መንገድ መቀየር በተለይ የትንሳኤ ክፍል ካሉት ጉዋደኞቿ ጋር ትንሳኤን ላለማየት እሱ ክፍል መምጣት ተወች
በተለይ የጉዋደኞቿ አይን ትንሳኤ ላይ በረታበት በአይናቸዉ ያወራሉ ሁሌ ሲያያቸወ እያሽሟጠጡበት እየተረቡት ይመስለዋል አንዳንዴ ወንድ ቢሆኑና ብደባደባቸዉ ብሎ ያስባል
በአይናቸዉ ጥንብእርኩሱን ያወጡት ጀመር።
ህሊናም ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ተጠየፈችዉ ትሸሸዉ ጀመር
ትንሳኤ ፍቅር ብሎ የጉዋደኛዉን የዮናስን ምክር ሳይሰማ ዘባርቆ የተምታታ ስሜት ዉስጥ ገብቶ
በተቀመጠበት ስዓት እዮብ
"ፈታ ላርግህ ወንድሜ"
ብሎ ይዞት ከትምህርት ቤቱ ግቢ ምሳ ሰአት ላይ ይዞት ወጣ
በአቅራቢያቸዉ ካለ ጠላ ቤት ገብተዉ የሚጣፍጥ ድንች በሚጥሚጣ ከበሉ በኋላ ጠላ በጣሳ ይዘዉ እየጠጡ ተቀመጡ
ትንሳኤ ስለ ህሊና መለዋወጥ በልቡ እያሰበ ጠላዉን መጎንጨት ተያያዘዉ ወደ ሞቅታ ሲገባ ተነስቶ ቆሞ
የለበሰዉን የትምህርት ቤቱን ሸሚዝ አዉልቆ በቲሸርት ሆኖ ወደ ትምህርት ቤቱ በፍጥነት መራመድ ጀመረ
ሁኔታዉ ያልጣመው እዮብ ሂሳብ ከፍሎ እየሮጠ ተከተለው
ትንሳኤ ደረጃ ወጥቶ ወደ ህሊና ክፍል ሊደርስ ሲል አፍንጫዉን ነካ አርጎ አየር ከሳበ በኋላ
ወደ ህሊና ክፍል ስትት ብሎ ገባ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...እንዴት ይባላል
ህሊና ደንገጥ ብላ አየችዉ እብድም ሳይመስላይ አይቀርም ፊቷ ላይ የመደንገጥ እና የመገረም የሚመስል ድባብ ይታይባታል ቶሎ ለመራቅ አስባ አፏ ላይ የመጣላትን
"ጉዋደኛ አለኝ"
ብላዉ ጥላዉ ወደ ጉዋደኞቿ ገባች።
የዛን ለት ወድያዉ እሷ ጥላዉ ስትገባ ደብተሩን እንኳን ሳይዝ እየተበሳጨ እየተመናቀረ ከትምህርት ቤቱ ግቢ ወጣ
ግራ የተጋባ ስሜት መናገሩ የልቡን መተንፈሱ ቢቀለዉም የመለሰችለት መልስ ያሳየችዉ ፊት ግን አስከፍቶታል
አፍቃሪ የሚጠብቀዉ እንደልቡ ፍላጎት ህልሙ ተሳክቶ ማየት ነዉ
ህይወት ግን ወጥንቅጧ የበዛ ስለሆነ አንዳንዴ በአንድ ወገን ያለ ፍቅር ለብቻዉ እንደሻማ በርቶ ይቀልጣል እንጂ አይሰምርም
መንገድ ላይ እየተሪመደ አንድ መንገድ ዳር የተቀመጠ ሲጋራ የሚያጨስ ከትንሳኤ እድሜ የሚበልጥ ልጅ
"ና" ብሎ ጠራዉ
ትንሳኤ እየተወዛገበ
"አቤት" እያለ ተጠጋዉ
"ስንት ብር ይዘሀል "
እያለ ልጁ ቆመ
ትንሳኤ ለራሱ ከባድ የፍቅር ረመጥ ዉስጥ ነዉ አደለም የማንም ጉልበተኛ ነኝ ባይ
"ና ያለህን አምጣ" ብሎት
ትንሳኤ ሳያንገራግር ወደ ልጁ ቦክስ ሰደደ ልጁም ወደ ትንሳኤ የመልስ ምት ላከ ገላጋይ ባይገባ ሁለቱም ይጎዳዱ ነበር። ትንሳኤን ሲያገላግሉ የያዙት ሰወች
"ምን አይነት ልብ ነዉ ያለህ ከታላቅህ ጋር ትጣላለህ"
እያሉ ሲመክለሩት የልብ ልብ ተሰምቶት ድጋሜ ካልተጣላሁ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ቢልም ጉልቤ ለመሆን የሞከረዉ ልጅ ግረግሩ እና የትንሳኤ ፉከራ ስላልጣመዉ ከአካባቢዉ ተሰወረ።
በነጋታዉ ትንሳኤ ወደ ክፍል እንደገባ ዮናስ በፈገግታ ተቀበለዉ
"ጀግናችን ወሬ አይደበቅም ስታዋራት ሰው አይቶካል ምን ተፈጠረ ጭዌዉን እንደወረደ"
ሲለዉ ሌሎች ጉዋደኞቹም በተሰበሰቡበት ትንሳኤ የተፈጠረዉን በሙሉ ነገራቸዉ ዮናስ ተበሳጨ
"አረ አፍቃሪዉ ተበልተሀል የሆነ በሙድ አትገባላትም ነበር ዝም ብለህ እወድሻለሁ አረ አይነፌክስ"
ትንሳኤ ላይ የእዉነት ወረደበት ተናዶ
ለትንሳኤ መልካም ስለሚያስብ ነበር
ምክንያቱም ሲጨነቅ ስለሷ ሲያስብ የእዉነት እንደወደዳት አስተዉሎታል
ትንሳኤም ግልፅ ስለሚያወራ ቀንም ማታም ስለሷ ቢያወራ ስለማይጠግብ ሁሉንም ስሜቱን ሳይደብቅ ይነግራቸዉ ስለነበረ ነዉ
በተቃራኒዉ እዮብ
"ዋናዉ ማዋራትህ ነዉ አንበሳ እኔኮ ትመቺኛለሽ"
ሲል በእጁ የትንሳኤን ትከሻ ከነካ በኃላ
"በቅርቡ የሆነ ብር አገኛለሁ እጋብዝሀለዉ ጭንቀትህንም ትረሳለህ"
ሲል አከለበት
ታሪኩ እንዲህ እያለ ቀጠለ ትንሳኤ እወድሻለሁ ካላት በኋላ ህሊና ገና ከሩቁ ትንሳኤን ካየችዉ መሸሽ መንገድ መቀየር በተለይ የትንሳኤ ክፍል ካሉት ጉዋደኞቿ ጋር ትንሳኤን ላለማየት እሱ ክፍል መምጣት ተወች
በተለይ የጉዋደኞቿ አይን ትንሳኤ ላይ በረታበት በአይናቸዉ ያወራሉ ሁሌ ሲያያቸወ እያሽሟጠጡበት እየተረቡት ይመስለዋል አንዳንዴ ወንድ ቢሆኑና ብደባደባቸዉ ብሎ ያስባል
በአይናቸዉ ጥንብእርኩሱን ያወጡት ጀመር።
ህሊናም ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ተጠየፈችዉ ትሸሸዉ ጀመር
ትንሳኤ ፍቅር ብሎ የጉዋደኛዉን የዮናስን ምክር ሳይሰማ ዘባርቆ የተምታታ ስሜት ዉስጥ ገብቶ
በተቀመጠበት ስዓት እዮብ
"ፈታ ላርግህ ወንድሜ"
ብሎ ይዞት ከትምህርት ቤቱ ግቢ ምሳ ሰአት ላይ ይዞት ወጣ
በአቅራቢያቸዉ ካለ ጠላ ቤት ገብተዉ የሚጣፍጥ ድንች በሚጥሚጣ ከበሉ በኋላ ጠላ በጣሳ ይዘዉ እየጠጡ ተቀመጡ
ትንሳኤ ስለ ህሊና መለዋወጥ በልቡ እያሰበ ጠላዉን መጎንጨት ተያያዘዉ ወደ ሞቅታ ሲገባ ተነስቶ ቆሞ
የለበሰዉን የትምህርት ቤቱን ሸሚዝ አዉልቆ በቲሸርት ሆኖ ወደ ትምህርት ቤቱ በፍጥነት መራመድ ጀመረ
ሁኔታዉ ያልጣመው እዮብ ሂሳብ ከፍሎ እየሮጠ ተከተለው
ትንሳኤ ደረጃ ወጥቶ ወደ ህሊና ክፍል ሊደርስ ሲል አፍንጫዉን ነካ አርጎ አየር ከሳበ በኋላ
ወደ ህሊና ክፍል ስትት ብሎ ገባ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍1
#ያልተቋጨ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ስተት ብሎ ገባ ህሊና ጥግ ላይ ወሬ እያወራች ነበር ስታየዉ በትንሹ ደንገጥ ብላ አፈጠጠችበት
ትንሳኤ ፊት ለፊቷ ቆሞ እጁን ወደ ኋላ ማረጉን ሲያስተዉል አሁን የመጣሁት ልለምናት እንዳይመስላት አለና እጆቹን አፍታቶ የእስዋ ዴስክን አሰደግፏቸዉ ጎንበስ ብሎ ቆመ
ህሊና ምን ሆኖ ነዉ እያለች በመገረም ታየዋለች
"ምን ሆነሽ ነዉ ግን"
አላት ቆጣ ብሎ
"ምን ሆንኩ"
አለችዉ ለስለስ ባለ ዜማ ባለዉ አነጋገር
ትንሳኤ ለአፍታ የጎዋደኞቿ ግልምጫ የእሷ መደባበቅ የእሱ የፍቅር ጥያቄ አለመሳካት ከጠጣዉ መጠጥ ጋር ተደራርቦ
"የወደድኩሽ መስሎሽ ነዉ እንደዚህ የሚያረግሽ አልወድሽም እሺ አልወድሽም"
ጮክ ብሎ ተናገረ ጉዋደኛዉ እዮብ ደርሶ እንዳይመታት ይሄ እብድ እያለ ይዞት ሊወጣ ሲሞክር
ትንሳኤ አስቸገረ አፉ
"አልወድሽም አልወድሽም "
ይበልእንጂ አሁንም ልቡ ዉስጥ ናት
ህሊና ምን ነካዉ በሚል አስተያየት እያየችዉ ትንሳኤ በጉዋደኛዉ እየተጎተተ ወጣ።
ከዛን ቡሀላ ህሊና ጭራሽ ከአይኑም እየራቀች መጣች
ሁሌ ሲገባ ግን በእሷ ክፍል እያለፈ አንገቱን ሰገግ አርግ በአይኖቹ ሳይፈልጋት ክፍሉ አይገባም
የጉዋደኞቿም አይን አፈር ከመሬት የሚያበላ ነበር
በዛ ሁሉ መሀል ግን ጉዋደኞቹ ሲያስባት እና ሲያስታዉሳት በቀልድ እያሳቁ እያስረሱት በተለይ ጠጥቶ
"አልወድሽም አልወድሽም"
ብሎ የጮሀዉን እያነሱ እሱንም ሲያፅናኑት በአይን ብቻ ጠዋት እና ከትምህርት ቤት ሲለቀቁ ስትወጣ ተደብቆ እያያት አመቱ አልቆ ክረምት ሲገባ በልቡ ብቻ ይዞ እያሰባት ተቀመጠ
በዛን ክረምት ትንሳኤ ብዙ አይነት መፅሀፍቶችን ሲያነብ ከጉዋደኞቹም ጋር ሲያዝግ ከሴቶች ጋር መቀራረብ መነጋገር የመሳሰሉት ፍርሀቶቹ ዘበት ሆነዉ ጠፍተዉ
በሚቀጥለዉ አመት ትምህርት ሲጀምሩ ምላስ አርዝሞ ከትምህርቱ ቀንሶ ሌላ ሰዉ ሆኖ ገባ
ያልተቀየረዉ የህሊና ፍቅር ግን አሁንም ልቡ ዉስጥ ነበር ትምህርት ቤት ውስጥ መጀመርያ ከህሊና ጋር ሲተያዩ በረንዳ ላይ ቆማ ነበር
እንዳያት ደስ አለዉ ፈገግ እያለ ተጠጋትና
"እዚህ ምን ትሰርያለሽ ገብተሽ አትማሪም"
አላት ህሊና አይኖቿን ወደ ላይ አርጋ
"ምን አገባህ"
አለችዉ
"ዋ ስትፎርፊ እንዳላይሽ"
እያለ ቆመዉ ወደሚጠብቁት ጉዋደኞቹ አመራ።
የሆነቀን ምሳ ሰአት ናፍቃዉ ወደሷ ክፍል አመራ
አሁንም ቢሆን ግን ከሌላ ሴት ልጅ ጋር ሲሆን እንደሚያወራዉ ከበፊቱ ፍርሀቱ ቀንሷል እንጂ እሷ ጋር ሲደርስ ቃላት ይጠፉበታል ሲገባ ነጭ ወረቀት ላይ ስዕል እየሳለች አገኛት
"ቆይ እኔ ልሳልልሽ"
እያለ እስራሱን ከእሷ እጅ ተቀበላት ከጎኗ ያሉት ገዋደኞቿ እሷ እርሳሱን ለማስመለስ ስትሞክር እያዩ ይስቃሉ
ትንሳኤ በቆመበት ሳያስበዉ አፍንጫውን ሲነካ የደረቀ ን ጥ ከአፍንጫዉ ወድቆ ወረቀቱ ላይ አረፈ ህሊና
"እእይይይይይ"
እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ።
ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ስተት ብሎ ገባ ህሊና ጥግ ላይ ወሬ እያወራች ነበር ስታየዉ በትንሹ ደንገጥ ብላ አፈጠጠችበት
ትንሳኤ ፊት ለፊቷ ቆሞ እጁን ወደ ኋላ ማረጉን ሲያስተዉል አሁን የመጣሁት ልለምናት እንዳይመስላት አለና እጆቹን አፍታቶ የእስዋ ዴስክን አሰደግፏቸዉ ጎንበስ ብሎ ቆመ
ህሊና ምን ሆኖ ነዉ እያለች በመገረም ታየዋለች
"ምን ሆነሽ ነዉ ግን"
አላት ቆጣ ብሎ
"ምን ሆንኩ"
አለችዉ ለስለስ ባለ ዜማ ባለዉ አነጋገር
ትንሳኤ ለአፍታ የጎዋደኞቿ ግልምጫ የእሷ መደባበቅ የእሱ የፍቅር ጥያቄ አለመሳካት ከጠጣዉ መጠጥ ጋር ተደራርቦ
"የወደድኩሽ መስሎሽ ነዉ እንደዚህ የሚያረግሽ አልወድሽም እሺ አልወድሽም"
ጮክ ብሎ ተናገረ ጉዋደኛዉ እዮብ ደርሶ እንዳይመታት ይሄ እብድ እያለ ይዞት ሊወጣ ሲሞክር
ትንሳኤ አስቸገረ አፉ
"አልወድሽም አልወድሽም "
ይበልእንጂ አሁንም ልቡ ዉስጥ ናት
ህሊና ምን ነካዉ በሚል አስተያየት እያየችዉ ትንሳኤ በጉዋደኛዉ እየተጎተተ ወጣ።
ከዛን ቡሀላ ህሊና ጭራሽ ከአይኑም እየራቀች መጣች
ሁሌ ሲገባ ግን በእሷ ክፍል እያለፈ አንገቱን ሰገግ አርግ በአይኖቹ ሳይፈልጋት ክፍሉ አይገባም
የጉዋደኞቿም አይን አፈር ከመሬት የሚያበላ ነበር
በዛ ሁሉ መሀል ግን ጉዋደኞቹ ሲያስባት እና ሲያስታዉሳት በቀልድ እያሳቁ እያስረሱት በተለይ ጠጥቶ
"አልወድሽም አልወድሽም"
ብሎ የጮሀዉን እያነሱ እሱንም ሲያፅናኑት በአይን ብቻ ጠዋት እና ከትምህርት ቤት ሲለቀቁ ስትወጣ ተደብቆ እያያት አመቱ አልቆ ክረምት ሲገባ በልቡ ብቻ ይዞ እያሰባት ተቀመጠ
በዛን ክረምት ትንሳኤ ብዙ አይነት መፅሀፍቶችን ሲያነብ ከጉዋደኞቹም ጋር ሲያዝግ ከሴቶች ጋር መቀራረብ መነጋገር የመሳሰሉት ፍርሀቶቹ ዘበት ሆነዉ ጠፍተዉ
በሚቀጥለዉ አመት ትምህርት ሲጀምሩ ምላስ አርዝሞ ከትምህርቱ ቀንሶ ሌላ ሰዉ ሆኖ ገባ
ያልተቀየረዉ የህሊና ፍቅር ግን አሁንም ልቡ ዉስጥ ነበር ትምህርት ቤት ውስጥ መጀመርያ ከህሊና ጋር ሲተያዩ በረንዳ ላይ ቆማ ነበር
እንዳያት ደስ አለዉ ፈገግ እያለ ተጠጋትና
"እዚህ ምን ትሰርያለሽ ገብተሽ አትማሪም"
አላት ህሊና አይኖቿን ወደ ላይ አርጋ
"ምን አገባህ"
አለችዉ
"ዋ ስትፎርፊ እንዳላይሽ"
እያለ ቆመዉ ወደሚጠብቁት ጉዋደኞቹ አመራ።
የሆነቀን ምሳ ሰአት ናፍቃዉ ወደሷ ክፍል አመራ
አሁንም ቢሆን ግን ከሌላ ሴት ልጅ ጋር ሲሆን እንደሚያወራዉ ከበፊቱ ፍርሀቱ ቀንሷል እንጂ እሷ ጋር ሲደርስ ቃላት ይጠፉበታል ሲገባ ነጭ ወረቀት ላይ ስዕል እየሳለች አገኛት
"ቆይ እኔ ልሳልልሽ"
እያለ እስራሱን ከእሷ እጅ ተቀበላት ከጎኗ ያሉት ገዋደኞቿ እሷ እርሳሱን ለማስመለስ ስትሞክር እያዩ ይስቃሉ
ትንሳኤ በቆመበት ሳያስበዉ አፍንጫውን ሲነካ የደረቀ ን ጥ ከአፍንጫዉ ወድቆ ወረቀቱ ላይ አረፈ ህሊና
"እእይይይይይ"
እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ።
ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍1
#ያልተቋጨ
#ክፍል_አምስት (የመጨረሻ ክፍል)
#በክፍለማርያም
ህሊና
"አይይይይይይይ" እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ
አንዳንዴ ተዋረድ ካለህ እንደዚህ ነዉ
አጠገቧ ተቀምጦ እጆቹን ወደ ሰደርያዋ ኪስ በቀስታ ሰዶ ከኪሷ ሶፍት አወጣ
አንደኛዋ ጉዋደኛዋ አይታዉ ሳቀች ህሊናም እንደወሰደባት ስታዉቅ ተናዳ አፈጠጠችበት
ትንሳኤም በሶፍቱ አፍንጫዉን እያበሰ በመዋረዱ በልቡ በጣም እያዘነ ሲወጣ በር ላይ ዮናስ ጠበቀዉ
"ባክህ ተዋረድኩልህ"
አለዉ ትንሳኤ በንዴት ከንፈሩን ነክሶ
"ምን ተፈጠረ"
ሲል ዮናስ አፋጠጠዉ
"ደረቅ መሆኑ ጠቅሞኛል ...."
እያለ ትንሳኤ የተፈጠረዉን ነገረዉ ከዛን ቀን ጀምሮ ነገሮች በህሊናና በእሱ መሀል ሴጣን እንዳለ ተገነዘበ እየወደዳት እያፈቀራትም ቢሆን ሌላ ሌላ ነገር ዉስጥ ገባ
የሆነ ቀን ሲያገረሽበት ለጉዋደኛዉ
"ጥራልኝ ላዋራት ናፈቀችኝ"
አለዉ
"ምን ጣጣ አለዉ"
ተከተለኝ አለዉና ወደ ህሊና ክፍል አምርተዉ ትንሳኤ በረንዳ ሲቆም ደፋሩ ጉዋደኛዉ ህሊናን አቀፍ አርጎ እያዋራት ይዧት ከወጣ በኋላ
"ተነጋገሩ "
ብሏቸዉ ትንሳኤን እና ህሊናን አገናኝቷቸዉ ሄደ።
"የመጀመርያ ቀን ቦርሳ በትከሻሽ ይዘሽ እየሳቅሽ ስትገቢ ነዉ ያየሁሽ
ደሞ በግራ እጅሽ ነዉ የምትፅፊዉ አደል"
ትንሳኤ ሊያዋራት የመጣዉ ሌላ ቢሆንም የልቡን በቻለዉ ቋንቋ መናገር ቀጠለ
ነገር ግን የህሊና መልስ
"ጉዋደኛ አለኝ አንደዉም አሁን እራሱ ሰዉ አይቶኝ ካንተ ጋር መቆሜን እንዳይነግሩት"
አለችዉ
ሀሳቡ ተበታተነ እኔ ነኝ እንጂ እስዋ አትወደኝም ሲል አስቦ በልቡ እሳት እየነደደ ዉስጡ በንዴት ግሎ
"እሺ ስታገኚኝ ግን አትዝጊኝ ሰላምታ እንኳን"
"እሺ"
ብላዉ ጥላዉ ገባች
ነገር ግን አንዴ ታክሲ ስትጠብቅ ከሩቅ አይቷት በደስታ ክንፍ ብሎ ሲጠጋት እየገላመጠች እራቀችዉ
ተከትሏት ጥቂት ለማዋራት እየሞከረ ተከተላት ነገር ግን እሷ ማዋራት አልፈለገችም
ትንሳኤ አመታት አልፈዉም አሁንም እንደ መጀመርያዉ ቦርሳ ይዛ እየሳቀች ስትገባ ያለዉ ምስል አይምሮዉ ዉስጥ አለ ፍቅሯ አመታት አልፎ እንደ ትላንት ይታወሰዋል መልኳ አይኗ ሰዉነቷ አወራሯ ሁሉ ነገሯ አይረሳዉም
ማፍቀር ማለት የማያገኙትን ሰዉ በተስፋ እንደመጠበቅ ነዉ ስሜቱ ያማል ያስከፋል መንገዱ ዉስጥ ግን አይረሴ ታሪኮች አሉ
አንድ ቀን አጊንቷት ያለ ፍርሀት ያለ ሰቀቀን እንደ ጉዋደኛ እንኳን ቢያዋራት ህልሙ ነዉ አንዳንዶች ለቀልድ ተዋዉቀዉ ይጋባሉ አንዳንዶች የእዉነት አፍቅረዉ ያጣሉ አለም ትገርማለች ፍቅርም ይገርማል ይሄ ታሪክ ለትንሳኤ የህይወቱ ክፍል ለህሊና ተራ ወሬ ሊሆን ይችላል
ትንሳኤ በልቡ የያዘዉ ታሪክ ነዉ ህሊና የናቀችዉ ተራ ነገር
ትንሳኤ በህሊና መፍረድ አቁሟል ምክንያቱም ሰዉ የፍላጎቱ ዉጤት ነዉ
የእሷ ምርጫና ፍላጎት የራሷ ዉሳኔ ነዉ
💫አለቀ💫
ነገ በተለመደው ሰዓት #ህመም_ያዘለ_ፍቅርን #ምእራፍ_ሁለት እንጀምራለን እሰከዛው መልካም ቆይታ🙏
#ክፍል_አምስት (የመጨረሻ ክፍል)
#በክፍለማርያም
ህሊና
"አይይይይይይይ" እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ
አንዳንዴ ተዋረድ ካለህ እንደዚህ ነዉ
አጠገቧ ተቀምጦ እጆቹን ወደ ሰደርያዋ ኪስ በቀስታ ሰዶ ከኪሷ ሶፍት አወጣ
አንደኛዋ ጉዋደኛዋ አይታዉ ሳቀች ህሊናም እንደወሰደባት ስታዉቅ ተናዳ አፈጠጠችበት
ትንሳኤም በሶፍቱ አፍንጫዉን እያበሰ በመዋረዱ በልቡ በጣም እያዘነ ሲወጣ በር ላይ ዮናስ ጠበቀዉ
"ባክህ ተዋረድኩልህ"
አለዉ ትንሳኤ በንዴት ከንፈሩን ነክሶ
"ምን ተፈጠረ"
ሲል ዮናስ አፋጠጠዉ
"ደረቅ መሆኑ ጠቅሞኛል ...."
እያለ ትንሳኤ የተፈጠረዉን ነገረዉ ከዛን ቀን ጀምሮ ነገሮች በህሊናና በእሱ መሀል ሴጣን እንዳለ ተገነዘበ እየወደዳት እያፈቀራትም ቢሆን ሌላ ሌላ ነገር ዉስጥ ገባ
የሆነ ቀን ሲያገረሽበት ለጉዋደኛዉ
"ጥራልኝ ላዋራት ናፈቀችኝ"
አለዉ
"ምን ጣጣ አለዉ"
ተከተለኝ አለዉና ወደ ህሊና ክፍል አምርተዉ ትንሳኤ በረንዳ ሲቆም ደፋሩ ጉዋደኛዉ ህሊናን አቀፍ አርጎ እያዋራት ይዧት ከወጣ በኋላ
"ተነጋገሩ "
ብሏቸዉ ትንሳኤን እና ህሊናን አገናኝቷቸዉ ሄደ።
"የመጀመርያ ቀን ቦርሳ በትከሻሽ ይዘሽ እየሳቅሽ ስትገቢ ነዉ ያየሁሽ
ደሞ በግራ እጅሽ ነዉ የምትፅፊዉ አደል"
ትንሳኤ ሊያዋራት የመጣዉ ሌላ ቢሆንም የልቡን በቻለዉ ቋንቋ መናገር ቀጠለ
ነገር ግን የህሊና መልስ
"ጉዋደኛ አለኝ አንደዉም አሁን እራሱ ሰዉ አይቶኝ ካንተ ጋር መቆሜን እንዳይነግሩት"
አለችዉ
ሀሳቡ ተበታተነ እኔ ነኝ እንጂ እስዋ አትወደኝም ሲል አስቦ በልቡ እሳት እየነደደ ዉስጡ በንዴት ግሎ
"እሺ ስታገኚኝ ግን አትዝጊኝ ሰላምታ እንኳን"
"እሺ"
ብላዉ ጥላዉ ገባች
ነገር ግን አንዴ ታክሲ ስትጠብቅ ከሩቅ አይቷት በደስታ ክንፍ ብሎ ሲጠጋት እየገላመጠች እራቀችዉ
ተከትሏት ጥቂት ለማዋራት እየሞከረ ተከተላት ነገር ግን እሷ ማዋራት አልፈለገችም
ትንሳኤ አመታት አልፈዉም አሁንም እንደ መጀመርያዉ ቦርሳ ይዛ እየሳቀች ስትገባ ያለዉ ምስል አይምሮዉ ዉስጥ አለ ፍቅሯ አመታት አልፎ እንደ ትላንት ይታወሰዋል መልኳ አይኗ ሰዉነቷ አወራሯ ሁሉ ነገሯ አይረሳዉም
ማፍቀር ማለት የማያገኙትን ሰዉ በተስፋ እንደመጠበቅ ነዉ ስሜቱ ያማል ያስከፋል መንገዱ ዉስጥ ግን አይረሴ ታሪኮች አሉ
አንድ ቀን አጊንቷት ያለ ፍርሀት ያለ ሰቀቀን እንደ ጉዋደኛ እንኳን ቢያዋራት ህልሙ ነዉ አንዳንዶች ለቀልድ ተዋዉቀዉ ይጋባሉ አንዳንዶች የእዉነት አፍቅረዉ ያጣሉ አለም ትገርማለች ፍቅርም ይገርማል ይሄ ታሪክ ለትንሳኤ የህይወቱ ክፍል ለህሊና ተራ ወሬ ሊሆን ይችላል
ትንሳኤ በልቡ የያዘዉ ታሪክ ነዉ ህሊና የናቀችዉ ተራ ነገር
ትንሳኤ በህሊና መፍረድ አቁሟል ምክንያቱም ሰዉ የፍላጎቱ ዉጤት ነዉ
የእሷ ምርጫና ፍላጎት የራሷ ዉሳኔ ነዉ
💫አለቀ💫
ነገ በተለመደው ሰዓት #ህመም_ያዘለ_ፍቅርን #ምእራፍ_ሁለት እንጀምራለን እሰከዛው መልካም ቆይታ🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅርን
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
#በክፍለማርያም
ፀሀይዋ ለመጥለቅ ጥቂት ሰዐታት ይቀራታል እስዋን እየተመለከቱ ብዛት ያላቸዉ ወንዶች ግቢዉ ዉስጥ ከወዲህ ወድያ ይንጎማለላሉ።
ፍፁም በብቸኝነት ተቆራምቶ ከተቀመጠበት ጥግ ተነስቶ ቆመና ወደ ሰፊዉ ክፍል አምርቶ ወረቀት እና እስኪርቢቶ አንስቶ መፃፍ ጀመረ።
ለመጀመርያ ጊዜ ቤዛዊትን ያገኛት ቀን ሰአት ጠይቃዉ ስትሰድበዉ ታሪኩን እየፃፈ ከታሰረ ለመጀመርያ ጊዜ ፊቱ ላይ ፈገግታ ተነበበ መፃፉን አላቋረጠም የሚያስታዉሳቸዉን የእሱን እና የቤዛዊትን ታሪክ ወረቀቱ ላይ እየከተበዉ ነዉ።
ትምህርት ቤት ዉስጥ የጠቀሰችዉን ሲያስታዉስ ድምፅ አዉጥቶ መንከትከት ጀመረ ከጎኑ የነበሩት እስረኞች እየገላመጡት ከአጠገቡ ተነስተዉ እራቁት ማንም ሰዉ ያንተን ህመም እንዳንተ አያመዉም
ማንም ሰዉ አንተ ያሳለፍከዉ ከባድ ነገር ለእሱ ክብደቱ አይታወቀዉም
መሸከም ስትችል ተቋቁመሀዉ ስታልፍ ያበረታሀል እንጂ አቅቶህ ስትወድቅ የሚያነሳህ ውስን ነዉ።
መፃፉን እየቀጠለ ነዉ ቤዛዊት ፅፋ የምትሰጠዉን ወረቀቶች አሁንም ድረስ ያስታዉሳቸዋል
ህመሟን እብደቷን ሳያዉቅ ቀሚስሽ አጥሯል ሲላት ጠልፎ የሚጥል እረጅም ቀሚስ ለብሳ ቤቱ የመጣችዉንም አልረሳዉም አሁንም እንደታመመች አዉቆ ስላልተዋት ስላልራቃት በራሱ ደስተኛ ነዉ።
ቤዛዊትን ሲያስብ ፈገግታዋ የፊቷ እንቅስቃሴ አይኑ ላይ ይታየዋል ሳቋ በጆሮወቹ ዛሬም ያስተጋባሉ
ንዴትዋን ኩርፊያዋን ህመሟን ሲያስብ ብታናድደዉም ስለተላመዳቸዉ እንደ እንከኖቿም አይቆጥርባትም
የእሱን በድንገት በአጋጣሚ ፍቃዱ የሚባልን የተረገመን ፍጥረት በንዴት ተገፋፍቶ መግደሉን ሲያስብ ፀፀት መላ ሰዉነቱን እየወረረዉ የጀመረዉን ፅሁፍ አቁዋርጦ ማልቀስ ጀመረ።
ፍፁም እስር አልተመቸዉም ለነገሩ መታሰር ለማን ይመቻል ገና አሁን ወዳለበት የእስር ግቢ እንደገባ የሬሽን መዝገብ ዉስጥ ስሙ ስላልተካተተ ደረቅ ዳቦ ብቻ ቀምሶ ትራስ እያስፈለገዉ
ፍራሽ ላይ ጋደም አለ ለማሰብ ግዜ አላገኘም እራሱን ሀይለኛ ህመም እየተሰማዉ ነዉ።
ሰዉነቱ በትኩሳት ግሎ ነገር ግን ብርድብርድ እያለዉ እየተንቀጠቀጠ ለሊቱን እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ
የመከራ ለሊት ይረዝማል ከታሰረ ሳምንት ወራት የቆየ ይመስለዋል ጠዋት ለህክምና የእስር ቤቱ ግቢ ካለዉ ክሊኒክ ለመሄድ ቢሞክርም ወረፋ ስላለ እንዲታገስ
ስለተነገረዉ መራመድ እያቃተዉ በልቡ
"መሞቴ ነዉ"
እያለ እንደምንም ፍራሹ ላይ ወድቆ ለመተኛት ሞከረ።
ቤዛዊት አይምሮዋ እየተረጋጋ ሲመጣ እማማ ስንቅነሽን ለፍፁም ምግብ እንዲቋጥሩለት አርጋ በተዘበራረቀ ስሜት ዉስጥ ሆና እንባ እየተናነቃት ወደ ፍፁም አመራች
እስካሁን ፍፁም ፍቃዱን መግደሉን አላመነችም
"የማይሆን የማይታሰብ ነገር"
ትላለች ከአፏ እያመለጣት ስትራመድ
የእስር ቤቱ ግቢ መግቢያ ስትደርስ የልብ ምቷ መፍጠን ጀመረ
ፍፁምን ካየችዉ ቆይታለች በፖሊሶች ታጅቦ ሲያልፍ ካየችዉ ወድያ ምንም የምታስታዉሰዉ ነገር አልነበረም እድሜ ለእማማ ስንቅነሽ እና ለልጃቸዉ ለጌታቸዉ ስታስቸግር ስትረብሽ ተንከባክበዉ ለዛሬ እንድትበቃ ላገዟት
ዉስጥ ገብታ የምትፈልገዉን ሰዉ ስም ተናግራ ቆማ መጠበቅ ጀመረች።
ፍፁም አይኖቹ ቀልተዉ ደም መስለዋል በተኛበት ፍራሽ እንደሰመመን "ፍፁም ደምሴ"
እየተባለ ሲጠራ ይሰማዋል መነሳት ግን አልቻለም
በሞት እና በህይወት መሀል ያለ እየመሰለዉ ሲያጣጥር ቆይቶ የቤዛዊት ምስል ፊቱ ላይ ድቅን ስላለበት አይኖቹ እንባ አዝለዉ እንደምንም ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ
"ፍፁም ደምሴ ጠያቂ መጥቶሎታል"
የሚል ድምፅ ስለሰማ እያቃሰተ ወደ ዘመድ ጥየቃዉ ቦታዉ ለመሄድ መታገል ጀመረ።
ቤዛዊት እንደሆነች አስቀድሞ ልቡ አዉቆታል ጥቂት እንደተራመደ ግን የማጥወልወል ስሜት
ስለተሰማዉ ለመረጋጋት አስቦ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ ጨለማ እየታየዉ የነበረ ቢሆንም ቀስበቀስ ጨለማዉም ጠፍቶ እራሱን ስቶ ወድቆ ቀረ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
#በክፍለማርያም
ፀሀይዋ ለመጥለቅ ጥቂት ሰዐታት ይቀራታል እስዋን እየተመለከቱ ብዛት ያላቸዉ ወንዶች ግቢዉ ዉስጥ ከወዲህ ወድያ ይንጎማለላሉ።
ፍፁም በብቸኝነት ተቆራምቶ ከተቀመጠበት ጥግ ተነስቶ ቆመና ወደ ሰፊዉ ክፍል አምርቶ ወረቀት እና እስኪርቢቶ አንስቶ መፃፍ ጀመረ።
ለመጀመርያ ጊዜ ቤዛዊትን ያገኛት ቀን ሰአት ጠይቃዉ ስትሰድበዉ ታሪኩን እየፃፈ ከታሰረ ለመጀመርያ ጊዜ ፊቱ ላይ ፈገግታ ተነበበ መፃፉን አላቋረጠም የሚያስታዉሳቸዉን የእሱን እና የቤዛዊትን ታሪክ ወረቀቱ ላይ እየከተበዉ ነዉ።
ትምህርት ቤት ዉስጥ የጠቀሰችዉን ሲያስታዉስ ድምፅ አዉጥቶ መንከትከት ጀመረ ከጎኑ የነበሩት እስረኞች እየገላመጡት ከአጠገቡ ተነስተዉ እራቁት ማንም ሰዉ ያንተን ህመም እንዳንተ አያመዉም
ማንም ሰዉ አንተ ያሳለፍከዉ ከባድ ነገር ለእሱ ክብደቱ አይታወቀዉም
መሸከም ስትችል ተቋቁመሀዉ ስታልፍ ያበረታሀል እንጂ አቅቶህ ስትወድቅ የሚያነሳህ ውስን ነዉ።
መፃፉን እየቀጠለ ነዉ ቤዛዊት ፅፋ የምትሰጠዉን ወረቀቶች አሁንም ድረስ ያስታዉሳቸዋል
ህመሟን እብደቷን ሳያዉቅ ቀሚስሽ አጥሯል ሲላት ጠልፎ የሚጥል እረጅም ቀሚስ ለብሳ ቤቱ የመጣችዉንም አልረሳዉም አሁንም እንደታመመች አዉቆ ስላልተዋት ስላልራቃት በራሱ ደስተኛ ነዉ።
ቤዛዊትን ሲያስብ ፈገግታዋ የፊቷ እንቅስቃሴ አይኑ ላይ ይታየዋል ሳቋ በጆሮወቹ ዛሬም ያስተጋባሉ
ንዴትዋን ኩርፊያዋን ህመሟን ሲያስብ ብታናድደዉም ስለተላመዳቸዉ እንደ እንከኖቿም አይቆጥርባትም
የእሱን በድንገት በአጋጣሚ ፍቃዱ የሚባልን የተረገመን ፍጥረት በንዴት ተገፋፍቶ መግደሉን ሲያስብ ፀፀት መላ ሰዉነቱን እየወረረዉ የጀመረዉን ፅሁፍ አቁዋርጦ ማልቀስ ጀመረ።
ፍፁም እስር አልተመቸዉም ለነገሩ መታሰር ለማን ይመቻል ገና አሁን ወዳለበት የእስር ግቢ እንደገባ የሬሽን መዝገብ ዉስጥ ስሙ ስላልተካተተ ደረቅ ዳቦ ብቻ ቀምሶ ትራስ እያስፈለገዉ
ፍራሽ ላይ ጋደም አለ ለማሰብ ግዜ አላገኘም እራሱን ሀይለኛ ህመም እየተሰማዉ ነዉ።
ሰዉነቱ በትኩሳት ግሎ ነገር ግን ብርድብርድ እያለዉ እየተንቀጠቀጠ ለሊቱን እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ
የመከራ ለሊት ይረዝማል ከታሰረ ሳምንት ወራት የቆየ ይመስለዋል ጠዋት ለህክምና የእስር ቤቱ ግቢ ካለዉ ክሊኒክ ለመሄድ ቢሞክርም ወረፋ ስላለ እንዲታገስ
ስለተነገረዉ መራመድ እያቃተዉ በልቡ
"መሞቴ ነዉ"
እያለ እንደምንም ፍራሹ ላይ ወድቆ ለመተኛት ሞከረ።
ቤዛዊት አይምሮዋ እየተረጋጋ ሲመጣ እማማ ስንቅነሽን ለፍፁም ምግብ እንዲቋጥሩለት አርጋ በተዘበራረቀ ስሜት ዉስጥ ሆና እንባ እየተናነቃት ወደ ፍፁም አመራች
እስካሁን ፍፁም ፍቃዱን መግደሉን አላመነችም
"የማይሆን የማይታሰብ ነገር"
ትላለች ከአፏ እያመለጣት ስትራመድ
የእስር ቤቱ ግቢ መግቢያ ስትደርስ የልብ ምቷ መፍጠን ጀመረ
ፍፁምን ካየችዉ ቆይታለች በፖሊሶች ታጅቦ ሲያልፍ ካየችዉ ወድያ ምንም የምታስታዉሰዉ ነገር አልነበረም እድሜ ለእማማ ስንቅነሽ እና ለልጃቸዉ ለጌታቸዉ ስታስቸግር ስትረብሽ ተንከባክበዉ ለዛሬ እንድትበቃ ላገዟት
ዉስጥ ገብታ የምትፈልገዉን ሰዉ ስም ተናግራ ቆማ መጠበቅ ጀመረች።
ፍፁም አይኖቹ ቀልተዉ ደም መስለዋል በተኛበት ፍራሽ እንደሰመመን "ፍፁም ደምሴ"
እየተባለ ሲጠራ ይሰማዋል መነሳት ግን አልቻለም
በሞት እና በህይወት መሀል ያለ እየመሰለዉ ሲያጣጥር ቆይቶ የቤዛዊት ምስል ፊቱ ላይ ድቅን ስላለበት አይኖቹ እንባ አዝለዉ እንደምንም ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ
"ፍፁም ደምሴ ጠያቂ መጥቶሎታል"
የሚል ድምፅ ስለሰማ እያቃሰተ ወደ ዘመድ ጥየቃዉ ቦታዉ ለመሄድ መታገል ጀመረ።
ቤዛዊት እንደሆነች አስቀድሞ ልቡ አዉቆታል ጥቂት እንደተራመደ ግን የማጥወልወል ስሜት
ስለተሰማዉ ለመረጋጋት አስቦ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ ጨለማ እየታየዉ የነበረ ቢሆንም ቀስበቀስ ጨለማዉም ጠፍቶ እራሱን ስቶ ወድቆ ቀረ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (#ክፍል_ሁለት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወድቆ ቀረ
ቤዛዊት ከዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ቆማ የፍፁምን መምጣት እየተጠባበቀች እንደ መለያ ከታጠረዉ ጥልፍልፍ የሽቦ አጥር መሀል ጥዉልግ ያለዉ ፍፁም እየተንቀራፈፈ ሲራመድ
እሱን እያየች ዉስጧ ስለተረበሸ በቆመችበት
"እኔን እኔን እኔን"
እያለች ለእሱ ያመጣችለትን ምግብ የያዘ ጎድጓዳ የምሳ እቃ መሬት ላይ እያስቀመጠች
በሁለቱም እጆቿ ደረቷን ለኮፍ ለኮፍ እያረገች መድቃት ጀመረች
"ምነው ለኔ ለበሽተኛዋ ባረገዉ እሱን ፈተዉ እኔን ባሰሩኝ"
ስትል ቆይታ ፍፁም መራመድ አቅቶት ሲቆም የእሷም ልብ በድንጋጤ ቆመ
መሬት ላይ ዝልፍልፍ እያለ ሲወድቅ እስዋም እንደሱ ወደ መሬት ተንበረከከች የለበሰችዉ ጥቁርበጥቁር ቀሚስ አዋራ ለበሰ ከአይኗ እንባ እንደ ዉሀ ትኩስ ሆኖ ጉንጮቿን አቁዋርጦ ይፈሳል
አጠገቧ የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች እና የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ሊያነሷት ቢጠጉም በጉልበቷ እንደተንበረከከች አንገቷን መሬቱ ላይ ደፍታ
"አስተማሪዬን አስተማሪዬን መልሱልኝ እኔ የሚያመኝን እሰሩኝና ፍፁሜን ፍቱልኝ"
ጩሀቷን የታመቀ ብሶቷን ማሰማት ጀመረች።
ፍፁምን እስረኞች በጥንቃቄ ደግፈዉ አቅፈዉ ወደ ክሊኒኩ ለመዉሰድ ሲሞክሩ ጠዋት የመለሰዉ ህክምና ወረፋ የሚያሲዘዉ ሰዉ እየተፀፀተ እና
"ምን አለ ጠዋቱኑ እንዲታከም በፈቀድኩለት"
በሚል ስሜት ዉስጥ ሆኖ ፍፁም ህክምናውን በፍጥነት እንዲያገኝ እረዳዉ
ፍፁም አይኑን ሲገልጥ ያስተዋለዉ አሁንም እስር ቤት ግቢ ዉስጥ መሆኑን ነዉ
አካባቢዉን እየቃኘ አንድ ወጣት ነጭ ገዋን የለበሰ ሀኪም መጥቶ
"ተከተለኝ"
አለዉ ፍፁምም ከተኛበት የክሊኒኩ አልጋ ቀስ እያለ ተነስቶ ተከተለዉ
ብዛት ያላቸዉ መድሀኒት ሰጥቶት ሰዐቱን ጠብቆ እንዲዉጥ ከመከረዉ በኋላ የደንብ ልብስ የለበሰ የማረምያ ቤቱ ፖሊት ወደ መታሰርያዉ ግቢ እየመለሰዉ።
መንገድ ላይ ለዘመድ ጥየቃ እንደተጠራ ሲያስታዉስ ከጎኑ ያለዉን ፖሊስ
"ዘመድ ፈልጎኝ ነበር እባክህ አንዴ ላናግራት"
አለ በተያያዘ አንደበት በህመም ቅላፄ ባለዉ አወራር
"ምንህ ናት"
ሲል ፖሊሱ ጥያቄዉን በጥያቄ መለሰለት
"ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ "
እየተንተባተበ መለሰለት
"ትንሽ አስቸግራ ነበር አልወጣም ብላ ትንሽ ቆይተን ተሽሎታል ሌላ ግዜ ነይ ስንላት ተመልሳ ሄዳለች"
አለዉና ፍፁም የታሰረበት ግቢ ሲደርሱ ለሌላኛዉ ፖሊስ አስረክቦ
"ፈጣሪ ይማርህ"
ብሎ ተለየዉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት በርቀት ፍፁምን በሽቦዉ አጮልቃ አፋፍሰዉ ሲወስዱት እየች
ሽቦዉን እየነቀነቀች መጮኋን አላቋረጠችም ነበር ፖሊሶች ሊያረጋጓት ቢሞክሩም የምትሰማበት ጆሮም ልብም አልነበራትም እናት አባት እንደተሞተበት ትኩስ ሀዘን ከልቧ አምርራ
"አረ ወገን አረ ፖሊስ አረ ወንድም አረ እህቴ"
እያለች ፊት ለፊቷ ያየችዉን ሰዉ ሁላ በለቅሶ እየለመነች
"አስፈቱልኝ አስለቅቁልኝ አስተማሪዬ እኮ ነዉ
ወደቀ እኮ ወ ደ ቀ አረ ላንሳዉ ኡኡኡኡ አረ የሰዉ ያለ..."
ልብሷ እንዳለ በአቧራ ተላዉሶ ፀጉሯን እያመነቃቀረች ደረቷን እየደቃች ስታስቸግር በሁኔታዋ ግራ የተጋቡት ፖሊሶች በስንት ልፋትና ትግል አረጋግተዋት ፍፁም ደህና እንደሆነና ህክምና እያገኘ እንደሆነ አስረድተዋት በፈለገችዉ ሌላ ቀን መጥታ ማየት እንደምትችል ነግረዋት እስከግቢዉ በር ደግፈው ሸኙዋት።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (#ክፍል_ሁለት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ወድቆ ቀረ
ቤዛዊት ከዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ቆማ የፍፁምን መምጣት እየተጠባበቀች እንደ መለያ ከታጠረዉ ጥልፍልፍ የሽቦ አጥር መሀል ጥዉልግ ያለዉ ፍፁም እየተንቀራፈፈ ሲራመድ
እሱን እያየች ዉስጧ ስለተረበሸ በቆመችበት
"እኔን እኔን እኔን"
እያለች ለእሱ ያመጣችለትን ምግብ የያዘ ጎድጓዳ የምሳ እቃ መሬት ላይ እያስቀመጠች
በሁለቱም እጆቿ ደረቷን ለኮፍ ለኮፍ እያረገች መድቃት ጀመረች
"ምነው ለኔ ለበሽተኛዋ ባረገዉ እሱን ፈተዉ እኔን ባሰሩኝ"
ስትል ቆይታ ፍፁም መራመድ አቅቶት ሲቆም የእሷም ልብ በድንጋጤ ቆመ
መሬት ላይ ዝልፍልፍ እያለ ሲወድቅ እስዋም እንደሱ ወደ መሬት ተንበረከከች የለበሰችዉ ጥቁርበጥቁር ቀሚስ አዋራ ለበሰ ከአይኗ እንባ እንደ ዉሀ ትኩስ ሆኖ ጉንጮቿን አቁዋርጦ ይፈሳል
አጠገቧ የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች እና የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ሊያነሷት ቢጠጉም በጉልበቷ እንደተንበረከከች አንገቷን መሬቱ ላይ ደፍታ
"አስተማሪዬን አስተማሪዬን መልሱልኝ እኔ የሚያመኝን እሰሩኝና ፍፁሜን ፍቱልኝ"
ጩሀቷን የታመቀ ብሶቷን ማሰማት ጀመረች።
ፍፁምን እስረኞች በጥንቃቄ ደግፈዉ አቅፈዉ ወደ ክሊኒኩ ለመዉሰድ ሲሞክሩ ጠዋት የመለሰዉ ህክምና ወረፋ የሚያሲዘዉ ሰዉ እየተፀፀተ እና
"ምን አለ ጠዋቱኑ እንዲታከም በፈቀድኩለት"
በሚል ስሜት ዉስጥ ሆኖ ፍፁም ህክምናውን በፍጥነት እንዲያገኝ እረዳዉ
ፍፁም አይኑን ሲገልጥ ያስተዋለዉ አሁንም እስር ቤት ግቢ ዉስጥ መሆኑን ነዉ
አካባቢዉን እየቃኘ አንድ ወጣት ነጭ ገዋን የለበሰ ሀኪም መጥቶ
"ተከተለኝ"
አለዉ ፍፁምም ከተኛበት የክሊኒኩ አልጋ ቀስ እያለ ተነስቶ ተከተለዉ
ብዛት ያላቸዉ መድሀኒት ሰጥቶት ሰዐቱን ጠብቆ እንዲዉጥ ከመከረዉ በኋላ የደንብ ልብስ የለበሰ የማረምያ ቤቱ ፖሊት ወደ መታሰርያዉ ግቢ እየመለሰዉ።
መንገድ ላይ ለዘመድ ጥየቃ እንደተጠራ ሲያስታዉስ ከጎኑ ያለዉን ፖሊስ
"ዘመድ ፈልጎኝ ነበር እባክህ አንዴ ላናግራት"
አለ በተያያዘ አንደበት በህመም ቅላፄ ባለዉ አወራር
"ምንህ ናት"
ሲል ፖሊሱ ጥያቄዉን በጥያቄ መለሰለት
"ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ "
እየተንተባተበ መለሰለት
"ትንሽ አስቸግራ ነበር አልወጣም ብላ ትንሽ ቆይተን ተሽሎታል ሌላ ግዜ ነይ ስንላት ተመልሳ ሄዳለች"
አለዉና ፍፁም የታሰረበት ግቢ ሲደርሱ ለሌላኛዉ ፖሊስ አስረክቦ
"ፈጣሪ ይማርህ"
ብሎ ተለየዉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት በርቀት ፍፁምን በሽቦዉ አጮልቃ አፋፍሰዉ ሲወስዱት እየች
ሽቦዉን እየነቀነቀች መጮኋን አላቋረጠችም ነበር ፖሊሶች ሊያረጋጓት ቢሞክሩም የምትሰማበት ጆሮም ልብም አልነበራትም እናት አባት እንደተሞተበት ትኩስ ሀዘን ከልቧ አምርራ
"አረ ወገን አረ ፖሊስ አረ ወንድም አረ እህቴ"
እያለች ፊት ለፊቷ ያየችዉን ሰዉ ሁላ በለቅሶ እየለመነች
"አስፈቱልኝ አስለቅቁልኝ አስተማሪዬ እኮ ነዉ
ወደቀ እኮ ወ ደ ቀ አረ ላንሳዉ ኡኡኡኡ አረ የሰዉ ያለ..."
ልብሷ እንዳለ በአቧራ ተላዉሶ ፀጉሯን እያመነቃቀረች ደረቷን እየደቃች ስታስቸግር በሁኔታዋ ግራ የተጋቡት ፖሊሶች በስንት ልፋትና ትግል አረጋግተዋት ፍፁም ደህና እንደሆነና ህክምና እያገኘ እንደሆነ አስረድተዋት በፈለገችዉ ሌላ ቀን መጥታ ማየት እንደምትችል ነግረዋት እስከግቢዉ በር ደግፈው ሸኙዋት።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (ክፍል ሶስት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
ቤዛዊት ቤትዋን እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት ካረገች ሰነባበተች ይሄ ሁሉ ምስቅልቅል ይፈጠራል ብላ አልነበረም ወደ እነ እማማ ቤት አመጣጧ ፍፁምንም የጋበዘችዉ በነፋሻዉ አየር ከሰዉ እራቅ ብለዉ የሰላም የፍቅር ጊዜ ለማሳለፍ ነበር
ነገር ግን አንዳንዴ ሀሳብ እንደ ንፋስ የማይታይ ሆኖ ይነፍከሳል ሀይል ካለዉም ነገሮችን ሳይጠበቅ እያንሳፈፈ እንደሚወስደዉ የታሰበዉ ሳይሆን ቀርቶ ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል
ከእስር ቤቱ በር ጥቂት እንደወጣች ድንጋይ አጊንታ አረፍ አለች ጭንቅላቷ ዉስጥ ፍፁም ሲወድቅ ያለዉ ሁኔታ አሁንም ይታያታል አይኖቿ በለቅሶ ብዛት እንባ ማዉጣት ቢያቅታቸዉም ለአመል በቀስታ የሚፈሱ የእንባ ዘለላወች የአፍንጫዋን መስመር አቋርጠዉ አፍዋን እያራሱ በአገጯ አርገዉ ልብሷን እያረጠቡት ነዉ።
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
በልቧ ይሄን ቃል ታነበንባለች እስካሁን መታሰሩ እዉነት አልመስልሽ እያላት እራሷን
"እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ"
እያለች ትጠይቃለች መመለስ እና መፍታት የማትችለዉ ጥያቄ ሲሆን አይምሮዋ እየተቃወሰም ቢሆን ከተቀመጠችበት ተነስታ እንባዋን በእጆቿ እያበሰች ወደ እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ፍፁም ለመጀመሪያ ግዜ መድሀኒቱን ዉጦ የሰላም እንቅልፍ ወሰደዉ በህልሙ
ቤዛዊት ፊት ለፊቱ ተቀምጣ ስትስቅ እያያት ከጀርባዋ ጥቁር አሞራ እየበረረ ትከሻዋ ላይ ተቀምጦ የማያስፈራ ድምፅ እያወጣ ሲጮህ ባኖ ተነሳ
እየነጋጋ ነበር ከእስር ቤቱ ሚዲያ ክፍል መዝሙር ድምፁ ከፍተደርጎ ተከፍቷ ይሰማዋል እስረኞች ከእንቅልፋቸዉ እየተነሱ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ ህመም አልተሰማዉም ተነስቶ ቆመ እራሱን ለቆታል
ፊቱ ላይ ጥልቅ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታይቶ እየተራመደ ወደ ዉጪ ወጣ አለ።
ቤዛዊት ከተኛችበት ስትነቃ የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ በጥቂት ተገልጧ ወደ ሚታየዉ ባቷ ሲያፈጥ ያዘችዉ ቀሚሷን እያስተካከለች ተነሳች ጌታቸዉ ግን አሁንም በአይኑ እየተከታተላት ነዉ
"ቆንጆ እንደሆንሽ ታዉቂያለሽ"
አላት ማታ የጠጣዉ መጠጥ አሁንም አለቀቀዉም አፉን አሳስሮታል
ቤዛዊት ልብ ብላ አልሰማችዉም እማማ ስንቅነሽ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በጠዋት ስለወጡ ሁለቱ ብቻ ናቸው ቤቱ ዉስጥ ያሉት።
(ከደቂቃ በፊት)
ቤዛዊት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ዉስጥ ሆና እማማ ስንቅነሽ
"ልጄ ቤዛዊት ቤተስኪያን ደርሰን እንምጣ"
እያሉ ሊቀሰቅሷት ቢሞክሩም አልሰማም ስላለቻቸዉ እሳቸዉ ደጅ ወጥተዉ ልብሳቸዉን ቀያይረዉ ነጠላ ቢጤ ደርበዉ እንደወጡ በሩን ለመዝጋት ሲሞክሩ ልጃቸዉ ጌታቸዉ ከእንቅልፉ ይነቃል
ጥቂት አልጋዉ ላይ ሆኖ ስለ ቤዛዊት ቆንጅና ስለ ገላዋ ስለ ሰዉነቷ በህሊናዉ ሲስል ቆይቶ በቀስታ ከአልጋዉ ይነሳና ወደ እማማ እና ቤዛዊት ወደ ተኙበት ክፍል ያመራል
ቤዛዊት ብርድ ልብስ ተሸፋፍና ጥቅልል ብላ ተኝታለች ጌታቸዉ ፊት ለፊቷ እያያት ከቆመ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀስ አርጎ ገለጠዉ ቤዛዊት አሁንም የእንቅልፍ ልብ ዉስጥ ናት
ቀስ ብሎ እረጅሙን ቀሚሷን እየገለጠዉ እና ታፋዋን እየተመለከተ ቤዛዊት ተገላብጣ ስትነቃ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ማየቱን ቀጠለ።
(አሁን)
ጌታቸዉ ከቤዛዊት ጀርባ ቀስ ብሎ እየተጠጋ ሊያቅፋት ሲሞክር
"ምን መሆንህ ነዉ"
እያለች ገፍትራዉ አይኗን አጉረጠረጠችበት
እንደ መፍራት እያለ
"ምንም ምን አረኩ ደህና መሆንሽን ለማወቅ ነው "
እያለ ወደኋላ አፈገፈገ ነገር ግን በልቡ መጥፎ ሀሳብ ጠንስሶ ጠብቂ አገኝሻለሁ እያለ ነበር።
"ደህና ነኝ "
እያለችዉ ቤዛዊት ዛሬስ ፍፁምን አየዉ ይሆን እያለች እራሶን እየጠየቀች ለእራሷ
ዛሬማ አገኘዋለሁ አዋራዋለሁ እያለች ወጣች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት (ክፍል ሶስት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
ቤዛዊት ቤትዋን እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት ካረገች ሰነባበተች ይሄ ሁሉ ምስቅልቅል ይፈጠራል ብላ አልነበረም ወደ እነ እማማ ቤት አመጣጧ ፍፁምንም የጋበዘችዉ በነፋሻዉ አየር ከሰዉ እራቅ ብለዉ የሰላም የፍቅር ጊዜ ለማሳለፍ ነበር
ነገር ግን አንዳንዴ ሀሳብ እንደ ንፋስ የማይታይ ሆኖ ይነፍከሳል ሀይል ካለዉም ነገሮችን ሳይጠበቅ እያንሳፈፈ እንደሚወስደዉ የታሰበዉ ሳይሆን ቀርቶ ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል
ከእስር ቤቱ በር ጥቂት እንደወጣች ድንጋይ አጊንታ አረፍ አለች ጭንቅላቷ ዉስጥ ፍፁም ሲወድቅ ያለዉ ሁኔታ አሁንም ይታያታል አይኖቿ በለቅሶ ብዛት እንባ ማዉጣት ቢያቅታቸዉም ለአመል በቀስታ የሚፈሱ የእንባ ዘለላወች የአፍንጫዋን መስመር አቋርጠዉ አፍዋን እያራሱ በአገጯ አርገዉ ልብሷን እያረጠቡት ነዉ።
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
በልቧ ይሄን ቃል ታነበንባለች እስካሁን መታሰሩ እዉነት አልመስልሽ እያላት እራሷን
"እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ"
እያለች ትጠይቃለች መመለስ እና መፍታት የማትችለዉ ጥያቄ ሲሆን አይምሮዋ እየተቃወሰም ቢሆን ከተቀመጠችበት ተነስታ እንባዋን በእጆቿ እያበሰች ወደ እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ፍፁም ለመጀመሪያ ግዜ መድሀኒቱን ዉጦ የሰላም እንቅልፍ ወሰደዉ በህልሙ
ቤዛዊት ፊት ለፊቱ ተቀምጣ ስትስቅ እያያት ከጀርባዋ ጥቁር አሞራ እየበረረ ትከሻዋ ላይ ተቀምጦ የማያስፈራ ድምፅ እያወጣ ሲጮህ ባኖ ተነሳ
እየነጋጋ ነበር ከእስር ቤቱ ሚዲያ ክፍል መዝሙር ድምፁ ከፍተደርጎ ተከፍቷ ይሰማዋል እስረኞች ከእንቅልፋቸዉ እየተነሱ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ ህመም አልተሰማዉም ተነስቶ ቆመ እራሱን ለቆታል
ፊቱ ላይ ጥልቅ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታይቶ እየተራመደ ወደ ዉጪ ወጣ አለ።
ቤዛዊት ከተኛችበት ስትነቃ የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ በጥቂት ተገልጧ ወደ ሚታየዉ ባቷ ሲያፈጥ ያዘችዉ ቀሚሷን እያስተካከለች ተነሳች ጌታቸዉ ግን አሁንም በአይኑ እየተከታተላት ነዉ
"ቆንጆ እንደሆንሽ ታዉቂያለሽ"
አላት ማታ የጠጣዉ መጠጥ አሁንም አለቀቀዉም አፉን አሳስሮታል
ቤዛዊት ልብ ብላ አልሰማችዉም እማማ ስንቅነሽ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በጠዋት ስለወጡ ሁለቱ ብቻ ናቸው ቤቱ ዉስጥ ያሉት።
(ከደቂቃ በፊት)
ቤዛዊት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ዉስጥ ሆና እማማ ስንቅነሽ
"ልጄ ቤዛዊት ቤተስኪያን ደርሰን እንምጣ"
እያሉ ሊቀሰቅሷት ቢሞክሩም አልሰማም ስላለቻቸዉ እሳቸዉ ደጅ ወጥተዉ ልብሳቸዉን ቀያይረዉ ነጠላ ቢጤ ደርበዉ እንደወጡ በሩን ለመዝጋት ሲሞክሩ ልጃቸዉ ጌታቸዉ ከእንቅልፉ ይነቃል
ጥቂት አልጋዉ ላይ ሆኖ ስለ ቤዛዊት ቆንጅና ስለ ገላዋ ስለ ሰዉነቷ በህሊናዉ ሲስል ቆይቶ በቀስታ ከአልጋዉ ይነሳና ወደ እማማ እና ቤዛዊት ወደ ተኙበት ክፍል ያመራል
ቤዛዊት ብርድ ልብስ ተሸፋፍና ጥቅልል ብላ ተኝታለች ጌታቸዉ ፊት ለፊቷ እያያት ከቆመ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀስ አርጎ ገለጠዉ ቤዛዊት አሁንም የእንቅልፍ ልብ ዉስጥ ናት
ቀስ ብሎ እረጅሙን ቀሚሷን እየገለጠዉ እና ታፋዋን እየተመለከተ ቤዛዊት ተገላብጣ ስትነቃ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ማየቱን ቀጠለ።
(አሁን)
ጌታቸዉ ከቤዛዊት ጀርባ ቀስ ብሎ እየተጠጋ ሊያቅፋት ሲሞክር
"ምን መሆንህ ነዉ"
እያለች ገፍትራዉ አይኗን አጉረጠረጠችበት
እንደ መፍራት እያለ
"ምንም ምን አረኩ ደህና መሆንሽን ለማወቅ ነው "
እያለ ወደኋላ አፈገፈገ ነገር ግን በልቡ መጥፎ ሀሳብ ጠንስሶ ጠብቂ አገኝሻለሁ እያለ ነበር።
"ደህና ነኝ "
እያለችዉ ቤዛዊት ዛሬስ ፍፁምን አየዉ ይሆን እያለች እራሶን እየጠየቀች ለእራሷ
ዛሬማ አገኘዋለሁ አዋራዋለሁ እያለች ወጣች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት ( #ክፍል_አራት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ ስለቤዛዊት እና ስለሱ መከራ የበዛበት የፍቅር ታሪክ መፃፉን ተያይዞታል
ህመሙ እየተሻለዉ ስለሆነ ጥሩ ስሜት ዉስጥ ነዉ ስላለፈዉ ታሪክ እያሰበ ይፅፋል አስደሳች ጊዜወቹ ታዉሰዉት ፊቱ ላይ ደማቅ ፈገግታ እየተነበበ አእምሮዉ ላይ ያለዉን ከወረቀቱ ጋር እያዋሀደዉ ነዉ።
እንደምትወደዉ የነገረችዉን ቀን አስታወሰ ፅፋ የሰጠችዉ ወረቀት ዉል አለበት የተጣሉበትን ቀን መሀል ላይ ፍቃዱ መሀላቸዉ ገብቶ የእህቱን ፎቶ ሚስቱ ናት ብሎ ያወራ ቀን የተፈጠረዉን ሲያስታዉስ የሚፅፉት እጆቹ መንቀጥቀጥ ጀመሩ
ለቤዛዊት ሊያስረዳት ዉሸት መሆኑን ሊያብራራላት ሲጣደፍ መኪና የገጨዉን ሲያስታዉስ መፃፍ ስላልቻለ እስኪቢርቶዉን ወረቀቱላይ ጥሎ በዝምታ ተቀመጠ
ከጎኑ አብሮት የታሰረዉ ማስረሻ የተባለ ታሪሚ የፍፁምን ሁኔታ በአይኖቹ ሲከታተል ስለነበረ
"ምን እየፃፍክ ነዉ ወዳጄ?"
ሲል ለዉቀት መከላከያ ብሎ ዉሀ ዉስጥ ነክሮ አናቱ ላይ ያስቀመጠዉን ፎጣ እያወረደ
ፍፁም የጠየቀዉን ልጅ ትኩር ብሎ ተመለከተዉ ማስረሻ ቀጠን ብሎ ቀዉላላ የሚባል ወጣት ነዉ አይኖቹን ሲያስተዉላቸዉ ከተረገመዉ ፍቃዱ ጋር ተመሳሰሉበት
ለመጀመርያ ግዜ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጮሀ
"ምን አገባት ምን አገባህ"
ደም ስሮቹ ተገታትረዉ ንዴት እያንቀጠቀጠዉ መናገሩን ተያያዘዉ
"ለምን አተወኝም ተዉኝ ተዉኝ"
እጆቹን እያወራጨ ወደ ማስረሻ ተጠጋዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየተገረመ እና ጥሎት እንደመሄድ እያለ
"እብድ ድሮስ ነብሰ በላ መጨረሻዉ ማበድ ነዉ"
ብሎት ወደ ዉጪ ፍፁምን ትቶት ወጣ።
ፍፁም ግን ማስረሻ የተናገረዉ ንግግር አይምሮዉ ላይ እያቃጨለበት ነበር
"ነብሰበላ ነብሰ በላ ማበድ ማበድ"
እዉነት ነዉ የሰዉ ደም ወደ ሰማይ ይጮሀል ገዳይም የሰላም እንቅልፍ አያገኝም ማንም መጥፎ ሰው ቢሆን እንኳን የፈጠረዉ ፈጣሪ በሞት ካልወሰደዉ በቀር በሰዉ ቢገደል
ገዳዩ ሀጥያቱን ይሸከማል
ቤዛዊት መንገድ ላይ ወደ እስር ቤቱ አቅራቢያ ስትደርስ ካገኘችዉ ጥሩ ምግብ ይሰራሉ ብላ ካሰበችበት ምግብ ቤት ገብታ ለፍፁም በገዛችዉ ሰፊ የምግብ መያዣ ምግብ አስቋጠረችለት
ደስ እያላት ነው በልቧ ፍፁምን ዛሬ እንደምታገኘዉ እንደምታዋራዉ እርግጠኛ ሆናለች።
ዘመድ መጠየቅያዉ ቦታ ላይ ቆማ የፍፁምን ሙሉ ስም ተናግራ መጠበቅ ጀመረች
ፍፁም ከላይ የተጣበቀ ቲሸርት ከስር ያረጀ ቁምጣ በሲሊፐር ለብሶ ሲመጣ በርቀት ተመለከተችዉ ልቧ እየተረበሸ ነዉ አሳዘናት የሴትነት አንጀቷ ባሀሪዋም እሩሩ ስለሆነች ሆድ ብሷት እንባ ማንባት ጀምራ ሲያየኝ እሱም ይጨነቃል ብላ አስባ እንባዋን ወድያዉ ጠራረገች።
የያዘችዉን ምግብ ፖሊሶቹ ፊት ለፊታቸዉ እንድትጎርስ አዘዟት እየጎረሰች ፍፁምን በከርታታ አይኗ እያየችዉ ነዉ ፍፁም አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬቱን እያየ ምግቡን በግዴለሽነት ተቀብሏት
መሬት ላይ አስቀምጦ በጨረፍታ እያያት
"ለምን ተቸገርሽ ለኔ ብለሽ መልፋት የለብሽም እኔ የብዙ አመት ፍርደኛ ነኝ..."
የጀመረላትን ሳታስጨርሰዉ
"ሁሌም ቢሆን እጠብቅካለሁ ሁሌም"
ቅድም ያስቆመቻቸዉ እንባወቿ መፍሰስ ጀመሩ።
"አስራ ምናምን አመት..."
አለና የፌዝ ሳቅ ሳቀ
ፍፁም እራሱ ማስረሻ ካዋራዉ ጀምሮ ፀባዩ እየተቀያየረ ነበር ዉስጡ ሰላም እየተሰማዉ አደለም
እሱ በእስር እየበሰበሰ የወጣቷን የቤዛዊትን ህይወትም የቁም እስር ዉስጥ አትክተተዉ የሚል እርኩስ መንፈስ ልቡ ዉስጥ ማደግ እየጀመረ ነበር መንፈሱ ህፃን ስለሆነም እያነጫነጨዉ ነዉ።
"እንዋደድ የለ አትወደኝም ስትል ጠየቀችው ?"
ቤዛዊት አይን አይኑን እያየች
"እወድሻለሁ"
አላትና ጥቂት አስቦ
"ነብሰ ገዳይ ሰው ግን ላንቺ አይጠቅምሽም ሌላ አዲስ ህይወት መጀመር ትችያለሽ አልቀየምሽም ባንቺ ደስተኛ ነኝ ሁለተኛ ግን እኔ ጋር እንዳትመጪ"
አላትና አይኗን ላለማየት እየተጣደፈ ሳይሰናበታት ወደ እስር ቤቱ አመራ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ምእራፍ_ሁለት ( #ክፍል_አራት)
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ ስለቤዛዊት እና ስለሱ መከራ የበዛበት የፍቅር ታሪክ መፃፉን ተያይዞታል
ህመሙ እየተሻለዉ ስለሆነ ጥሩ ስሜት ዉስጥ ነዉ ስላለፈዉ ታሪክ እያሰበ ይፅፋል አስደሳች ጊዜወቹ ታዉሰዉት ፊቱ ላይ ደማቅ ፈገግታ እየተነበበ አእምሮዉ ላይ ያለዉን ከወረቀቱ ጋር እያዋሀደዉ ነዉ።
እንደምትወደዉ የነገረችዉን ቀን አስታወሰ ፅፋ የሰጠችዉ ወረቀት ዉል አለበት የተጣሉበትን ቀን መሀል ላይ ፍቃዱ መሀላቸዉ ገብቶ የእህቱን ፎቶ ሚስቱ ናት ብሎ ያወራ ቀን የተፈጠረዉን ሲያስታዉስ የሚፅፉት እጆቹ መንቀጥቀጥ ጀመሩ
ለቤዛዊት ሊያስረዳት ዉሸት መሆኑን ሊያብራራላት ሲጣደፍ መኪና የገጨዉን ሲያስታዉስ መፃፍ ስላልቻለ እስኪቢርቶዉን ወረቀቱላይ ጥሎ በዝምታ ተቀመጠ
ከጎኑ አብሮት የታሰረዉ ማስረሻ የተባለ ታሪሚ የፍፁምን ሁኔታ በአይኖቹ ሲከታተል ስለነበረ
"ምን እየፃፍክ ነዉ ወዳጄ?"
ሲል ለዉቀት መከላከያ ብሎ ዉሀ ዉስጥ ነክሮ አናቱ ላይ ያስቀመጠዉን ፎጣ እያወረደ
ፍፁም የጠየቀዉን ልጅ ትኩር ብሎ ተመለከተዉ ማስረሻ ቀጠን ብሎ ቀዉላላ የሚባል ወጣት ነዉ አይኖቹን ሲያስተዉላቸዉ ከተረገመዉ ፍቃዱ ጋር ተመሳሰሉበት
ለመጀመርያ ግዜ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጮሀ
"ምን አገባት ምን አገባህ"
ደም ስሮቹ ተገታትረዉ ንዴት እያንቀጠቀጠዉ መናገሩን ተያያዘዉ
"ለምን አተወኝም ተዉኝ ተዉኝ"
እጆቹን እያወራጨ ወደ ማስረሻ ተጠጋዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየተገረመ እና ጥሎት እንደመሄድ እያለ
"እብድ ድሮስ ነብሰ በላ መጨረሻዉ ማበድ ነዉ"
ብሎት ወደ ዉጪ ፍፁምን ትቶት ወጣ።
ፍፁም ግን ማስረሻ የተናገረዉ ንግግር አይምሮዉ ላይ እያቃጨለበት ነበር
"ነብሰበላ ነብሰ በላ ማበድ ማበድ"
እዉነት ነዉ የሰዉ ደም ወደ ሰማይ ይጮሀል ገዳይም የሰላም እንቅልፍ አያገኝም ማንም መጥፎ ሰው ቢሆን እንኳን የፈጠረዉ ፈጣሪ በሞት ካልወሰደዉ በቀር በሰዉ ቢገደል
ገዳዩ ሀጥያቱን ይሸከማል
ቤዛዊት መንገድ ላይ ወደ እስር ቤቱ አቅራቢያ ስትደርስ ካገኘችዉ ጥሩ ምግብ ይሰራሉ ብላ ካሰበችበት ምግብ ቤት ገብታ ለፍፁም በገዛችዉ ሰፊ የምግብ መያዣ ምግብ አስቋጠረችለት
ደስ እያላት ነው በልቧ ፍፁምን ዛሬ እንደምታገኘዉ እንደምታዋራዉ እርግጠኛ ሆናለች።
ዘመድ መጠየቅያዉ ቦታ ላይ ቆማ የፍፁምን ሙሉ ስም ተናግራ መጠበቅ ጀመረች
ፍፁም ከላይ የተጣበቀ ቲሸርት ከስር ያረጀ ቁምጣ በሲሊፐር ለብሶ ሲመጣ በርቀት ተመለከተችዉ ልቧ እየተረበሸ ነዉ አሳዘናት የሴትነት አንጀቷ ባሀሪዋም እሩሩ ስለሆነች ሆድ ብሷት እንባ ማንባት ጀምራ ሲያየኝ እሱም ይጨነቃል ብላ አስባ እንባዋን ወድያዉ ጠራረገች።
የያዘችዉን ምግብ ፖሊሶቹ ፊት ለፊታቸዉ እንድትጎርስ አዘዟት እየጎረሰች ፍፁምን በከርታታ አይኗ እያየችዉ ነዉ ፍፁም አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬቱን እያየ ምግቡን በግዴለሽነት ተቀብሏት
መሬት ላይ አስቀምጦ በጨረፍታ እያያት
"ለምን ተቸገርሽ ለኔ ብለሽ መልፋት የለብሽም እኔ የብዙ አመት ፍርደኛ ነኝ..."
የጀመረላትን ሳታስጨርሰዉ
"ሁሌም ቢሆን እጠብቅካለሁ ሁሌም"
ቅድም ያስቆመቻቸዉ እንባወቿ መፍሰስ ጀመሩ።
"አስራ ምናምን አመት..."
አለና የፌዝ ሳቅ ሳቀ
ፍፁም እራሱ ማስረሻ ካዋራዉ ጀምሮ ፀባዩ እየተቀያየረ ነበር ዉስጡ ሰላም እየተሰማዉ አደለም
እሱ በእስር እየበሰበሰ የወጣቷን የቤዛዊትን ህይወትም የቁም እስር ዉስጥ አትክተተዉ የሚል እርኩስ መንፈስ ልቡ ዉስጥ ማደግ እየጀመረ ነበር መንፈሱ ህፃን ስለሆነም እያነጫነጨዉ ነዉ።
"እንዋደድ የለ አትወደኝም ስትል ጠየቀችው ?"
ቤዛዊት አይን አይኑን እያየች
"እወድሻለሁ"
አላትና ጥቂት አስቦ
"ነብሰ ገዳይ ሰው ግን ላንቺ አይጠቅምሽም ሌላ አዲስ ህይወት መጀመር ትችያለሽ አልቀየምሽም ባንቺ ደስተኛ ነኝ ሁለተኛ ግን እኔ ጋር እንዳትመጪ"
አላትና አይኗን ላለማየት እየተጣደፈ ሳይሰናበታት ወደ እስር ቤቱ አመራ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
....ወደ እስር ቤቱ አመራ
ከጀርባው በህይወቴ አጊንቼ አጣሁዋት ብሎ በትዝታ በናፍቆት እስሩን እስኪጨርስ ከልቡ የማያወጣትን ቤዛዊትን ጨክኖባት ትቷት ጀርባውን ሰጥቷት ከእይታዋ እየራቀ ሄደ
እየተራመደ ዞረህ ተመለስ ዞረህ አዋራት ተስፋ ስጣት ስወጣ ተጋብተን ልጆች ወልደን በፍቅር እንኖራለን በላይ የሚለዉ ስሜት ቢኖርም
መጥፎዉ ስሜት በተቃራኒዉ የምን ተስፋ ነዉ የምታስበዉ ልጅቷም ህይወት አላት አንተ ህይወትህ አበቃ ታሰርክ እና እስዋ ሌላ ህይወት የላትም የሚለዉ ስሜት አሸንፎ ወደ ኋላም ሳይዞር እየተንቀራፈፈ እየተጎተተ መራመዱን ቀጠለ።
ህይወት ግን እስትንፋስ ይዛ እስከቀጠለች ድረስ የሚፈጠረው አይታወቅም አበቃ ተዘጋ ተደመደመ የተባለዉ አንድ ቀን ጊዜዉን ጠብቆ ይጀምራል ይከፈታል
ተጀመረ ተከፈተ የተባለዉም በድንገት ሊዘጋ ይችላል
ህይወትንም ዉስብስብ የሚያረጋት ገፅታ ይሄ ነዉ የተዘጋዉ በር ሲከፈት የሚገኘዉ ደስታ እና የተከፈተዉ በር ሲዘጋ የሚገኘዉ ሀዘን ሲፈራረቅ የህይወት መስመርም ከዚህ ጋር ተቆራኝቶ ይሄዳል።
ቤዛዊት ከአይኗ እየራቀ ያለዉን ከቤተሰብ ከአባት ከእናት ከእህቷ ያስበለጠችዉ ፍቅርን በእሱ የጀመረችዉ ሰዉ እርቋት ሲሄድ በቆመችበት ምንም ሳትንቀሳቀስ ከአይኗ እስኪርቅ ካየችዉ በኋላ በጥልቅ ዝምታ ዉስጥ ሆና መራመድ ጀመረች።
ትላንት ስትጮህ ስታለቅስ ያዩዋት የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች
"እንዴት ነሽ እህት..."
እያሉ ሊያዋሯት ሊያፅናኗት ቢሞከሩም ልትመልስላቸዉ ልታዋራቸዉ ይቅርና በዙርያዋ ምን እንደሚፈጠር ሁሉ የምታዉቅ አትመስልም
የቀኝ እጇን የሌባ ጣት ጥፍር አፍዋ ዉስጥ ከታ እየቆረጠች ቢመስላትም በሀሳብ ግን ጀርባዉን ሰጥቷት የሄደዉን ፍፁምን እያሰበች
ህመሞም መጣሁ መጣሁ እያለ አይኖቿ ፍዝዝ እያሉ ትራንስፖርት ይዛ ከኋላ ወንበር ተቀምጣ መጉዋዝ ጀመረች።
"እናቱ ሂሳብ"
በተደጋጋሚ ይጮሀል የታክሲዉ ረዳት ቤዛዊት የፈዘዙት አይኖቿ እየቀሉ ታክሲዉ ላይ ከተለጠፈዉ ጥቅስ ላይ አይኖቿን ተክላ እየሰማችዉ አደለም
ከጎኗ የተቀመጠችዉ ተሳፋሪ ቤዛዊት የምታየውን ጥቅስ አየችዉ
"ቀን ሲጥል ፈራጁ ብዙ ነዉ"
የቤዛዊትን አይኖች ስታይ የሆነ ችግር ዉስጥ ያለች ስለመሰለቻት
"ከኔ ላይ ቁረጥ"
ብላ ለእረዳቱ እየነገረችዉ ወደ ቤዛዊት ተመልሳ ዞራ
"ደህና ነሽ ?"
ስትል ጠየቀቻት የቤዛዊትን ትከሻ ነካ ነካ እያረገች
ቤዛዊት አጠገቧ እያዋራቻት ያለችዉን ልጅ በሚንከራተቱት አይኖቿ እያየቻት
"እ ኔ እንጃ "
ስትል መለሰችላት
"እና አሁን ወዴት እየሄድሽ ነዉ?"
ለቤዛዊት አዝናላት አሟት ይሆን ስትል እያሰበች ልትረዳት ፈልጋ
አለም ላይ ብዙ የሰዉን መጥፎ ማየት የሚፈልጉ ለሰው መልካም የማያስቡ የተረገሙ ሰወች ቢኖሩም ሌሎች ለቁጥር የሚታክቱም ደግ እና መልካም ሰወችም አሉ።
"እማማ ስንቅነሽ ቤት እየሄድኩ ነዉ"
ቤዛዊት አፏ እየተሳሰረ ነገረቻት
ተሳፉሪዋ ከቤዛዊት ጋር አብራት ወርዳ የምትሄድበትን ቀጠሮ ሰርዛ ለመራመድ አቅም ያጣችዉን
ለህመሞ መነሳት ቋፍ ላይ ያለችውን ቤዛዊትን እያታለለች በዘዴ የእማማ ስንቅነሽን ቤት አቅጣጫ እያወጣጣቻት በእግር መጉዋዝ ጀመሩ።
"እማማ ስንቅነሽ እርሶ ኖት አደል"
አለች ተሳፋሪዋ የእማማን ግቢ ቆርቆሮ አጥር አልፈዉ ሲገቡ ቤዛዊትን ገብታ እንድትተኛ እየነገረቻት በእድሜ ገፋ ያሉ ሴትዮ ስታይ እማማ ስንቅነሽ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ ብላ
እማማ ለልጅቷ መልስ አልመለሱላትም ፈዛ ነዉልላ የቆመችዉን ቤዛዊትን እሮጠዉ አጠገቧ ደርሰዉ በእጃቸዉ ፊቷን እየደባበሱ
"ምን ሆንሽብኝ ምትኬ ምን ነካብኝ "
እያሉ ደግፈዋት ወደ ዉስጥ ካስገቧት በኋላ አልጋ ላይ እንድትተኛ ነግረዋት ልጅቷን
"የተባረክሽ ልጅ ፈጣሪ ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሽ ግቢና ሻይ ጠጪ"
እያሉ እየመረቁ እንድትገባ ቢለምኗትም
"ሌላ ግዜ እመጣለሁ"
እያለች
"ልጆትን ፈጣሪ ይማርሎት"
ብላ ተሰናብታ ወጣች።
ቤዛዊት የአልጋዉን ፍራሽ እየነጨች መሬት ላይ እንደ ቄጤማ እየጎዘጎዘችዉ ነበረ።
💫ይቀጥላል...💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
....ወደ እስር ቤቱ አመራ
ከጀርባው በህይወቴ አጊንቼ አጣሁዋት ብሎ በትዝታ በናፍቆት እስሩን እስኪጨርስ ከልቡ የማያወጣትን ቤዛዊትን ጨክኖባት ትቷት ጀርባውን ሰጥቷት ከእይታዋ እየራቀ ሄደ
እየተራመደ ዞረህ ተመለስ ዞረህ አዋራት ተስፋ ስጣት ስወጣ ተጋብተን ልጆች ወልደን በፍቅር እንኖራለን በላይ የሚለዉ ስሜት ቢኖርም
መጥፎዉ ስሜት በተቃራኒዉ የምን ተስፋ ነዉ የምታስበዉ ልጅቷም ህይወት አላት አንተ ህይወትህ አበቃ ታሰርክ እና እስዋ ሌላ ህይወት የላትም የሚለዉ ስሜት አሸንፎ ወደ ኋላም ሳይዞር እየተንቀራፈፈ እየተጎተተ መራመዱን ቀጠለ።
ህይወት ግን እስትንፋስ ይዛ እስከቀጠለች ድረስ የሚፈጠረው አይታወቅም አበቃ ተዘጋ ተደመደመ የተባለዉ አንድ ቀን ጊዜዉን ጠብቆ ይጀምራል ይከፈታል
ተጀመረ ተከፈተ የተባለዉም በድንገት ሊዘጋ ይችላል
ህይወትንም ዉስብስብ የሚያረጋት ገፅታ ይሄ ነዉ የተዘጋዉ በር ሲከፈት የሚገኘዉ ደስታ እና የተከፈተዉ በር ሲዘጋ የሚገኘዉ ሀዘን ሲፈራረቅ የህይወት መስመርም ከዚህ ጋር ተቆራኝቶ ይሄዳል።
ቤዛዊት ከአይኗ እየራቀ ያለዉን ከቤተሰብ ከአባት ከእናት ከእህቷ ያስበለጠችዉ ፍቅርን በእሱ የጀመረችዉ ሰዉ እርቋት ሲሄድ በቆመችበት ምንም ሳትንቀሳቀስ ከአይኗ እስኪርቅ ካየችዉ በኋላ በጥልቅ ዝምታ ዉስጥ ሆና መራመድ ጀመረች።
ትላንት ስትጮህ ስታለቅስ ያዩዋት የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች
"እንዴት ነሽ እህት..."
እያሉ ሊያዋሯት ሊያፅናኗት ቢሞከሩም ልትመልስላቸዉ ልታዋራቸዉ ይቅርና በዙርያዋ ምን እንደሚፈጠር ሁሉ የምታዉቅ አትመስልም
የቀኝ እጇን የሌባ ጣት ጥፍር አፍዋ ዉስጥ ከታ እየቆረጠች ቢመስላትም በሀሳብ ግን ጀርባዉን ሰጥቷት የሄደዉን ፍፁምን እያሰበች
ህመሞም መጣሁ መጣሁ እያለ አይኖቿ ፍዝዝ እያሉ ትራንስፖርት ይዛ ከኋላ ወንበር ተቀምጣ መጉዋዝ ጀመረች።
"እናቱ ሂሳብ"
በተደጋጋሚ ይጮሀል የታክሲዉ ረዳት ቤዛዊት የፈዘዙት አይኖቿ እየቀሉ ታክሲዉ ላይ ከተለጠፈዉ ጥቅስ ላይ አይኖቿን ተክላ እየሰማችዉ አደለም
ከጎኗ የተቀመጠችዉ ተሳፋሪ ቤዛዊት የምታየውን ጥቅስ አየችዉ
"ቀን ሲጥል ፈራጁ ብዙ ነዉ"
የቤዛዊትን አይኖች ስታይ የሆነ ችግር ዉስጥ ያለች ስለመሰለቻት
"ከኔ ላይ ቁረጥ"
ብላ ለእረዳቱ እየነገረችዉ ወደ ቤዛዊት ተመልሳ ዞራ
"ደህና ነሽ ?"
ስትል ጠየቀቻት የቤዛዊትን ትከሻ ነካ ነካ እያረገች
ቤዛዊት አጠገቧ እያዋራቻት ያለችዉን ልጅ በሚንከራተቱት አይኖቿ እያየቻት
"እ ኔ እንጃ "
ስትል መለሰችላት
"እና አሁን ወዴት እየሄድሽ ነዉ?"
ለቤዛዊት አዝናላት አሟት ይሆን ስትል እያሰበች ልትረዳት ፈልጋ
አለም ላይ ብዙ የሰዉን መጥፎ ማየት የሚፈልጉ ለሰው መልካም የማያስቡ የተረገሙ ሰወች ቢኖሩም ሌሎች ለቁጥር የሚታክቱም ደግ እና መልካም ሰወችም አሉ።
"እማማ ስንቅነሽ ቤት እየሄድኩ ነዉ"
ቤዛዊት አፏ እየተሳሰረ ነገረቻት
ተሳፉሪዋ ከቤዛዊት ጋር አብራት ወርዳ የምትሄድበትን ቀጠሮ ሰርዛ ለመራመድ አቅም ያጣችዉን
ለህመሞ መነሳት ቋፍ ላይ ያለችውን ቤዛዊትን እያታለለች በዘዴ የእማማ ስንቅነሽን ቤት አቅጣጫ እያወጣጣቻት በእግር መጉዋዝ ጀመሩ።
"እማማ ስንቅነሽ እርሶ ኖት አደል"
አለች ተሳፋሪዋ የእማማን ግቢ ቆርቆሮ አጥር አልፈዉ ሲገቡ ቤዛዊትን ገብታ እንድትተኛ እየነገረቻት በእድሜ ገፋ ያሉ ሴትዮ ስታይ እማማ ስንቅነሽ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ ብላ
እማማ ለልጅቷ መልስ አልመለሱላትም ፈዛ ነዉልላ የቆመችዉን ቤዛዊትን እሮጠዉ አጠገቧ ደርሰዉ በእጃቸዉ ፊቷን እየደባበሱ
"ምን ሆንሽብኝ ምትኬ ምን ነካብኝ "
እያሉ ደግፈዋት ወደ ዉስጥ ካስገቧት በኋላ አልጋ ላይ እንድትተኛ ነግረዋት ልጅቷን
"የተባረክሽ ልጅ ፈጣሪ ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሽ ግቢና ሻይ ጠጪ"
እያሉ እየመረቁ እንድትገባ ቢለምኗትም
"ሌላ ግዜ እመጣለሁ"
እያለች
"ልጆትን ፈጣሪ ይማርሎት"
ብላ ተሰናብታ ወጣች።
ቤዛዊት የአልጋዉን ፍራሽ እየነጨች መሬት ላይ እንደ ቄጤማ እየጎዘጎዘችዉ ነበረ።
💫ይቀጥላል...💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...እየጎዘጎዘች ነበር
እማማ ስንቅነሽ እንግዳዋን ሸኝተዉ የቤዛዊት ጤንነት ፊቷን አንብበዉ እየሰጉ
"ደሞ እንዳይጀምራት"
በልባቸዉ እያሉ ወደ ቤታቸዉ ወደ ዉስጥ ሲዘልቁ ቤታቸዉ በብጥስጣሽ እስፖንጅ ተሞልቶ ቤዛዊት የማይሰሙ ቃላቶች እያነበነበች በእጆቿ ቀሪዉን የፍራሹን አካል እየቧጠጠች እና እየነጨች እየወረወረችዉ ነበር።
እንባ ተናነቃቸዉ በድህነታቸዉ በቅጡ የማያዉቋት ሴት በልፋት የገዙት ፍራሽ ተበታትኖ በማለቁም አልተፀፀቱም ሁሌ የቤዛዊትን ሲያዩዋት በህይወት የሌለችዉን ልጃቸዉ ስለምትታያቸዉ እንደ ልጃቸዉ ህመም አስበዉ
"ቤዛዊቴ ቤዛዊት ምን ሆንሽብኝ ምን ነካብኝሳ"
ከጎኗ እንደ ህፃን ልጅ ኩርምት ብለዉ ተቀመጡ
ቤዛዊት መልስ አልመለሰችላቸዉም እጆቿ ይቧጥጣሉ ከባድ ስራ እንደያዘ ሰዉ ተመስጣ ጥፋት ታጠፋለች ለእሷ የሚታወቃት ነገር የለም
"እ እህህ እህህህ እህ እህ እህህ"
ነገር እንደሚበላ ሰዉ ከንፈሮቿን በቀስታ እያኘከች ታጉተመትማለች የምታስበዉ ለእማማ ስንቅነሽ ስላልገባቸዉ እያቀፏት እና ፍፁም ብላ ያወራችላቸዉ ሰዉዬ ትዝ ብሏቸዉ
"ፍፁም ጋር ሄደሽ ነበር?"
ሲሉ ጠየቋት
ቤዛዊት የፍፁምን ስም እንደሰማች እማማ ስንቅነሽ ላይ አፈጠጠችባቸዉ
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
ቃላቶቹን እየደጋገመች አይኖቿን እማማ ስንቅነሽ ላይ ተክላ ቆይታ
"ቤቴ ልሂድ ፍፁም አይመጣም"
አለችና ትንሽ እንደማሰብ ብላ
"ይመጣል እንዴ?"
እማማ ስንቅነሽን አፋጠጠቻቸዉ
"ታስሮ የለ ሲፈታ ይመጣል"
አሏት የእርጅና ነገር ሀቅ ሀቁን ሳይደብቁ እያወሩ
ቤዛዊት የሆነ ነገር ያሰበች ይመስል የእማማ ስንቅነሽን የተገነጣጠለ ኮርኒስ ላይ ካፈጠጠች በኋላ
"አይጥ ማታ ማታ በዚህ ላይ ይሄዳል አደል
እኔኮ አይጥ እፈራለሁ..."
እማማ ስንቅነሽ እንዳመማት በጤናዋ እንዳልሆነች አሁን አረጋገጡ እንባ ያቀረረ ፊታቸዉን በነጠላቸዉ እያበሱ የቆመችዉን ቤዛዊትን ወደ እራሳቸዉ አልጋ ወስደዉ እያስተኟት
"አይ ሰዉ መሆን"
እያሉ እየተብከነከኑ ቤዛዊት እንቅልፍ እስኪወስዳት ፀጉሯን እየደባበሱ አስተኝተዋት ሰካራሙ ልጃቸዉ ጌታቸዉ እንዲገባ በሩን ሳይቀረቅሩት ዘጋ አርገዉት ከጎኗ እሳቸዉም ስለቤዛዊት እና ስለበፊት ልጃቸዉ መመሳሰል እያሰቡ አሸለቡ።
ፍፁም ቤዛዊትን አዋርቶ እንደተመለሰ እሱ የሚተኛበት አቅራቢያ አናቱ ላይ ፎጣ የደረበ ሰዉ ወረቀት እያነበበ አይቶ እንዳላየ ሊያልፈዉ ሲል ማስረሻ መሆኑን ሲያረጋግጥ ፍቃዱን እንዳያስታዉስበት ፊቱን አዙሮ አልፎት ቦታዉ ደርሶ እንደተቀመጠ የቤዛዊትን እና የሱን ታሪክ የፃፈበት ወረቀት ከቦታዉ እንደሌለ ሲያስታዉስ እንደማበድ አረገዉ።
ፍቃዱን በያዘዉ ክራንች በንዴት አናት አናቱን ሲመታዉ የነበረዉ ሁኔታ አይምሮዉ ላይ ታየዉ
ክራንቹ በፍቃዱ ደም ተላዉሶ የፍቃዱ ፀጉር በደም ተለዉሶ ታየዉ አፉ ዉስጥ የሚጎመዝዝ ነገር ያለ እየመሰለዉ ምራቁን እየተፋ እየተበሳጨ ወደ ማስረሻ ተንደረደረ
"አምጣ የወሰድከዉን አምጣ አምጣ"
ሲል ማስረሻ ላይ አንባረቀበት
ማስረሻ የፌዝ ሳቅ እየሳወቀ
"እብድ አፍቅረህ ነዉ ለካ"
ሲል በንቀት ወረቀቱን የፍፁም ፊት ላይ በተነለት
"ቤዛዊት እብድ አደለችም "
መሬት ላይ የተበተነዉን ወረቀት እየሰበሰበ አጣጥፎ ኪሱ ዉስጥ ከከተተ በኋላ
"ቤዛዊትን እብድ እንድትላት ማን ፈቀደልህ
ማንስ ህይወቴን አንብብ አለህ"
ፍፁም በንዴት እየተለዋወጠ ነዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየሳቀ ነዉ
በቀልድ ለዛ ባለዉ ንግግር
"ታሪክህ ሰዉ በመግደል ስላለቀ ያሳዝናል"
አለዉና አክሎበት
"ቤዛዊትን አንዱ ላፍ ያረግልሀል ኪኪ ኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
ተንከተከተ
አብዛኛው ሰዉ በታሪክህ ይስቅብሀል በዉድቀትህ ያላግጥብሀል በድክመትህ ይመጣብሀል
ቀን ሲጥልህ ብዙ ብዙ ነገሮች ይቀያየሩብሀል ከተከበረ አስተማሪነት ወደ ወንጀለኛ በአንዴዉ ስትለወጥ የሰዉ ደም አእምሮህ ዉስጥ ሲመላለስ ፍቅር ያልከዉ ነገር እሩቅ ሲሆንብህ አለም የተደፋችብህ ሲመስልህ የምታየዉ የሚያጋጥምህ ነገር ሁሉ አስከፊ ይሆናል
"ምንድነዉ ያልከዉ"
አለ ፍፁም ሁለቱንም እጆቹን ገትሮ ፊቱ ተቀያይሮ ወደ ማስረሻ አንገት እየተንደረደረ ደርሶ ማስረሻን ሲጥ አርጎ ይዞት ተያይዘዉ ወደ መሬት ወደቁ ማስረሻ ከስር ተኝቶ ይንፈራፈራል ፍፁም
ከላይ ያለ የሌለ ሀይሉን ተጠቅሞ አንቆታል።
💫ይቀጥላል ...💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...እየጎዘጎዘች ነበር
እማማ ስንቅነሽ እንግዳዋን ሸኝተዉ የቤዛዊት ጤንነት ፊቷን አንብበዉ እየሰጉ
"ደሞ እንዳይጀምራት"
በልባቸዉ እያሉ ወደ ቤታቸዉ ወደ ዉስጥ ሲዘልቁ ቤታቸዉ በብጥስጣሽ እስፖንጅ ተሞልቶ ቤዛዊት የማይሰሙ ቃላቶች እያነበነበች በእጆቿ ቀሪዉን የፍራሹን አካል እየቧጠጠች እና እየነጨች እየወረወረችዉ ነበር።
እንባ ተናነቃቸዉ በድህነታቸዉ በቅጡ የማያዉቋት ሴት በልፋት የገዙት ፍራሽ ተበታትኖ በማለቁም አልተፀፀቱም ሁሌ የቤዛዊትን ሲያዩዋት በህይወት የሌለችዉን ልጃቸዉ ስለምትታያቸዉ እንደ ልጃቸዉ ህመም አስበዉ
"ቤዛዊቴ ቤዛዊት ምን ሆንሽብኝ ምን ነካብኝሳ"
ከጎኗ እንደ ህፃን ልጅ ኩርምት ብለዉ ተቀመጡ
ቤዛዊት መልስ አልመለሰችላቸዉም እጆቿ ይቧጥጣሉ ከባድ ስራ እንደያዘ ሰዉ ተመስጣ ጥፋት ታጠፋለች ለእሷ የሚታወቃት ነገር የለም
"እ እህህ እህህህ እህ እህ እህህ"
ነገር እንደሚበላ ሰዉ ከንፈሮቿን በቀስታ እያኘከች ታጉተመትማለች የምታስበዉ ለእማማ ስንቅነሽ ስላልገባቸዉ እያቀፏት እና ፍፁም ብላ ያወራችላቸዉ ሰዉዬ ትዝ ብሏቸዉ
"ፍፁም ጋር ሄደሽ ነበር?"
ሲሉ ጠየቋት
ቤዛዊት የፍፁምን ስም እንደሰማች እማማ ስንቅነሽ ላይ አፈጠጠችባቸዉ
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
ቃላቶቹን እየደጋገመች አይኖቿን እማማ ስንቅነሽ ላይ ተክላ ቆይታ
"ቤቴ ልሂድ ፍፁም አይመጣም"
አለችና ትንሽ እንደማሰብ ብላ
"ይመጣል እንዴ?"
እማማ ስንቅነሽን አፋጠጠቻቸዉ
"ታስሮ የለ ሲፈታ ይመጣል"
አሏት የእርጅና ነገር ሀቅ ሀቁን ሳይደብቁ እያወሩ
ቤዛዊት የሆነ ነገር ያሰበች ይመስል የእማማ ስንቅነሽን የተገነጣጠለ ኮርኒስ ላይ ካፈጠጠች በኋላ
"አይጥ ማታ ማታ በዚህ ላይ ይሄዳል አደል
እኔኮ አይጥ እፈራለሁ..."
እማማ ስንቅነሽ እንዳመማት በጤናዋ እንዳልሆነች አሁን አረጋገጡ እንባ ያቀረረ ፊታቸዉን በነጠላቸዉ እያበሱ የቆመችዉን ቤዛዊትን ወደ እራሳቸዉ አልጋ ወስደዉ እያስተኟት
"አይ ሰዉ መሆን"
እያሉ እየተብከነከኑ ቤዛዊት እንቅልፍ እስኪወስዳት ፀጉሯን እየደባበሱ አስተኝተዋት ሰካራሙ ልጃቸዉ ጌታቸዉ እንዲገባ በሩን ሳይቀረቅሩት ዘጋ አርገዉት ከጎኗ እሳቸዉም ስለቤዛዊት እና ስለበፊት ልጃቸዉ መመሳሰል እያሰቡ አሸለቡ።
ፍፁም ቤዛዊትን አዋርቶ እንደተመለሰ እሱ የሚተኛበት አቅራቢያ አናቱ ላይ ፎጣ የደረበ ሰዉ ወረቀት እያነበበ አይቶ እንዳላየ ሊያልፈዉ ሲል ማስረሻ መሆኑን ሲያረጋግጥ ፍቃዱን እንዳያስታዉስበት ፊቱን አዙሮ አልፎት ቦታዉ ደርሶ እንደተቀመጠ የቤዛዊትን እና የሱን ታሪክ የፃፈበት ወረቀት ከቦታዉ እንደሌለ ሲያስታዉስ እንደማበድ አረገዉ።
ፍቃዱን በያዘዉ ክራንች በንዴት አናት አናቱን ሲመታዉ የነበረዉ ሁኔታ አይምሮዉ ላይ ታየዉ
ክራንቹ በፍቃዱ ደም ተላዉሶ የፍቃዱ ፀጉር በደም ተለዉሶ ታየዉ አፉ ዉስጥ የሚጎመዝዝ ነገር ያለ እየመሰለዉ ምራቁን እየተፋ እየተበሳጨ ወደ ማስረሻ ተንደረደረ
"አምጣ የወሰድከዉን አምጣ አምጣ"
ሲል ማስረሻ ላይ አንባረቀበት
ማስረሻ የፌዝ ሳቅ እየሳወቀ
"እብድ አፍቅረህ ነዉ ለካ"
ሲል በንቀት ወረቀቱን የፍፁም ፊት ላይ በተነለት
"ቤዛዊት እብድ አደለችም "
መሬት ላይ የተበተነዉን ወረቀት እየሰበሰበ አጣጥፎ ኪሱ ዉስጥ ከከተተ በኋላ
"ቤዛዊትን እብድ እንድትላት ማን ፈቀደልህ
ማንስ ህይወቴን አንብብ አለህ"
ፍፁም በንዴት እየተለዋወጠ ነዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየሳቀ ነዉ
በቀልድ ለዛ ባለዉ ንግግር
"ታሪክህ ሰዉ በመግደል ስላለቀ ያሳዝናል"
አለዉና አክሎበት
"ቤዛዊትን አንዱ ላፍ ያረግልሀል ኪኪ ኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
ተንከተከተ
አብዛኛው ሰዉ በታሪክህ ይስቅብሀል በዉድቀትህ ያላግጥብሀል በድክመትህ ይመጣብሀል
ቀን ሲጥልህ ብዙ ብዙ ነገሮች ይቀያየሩብሀል ከተከበረ አስተማሪነት ወደ ወንጀለኛ በአንዴዉ ስትለወጥ የሰዉ ደም አእምሮህ ዉስጥ ሲመላለስ ፍቅር ያልከዉ ነገር እሩቅ ሲሆንብህ አለም የተደፋችብህ ሲመስልህ የምታየዉ የሚያጋጥምህ ነገር ሁሉ አስከፊ ይሆናል
"ምንድነዉ ያልከዉ"
አለ ፍፁም ሁለቱንም እጆቹን ገትሮ ፊቱ ተቀያይሮ ወደ ማስረሻ አንገት እየተንደረደረ ደርሶ ማስረሻን ሲጥ አርጎ ይዞት ተያይዘዉ ወደ መሬት ወደቁ ማስረሻ ከስር ተኝቶ ይንፈራፈራል ፍፁም
ከላይ ያለ የሌለ ሀይሉን ተጠቅሞ አንቆታል።
💫ይቀጥላል ...💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2