አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#በድን_ላይነሳ

ሞኝ ነው ተላላ
ሰው ተብየው ፍጥረት
ጥብቅና የሚቆም
በ'ጁ አጥፍቶ ህይወት
እፅዋት ጨፍጭፎ
አምርቶ ወረቀት
ከመጥረቢያ በደለደመው
በብዕሩ ስለት
ቀለማት አጣቅሶ
ሙቱን አንተርሶ
ህግ ደነገጎ
መመሪያም አወጣ
በድኑ ላይነሳ
ዳግመኛ ላይመጣ፡፡

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍1
#ሽፍታው_አዕምሮአችን

በበርሃ ተጓዥ
ሽፍታው አዕምሮአቸን
ስንቅና ትጥቅ ይዞ
ምስኪኑን ገላችን
ደምን ከስጋ ጋ
በልቶ የሚፋፋ
አጥንት ምርኩዝ ሆኖት
የሚጓዝ በተስፋ
ነቀዝ ነው አምሳያው
ጠቅላላው ተፈጥሮ
አመንምኖ የሚያስቀር
አካልን ሽርሽሮ፡፡

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ስድስት


#በጥላሁን

በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን
"አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ!"
ታድያ ሀኪም ቤት አልወሰዳችሁትም ?
"ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ!"
እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል።
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
ገና ብቅ ስል ያየችኝ ሊሊ እየተርገበገበች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ብዙ ሰው አይመጣም ብላኝ አልነበር እንዴ እያልኩ በሀሳብ ቢዥታ ውስጥ ሆኜ እኔም አቀፍኳት የሷስ ይሁን ከታዳሚው ተገንጥለው አብረዋት የነበሩ አራት ጓደኛቿ በየተራ "ሰላም ነህ?" ቅብርጥሶ እያሉ በጉንጮቻቸው ጉንጬን ደበደቡት "አትሳሳሙ" የሚለው ማስታወቂያ ትዝ አለኝ ወደ ቤት ከመጣሁና ባባዬ ቁጥጥር ስር ከዋልኩ ወድሂ የመጀሚሪያውን የአትሳሳሙ ህግ ለመጀመሪያ ግዜ ጣስኩ።

በተለይ መጨረሻ ላይ የሳመችኝ የምግብ ብዛት እና አይነቱ እየዘጋት እህል በልታ የማታውቅ የምትመስለው ቅጭጭ ያለች ቀጫጫ ልጅ የፀጉር አሰራራ ነው መሰለኝ እሱን እንድትመስለኝ ያደረገኝ ብቻ የጉንጫ አጥንት ጉንጬን ሲወጋው እራሱ ኮረና ዛሬ አታመልጠኝም አገኘሁህ ያለኝ ነው የመሰለኝ።

ኪሴ ውስጥ ያለችውን በትንሽ ብልቃጥ የያዝኳትን ሳኒታይዘር አውጥቼ እጄን ሳይሆን ፊቴን ልታጠብበት ፈለኩ። ለካ ለእጅ እንጂ ለፊት አይሆንም። ቢሆን ኖሮስ ቤት በኩል ልታጠብ
እንኳን ለመታጠቢያ ለመተንፈሻም ግዜ ሳይሰጡኝ
ሊሊ እና ጓደኞቿ መሀላቸው አስገብተው እያዋከቡ እቤት ውስጥ ወዳሉት ታዳሚዎች መሀል ወሰዱኝ።
እነዛ እቤታቸው ግርግዳ ላይ አንዲት በረሮ ቢያዩ እርርርይ እያሉ ቤቱን ጥለው የሚጠፉ የሀብታም ልጆች ኮሮናን አይፈሩትም ብቻ ሳይሆን ትዝም አይላቸውም ማለት ነው ብዬ እራሴን ጠየኩ ሌላ ማንን እጠይቃለሁ ብጠይቅስ ማን ይመልስልኛል?።

ሁሉንም ሳያቸው ሀገራችንን ጨምሮ በአለም ዙርያ ስለዚህ በሽታ በሚድያ የሚለፈፈውን የሚስበው የኛ ቴሌቭዥን እና ዲሽ ብቻ ነው እንዴ አልኩ።የሚያዳምጠውም የሚያየውም አባዬ ብቻ መስሎ ተሰማኝ።
ጭራሽ ሊሊዬን ሞቀኝ ወደ በሩ አከባቢ ብንሆንስ ብዬ ስጠይቃት የሰመችው ያቺ ኮሮና ስጋ ለብሶ መስላ የታየችኝ ቀጭኗ ልጅ ያጋመሰችውን ቢራ ወደ አፌ እያስጠጋች •••
"እንካ ጎንጨት በልበትና ሞቅ ይበልህ ሞቅ ሲልህ የቤቱ ሙቀት አይታወቅህም ክክክክክክ" አለች። ተከትለዋት ሁሉም ሳቁ ። እኔ እንኳን የምስቅበት የማገጥበትም ጥርስ አልነበረኝም።
አመሰግናለሁ ግን አልጠጣም ብዬ ቢራዋን ከነጇ ከአፌ አከበቢ ገፋ አደረኩት።

ጓደኛዬንና ፍቅረኛውን ከሩቅ አየኋቸው እራሳቸውን አያውቁም በራሳቸው አለም ርቀው ሄደዋል ሊሊዮዬን ጠጋ አልኩና በድጋሚ •••
ስገባ አጎትሽን አየሁት ልበል? አሞታል እንዴ ሊሊዬ? ለምን አልነገርሽኝም እንዳስተዋወቅሽኝ ረስተሽው ነው። መጥቼ እጠይቀው ነበርኮ ።
ዘንድሮ በሽትኛ መጠየቅ ቀርቷል እኮ አልሰማህም እንዴ ኧረ በክህ በልደቷ ቀን ጓደኛዬን ስለበሽታ ስለጥየቃ ምናምን ማውራቱን ተውና ዘና በል " አለችኝ። አሁንም ያችው ልጅ። ወይ ጣጣ ልጅቷ ሊሊ በፊርማዋ አረጋግጣ ውክልና የሰጠቻት ነው እምትመስለው ገና ሊሊን ማናገር ስጀምር ወሬዬን ሳልጨርስ እሷ መልስ እየሰጠች አላስወራ አለችኝ።
ከዛ ቡሀላ አንዳች የሚገላግል ነገር ከዛች ልጅ ካልገላገለኝ በቀር ላለማውራት ወሰንኩ።

ሊሊዬ ከዛም ከዛም እየጠሯት ውክብክብ ስላለች ፍቴን ማየትና መረዳት እንኳን አልቻለችም ነበር።ሁለተኛውን ህግ ጥሻለሁ ርቀቴን ሳልጠብቅ በብዙ የሊሊ ልደት ተጋባዦች መሀል ሆኜ ድንገት ወጥመድ ውስጥ ገብታ መውጫ እንዳጣች ጦጣ ግራ ተጋብቼ ግራ እና ቀኝ ስቁለጨለጭ ቆየሁና በሚጠጡ ፣በሚደንሱ፣ በሚሳሳሙ፣ በሚተሸሹ ሰዎች መሀል ሆኖ በተጨነቀ ፊት መቆየት ከባድ ሆነብኝ።
ይለይለት ብዬ ይሁን ይለይልኝ ብቻ ከቢራውም ከውስኪውም ከወይኑም ቀላቅዬ ስጠጣ ፍርሀት እና ደስታ የተቀላቀለበት ስካር ሰከርኩ።
መጠጡ በላይ በላይ ሲመጣ ፍርሀቱ ጠፍቶ ጊዛዊው ጀግንነት መጣ ድፍረቴ ጨቅ አለ።
ባንድ ግዜ እንደማያ ተለዋውጬላችሁ ቁጭ አልኩ።ኧረ የምናባቱ ኮሮና ሺ አመት አይኖር ሙዚቃውን ከፍ አድርገው ዲጄው ምንድን ነው ለቅሶ ቤት አስመሰለው እኮ ሊሊዬ ዲጄውን ከሰልስት ላይ ነው እንዴ አስነስታችሁ ያመጣችሁት ኬኬኬኬኬኬኬኬ"
እሷም ተከትላኝ
" ኪኪኪኪኪኪኪኪ እሄንን ሶል ነው ስፈልገው የነበረው!" ሊሊም ጓደኞቻም ሳቁ።
ቤቱ አልበቃ አለኝ ከላይ የለበስኩትን ጃኬት አውልቄ ጣልኩት።
ተቀላቀልኩ ፣ ጨፈርኩ ፣ዘለልኩ፣ እየተቀባበልኩ ጠጣሁ፣ ከሊሊዬ ጋር በየደቂቃው መሳሳም፣ መደነስ እስኪደክመን ከጓደኛቿም ጋር ተራ በተራ ጨፈርን አበድን ፣ ከነፍን በረርን ፣
እነሱ የረሱትን ሁሉ ረሳሁ። እነሱ የናቁትን ሁሉ ናቅሁ! እነሱ የሆንኩትን ሁሉ ሆንኩ።
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ?

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1👏1
#ዝማሬ

በሽንቁር ሰማይ ሥር፣ በስንጥቅ ምጣድ ላይ
ባ'ንድ ላይ ጠልቆባት፣ ጀንበር እና ሲሳይ
ምድጃው ሥር ኾና፣ ስትተክዝ ነፍሴ
ራት ኾኖ መጣ፣ የመሸበት ቁርሴ፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ፈረቃ

ሞት እና ሰውነት ሁሌም ይነቃሉ
ነፍስ እና ነፋስ ግን ወቅት ይጠብቃሉ፡፡
ሁሌ ሕያው መኾን አከተመ በቃ
የኛ ሕያውነት ኾኗል በፈረቃ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ግዞት

እፍኝ ተበድሮ ነፍሱን ሊያድናት
ባርያ ሆኖ ሞተ ያባቴ አባት
እዳው ተጭኖት
ባርነት ሲመረው ሲያቅት ለግዞት
የጭሰኛ ክብር ሰጡት ለኔ አባት
አርሶ፣ ዘርቶ፣ አጭዶ ጭሰኛው አባቴ
ምርቱን ሲገብረው ለመሬት ከበርቴ
መሬት ለአራሹ ” መፈክር አንስቼ

ታግዬ አሸነፍኩ ከጫካ ገብቼ
ወገኖቼ ሁሉ ቀድመው የተገፉት
በኔ በልጃቸው አሁን ገና አረፉት
ብዬ በተስፋ ስንቅ ቃላት ስደረድር
አንደበት ሳደድር
ከኔም ለካ አልጠፋም የጭቆናው ቀንበር
ካ'ብታም ግዞት ስር ነኝ ተብዬ “ወዝ አደር”
መደብ ከታች እላይ ጎባጣው ሳይቀና
ነጻነት ከቃላት መቼስ አልፎ ያቅና፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#በኔ_የደረሰ


#ክፍል_ሰባት (የመጨረሻው ክፍል)


#በጥላሁን

ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።

ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።

ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ••••
እምለው እማረገው ሁሉ ጨነቀኝ ቀና ብዬ እዛው አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩና ሁለቱን እጄቼን ወደ ፊት ዘርግቼ እያየኋቸው •••
ማታ እንዳልተለከፍኩ በምን እርግጠኛ ነኝ እራሴን ጠየኩት?
በምንም ደሞ ጉሮሮህ አከባቢ ህመም እየተሰማህ ነው ይዞህ ይሆን እንዴ ? አለኝ ውስጤ
ጉሮሮዬ እንኳን ማታ ብዙ አይነት መጠጥ እየቀላቀልኩ ስለጠጣሁ ሊሆን ይችላል ያመመኝ ።

ላይሆንም ይችላል በሽታውም አንዱ ምልክቱ እንደዛ ነው?
እስቲ አስበው በዚህ እጅህ ስንቱን ነገር ነክተሀል፣ ከስንቱ ጋር ተጎራርሰህ በልተሀል ፣ከስንቱ ጋር እየተቀባበልክ ጠጥተሀል ፣ ስንቱ የተቀባበለውን ቢራ መክፈቻ ተጠቅመሀል
ውስጤ ሌላ ሰው ተቀምጦ የሚያስፈራራኝ መሰለኝ በሁለት ሀሳብ ተከፍዬ ከራሴ ጋር ስከራከር እራሴን አመመኝ።
አንድ ሰው የማንፈልገውን ወይም የሚረብሸንን ወሬ ቢያወራብን ዝም እንዲል አልያም ወሬ እንዲቀይር እንነግረዋለን ካልሆነ ካጠገቡ ተነስተን እንሄዳለን ከሚድያ ላይ የሚወራውን መስማት ካልፈለግን ተነስተን እንጠረቅመዋለን።
ከደጅ የሚመጣን ጩኸት መስማት ካልፈለግን ጆሮአችንን እንይዛለን
ከውስጣችን የሚመጣውን ጩከት መስማት ባንፈልግ ምናችንን እንይዘዋለን ወዴትስ እንሸሻለን?
እማዬ ድጋሚ የክፍሌን በር አንኳኩታ "ኧረ አባትህ እየጠበቀህ ነው ሰለሞኔ ቁርስ ቀርቧል እኮ!" አለችኝ።
ወጥቼ ሻወር ቤት ገባሁና ከሰዉነቴ ክፍሎች ሁሉ እጄን ደጋግሜ ታጠብኩት።
"ውስጥህንስ በምን ታጥበዋለህ ይዞህ ከሆነ በትንፋሽም እኮ ይተላለፋል አለኝ ከበሽታው በላይ ውጋት የሆነብኝ የውጤ ሀሳብ ነው።

እናባዬ ወዳሉበት ሳሎን ገባሁ ። ግን ሳልጠገቸው ፈንጠር ብዬ ብቻዬን ተቀመጥኩ።
"ዛሬ ምን ሆኗል ልጄ ና እንጂ ቁርስ እንብላ አንተን አይደለም እንዴ የምንጠብቀው" አለ አባዬ።
አይ አይሆንም አባ ካሁን ቡሀላ እሄ ክፉ በሽታ ከሀገራችን ተጠራርጎ እስኪወጣ ምግብም ቢሆን አብረን ለመብላት ስንል መቀራረብ የለብንም ። ለብቻዬ ብታቀርብልኝ ይሻላል አይሻልም አባ? ስል•••
እማ ጣልቃ ገብታ " አበስኩ ገበርኩ የደጁን ይሁን ስል ልጆቼንም ከጉያዬ ሊያርቅብኝ ነው እሄ በሽታ ከመች ወዲህ ነው ልጄ መአድ ተነጣጥለን በልተን የምናውቀው መአድ በአንድ ላይ ቀርቦ መብላት ፍቅርን ያደረጃል ልጄ።
ደሞ በኛ መሀል ኬት ይመጣል ከቤት ወጥተን አናውቅ የምንፈልገውን እቃ እንኳን የባታችሁ ወንድም ነው ገዝቶ የሚያመጣልን እቃ ገዝቶ መጥቶ እንኳን በር ላይ አስቀምጠህ ሂድ እንጂ ግባ ብሎት አያውቅ አባታችሁ።
ዛሬ ድንገት ተነስተህ ለብቻዬ አቅርቡልኝ ማለቱን ምን አመጣው ጥሩ ህልም አላየህም ልጄ እስቲ ንገረኝ?" ብላ ዝም ብዬ ሳያት እኔን ትታ ወደአባዬ ፍቷን መለሰችና
"፣እሄው ልጆቼን የፀሀይ ብርሀን እስኪናፍቃቸው ድረስ አላላውስ ብለህ ተጭነህ ስታስጨንቃቸው በጭንቀት ብዛት የልጄን አይምሮ እንዲቃወስ አድርገከው አረፍክ " ብላ ስታፈጥበት
ደና ነኝ እማዬ ምንም የሆንኩት ነገር የለም አባንም እንደዛ ማለት የለብሽም አባ ልክ ነው ። በቃ ተራራቁ ተብሏል እንራራቅ ነው ያልኩት ቀለል አርጋችሁ እዩትና እሺ በሉኝ እናንተ አንድ ላይ ብሉ ለኔ ለብቻዬ ስጪኝ። ስል እህቴ ከነበረችበት ተነስታ •••
"ባክህ የሌለ ነገር እያወራህ አታጨናንቃቸው ተነስና እንብላ!" እያለች እጄን ይዛ ልትጎትተኝ ነው መሰለኝ ወደኔ ስትጠጋ
ከተቀመጥኩበት ተፈናጥሬ በመነሳት እንዳትጠጊኝ እህቴ ነግሬሻለሁ እንዳትጠጊኝ በቃ ስል አባም ግራ ተጋብቶ ተነስቶ ሲቆም
ተጠግቶ ሳይዘኝ ቤቱን ጥየላቸው ብን ብዬ ልጠፋ አሰብኩና እናቴ ልጄ አበደ ብላ እራሷን ከማጥፋት እንደማትመለስ ሳስበው ፈራሁ።
አንተም እንዳትጠጋኝ አባ በቃ ተረዱኝ አትጠጉኝ አልኩ አትጠጉኝ እያልኩ ወደ ክፍሌ በመግባት ከውስጥ ዘጋሁት።
በስንት ውዝግብ አሳምኛቸው ምግብ መስኮት ላይ እየተደረገልኝ በልቼ አጥቤ እየመለስኩ ስምንት ቀን ሆነኝ ። በዘጠነኛው ቀን ጥዋት ጋደኛዬ ደውሎ
የነ ሊሊ ቤተሰቦች በሽተኛ እቤት ውስጥ መኖሩ ተጠቁሞባቸው ቤተሰቡን በሙሉ አፋፍሰው ካስገባቸው ቡሀላ በምርመራ ሌሎቹ የቤተሰብ አባላት ላይም ስለተገኘ ያን ቀን የሊሊ ልደት ላይ የተገኙት በሙሉ እየታደኑ ወደማቆያ እየተወሰዱ ነው አሉ እኛ ጋም መምጣታቸው አይቀርም አልቆልናል ሶል!"
ሲለኝ እኔ እዛው በተኛሁበት አለቀልኝ ። የተኛሁበት በላብ ሲዘፈቅ ትዝ ይለኛል ካልጋዬ ላይ መነሳት አቃተኝ ካንድ ቀን ቡሀላ ብንን ስል መስኮት ላይ ያስቀመጡትን ምግብ ወስጄ አለመብላቴ ያስጨነቃቸው ቤተሰቦቼ እህቴን በመስኮት አዘልለው በማስገባትና ከውስጥ እንድትከፍት በማረግ አልጋዬ ላይ ዙሪያዬን ከበውኝ እስክነቃ በጭንቀት ሲጠባበቁ ተመለከትኩ ። በሂወቴ እንደዛች ቅፅበት መሪር ሀዘን እና የነብሰ ገዳይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ። እርርይ አልኩ።
በንጋታው ሁላችንንም ወደ ማቆያ ወሰዱን ከቀናት ቡሀላ የምርመራ ውጤቱ ሁላችንም እንዳለብን አመለከተ።
ውጤቱን ስሰማ በተለይ ቤተሰቦቼን በመሉ ማስያዜን ስሰማ ድጋሚ እራሴን ሳትኩ ከሳምንታት ቡሀላ ወደራሴ ስመለስ እና ስነቃ እቤታችን ውስጥ ነኝ።
ሶስታችን አገገምን አባዬ ግን ከመሀላችን
ጎድሏል ።
በነበረበት ስኳር እና ሌላ ተጓዳኝ ህመም ምክንያት በሽታውን መቋቋም አቅቶት በሀገራችን በዚህ በሽታ ከሞቱት ሰዎች መሀል አንዱ ሆነ ።
ይህ ሁሉ በኔ ነው በኔ የደረሰ በማንም አይድረስ!!

💫ተፈፀመ💫

እስቲ ሁላችሁም ይቺን ፅሁፍ በዚች ደቂቃ እያነበባችሁ ያላችሁ #ኮረና የመጣ ጊዜ #ጥንቃቂያችሁ እንዴት ነበር#አሁንስ መልሱን ለራሳችሁ
ግን አሁንም በሽታው ምንም የተቀየረ ነገር የለም መድሃኒት አልተገኘለትም አሁንም የኛ ብቻ ሳይሆን የአለም ስጋት ነው። በየቤታችን እስኪገባ አንጠብቅ እናም ይሄ ታሪክ አንድ ሰው ያስተምራልና #Share እያደረጋቹ።

🛑አሁንም ግን🛑

#እርቀታችንን_እንጠብቅ
#ማክስ_በአግባቡ_እናድርግ
#እጃችንን_በአግባቡ_እንታጠብ
#ከቻልን_ቤት_እንቆይ #ውዶቼ

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#አልወጣም_ተራራ

አልወጣም ተራራ
ደመናን ልዳብስ
ቀስተ ደመናውን፣ ሽቅብ ልቀለብስ
አልዋስም እኔ
ካ'ቡነ ተክሌ ክንፍ
ከያዕቆብ መሰላል
እኔ መውጣት ሳስብ
ሰማዩ ዝቅ ይላል፡፡

🔘በዕውቀቱ ሰዪም🔘
#ፍግ_ላይ_የበቀለች_አበባ

አበባዪቱም አለች፣
ፍግ ላይ የበቀለች
«ምንድን ነው ጥበቡ?»
ሄክታር ማጣፈጠ
አደይን ማስዋቡ፣
እኔም መለስኩላት፣
"ይብላኝ ለንብ እንጂ ዝንብማ ይተጋል
ከቆሻሻ ዓለም ውስጥ ጣ'ምን ይፈልጋል፡፡››

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ክልክል ነው!

ማጨስ ክልል ነው!
ማፏጨት ክልክል ነው!
መሽናት ክልክል ነው!
ግድግዳው በሙሉ ተሠርቶ በክልክል
የቱ ነው ትክክል?
ትንሽ ግድግዳ እና ትንሽ ኀይል ባደለኝ
"መከልከል ክልክል ነው! » የሚል ትእዛዝ አለኝ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ፍሬሙ

ፎቶዋ
የወጣትነቷ
ግድግዳው ላይ ያለ
በኔና በሷ ፊት የተንጠለጠለ
ስንቱን አሳሰበኝ

የሚያምሩት ዐይኖቿ
የሚያምሩት ጉንጮቿ
የሚያምሩት ጭኖቿ
አሉ አሁንም አምረው
በፍሬም ውስጥ ታጥረው፡፡

አጠገቧ ሁኜ
ሶፋ ላይ ቁጭ ብላ
እርጅናዋን አቅፋ
ለጋነቷን ሰቅላ
እኔም ተአምር ሳይ
«ነው» ሶፋ ላይ ኾኖ
«ነበር» ግድግዳ ላይ፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#መልክአ_እናት

ሰላም ለኪ እናታችን
ባለሽበት እንዳለሽ
ከዘመኑ ሴቶች ተለይተሽ
አንቺ የተባረክሽ ነሽ
ሰላም ለዐይኖችሽ
ከጭስ ጋራ ለሚሟገቱ
ከእንቅልፍ ጋራ ለተፋቱ
ተቅበዝባዥ ፍጡር ኾኜ ኑሮዬን ከምገፋ
ምነው እንባሽን በኾንኩ
ካይኖችሽ ሥር እንዳልጠፋ፡፡
ሰላም ለከንፈሮችሽ
ትላንት ለማውቃቸው
ዛሬ ለምናፍቃቸው
ውዳሴ ክብር ምርቃት
ጭብጨባ ሙገሳ ሽልማት በተረፈበት ቀዬ
ምነው ያንቺን እርግማን - ይናፍቃል ጆሮዬ
ከሌሎች ውዳሴና ክብር እልፍ ጊዜ የተሻለ
ለካ በ'ርግማንሽ ውስጥ እናትነትሽ አለ፡፡
ሰላም ለጣቶችሽ
ለሰዎች የቀረቡ፣ ከራስሽ ግን የራቁ
መስጠት መለገስ እንጂ መቀበልን ለማያውቁ
ሰላም ለኪ!
ባለሽበት እንዳላሽ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_አንድ


#በጥላሁን

የጫካ ስሜ ፍልፈሉ ይባላል ። አሁን ካለሁበት የሰው ጫካ ከሞላበት ከተማ ውስጥ መኖር ከመጀመሬ በፊት በየዱራዱሩ እና ጫካ ውስጥ ባሉ የተያዩ ዋሻዎች ከ ስምንት እመት በላይ ኖሪያለሁ። ጫካ የምኖረው አውሬ አልያም ከሰው ተቀላቅሎ መኖር የማይችል ልዩ ፍጡር ስለሆንኩ
አልነበረም ።

በግዜውና በነሱ ምልከታ ትክክል የመሰላቸውን እኔም በግዜው ትክክል የመሰለኝን ፈፅሜ ልፈፅም እንጂ።
አስተሳሰብ የሚያቀና እውቀትን አልያም ሀብትና መሬትን ሳይሆን ከፊቱ አደራ የታከለበት በቀልን አውርሰውኝ ከሞተው አባቴ የተቀበልኩትን ገሎ የመበቀል ውርስ ለመፈፀም ባጠፋሁት ነብስ ምክንያት ከሚደርስብኝ የበቀል ዱላና ቅጣት ለመደበቅ መኖሪያዬን በዱር እንዳደርግ ግድ ሆኖብኝ እንጂ ።

ገና አስራ ስምንት አመት ሳይሞላኝ ከሁለት አመት በፊት ከተለየኝ አባቴ የተሰጠኝን ነገር ቢኖር የምበቀለው እነማንን እንደሆነና የት አከባቢ ሊኖሩ እንደሚችሉ እና መሳርያ ብቻ ነበር።

18 አመት እንደሞላኝ ካባቴ የተሰጠችኝን መሳሪያ ጠራርጌ እናቴን ተሰናብቼ ከቤት ወጣሁ ለስድስት ወራት በአከባቢው ካለ ጫካ ውስጥ ተደብቄ የበቀል ኢላማዬ የሚያርፍባቸውን ካባቴ ዘር ነብስ አጥፍተው የተሸሸጉ ሁለት ሰዎችን መውጫያ መግቢያ ሳጠና እና አመቺ ግዜ ስጠብቅ ቆየሁ።

በሶስተኛው አመት መገባደጃ ላይ ግዳጄን እንደፈፀምኩ ከሶስት ቀን በላይ በግር ተጉዤ ከነበርኩበት ራቅ ወዳለ ሌላ ጫካ ገባሁ።
እልፎ እልፎ ከምኖርባት የጫካ ዋሻ በቅርብ ርቀት ባለች አንዲት ተራራማ መንደር እየሄድኩ የሚያስፈልገኝን ይዤ እመለሳለሁ ።

በአምስት አመት ውስጥ በአሳቻ ሰአት እራሴን ቀይሬ ሁለት ግዜ ብቻ እናቴን ጠይቂያታለሁ።
ወደዚች ከተሸሸኩበት ጫካ በቅርብ ርቀት ወዳለች የገጠር መንደር ግን በሳምት ውስጥ ከሁለት ግዜ ብላይ መሄድ ጀመርኩ።

በ አንድ የገና አውዳ አመት እለት ወደ መንደሯ ጎራ ብዬ በግሬ ሳዘግም አንድ ጠላ ቤት በር ላይ እንደደረስኩ ሽታው አወደኝ የሚያውቀኝ ሰው እንዳይኖር ፈራ ተባ እያልኩ ዘው ብዬ ስገባ አመት በአል ስለነበር ከሶስት ጎረምሶችና ካንድ በድሜ ጠና ካለ ሽማግሌ ውጪ ብዙም ሰው አልነበረም። ጥጌን ይዤ እንደተቀመጥኩ አንድ እድሚያቸው በሀምሳዎቹ አፋፍ ላይ የሚሆናቸው ባልቴት ጠላውን ፊት ለፊቴ ባለችው ትንሽ ጠረጴዛ ላይ እያስቀመጡ ደና ዋልህ ልጄ አሉኝ።

ለሰላምታው ምላሽ ሰጥቼ ጠላውን አንስቼ ጎንጨት አልኩት አላወረድኩትም ግሩም ነበርና ባንድ ትንፋሽ ግማሽ አደረስኩት።
እቤቱ ውስጥ ያሉት ሶስት ጎረምሶች ስለ ባለጠላ ቤቷ ሴትዬ ልጅ ቁንጁና ከሚገባው በላይ እያደነቁ ያወራሉ ።

ያን ያመሰለ ውበት ይዛ እስካሁን ባለማግባታ ይደመማሉ። እሷ እዛ የገጠር መንደር ውስጥ ዘናጭ የሆነ ቤት ሰርታ ለብቻዋ እየኖረች የሳቸው ጠላ መሸጥ አይገርምም እያሉ ያሽማጥጣሉ። ሴትዬዋ ጠላውን ሊቀዱላቸው ጠጋ ሲሉ ወሬያቸውን ያቋርጣሉ። ልጅቷን የማየት ጉጉቴ ጨመረ ።አልፎ አልፎ ወደዛ ጠላ ቤት እንድምትመጣ ስለሰማሁ ላይን ያዝ እስኪያደርግ ጠላውን እየደጋገምኩ ብጠብቅም እሷ ሳትመጣ እኔ ሰከርኩ።
ጠላው በሳምት ውስጥ ማክሰኛ እና ቅዳሜ ብቻ ነው የሚኖረው ። የኔም የማክሰኛና ቅዳሜ ውሎ ጫካ ሳይሆን እዛ ቤት ሆነ ከሶስት ሳምንት የማክሰኛና ቅዳሜ ምልልስ ቡሀላ በአራተኛው ሳምንት ቅዳሜ ቁጭ ብዬ ጠላዬን ሳጣጥም ድንገት ዘው ብላ የገባችውን ሴት ስመለከት የተሰማኝ ስሜት ከዛ በፊትም ከዛ ቡኋላም እስከዛሬ ድረስ ተሰምቶኝ አያውቅም።

ምድር ላይ ካሉ ሴቶች ሁሉ ውበት ቀምቶ ለሷ የሰጣት ነው የምትመስለው አይኖቿ ልብ ያሸብራሉ።
ሀር የመሰለው ቀጭን ወገባ ላይ የሚንከባለለው ጥቁር አንፀባራቂ ፀጉሯ ለካ እስከዛሬ ፀጉር አይቼ አላውቅም ያስብላል።

ወደ ውስጥ ስትዘልቅ ከቀጭን ወገባ ቁልቁል ግዛቱን እያሰፋ የሄደው ዳሌዋ ሲውረገረግ ቁጭ ብድግ ያሰኛል። ጥርት ያለው ጠይምነቷ እንኳንም ነጫጭባ ፈረንጅ አልሆንኩ እንኳንም ኢትዬጲያዊ ሆንኩ ያሰኛል ።
ፈገግታዋ ልብ ላይ የተተኮሰ ጥይት ይመስል ልብ ይንዳል ። አንድ ባል አይደለም አንድ ክፍለጦር በውበት አንበርክኮ የሚያስከትል ይሄን ሁሉ ውበት ይዛ ያላገባችበት ምስጢር ምን ይሆን አልኩ ለራሴ።

ተወልጄ ባደግኩበትም ይሁን በሄድኩበት ሁሉ እስከዛሬ ይችን የመሰለች የውበት ሚስጥሩን የገለጠባት ከ
ኮረዳ ተመልክቼ አላውቅም።
ወይ ጣጣ ከፊቴ ተቀምጣ አይኔን እንዴት ከሷ ላይ ልንቀልና ልጠጣ ።

የምትኖርበት መንደር በመሀላቸው ጫካ እርሻ እና ተራራ ያራራቃቸው እዚህም እዛም ተራርቀው ካሉት ውስን ቤቶች በቀር ብዙም ነዋሪ የለም ።
ለመንደሩ አዲስ እንደሆንኩ ታውቋታል መሰለኝ ከናቷ ጋር እያወጋች አልፎ አልፎ እነኛን ውብ እይኖቿ ከብለል እያረገች ትመለከተኛለች ።
እንደተቆጡት ህጣን ልጅ እርበተበታለሁ።
አለባበሷ ግን ከተሜ ቀመስ ትመስላለች እንደው ወደ ከተማ ባል ይኖራት ይሆን? ካላት ታድያ እዚህ ለምን ትኖራለች ?።
ስፈራ ስቸር ቆይቼ አንድ ቃል ካፌ ወጣ።
እናት አለም ጠላ እንጠጣ?
"አባት አለም አልጠጣም! ክክክ"
ደነገጥኩ ስደነግጥ አይታ ይባስበት ይደንብር ብላ ነው መሰል ሳቋን ለቀቀችው።

ስትስቅብኝ ወንድነቴ ኬት እንደመጣ እንጃ ፍርሀቱን ትቼ ደፈር ብዬ አጫውታት ጀመር በስም ብቻ እማውቀው ፍቅር እኔን ለመቆጣጠር ቀጠሮም አላስፈለገው አልቻልኩም ከማክሰኛና ከቅዳሜ ውጪ ጠላ ኖረም አልኖረም ከተደበቅሁበት ዋሻ ወደሷ መሮጥ የየለት ተግባሬ ሆነ እኔ ቀድሜ በፍቅሯ ብወድቅም እሷ ቀስ በቀስ ለምዳኝ ይሁን ወዳኝ እርግጠኛ ባልሆንም ስንለያይ " ነገ ትመጣለህ ?" ማለት ጀመረች።

ማን እንደሆንኩ አንድም ቀን ሳትጠይቀኝ ለምን እስካሁን እንዳላገባች እንድጠይቃት ሳትፈቅድልኝ ከሶስት ወር ምልልስ ቡሀላ ጠቅልዬ ቤቷ ገባሁ። ተጋባን ።

ተጋብተን በሁለተኛው ቀን ግራ የሚያጋባ ነገር ገጠመኝ ማታ አጠገቤ የተኛችው ፍቅሬ እኩለ ለሊት ካለፈ ቡሀሏ ድንገት ስነቃ አጠገቤ የለችም •••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#እንደ_ሚስት_አውለኝ

በእንቁ ተሽሞንሙኜ ገነት ባያውለኝ
ከቸነፈር ከ'ሳት ከሲኦል ባይጥለኝ
እንደ እናቴ ግን አይሁን
እንደ ሚስቴ አውለኝ
ርሃብ ጉስቁልና አንዳችም ሳይነካኝ
በደስታና ሃሴት ሳውካካ እንድገኝ፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ዘመን_በወፍ_በረር

ነበረ ወጉማ የመተጫጨቱ
ሎሚ ተወራውሮ ደረት መማታቱ
ወንዝ ወረድም ብሎ ውሃ ማቃዳቱ
እኔን ግን ከበበኝ ዘመኑ ለወጠኝ
የግዜ ጥበቡን መነጽሩን ሰጠኝ
እኔም ዘመንኩና ለውጥን ተቀበልኩት
አይኔን ብወረውር ደረቷን መታሁት፡፡

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#ከዛፍ_የተቀሰመ_ዜማ

ካ'ለም እቅፍ ወጥቶ
ካ'ለም እቅፍ ሸሽቶ
ወደ ገዳም ሲሄድ
ደክሞት ተዝለፍልፎ
ብላቴናው ያሬድ ካ'ንድ ዛፍ ሥር ዐርፎ
ከዛፉ ግንድ ሥር ትል ሲሸልል ሰማ
እንዲህ በሚል ዜማ
ዛፉ ነው ሕይወቴ
ቅጠሏም እራቴ
ሰባት ጊዜ ልውደቅ
ሰባቴ እንድወጣ
የኋላ ኋላ ራቴን ኣላጣ”
ይህን ስትሰማ ቅጠሊቱ ራደች
መሸሽ ባይኾንላት ሙሾን አወረደች
ዛፉ ሕይወቴ ነው
ግን ኀያል ቢመስልም
ተራራ ቢያክልም
የማታ የማታ
ከትል አያስጥልም”
ያሬድ ይኼን ሰምቶ
ትሉ በጥረቱ ራት ሲበላ አይቶ
ተስፋውን አጸናው
በቅጠሏ ዕጣ ግን ተነካ ልቡናው
ከዚያም ተመልሶ
የትሉን ፉከራ
የቅጠሏን ለቅሶ
ባ'ንድ ላይ ለውሶ
ዜማውን ቀመረ
ዜማው ተዘመረ
ከሰው ነፍስ ተስማማ
በሰው ድምፅ አማረ።

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
👍1
#ሚስቴ_ማነች?


#ክፍል_ሁለት


#በጥላሁን

ተጋብተን በሁለተኛው ቀን ግራ የሚያጋባ ነገር ገጠመኝ ማታ አጠገቤ የተኛችው ፍቅሬ እኩለ ለሊት ካለፈ ቡሀሏ ድንገት ስነቃ አጠገቤ የለችም።

ደነገጥኩ ቤቱ ሁለት ክፍል ነው ከተኛሁበት ክፍል ተነስቼ ሌላኛው ክፍል ውስጥ መኖር አለመኖሯን ለማረጋገጥ ባስብም ከማሰብ ውጪ ካልጋው ላይ መውረድ አቃተኝ አልቻልኩም።
በተፈጥሮ ከንቅልፍ ነቅተን ለመነሳት ከሚጫጫነን ስሜት እጅግ በላቀ ሁኔታ እንዳልነሳ ተጫጫነኝ ቀና ማለት እየፈለኩ ቀና ማለት ተሳነኝ እስርስር ድብት የሚያረግ መንፈስ ወረሰኝ። መነሳት እየፈለኩ መልሶ እንቅልፍ ጣለኝ።ወፍ ጭጭጭጭ ሲል ነቃሁ። አጠገቤ ተኝታለች። ግራ ተጋባሁ ለሊት ካጠገቤ ያጧኋት በህልሜ ይሁን በውኔ መለየት ፈተና እንደሆነብኝ መምሸቱ አይቀርም ዳግም መሸ።

ትናንት በነቃሁበት በተመሳሳይ ሰአት እኩለ ለሊት እንደተሻገረ ነቃሁ አጠገቤ ተኝታለች። ያን ቀን ደግሞ ከትናንቱ በተቃራኒ አንዴ ከነቃሁ ቡሀላ እንቅልፍ አልወስድ ብሎኝ ስገላበጥ ነጋ ።
አራተኛው ምሽት መጣ ስንጨዋወት አምሽተን እራት በልተን ተኛን። በተለመደው ሰአት በር ሲከፈት ይሁን ሲዘጋ እንጃ ብቻ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝና ብንን አልኩ። ኧእምሬዬ ከተኛበት ቢነቃም አይኔ አልተገለጠም ነበርና እጄን ወደ ጎን ልኬ ዳበስ ዳሰስ ሳደርግ ከፍራሹ ካንሶላ እና ከብርድልብሱ ውጪ ማታ አጠገቤ የተኛችው ሚስቴ የለችም ።ፈራሁ። አይኔን መግለጥ ፈራሁ።

በትግል የገለጥኩት አይኔ በፋኖሱ ብርሀን የኔዋ ጉድ አጠገቤም የተኛሁበት ክፍል ውስጥም ያለመኖሯን አረጋገጠልኝ። እቤቱ ውስጥ ምንም ድምፅ የለም ፀጥ ረጭ ብሏል። መነሳት እየፈለኩ አልነሳም መጣራት እየፈለኩ አልጣራም።ጭራሽ ከመነሳት ሀሳቤ ጋር ያልተናበበው አይኔ ካልተከደንኩ እያለ ይታገለኝ ጀመረ ። አይኔ እየተከደነ እንቅልፍ ሊጥለኝ ሲሞክር ላለመተኛት ያደረኩት ትግል ከውስን ደቂቃዎች መሻገር አልቻለም። መሸነፌ የገባኝ ጥዋት ስነቃ ነው ለሊት ያልነበረችው ሚስቴ አጠገቤ ጧ ብላ ተኝታ እራሷን አታውቅም ።

የኔ ፍቅር ማነሽ አቅሌን እስካጣ በፍቅርሽ መውደቄ ይሆን እያቃዥኝ ያለው ።
የፍቅሬ ደረጃ ይሆን ጥለሽኝ የወጣሽ ካጠገቤ የራቅሽ እየመሰለኝ እንድጨነቅ የሚያደርገኝ ነው ወይስ የእውነት ነቅቼ ካጠገቤ እያጣሁሽ ነው ።
እንደዛ ከሆነስ በውድቅት ለሊት የት እየሄድሽ ነው ? መቼስ ባዛ የሰይጣን ሰአት መብራት በሌለበት በዚህ የገጠር መንደር ውስጥ ከቤት መውጣት እንኳን ለሴት ለወንድም ያስፈራል ። ታድያ ምን እየሆንኩ ነው የእውነት ነቅቼ ካጠገቤ አጥቼሽ ከሆነስ ለምንድን ነው ተነስቼ ሁለተኛው ክፍል ውስጥም አለመኖርሽን እና ቤቱ ቤት በኩል እንደተዘጋ ከውጪ ይሁን ከውስጥ ማረጋገጥ ያቃተኝ ።

በለሊት ካጠገቤ ተነስተሽ የት ሄደሽ ነው አልነበርሽም ብዬ እንዳልጠይቅሽ ችግሩ ከኔ ከሆነ እንዳላስቀይምሽ ሰጋሁ። አልኩኝ በውስጤ ብርድልብስም አንሶላም ሳትለብስ ተዘረጋግታ በተኛችው ሚስቴ ላይ እንደጥዋት ፀሀይ ሰውነት የሚያሞቀውን የውበት መአት የፈሰሰበትን ገላ ከታች እስከ ላይ እያየሁ። ምን ዋጋ አለው የትዳር ጣእም የላይ ውበት ሳይሆን የውስጥ ሰላም መሆኑ አሁን ነው የገባኝ።

እሄ ነገር አንድ ቀን እየዘለለ በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጠለ። ተአምር የሆነብኝ ነገር ለሊት ስነቃ አጠገቤ ካለች ከነቃሁ ቡሀላ በጭራሽ እንቅልፍ አይወስደኝም ። በሚቀጥለው ቀን ስነቃ ደግሞ አጠገቤ አትኖርም ግን መነሳትም አልችልም በዛ ላይ ወድያው እንቅልፍ ይጥለኛል።ጭንቀቴን ለማን ላዋየው ያለሁት ከሷ ውጪ ማንንም በማላውቅበት ሀገር ነው ።
ጭንቀቴ እና ፍርሀቴ ለሊቱን ብቻ ሳይሆን ቀኑኑም አጨለመብኝ።
እሄን ግዜ ነበር እናቴ ያለችኝ ነገር ትዝ ያለኝ ።
ያባቴን የበቀል ውርስ ልፈፅም ስነሳ ብቻ ብርክክ አለችና ጉልበቶቼን ይዛ "ተው ልጄ የሰው ደም ደግ አይደለም በምድርም በሰማይም ሰላም አይሰጥም ።የሰው ነብስ ያጠፋ የሰላም እንቅልፍ የለውም።የገደለው ሰው ነብስ ታስጨንቀዋለች። አንድ ሰው ስትገድል በህይወት ዘመኑ የሰራው ሀጥያት በሙሉ ወዳንተ ይዞርና እሱ ይፀድቃል አንተ ትኮነናለህ ።
በምድርም በሰማይም ብኩን ሆነህ ትቀራለህ። እሄን ባለማድረግህ አባትህን እንደከዳኸው ቃሉን እንዳላከበርክ አይሰማህ። ይልቅ የነሱን ስተት አትድገመው ካለፈ ነገር ማስቀጠል ያለብን ደግ ደጉንና የሚጠቅመንን እንጂ ክፋቱንና የሚያጠፋንን መሆን የለበትም። ይህን የበቀል መንገድ አንተ ካላቆምከው ማን ያቆመዋል። ሰው በመግደል ጀግንነት ነው ብሎ ማሰብ ሗላ ቀር አመለካከት ነው ። ልጄ ተለመነኝ አትሂድ!"
ልመናዋን መቀበል ፈሪ መሆን ከወንድነት ዝቅ ማለት መስሎ ተሰማኝ ።
እማምዬን ከጉልበቴ ላይ አነሳሗትና ጥያት ወጣሁ። ታድያ አግብቼ ወር ሳይሞላኝ መቋጠሪያውም መፍቻውም የማይታወቅ ፈተና ሲገጥመኝ ። እማማ እንዳለችው ያ ያጠፋሁት ነብስ በቁሜ እያቃዥኝ እንጂ የኔ ንግስት በለሊት የምትወጣበት ምንም ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብዬ እራሴን ለማፅናናትም ለመኮነንም ሞከርኩ።

ከብዙ አስጨናቂ ቀናት ቡሀላ አንድ ቀን ወደ ጫካ ወርጄ ለብዙ ሰአት ተቀምጬ ያሳለፍኳት እያንዳንዷን አስጨናቂ ቀን ስፈትሽ ሚስቴ ማታ ማታ ከምታደርጋቸው ነገሮች እስካሁን የተጋረደብኝ እና ያላስተዋልኩት አንድ ነገር ብልጭ አለልኝ።
በድንጋጤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቆምኩ በለሊት ከአጠገቤ የሄደች በመሰሉኝ ቀናት በሙሉ ማታ ማታ ወደ ምኝታዬ ልሄድ ስል በንድ ከቀንድ በተሰራ የጠላ መጠጫ ቀላስ ሙሉ ጠላ ትሰጠኝ ነበር አጠገቤ በነበረችባቸው ለሊቶች ምሽት ግን ያ ጠላ ተሰጥቶኝ እንደማያውቅ ተገለጠልኝ ። ከምኝታዬ እንዳልነሳ ጠፍንጎ የሚይዘኝ ሚስጥር ከጠላው ጋር የተያያዘ መሆን አለበት አልኩ።

ከሩጫ በማይተናነስ እርምጃ ወደ ቤት አመራሁም። ያን ቀን ማታ ጠላው አልተሰጠኝም። እሳም ለሊት አጠገቤ ነበረች።
በሚቀጥለው ቀን ማታ ከራት ቡሀላ ልተኛ ስል "እንካ ጠጣ ለንቅልፍ ይሆንሀል"እያለች ጠላውን በዛው መጣጫ ይዛልኝ መጣች። ተቀብያት ወደ ውስጥ ገባሁና ሳታዬኝ ደፋሁት።
ምኝታዬ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በመምሰል እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር እየተጠባበኩ እኩለ ለሊት አለፈ። በግምት ከለሊቱ ስምንት ሰአት አከባቢ ድምፁ ቀጭን የሰው ሳቅ የሚመስል ጅብ ወደ አለንበት ግቢ ተጠግቶ ማስካካት ጀመረ ። ትንሽ ቆይቶ የማስካካቱ ድምፅ እየቀረበ የሚያሽካኩትም ጅቦች እየበዙ መጡ።
ድምፁን በሰማሁ በሰከንዶች ውስጥ ጉደኛዋ ሚስቴ ድንገት ብድግ አለች። ፊቴን አዙሬ በተኛሁበት በድንጋጤ ላብ አዘፈቀኝ ። ፋኖሱን ይዛ ወደ ሚቀጥለው ክፍል ስትገባ በቀስታ ተነስቾ በመሀለኛው በር ጠርዝ አጮልቄ መመልከት ጀመርኩ። ከመቅፅበት መሶብ ወርቅ ከሚባለው የመሶብ አይነት ውስጥ ቅጠል የመሰለ ነገር አንስታ አፏ ውስጥ ከተተችና ትርጉሙ ባልገባኝ ቋንቋ በጣም በፍጥነት እየለፈለፈች ከግንባሯ በላይ ያለውን የራስ ቅሏን ልክ እንደኮፍያ ከነፀጉራ አውልቃ መሶብ ወርቁን ከፍታ አስቀመጠችው። ወንድነቴ ተፈተነ እግሮቼ መቆም ተሳናቸው በሩን ከፍታ ስትወጣ ከቆምኩበት መንቀሳቀስ አቃተኝ•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ይድረስ_ላድርባይ_ጓዴ

እየለየ ጊዜ ቦታ እየመረጠ
እስስታማ መልክ ገጽኽ ተለወጠ
አህያ እዳልነበርህ በሰርዶዎች መሀል
አህዮች ሲበዙ ዛሬ ጅብ ኾነሀል፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#የለንበትም

ልብህ የወዳጅ ፤ ልብስህ የጠላት
በምን እንለይህ፤ በምን ብልሀት
መሳይ ልብስ'ንጂ፧ መሳይ ልቡና
ለይተን ማወቅ ፤ አንችልምና
ድንገት አግኝተን ብንገድልኽ የትም
የለንበትም! የለህበትም!

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#አፅናኝ_የጠፋ_ለት

የወላድ አንጀቷን
ሀዘን ሲያላውሰው
በእናት አይኖች ነው
ሀገር ምታለቅሰው።

🔘ኢዛና መስፍን🔘

#Stop_killing_Amhara