#ማን_ልበላት?
አያችኋት ያቺን - ከሰው ተነጥላ?
መልኬ ይኼውላችሁ - ስሜ ይቆይ ብላ፡፡
አትረዝም፣አታጥር
አትቀላ፣አትጠቁር ፤
ክሽን ያለ ቁመት ፣ ክሽን ያለ ከለር
በጣም የምትስብ ፣ በጣም የምታምር
አያችኋት ያቺን?
አትወፍር፣አትቀጥን
አትዘገይ፣አትፈጥን
የአይኖቿ ብርሐን ፣ ፅልመትን የሚያሸሽ
ለአይን የምታሳሳ ፣ ቢነኳት ምትቆሽሽ፡፡
አይችኋት ያቺን ?
ብዙም ዝም ያላለች ፣ ብዙም ማታወራ
ብዙም የማትደፍር ፣ ብዙም የማትፈራ
የማትንቅ ፣ ግን ኩሩ
የውበት ድንበሩ፡፡
ያቺን አያችኋት?
ስሟን ባላውቀውም - ስም እንዳወጣላት
ምናልባት
ምናልባት
እሷን የሚመጥን - ስም ከተገኘላት
ውቧን ማን ልበላት???
አያችኋት ያቺን - ከሰው ተነጥላ?
መልኬ ይኼውላችሁ - ስሜ ይቆይ ብላ፡፡
አትረዝም፣አታጥር
አትቀላ፣አትጠቁር ፤
ክሽን ያለ ቁመት ፣ ክሽን ያለ ከለር
በጣም የምትስብ ፣ በጣም የምታምር
አያችኋት ያቺን?
አትወፍር፣አትቀጥን
አትዘገይ፣አትፈጥን
የአይኖቿ ብርሐን ፣ ፅልመትን የሚያሸሽ
ለአይን የምታሳሳ ፣ ቢነኳት ምትቆሽሽ፡፡
አይችኋት ያቺን ?
ብዙም ዝም ያላለች ፣ ብዙም ማታወራ
ብዙም የማትደፍር ፣ ብዙም የማትፈራ
የማትንቅ ፣ ግን ኩሩ
የውበት ድንበሩ፡፡
ያቺን አያችኋት?
ስሟን ባላውቀውም - ስም እንዳወጣላት
ምናልባት
ምናልባት
እሷን የሚመጥን - ስም ከተገኘላት
ውቧን ማን ልበላት???
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አምስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
በቡድን መሆናችን እንድንተጋገዝ እና ችግርን በጋራ እንድናልፍ ቢረዳንም ሰዎች እኛን ሲያዩ ይፈሩ ጀመር። በእኛ
እድሜ ያሉ ታዳጊዎች በአማጺዎች ተገደው ይገድሉ ያቆስሉ ነበር። ስለዚህ ሰዎች ቤተሰቦቻቸውን ለመጠበቅ ሲሉ እኛን ለመጉዳት ጥረዋል። እኛም ጥግጥጉን ይዘን መንደሮችን ማለፍ
ጀመርን። የጦርነት አንዱ መዘዝ ይሄ ነው። ሁሉም ሰው መተማመን ያቆማል፣ ጸጉረ ልውጥ ሰው በሙሉ እንደጠላት
ይቆጠራል። የሚያውቁህ ሰዋች እንኳ ሲያቀርቡህ ሲያወሩህ በጥንቃቄ ነው::
በአንድ መንደር ስናልፍ ገብሬላን የምታውቅ ሴትዮ አክስቱ ወደ ሰላሳ ኪሎሜትር የምትርቅ መንደር ውስጥ እንዳለች ነገረችው: አቅጣጫውን ጠቁማን ጉዞ ጀመርን።
የአዝመራ ወቅት እየተቃረበ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ዝናብ ዘንቧል መሬቱ ረስርሷል፡፡ ወፎች በማንጎ ዛፍ ላይ ቤታቸውን ይሰራሉ፡፡ ጠዋት ጠዋት ጤዛ ይታይ ነበር። አጎቴ በዚህ ወቅት
ነው መሞት ምፈልገው እያለ ይቀልድ ነበር። ፀሐይ ቀድማ ወጥታ በሰማያዊው ሰማይ ላይ ትታያለች።
የካማቶር ነዎሪዎች ሁሉም ገበሬ ናቸው። ማገዝ የግድ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከግብርና ጋር ተገናኘን። የመጀመሪያ
ስራችን የነበረው ማሳ ማጽዳት ነበር፡፡ ቅጠላቸው የተቆላለፈ የወይን ዛፎችን መቁረጥ በጣም አስቸጋሪ ነበር። ሶስት ስዓት የሚፈጀውን ሶስት ቀን ቆየንበት።
ከዛ ዘራን።
ለሶስት ወራት ያህል በካማቶር በእርሻ ስራ ላይ ብንቆይም ልለምደው አልቻልኩም። የተመቸኝ ከስዐት እረፍት ላይ ለዋና ወደ ወንዝ የምንወርድበት ጊዜ ብቻ ነበር። ስራው ለፍቶ መና
ነበር። ምክንያቱም አማጺዎች ሲመጡ ትተነው እንሮጣለን ሰብሉ በአረም ይዋጣል ወይም እንስሳት ይበላል::
አንድ የአማጺዎች ጥቃት ግን ይባስ ብሎ ከወንድሜ ጋር አለያየኝ። ትልቅ ወንድሜን ጅኒ የርን ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት
ያን ጊዜ ነበር።
ጥቃቱ የደረሰው በአንድ ለሊት ድንገት ነበር። ስለ አማጺዎች መድረስ ምንም ወሬ አልተሰማም :: ከየት መጡ ሳይባል
መንደራችን ገቡ።
ከምሽቱ ሁለት ስዐት አካባቢ ህዝቡ የቀኑን የመጨረሻ ጸሎት እያደረገ ነበር። ኢማሙ ብዙ እንደሚቆይ ይታወቃል፡፡ በህዝቡ ፊት ለፊት ሁኖ ረዥም የሱራ ጸሎት ያደርሳል። የአማጺዎችን
መግባት ሲሰማ ከኢማሙ በስተቀር ሁሉም መስጊዱን ጥሎ ሄደ። አማጺዎች ኢማሙን ብቻውን አግንተው ህዝቡ በየት
በኩል እንደሄደ ጠየቁት፡፡አልመለሰላቸውም፡፡ እጁን እና እግሩን
አስረው አቃጠሉት።
የአማጺዎች ጥቃት ሲጀምር ጅኒ የር እና ጓደኞቼ ቤት ውስጥ ነበሩ። እኔ ግን ደጃፍላይ ነበርኩ። ድንገት ተኩስ ሲጀምር
ፌቴን ሳላዞር ሩጬ ጫካ ውስጥ ገባሁ።አንድ ዛፍ ስር ብቻየን
አደርኩ። ሲነጋ ካሎኮን አገኘሁት። መንደሩ መሃል ላይ የኢማሙ የተቃጠለ አስክሬን ተጥሏል፤ ቤቶች ተቃጥለዋል
ህይወት የሚባል የለም:: በጥቅጥቁ ደን መኋል ጅኒ የር እና ጓደኞቻችንን ፈለግን
ግን ልናገኛቸው አልቻልንም።
የምናውቃቸው ሰዎች አግኝተን ለሁለት ሳምንታት ያህል ከነሱ ጋር በረግረጉ አካባቢ ተደበቅን። ሁለት ሳምንት ሁለት ወር ሆነብኝ፡፡ ስለእነ ጅኒየር አስባለሁ። አምልጠው ይሆን? ሁሉንም እያጣሁ ነው፦ቤተሰቦቼን፣ጓደኞቼን። በፍርሃት ውስጥ መኖር ሰለቸኝ:: ሞትን የምጠብቅ መስሎ ተሰማኝ። መንደሩ መልቀቅ ሰላም ወደ ሚገኝበት መሄድ እንዳለብኝ ተሰማኝ:: ቆረጥኩ። ካሎኮ ግን ፈራ፤ በረግረጉ መቆየትን መረጠ።
ጠዋት ሁሉንም ተሰናብቼ ወደ ምዕራብ መጓዝ ጀመርኩ።በኪሴ ከያዝኩት ያልበሰለ ብርቱካን ውጭ ሌላ ምንም
አልያዝኩም:: ለስድስት ቀናት ያገኘሁትን እየበላሁ ተጓዝኩ።
በስድስተኛው ቀን ሰው አገኘሁ፡፡ የአንድ ቤተሰብ አባላት እየዋኙ ነበር። ሰላምታ ሰጠኋቸው፡፡ አልመለሱልኝም። ልብሴን አውልቄ ወደ ወንዙ ገባሁ፡፡ " ከየት ነው የመጣሃው ወዴት እየሄድክ ነው?” ሲል ጠየቀኝ።
ከማታሩ ጆንግ ነኝ ወዴት እንደምሄድ ግን አላውቅም” ስል መለስኩለት። ቀጥየ "ወደ ቦንቴ ለመሄድ አቋራጩ መንገድ የቱ
ነው” ስል ጠየቁ፡፡ ቦንቴ ስላማዊ ቦታ ነው ይባላል። በባህሩ በኩል እንድሄድ እና ሰዎችን እንድጠይቅ ነገረኝ።
ብዙ የተቃጠሉ መንደሮችን እያለፍኩ ተጓዝኩ፡፡ በመንደሮቹ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሰዎች ከአዋቂ እስከ ህጻናት አየሁ።አይናቼን ለመጨፈን ሞከርኩ ግን አልቻልኩም። በመጨረሻ ደነዘዝኩ።
ብዙ ስጓዝ ውየ ራሴን ጥቅጥቅ ያለ ጫካ መሃል አገኘሁት።ከቆምኩበት ጫካ
ሰማዩን እንዳላይ በረጃጂም ዛፎች
ቅርንጫፎች እና ቅጠሎች ተጋርድዋል፡ እንዴት እዚህ ጫካ እንደገባሁ እንኳ አላውቅም። ለሊቱ ሲቃረብ ረጂም ቅርንጫፍ ካለው አንድ ዛፍ ላይ ወጥቼ አደርኩ።
በሚቀጥለው ቀን ከጫካው ለመውጣት ወሰንኩ። በጉዞየ በአንድ ትልቅ አለት ላይ የሚወርድ ፏፏቴ አየሁ። በዳርቻው
ትንሽ ለማረፍ ወሰንኩ። ግን ብዙም አልቆየሁም። ወደ ሃሳብ ከምገባ ብየ ጉዞየን ቀጠልኩ። ቀኑን ሙሉ ተጓዝኩ። ዙሬ ዙሬ በመጨረሻ ራሴን ትናንት ማታ ካደርኩብት እዛው ቦታ ላይ
አገኘሁት፡፡ እንደጠፋሁ አመንኩ። ስለዚህ ራሴን ማደላደል አዲሱ ቤቴን ማመቻቸት ጀመርኩ። ቅርንጫፎች ላይ ቅጠሎችን
ጨመርኩ።አካባቢውን ዙሬ ቃኘሁ። ምንም እንኳ ብጠፋ እና ብቻየን ብሆንም ለጊዜው ይሄ ቦታ ሰላማዊ ነው።
የፏፏቴው ጥግ ባልበሰሉ ፍራፍሬዎች ተሸፍኗል። አንዱን ቆርጬ በላሁ። መራራ ነው:: ነገር ግን ረሃብ ያስታግሳል።
ስለዚህ ወደ አስራ ሁለት የሚሆኑ ፍሬዎችን በላሁ። ከተወሰኑ ስዓታት በኋላ ገላየን ለመታጠብ አሰብኩ። ልብሴ ቋሽሽዋል፣የሰውነቴም ሽታ ተቀይሯል። መጀመሪያ በንጹህ ውሃ ቀጥሎ
በእንዶድ ገላየን ታጠብኩ ልብሴንም አጠብኩ።
አስቸጋሪው ነገር ብቸኝነት ነበር። ብቻህን ስትሆን ብዙ ታስባለህ ላቸማሰብ ሞከርኩ ግን አልቻልኩም፡፡ ወደ ጭንቅላቴ የሚመጡትን ሁሉንም ሃሳቦች ለመከላከል ወሰንኩ ብዙውን
ጊዜየን ሃሳብን በመዋጋት ማለትም ስለ ወደፊት ህይወቴ ማሰብ፡
ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ የት ናቸው የሚሉ ሃሳቦችን በመሸሽ አሳልፍ ነበር።
ይሄን ሳደርግ ራሴ ከመቼውም በላይ የጠነከረ መስለኝ። ሃሳቦቹ በህልሜ ይመጣሉ በማለት መተኛት ፈራሁ::
በጣም ትንሽ እያለሁ አባቴ የሚለው አባባል ነበር " በህይወት እስካለህ የተሻለ ቀን እንደሚመጣ እና መልካም ነገር እንደሚሆን ተስፋ አለ። እጣ ፈንታቸው መጥፎ የሆነ ደግ ጊዜ
የማይመጣለቸው ሰዎች ግን ይሞታሉ።”በጉዞየ ስለዚህ አባባል
አስብ ነበር፡፡ እነዚህ ቃላቶች ወደፊት እንድሄድ እንድገፋ አበረቱኝ፡፡
በረሃብ ደክሜ እያዘገምኩ ስሄድ በእኔ የእድሜ ክልል ያሉ ህጻናት አጋጠሙኝ። ስድስት ነበሩ፤ ከስድስቱ ሶስቱ አልሃጂ፣
ሙሳ እና ኬን ማታሩ ጆንግ በሚገኘው ሴንትያል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አብረውኝ ተምረዋል። እጃችንን በመጨባበጥ ሰላም ከተለዋወጥን በኋላ ወደየት እየሄዱ እንደሆነ ጠየቅኳቸው፡፡ በቦንቴ ወረዳ ወደ ምትገኝ የል ወደ ምትባል ሰፈር እየሄዱ እንደሆነ እና የል በ ሴራሌዮን መከላከያ ኃይል የሚጠበቅ
አስተማማኝ ሰላም ያለበት አካባቢ እንደሆነ ነገሩኝ። ተከተልኳቸው::
እንደገና የሰባት ህጻናት ቡድን፡፡ ሰዎች እኛን ሲያዩ ይጮሃሉ ይሮጣሉ። እንደአውሬዎች ተቆጠርን፡፡ ቦታ የሚያመለክተን አቅጣጫ የሚጠቁመን ሰው አልነበረም። ከስድስት ቀናት ጉዞ
በኋላ አንድ ሽማግሌ ሰው አገኘን። የመንደሩ ሰው እኛን ሲያይ ሩጦ እንደጠፋ እሱ ግን መሮጥ እንደማይችል ነገረን። ከየት እንደመጣን እና ወዴት መሄድ እንደምንፈልግ ነገርነው፡፡
ለተወሰኑ ቀናት ከእሱ ጋር
#ክፍል_አምስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
በቡድን መሆናችን እንድንተጋገዝ እና ችግርን በጋራ እንድናልፍ ቢረዳንም ሰዎች እኛን ሲያዩ ይፈሩ ጀመር። በእኛ
እድሜ ያሉ ታዳጊዎች በአማጺዎች ተገደው ይገድሉ ያቆስሉ ነበር። ስለዚህ ሰዎች ቤተሰቦቻቸውን ለመጠበቅ ሲሉ እኛን ለመጉዳት ጥረዋል። እኛም ጥግጥጉን ይዘን መንደሮችን ማለፍ
ጀመርን። የጦርነት አንዱ መዘዝ ይሄ ነው። ሁሉም ሰው መተማመን ያቆማል፣ ጸጉረ ልውጥ ሰው በሙሉ እንደጠላት
ይቆጠራል። የሚያውቁህ ሰዋች እንኳ ሲያቀርቡህ ሲያወሩህ በጥንቃቄ ነው::
በአንድ መንደር ስናልፍ ገብሬላን የምታውቅ ሴትዮ አክስቱ ወደ ሰላሳ ኪሎሜትር የምትርቅ መንደር ውስጥ እንዳለች ነገረችው: አቅጣጫውን ጠቁማን ጉዞ ጀመርን።
የአዝመራ ወቅት እየተቃረበ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ዝናብ ዘንቧል መሬቱ ረስርሷል፡፡ ወፎች በማንጎ ዛፍ ላይ ቤታቸውን ይሰራሉ፡፡ ጠዋት ጠዋት ጤዛ ይታይ ነበር። አጎቴ በዚህ ወቅት
ነው መሞት ምፈልገው እያለ ይቀልድ ነበር። ፀሐይ ቀድማ ወጥታ በሰማያዊው ሰማይ ላይ ትታያለች።
የካማቶር ነዎሪዎች ሁሉም ገበሬ ናቸው። ማገዝ የግድ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ከግብርና ጋር ተገናኘን። የመጀመሪያ
ስራችን የነበረው ማሳ ማጽዳት ነበር፡፡ ቅጠላቸው የተቆላለፈ የወይን ዛፎችን መቁረጥ በጣም አስቸጋሪ ነበር። ሶስት ስዓት የሚፈጀውን ሶስት ቀን ቆየንበት።
ከዛ ዘራን።
ለሶስት ወራት ያህል በካማቶር በእርሻ ስራ ላይ ብንቆይም ልለምደው አልቻልኩም። የተመቸኝ ከስዐት እረፍት ላይ ለዋና ወደ ወንዝ የምንወርድበት ጊዜ ብቻ ነበር። ስራው ለፍቶ መና
ነበር። ምክንያቱም አማጺዎች ሲመጡ ትተነው እንሮጣለን ሰብሉ በአረም ይዋጣል ወይም እንስሳት ይበላል::
አንድ የአማጺዎች ጥቃት ግን ይባስ ብሎ ከወንድሜ ጋር አለያየኝ። ትልቅ ወንድሜን ጅኒ የርን ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት
ያን ጊዜ ነበር።
ጥቃቱ የደረሰው በአንድ ለሊት ድንገት ነበር። ስለ አማጺዎች መድረስ ምንም ወሬ አልተሰማም :: ከየት መጡ ሳይባል
መንደራችን ገቡ።
ከምሽቱ ሁለት ስዐት አካባቢ ህዝቡ የቀኑን የመጨረሻ ጸሎት እያደረገ ነበር። ኢማሙ ብዙ እንደሚቆይ ይታወቃል፡፡ በህዝቡ ፊት ለፊት ሁኖ ረዥም የሱራ ጸሎት ያደርሳል። የአማጺዎችን
መግባት ሲሰማ ከኢማሙ በስተቀር ሁሉም መስጊዱን ጥሎ ሄደ። አማጺዎች ኢማሙን ብቻውን አግንተው ህዝቡ በየት
በኩል እንደሄደ ጠየቁት፡፡አልመለሰላቸውም፡፡ እጁን እና እግሩን
አስረው አቃጠሉት።
የአማጺዎች ጥቃት ሲጀምር ጅኒ የር እና ጓደኞቼ ቤት ውስጥ ነበሩ። እኔ ግን ደጃፍላይ ነበርኩ። ድንገት ተኩስ ሲጀምር
ፌቴን ሳላዞር ሩጬ ጫካ ውስጥ ገባሁ።አንድ ዛፍ ስር ብቻየን
አደርኩ። ሲነጋ ካሎኮን አገኘሁት። መንደሩ መሃል ላይ የኢማሙ የተቃጠለ አስክሬን ተጥሏል፤ ቤቶች ተቃጥለዋል
ህይወት የሚባል የለም:: በጥቅጥቁ ደን መኋል ጅኒ የር እና ጓደኞቻችንን ፈለግን
ግን ልናገኛቸው አልቻልንም።
የምናውቃቸው ሰዎች አግኝተን ለሁለት ሳምንታት ያህል ከነሱ ጋር በረግረጉ አካባቢ ተደበቅን። ሁለት ሳምንት ሁለት ወር ሆነብኝ፡፡ ስለእነ ጅኒየር አስባለሁ። አምልጠው ይሆን? ሁሉንም እያጣሁ ነው፦ቤተሰቦቼን፣ጓደኞቼን። በፍርሃት ውስጥ መኖር ሰለቸኝ:: ሞትን የምጠብቅ መስሎ ተሰማኝ። መንደሩ መልቀቅ ሰላም ወደ ሚገኝበት መሄድ እንዳለብኝ ተሰማኝ:: ቆረጥኩ። ካሎኮ ግን ፈራ፤ በረግረጉ መቆየትን መረጠ።
ጠዋት ሁሉንም ተሰናብቼ ወደ ምዕራብ መጓዝ ጀመርኩ።በኪሴ ከያዝኩት ያልበሰለ ብርቱካን ውጭ ሌላ ምንም
አልያዝኩም:: ለስድስት ቀናት ያገኘሁትን እየበላሁ ተጓዝኩ።
በስድስተኛው ቀን ሰው አገኘሁ፡፡ የአንድ ቤተሰብ አባላት እየዋኙ ነበር። ሰላምታ ሰጠኋቸው፡፡ አልመለሱልኝም። ልብሴን አውልቄ ወደ ወንዙ ገባሁ፡፡ " ከየት ነው የመጣሃው ወዴት እየሄድክ ነው?” ሲል ጠየቀኝ።
ከማታሩ ጆንግ ነኝ ወዴት እንደምሄድ ግን አላውቅም” ስል መለስኩለት። ቀጥየ "ወደ ቦንቴ ለመሄድ አቋራጩ መንገድ የቱ
ነው” ስል ጠየቁ፡፡ ቦንቴ ስላማዊ ቦታ ነው ይባላል። በባህሩ በኩል እንድሄድ እና ሰዎችን እንድጠይቅ ነገረኝ።
ብዙ የተቃጠሉ መንደሮችን እያለፍኩ ተጓዝኩ፡፡ በመንደሮቹ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሰዎች ከአዋቂ እስከ ህጻናት አየሁ።አይናቼን ለመጨፈን ሞከርኩ ግን አልቻልኩም። በመጨረሻ ደነዘዝኩ።
ብዙ ስጓዝ ውየ ራሴን ጥቅጥቅ ያለ ጫካ መሃል አገኘሁት።ከቆምኩበት ጫካ
ሰማዩን እንዳላይ በረጃጂም ዛፎች
ቅርንጫፎች እና ቅጠሎች ተጋርድዋል፡ እንዴት እዚህ ጫካ እንደገባሁ እንኳ አላውቅም። ለሊቱ ሲቃረብ ረጂም ቅርንጫፍ ካለው አንድ ዛፍ ላይ ወጥቼ አደርኩ።
በሚቀጥለው ቀን ከጫካው ለመውጣት ወሰንኩ። በጉዞየ በአንድ ትልቅ አለት ላይ የሚወርድ ፏፏቴ አየሁ። በዳርቻው
ትንሽ ለማረፍ ወሰንኩ። ግን ብዙም አልቆየሁም። ወደ ሃሳብ ከምገባ ብየ ጉዞየን ቀጠልኩ። ቀኑን ሙሉ ተጓዝኩ። ዙሬ ዙሬ በመጨረሻ ራሴን ትናንት ማታ ካደርኩብት እዛው ቦታ ላይ
አገኘሁት፡፡ እንደጠፋሁ አመንኩ። ስለዚህ ራሴን ማደላደል አዲሱ ቤቴን ማመቻቸት ጀመርኩ። ቅርንጫፎች ላይ ቅጠሎችን
ጨመርኩ።አካባቢውን ዙሬ ቃኘሁ። ምንም እንኳ ብጠፋ እና ብቻየን ብሆንም ለጊዜው ይሄ ቦታ ሰላማዊ ነው።
የፏፏቴው ጥግ ባልበሰሉ ፍራፍሬዎች ተሸፍኗል። አንዱን ቆርጬ በላሁ። መራራ ነው:: ነገር ግን ረሃብ ያስታግሳል።
ስለዚህ ወደ አስራ ሁለት የሚሆኑ ፍሬዎችን በላሁ። ከተወሰኑ ስዓታት በኋላ ገላየን ለመታጠብ አሰብኩ። ልብሴ ቋሽሽዋል፣የሰውነቴም ሽታ ተቀይሯል። መጀመሪያ በንጹህ ውሃ ቀጥሎ
በእንዶድ ገላየን ታጠብኩ ልብሴንም አጠብኩ።
አስቸጋሪው ነገር ብቸኝነት ነበር። ብቻህን ስትሆን ብዙ ታስባለህ ላቸማሰብ ሞከርኩ ግን አልቻልኩም፡፡ ወደ ጭንቅላቴ የሚመጡትን ሁሉንም ሃሳቦች ለመከላከል ወሰንኩ ብዙውን
ጊዜየን ሃሳብን በመዋጋት ማለትም ስለ ወደፊት ህይወቴ ማሰብ፡
ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ የት ናቸው የሚሉ ሃሳቦችን በመሸሽ አሳልፍ ነበር።
ይሄን ሳደርግ ራሴ ከመቼውም በላይ የጠነከረ መስለኝ። ሃሳቦቹ በህልሜ ይመጣሉ በማለት መተኛት ፈራሁ::
በጣም ትንሽ እያለሁ አባቴ የሚለው አባባል ነበር " በህይወት እስካለህ የተሻለ ቀን እንደሚመጣ እና መልካም ነገር እንደሚሆን ተስፋ አለ። እጣ ፈንታቸው መጥፎ የሆነ ደግ ጊዜ
የማይመጣለቸው ሰዎች ግን ይሞታሉ።”በጉዞየ ስለዚህ አባባል
አስብ ነበር፡፡ እነዚህ ቃላቶች ወደፊት እንድሄድ እንድገፋ አበረቱኝ፡፡
በረሃብ ደክሜ እያዘገምኩ ስሄድ በእኔ የእድሜ ክልል ያሉ ህጻናት አጋጠሙኝ። ስድስት ነበሩ፤ ከስድስቱ ሶስቱ አልሃጂ፣
ሙሳ እና ኬን ማታሩ ጆንግ በሚገኘው ሴንትያል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አብረውኝ ተምረዋል። እጃችንን በመጨባበጥ ሰላም ከተለዋወጥን በኋላ ወደየት እየሄዱ እንደሆነ ጠየቅኳቸው፡፡ በቦንቴ ወረዳ ወደ ምትገኝ የል ወደ ምትባል ሰፈር እየሄዱ እንደሆነ እና የል በ ሴራሌዮን መከላከያ ኃይል የሚጠበቅ
አስተማማኝ ሰላም ያለበት አካባቢ እንደሆነ ነገሩኝ። ተከተልኳቸው::
እንደገና የሰባት ህጻናት ቡድን፡፡ ሰዎች እኛን ሲያዩ ይጮሃሉ ይሮጣሉ። እንደአውሬዎች ተቆጠርን፡፡ ቦታ የሚያመለክተን አቅጣጫ የሚጠቁመን ሰው አልነበረም። ከስድስት ቀናት ጉዞ
በኋላ አንድ ሽማግሌ ሰው አገኘን። የመንደሩ ሰው እኛን ሲያይ ሩጦ እንደጠፋ እሱ ግን መሮጥ እንደማይችል ነገረን። ከየት እንደመጣን እና ወዴት መሄድ እንደምንፈልግ ነገርነው፡፡
ለተወሰኑ ቀናት ከእሱ ጋር
እንድንቆይ ጠየቀን። ምግብ ስጠን። ከበላን በኋላ ወደ የል የሚወስደውን አቅጣጫ በምርኩዙ ምድር ላይ ስሉ አሳየን።
ኦና የሆነውን መንደር አልፈን ከወጣን ከቀናት በኋላ አንድ ጥዋት ከትልቅ ማሽን የሚወጣ ሚመስል ከፍተኛ ድምጽ ሰማን።
አንዴ ከአስፓልት መንገድ ላይ ብረት ሲወድቅ፣ መብረቅ መንከባለል። እነዚህ
ሲያንጎዳጉድ፤ መንከባለል አሁንም
ድምጾች በሙሉ ጆሮችን ደረሱ። ወዲያው ወደ ጫካው በመግባት ተደበቅን። ተያየን። ማንም መልስ የለውም። ኬን መንፏቀቅ ጀመረ። ተከተልነው:: ቦታውን ከቃኘ በኋላ
" ውሃ ነው፤ ብዙ ውሃ እና አሽዋ::”
እና ድምጹ ምንድን ነው?” አለ አልሃጂ።
የማየው ነገር ውሃ እና አሽዋ ብቻ ነው።
አትላንቲክ ውቅያኖስ ነበር፡፡ የምንሰማው ድምጸ ዳርቻው በማዕበል ሲናጥ የሚፈጠር ነበር። የውቅያኖስ የተወሰነውን ክፍል አይቼ አውቃለሁ፡፡ የዚህን ያህል ሰፊ ዳርቻ ግን አይቼ
አላውቅም:አይኔ ከሚደርስበት ጥግ በላይ ዳርቻው ተዘርግቷል።
በሩቅ ሲታይ በእጀጉ ሰማያዊው ቀለም የያዘው ሰማይ በአግድሞሺ ወርዶ ውቅያኖሱን የነካው ይመስላል።
ወደ ውቅያኖሱ ቀረብን፤ በአሽዋው ጥግ ተቀምጠን ውቅያኖሱን ተመለከትን ተደጋጋሚ ማዕበል እያየን ተደነቅን።
ሁሉን ረስተን መሯሯጥ ጀመርን፤ አሽዋው ለይ ትግል ገጠምን ከዛ ደግሞ የእጅ ኳስ እግር ኳስ ያልተጫወትነው ጭዋታ የለም። ልባችን በሐሴት ተሞላ። ለትንሽ ጊዜም ቢሆን ችግራችንን ያየነውን መከራ ሁሉ ረሳን፡፡ በቀጣዩ ቀን ንጋት ላይ ጉዞችንን ቀጠልን። ረፋድ ላይ
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ኦና የሆነውን መንደር አልፈን ከወጣን ከቀናት በኋላ አንድ ጥዋት ከትልቅ ማሽን የሚወጣ ሚመስል ከፍተኛ ድምጽ ሰማን።
አንዴ ከአስፓልት መንገድ ላይ ብረት ሲወድቅ፣ መብረቅ መንከባለል። እነዚህ
ሲያንጎዳጉድ፤ መንከባለል አሁንም
ድምጾች በሙሉ ጆሮችን ደረሱ። ወዲያው ወደ ጫካው በመግባት ተደበቅን። ተያየን። ማንም መልስ የለውም። ኬን መንፏቀቅ ጀመረ። ተከተልነው:: ቦታውን ከቃኘ በኋላ
" ውሃ ነው፤ ብዙ ውሃ እና አሽዋ::”
እና ድምጹ ምንድን ነው?” አለ አልሃጂ።
የማየው ነገር ውሃ እና አሽዋ ብቻ ነው።
አትላንቲክ ውቅያኖስ ነበር፡፡ የምንሰማው ድምጸ ዳርቻው በማዕበል ሲናጥ የሚፈጠር ነበር። የውቅያኖስ የተወሰነውን ክፍል አይቼ አውቃለሁ፡፡ የዚህን ያህል ሰፊ ዳርቻ ግን አይቼ
አላውቅም:አይኔ ከሚደርስበት ጥግ በላይ ዳርቻው ተዘርግቷል።
በሩቅ ሲታይ በእጀጉ ሰማያዊው ቀለም የያዘው ሰማይ በአግድሞሺ ወርዶ ውቅያኖሱን የነካው ይመስላል።
ወደ ውቅያኖሱ ቀረብን፤ በአሽዋው ጥግ ተቀምጠን ውቅያኖሱን ተመለከትን ተደጋጋሚ ማዕበል እያየን ተደነቅን።
ሁሉን ረስተን መሯሯጥ ጀመርን፤ አሽዋው ለይ ትግል ገጠምን ከዛ ደግሞ የእጅ ኳስ እግር ኳስ ያልተጫወትነው ጭዋታ የለም። ልባችን በሐሴት ተሞላ። ለትንሽ ጊዜም ቢሆን ችግራችንን ያየነውን መከራ ሁሉ ረሳን፡፡ በቀጣዩ ቀን ንጋት ላይ ጉዞችንን ቀጠልን። ረፋድ ላይ
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
❤2👍1
#እንዲህ_አይነት_ሰው_አይታችኋል?
ጥርስ እያለው - የማይስቅ
ሐሳብ እያለው
የማይጠይቅ፤
አፍ እያለው - ማያወራ
እጅ እያለው - የማይሰራ::
ዝም ብሎ
አይኑ ብቻ ሚንቀዋለል
በአውራ ጎዳና ሚንገዋለል፧
እንዲህ አይነት ሰው አይታችኋል?
ጤነኛ መሳይ - ግን ያበደ
ብቸኛ ፍጡር - የተካደ፤
መንገደኛን በአይኑ ሲከተል
ህዝብ ቆጣሪ የሚመስል፤
እንዲህ አይነት ሰው አይታችኋል?
ስሜት ያለው የማይመስል
በሰው አሽሙር ልቡ ማይቆስል፤
እሾህና አስፓልት የማይመርጥ
እግሩ የትም የሚረግጥ፤
ማዶ ማዶውን እያየ
ከገሃዱ ዓለም የተለየ፤
እንዲህ አይነት ሰው አይታችኋል?
ጥርስ እያለው - የማይስቅ
ሐሳብ እያለው
የማይጠይቅ፤
አፍ እያለው - ማያወራ
እጅ እያለው - የማይሰራ::
ዝም ብሎ
አይኑ ብቻ ሚንቀዋለል
በአውራ ጎዳና ሚንገዋለል፧
እንዲህ አይነት ሰው አይታችኋል?
ጤነኛ መሳይ - ግን ያበደ
ብቸኛ ፍጡር - የተካደ፤
መንገደኛን በአይኑ ሲከተል
ህዝብ ቆጣሪ የሚመስል፤
እንዲህ አይነት ሰው አይታችኋል?
ስሜት ያለው የማይመስል
በሰው አሽሙር ልቡ ማይቆስል፤
እሾህና አስፓልት የማይመርጥ
እግሩ የትም የሚረግጥ፤
ማዶ ማዶውን እያየ
ከገሃዱ ዓለም የተለየ፤
እንዲህ አይነት ሰው አይታችኋል?
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ስድስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
የተጠጋጉ ጎጆ ቤቶችን ተመለከትን። ከመንደሩ ስንደርስ ማንም የለም። ከእኛ ተደብቀው ነበር። ብዙም ሳይቆይ አሳ አጥማጆች መጥረቢያ፣ ጦር እና መረብ ይዘው ወጡ። ምንም ማድረግ
አልቻልንም። ባለንበት ደርቀን ቆምን።
እንግዲያውስ "እባካችሁ እኛ ልንጎዳችሁ አልመጣንም፧ መንገደኞች ነን”ብለን ጮህን።አሳ አጥማጆች በሰደፍ መተው ጣሉን፡፡ ከበላያችን ላይ ተቀምጠው ካስሩን በኋላ ወደ አለቃቸው ወሰዱን። ብዙ ጥያቄዎች ጠየቁን። ከየት እንደመጣን፣ የት እንደምንሄድ እና
ለምን ይሄን አቅጣጫ እንደመረጥን ተጠየቅን፡፡ በመጨረሻ እጅ እና እግሮቻችንን ፈተው ከመንደራቸው አባረሩን። ጫማችንን ግን አልሰጡንም::
ብዙ ከተጓዝን በኋላ ነበር አሳ አጥማጆቹ ምን እንደቀጡን የገባን፡፡ ፀሐይ ስትወጣ 120 ዲግሪ ሆነ። ምንም ምንጠጋበት
ዛፍ እንኳ አልነበረም፡፡ ፀሐይዋ አሽዋው ላይ ስታርፍ በጣም ሞቀ፤ ግለት ሆነ። በባዶ እግር አሽዋ ላይ ተራመድን።
እግሮቻችንን ቆሰሉ። ደነዘዝን።በመጨረሻ አንድ ጎጆ ቤት ላይ ደረስን፡፡ ወደ ውስጥ ገብተን ተቀመጥን፡፡ የቤቱ ባለቤት ብዙም
ሳይቆይ መጣ። በሩ ላይ ቆሞ ተመለከተን እና ጉዳታችንን ሲያይ ፊቱን ዙሮ ሄደ፡፡
ከትንሽ ቆይታ በኋላ ሳር ይዞ መጣ። እሳት አያያዘ ከዛ ሳሩን በጥቂቱ እሳቱ እንዲለበለብ ካደረገ በኋላ ሳሩን ወደ እግሮቻችንን አስጠጋው:: ሙቀቱ ስቃያችንን አስታገስልን።ቀጥሎ የተጠበሰ አሳ ሾርባ፣ ሩዝ እና ውሃ ይዞ መጣ እና
ፊታችን ላይ አስቀምጦ እንድንበላ ጠየቀን፡፡ እንደገና ወቶ ሄደ፤
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ተመለሰ። የምንተኛበትን ምንጣፍ አሳየን፤ ከመተኛታችን በፊት እግሮቻችንን የምንቀባው ቅባት ሰጠን።
በሚቀጥለው ቀን ስም አልባው እንግዳ ተቀባይ ሰው ምግብ ይዞልን መጣ። ፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ እየተሻለን እንደሆነና እሱም ደስ እንዳለው ነገረን።
በጎጆው ለሳምንት ቆየን።እንግዳ ተቀባዩ ጥዋት እና ማታ ምግብ ይሰጠናል።ጥርሱ ነጭ በረዶ ይመስላል ከወገብ በላይ ሁሌም ራቁቱን ነው ልብስ አይለብስም።አንድ ቀን ስሙን ጠየቁት።ምን ይጠቅምሀል ብለህ ነው። እንደዚሁ ይሻለናል ለደንነታችን አለኝ።
በሚቀጥለው ቀን አመሻሽ ላይ ወደ ውቅያኖስ ይዞን ወረደ።እግራችንን እንድንነክር ነገረን።ጨዋማ ውሃ ከስቃይ እንደሚያስታግስ እና ከቲታኖስ እንደሚጠብቀን ገገረን።
በሁለት ሳምንት ውስጥ ከህመማችን አገገጀምን።አንድ ጠዋት ግን ሽማግሌ ሴትዮ ከእንቅልፋችን ቀስቅሳ መሄድ እንዳለብን ነገረችኝ።የአስተናጋቻችን እናት ነበረች።መንደሩ ስለኛ እንደሰማና ሊይዙን እየመጡ እንደሆነ ነገረችን።የተጠበሰ አሳ እና ውሃ ሰታን 'ልጆቼ መፍጠን አለባችሁ ጸሎቴ ከናንተ ጋር ነው" አለች።
ፈጥነን ከአሳዳጆቻችን ማምለጥ አልቻልንም አስራ ሁለት ነበሩ። አሸዋ ላይ ጥለው እጆቻችንን አሰሩ።ወደ መንደሩ መልሰው አለቃቸው ፊት አቀረቡን።
እናንተ ህፃናት ትናንሽ ሰይጣናት ሁናችኋል። አሁን ግን ወደተሳሳተ መንደር ነው የመጣችሁት አለ። እንደእናንተ ላለ ሰይጣኖች እዚህ ጋር ይበቃል።
ልብሳችሁን አውልቁ ብሎ አዘዘ አለ ስም አልባው አስተናጋጃችን እና እናቱ በ ህዝብ መሃል ነበሩ። በአለቃው መቆጣት ስለ እኛ ሲሳቀቁ እና ሲከፉ አየሁቸው። ልብሴን
ሲያወልቁ የራፕ ካሴት ከኪሴ ወደቀ። አለቃው ካሴቱን መረመረ እና የካሴት መጫወቻ እንዲመጣ አዘዘ፡፡
መጥቶ ሙዚቃው ተከፈተ። አለቃው ጠራኝ እና እንዴት እንደምንደንስ ማሳየት ጀመርኩ። ሞቴን ሳስብ መዳነስ ከበደኝ፤
ምቱም ጠፋብኝ፡፡ አለቃው ግን መረጋጋት ጀመረ። ልጆች መሆናችንን አወቀ። በድንገት ጓደኞቼ እንዲፈቱ አዘዘ። አለቃው ለህዝቡ ስህተት እንደሆነ እና ልጆች መሆናችንን እና ራሳችንን
ለማትረፍ እንደመጣን ተናገረ::
አለቃው ነጻ እንዳደረገን እና በፍጥነት አካባቢውን ለቀን እንድንወጣ ነገረን።
በጉዞየ ከሚረብሽኝ አንድና ዋናው ነገር ጉዞው የት እና መቼ እንደሚቋጭ አለማወቄ ነው፡፡ ይሄ ጥያቄ አዕምሮየን፣ ሰውነቴን እና ስሜቴን በጉዞየ ሁሉ ሲጎዳ ቆይቷል። በህይወቴ ምን እንደምሰራ ወደ የት እንደማመራ አላውቅም:: በየጊዜው እንደገና እንደምጀምር ይሰማኛል። አሁን የህይወቴ ዋና አላማ መትረፍ
ብቻ ነው። ለትንሽ ጊዜም ቢሆን እራሳችንን በምግብ እና በንጹህ
ውሃ ለማስደስት እንሞክር ነበር። በተለያዩ ስሜቶች ከመዋለል መከፋት ቀላል ነበር፡፡ ወደፊት መግፋት እንዳለብኝ አወቅኩ።
የባሰ አለ ብየ ስላሰብኩ አልተካፋሁም።
ጉዞችን ደመና እንደሽፈናት እና ለመውጣት እንደምትፍጨረጨር ጨረቃ መስሎ ታየኝ፡፡ ጨረቃዋ በመጨረሻ ትወጣለች ለሊቱንም ሙሉ ብርሃንዋን ትሰጣለች::
አንድ ቀን ሰኢዱ ”ብዙ ቀን ሰዎች ሊገድሉን ሲመጡ አይኖቼን ጨፍኜ ሞትን ጠብቄለሁ። እስከአሁን አልሞትኩም::
ሞትን በተቀበልኩ ቁጥር ግን አንድ አካሌ እንደሞተ ይሰማኛል። ከትንሽ ጊዜ በኋላ ሙሉ ለሙሉ እንድምሞት ይሰማኛል። ያኔ
ባዶ ስውነቴ ብቻ አብሮችሁ ይጓዛል። ከአሁኑ በላይ ዝምተኛ ይሆናል" አለ። አይኖቼ እንባን አቀረሩ፤ ግንባሬም ሞቀ። የሰኢዱ ን ቃላቶች እያሰብኩ እስኪነጋ ድረስ መተኛት አልቻልኩም::
ጉዞችን አስቸጋሪ ቢሆንም አንዳንዴ ለትንሽ ደቂቃ ቢሆንም መዝናናት እንሞክራለን። አንድ ቀን አንድ መንደር ስንደርስ ሰዎች ለአደን እየተዘጋጁ ነበር። አብረናቸው እንድናድን ጋበዙን፡፡ ከአደን በኋል ምግብ ለሚያዘጋጁ ሴቶች ውሃ በመቅዳት አገዝን፡፡
ምሽት ላይ ሁሉም መንደርተኛ ወደ መንደሩ ተመለሰ፡፡ምግቡ ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣ፡፡ ለሁሉም በስሃን ታደለ።
ከምግቡ በኋላ ከበሮ መምታት ተጀመረ:: ሁላችንም እጅ ለ እጅ ተያይዘን ክብ ሰርተን በጨረቃ ብርሃን መዳነስ ጀመርን።
በመሃል የት እንደመጣን ስለእኛ ታሪክ እንድናካፍል ተጠየቅን፡፡ቆይቶ ዳንሱ ቀጠለ።
ሲነጋ ውሃ እና መንደርተኛው የሰጠንን የተጠበሰ ስጋ ይዘን ጉዞችንን ቀጠልን፡፡ "የአባቶቻችሁ አምላክ ይከተላቹህ" ብለው ሸኙን።
ፀሐይዋ ስታዘቀዝቅ ወደ አንድ ልዩ መንደር ደረስን። መንደር ለማለት ይከዳል:: አንድ ትልቅ ቤት አንድ ኪሎ ሜትር ራቅ ብሎ ደግሞ ጭስ ቤት ብቻ ነበር የሚገኘው:: አማጺዎች በቀላሉ
ሊይዙት የሚችሉት ሰፈር" ብሎ ጅማህ ሳቀ።
ሰው መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሰፈሩን ሙሉ ዙረን አየነው:: የወይራ ዘይት ሲመረት እንደነበር ምልክቶች አሉ።
ወንዙ ላይ ሳር የበቀለብት ታንኳ አለ። ወደ ትልቁ ቤት ተመልሰን ይዘነው የመጣነውን የተጠበሰ ስጋውን እና ውሃ አስቀመጥን።
ብዙም ሳይቆይ መሸ እና ከጓደኞቼ ጋር ተኛን፡፡ የሊሊቱ አጋማሽ እስከሚደርስ ግን እንቅልፍ አልወሰደኝም። ሴት አያቴን
አስታወስኩ:: "እንደ እሳት እኮ ነው ያደግከው: ስም የወጣልህ ቀን እንደ ትናንት ትዝ ይለኛል" ትላለች :: ሰፊ ድግስ ተደግሶ በግ ዶሮ ታርዶ ከተበላ ከተጠጣ በኋላ ኢማሙ ፊት ቀርቤ "ኢስማኤል ተብሎ ይጠራ እንዳለ እና ታዳሚው እንዳጨበጨበ ከዛም ጭፈራ እልልታ እንደነበረ ትነግረኛለች...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ክፍል_ስድስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
የተጠጋጉ ጎጆ ቤቶችን ተመለከትን። ከመንደሩ ስንደርስ ማንም የለም። ከእኛ ተደብቀው ነበር። ብዙም ሳይቆይ አሳ አጥማጆች መጥረቢያ፣ ጦር እና መረብ ይዘው ወጡ። ምንም ማድረግ
አልቻልንም። ባለንበት ደርቀን ቆምን።
እንግዲያውስ "እባካችሁ እኛ ልንጎዳችሁ አልመጣንም፧ መንገደኞች ነን”ብለን ጮህን።አሳ አጥማጆች በሰደፍ መተው ጣሉን፡፡ ከበላያችን ላይ ተቀምጠው ካስሩን በኋላ ወደ አለቃቸው ወሰዱን። ብዙ ጥያቄዎች ጠየቁን። ከየት እንደመጣን፣ የት እንደምንሄድ እና
ለምን ይሄን አቅጣጫ እንደመረጥን ተጠየቅን፡፡ በመጨረሻ እጅ እና እግሮቻችንን ፈተው ከመንደራቸው አባረሩን። ጫማችንን ግን አልሰጡንም::
ብዙ ከተጓዝን በኋላ ነበር አሳ አጥማጆቹ ምን እንደቀጡን የገባን፡፡ ፀሐይ ስትወጣ 120 ዲግሪ ሆነ። ምንም ምንጠጋበት
ዛፍ እንኳ አልነበረም፡፡ ፀሐይዋ አሽዋው ላይ ስታርፍ በጣም ሞቀ፤ ግለት ሆነ። በባዶ እግር አሽዋ ላይ ተራመድን።
እግሮቻችንን ቆሰሉ። ደነዘዝን።በመጨረሻ አንድ ጎጆ ቤት ላይ ደረስን፡፡ ወደ ውስጥ ገብተን ተቀመጥን፡፡ የቤቱ ባለቤት ብዙም
ሳይቆይ መጣ። በሩ ላይ ቆሞ ተመለከተን እና ጉዳታችንን ሲያይ ፊቱን ዙሮ ሄደ፡፡
ከትንሽ ቆይታ በኋላ ሳር ይዞ መጣ። እሳት አያያዘ ከዛ ሳሩን በጥቂቱ እሳቱ እንዲለበለብ ካደረገ በኋላ ሳሩን ወደ እግሮቻችንን አስጠጋው:: ሙቀቱ ስቃያችንን አስታገስልን።ቀጥሎ የተጠበሰ አሳ ሾርባ፣ ሩዝ እና ውሃ ይዞ መጣ እና
ፊታችን ላይ አስቀምጦ እንድንበላ ጠየቀን፡፡ እንደገና ወቶ ሄደ፤
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ተመለሰ። የምንተኛበትን ምንጣፍ አሳየን፤ ከመተኛታችን በፊት እግሮቻችንን የምንቀባው ቅባት ሰጠን።
በሚቀጥለው ቀን ስም አልባው እንግዳ ተቀባይ ሰው ምግብ ይዞልን መጣ። ፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ እየተሻለን እንደሆነና እሱም ደስ እንዳለው ነገረን።
በጎጆው ለሳምንት ቆየን።እንግዳ ተቀባዩ ጥዋት እና ማታ ምግብ ይሰጠናል።ጥርሱ ነጭ በረዶ ይመስላል ከወገብ በላይ ሁሌም ራቁቱን ነው ልብስ አይለብስም።አንድ ቀን ስሙን ጠየቁት።ምን ይጠቅምሀል ብለህ ነው። እንደዚሁ ይሻለናል ለደንነታችን አለኝ።
በሚቀጥለው ቀን አመሻሽ ላይ ወደ ውቅያኖስ ይዞን ወረደ።እግራችንን እንድንነክር ነገረን።ጨዋማ ውሃ ከስቃይ እንደሚያስታግስ እና ከቲታኖስ እንደሚጠብቀን ገገረን።
በሁለት ሳምንት ውስጥ ከህመማችን አገገጀምን።አንድ ጠዋት ግን ሽማግሌ ሴትዮ ከእንቅልፋችን ቀስቅሳ መሄድ እንዳለብን ነገረችኝ።የአስተናጋቻችን እናት ነበረች።መንደሩ ስለኛ እንደሰማና ሊይዙን እየመጡ እንደሆነ ነገረችን።የተጠበሰ አሳ እና ውሃ ሰታን 'ልጆቼ መፍጠን አለባችሁ ጸሎቴ ከናንተ ጋር ነው" አለች።
ፈጥነን ከአሳዳጆቻችን ማምለጥ አልቻልንም አስራ ሁለት ነበሩ። አሸዋ ላይ ጥለው እጆቻችንን አሰሩ።ወደ መንደሩ መልሰው አለቃቸው ፊት አቀረቡን።
እናንተ ህፃናት ትናንሽ ሰይጣናት ሁናችኋል። አሁን ግን ወደተሳሳተ መንደር ነው የመጣችሁት አለ። እንደእናንተ ላለ ሰይጣኖች እዚህ ጋር ይበቃል።
ልብሳችሁን አውልቁ ብሎ አዘዘ አለ ስም አልባው አስተናጋጃችን እና እናቱ በ ህዝብ መሃል ነበሩ። በአለቃው መቆጣት ስለ እኛ ሲሳቀቁ እና ሲከፉ አየሁቸው። ልብሴን
ሲያወልቁ የራፕ ካሴት ከኪሴ ወደቀ። አለቃው ካሴቱን መረመረ እና የካሴት መጫወቻ እንዲመጣ አዘዘ፡፡
መጥቶ ሙዚቃው ተከፈተ። አለቃው ጠራኝ እና እንዴት እንደምንደንስ ማሳየት ጀመርኩ። ሞቴን ሳስብ መዳነስ ከበደኝ፤
ምቱም ጠፋብኝ፡፡ አለቃው ግን መረጋጋት ጀመረ። ልጆች መሆናችንን አወቀ። በድንገት ጓደኞቼ እንዲፈቱ አዘዘ። አለቃው ለህዝቡ ስህተት እንደሆነ እና ልጆች መሆናችንን እና ራሳችንን
ለማትረፍ እንደመጣን ተናገረ::
አለቃው ነጻ እንዳደረገን እና በፍጥነት አካባቢውን ለቀን እንድንወጣ ነገረን።
በጉዞየ ከሚረብሽኝ አንድና ዋናው ነገር ጉዞው የት እና መቼ እንደሚቋጭ አለማወቄ ነው፡፡ ይሄ ጥያቄ አዕምሮየን፣ ሰውነቴን እና ስሜቴን በጉዞየ ሁሉ ሲጎዳ ቆይቷል። በህይወቴ ምን እንደምሰራ ወደ የት እንደማመራ አላውቅም:: በየጊዜው እንደገና እንደምጀምር ይሰማኛል። አሁን የህይወቴ ዋና አላማ መትረፍ
ብቻ ነው። ለትንሽ ጊዜም ቢሆን እራሳችንን በምግብ እና በንጹህ
ውሃ ለማስደስት እንሞክር ነበር። በተለያዩ ስሜቶች ከመዋለል መከፋት ቀላል ነበር፡፡ ወደፊት መግፋት እንዳለብኝ አወቅኩ።
የባሰ አለ ብየ ስላሰብኩ አልተካፋሁም።
ጉዞችን ደመና እንደሽፈናት እና ለመውጣት እንደምትፍጨረጨር ጨረቃ መስሎ ታየኝ፡፡ ጨረቃዋ በመጨረሻ ትወጣለች ለሊቱንም ሙሉ ብርሃንዋን ትሰጣለች::
አንድ ቀን ሰኢዱ ”ብዙ ቀን ሰዎች ሊገድሉን ሲመጡ አይኖቼን ጨፍኜ ሞትን ጠብቄለሁ። እስከአሁን አልሞትኩም::
ሞትን በተቀበልኩ ቁጥር ግን አንድ አካሌ እንደሞተ ይሰማኛል። ከትንሽ ጊዜ በኋላ ሙሉ ለሙሉ እንድምሞት ይሰማኛል። ያኔ
ባዶ ስውነቴ ብቻ አብሮችሁ ይጓዛል። ከአሁኑ በላይ ዝምተኛ ይሆናል" አለ። አይኖቼ እንባን አቀረሩ፤ ግንባሬም ሞቀ። የሰኢዱ ን ቃላቶች እያሰብኩ እስኪነጋ ድረስ መተኛት አልቻልኩም::
ጉዞችን አስቸጋሪ ቢሆንም አንዳንዴ ለትንሽ ደቂቃ ቢሆንም መዝናናት እንሞክራለን። አንድ ቀን አንድ መንደር ስንደርስ ሰዎች ለአደን እየተዘጋጁ ነበር። አብረናቸው እንድናድን ጋበዙን፡፡ ከአደን በኋል ምግብ ለሚያዘጋጁ ሴቶች ውሃ በመቅዳት አገዝን፡፡
ምሽት ላይ ሁሉም መንደርተኛ ወደ መንደሩ ተመለሰ፡፡ምግቡ ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣ፡፡ ለሁሉም በስሃን ታደለ።
ከምግቡ በኋላ ከበሮ መምታት ተጀመረ:: ሁላችንም እጅ ለ እጅ ተያይዘን ክብ ሰርተን በጨረቃ ብርሃን መዳነስ ጀመርን።
በመሃል የት እንደመጣን ስለእኛ ታሪክ እንድናካፍል ተጠየቅን፡፡ቆይቶ ዳንሱ ቀጠለ።
ሲነጋ ውሃ እና መንደርተኛው የሰጠንን የተጠበሰ ስጋ ይዘን ጉዞችንን ቀጠልን፡፡ "የአባቶቻችሁ አምላክ ይከተላቹህ" ብለው ሸኙን።
ፀሐይዋ ስታዘቀዝቅ ወደ አንድ ልዩ መንደር ደረስን። መንደር ለማለት ይከዳል:: አንድ ትልቅ ቤት አንድ ኪሎ ሜትር ራቅ ብሎ ደግሞ ጭስ ቤት ብቻ ነበር የሚገኘው:: አማጺዎች በቀላሉ
ሊይዙት የሚችሉት ሰፈር" ብሎ ጅማህ ሳቀ።
ሰው መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሰፈሩን ሙሉ ዙረን አየነው:: የወይራ ዘይት ሲመረት እንደነበር ምልክቶች አሉ።
ወንዙ ላይ ሳር የበቀለብት ታንኳ አለ። ወደ ትልቁ ቤት ተመልሰን ይዘነው የመጣነውን የተጠበሰ ስጋውን እና ውሃ አስቀመጥን።
ብዙም ሳይቆይ መሸ እና ከጓደኞቼ ጋር ተኛን፡፡ የሊሊቱ አጋማሽ እስከሚደርስ ግን እንቅልፍ አልወሰደኝም። ሴት አያቴን
አስታወስኩ:: "እንደ እሳት እኮ ነው ያደግከው: ስም የወጣልህ ቀን እንደ ትናንት ትዝ ይለኛል" ትላለች :: ሰፊ ድግስ ተደግሶ በግ ዶሮ ታርዶ ከተበላ ከተጠጣ በኋላ ኢማሙ ፊት ቀርቤ "ኢስማኤል ተብሎ ይጠራ እንዳለ እና ታዳሚው እንዳጨበጨበ ከዛም ጭፈራ እልልታ እንደነበረ ትነግረኛለች...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
ፖሊስና እርምጃው በግንቦት 30 ፣ 2ዐዐ5 እትሙ በምስራቅ ሸዋ መቂ ከተማ ውስጥ ፣ አንድ ግለሰብ ጅብ አጥምዶ ፤ ከማጥመዱም በአህያ በሚጎተት ጋሪ ጭኖ ሲዘዋወር በመገኘቱ ፣ “ እናሰሳትን፣ በማንገላታት ” ክስ መታሰሩን ነግሮናል።
ሰውየው ፣ “ጅቡን ከነነፍሱ ያጠመድኩት እየተፋፋመ ያለውን የፀረ ሙስና ትግል መቀላቀሌን ለማሳየት ነው” ካላለ ትንሽ በቁጥጥር ሥር ሳይቆይ አይቀርም : :
“እንሰሳትን በማንገላታት” የሚለው ክስ ፣ እንግልቱ በየትኛው እንስሳ ላይ እንደተፈጸመ አጥርቶ ባይገልጽም ፣ እንደኔ በዚህ ጉዳይ ዋነኛው
የእንግልት ሰለባ አህያው ነው : :
መደበኛ የሽክም እንግልቱን ተዉት ፡ : ይህ አህያ ታሪካዊ አዳኙን ከነነፍሱ ተሸክሞ ሲዞር ፣ “ካሁን አሁን ዘነጠለኝ፤” እያለ መሳቀቁ ብቻ ከባድ የሥነ ልቦና እንግልት አይደለም?
ይሄንን ጅቦችን ተሸክመው ሲሄዱ የኖሩ ፣
ምስኪን አህዮች ሁኑ ጠንቅቀው ያውቃኩ
ወጣም ወረደ ክሱ ጅቡን የእንግልቱ ተጠቂ አድርጎ ያቀርበ መሆኑን፤
ከሰማን ፣ “ድሮም የኛ ሕግ ለጅቦች ያዳላል" ማለታችን የማይቀር ነው
🔘ሕይወት እምሻው🔘
ሰውየው ፣ “ጅቡን ከነነፍሱ ያጠመድኩት እየተፋፋመ ያለውን የፀረ ሙስና ትግል መቀላቀሌን ለማሳየት ነው” ካላለ ትንሽ በቁጥጥር ሥር ሳይቆይ አይቀርም : :
“እንሰሳትን በማንገላታት” የሚለው ክስ ፣ እንግልቱ በየትኛው እንስሳ ላይ እንደተፈጸመ አጥርቶ ባይገልጽም ፣ እንደኔ በዚህ ጉዳይ ዋነኛው
የእንግልት ሰለባ አህያው ነው : :
መደበኛ የሽክም እንግልቱን ተዉት ፡ : ይህ አህያ ታሪካዊ አዳኙን ከነነፍሱ ተሸክሞ ሲዞር ፣ “ካሁን አሁን ዘነጠለኝ፤” እያለ መሳቀቁ ብቻ ከባድ የሥነ ልቦና እንግልት አይደለም?
ይሄንን ጅቦችን ተሸክመው ሲሄዱ የኖሩ ፣
ምስኪን አህዮች ሁኑ ጠንቅቀው ያውቃኩ
ወጣም ወረደ ክሱ ጅቡን የእንግልቱ ተጠቂ አድርጎ ያቀርበ መሆኑን፤
ከሰማን ፣ “ድሮም የኛ ሕግ ለጅቦች ያዳላል" ማለታችን የማይቀር ነው
🔘ሕይወት እምሻው🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ሰባት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ጥዋት ስንነሳ ስጋው ተበልቶ አገኘን። ማን እንደበላው ግራ ገባን። መጀመሪያ ራስ በራሳችን ተጠቋቁመን ነበር። በኋል ግን ውሻ ሆኖ አገኘነው አልሀጂ በጣም ተናዶ ውሻውን ካልደበደብኩ ብሎ ተከላከልነው፡፡ ውሃችንን ይዘን ጉዞችንን
ቀጠልን፡፡ ቀትር ላይ ያገኘነውን ፍራፍሬ ለመብላት ሞከርን።እስከ ማታ ድረስ በመካከላችን ምንም አይነት ንግግር
አልነበረም። ምሽት ላይ ለማረፍ ወሰን።
አልሃጂ "ውሻውን መግደል ነበረብኝ" አለ።
ለምን? አልኩ እኔ
እኔን ተከትሎ “ምን ትርጉም አለው? የሱ መሞት ምን ያደርግናል" አለ ሞሪባ፡፡
አልሃጂ " ያለንን ብቸኛ ምግብ ነዋ የበላብን። ጥሩ ስጋ ይሆን ነበር።
"አይመስለኝም! ደግሞ ማዘጋጀቱ አስቸጋሪ ይሆን ነበር አልኩ።
ሙሳ ደግሞ ውሻውን ቢገድለው ኖሮ እበላው ነበር አለ። አባቴ ማሌዥያውያን ውሻ እንደሚበሉ ነግሮኛል።አልሃጂ ገድሉት ቢሆን ንሮ በልቼ እሞክረው ነበር። አባቴን እንደገና ሳገኘው የውሻ
ስጋ እንደሚጥም እና እንደማይጥም እነግረው ነበር አለ፡፡ጉዞችንን ማታ ለማድረግ ወሰን፡፡ ቀን ምግብ እንፈልጋለን
ተራ ይዘን እንተኛለን፡፡ ማታ ጨረቃዋ ምትከተለን ይመስላል።ሲነጋ ትጠፋ እና በሚቀጠለው ቀን እንደገና መታ መንገዳችንን ትመራለች።
አንድ ቀትር ላይ ኦና በሆነ መንደር ዉስጥ ምግብ ስንፈልግ ቁራ ከየት እንደመጣ ሳይታወቅ ከሰማይ ወደቀ። አልሞተም ነገር ግን መብረር አልቻለም፡፡ ያልተመደ ነገር ነበር፤ ምግብ ግን ፈልገን ነበር። ላባዋን ስንነጭ ሞሪባ ምን ቀን እንደሆነ ጠየቀን። ማንም ሚያውቅ አልነበረም::
"ዛሬ የባዕል ቀን ነው" አለ ኬን እየሳቀ፡፡ "የፈለጋችሁትን ቀን ልትሰይሙት ትችላላችሁ::"
" የቁራው መውደቅ የእርግማን ምልክት ነው መብላት የለብንም" አለ ሙሳ።
"እንግዲህ የእርግማን ምልክት ከሆነ እኛም እርጉማን ነን፡፡ ስለዚህ በደንብ አድርጌ ነው ምበላው:: የፈለከውን ማድረግ ትችላላህ" አለ ኬን፡፡
ብዙም ሳይቆይ ማታ ሆነ፡፡ ከባድ ጸጥታ! ንፋሱ እና ደመና አንድ የሚጠብቁት ነገር ያለ ይመስል መንቀሳቀሳቸውን
አቆሙ:: ለሊቱ በጣም ጨለማ ነበር። ጫካ ላይ አልነበርንም ጨለማው ግን ለመተያየት አስቸጋሪ ነበር። ሶስት ሰዎች ወደ እኛ ሲመጡ አየን፡፡ በዛፎች መሃል ተደብቀን ማየት ጀመርን።እኛ በመጣንበት አቅጣጫ ሄዱ፡፡ ከተደበቅንበት እየተጠራራን መውጣት ጀመርን። ሰኢድ ግን ሊነሳ አልቻለም። በፍርሃት ደነዘዘ ሊንቀሳቀስ አልቻለም:: በመጨረሻ ኬን ተሸክሞት ድልድዩን ተሻገርን፡፡
ድልድዩን እንደተሻገርን ሰኢድ አስነጠሰ፡፡ ኬን አስቀመጠው እና አስታወከ፡፡ በኋላ " መናፍስት ነበሩ አይደል ማታ ያየናቸው" አለ፡፡
ሁላችንም ተስማማን፡፡
“ራሴን ስቼ ነበር። አሁን ደህና ነኝ እንሂድ" አለ፡፡ እኩለ ቀን ሲሆን አንድ ትልቅ መንደር ደረስን። ገበያ ነበር የሚመስለው:: ሰዎች ያዜማሉ ይጨፍራሉ ልጆች ውርውር
ሲሉ የምግብ ሽታ:: ወደ መንደር ቀስ ብለን ገብተን እንጨት ላይ ተቀመጥን።
ሰዎች አዩን አንዳንዶቹ ከዚህ በፊት የምናውቃቸው ይመስላሉ::
እጃቸውን እያውለበለቡ ሰላም አሉን፡፡ አንድ ሴት ወደ እኛ መጥታ አውቅሃልሁ አለችኝ፡፡ አኔ ግን ላውቃት አልቻልኩም::
ጅኒየር እኔን እየፈለገ መጥቶ እንደነበረ እና እናቴን አባቴን እና ትንሽ ወንድሜን ከሚቀጥለው መንደር እንዳየቻቸው
ነገረችኝ፡፡ ከዛ መንደር ብዙ የማታሩ ጆንግ ሰው አለ እናንተም ዘመዶቻችሁን ልታገኙ ትችላላችህ አለች ወደ ጓደኞቼ ፊትዋን
ዙራ።
ወዲያው ለመሄድ ፈልጌ ነበር ነገር ግን በቀጣዩ ቀን ለመሄድ ተስማማን፡፡ በዛ ላይ ሰኢድ እረፍት ያስፈልገዋል::
ወደ ወንዝ ወርደን ዋኘን ድብብቆሽ ከተጫወትን በኋላ ድስት ሙሉ ሩዝ ሰርቀን በላን፡፡
ያን ምሽት መተኛት አልቻልኩም::
አልሃጂ "ውሾቹ ቀሰቀሱኝ” አለ
እኔ እንኳን ከመጀመሪያው አልተኛሁም አልኩ፡፡
ቤተሰቦችህን ለማየት ጓጉተሃል አይደል አለ አልሃጂ። "እኔም አለ እየሳቀ፡፡ ውሻወቹ ጩሀት ግን አልተለየብሁም?”
ትንሽ ቆይቶ መንደርተኛው ነቃ:: እኔ እና አልሃጂ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀሰቀስና ቸው:: ሰኢድ ሊነሳ አልቻለም:: "ተነስ
መሂድ አለብን" እያልን በጣም አንቀሳቀስነው። ሊነሳ ግን አልቻለም:: እንደገና ራሱን ስቶ ይሆን አልን። አንድ ትልቅ ሰው መጥቶ ውሃ አፈሰሰበት። ሰዒድ አልተንቀሳቀስም። ሰውየዋ
ፊቱን አዙሮ ትንፋሹ አዳመጠ። ቀስ ብሎ " ከዚህ መንደር የምታውቁት ሰው አለ ብሎ ጠየቀን፡፡ አናውቅም ብለን መለስን።
ኬንን ወስዶ በጆሮው አንድ ነገር ነገረው:: ኬን ማልቀስ ጀመረ። ሰዒድ ጥሎን እንደሄደ አወቅን፡፡ ሁሉም ማልቀስ ጀመሩ እኔ ግን ለደቂቃዎች ደንዝዥ ነበር። ኬን እና ትልቁ ሰውየ የመቃብር ሳጥን አምጥተው የስዒድን አስክሬን ሳጥኑ ውስጥ አስገቡ።በነጭ አንሶላ ተጠቅልሎ በእንጨት ሳጥን ውስጥ ከጠረጴዛ ላይ
ተቀመጦ ጸሎት ማድረግ ተጀመረ። ሰሙን እየጠራ ጸሎት ማድረግ ሲጀመር እንባየ ከፊቴ ላይ ኮለል ብሎ መፍሰስ ጀመረ።የስዒድን ትቶን መሄድ ማመን አልቻልኩም፡፡ ራሱን እንደሳተ
እና እንደሚመለስ ለማስብ ስጀምር ወደ መቃብር አስገቡት።እንባየ መሬት ላይ ተንጠባጠበ።
ከቀብር ስነ ስርዐቱ በኋላ ብቻችንን ቀረን። አንድ ነገር እንደሚጠብቅ ሰው ለስዓታት በመቃብሩ ቦታ ተቀመጥን። በጣም ልጆችን ነበርን። ከኬን በስተቀር ከአስራ ሶስት አመት በታች! ኬን ሶስት አመት ይበልጠናል። ምሽቱ ሲቃረብ
ከመቃብር ስፍራው ተንቀሳቀስን።
ሰዒድ ያለው አንድ ነገር ትዝ አለኝ " አንድ አካሌ እንደሞተ ይሰማኛል ::"
ሲነጋ የቀብር ስነ ስርዐቱ እንዲፈጸም የረዱንን አመስገን።ከመካከላቸው አንድ "የት እንዳረፈ ሁሌም ታውቃላችሁ አለ"።
በስምምነት ራሳችንን ነቀነቅን፡፡ ወደዚህ መንደር የመመለስ እድላችን አንስተኛ ነው:: ነገን አናውቅምና። ጓደኛችንን ጥለነው እየሄድን ነው" እናቴ እንደምትለም "የዚህ አለም ጊዚያዊ ሩጫውን ጨረሰ”::
ለሊቱን ሙሉ በጸጥታ ተጓዝን። ለትንሽ ደቂቃ ስናርፍ ሞሪባ ራቅ ብሎ ከተቀመጠ በኋላ ማልቀስ ጀመረ። ራሱን ለመቆጣጠር በቅጠሎች መጫወት ጀመረ።ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ጉዟችንን ቀጠልን።
"መንደሩ ስንደርስ እናቴን ጥብቅ አድርጌ ነው ማቅፋት” አለ አልሃጂ።
ሁላችንም ሳቅን፡፡
ወደ መንደሩ ስንቃረብ ቤተሰቦቻችንን እንደምናገኛቸው ተሰማኝ፡፡ ፈገግታየ አልተቋረጠም። የቡና ዛፎች ደኑን መተካት ጀምረዋል። በቡናው ተቃራኒ መለስተኛ የሙዝ እርሻ አለ፡፡ ከኛ
ተሻግሮ አንድ ሰው ያልበሰለ ሙዝ ሲቆርጥ አገኘነው::
ሰላም ዋሉ?" አለ ኬን።
ሰውየው ጎር ጋስሙ ይባላል። ወንደላጤ ነው:: ሰዎች ትልቅ ሰው አይደል ለምንድን ነው የማያገባው:: የግድየለሽ ኑሮ
የሚኖረው" ይላሉ። ምንም መልስ አይሰጥም::
ጋስሙ ፈገግ አለ። ያዙ አለን ሙዝ።
“አባትህ እና እናትህ ሁሌም ስለ አንተ ያወራሉ ይጸልያሉ” አለ ወደ እኔ ዙሮ።" አሁን ሲያዩህ በጣም ነው ደስ ሚላቸው" አለኝ።መንደሩ ተራራ ላይ ነው አለኝ እና መሮጥ ጀመርኩ። መንገዱ አዙሪት ነበር፡፡ ጫፍ ላይ ስንደርስ ደክሞን ተቀመጥን፡፡
ከተራራው ስወርድ የጥይት ተኩስ ተሰማ።ሰዎች መጮህ ማልቀስ ጀመሩ:: ሙዙን ጥለን በዛፎች መሃል ተሸሸግን።
በመጨረሻ አቆመ ሁሉም ነገር ጸጥ ረጭ አለ። ጋስሙን ወደ መንደሩ መሄድ እንደምፈልግ ስነግረው እጆቼን ያዘኝ፡፡ እጄን አስለቅቄ ወደ ታች ሮጥኩ፡፡ መንደሩ ስደርስ ሁሉም ነገር ተቃጥሏል። የት ጀምሬ እንደምፈልጋቸው
#ክፍል_ሰባት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ጥዋት ስንነሳ ስጋው ተበልቶ አገኘን። ማን እንደበላው ግራ ገባን። መጀመሪያ ራስ በራሳችን ተጠቋቁመን ነበር። በኋል ግን ውሻ ሆኖ አገኘነው አልሀጂ በጣም ተናዶ ውሻውን ካልደበደብኩ ብሎ ተከላከልነው፡፡ ውሃችንን ይዘን ጉዞችንን
ቀጠልን፡፡ ቀትር ላይ ያገኘነውን ፍራፍሬ ለመብላት ሞከርን።እስከ ማታ ድረስ በመካከላችን ምንም አይነት ንግግር
አልነበረም። ምሽት ላይ ለማረፍ ወሰን።
አልሃጂ "ውሻውን መግደል ነበረብኝ" አለ።
ለምን? አልኩ እኔ
እኔን ተከትሎ “ምን ትርጉም አለው? የሱ መሞት ምን ያደርግናል" አለ ሞሪባ፡፡
አልሃጂ " ያለንን ብቸኛ ምግብ ነዋ የበላብን። ጥሩ ስጋ ይሆን ነበር።
"አይመስለኝም! ደግሞ ማዘጋጀቱ አስቸጋሪ ይሆን ነበር አልኩ።
ሙሳ ደግሞ ውሻውን ቢገድለው ኖሮ እበላው ነበር አለ። አባቴ ማሌዥያውያን ውሻ እንደሚበሉ ነግሮኛል።አልሃጂ ገድሉት ቢሆን ንሮ በልቼ እሞክረው ነበር። አባቴን እንደገና ሳገኘው የውሻ
ስጋ እንደሚጥም እና እንደማይጥም እነግረው ነበር አለ፡፡ጉዞችንን ማታ ለማድረግ ወሰን፡፡ ቀን ምግብ እንፈልጋለን
ተራ ይዘን እንተኛለን፡፡ ማታ ጨረቃዋ ምትከተለን ይመስላል።ሲነጋ ትጠፋ እና በሚቀጠለው ቀን እንደገና መታ መንገዳችንን ትመራለች።
አንድ ቀትር ላይ ኦና በሆነ መንደር ዉስጥ ምግብ ስንፈልግ ቁራ ከየት እንደመጣ ሳይታወቅ ከሰማይ ወደቀ። አልሞተም ነገር ግን መብረር አልቻለም፡፡ ያልተመደ ነገር ነበር፤ ምግብ ግን ፈልገን ነበር። ላባዋን ስንነጭ ሞሪባ ምን ቀን እንደሆነ ጠየቀን። ማንም ሚያውቅ አልነበረም::
"ዛሬ የባዕል ቀን ነው" አለ ኬን እየሳቀ፡፡ "የፈለጋችሁትን ቀን ልትሰይሙት ትችላላችሁ::"
" የቁራው መውደቅ የእርግማን ምልክት ነው መብላት የለብንም" አለ ሙሳ።
"እንግዲህ የእርግማን ምልክት ከሆነ እኛም እርጉማን ነን፡፡ ስለዚህ በደንብ አድርጌ ነው ምበላው:: የፈለከውን ማድረግ ትችላላህ" አለ ኬን፡፡
ብዙም ሳይቆይ ማታ ሆነ፡፡ ከባድ ጸጥታ! ንፋሱ እና ደመና አንድ የሚጠብቁት ነገር ያለ ይመስል መንቀሳቀሳቸውን
አቆሙ:: ለሊቱ በጣም ጨለማ ነበር። ጫካ ላይ አልነበርንም ጨለማው ግን ለመተያየት አስቸጋሪ ነበር። ሶስት ሰዎች ወደ እኛ ሲመጡ አየን፡፡ በዛፎች መሃል ተደብቀን ማየት ጀመርን።እኛ በመጣንበት አቅጣጫ ሄዱ፡፡ ከተደበቅንበት እየተጠራራን መውጣት ጀመርን። ሰኢድ ግን ሊነሳ አልቻለም። በፍርሃት ደነዘዘ ሊንቀሳቀስ አልቻለም:: በመጨረሻ ኬን ተሸክሞት ድልድዩን ተሻገርን፡፡
ድልድዩን እንደተሻገርን ሰኢድ አስነጠሰ፡፡ ኬን አስቀመጠው እና አስታወከ፡፡ በኋላ " መናፍስት ነበሩ አይደል ማታ ያየናቸው" አለ፡፡
ሁላችንም ተስማማን፡፡
“ራሴን ስቼ ነበር። አሁን ደህና ነኝ እንሂድ" አለ፡፡ እኩለ ቀን ሲሆን አንድ ትልቅ መንደር ደረስን። ገበያ ነበር የሚመስለው:: ሰዎች ያዜማሉ ይጨፍራሉ ልጆች ውርውር
ሲሉ የምግብ ሽታ:: ወደ መንደር ቀስ ብለን ገብተን እንጨት ላይ ተቀመጥን።
ሰዎች አዩን አንዳንዶቹ ከዚህ በፊት የምናውቃቸው ይመስላሉ::
እጃቸውን እያውለበለቡ ሰላም አሉን፡፡ አንድ ሴት ወደ እኛ መጥታ አውቅሃልሁ አለችኝ፡፡ አኔ ግን ላውቃት አልቻልኩም::
ጅኒየር እኔን እየፈለገ መጥቶ እንደነበረ እና እናቴን አባቴን እና ትንሽ ወንድሜን ከሚቀጥለው መንደር እንዳየቻቸው
ነገረችኝ፡፡ ከዛ መንደር ብዙ የማታሩ ጆንግ ሰው አለ እናንተም ዘመዶቻችሁን ልታገኙ ትችላላችህ አለች ወደ ጓደኞቼ ፊትዋን
ዙራ።
ወዲያው ለመሄድ ፈልጌ ነበር ነገር ግን በቀጣዩ ቀን ለመሄድ ተስማማን፡፡ በዛ ላይ ሰኢድ እረፍት ያስፈልገዋል::
ወደ ወንዝ ወርደን ዋኘን ድብብቆሽ ከተጫወትን በኋላ ድስት ሙሉ ሩዝ ሰርቀን በላን፡፡
ያን ምሽት መተኛት አልቻልኩም::
አልሃጂ "ውሾቹ ቀሰቀሱኝ” አለ
እኔ እንኳን ከመጀመሪያው አልተኛሁም አልኩ፡፡
ቤተሰቦችህን ለማየት ጓጉተሃል አይደል አለ አልሃጂ። "እኔም አለ እየሳቀ፡፡ ውሻወቹ ጩሀት ግን አልተለየብሁም?”
ትንሽ ቆይቶ መንደርተኛው ነቃ:: እኔ እና አልሃጂ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀሰቀስና ቸው:: ሰኢድ ሊነሳ አልቻለም:: "ተነስ
መሂድ አለብን" እያልን በጣም አንቀሳቀስነው። ሊነሳ ግን አልቻለም:: እንደገና ራሱን ስቶ ይሆን አልን። አንድ ትልቅ ሰው መጥቶ ውሃ አፈሰሰበት። ሰዒድ አልተንቀሳቀስም። ሰውየዋ
ፊቱን አዙሮ ትንፋሹ አዳመጠ። ቀስ ብሎ " ከዚህ መንደር የምታውቁት ሰው አለ ብሎ ጠየቀን፡፡ አናውቅም ብለን መለስን።
ኬንን ወስዶ በጆሮው አንድ ነገር ነገረው:: ኬን ማልቀስ ጀመረ። ሰዒድ ጥሎን እንደሄደ አወቅን፡፡ ሁሉም ማልቀስ ጀመሩ እኔ ግን ለደቂቃዎች ደንዝዥ ነበር። ኬን እና ትልቁ ሰውየ የመቃብር ሳጥን አምጥተው የስዒድን አስክሬን ሳጥኑ ውስጥ አስገቡ።በነጭ አንሶላ ተጠቅልሎ በእንጨት ሳጥን ውስጥ ከጠረጴዛ ላይ
ተቀመጦ ጸሎት ማድረግ ተጀመረ። ሰሙን እየጠራ ጸሎት ማድረግ ሲጀመር እንባየ ከፊቴ ላይ ኮለል ብሎ መፍሰስ ጀመረ።የስዒድን ትቶን መሄድ ማመን አልቻልኩም፡፡ ራሱን እንደሳተ
እና እንደሚመለስ ለማስብ ስጀምር ወደ መቃብር አስገቡት።እንባየ መሬት ላይ ተንጠባጠበ።
ከቀብር ስነ ስርዐቱ በኋላ ብቻችንን ቀረን። አንድ ነገር እንደሚጠብቅ ሰው ለስዓታት በመቃብሩ ቦታ ተቀመጥን። በጣም ልጆችን ነበርን። ከኬን በስተቀር ከአስራ ሶስት አመት በታች! ኬን ሶስት አመት ይበልጠናል። ምሽቱ ሲቃረብ
ከመቃብር ስፍራው ተንቀሳቀስን።
ሰዒድ ያለው አንድ ነገር ትዝ አለኝ " አንድ አካሌ እንደሞተ ይሰማኛል ::"
ሲነጋ የቀብር ስነ ስርዐቱ እንዲፈጸም የረዱንን አመስገን።ከመካከላቸው አንድ "የት እንዳረፈ ሁሌም ታውቃላችሁ አለ"።
በስምምነት ራሳችንን ነቀነቅን፡፡ ወደዚህ መንደር የመመለስ እድላችን አንስተኛ ነው:: ነገን አናውቅምና። ጓደኛችንን ጥለነው እየሄድን ነው" እናቴ እንደምትለም "የዚህ አለም ጊዚያዊ ሩጫውን ጨረሰ”::
ለሊቱን ሙሉ በጸጥታ ተጓዝን። ለትንሽ ደቂቃ ስናርፍ ሞሪባ ራቅ ብሎ ከተቀመጠ በኋላ ማልቀስ ጀመረ። ራሱን ለመቆጣጠር በቅጠሎች መጫወት ጀመረ።ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ጉዟችንን ቀጠልን።
"መንደሩ ስንደርስ እናቴን ጥብቅ አድርጌ ነው ማቅፋት” አለ አልሃጂ።
ሁላችንም ሳቅን፡፡
ወደ መንደሩ ስንቃረብ ቤተሰቦቻችንን እንደምናገኛቸው ተሰማኝ፡፡ ፈገግታየ አልተቋረጠም። የቡና ዛፎች ደኑን መተካት ጀምረዋል። በቡናው ተቃራኒ መለስተኛ የሙዝ እርሻ አለ፡፡ ከኛ
ተሻግሮ አንድ ሰው ያልበሰለ ሙዝ ሲቆርጥ አገኘነው::
ሰላም ዋሉ?" አለ ኬን።
ሰውየው ጎር ጋስሙ ይባላል። ወንደላጤ ነው:: ሰዎች ትልቅ ሰው አይደል ለምንድን ነው የማያገባው:: የግድየለሽ ኑሮ
የሚኖረው" ይላሉ። ምንም መልስ አይሰጥም::
ጋስሙ ፈገግ አለ። ያዙ አለን ሙዝ።
“አባትህ እና እናትህ ሁሌም ስለ አንተ ያወራሉ ይጸልያሉ” አለ ወደ እኔ ዙሮ።" አሁን ሲያዩህ በጣም ነው ደስ ሚላቸው" አለኝ።መንደሩ ተራራ ላይ ነው አለኝ እና መሮጥ ጀመርኩ። መንገዱ አዙሪት ነበር፡፡ ጫፍ ላይ ስንደርስ ደክሞን ተቀመጥን፡፡
ከተራራው ስወርድ የጥይት ተኩስ ተሰማ።ሰዎች መጮህ ማልቀስ ጀመሩ:: ሙዙን ጥለን በዛፎች መሃል ተሸሸግን።
በመጨረሻ አቆመ ሁሉም ነገር ጸጥ ረጭ አለ። ጋስሙን ወደ መንደሩ መሄድ እንደምፈልግ ስነግረው እጆቼን ያዘኝ፡፡ እጄን አስለቅቄ ወደ ታች ሮጥኩ፡፡ መንደሩ ስደርስ ሁሉም ነገር ተቃጥሏል። የት ጀምሬ እንደምፈልጋቸው
👍1
አላውቅም። ጋስሙ እና ጓደኞቼ ተከትለውኝ ነበር። የሚቃጠለውን መንደር ቁመን
መመልክት ጀመርን። ጋስሙ እየተንቀሳቀሰ ማየት ጀመረ፡፡ እኛ
በቆምንበት ተቃራኒ ጋስሙ ጩሆ ሲያለቅስ ሰምተን ሮጥን።ከሃያ በላይ ስዎች በጥይት ተደብድበው ወድቀዋል፡፡ አብዛኞቹ ወጣት ወንዶች ነበሩ። ቤተሰቦቻችንን ሁሉም ቦታ ዙረን ፈለግናቸው ልናገኛቸው ግን አልቻልንም፡፡
በጣም አዘንኩ። ጋስሙን ሰላም ለማለት ባንቆም፤ ተራራው ላይ ባናርፍ ቤተሰቦቻችንን ባየናቸው ብየ ተቆጨሁ። ተናደድኩ።ከጋስሙ ጋር ተናነቅኩ። በኋላ ጓደኞቼ ገላገሉን። ከዛ እነሱም ንትርክ ውስጥ ገቡ እርስበርሳችንን መደባደብ ጀመርን። ጋስሙ የማንም ጥፋት አይደለም ሲል እንደገና ለጠብ ተነሳሁ። ብዙም ሳይቆይ የሰዎች ድምጽ ሰማን። ወደ ቡናው እርሻ ሩጠን በመሄድ
ተደበቅን፡፡
ከአስር የሚበልጡ አማጺዎች ነበሩ። ልብሳቸው በደም ጨቅይቷል። አማጺዎቹ መሬት ላይ ተቀምጠው ማሪዋና
እያጨሱ ካርታ መጫወት ጀመሩ።
አንዱ “ዛሬ ሶስት መንደሮችን አቃጠልን" ሲል።ሌላው
“በትንሽ ስዓታት ሶስት መንደር ማቃጠል ደስ ይላል። ከዚህ መንደር ደግሞ ማንም የተረፈ የለም ሁሉንም ነገር ነው
ያቃጠልነው:: ኮማንደር እንደሚኮራብን ተስፋ አለኝ" አለ።
አንዱ ወደ ቡና ቅጠሉ ሲመጣ የቡና ቅጠሎቹ ድምጽ ተሰማ።
አማጺዎቹ ጨዋታቸውን አቁመው እሱን ለመሸፈን በሁሉም ቦታ ሮጡ። ሁላችንም አንዴ ተነስተን ሮጥን።ጋስሙ ፊት
ለፊታችን ነበር። የት እንደሚሄድ ስለሚያውቅ ሁላችንም ተከተልነው። ለስዓታት ሮጥን፡፡ ተኩሱ ቀጥለ። ጋስሙ ተኩሱ እንዳይደርስብን እሱ ከኋላ ካትሮ እኛ ከፊት መሮጥ ጀመርን።
ብዙም ሳይቆይ ጋስሙ ማልቀስ ጀመረ። ተንከባለለ። በጥይት ተመቶ ነበር። ብዙ ደም መፍሰስ ጀመረ። አልሃጂ እና እኔ
ቲሽርቱን አወልቀን ደሙን ለማቆም ሞከርን፡ አልቻልንም! እጁ ቀዘቀዘ ደሙ መፍሰሱን ቀጠለ። ምንም አላልንም። ምን እንደሆነ አውቀናል።
አልሃጂ የጋስሙን አይኖችን ከደናቸው::
የመታሁት ጸጸተኝ፡፡ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ። የምታዘቀዝቀው ፀሐይ ጋስሙን ይዛው ሄደች።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
መመልክት ጀመርን። ጋስሙ እየተንቀሳቀሰ ማየት ጀመረ፡፡ እኛ
በቆምንበት ተቃራኒ ጋስሙ ጩሆ ሲያለቅስ ሰምተን ሮጥን።ከሃያ በላይ ስዎች በጥይት ተደብድበው ወድቀዋል፡፡ አብዛኞቹ ወጣት ወንዶች ነበሩ። ቤተሰቦቻችንን ሁሉም ቦታ ዙረን ፈለግናቸው ልናገኛቸው ግን አልቻልንም፡፡
በጣም አዘንኩ። ጋስሙን ሰላም ለማለት ባንቆም፤ ተራራው ላይ ባናርፍ ቤተሰቦቻችንን ባየናቸው ብየ ተቆጨሁ። ተናደድኩ።ከጋስሙ ጋር ተናነቅኩ። በኋላ ጓደኞቼ ገላገሉን። ከዛ እነሱም ንትርክ ውስጥ ገቡ እርስበርሳችንን መደባደብ ጀመርን። ጋስሙ የማንም ጥፋት አይደለም ሲል እንደገና ለጠብ ተነሳሁ። ብዙም ሳይቆይ የሰዎች ድምጽ ሰማን። ወደ ቡናው እርሻ ሩጠን በመሄድ
ተደበቅን፡፡
ከአስር የሚበልጡ አማጺዎች ነበሩ። ልብሳቸው በደም ጨቅይቷል። አማጺዎቹ መሬት ላይ ተቀምጠው ማሪዋና
እያጨሱ ካርታ መጫወት ጀመሩ።
አንዱ “ዛሬ ሶስት መንደሮችን አቃጠልን" ሲል።ሌላው
“በትንሽ ስዓታት ሶስት መንደር ማቃጠል ደስ ይላል። ከዚህ መንደር ደግሞ ማንም የተረፈ የለም ሁሉንም ነገር ነው
ያቃጠልነው:: ኮማንደር እንደሚኮራብን ተስፋ አለኝ" አለ።
አንዱ ወደ ቡና ቅጠሉ ሲመጣ የቡና ቅጠሎቹ ድምጽ ተሰማ።
አማጺዎቹ ጨዋታቸውን አቁመው እሱን ለመሸፈን በሁሉም ቦታ ሮጡ። ሁላችንም አንዴ ተነስተን ሮጥን።ጋስሙ ፊት
ለፊታችን ነበር። የት እንደሚሄድ ስለሚያውቅ ሁላችንም ተከተልነው። ለስዓታት ሮጥን፡፡ ተኩሱ ቀጥለ። ጋስሙ ተኩሱ እንዳይደርስብን እሱ ከኋላ ካትሮ እኛ ከፊት መሮጥ ጀመርን።
ብዙም ሳይቆይ ጋስሙ ማልቀስ ጀመረ። ተንከባለለ። በጥይት ተመቶ ነበር። ብዙ ደም መፍሰስ ጀመረ። አልሃጂ እና እኔ
ቲሽርቱን አወልቀን ደሙን ለማቆም ሞከርን፡ አልቻልንም! እጁ ቀዘቀዘ ደሙ መፍሰሱን ቀጠለ። ምንም አላልንም። ምን እንደሆነ አውቀናል።
አልሃጂ የጋስሙን አይኖችን ከደናቸው::
የመታሁት ጸጸተኝ፡፡ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ። የምታዘቀዝቀው ፀሐይ ጋስሙን ይዛው ሄደች።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#የክረምት_ግጥም
እትትትትትትት - ብርዱ እንዴት አይሏል
አየሩ ቀዝቅዞ - ሰውነቴ ግሏል።
በተወደደ እንጨት- ከሰል በጠፋበት
መብራት ሲፈልጉት - በማይገኝበት።
እንዳይቀዘቅዘን - እንዳይሰማን ብርድ
ነይ እሳት እንፍጠር
ነይ እሳት እናንድድ።
እትትትትትትት - ብርዱ እንዴት አይሏል
አየሩ ቀዝቅዞ - ሰውነቴ ግሏል።
በተወደደ እንጨት- ከሰል በጠፋበት
መብራት ሲፈልጉት - በማይገኝበት።
እንዳይቀዘቅዘን - እንዳይሰማን ብርድ
ነይ እሳት እንፍጠር
ነይ እሳት እናንድድ።
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ስምንት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
..ለቀናት የተጓዝን ይመስለኛል። ሁለት ስዎች ድንገት ግንባራችን ላይ መሳሪያ ደቅነው ተንቀሳቀሱ እስከ ሚሉን ድረስ
ምንም አላስታውስም:: ከባድ መሳሪያ AK 47፣03 እና HPG ይዘው በሁለት ረድፍ ነዱን:: ፊታቸው በጣም ጥቁር ከመሆኑ የተነሳ ክስል የተቀቡ ነበር ሚመስለው። ቀይ በርበሬ በሚመስሉ
አይኖቻቸው አፈጠጡብን። በመንገዳችን የደንብ ልብሳቸው በደም የተጨማለቀ አራት ሰዎች መሬት ላይ ወድቀዋል። ፊቴን
ለማዞር ስሞክር ራሱን የተመታ ሌላ ሰው ተመለከትኩ።አጥወለወለኝ፡፡ ሁሉም ነገር በዙሪያዬ ሲሽከረከር፤ ሲዞርብኝ አንዱ ወታደር ተመለከተኝ። የውሃ ዕቃውን አውጥቶ ትንሽ ከተጎነጨ በኋላ የቀረውን ፊቴ ላይ ደፋብኝ፡፡
“ትለምደዋለህ ፤ ሁሉም ሰው በመጨረሻ ይለምደዋል” አለ።
የተኩስ ድምፅ ድንገት አካባቢውን አናወጠው። ወታደሮቹ ስድስታችንን ይዘው ተንቀሳቀሱ፡፡ የወታደር ጀልባ ከመተረጊስ ጋር የሚንሳፈፍበት አንድ ወንዝ ደረስን :: በወንዙ ዳርቻ የአስራ
አንድ ፣ አስራ ሁለት አመት የሚሆናቸው ታዳጊ ወታደሮች አስክሬን ወድቋል:: ፊታችን አዙረን ጉዞችንን ቀጠልን። የተኩሱ ድምጸ እየጨመረ መጣ፡፡ ወደ ጀልባው ስንወጣ ተኩሱ ወደ እኛ
ተቃረበ። ሮኬት ይወረውራሉ፤ የወንዙ የላይኛው ክፍል በተኩስ ተናወጠ፡፡ እሳት ላይ እንደተጣደ ወሃ ወንዙ በጥይት ናዳ ፈልቶ ይፈለቀለቃል:: የወታደር ልብስ የለበሰ ሰው ወደ ጀልባዎች እየሮጠ ወደ ወታደሮቹ መተኮስ ጀመረ:: ከእኛ ጀልባ ካሉት ወታደሮች አንዱ ተኩሶ ሰውየውን ጣለው:: ጀልባዎቹ ወደ ታች ሲወርዱ ዘለን ወጣን፡ ወታደሩ ጦር ወደ ሰፈረበት የል ወደ ሚባል መንደር ይዞን መራን። ከአስር ቤቶች በላይ ያሉበት ትልቅ
ሰፈር ነው። አብዛኞቹ ቤቶች በወታደሮቹ የተያዙ ናቸው።ወታደሮቹ እኛ በገባንበት በወንዝ ዳርቻ በኩል ካሉት ዛፎች
በስተቀር በአካባቢው ያሉ ዛፎችን ቆርጠዋል። ከድንገተኛ ጥቃት
ራሳቸውን ለመታደግ እንዳደረጉት አስረዱን::
በመጀመሪያ በዚህ በ የል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ደህንነት ያገኘን መስሎን ነበር። መንደሩ ሞቅ ደመቅ ያለ ሳቅ
እናጨዋታ የሞላበት ነበር፡፡ አዋቂዎች፣ የታጠቁ እና ያልታጠቁ የመንደሩ ሰዎች ስለ አየር ንብረት፣ ስለ አዝመራ እና ስለ አደን ያወራሉ። ስለ ጦርነቱ ግን ምንም ማውራት አይፈልጉም አያወሩም፡፡ በመጀመሪያ ሰዎች ለምን እንደዚህ እንደሚሆኑ አልገባኝም ነበር፡፡ ቀስ በቀስ የሰዎች ፈገግታ ስለ ምንም ነገር
መጨነቅ እንደሌለብኝ እምነት አሳደረብኝ፡፡ የሰፈሩ ቀልብ ግን
ያለ አባት እና እናት በቀሩ ልጆች የደበዘዘ ይመስላል።እድሜቸው ከስድስት እስከ አስራ ስድስት የሚሆኑ ወደ ሰላሳ
የሚጠጉ ልጆች ነበሩ። አንዱ እኔ ነበርኩ። ልጅነታችን ለጊዜው ችግር ይግጠመው ወይም ሙሉ ለ ሙሉ እንሰረቅ አናውቅም።
ተሰርቶ ባላላቀ የጡብ ቤት ውስጥ ከሌሎች ልጆች ጋር ማደር ጀመርን። ወታደሮቹ ከእኛ ራቅ ብሎ ባለ አንድ ትልቅ ቤት ውስጥ ፊልም ያያሉ፣ሙዚቃ ያደምጣሉ፣ ይስቃሉ ማሪዋና ያጨሳሉ
ሽታው ስፈሩን ሁሉ ያዳርስ ነበር። ቀን ቀን ከህዝቡ ጋ ተደባልቀው ምግብ እየሰሩ ያሳልፋሉ። ኬን እና እኔ ውሃ በመቅዳት ስሃን በማጠብ እናግዝ ነበር። ሌሎቹ ጓደኞቻችን ሽንኩርት ከተፋ እና መሰል የማዕድ ቤት ስራዎችን ይረዱ ነበር፡፡ ሙሉ ቀን በስራ መጠመዴን ወደድኩት፥
ወንዝ መውረድ፣ መመለስ እና ስሃን ማጠብ፡፡ ከባድ ራስ ምታት
ከሚያስከትልብኝ ሃሳቦች መራቂያ መንገዱ ይሄ ብቻ ነበር።
እኩለ ቀን ሲሆን ሁሉም ስራ አልቆ ምግብ ይቀርባል። ወላጆች ደጃፍ ላይ ተቀምጠው የልጆቻቸውን ፀጉር ይሰራሉ፣ ሴቶች ይዘፍናሉ ወንዶች ደግሞ ኳስ ይጫወቱ ነበር። ደስታው ጫጫታው ከወንዙ ባሻገር ሳይሰማ አይቀርም። በዚህ መንደር ህይወት በፍርሃት አይኖርም፡፡
የኳስ ጨዋታው በማጊቦ የነበረውን የሊግ ጨዋታ አስታወሰኝ፡፡ የእኔ ቡድን ማለትም እኔ እና የተወሰኑ ጓደኞቼ ያሸነፍንበት የዋንጫ ጨዋታ ትዝ ይለኛል። ወላጆቼ ጨዋታውን ለመመልከት ታድመው ነበር፡፡ ጨዋታው ሲጠናቀቅ እናቴ ኩራት እና ደስታ በተደባለቁበት ስሜት ፊቷ በርቶ ተነስታ አጨበጨበች፡፡ አባቴ ደግሞ እኔ ወዳለሁበት ከመጣ በኋላ ራሴን
አሻሽቶ ቀኝ እጄን ወደ ላይ በማንሳት አሸናፊነቴን አወጀ፡፡ ለጁንየርም ተመሳሳይ አደረገ። እናታችን ቀዝቃዛ ውሃ በኩባያ
አመጣችልን። ደስታው የልብ ምቴን ጨመረ፤ ሰውነቴ በላበት ተጠመቆ ነበር። ከጨዋታው በላይ የአባቴ እና እናቴ ደስተኛ መሆን ደስታየን ጨመረው፡፡
አሁን ግን ራሴን ከጨዋታው አገለልኩ። ከቤቱ ጀርባ ተቀምጨ የራስ ምታቴ እስኪበርድ ድረስ ሰማዩን ስመለከት
ቆየሁ፡፡ የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን እንደሚያሰቃየኝ ለማንም አልተናገርኩም፡፡ የወታደሮቹ ሐኪም ጠዋት ጠዋታ ልጆችን ስብስቦ ጉንፋን እና ሌሎችን በሽታዎች እንደተሰማቸው ጠይቆ ህክምና ይሰጣል፡፡ አንድም ቀን ግን ቅዥት ወይም የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን የሚያስቃየው ልጅ ካለ ብሎ ጠይቆ አያውቅም!ማታ አል ሃጂ፣ ጁማህ፣ ሞሪባ እና ኬን በትናንሽ የአለት
ድንጋዮች ገበጣ ሲጫወቱ ነበር። ሙሳ በሰፈሩ ታዋቂ ለመሆን ብዙም ጊዜ አልፈጀበትም። ልክ እንደ ዛሬው ሙሳ ሁሌም ማታ ማታ ለሰፈሩ ልጆች ተረት ተረት ያወራል። እኔ ግን በቤቱ ጥግ
ላይ ቁጭ ብየ ጥርሴን ነክሼ ስቃየን ውጭ አያቸዋለሁ። በአይነ ህሊናየ የእሳት ነበልባል፤ በመንገዴ ያየሁዋቸው አስቃቂ ነገሮች በጨረፍታ እና የህጻናት እና ሴቶች መራራ ጩኸት ይመጣል።ጭንቅላቴ እንደ ደወል ሲደበደብ በዝምታ አለቅሳለሁ። አንዳንዴ የራስ ምታት በሽታው ማይግሬኔ ሲበርድልኝ ለአፍታ ቢሆንም እንቅልፍ ይወስደኛል። ብዙም ሳልቆይ በቅኝዥት እባንናለሁ።
አንዴ ጭንቅላቴ ላይ በጥይት ሲመታ በህልሜ አየሁ። በደም ተጨመለቄ ወድቄለሁ ሰዎች ግን በጥድፊያ ያልፉኛል። ዉሻ መጥቶ ደሜን ይልሳል። ላባርረው ብፈልግም አቅም አልነበረኝም
መንቀሳቀስም አልቻልኩም። በመጨረሻ የፈራሁትን ነገር ከማድረጉ በፊት ከእንቅልፌ ባነንኩ። ከዛ በኋላ የቀሪውን ለሊት መተኛት አልቻልኩም:: አልቦኝም ነበር።
አንድ ቀን የመንደሩ ሁኔታ ድንገት ተለወጠ። ወጥረት ሆነ የውጥረቱ ምክንያት ባይታወቅም አንድ ከባድ
ነገር እንደሚከተል መገመት ይቻላል። በመንደሩ የሚገኙ ሁሉ ወታደሮች የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ትጥቃቸዉ
አሟልተው ተሰበሰቡ፡፡ “ተጠንቀቅ” “አሳርፍ” “ተጠንቀ “አሳርፍ” :: ከአል ሃጂ ጋር ውሃ ለመቅዳት ወንዝ ስወርድ ነው
የአሰልጣኙን ድምፅ የሰማሁት። ስመለስ ልምምድ አብቅቶ መቶ አለቃ ጃባቲ በወታደሮቹ ፊት ቁሞ ይናገራል። ለምሳ
እስከሚለቀቁ ድረስ ለስዐታት ንግግር አደረገ። መቶ አለቃ በሚናገርበት ወቅት የዕለት ተዕለት ስራችንን እየሰራን ምን
እንደሆነ በልጅ አዕምሮችን ለመረዳት እንሞክር ነበር።
ማታ ወታደሮቹ ጠበንጃዎችን ሲያጸዱ ፤ አልፎ አልፎ ወደ ሰማይ በመተኮስ አሳለፉ። ህጻናት ተኩሱን ሲስሙ ወደ ወላጆች እቅፍ ሮጡ። ወታደሮቹ ገሚሶቹ ሲጋራ ማሪዋና ሲያጨሱ የቀሩት ቁማር ሲጫወቱ እና ፊልም ሲያዩ ለሊቱ ተቃረበ።
መቶ አለቃ ጃባቲ ቤቱ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሐፍ ያነብ ነበር።ቀና ብሎ አያይም። ቢጮሁ ቢያፏጩ ቀና ብሎ አያይም።ያለ ወትሮው ፀጥታ ሲሰፍን ድምጸ ሲጠፋ ግን ቀና ብሎ አካባቢውን ይቃኛል። ወደ እሱ ስመለከት አይናችን ተጋጨ እና ወደ እሱ እንድመጣ ጠራኝ፡፡ ቁመቱ ረጂም፣ ፀጉሩ የሳሳ፣ አይኖቹ ትልልቅ እና ጉንጩ ወፍራም ነበሩ። ዝምተኛ ነገር ግን በዝምታው
#ክፍል_ስምንት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
..ለቀናት የተጓዝን ይመስለኛል። ሁለት ስዎች ድንገት ግንባራችን ላይ መሳሪያ ደቅነው ተንቀሳቀሱ እስከ ሚሉን ድረስ
ምንም አላስታውስም:: ከባድ መሳሪያ AK 47፣03 እና HPG ይዘው በሁለት ረድፍ ነዱን:: ፊታቸው በጣም ጥቁር ከመሆኑ የተነሳ ክስል የተቀቡ ነበር ሚመስለው። ቀይ በርበሬ በሚመስሉ
አይኖቻቸው አፈጠጡብን። በመንገዳችን የደንብ ልብሳቸው በደም የተጨማለቀ አራት ሰዎች መሬት ላይ ወድቀዋል። ፊቴን
ለማዞር ስሞክር ራሱን የተመታ ሌላ ሰው ተመለከትኩ።አጥወለወለኝ፡፡ ሁሉም ነገር በዙሪያዬ ሲሽከረከር፤ ሲዞርብኝ አንዱ ወታደር ተመለከተኝ። የውሃ ዕቃውን አውጥቶ ትንሽ ከተጎነጨ በኋላ የቀረውን ፊቴ ላይ ደፋብኝ፡፡
“ትለምደዋለህ ፤ ሁሉም ሰው በመጨረሻ ይለምደዋል” አለ።
የተኩስ ድምፅ ድንገት አካባቢውን አናወጠው። ወታደሮቹ ስድስታችንን ይዘው ተንቀሳቀሱ፡፡ የወታደር ጀልባ ከመተረጊስ ጋር የሚንሳፈፍበት አንድ ወንዝ ደረስን :: በወንዙ ዳርቻ የአስራ
አንድ ፣ አስራ ሁለት አመት የሚሆናቸው ታዳጊ ወታደሮች አስክሬን ወድቋል:: ፊታችን አዙረን ጉዞችንን ቀጠልን። የተኩሱ ድምጸ እየጨመረ መጣ፡፡ ወደ ጀልባው ስንወጣ ተኩሱ ወደ እኛ
ተቃረበ። ሮኬት ይወረውራሉ፤ የወንዙ የላይኛው ክፍል በተኩስ ተናወጠ፡፡ እሳት ላይ እንደተጣደ ወሃ ወንዙ በጥይት ናዳ ፈልቶ ይፈለቀለቃል:: የወታደር ልብስ የለበሰ ሰው ወደ ጀልባዎች እየሮጠ ወደ ወታደሮቹ መተኮስ ጀመረ:: ከእኛ ጀልባ ካሉት ወታደሮች አንዱ ተኩሶ ሰውየውን ጣለው:: ጀልባዎቹ ወደ ታች ሲወርዱ ዘለን ወጣን፡ ወታደሩ ጦር ወደ ሰፈረበት የል ወደ ሚባል መንደር ይዞን መራን። ከአስር ቤቶች በላይ ያሉበት ትልቅ
ሰፈር ነው። አብዛኞቹ ቤቶች በወታደሮቹ የተያዙ ናቸው።ወታደሮቹ እኛ በገባንበት በወንዝ ዳርቻ በኩል ካሉት ዛፎች
በስተቀር በአካባቢው ያሉ ዛፎችን ቆርጠዋል። ከድንገተኛ ጥቃት
ራሳቸውን ለመታደግ እንዳደረጉት አስረዱን::
በመጀመሪያ በዚህ በ የል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ደህንነት ያገኘን መስሎን ነበር። መንደሩ ሞቅ ደመቅ ያለ ሳቅ
እናጨዋታ የሞላበት ነበር፡፡ አዋቂዎች፣ የታጠቁ እና ያልታጠቁ የመንደሩ ሰዎች ስለ አየር ንብረት፣ ስለ አዝመራ እና ስለ አደን ያወራሉ። ስለ ጦርነቱ ግን ምንም ማውራት አይፈልጉም አያወሩም፡፡ በመጀመሪያ ሰዎች ለምን እንደዚህ እንደሚሆኑ አልገባኝም ነበር፡፡ ቀስ በቀስ የሰዎች ፈገግታ ስለ ምንም ነገር
መጨነቅ እንደሌለብኝ እምነት አሳደረብኝ፡፡ የሰፈሩ ቀልብ ግን
ያለ አባት እና እናት በቀሩ ልጆች የደበዘዘ ይመስላል።እድሜቸው ከስድስት እስከ አስራ ስድስት የሚሆኑ ወደ ሰላሳ
የሚጠጉ ልጆች ነበሩ። አንዱ እኔ ነበርኩ። ልጅነታችን ለጊዜው ችግር ይግጠመው ወይም ሙሉ ለ ሙሉ እንሰረቅ አናውቅም።
ተሰርቶ ባላላቀ የጡብ ቤት ውስጥ ከሌሎች ልጆች ጋር ማደር ጀመርን። ወታደሮቹ ከእኛ ራቅ ብሎ ባለ አንድ ትልቅ ቤት ውስጥ ፊልም ያያሉ፣ሙዚቃ ያደምጣሉ፣ ይስቃሉ ማሪዋና ያጨሳሉ
ሽታው ስፈሩን ሁሉ ያዳርስ ነበር። ቀን ቀን ከህዝቡ ጋ ተደባልቀው ምግብ እየሰሩ ያሳልፋሉ። ኬን እና እኔ ውሃ በመቅዳት ስሃን በማጠብ እናግዝ ነበር። ሌሎቹ ጓደኞቻችን ሽንኩርት ከተፋ እና መሰል የማዕድ ቤት ስራዎችን ይረዱ ነበር፡፡ ሙሉ ቀን በስራ መጠመዴን ወደድኩት፥
ወንዝ መውረድ፣ መመለስ እና ስሃን ማጠብ፡፡ ከባድ ራስ ምታት
ከሚያስከትልብኝ ሃሳቦች መራቂያ መንገዱ ይሄ ብቻ ነበር።
እኩለ ቀን ሲሆን ሁሉም ስራ አልቆ ምግብ ይቀርባል። ወላጆች ደጃፍ ላይ ተቀምጠው የልጆቻቸውን ፀጉር ይሰራሉ፣ ሴቶች ይዘፍናሉ ወንዶች ደግሞ ኳስ ይጫወቱ ነበር። ደስታው ጫጫታው ከወንዙ ባሻገር ሳይሰማ አይቀርም። በዚህ መንደር ህይወት በፍርሃት አይኖርም፡፡
የኳስ ጨዋታው በማጊቦ የነበረውን የሊግ ጨዋታ አስታወሰኝ፡፡ የእኔ ቡድን ማለትም እኔ እና የተወሰኑ ጓደኞቼ ያሸነፍንበት የዋንጫ ጨዋታ ትዝ ይለኛል። ወላጆቼ ጨዋታውን ለመመልከት ታድመው ነበር፡፡ ጨዋታው ሲጠናቀቅ እናቴ ኩራት እና ደስታ በተደባለቁበት ስሜት ፊቷ በርቶ ተነስታ አጨበጨበች፡፡ አባቴ ደግሞ እኔ ወዳለሁበት ከመጣ በኋላ ራሴን
አሻሽቶ ቀኝ እጄን ወደ ላይ በማንሳት አሸናፊነቴን አወጀ፡፡ ለጁንየርም ተመሳሳይ አደረገ። እናታችን ቀዝቃዛ ውሃ በኩባያ
አመጣችልን። ደስታው የልብ ምቴን ጨመረ፤ ሰውነቴ በላበት ተጠመቆ ነበር። ከጨዋታው በላይ የአባቴ እና እናቴ ደስተኛ መሆን ደስታየን ጨመረው፡፡
አሁን ግን ራሴን ከጨዋታው አገለልኩ። ከቤቱ ጀርባ ተቀምጨ የራስ ምታቴ እስኪበርድ ድረስ ሰማዩን ስመለከት
ቆየሁ፡፡ የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን እንደሚያሰቃየኝ ለማንም አልተናገርኩም፡፡ የወታደሮቹ ሐኪም ጠዋት ጠዋታ ልጆችን ስብስቦ ጉንፋን እና ሌሎችን በሽታዎች እንደተሰማቸው ጠይቆ ህክምና ይሰጣል፡፡ አንድም ቀን ግን ቅዥት ወይም የራስ ምታት በሽታ ማይግሬን የሚያስቃየው ልጅ ካለ ብሎ ጠይቆ አያውቅም!ማታ አል ሃጂ፣ ጁማህ፣ ሞሪባ እና ኬን በትናንሽ የአለት
ድንጋዮች ገበጣ ሲጫወቱ ነበር። ሙሳ በሰፈሩ ታዋቂ ለመሆን ብዙም ጊዜ አልፈጀበትም። ልክ እንደ ዛሬው ሙሳ ሁሌም ማታ ማታ ለሰፈሩ ልጆች ተረት ተረት ያወራል። እኔ ግን በቤቱ ጥግ
ላይ ቁጭ ብየ ጥርሴን ነክሼ ስቃየን ውጭ አያቸዋለሁ። በአይነ ህሊናየ የእሳት ነበልባል፤ በመንገዴ ያየሁዋቸው አስቃቂ ነገሮች በጨረፍታ እና የህጻናት እና ሴቶች መራራ ጩኸት ይመጣል።ጭንቅላቴ እንደ ደወል ሲደበደብ በዝምታ አለቅሳለሁ። አንዳንዴ የራስ ምታት በሽታው ማይግሬኔ ሲበርድልኝ ለአፍታ ቢሆንም እንቅልፍ ይወስደኛል። ብዙም ሳልቆይ በቅኝዥት እባንናለሁ።
አንዴ ጭንቅላቴ ላይ በጥይት ሲመታ በህልሜ አየሁ። በደም ተጨመለቄ ወድቄለሁ ሰዎች ግን በጥድፊያ ያልፉኛል። ዉሻ መጥቶ ደሜን ይልሳል። ላባርረው ብፈልግም አቅም አልነበረኝም
መንቀሳቀስም አልቻልኩም። በመጨረሻ የፈራሁትን ነገር ከማድረጉ በፊት ከእንቅልፌ ባነንኩ። ከዛ በኋላ የቀሪውን ለሊት መተኛት አልቻልኩም:: አልቦኝም ነበር።
አንድ ቀን የመንደሩ ሁኔታ ድንገት ተለወጠ። ወጥረት ሆነ የውጥረቱ ምክንያት ባይታወቅም አንድ ከባድ
ነገር እንደሚከተል መገመት ይቻላል። በመንደሩ የሚገኙ ሁሉ ወታደሮች የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ትጥቃቸዉ
አሟልተው ተሰበሰቡ፡፡ “ተጠንቀቅ” “አሳርፍ” “ተጠንቀ “አሳርፍ” :: ከአል ሃጂ ጋር ውሃ ለመቅዳት ወንዝ ስወርድ ነው
የአሰልጣኙን ድምፅ የሰማሁት። ስመለስ ልምምድ አብቅቶ መቶ አለቃ ጃባቲ በወታደሮቹ ፊት ቁሞ ይናገራል። ለምሳ
እስከሚለቀቁ ድረስ ለስዐታት ንግግር አደረገ። መቶ አለቃ በሚናገርበት ወቅት የዕለት ተዕለት ስራችንን እየሰራን ምን
እንደሆነ በልጅ አዕምሮችን ለመረዳት እንሞክር ነበር።
ማታ ወታደሮቹ ጠበንጃዎችን ሲያጸዱ ፤ አልፎ አልፎ ወደ ሰማይ በመተኮስ አሳለፉ። ህጻናት ተኩሱን ሲስሙ ወደ ወላጆች እቅፍ ሮጡ። ወታደሮቹ ገሚሶቹ ሲጋራ ማሪዋና ሲያጨሱ የቀሩት ቁማር ሲጫወቱ እና ፊልም ሲያዩ ለሊቱ ተቃረበ።
መቶ አለቃ ጃባቲ ቤቱ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሐፍ ያነብ ነበር።ቀና ብሎ አያይም። ቢጮሁ ቢያፏጩ ቀና ብሎ አያይም።ያለ ወትሮው ፀጥታ ሲሰፍን ድምጸ ሲጠፋ ግን ቀና ብሎ አካባቢውን ይቃኛል። ወደ እሱ ስመለከት አይናችን ተጋጨ እና ወደ እሱ እንድመጣ ጠራኝ፡፡ ቁመቱ ረጂም፣ ፀጉሩ የሳሳ፣ አይኖቹ ትልልቅ እና ጉንጩ ወፍራም ነበሩ። ዝምተኛ ነገር ግን በዝምታው
👍2❤1
ውስጥ ጉልበቱ ስልጣኑ የሚታይ ሞገሱ የሚያስፈራ አለቃ ነበር። ከፊቱ ጥቁረት የተነሳ ሙሉ ፊቱን ለማየት ድፍረት
ይጠይቃል።
በቂ ምግብ እያገኘህ ነው?› ሲል ጠየቀኝ፡፡
“አዎ አልኩ” የሚያነበውን መፅሃፍ ለማየት እየሞከርኩ።
“ሼክስፒር ነው”:: ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ብሎ የመፅሃፉን ሽፋን አሳየኝ። “አንብበህዋል?
ትምህርት ቤት እያለሁ አንብቤው ነበር አልኩት።
የምታስታውሰው ነገር አለ? ብሎ ጠየቀኝ።
“ፈሪ ከመሞቱ አስቀድሞ ብዙ ጊዜ ይሞታል , ብየ ስጀምር ሙሉ ቃለ ተውኔቱን ከእኔ ጋር ደገመ። ልክ እንደጨረስን ፊቱን መልሶ ተኮሳተረ:: እኔን ትቶኝ ትኩረቱን ወደ መፅሃፉ መለሰ።
በሚያነበው መፅሃፍ ይሁን ወይም በአዕምሮ ውስጥ ባለ ሃሳብ ምክንያት ግንባሩ ላይ ያሉ የደም ስሮቹ ሲገታተሩ አየሁ። ቀስ ብዬ ከእሱ ተለይቼ ስሄድ ሰማዩ ከፀሃይ ብርሃን ወደ ጨለማ
እየተሸጋገረ ነበር...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ይጠይቃል።
በቂ ምግብ እያገኘህ ነው?› ሲል ጠየቀኝ፡፡
“አዎ አልኩ” የሚያነበውን መፅሃፍ ለማየት እየሞከርኩ።
“ሼክስፒር ነው”:: ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ብሎ የመፅሃፉን ሽፋን አሳየኝ። “አንብበህዋል?
ትምህርት ቤት እያለሁ አንብቤው ነበር አልኩት።
የምታስታውሰው ነገር አለ? ብሎ ጠየቀኝ።
“ፈሪ ከመሞቱ አስቀድሞ ብዙ ጊዜ ይሞታል , ብየ ስጀምር ሙሉ ቃለ ተውኔቱን ከእኔ ጋር ደገመ። ልክ እንደጨረስን ፊቱን መልሶ ተኮሳተረ:: እኔን ትቶኝ ትኩረቱን ወደ መፅሃፉ መለሰ።
በሚያነበው መፅሃፍ ይሁን ወይም በአዕምሮ ውስጥ ባለ ሃሳብ ምክንያት ግንባሩ ላይ ያሉ የደም ስሮቹ ሲገታተሩ አየሁ። ቀስ ብዬ ከእሱ ተለይቼ ስሄድ ሰማዩ ከፀሃይ ብርሃን ወደ ጨለማ
እየተሸጋገረ ነበር...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
በአንዱ ቀን ነው
ሃያ ሁለት ማዞሪያ ጋር የሜክሲኮ ታክሲ
ያዝኩና እስኪሞላ እጠብቃለሁ "በሃሎ ሃሎ" ሜጋፎን የሚለፍፍ የሚመስል ከኋላዬ ያለ ተሳፋሪ ስልክ ይዞ ከጣሪያ በላይ ይጮሃል።
በአማርኛ ፣ ከዚያ ደግሞ በእንግሊዝኛ ፤ በእንግሊዝኛ ፣ መልሶ ደግሞ በአማርኛ : :
አልኩህ እኮ... ዊዝ አውት አይሰጡም : : ዊዝ ይሰጣኩ : :...እ... እ... ኖ... ኖ ሊስን፣ ሚ እንጂ ኖ...! ..ኖ.፣ ... ሊስን ሚ.....መልዕክቱ ቢደርሰው ብዬ ሁለት ሦስቴ እየዞርኩ እንደ ማያትም
እንደመገላመጥም አደርግሁት እሱ እቴ!
"ሊስን ሚ! አይ ቴል ዩ... ሊንስ ሚ ! ... ፈርስት ... ራስህ ሂድ...ሰከንድ ለሬጀስትራር ቶክ አደርጋቸውና ኖ ቤዛ ጋር አይደለም : : ቤዛ ጥርስ የሌለው ላየን' ማለት ናት ... ሊስን ሚ! ሊስን፣
ሚ እንጂ ! ”
እንደዚህ የተሳፋሪውን ጆሮ አስገድዶ ሲደፍር ቆይቶ ታክሲው ሊሞላ አንድ
ሰው እየቀረው መንገድ ጀመር : : ስልኩም ተዘጋ : :
እፎይ አልኩ ።
ትንሽ ዝቅ እንዳልን ታክሲው ቆመና የቀረችው ቦታ ላይ ከባለ ሞባይሉ
ሰውዬ አጠገብ አንድ ፈረንጅ ጫነ : :
እደ ገና መሄድ ጀመርን፡፡
ረዳቱ ሒሳብ እየተቀበለ ፈረንጁ ጋር ሲደርስ ፈረንጁ ፣ “ኢትዮጵያ ሆቴል” ሲል ተሰማኝ ።
ረዳቱ "አይሄድም ይለዋል ፈረንጁ ደጋግሞ "ኢትዬጵያ ሆቴል ይለዋል ”
ከብዙ ወዲህና ወዲያ በኋካ ፣ “ኢትዮጵያ ሆቴል ኖ ጎ” ብሎ ረዳቱ መለሰ።
ነገሩ በዚሁ ያበቃ መስሎኝ ነበር ግን ፈረንጁ ሆድ ብሶት ይምጣ ወይ ሌላ "ለምን አይሄድም" አይነት ጠንካራ ክርክር ሲጀምር ተሳፋሪ ሁሉ የራሱን አስተያየት መስጠት ጀመረ።
“አይ...ያታለልከው መስሎት እኮ ነው... መንገዴ አይደለም ብለህ
አስረዳው።
ፈ
“ኢትዮጵያ ሆቴል በዚህ ጋር አይደለም ... እኔ ሜክሲኮ ነኝ በለው : "
“አታስብ ፣ የፍልውሃ ታክሲ እዚህ ጋር አስይዝዓhሁ አትለውም? ”
ቋቋ እንጂ ሐሳብ ላልቸጀረው ሰው ፣ የሐሳብ መዓት ያዋጣል : :
እኔ ግን ተንኮል ቅልቅል ሐሳብ መጣልኝ ፡ ታክሲው ሳይነሳ በእንግhዝኛው “ሲያስደንቀን፣” ወደነበረው ባለ ሞባይል ሰው ዞር አልኩና ፣
ወንድሜ ፣ አንድ በለን እንጂ ?” አልኩት :
በአንድ ጊዜ ሰው ሁኩ ወደ እሱ ዞረ: : ትንሽ ካቅማማ በኋካ ፣
"ዘ ታክሲ ኢትዮጵያ ሆቴል ኖ ጎ” ሲል ረዳቱ ተቀበለና ፣ “ ይህንንማ እኔም ብይዋhሁ ... ምን አይነቱ ነው!
ብሎ አሣቀን: :
ለካስ የአቶ ፣ “ሊስን ሚ ” እንግሊዝኛ ሀግርግር እንጂ ለችግር አይሆንም!
ለጉራ እንጂ ለስራ የማይሆን እንግሊዘኛ ይዘን ከተማው ውስጥ የምንሸልል ሰዎች ወዮልን!
🔘በሕይወት እምሻው🔘
ሃያ ሁለት ማዞሪያ ጋር የሜክሲኮ ታክሲ
ያዝኩና እስኪሞላ እጠብቃለሁ "በሃሎ ሃሎ" ሜጋፎን የሚለፍፍ የሚመስል ከኋላዬ ያለ ተሳፋሪ ስልክ ይዞ ከጣሪያ በላይ ይጮሃል።
በአማርኛ ፣ ከዚያ ደግሞ በእንግሊዝኛ ፤ በእንግሊዝኛ ፣ መልሶ ደግሞ በአማርኛ : :
አልኩህ እኮ... ዊዝ አውት አይሰጡም : : ዊዝ ይሰጣኩ : :...እ... እ... ኖ... ኖ ሊስን፣ ሚ እንጂ ኖ...! ..ኖ.፣ ... ሊስን ሚ.....መልዕክቱ ቢደርሰው ብዬ ሁለት ሦስቴ እየዞርኩ እንደ ማያትም
እንደመገላመጥም አደርግሁት እሱ እቴ!
"ሊስን ሚ! አይ ቴል ዩ... ሊንስ ሚ ! ... ፈርስት ... ራስህ ሂድ...ሰከንድ ለሬጀስትራር ቶክ አደርጋቸውና ኖ ቤዛ ጋር አይደለም : : ቤዛ ጥርስ የሌለው ላየን' ማለት ናት ... ሊስን ሚ! ሊስን፣
ሚ እንጂ ! ”
እንደዚህ የተሳፋሪውን ጆሮ አስገድዶ ሲደፍር ቆይቶ ታክሲው ሊሞላ አንድ
ሰው እየቀረው መንገድ ጀመር : : ስልኩም ተዘጋ : :
እፎይ አልኩ ።
ትንሽ ዝቅ እንዳልን ታክሲው ቆመና የቀረችው ቦታ ላይ ከባለ ሞባይሉ
ሰውዬ አጠገብ አንድ ፈረንጅ ጫነ : :
እደ ገና መሄድ ጀመርን፡፡
ረዳቱ ሒሳብ እየተቀበለ ፈረንጁ ጋር ሲደርስ ፈረንጁ ፣ “ኢትዮጵያ ሆቴል” ሲል ተሰማኝ ።
ረዳቱ "አይሄድም ይለዋል ፈረንጁ ደጋግሞ "ኢትዬጵያ ሆቴል ይለዋል ”
ከብዙ ወዲህና ወዲያ በኋካ ፣ “ኢትዮጵያ ሆቴል ኖ ጎ” ብሎ ረዳቱ መለሰ።
ነገሩ በዚሁ ያበቃ መስሎኝ ነበር ግን ፈረንጁ ሆድ ብሶት ይምጣ ወይ ሌላ "ለምን አይሄድም" አይነት ጠንካራ ክርክር ሲጀምር ተሳፋሪ ሁሉ የራሱን አስተያየት መስጠት ጀመረ።
“አይ...ያታለልከው መስሎት እኮ ነው... መንገዴ አይደለም ብለህ
አስረዳው።
ፈ
“ኢትዮጵያ ሆቴል በዚህ ጋር አይደለም ... እኔ ሜክሲኮ ነኝ በለው : "
“አታስብ ፣ የፍልውሃ ታክሲ እዚህ ጋር አስይዝዓhሁ አትለውም? ”
ቋቋ እንጂ ሐሳብ ላልቸጀረው ሰው ፣ የሐሳብ መዓት ያዋጣል : :
እኔ ግን ተንኮል ቅልቅል ሐሳብ መጣልኝ ፡ ታክሲው ሳይነሳ በእንግhዝኛው “ሲያስደንቀን፣” ወደነበረው ባለ ሞባይል ሰው ዞር አልኩና ፣
ወንድሜ ፣ አንድ በለን እንጂ ?” አልኩት :
በአንድ ጊዜ ሰው ሁኩ ወደ እሱ ዞረ: : ትንሽ ካቅማማ በኋካ ፣
"ዘ ታክሲ ኢትዮጵያ ሆቴል ኖ ጎ” ሲል ረዳቱ ተቀበለና ፣ “ ይህንንማ እኔም ብይዋhሁ ... ምን አይነቱ ነው!
ብሎ አሣቀን: :
ለካስ የአቶ ፣ “ሊስን ሚ ” እንግሊዝኛ ሀግርግር እንጂ ለችግር አይሆንም!
ለጉራ እንጂ ለስራ የማይሆን እንግሊዘኛ ይዘን ከተማው ውስጥ የምንሸልል ሰዎች ወዮልን!
🔘በሕይወት እምሻው🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_ዘጠኝ
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
የሰባት አመት ልጅ እያለሁ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን ለማቅረብ ወደ ከተማ አዳራሽ እሄድ ነበር፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ
አዋቂዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ። ረጂም ጣውላ ወንበር ላይ ተቀምጠው ውይይታቸው ሲያልቅ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን እንዳቀርብ እጠራለሁ። አባቴ ጸጥታ እንዲሰፍን እና
ተውኔቱ እንዲጀምር ደመቅ አርጎ ያነጥሳል። እጁን አጣምሮ ከደማቅ ፈገግታ ጋር ፊት ለፊት ይቀመጥ ነበር። ወንበር ላይ እወጣና ረጂም ዱላ እንደ ሰይፍ በመጠቀም እጀምራለሁ።
ከጅሊየስ ቄሳር “ጓደኞቼ፣ ሮማዊያን፣ የሃገሬ ልጆች እስኪ ጀሮችሁን ስጡኝ፡፡ ብየ እጀምራለሁ። አዋቂዎች የሚወዷቸው
ስለነበሩ ብዙ ጊዜ ማክቤዝ እና ጅሊየስ ቄሳርን ነበር ማቀርበው።የእንግሊዝኛ ቋንቋን የመናገር ችሎታየ የዳበረ እና ጥሩ የሆነ ስለሚመስለኝ በከፍተኛ ጉጉት እና ደስታ ነበር ማቀርበው::
ወታደሮቹ በእኩለ ለሊት ሲገሰግሱ ነቅቼ ነበር። የኮቴቸው ድምጸ በሙሉ መንደሩ አስተጋባ። ቀኑን ሙሉ ጆሮዎየ ላይ
ሲያቃጭልብኝ ዋለ። አስር ወታደሮች ሰፈሩን እንዲጠብቁ ከእኛ ጋር ቀሩ። በየምድብ ቦታቸው ቀኑን ሙሉ ሲጠብቁ ዋሉ። ምሽቱ ፥ሲቃረብ ወታደሮቹ ወደ ሰማይ በመተኮስ እና የመንደሩ ሰዎች
ወደ “ቤት እንዲገቡ” እንዲሸሸጉ በማዘዝ የስዓት እላፊ አወጁ።ያን ምሽት ሙሳ ተረት አላወራም ሞሪባም ከልጆች ጋር ገበጣ አልተጫወተም፡፡ በዝምታ ጀርባችንን ለግድግዳው ሰጠን
ተቀምጠን የተኩስ እሩምታ ሲዘንብ ከርቀት እናዳምጥ ነበር።ለሊቱ እስኪገባደድ የመጨረሻ ስዓት፤ ጨረቃ በጉም መሃል አልፋ ፊቷን በክፍቱ የቤታችን መስኮት እስከምታሳይ እና
በአውራ ዶሮ ጩኅት ለሊቱ እስከሚባረር ድረስ ተኩሱ ቀጠለ።
ፀጠዋት ከፀሐይዋ መውጣት ጋር መመለስ የቻሉ የተወሰኑ ወታደሮች ብቻ ወደ መንደር መጡ። የተወለወለ ኮሬ ጫማቸው በጭቃ ተበላሽቷል። ፈንጠር ፈንጠር ብለው መተማማኛ የመሰላቸውን መሳሪያቸውን አቅፈው ተቀምጠዋል። ብሎኬት ላይ ተቀምጦ የነበረ አንድ ወታደር እጁን በራሱ ላይ ጭኖ
ተርገፈገፈ። ተነስቶ መንደሩን ዙሮ ወደነበረበት ተመለሰ።በተደጋጋሚ እንደዚህ ሲያረግ ቆየ። መቶ አለቃ ጃባቲ ሬዲዮ ላይ መልዕክት ሲያስተላልፍ ከቆየ በኋላ ሬዲዮውን ወረውሮ ወደ ቤቱ ገባ። መንደርተኛው ምንም አላወራም:: ዝም
ብሎ የወረደውን መዓት ታዘበ።
እኩለ ቀን ሲሆን ከሃያ የሚበልጡ ወታደሮች ወደ መንደሯ መጡ። መቶ አለቃ ሲያቸው ማመን አልቻለም ተገረመ ተደሰተ ብዙም ሳይቆይ ቁጥብ ሆነ። ወታደሮቹ ራሳቸዉን እንደገና ካዘጋጁ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ወረዱ። ምንም መደበቅ አላስፈለገም ጦርነቱ ቅርብ ነው። ብዙም ሳይቆይ የተኩስ እሩምታ መስማት ጀመርን። መንደሩን የሚጠብቁት ወታደሮች ወደ ቤት እንድንገባ አዘዙን። ተኩሱ ከወፎችን እና ዶሮዎች ጩኅት ጋር እስከ ምሽት ድረስ ቀጠለ። ለሊት ጥይት ለማምጣት እና ለአጭር ረፍት ጊዜ ወታደሮች እየሮጡ ወደ መንደር መጡ። የቆሰሉ ወታደሮች በፋኑስ የታገዘ ቀላል ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም አብዛኞቹ ይሞታሉ። ወታደሮቹ የሞቱ ጓዶቻቸዉን ወደ መንደር
አያመጡም። ምርኮኛዎችን አሰልፈው ግንባራቸውን በጥይት በመምታት ይገድሉዋቸዋል።
ጦርነቱ ለቀናት ቀጠለ።ወታደሮች ቀስ በቀስ ቁጥራቸው እየቀነሰ ሄደ፡፡ ወታደሮቹ እረፍት አጡ ፤ ኮሽ ካለ የመንደሩ ሰዎች
ላይ ሳይቀር መተኮስ ጀመሩ:: መቶ አለቃዉ የመንደሩን ነዋሪዎች ወደ አደባባይ ወጥተው እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ሰጠ።
“ጫካው ውስጥ ህይወታችንን ሊያጠፉ ዕድላችንን ሊያበላሹ የሚጠብቁ ወታደሮች ተዋግተናቸዋል። በቁጥር ግን ይበልጡናል። መንደሩን በሙሉ ከበው አሉ። ይሄን መንደር እስከሚይዙ ድረስ ተስፋ አልቆርጥም:: የእኛን ምግብ እና መሳሪያ የራሳቸው ማድረግ ይፈልጋሉ።” ብሎ ንግግሩን ገታ አደረገና ቀስ ብሎ እንደገና ቀጠለ። አንዳንዶቻችሁ ከዚህ የምትገኙት ወላጆቻችሁን ቤተሰቦቻችሁን ስለገደሉባችሁ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ አስተማማኝ መጠጊያ መሸሸጊያ ነው ብላችሁ ነው:: እንግዲህ ከዚህ በኋላ
አስተማማኝ አይደለም:: ለዚህ ነው ጠንካራ ወንዶችን ታደጊዎችን የምንፈልገው:: እነዚህን እንድታግዙን የሰፈሩን ሰላም እና ደህንነት እንድንጠብቅ
እንፈልጋለን። መዋጋት ወይም ማገዝ ካልፈለጋችህ ምንም አይደል፡፡ ነገር ግን ቀለብ አይሰፈርላችሁም በመንደሩም መቆየት አትችሉም። መሄድ ትችላላችሁ ከዚህ የምንፈልጋቸው ምግብ
በማብሰል መሳሪያ በማዘጋጀት ጥይት በማቀበል የሚረድን የሚዋጉ ናቸዉ። ለምግብ ማብሰል በቂ ሴቶች አሉ። ስለዚህ ብቁ የሆኑ ታዳጊ ወንዶች እና ወጣቶች ነው እነዚህን አማጺዎች
እንዲዋጉ ምንፈልገው:: አሁን ነው የወላጆቻችሁን ደም የምትመልሱት፤ ሌሎች ልጆችንም ወላጆቻቸውን ከማጣት
ማስቀረት የምትችሉት::” ትንፋሽ ወሰደ። “ ነገ ጠዋት ሁላችሁም ከዚህ ቦታ እንድትሰለፉ ለተለያዩ ስራዎች ሰዎችን
እንመርጣለን።” አደባባዩን ለቆ ሲሄድ ጠባቂዎቹ ተከተሉት።
ለተወሰነ ጊዜ ደርቀን ባለንበት ቁመን ቀረን። ከዛ የስዓት እላፊው ሲቃረብ ወደየ ምኝታ ቦታችን ተበተን። ቤት ውስጥ
ጁማህ፣ አል ሃጂ ሞሪባ፣ ሙሳ እና እኔ ምን ማድረግ እንዳለብን ድምጻችንን ቀንሰን ተወያየን፡፡
“አማጺዎች ከዚህ መንደር የሆነ ማንም ሰው ጠላት ወይም ስላይ ነው ብለው ስለሚገምቱ ሁሉንም ይገድላሉ። ይሄን
ነው ያለው አምሳ አለቃው።” አለ አል ሃጂ የገጠመንን ኣጣብቂኝ ለማስረዳት ሲሞክር። ሌሎቹ ወንዶች ከተጋደሙበት ስጋጃ ተነስተው ውይይቱን ተቀላቀሉ። አል ሃጂ ቀጠለ “የሚሻለው ለጊዜውም ቢሆን ከዚህ መቆየት ነው።” ሌላ ምርጫ
አልነበረንም። መንደሩን ለቆ መሄድ ማለት መሞት ማለት ነው::
“አዳምጡ! ይህ ከመቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው፡፡ ሁላችሁም አሁንኑ ወደ አደባባይ በመውጣት ተሰብሰቡ።” ብሎ በድምጽ ማጉያ ለፈለፈ። ተናግሮ ሳይጨርስ አደባባዩ በሰዎች ሞላ፡፡
ሁሉም ሰው ለደህንነቱ ምን ማድረግ እንዳለበት የሚወስነውን ይህን ጊዜ በጉጉት ይጠብቅ ነበር። ከአዋጁ በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኩሽና ቤቱ ውስጥ ተቀምጬ ነበር። ፊታቸው ባዶ ምንም ስሜት የማይታይበት አይናቸው ግን በሃዘን ገርጥቶ ነበር። አይን ለ አይን ላያቸው ብሞክርም ፊታቸውን አዞሩ። ቁርሴን ለመብላት ብሞክርም ፍርሃት የመብላት ፍላጎቴን ነጥቆኛል።
በሰልፍ መሃል ቦታ ስናገኝ የተኩስ እሩምታ አየሩን ተቆጣጠረው:: ከዚያ ከተኩሱ የሚከብድ ጸጥታ ሆነ።
መቶ አለቃ ለሁሉም ለመታየት ከተደረደረ ጡብ ላይ ወጣ።አጥንት ከሚሰብር ዝምታ በኋላ ወደ ወታደሮቹ እጁን
አመለከተ:: ወታደሮቹ የአንድ ወጣት እና ሌላ ታዳጊ አስክሬን ከፊታችን አስቀመጡ፡፡ የመንደሩ ነዋሪዎች ነበሩ። ልብሳቸው በደም ተጠምቋል አይናቸው እንደተከፈተ ነው፡፡ ሰዎች ፊታቸውን ለማዞር ሲሞክሩ ትንንሽ ልጆች ማልቀስ ጀመሩ።መቶ አለቃው ጉሮሮውን አጥርቶ መናገር ጀመረ፡፡እነዚህን አሰቃቂ አስክሬን በተለይ ልጆች ባሉበት
#ክፍል_ዘጠኝ
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
የሰባት አመት ልጅ እያለሁ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን ለማቅረብ ወደ ከተማ አዳራሽ እሄድ ነበር፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ
አዋቂዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ። ረጂም ጣውላ ወንበር ላይ ተቀምጠው ውይይታቸው ሲያልቅ የሼክስፒር ቃለ ተውኔትን እንዳቀርብ እጠራለሁ። አባቴ ጸጥታ እንዲሰፍን እና
ተውኔቱ እንዲጀምር ደመቅ አርጎ ያነጥሳል። እጁን አጣምሮ ከደማቅ ፈገግታ ጋር ፊት ለፊት ይቀመጥ ነበር። ወንበር ላይ እወጣና ረጂም ዱላ እንደ ሰይፍ በመጠቀም እጀምራለሁ።
ከጅሊየስ ቄሳር “ጓደኞቼ፣ ሮማዊያን፣ የሃገሬ ልጆች እስኪ ጀሮችሁን ስጡኝ፡፡ ብየ እጀምራለሁ። አዋቂዎች የሚወዷቸው
ስለነበሩ ብዙ ጊዜ ማክቤዝ እና ጅሊየስ ቄሳርን ነበር ማቀርበው።የእንግሊዝኛ ቋንቋን የመናገር ችሎታየ የዳበረ እና ጥሩ የሆነ ስለሚመስለኝ በከፍተኛ ጉጉት እና ደስታ ነበር ማቀርበው::
ወታደሮቹ በእኩለ ለሊት ሲገሰግሱ ነቅቼ ነበር። የኮቴቸው ድምጸ በሙሉ መንደሩ አስተጋባ። ቀኑን ሙሉ ጆሮዎየ ላይ
ሲያቃጭልብኝ ዋለ። አስር ወታደሮች ሰፈሩን እንዲጠብቁ ከእኛ ጋር ቀሩ። በየምድብ ቦታቸው ቀኑን ሙሉ ሲጠብቁ ዋሉ። ምሽቱ ፥ሲቃረብ ወታደሮቹ ወደ ሰማይ በመተኮስ እና የመንደሩ ሰዎች
ወደ “ቤት እንዲገቡ” እንዲሸሸጉ በማዘዝ የስዓት እላፊ አወጁ።ያን ምሽት ሙሳ ተረት አላወራም ሞሪባም ከልጆች ጋር ገበጣ አልተጫወተም፡፡ በዝምታ ጀርባችንን ለግድግዳው ሰጠን
ተቀምጠን የተኩስ እሩምታ ሲዘንብ ከርቀት እናዳምጥ ነበር።ለሊቱ እስኪገባደድ የመጨረሻ ስዓት፤ ጨረቃ በጉም መሃል አልፋ ፊቷን በክፍቱ የቤታችን መስኮት እስከምታሳይ እና
በአውራ ዶሮ ጩኅት ለሊቱ እስከሚባረር ድረስ ተኩሱ ቀጠለ።
ፀጠዋት ከፀሐይዋ መውጣት ጋር መመለስ የቻሉ የተወሰኑ ወታደሮች ብቻ ወደ መንደር መጡ። የተወለወለ ኮሬ ጫማቸው በጭቃ ተበላሽቷል። ፈንጠር ፈንጠር ብለው መተማማኛ የመሰላቸውን መሳሪያቸውን አቅፈው ተቀምጠዋል። ብሎኬት ላይ ተቀምጦ የነበረ አንድ ወታደር እጁን በራሱ ላይ ጭኖ
ተርገፈገፈ። ተነስቶ መንደሩን ዙሮ ወደነበረበት ተመለሰ።በተደጋጋሚ እንደዚህ ሲያረግ ቆየ። መቶ አለቃ ጃባቲ ሬዲዮ ላይ መልዕክት ሲያስተላልፍ ከቆየ በኋላ ሬዲዮውን ወረውሮ ወደ ቤቱ ገባ። መንደርተኛው ምንም አላወራም:: ዝም
ብሎ የወረደውን መዓት ታዘበ።
እኩለ ቀን ሲሆን ከሃያ የሚበልጡ ወታደሮች ወደ መንደሯ መጡ። መቶ አለቃ ሲያቸው ማመን አልቻለም ተገረመ ተደሰተ ብዙም ሳይቆይ ቁጥብ ሆነ። ወታደሮቹ ራሳቸዉን እንደገና ካዘጋጁ በኋላ ወደ ጦር ሜዳ ወረዱ። ምንም መደበቅ አላስፈለገም ጦርነቱ ቅርብ ነው። ብዙም ሳይቆይ የተኩስ እሩምታ መስማት ጀመርን። መንደሩን የሚጠብቁት ወታደሮች ወደ ቤት እንድንገባ አዘዙን። ተኩሱ ከወፎችን እና ዶሮዎች ጩኅት ጋር እስከ ምሽት ድረስ ቀጠለ። ለሊት ጥይት ለማምጣት እና ለአጭር ረፍት ጊዜ ወታደሮች እየሮጡ ወደ መንደር መጡ። የቆሰሉ ወታደሮች በፋኑስ የታገዘ ቀላል ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም አብዛኞቹ ይሞታሉ። ወታደሮቹ የሞቱ ጓዶቻቸዉን ወደ መንደር
አያመጡም። ምርኮኛዎችን አሰልፈው ግንባራቸውን በጥይት በመምታት ይገድሉዋቸዋል።
ጦርነቱ ለቀናት ቀጠለ።ወታደሮች ቀስ በቀስ ቁጥራቸው እየቀነሰ ሄደ፡፡ ወታደሮቹ እረፍት አጡ ፤ ኮሽ ካለ የመንደሩ ሰዎች
ላይ ሳይቀር መተኮስ ጀመሩ:: መቶ አለቃዉ የመንደሩን ነዋሪዎች ወደ አደባባይ ወጥተው እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ሰጠ።
“ጫካው ውስጥ ህይወታችንን ሊያጠፉ ዕድላችንን ሊያበላሹ የሚጠብቁ ወታደሮች ተዋግተናቸዋል። በቁጥር ግን ይበልጡናል። መንደሩን በሙሉ ከበው አሉ። ይሄን መንደር እስከሚይዙ ድረስ ተስፋ አልቆርጥም:: የእኛን ምግብ እና መሳሪያ የራሳቸው ማድረግ ይፈልጋሉ።” ብሎ ንግግሩን ገታ አደረገና ቀስ ብሎ እንደገና ቀጠለ። አንዳንዶቻችሁ ከዚህ የምትገኙት ወላጆቻችሁን ቤተሰቦቻችሁን ስለገደሉባችሁ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ አስተማማኝ መጠጊያ መሸሸጊያ ነው ብላችሁ ነው:: እንግዲህ ከዚህ በኋላ
አስተማማኝ አይደለም:: ለዚህ ነው ጠንካራ ወንዶችን ታደጊዎችን የምንፈልገው:: እነዚህን እንድታግዙን የሰፈሩን ሰላም እና ደህንነት እንድንጠብቅ
እንፈልጋለን። መዋጋት ወይም ማገዝ ካልፈለጋችህ ምንም አይደል፡፡ ነገር ግን ቀለብ አይሰፈርላችሁም በመንደሩም መቆየት አትችሉም። መሄድ ትችላላችሁ ከዚህ የምንፈልጋቸው ምግብ
በማብሰል መሳሪያ በማዘጋጀት ጥይት በማቀበል የሚረድን የሚዋጉ ናቸዉ። ለምግብ ማብሰል በቂ ሴቶች አሉ። ስለዚህ ብቁ የሆኑ ታዳጊ ወንዶች እና ወጣቶች ነው እነዚህን አማጺዎች
እንዲዋጉ ምንፈልገው:: አሁን ነው የወላጆቻችሁን ደም የምትመልሱት፤ ሌሎች ልጆችንም ወላጆቻቸውን ከማጣት
ማስቀረት የምትችሉት::” ትንፋሽ ወሰደ። “ ነገ ጠዋት ሁላችሁም ከዚህ ቦታ እንድትሰለፉ ለተለያዩ ስራዎች ሰዎችን
እንመርጣለን።” አደባባዩን ለቆ ሲሄድ ጠባቂዎቹ ተከተሉት።
ለተወሰነ ጊዜ ደርቀን ባለንበት ቁመን ቀረን። ከዛ የስዓት እላፊው ሲቃረብ ወደየ ምኝታ ቦታችን ተበተን። ቤት ውስጥ
ጁማህ፣ አል ሃጂ ሞሪባ፣ ሙሳ እና እኔ ምን ማድረግ እንዳለብን ድምጻችንን ቀንሰን ተወያየን፡፡
“አማጺዎች ከዚህ መንደር የሆነ ማንም ሰው ጠላት ወይም ስላይ ነው ብለው ስለሚገምቱ ሁሉንም ይገድላሉ። ይሄን
ነው ያለው አምሳ አለቃው።” አለ አል ሃጂ የገጠመንን ኣጣብቂኝ ለማስረዳት ሲሞክር። ሌሎቹ ወንዶች ከተጋደሙበት ስጋጃ ተነስተው ውይይቱን ተቀላቀሉ። አል ሃጂ ቀጠለ “የሚሻለው ለጊዜውም ቢሆን ከዚህ መቆየት ነው።” ሌላ ምርጫ
አልነበረንም። መንደሩን ለቆ መሄድ ማለት መሞት ማለት ነው::
“አዳምጡ! ይህ ከመቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው፡፡ ሁላችሁም አሁንኑ ወደ አደባባይ በመውጣት ተሰብሰቡ።” ብሎ በድምጽ ማጉያ ለፈለፈ። ተናግሮ ሳይጨርስ አደባባዩ በሰዎች ሞላ፡፡
ሁሉም ሰው ለደህንነቱ ምን ማድረግ እንዳለበት የሚወስነውን ይህን ጊዜ በጉጉት ይጠብቅ ነበር። ከአዋጁ በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኩሽና ቤቱ ውስጥ ተቀምጬ ነበር። ፊታቸው ባዶ ምንም ስሜት የማይታይበት አይናቸው ግን በሃዘን ገርጥቶ ነበር። አይን ለ አይን ላያቸው ብሞክርም ፊታቸውን አዞሩ። ቁርሴን ለመብላት ብሞክርም ፍርሃት የመብላት ፍላጎቴን ነጥቆኛል።
በሰልፍ መሃል ቦታ ስናገኝ የተኩስ እሩምታ አየሩን ተቆጣጠረው:: ከዚያ ከተኩሱ የሚከብድ ጸጥታ ሆነ።
መቶ አለቃ ለሁሉም ለመታየት ከተደረደረ ጡብ ላይ ወጣ።አጥንት ከሚሰብር ዝምታ በኋላ ወደ ወታደሮቹ እጁን
አመለከተ:: ወታደሮቹ የአንድ ወጣት እና ሌላ ታዳጊ አስክሬን ከፊታችን አስቀመጡ፡፡ የመንደሩ ነዋሪዎች ነበሩ። ልብሳቸው በደም ተጠምቋል አይናቸው እንደተከፈተ ነው፡፡ ሰዎች ፊታቸውን ለማዞር ሲሞክሩ ትንንሽ ልጆች ማልቀስ ጀመሩ።መቶ አለቃው ጉሮሮውን አጥርቶ መናገር ጀመረ፡፡እነዚህን አሰቃቂ አስክሬን በተለይ ልጆች ባሉበት
👍1
ስላሳየኋችሁ ይቅርታ። ነገር ግን ከዚህ ያለነው ሁላችንም ሞትን አይተናል ወይም አፋፍ ላይ ደርሰንም እናውቃለን።” ወደ
አስክሬኖቹ እያመለከተ ይህ ሰው እና ልጁ አደገኛ እንደሆነ ብነግራቸውም በጠዋት ተነስተው ለመሄድ ወስነው ነበር።ሰውየው በዚህ ጦርነት መካፈል እንዳማይፈልግ ነግሮኝ ነበር።
ስለዚህ የፍላጎቱን ያደርግ ዘንድ ተውኩት፤ ለቀቁት። ምን እንደሆነ አሁን ተመልከቱ። አማጺዎች በምንጥሩ ቦታ ሲደርሱ
ተኩሰው ገደሉዋቸው። አሁን የማስያችሁ ያለንበት ሁኔታ እንዲገባችሁ ነው። መቶ አለቃው ለአንድ ስዓት የሚሆን ንግግር
አደረገ። አማጺዎች የፈጸሙዋቸውን ግፉዎች ዘረዘረ። አንገት መቅላት፣ እጅ መቁረጥ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ሙሉ መንደር ነዋሪዎች እያሉ ማቃጠል እያለ ሰዎችን እንዴት እየጎድ እንደሆነ
ለተሰብሳቢዎች ገለጸ።
“ስውነታቸውን አጥተዋል። መኖር የለባቸውም:: ለዚህ ነው አንድ በ አንድ ሁሉንም መግደል ያለብን። ክፉ ነገርን
እንዳጠፋችሁ ቁጠሩት። ለሃገራችሁ ትልቅ ውለታ ዋሉ።” መቶ አለቃው ሽጉጡን አውጥቶ ወደ ሰማይ ሁለት ጊዜ ተኮስ። ሰዎች መጮህ ጀመሩ ሁሉንም ልንገድላቸው ይገባል። በምድር ላይ
ከዚህ በኋላ እንዳይራመዱ ልናደርጋቸው ይገባል።” ሁላችንም አማጺዎችን አምርረን ጠላን ከመቼውም ጊዜ በላይ
መንደራችንን ላለማስደፈር ቆርጠን ተነሳን፡፡ የሁሉም ስው ፊት ላይ ቁጣ ይነበባል፡፡ ከንግግሩ በኋላ የሰፈሩ ስሜት በፍጥነት ተቀይሯል፡፡ እኔ እና ጓደኞቼ ደግሞ ተቆጥተናል ፈርተናልም።
ሁሉም ሴቶች ወደ ምግብ ማብሰል ሲሄዱ ወንዶች ደግሞ ወደ ጦር መጋዝን አመሩ።ወደ ህንጻው ስንቀርብ G3 የታጠቀ ወታደር ከህንጻው ወጥቶ
በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አስክሬኖቹ እያመለከተ ይህ ሰው እና ልጁ አደገኛ እንደሆነ ብነግራቸውም በጠዋት ተነስተው ለመሄድ ወስነው ነበር።ሰውየው በዚህ ጦርነት መካፈል እንዳማይፈልግ ነግሮኝ ነበር።
ስለዚህ የፍላጎቱን ያደርግ ዘንድ ተውኩት፤ ለቀቁት። ምን እንደሆነ አሁን ተመልከቱ። አማጺዎች በምንጥሩ ቦታ ሲደርሱ
ተኩሰው ገደሉዋቸው። አሁን የማስያችሁ ያለንበት ሁኔታ እንዲገባችሁ ነው። መቶ አለቃው ለአንድ ስዓት የሚሆን ንግግር
አደረገ። አማጺዎች የፈጸሙዋቸውን ግፉዎች ዘረዘረ። አንገት መቅላት፣ እጅ መቁረጥ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ሙሉ መንደር ነዋሪዎች እያሉ ማቃጠል እያለ ሰዎችን እንዴት እየጎድ እንደሆነ
ለተሰብሳቢዎች ገለጸ።
“ስውነታቸውን አጥተዋል። መኖር የለባቸውም:: ለዚህ ነው አንድ በ አንድ ሁሉንም መግደል ያለብን። ክፉ ነገርን
እንዳጠፋችሁ ቁጠሩት። ለሃገራችሁ ትልቅ ውለታ ዋሉ።” መቶ አለቃው ሽጉጡን አውጥቶ ወደ ሰማይ ሁለት ጊዜ ተኮስ። ሰዎች መጮህ ጀመሩ ሁሉንም ልንገድላቸው ይገባል። በምድር ላይ
ከዚህ በኋላ እንዳይራመዱ ልናደርጋቸው ይገባል።” ሁላችንም አማጺዎችን አምርረን ጠላን ከመቼውም ጊዜ በላይ
መንደራችንን ላለማስደፈር ቆርጠን ተነሳን፡፡ የሁሉም ስው ፊት ላይ ቁጣ ይነበባል፡፡ ከንግግሩ በኋላ የሰፈሩ ስሜት በፍጥነት ተቀይሯል፡፡ እኔ እና ጓደኞቼ ደግሞ ተቆጥተናል ፈርተናልም።
ሁሉም ሴቶች ወደ ምግብ ማብሰል ሲሄዱ ወንዶች ደግሞ ወደ ጦር መጋዝን አመሩ።ወደ ህንጻው ስንቀርብ G3 የታጠቀ ወታደር ከህንጻው ወጥቶ
በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#መልክአ_ሰዋሰው
መንገድ የሚያበጁ
አቅጣጫ 'ሚያስቱ
ብኩን አመልካቾች ፣
ጎዳና አሳምረው
መኼጃን ያጠፉ
እልፍ ባለጸጎች ፣
ሰዉን ቤት ከልክለው ፤
በድንኳን ያኖሩ ከጎጆ ነጥለው
እንደ ጲላጦስም
እውነትን የሸሹ ፣ እጃቸውን ታጥበው
ፍርድን የሚያዛቡ ፣ ዙፋን ተከልለው።
“ከደሙ ንጹሕ ነኝ. . .
እያሉ በድፍረት ፣ በደም የረጠቡ ፣
ስንቶች ስንት ናቸው . . . ?
ለሞት ጥቀር ወተት! ሕይወት የሚያጠቡ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
መንገድ የሚያበጁ
አቅጣጫ 'ሚያስቱ
ብኩን አመልካቾች ፣
ጎዳና አሳምረው
መኼጃን ያጠፉ
እልፍ ባለጸጎች ፣
ሰዉን ቤት ከልክለው ፤
በድንኳን ያኖሩ ከጎጆ ነጥለው
እንደ ጲላጦስም
እውነትን የሸሹ ፣ እጃቸውን ታጥበው
ፍርድን የሚያዛቡ ፣ ዙፋን ተከልለው።
“ከደሙ ንጹሕ ነኝ. . .
እያሉ በድፍረት ፣ በደም የረጠቡ ፣
ስንቶች ስንት ናቸው . . . ?
ለሞት ጥቀር ወተት! ሕይወት የሚያጠቡ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የዘልማድ_እውነት
ዶፍ ዝናብ ከጣለ . . .
በጠራራ ፀሓይ በቀን እኩሌታ፣
ካ'ገጣጠማቸው . . .
ቍርና ሐሩሩን በልዩነት ዋልታ፣
(ጠርጥር! ትርጉም አለው)
የተፈጥሮ ኹነት ከተዘባረቀ . . .
ትውልድ የሚበላ ሕዝብን አስጨንቆ
ጅብ ልጅ ተወልዶ ነው ! በዘልማድ ረቆ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
ዶፍ ዝናብ ከጣለ . . .
በጠራራ ፀሓይ በቀን እኩሌታ፣
ካ'ገጣጠማቸው . . .
ቍርና ሐሩሩን በልዩነት ዋልታ፣
(ጠርጥር! ትርጉም አለው)
የተፈጥሮ ኹነት ከተዘባረቀ . . .
ትውልድ የሚበላ ሕዝብን አስጨንቆ
ጅብ ልጅ ተወልዶ ነው ! በዘልማድ ረቆ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስር
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
...በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።
አንድ ፊሽካ ባንገቱ ላይ ያንጠለጠለ ነገር ግን መለዮ ያልለበስ ወታደር AK-47 ካለበት ሳጥን በማውጣት አንድ አንድ ለሁላችን አደለን። ወደ እኔ ሲደርስ ቀና ብየ ላየው ስላልቻልኩ ራሴን ቀና
አድርጎ ነበር የሰጠኝ። እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር።
“ሁላችሁም በሁለት ነገሮች ትመሳሰላላችሁ” አለ ወታደሩ።
“ስው ቀና ብላችሁ አይን ለአይን ማየት አትችሉም እና መሳሪያ መያዝ ያስፈራችኋል። ራሳችሁ ላይ የተደቀነ ይመስል ትንቀጠቀጣላችሁ። ይሄ መሳሪያ ከእንግዲህ የናንተ ነው።እንዴት መያዝ እንዳለባችሁ ከአሁኑ ተማሩ። ለዛሬ ይበቃል”አለ ወታደሩ።
ያ ለሊት በድንኳኔ መግቢያ ላይ ለተወሰነ ደቂቃ ቆምኩ።ጓደኞቼ መጠው ያወሩኛል ብየ ስጠብቅ ነበር። ማንም ከድንኳኑ
አልወጣም:: እጄን ራሴ ላይ ጭኜ ተቀመጥኩ። የራስ ምታቴ ያን ምሽት ጠፋ።
ከእኔ ጋር ድንኳን የሚጋሩት ሼኩ እና ጆሲያህ ደወል እስከ ሚደወል ንጋት 12 ስዓት ድረስ ተኝተው ነበር።ለስልጠና
መነሳት ነበረብን። ኑ እንሂድ” ብየ ቀስ አድርጌ ልቀሰቅሳቸው ሞከርኩ። ወደ ሌላ ጎናቸው እየተንከባለሉ ከእንቅልፋቸው ሊነሱ አልቻሉም፡፡ ከዛ ሰሌኑን አንስቼ መትቼ አስነሳሁዋቸው።
አዲስ የወታደር ጫማ፣ ሱሪ እና ዝንጉርጉር ቲሸርት ተስጥቶን ልምምዳችን ጀመርን። ሱሪ ስቀይር ወታደሩ ወደ እኔ
መጥቶ አሮጌውን ሱሪ ወደ እሳት ጨመረው። አሮጌው ሱሪ የራፕ ካሴቴን ይዞ ስለነበር ወደ እሳቱ ሩጬ ላተርፈው ሞከርኩ።ካሴቱ ግን መቃጠል ጀምሯል። አይኔ እንባ አቀረረ።
ወደ ጎን ረድፍ ሰርተን እግራችን ከፍተን እጃችንን አጣምረን መጠበቅ ጀመርን። አንዳንድ ወታደሮች ከጦር ሜዳ ተመልሰው የጦር መሳሪያቸውን አስተካከሉ ጥይቶችን በጎናቸው ባለ
ከረጢት ያዙ። አንዳንዶቹ ልብሳቸው እና ፊታቸው ደም ይታይበታል። ቁርሳቸውን በፍጥነት በልተው ተመለሱ::
ሼኩ እና ጆሲያህ ከእኔ ጎን ነበሩ። አንድ ድንኳን መጋራታችን እንደ ትልቅ ወንድም እንዲሰማኝ አድርጓል። በልምምድ መሃል
እኔን ያያሉ፤ ከአሰልጣኝ በላይ እኔ የማደርገውን ያደርጉ ነበር፡፡አሰልጣኙ ራሱን አስር አለቃ ጋዳፊ ብሎ ነበር ያስተዋወቀን ከመቶ አለቃ ጃባቲ እና ከሃምሳ አለቃው ጋር ሲነጻጸር በእድሜ
ያንሳል፤ ራሰ በራ መሆኑ እና ኮስታራ ፊቱ ግን ትልቅ ሰው ያስመስለዋል ::
መጀመሪያ በህንጻው ዙሪያ ለተወሰነ ደቂቃ ሮጥን። ቀጥሎ በዱር ውስጥ አድብቶ መግባት ተማርን። ዛፎ ላይ መውጣት መውረድ፣ ድምጸ ሳናሰማ መንቀሳቀስ እና ተመልሶ ወደ ነበሩበት
ሩጦ መመለስ በተደጋጋሚ ሰራን። አስር አለቃ ጋዳፊ ብዙ አይናገርም:: “መጥፎ አይደለም”፣ “መጥፎ” እና “ፍጥነት” ብቻ
ይል ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ በምልክት ይጠቀማል። ወደ ጫካው ከገባን
በእጃችን እንቅስቃሴ መግባባት እንዳለብን ነገረን። “ቃላት ተናገራችህ ማለት ግንባራችሁን ለጥይት አሳልፋችሁ ሰጣችሁ ማለት ነው” ይላል፡፡ በስልጠና መሃከል ቁርስ እንድንበላ አንድ ደቂቃ ብቻ ይሰጠናል። በመጀመሪያ ቀን ብዙ ሳንበላ ነበር ምግቡ የተነሳው። ከሳምንት በኋላፀ በፍጥነት መብላት ለመድን።
ከስዓት AK-47 ያደለንን አስር አለቃ ፊት ለፊት ገጥመን ተሰለፍን። የእኔ ተራ ሲደርስ አፍጥጦ አየኝ እና ከእንጨት ሳጥን ውስጥ መሳሪያ አውጥቶ ደረቴ ላይ አስታቀፈኝ፡፡ መሳሪያየን
ይዥ ወደ ሰልፉ ተመለስኩ፡፡ እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር፡፡ በእጆቼ
ይዤው እንኳ ላየው ፈራሁ። እኔ ማውቀው በቅርቅሃ ሚስራ የአሻንጉሊት ሽጉጥ ነበር። እኔ እና ጓደኞቼ ከቅርቅሃ ሰርተን በቡና ማሳ ወይም በግንባታ ላይ ባሉ ቤቶች መሃል እንጫወት ነበር። አሁን የዕቃ ዕቃ ጨዋታ አይደለም የእውነት AK-47 ይዘናል። ለጊዜው ያለ ጥይት መሳሪያውን ይዘን መሮጥ መንከባለል ተማርን። ቀጥሎ ወደ ሙዝ ማሳ በመውረድ ሙዙን በሰንጢ መውጋት ጀመርን፡፡ “ሙዙን እንደ ጠላት ተመልከቱት።ወላጃችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን እንደገደሉት አማጺዎች” አስር አለቃ ጮኸ። “ቤተሰቦቻችሁን የገደለን ሰው እንደዚህ ነው ምትወጉት?” እንደዚህ ነው ብሎ እየጮኸ መውጋት ጀመረ።
መጀመሪያ ሆዱን፣ ከዛ አንገቱ ላይ፣ ልቡን” እያለ ቀጠለ። እኛም በንዴት ስሜት ሙዙን መውጋት ቀጠልን:: ምሽት ላይ አልሞ መተኮስ ሰለጠን። ሼኩ እና ጆሲያህ መሳሪያቸውን ለማንሳት
አቅም አልነበራቸውም:: አስር አለቃ ከፍ ያለ ኩርሲ ነገር ሰጣቸው እና ልምምዳቸውን ቀጠሉ። በመጨረሻ መሳሪያ ፈቶ መጠገን እንደይዝጉ ዘይት መቀባት ተማርን፡፡ ያ ምሽት ሁላችንም ደክሞን ስለነበር በቀጥታ ወደ ምኝታችን አመራን።
ሼኩ እና ጆሊያህ ቀን የሰሙትን “አንድ ሁለት” “ፓው ፓው ቡም” ድምጾች በእንቅልፍ ልባቸው ይሉ ነበር።
እሁድ ጠዋት ነበር አስር አለቃ ያን ቀን ስልጠና እንደሌለ እና እንድናርፍ ሲነገረን፡፡ “ሃይማኖተኛ ከሆናችሁ ማለት
ክርስቲያን ከሆናችሁ ዛሬ አምላካችሁን የማምለኪያ ቀን ይሁናችሁ ፤ ምን አልባት ሌላ ጊዜ ላይኖራችሁ ይችላል። ሂዱ”
የወታደር ልብሳችንን እንደለበስን ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣን። ኳስ መጫወት ስንጀምር መቶ አለቃ ከቤቱ ደጃፍ ወጥቶ
ሊቀመጠ ነበር። ጨዋታውን አቁመን ለመቶ አለቃ ሰላምታ ሰጠን። “ጨዋታችሁን ቀጥሉ። አሁን የምፈልገው ወታደሮቹ ኳስ ሲጫወቱ ማየት ነው።” ብሎ ባርጩሜ ላይ ተቀመጦ
ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ን ማንበቡን ቀጠለ ::
ኳስ ጨዋታው ሲበቃን፤ ለመዋኘት ወሰን እና ወደ ወንዝ ወረድን። ፀሐይማ ቀን ነበር፡፡ ወደ ወንዝ ስንወርድ ሰዉነታችን
ላይ የነበረው ላብ እየደረቀ ነበር። ለተወሰኑ ደቂቃዎች ከተንቦጫረቅን በኋላ በሁለት ቡደን ተከፍለን መወዳደር
ጀመርን።
እንሂድ ጓዶች: በዓሉ አብቅቷል።” ብሎ አስር አለቃ ከወንዙ ዳር ሁኖ ጮኸ። ጨዋታውን አቁመን አሱን ተከትለን
ወደ መንደራችን ሄድን።
መንደር እንደደረስን መሳሪያችንን እንድጠግን ትዕዛዝ ተሰጠን። መሳሪያችንን እያጸዳን የወገብ እና የጀርብ ቦርሳ ተሰጠን። ጥይቶችንን የፈለግነውን ያህል እንድንወስድ ተነገረን።
መሸከም ከምንችለው በላይ ከሆነ በፍጥነት መሮጥ እንደማንችል
ነገረን። ከአል ሃጂ እና ከእኔ በስተቀር ሌሎች ደስተኛ ነበሩ።ፀተጨማሪ ልምምድ የሚሄድ ነበር የመሰላቸው። አል ሃጂ መሳርያውን አጥብቆ ያዘ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ክፍል_አስር
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
...በር ላይ ቆመ። ፈገግ ብሎ መሳሪያውን ካነሳ በኋላ ወደ ስማይ ብዙ ተኮሰ። መሬት ላይ ወደቅን። ስቆ ወደ ውስጥ ገባ። ተነስተን ወደ ህንጻው ገባን። ሀምሳ አለቃው በቤቱ ጀርባ ወዳለ ክፍል
መራን። ወደ ሰላሳ የሚጠጉ ታዳጊዎች ነበሩ።
አንድ ፊሽካ ባንገቱ ላይ ያንጠለጠለ ነገር ግን መለዮ ያልለበስ ወታደር AK-47 ካለበት ሳጥን በማውጣት አንድ አንድ ለሁላችን አደለን። ወደ እኔ ሲደርስ ቀና ብየ ላየው ስላልቻልኩ ራሴን ቀና
አድርጎ ነበር የሰጠኝ። እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር።
“ሁላችሁም በሁለት ነገሮች ትመሳሰላላችሁ” አለ ወታደሩ።
“ስው ቀና ብላችሁ አይን ለአይን ማየት አትችሉም እና መሳሪያ መያዝ ያስፈራችኋል። ራሳችሁ ላይ የተደቀነ ይመስል ትንቀጠቀጣላችሁ። ይሄ መሳሪያ ከእንግዲህ የናንተ ነው።እንዴት መያዝ እንዳለባችሁ ከአሁኑ ተማሩ። ለዛሬ ይበቃል”አለ ወታደሩ።
ያ ለሊት በድንኳኔ መግቢያ ላይ ለተወሰነ ደቂቃ ቆምኩ።ጓደኞቼ መጠው ያወሩኛል ብየ ስጠብቅ ነበር። ማንም ከድንኳኑ
አልወጣም:: እጄን ራሴ ላይ ጭኜ ተቀመጥኩ። የራስ ምታቴ ያን ምሽት ጠፋ።
ከእኔ ጋር ድንኳን የሚጋሩት ሼኩ እና ጆሲያህ ደወል እስከ ሚደወል ንጋት 12 ስዓት ድረስ ተኝተው ነበር።ለስልጠና
መነሳት ነበረብን። ኑ እንሂድ” ብየ ቀስ አድርጌ ልቀሰቅሳቸው ሞከርኩ። ወደ ሌላ ጎናቸው እየተንከባለሉ ከእንቅልፋቸው ሊነሱ አልቻሉም፡፡ ከዛ ሰሌኑን አንስቼ መትቼ አስነሳሁዋቸው።
አዲስ የወታደር ጫማ፣ ሱሪ እና ዝንጉርጉር ቲሸርት ተስጥቶን ልምምዳችን ጀመርን። ሱሪ ስቀይር ወታደሩ ወደ እኔ
መጥቶ አሮጌውን ሱሪ ወደ እሳት ጨመረው። አሮጌው ሱሪ የራፕ ካሴቴን ይዞ ስለነበር ወደ እሳቱ ሩጬ ላተርፈው ሞከርኩ።ካሴቱ ግን መቃጠል ጀምሯል። አይኔ እንባ አቀረረ።
ወደ ጎን ረድፍ ሰርተን እግራችን ከፍተን እጃችንን አጣምረን መጠበቅ ጀመርን። አንዳንድ ወታደሮች ከጦር ሜዳ ተመልሰው የጦር መሳሪያቸውን አስተካከሉ ጥይቶችን በጎናቸው ባለ
ከረጢት ያዙ። አንዳንዶቹ ልብሳቸው እና ፊታቸው ደም ይታይበታል። ቁርሳቸውን በፍጥነት በልተው ተመለሱ::
ሼኩ እና ጆሲያህ ከእኔ ጎን ነበሩ። አንድ ድንኳን መጋራታችን እንደ ትልቅ ወንድም እንዲሰማኝ አድርጓል። በልምምድ መሃል
እኔን ያያሉ፤ ከአሰልጣኝ በላይ እኔ የማደርገውን ያደርጉ ነበር፡፡አሰልጣኙ ራሱን አስር አለቃ ጋዳፊ ብሎ ነበር ያስተዋወቀን ከመቶ አለቃ ጃባቲ እና ከሃምሳ አለቃው ጋር ሲነጻጸር በእድሜ
ያንሳል፤ ራሰ በራ መሆኑ እና ኮስታራ ፊቱ ግን ትልቅ ሰው ያስመስለዋል ::
መጀመሪያ በህንጻው ዙሪያ ለተወሰነ ደቂቃ ሮጥን። ቀጥሎ በዱር ውስጥ አድብቶ መግባት ተማርን። ዛፎ ላይ መውጣት መውረድ፣ ድምጸ ሳናሰማ መንቀሳቀስ እና ተመልሶ ወደ ነበሩበት
ሩጦ መመለስ በተደጋጋሚ ሰራን። አስር አለቃ ጋዳፊ ብዙ አይናገርም:: “መጥፎ አይደለም”፣ “መጥፎ” እና “ፍጥነት” ብቻ
ይል ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ በምልክት ይጠቀማል። ወደ ጫካው ከገባን
በእጃችን እንቅስቃሴ መግባባት እንዳለብን ነገረን። “ቃላት ተናገራችህ ማለት ግንባራችሁን ለጥይት አሳልፋችሁ ሰጣችሁ ማለት ነው” ይላል፡፡ በስልጠና መሃከል ቁርስ እንድንበላ አንድ ደቂቃ ብቻ ይሰጠናል። በመጀመሪያ ቀን ብዙ ሳንበላ ነበር ምግቡ የተነሳው። ከሳምንት በኋላፀ በፍጥነት መብላት ለመድን።
ከስዓት AK-47 ያደለንን አስር አለቃ ፊት ለፊት ገጥመን ተሰለፍን። የእኔ ተራ ሲደርስ አፍጥጦ አየኝ እና ከእንጨት ሳጥን ውስጥ መሳሪያ አውጥቶ ደረቴ ላይ አስታቀፈኝ፡፡ መሳሪያየን
ይዥ ወደ ሰልፉ ተመለስኩ፡፡ እጆቼ ይንቀጠቀጡ ነበር፡፡ በእጆቼ
ይዤው እንኳ ላየው ፈራሁ። እኔ ማውቀው በቅርቅሃ ሚስራ የአሻንጉሊት ሽጉጥ ነበር። እኔ እና ጓደኞቼ ከቅርቅሃ ሰርተን በቡና ማሳ ወይም በግንባታ ላይ ባሉ ቤቶች መሃል እንጫወት ነበር። አሁን የዕቃ ዕቃ ጨዋታ አይደለም የእውነት AK-47 ይዘናል። ለጊዜው ያለ ጥይት መሳሪያውን ይዘን መሮጥ መንከባለል ተማርን። ቀጥሎ ወደ ሙዝ ማሳ በመውረድ ሙዙን በሰንጢ መውጋት ጀመርን፡፡ “ሙዙን እንደ ጠላት ተመልከቱት።ወላጃችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን እንደገደሉት አማጺዎች” አስር አለቃ ጮኸ። “ቤተሰቦቻችሁን የገደለን ሰው እንደዚህ ነው ምትወጉት?” እንደዚህ ነው ብሎ እየጮኸ መውጋት ጀመረ።
መጀመሪያ ሆዱን፣ ከዛ አንገቱ ላይ፣ ልቡን” እያለ ቀጠለ። እኛም በንዴት ስሜት ሙዙን መውጋት ቀጠልን:: ምሽት ላይ አልሞ መተኮስ ሰለጠን። ሼኩ እና ጆሲያህ መሳሪያቸውን ለማንሳት
አቅም አልነበራቸውም:: አስር አለቃ ከፍ ያለ ኩርሲ ነገር ሰጣቸው እና ልምምዳቸውን ቀጠሉ። በመጨረሻ መሳሪያ ፈቶ መጠገን እንደይዝጉ ዘይት መቀባት ተማርን፡፡ ያ ምሽት ሁላችንም ደክሞን ስለነበር በቀጥታ ወደ ምኝታችን አመራን።
ሼኩ እና ጆሊያህ ቀን የሰሙትን “አንድ ሁለት” “ፓው ፓው ቡም” ድምጾች በእንቅልፍ ልባቸው ይሉ ነበር።
እሁድ ጠዋት ነበር አስር አለቃ ያን ቀን ስልጠና እንደሌለ እና እንድናርፍ ሲነገረን፡፡ “ሃይማኖተኛ ከሆናችሁ ማለት
ክርስቲያን ከሆናችሁ ዛሬ አምላካችሁን የማምለኪያ ቀን ይሁናችሁ ፤ ምን አልባት ሌላ ጊዜ ላይኖራችሁ ይችላል። ሂዱ”
የወታደር ልብሳችንን እንደለበስን ወደ መንደሩ አደባባይ ወጣን። ኳስ መጫወት ስንጀምር መቶ አለቃ ከቤቱ ደጃፍ ወጥቶ
ሊቀመጠ ነበር። ጨዋታውን አቁመን ለመቶ አለቃ ሰላምታ ሰጠን። “ጨዋታችሁን ቀጥሉ። አሁን የምፈልገው ወታደሮቹ ኳስ ሲጫወቱ ማየት ነው።” ብሎ ባርጩሜ ላይ ተቀመጦ
ጅሊየስ ሲዘር (ቄሳር) ን ማንበቡን ቀጠለ ::
ኳስ ጨዋታው ሲበቃን፤ ለመዋኘት ወሰን እና ወደ ወንዝ ወረድን። ፀሐይማ ቀን ነበር፡፡ ወደ ወንዝ ስንወርድ ሰዉነታችን
ላይ የነበረው ላብ እየደረቀ ነበር። ለተወሰኑ ደቂቃዎች ከተንቦጫረቅን በኋላ በሁለት ቡደን ተከፍለን መወዳደር
ጀመርን።
እንሂድ ጓዶች: በዓሉ አብቅቷል።” ብሎ አስር አለቃ ከወንዙ ዳር ሁኖ ጮኸ። ጨዋታውን አቁመን አሱን ተከትለን
ወደ መንደራችን ሄድን።
መንደር እንደደረስን መሳሪያችንን እንድጠግን ትዕዛዝ ተሰጠን። መሳሪያችንን እያጸዳን የወገብ እና የጀርብ ቦርሳ ተሰጠን። ጥይቶችንን የፈለግነውን ያህል እንድንወስድ ተነገረን።
መሸከም ከምንችለው በላይ ከሆነ በፍጥነት መሮጥ እንደማንችል
ነገረን። ከአል ሃጂ እና ከእኔ በስተቀር ሌሎች ደስተኛ ነበሩ።ፀተጨማሪ ልምምድ የሚሄድ ነበር የመሰላቸው። አል ሃጂ መሳርያውን አጥብቆ ያዘ።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ