#ማዕዶት
፡
፡
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፋል)
፡
፡
#በየዝና_ወርቁ
“እኔ ኮ ራሴን አላቀውም ሳሚ” አለችው በሚለማመጥ ቅላፄና በጨዋ ቋንቋ፡፡
ምንድን ነው የማታውቂው” ? አላት ግር
እንደመሰኘት ብሎ፡፡
«ኤች.አይ.ቪ ምርመራ ነዋ »አለችው::
«እኔም ወደውጭ አገር ስሄድ ተመርምሬ ነፃ መሆኔን ካወቅሁ ዓመት አልፎኛል፡፡ እንደገና ማድረግ ይኖርብኛል።
ይጠቀማል፡፡ ካልሆነ ግን እንደማዕዶት ዓይነት ያማረ
መልክና ቁመና ያላቸውና ረጋ ያሉ ሴቶችን ሲያገኝ
“ምንድ ነወ
“ታዲያ! አለችው - የምርመራ ነገር ሲነሳ ደፋር ለመምሰል ብትጣጣርም ፍርሃቷ ከውስጧ ማንሰራራት ጀምሯል።
«ታዲያማ ሰው የሚመረመረው፤ አስገዳጅ ሁኔታ ሲያጋጥመው ወይም ደግሞ ሲያገባ ወይም ልጅ ሊወልድ
ሲፈልግ ነው› አላት::
“ካልሆነስ?” አለችው - አንደበቷ እየጐለደፈባት፡፡
“መቼም እንዳንቺ የተማረ ሰው ኮንዶም አላቅም አይለኝም አላት በቀልድ ቃና እየሳቀ….ሳምሶን የሷን አቅጣጫ ተከትሎ ስለ ኮንዶም አወራ እንጂ በመሰረቱ ኮንዶም መጠቀም አይወድም::
አንዳንድ ጊዜ እንዲሁ አይቶ ወይም ሁኔታቸውን ታዝቦ የሚጠራጠራቸው ሴቶች ሊያጋጥሙት ብቻ ሳይወድ ይጠቀማል ካልሆነ ግን እንደ ማእዶት ያማረ መልክና ጠቁመናል ቁመና ያላቸውና ረጋ ያሉ ሴቶችን ሲያገኝ በነሱ በኩል ግፊቱን ካልመጣ እሱ አያስበውም። ስሜቱን
አርክቶ ማገናዘብ ሲጀምር ነው “ጭንቀት የሚሰማው፡፡በሌላ ጊዜ ግን መልሶ ያደርገዋል፡፡
ማዕዶት አነጋገሩን እስተዋለችና ጥሩ ግንዛቤ እንዳለው ገመተች፡፡ ለሷም ቢሆን ጥሩ ነገር እንደሆነ አሰበች፡፡ “ለጊዜው እሱ እንዳለው በኮንዶም እንቆያለን፡፡
ለመጋባት ስንወስን ደግሞ በቃ በመጀመሪያ ሳልነግረው ተደብቄ እመረምራለሁ። ፈጣሪ ረድቶኝ ነፃ ከሆንኩ
አብረን እንመረመራለን፡፡ ቫይረሱ ቢገኝብኝስ ... " ሐሳቧን መጨረስ አቃታት።ሰውነቷ ተንዘፈዘፈ....
መኪናቸው ውስጥ እንዳሉ ቦዩን ጠራውና
መኝታ ክፍል ተከራየ:: ወደዚያው ሲሄዱ
ብርጭቆዎቻቸውንና ጠርሙሱን ቦዩ ይዞ ተከተላቸው፡፡
እንደገቡ ሳምሶን ኮሞዲኖውን ከፈት አድርጎ ኮንዶም ሲያረጋግጥ አየችው:: ተረጋጋች።
ልብሶቻቸውን አውልቀው አልጋው ውስጥ ገቡ:: ትንሽ እንደተሳሳሙ ከኮሞዲኖው ውስጥ አንድ ፖኬት ኮንዶም
አወጣና ከውስጡ አንዱን ነጥሎ ጐረደው:: ቀሪውን ደግሞ ኮሞዲኖው ላይ አስቀመጠው:: ከዚያ ማሽጊያውን
ከፍቶ የውስጡን መዘዘና መብራቱን አጠፋው።
“መብራት አትወድም? አለችው።
“አዎ አላት - ድምጹም ድንገት ስልቱን አጣባት፡፡ስሜት ይዟቸው እልም አለ… በመጨረሻ አንሶላውን ከውስጥ ጎተተና አሸርጦ ወደ መታጠቢያ ቤት ሄደ፡፡
ታጥቦ እንደተመለሰ መለኪያው ውስጥ የነበረው ማርቲኒ በአንድ ትንፋሽ ጨለጠውና ሌላ ቀዳ:: የቀዳውን
ምንም ሳያናግራት ጨለጠው።
ግራ ተጋብታ አየችው:: ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ብሩህ ፈገግታ የነበረው ፊቱ ዳምኗል፡፡እንደገና ሲቀዳ
ፈራችውና ፤
“እንሂድ እየመሸ ነው አለች
አትጠውጪም? አላት- ስልቱን ባጣ ድምጽ፡፡
«በቃኝ» አለች - ለመልበስ እየተነሳች:: ለባበሱ ወጥተው ወደ ሳምሶን መኪና ሄዱ::
በቀጠሉት ሶስት ሳምንታት ሶስት ጊዜ ተገናኝተን ተመሳሳይ ሁኔታ አሳልፈዋል:: ማዕዶት ከድሮው ባህሪዋ በተለየ ሁኔታ ከሱ ጋር ስትሆን ሞቅ እስኪላት መጠጣት መጀመሯ ታውቋታል። ግን እያቀበጠ ስለሚያጠጣ ደስ ይላታል፡፡ እንደ ህፃን ስሜቱን መደበቅ የማይችል
መሆኑን እያስተዋለችም አብረውት ለመኖር የማይከብድ ዓይነት ሆኖባት ለማይቀረው የእንመርመር ጥያቄ
እንዲያበረታት ፈጣሪዋን እየተማፀነች ለጋብቻ ተመኝተዋለች
ድንገት ግን ያልጠበቀችው ነገር ተከሰተ፡፡ የወር አበባዋ በቀኑ ሳይመጣ ቀረ፡፡ ግራ ቢገባት መምጫ ቀኑን ኣዛብቶ የማያውቀውን የወር አበባዋን ሳምንት ሙሉ በተስፋ ጠበቀችው።መቅረቱን ስታረጋግጥ ብርክ ያዛት።
በስሜት ውስጥ ሆነን ሳናውቀውየተፈጠረ ስህተት ይኖር ይሆን?! ይኼ አደጋ ነው! ወይ በኔ ወይ
በሱ ላይ የመጣ እያለች አንጎራጎረች :: ልጁንም' ኮ ላይቀበለኝ ፣ ላያምነኝ ይችላል» ብላ አሰበችና ልትነግረው
ፈራች፡፡ እየቆየች ስታስበው ስታብላላው ግን ከመንገር ሌላ አማራጭ አጣችለት:: ሁለታችንም ሳናስበው የወደቅንበት አደጋ ላይ መወያየትና መፍትሄ መፈለግ
አለብን " አለች - ልትነግረው ወሰነችና ደውላ ለማታ ፕሮግራም አስያዘችው።
እንደሌለቹ ቀናት የመዝናናት ስሜት
አልነበራትም ራት መብላት አቅቷት መጠጣትም አስጠልቷት ስለነበር አሞኛል ብላ ዋሸችው:: ከዚያም
ብዙ ሳይቆዩ መብራቱን አጠፋው:: እሱ ስሜት ውስጥ ገብቷል፡፡ እሷግን ሀሳቧ ግራ በገባት ነገር እየተሰረቀ
አስቸግራት በስሜት ልትከተለው አልቻለችም፡፡ እና እሱን ለማስደሰት ብቻ እንደሚፈልገው እየሆነችለት ሳለ
መሀከል ላይ የተለየ ነገር ተሰማት:: ድንገት ጠረጠረችው።ድንጋጤ አስፈንጥራት ተነሳችና መብራቱን ቦግ አድርጋ አበራችው::ሳምሶን ኮንዶሙን በእጁ እንዳንጠለጠለው
ክው ብሎ ቀረ:: ማዕዶትም አንገቱን አንቃ ተንቀጠቀጠች። ከዚያ አንገቱን ለቃ ተስፋ በቆረጠ መንፈስ ፍራሹን እየደበደበችና፤
“አንተ አውሬ ነህ! ጭራቅ ነህ! ተኩሰህ እንደገደልከኝ ቁጣረው..... ምነው? ምን በደልኩህ?...” እያለች ትራሱ ላይ ተደፍታ ተንሰቀሰቀች፡፡ ሳምሶን ድንጋጤው መለስ
ሲልለት ፤
ምን እንዲህ ያደርግሻል? አንቺ ብቻ ነሽ ለህይወትሽ የምታስቢ? እኔ ከማንም ጋር የምጋደም መሰለሽ? ሰው መርጫ ነው" አለ በላይ ሆኖ እንደመቆጣት' እያደረገው
ከአፈርኩ አይመልሰኝ ዓይነት።
“የጅል ወግህን ተወውና ይኼንን ተንኮል የፈፀምክብኝ እውነት ተመርምረህ ቫይረሱ እንዳለብህ ሳታውቅ ከሆነ
ነገ እንመርመር " አለችው - እልህ እያንቀጠቀጣት፡፡
ሳምሶን ትኩር አድርጎ አያትና፤
“ይቻላል አለ - ትከሻዎቹን ከፍ አድርጎ ቁልቁል እየለቀቃቸው:: ዐይኖቹ ውስጥ ግን ፍርሃት በጉልህ ነግሶ ታየ።
እንደተኮራረፉ ልብሶቻቸውን ለብሰው ወጡ፡፡
በማግስቱ ለመመርመር ከተቃጠሩበት አሁን ውጤቷን እየጠበቀችበት ካለው ክሊኒክ ከሰዓቱ ቀድማ ደረሰች፡፡ ለዘመናት የራቀ የመሰላትን ያህል ጊዜ ጠብቃው ሲቀርባት በሞባይል ስልኳ ሞባይል ስልኩ ላይ ደወለችለት። ዘጋባት:: ሰዓቱ ሶስት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ግማሽ ሰዓት አሳልፏል:: ትንሽ ቆየችና ሞክረች። መልሶ ዘጋባት፡፡ ብርክ እንደያዛት ተስፋ ቆርጣ በየመንገዱ እንባዋን ለመዋጥ እየታገለች በኮንትራት ታክሲ ወደቤቷ ሄደች መሥሪያ ቤቷ ደውላ መታመሟን ለአለቃዋ አሳውቀችና ተኛች፡፡ ከሰዓት በኋላ ለሳምሶን በሱቅ ስልክ ደወለችለት
አነሳውና እሷ መሆኗን ሲያውቅ ዘጋባት፡፡
ደጋግማ ሞከረች፡፡ ሊያናግራት ፈቃደኛ አልሆነም…
ማዕዶት የተፈጠረውን ነገር እንደክፉ ቅዥት ስትባንን ለቀናት አሰበችው::
ሳምሶንን ለማግኘት የምታደርገው ጥረትም ጥቅም የሌለው ሆነባት፡፡ ከዚህ ወዲያ ባገኘውስ ምን ያደርግልኛ
ል? ጠላቴን የልጄ አባት አድርጌ አልቀበለው አለችናእርግፍ አድርጋ ተወችው::
እያደር ግን ለራሷ ከመጨነቅ አልፋ በማህፀኗ ውስጥ ስላለው ልጅ ማሰብ ጀመረችና ትናንት ደሟን ለምርመራ ሰጠች….
ማዕዶት የሰመጠችበትን የትዝታ ባህር ዋኝታ ስትጨርስ ያው የተጠናወታት ቫይረሱ ቢገኝብኝስ የሚለው ጭንቀት በውስጧ እያንሰራራ ነበር ። እና
የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሰውነቷን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ሲበላው ቤተሰቦቿ እንኳ ሊያስታምሟት ሲሳቀቁ ፣ከወዳጅ ዘመዶቿ መሀል ተነጥላ ብቻዋን ስትንጠራወዝ ታያት፡፡ በውስጧ የጭንቀት ትኩሳት ተሰራጨ፡፡
ጨምድዶ። ከያዛት ጭንቀት ለመውጣት እያባ ት : ንቀት እየተወራጨች ! 'ቢኖርብኝም ቫይረስ ላለባቸው
፡
፡
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፋል)
፡
፡
#በየዝና_ወርቁ
“እኔ ኮ ራሴን አላቀውም ሳሚ” አለችው በሚለማመጥ ቅላፄና በጨዋ ቋንቋ፡፡
ምንድን ነው የማታውቂው” ? አላት ግር
እንደመሰኘት ብሎ፡፡
«ኤች.አይ.ቪ ምርመራ ነዋ »አለችው::
«እኔም ወደውጭ አገር ስሄድ ተመርምሬ ነፃ መሆኔን ካወቅሁ ዓመት አልፎኛል፡፡ እንደገና ማድረግ ይኖርብኛል።
ይጠቀማል፡፡ ካልሆነ ግን እንደማዕዶት ዓይነት ያማረ
መልክና ቁመና ያላቸውና ረጋ ያሉ ሴቶችን ሲያገኝ
“ምንድ ነወ
“ታዲያ! አለችው - የምርመራ ነገር ሲነሳ ደፋር ለመምሰል ብትጣጣርም ፍርሃቷ ከውስጧ ማንሰራራት ጀምሯል።
«ታዲያማ ሰው የሚመረመረው፤ አስገዳጅ ሁኔታ ሲያጋጥመው ወይም ደግሞ ሲያገባ ወይም ልጅ ሊወልድ
ሲፈልግ ነው› አላት::
“ካልሆነስ?” አለችው - አንደበቷ እየጐለደፈባት፡፡
“መቼም እንዳንቺ የተማረ ሰው ኮንዶም አላቅም አይለኝም አላት በቀልድ ቃና እየሳቀ….ሳምሶን የሷን አቅጣጫ ተከትሎ ስለ ኮንዶም አወራ እንጂ በመሰረቱ ኮንዶም መጠቀም አይወድም::
አንዳንድ ጊዜ እንዲሁ አይቶ ወይም ሁኔታቸውን ታዝቦ የሚጠራጠራቸው ሴቶች ሊያጋጥሙት ብቻ ሳይወድ ይጠቀማል ካልሆነ ግን እንደ ማእዶት ያማረ መልክና ጠቁመናል ቁመና ያላቸውና ረጋ ያሉ ሴቶችን ሲያገኝ በነሱ በኩል ግፊቱን ካልመጣ እሱ አያስበውም። ስሜቱን
አርክቶ ማገናዘብ ሲጀምር ነው “ጭንቀት የሚሰማው፡፡በሌላ ጊዜ ግን መልሶ ያደርገዋል፡፡
ማዕዶት አነጋገሩን እስተዋለችና ጥሩ ግንዛቤ እንዳለው ገመተች፡፡ ለሷም ቢሆን ጥሩ ነገር እንደሆነ አሰበች፡፡ “ለጊዜው እሱ እንዳለው በኮንዶም እንቆያለን፡፡
ለመጋባት ስንወስን ደግሞ በቃ በመጀመሪያ ሳልነግረው ተደብቄ እመረምራለሁ። ፈጣሪ ረድቶኝ ነፃ ከሆንኩ
አብረን እንመረመራለን፡፡ ቫይረሱ ቢገኝብኝስ ... " ሐሳቧን መጨረስ አቃታት።ሰውነቷ ተንዘፈዘፈ....
መኪናቸው ውስጥ እንዳሉ ቦዩን ጠራውና
መኝታ ክፍል ተከራየ:: ወደዚያው ሲሄዱ
ብርጭቆዎቻቸውንና ጠርሙሱን ቦዩ ይዞ ተከተላቸው፡፡
እንደገቡ ሳምሶን ኮሞዲኖውን ከፈት አድርጎ ኮንዶም ሲያረጋግጥ አየችው:: ተረጋጋች።
ልብሶቻቸውን አውልቀው አልጋው ውስጥ ገቡ:: ትንሽ እንደተሳሳሙ ከኮሞዲኖው ውስጥ አንድ ፖኬት ኮንዶም
አወጣና ከውስጡ አንዱን ነጥሎ ጐረደው:: ቀሪውን ደግሞ ኮሞዲኖው ላይ አስቀመጠው:: ከዚያ ማሽጊያውን
ከፍቶ የውስጡን መዘዘና መብራቱን አጠፋው።
“መብራት አትወድም? አለችው።
“አዎ አላት - ድምጹም ድንገት ስልቱን አጣባት፡፡ስሜት ይዟቸው እልም አለ… በመጨረሻ አንሶላውን ከውስጥ ጎተተና አሸርጦ ወደ መታጠቢያ ቤት ሄደ፡፡
ታጥቦ እንደተመለሰ መለኪያው ውስጥ የነበረው ማርቲኒ በአንድ ትንፋሽ ጨለጠውና ሌላ ቀዳ:: የቀዳውን
ምንም ሳያናግራት ጨለጠው።
ግራ ተጋብታ አየችው:: ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ብሩህ ፈገግታ የነበረው ፊቱ ዳምኗል፡፡እንደገና ሲቀዳ
ፈራችውና ፤
“እንሂድ እየመሸ ነው አለች
አትጠውጪም? አላት- ስልቱን ባጣ ድምጽ፡፡
«በቃኝ» አለች - ለመልበስ እየተነሳች:: ለባበሱ ወጥተው ወደ ሳምሶን መኪና ሄዱ::
በቀጠሉት ሶስት ሳምንታት ሶስት ጊዜ ተገናኝተን ተመሳሳይ ሁኔታ አሳልፈዋል:: ማዕዶት ከድሮው ባህሪዋ በተለየ ሁኔታ ከሱ ጋር ስትሆን ሞቅ እስኪላት መጠጣት መጀመሯ ታውቋታል። ግን እያቀበጠ ስለሚያጠጣ ደስ ይላታል፡፡ እንደ ህፃን ስሜቱን መደበቅ የማይችል
መሆኑን እያስተዋለችም አብረውት ለመኖር የማይከብድ ዓይነት ሆኖባት ለማይቀረው የእንመርመር ጥያቄ
እንዲያበረታት ፈጣሪዋን እየተማፀነች ለጋብቻ ተመኝተዋለች
ድንገት ግን ያልጠበቀችው ነገር ተከሰተ፡፡ የወር አበባዋ በቀኑ ሳይመጣ ቀረ፡፡ ግራ ቢገባት መምጫ ቀኑን ኣዛብቶ የማያውቀውን የወር አበባዋን ሳምንት ሙሉ በተስፋ ጠበቀችው።መቅረቱን ስታረጋግጥ ብርክ ያዛት።
በስሜት ውስጥ ሆነን ሳናውቀውየተፈጠረ ስህተት ይኖር ይሆን?! ይኼ አደጋ ነው! ወይ በኔ ወይ
በሱ ላይ የመጣ እያለች አንጎራጎረች :: ልጁንም' ኮ ላይቀበለኝ ፣ ላያምነኝ ይችላል» ብላ አሰበችና ልትነግረው
ፈራች፡፡ እየቆየች ስታስበው ስታብላላው ግን ከመንገር ሌላ አማራጭ አጣችለት:: ሁለታችንም ሳናስበው የወደቅንበት አደጋ ላይ መወያየትና መፍትሄ መፈለግ
አለብን " አለች - ልትነግረው ወሰነችና ደውላ ለማታ ፕሮግራም አስያዘችው።
እንደሌለቹ ቀናት የመዝናናት ስሜት
አልነበራትም ራት መብላት አቅቷት መጠጣትም አስጠልቷት ስለነበር አሞኛል ብላ ዋሸችው:: ከዚያም
ብዙ ሳይቆዩ መብራቱን አጠፋው:: እሱ ስሜት ውስጥ ገብቷል፡፡ እሷግን ሀሳቧ ግራ በገባት ነገር እየተሰረቀ
አስቸግራት በስሜት ልትከተለው አልቻለችም፡፡ እና እሱን ለማስደሰት ብቻ እንደሚፈልገው እየሆነችለት ሳለ
መሀከል ላይ የተለየ ነገር ተሰማት:: ድንገት ጠረጠረችው።ድንጋጤ አስፈንጥራት ተነሳችና መብራቱን ቦግ አድርጋ አበራችው::ሳምሶን ኮንዶሙን በእጁ እንዳንጠለጠለው
ክው ብሎ ቀረ:: ማዕዶትም አንገቱን አንቃ ተንቀጠቀጠች። ከዚያ አንገቱን ለቃ ተስፋ በቆረጠ መንፈስ ፍራሹን እየደበደበችና፤
“አንተ አውሬ ነህ! ጭራቅ ነህ! ተኩሰህ እንደገደልከኝ ቁጣረው..... ምነው? ምን በደልኩህ?...” እያለች ትራሱ ላይ ተደፍታ ተንሰቀሰቀች፡፡ ሳምሶን ድንጋጤው መለስ
ሲልለት ፤
ምን እንዲህ ያደርግሻል? አንቺ ብቻ ነሽ ለህይወትሽ የምታስቢ? እኔ ከማንም ጋር የምጋደም መሰለሽ? ሰው መርጫ ነው" አለ በላይ ሆኖ እንደመቆጣት' እያደረገው
ከአፈርኩ አይመልሰኝ ዓይነት።
“የጅል ወግህን ተወውና ይኼንን ተንኮል የፈፀምክብኝ እውነት ተመርምረህ ቫይረሱ እንዳለብህ ሳታውቅ ከሆነ
ነገ እንመርመር " አለችው - እልህ እያንቀጠቀጣት፡፡
ሳምሶን ትኩር አድርጎ አያትና፤
“ይቻላል አለ - ትከሻዎቹን ከፍ አድርጎ ቁልቁል እየለቀቃቸው:: ዐይኖቹ ውስጥ ግን ፍርሃት በጉልህ ነግሶ ታየ።
እንደተኮራረፉ ልብሶቻቸውን ለብሰው ወጡ፡፡
በማግስቱ ለመመርመር ከተቃጠሩበት አሁን ውጤቷን እየጠበቀችበት ካለው ክሊኒክ ከሰዓቱ ቀድማ ደረሰች፡፡ ለዘመናት የራቀ የመሰላትን ያህል ጊዜ ጠብቃው ሲቀርባት በሞባይል ስልኳ ሞባይል ስልኩ ላይ ደወለችለት። ዘጋባት:: ሰዓቱ ሶስት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ግማሽ ሰዓት አሳልፏል:: ትንሽ ቆየችና ሞክረች። መልሶ ዘጋባት፡፡ ብርክ እንደያዛት ተስፋ ቆርጣ በየመንገዱ እንባዋን ለመዋጥ እየታገለች በኮንትራት ታክሲ ወደቤቷ ሄደች መሥሪያ ቤቷ ደውላ መታመሟን ለአለቃዋ አሳውቀችና ተኛች፡፡ ከሰዓት በኋላ ለሳምሶን በሱቅ ስልክ ደወለችለት
አነሳውና እሷ መሆኗን ሲያውቅ ዘጋባት፡፡
ደጋግማ ሞከረች፡፡ ሊያናግራት ፈቃደኛ አልሆነም…
ማዕዶት የተፈጠረውን ነገር እንደክፉ ቅዥት ስትባንን ለቀናት አሰበችው::
ሳምሶንን ለማግኘት የምታደርገው ጥረትም ጥቅም የሌለው ሆነባት፡፡ ከዚህ ወዲያ ባገኘውስ ምን ያደርግልኛ
ል? ጠላቴን የልጄ አባት አድርጌ አልቀበለው አለችናእርግፍ አድርጋ ተወችው::
እያደር ግን ለራሷ ከመጨነቅ አልፋ በማህፀኗ ውስጥ ስላለው ልጅ ማሰብ ጀመረችና ትናንት ደሟን ለምርመራ ሰጠች….
ማዕዶት የሰመጠችበትን የትዝታ ባህር ዋኝታ ስትጨርስ ያው የተጠናወታት ቫይረሱ ቢገኝብኝስ የሚለው ጭንቀት በውስጧ እያንሰራራ ነበር ። እና
የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሰውነቷን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ሲበላው ቤተሰቦቿ እንኳ ሊያስታምሟት ሲሳቀቁ ፣ከወዳጅ ዘመዶቿ መሀል ተነጥላ ብቻዋን ስትንጠራወዝ ታያት፡፡ በውስጧ የጭንቀት ትኩሳት ተሰራጨ፡፡
ጨምድዶ። ከያዛት ጭንቀት ለመውጣት እያባ ት : ንቀት እየተወራጨች ! 'ቢኖርብኝም ቫይረስ ላለባቸው
❤2👍1
የሚረዳ የእድሜ ማራዘሚያ መድሃኒት አገራችን ገብቷል ይባላል ለምን ያህል ጊዜ እንደሚያቆየኝ ባላውቅም፡፡ ደግሞም ከእውነታ ጋር መኖር ይቻል ይመስለኛ ል።እንዲያወም ባላወቀው ነበር የምጎዳወ ! ! አለች
ከሚያንገላታት ጭፍን ፍርሃት ለመወጣት
ከተቀመጠችበት ተነስታ እየተንጎራደደች
ለጥቂት ጊዜ ወደላይና ወደ ታች ስትንጎራደድ እንደቆየች የወረፋ ቁጥራ ተጠራ:: በድንጋጤ ውሃ ሆነቾ ዐይኖቿ ስለጨለመባት ወንበሩ ላይ ተመልሳ
ቁጭ አለች። ወዲያዉ ግን ሚዛኗን ለመጠበቅ እየተጠነቀቀች ወደተጠራችበት ክፍል ገባች፡፡
የምክር አገልግሎት የምትሰጠው ነርስ በፈገግታ ተቀበለቻት:: ማዕዶት ጭንቀቷ እንዳይታወቅባት የተረጋጋች ለመምሰል እየሞከረች ለሰላምታ ያህል እጅ
ነስታ ወንበሩ ላይ ተቀመጠች።
ነርሷ ፤ ማዕዶት ደም ከመስጠቷ በፊት ከሞላችው ፎርም ላይ የትምህርት ደረጃዋንና ራሷን ለማወቅ ብቻ
ለመመርመር መፈለጓን አንብባ ስለነበር፡
“ጎበዝ! ! አለች-አተካራ እያስተዋለቻት::
አያይዛም “አንድ ሰው ተማረ የሚባለው የነገሮችን ትክክለኛ ገፅታ ለማወቅና ለማገናዘብ ሲጥር ነው፡፡ በጭፍኑ ፣ በስሜቱ ብቻ እየተመራ የሚጓዝ ከሆነ መማሩ ዋጋ የለውም አለቻት መንፈስን በሚያረጋጋ ፈገግታዋ ግርማ ሞገስ ተላብሳ፡ የማዕዶት ልብ ግን ምቱን ጨምሯል በጣም የሚያሳዝንሽ ነገር አብዛኞቹ በክፍተኛ የትምህርት ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎችም እንኳ አንድ አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ካልገቡ በስተቀር ራሳቸውን
ለማወቅና ለማዘጋጀት ብለው አይመረመሩም:: ነርሷ በሚያቀራርብ እንደበት የሚሰማትን ትገልፅላት ቀጠለች:: ማእዶት ግን ትዕግስት አጣች፡፡ የነርሷ ሁኔታ እሷን ለመርዶ የማዘጋጀት ዓይነት ሆነባት:: እና፤
«ሲስተር ሰመጀመሪያ ውጤቴን ልወቀው እለች ረጋ ለማለት የሞከረችው ሁሉ እየከዳት፡፡ ጭንቀቷፊቷ ላይ ወለል ብሎ
ይታያል፡፡ ነርሷ የለመደችው ሁኔታ ስለነበር ፈገግ አለችና ፤
ቫይረሱ በደምሽ ውስጥ አልተገኘም አለች፡፡
ማዕዶት በህልም ዓለም ውስጥ ያለች መሰላት።እና አንደበቷ ታስሮ የባሰውኑ ሃውልት መሰለች።የዓመታት ጭንቀቷ ..
ነርሷ የማዕዶትን ሁኔታ እያስተዋለች ፤
“ይኼ ግን ምን ማለት እንደሆነ መቼም
«ከቫይረሱ ነፃ ነሽ አይደል ያልሽኝ? አለች
ታውቂያለሽ፤- አለች እውነት እየተጠራጠረች።
«ቫይረሱ ዊንዶ ፔሬድ ወይም የመደበቂያ ጊዜ አለሁ፡፡ ስለዚህ በምርመራ ውጤት የሚገለፀው ከሶስት ወር በፊት ያለው ሁኔታ ነው፡፡ ከሶስት ወር ወዲህ
የምትጠራጠሪው ለቫይረሰ የሚያጋልጥ ሁኔታ ካለ ወር በኋላ እንደገና ተመርምረሽ ታረጋግጪያለሽ፡፡ ለወደፊቱም ቢሆን ከምታገቢው ሰው
ጋር እንድ ላይ በግንባር ቀርበሽ ነው ውጤታችሁን መስማት ያለብሽ:: የሀሰት ማስረጃዎች መኖራቸው ተደርሶበታል አለቻት። ፈገግታዋና ግርማ ሞገሷ ፊቷ
ላይ ወለል እንዳለ ነው።
ማዕዶት ግን ደስታም ቁጭትም ተደባልቀው ስሜቷን አሳክሩትና እስከመጨረሻው አላዳመጠቻትም፡፡
ጭንቀት- እንደገና!
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
ከሚያንገላታት ጭፍን ፍርሃት ለመወጣት
ከተቀመጠችበት ተነስታ እየተንጎራደደች
ለጥቂት ጊዜ ወደላይና ወደ ታች ስትንጎራደድ እንደቆየች የወረፋ ቁጥራ ተጠራ:: በድንጋጤ ውሃ ሆነቾ ዐይኖቿ ስለጨለመባት ወንበሩ ላይ ተመልሳ
ቁጭ አለች። ወዲያዉ ግን ሚዛኗን ለመጠበቅ እየተጠነቀቀች ወደተጠራችበት ክፍል ገባች፡፡
የምክር አገልግሎት የምትሰጠው ነርስ በፈገግታ ተቀበለቻት:: ማዕዶት ጭንቀቷ እንዳይታወቅባት የተረጋጋች ለመምሰል እየሞከረች ለሰላምታ ያህል እጅ
ነስታ ወንበሩ ላይ ተቀመጠች።
ነርሷ ፤ ማዕዶት ደም ከመስጠቷ በፊት ከሞላችው ፎርም ላይ የትምህርት ደረጃዋንና ራሷን ለማወቅ ብቻ
ለመመርመር መፈለጓን አንብባ ስለነበር፡
“ጎበዝ! ! አለች-አተካራ እያስተዋለቻት::
አያይዛም “አንድ ሰው ተማረ የሚባለው የነገሮችን ትክክለኛ ገፅታ ለማወቅና ለማገናዘብ ሲጥር ነው፡፡ በጭፍኑ ፣ በስሜቱ ብቻ እየተመራ የሚጓዝ ከሆነ መማሩ ዋጋ የለውም አለቻት መንፈስን በሚያረጋጋ ፈገግታዋ ግርማ ሞገስ ተላብሳ፡ የማዕዶት ልብ ግን ምቱን ጨምሯል በጣም የሚያሳዝንሽ ነገር አብዛኞቹ በክፍተኛ የትምህርት ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎችም እንኳ አንድ አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ካልገቡ በስተቀር ራሳቸውን
ለማወቅና ለማዘጋጀት ብለው አይመረመሩም:: ነርሷ በሚያቀራርብ እንደበት የሚሰማትን ትገልፅላት ቀጠለች:: ማእዶት ግን ትዕግስት አጣች፡፡ የነርሷ ሁኔታ እሷን ለመርዶ የማዘጋጀት ዓይነት ሆነባት:: እና፤
«ሲስተር ሰመጀመሪያ ውጤቴን ልወቀው እለች ረጋ ለማለት የሞከረችው ሁሉ እየከዳት፡፡ ጭንቀቷፊቷ ላይ ወለል ብሎ
ይታያል፡፡ ነርሷ የለመደችው ሁኔታ ስለነበር ፈገግ አለችና ፤
ቫይረሱ በደምሽ ውስጥ አልተገኘም አለች፡፡
ማዕዶት በህልም ዓለም ውስጥ ያለች መሰላት።እና አንደበቷ ታስሮ የባሰውኑ ሃውልት መሰለች።የዓመታት ጭንቀቷ ..
ነርሷ የማዕዶትን ሁኔታ እያስተዋለች ፤
“ይኼ ግን ምን ማለት እንደሆነ መቼም
«ከቫይረሱ ነፃ ነሽ አይደል ያልሽኝ? አለች
ታውቂያለሽ፤- አለች እውነት እየተጠራጠረች።
«ቫይረሱ ዊንዶ ፔሬድ ወይም የመደበቂያ ጊዜ አለሁ፡፡ ስለዚህ በምርመራ ውጤት የሚገለፀው ከሶስት ወር በፊት ያለው ሁኔታ ነው፡፡ ከሶስት ወር ወዲህ
የምትጠራጠሪው ለቫይረሰ የሚያጋልጥ ሁኔታ ካለ ወር በኋላ እንደገና ተመርምረሽ ታረጋግጪያለሽ፡፡ ለወደፊቱም ቢሆን ከምታገቢው ሰው
ጋር እንድ ላይ በግንባር ቀርበሽ ነው ውጤታችሁን መስማት ያለብሽ:: የሀሰት ማስረጃዎች መኖራቸው ተደርሶበታል አለቻት። ፈገግታዋና ግርማ ሞገሷ ፊቷ
ላይ ወለል እንዳለ ነው።
ማዕዶት ግን ደስታም ቁጭትም ተደባልቀው ስሜቷን አሳክሩትና እስከመጨረሻው አላዳመጠቻትም፡፡
ጭንቀት- እንደገና!
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ለኔ_ሲል_አይነጋም
ኢያሱ የሚሉት
በገባኦን ሰማይ ፥ ሲያቆማት ፀሀይን
እጋርድሽ ብዬ
እከልልሽ ብዬ ፥ አንቺን ከሰው ዐይን
ማንም እንዳያይሽ
አይቶ እንዳይመኝሽ ፥ ልቤ ስለሰጋ
እኔ ነኝ እመኚኝ !
በሀገሬ ሰማይ ላይ
ጨለማን ያቆምኩት ፥ መቼም እንዳይነጋ ።
ይኸው ከዛ ወዲህ
ህዝብሽና ህዝቤ
በብርሃን ናፍቆት ፥ ተሰብሮ እየታሽ
በተስፋ መንገድ ላይ ፥ እድሜው እየሸሽ
ጨለማን አቁሜው
“ይነጋል " ነው ቃሉ ፥ ሁሌም እየመሽ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
ኢያሱ የሚሉት
በገባኦን ሰማይ ፥ ሲያቆማት ፀሀይን
እጋርድሽ ብዬ
እከልልሽ ብዬ ፥ አንቺን ከሰው ዐይን
ማንም እንዳያይሽ
አይቶ እንዳይመኝሽ ፥ ልቤ ስለሰጋ
እኔ ነኝ እመኚኝ !
በሀገሬ ሰማይ ላይ
ጨለማን ያቆምኩት ፥ መቼም እንዳይነጋ ።
ይኸው ከዛ ወዲህ
ህዝብሽና ህዝቤ
በብርሃን ናፍቆት ፥ ተሰብሮ እየታሽ
በተስፋ መንገድ ላይ ፥ እድሜው እየሸሽ
ጨለማን አቁሜው
“ይነጋል " ነው ቃሉ ፥ ሁሌም እየመሽ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በጥላሁን
የኔም የጓደኛዬም ፍቅረኞች ሁለቱም ሀብታም የሚለው ምን አይነት ሀብታም? የሚለን ጥያቄ የማያብራራ ጥቅል መጠሪያ ከማይገልፃቸው ከበቃቸው ሀብታም ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው።
የኔና የጋደኛዬ ቤተሰቦች ለመኖር የማይቸገሩ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ በመባል የሚጠራውን አይነት ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ። የኔ ፍቅር ሊሊ ስትባል የጋደኛዬ ፍቅረኛ ኪሪያ ትባላለች ትርጉሙስ ካላችሁ እኔን ሳይሆን እራሷን ጠይቋት ።
ገና በአዳማ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ አመት የአካውንቲንግ ተማሪ ነኝ ፍቅር የጀመርኩት አስረኛ ክፍል ሆኜ ነው ታድያ ለፍቅር ምን አጣደፈህ አትበሉኝ የደረሰበት እንኳን እንደማይለኝ አውቃለሁ ያልደረሰባችሁ ካላችሁ
" አርፎ ትምህርቱን አይማርም ለፍቅሩ ይደርስበታል!" ምናምን እያለችሁ ብትሞልጩኝም እችለዋለሁ።
መጀመሪያ በጥፊ ተመቶ ቀጥሎ በኮብል የተፈነከተ ሰው የመጀመሪያውን ጥፊ ወድያው ረሳው ቢሉት ባይረሳው ገረመውን ይገርመው ነበር አለ ገረመው
የራሴ አባባል ነች ስለዚህ አሁን በተቆለለብኝ ዱብዳ የተነሳ ጭንቅላቴ ስድብም ብጨቃም ዝልዘላም አይሰማውም አቅማችሁ የቻለውን ያህል ተሳደቡ አጋጣሚውን ተጠቀሙበት።
እናላችሁ ••• ከዚቹ ከኔ ፍቅር ከሊሊ ጋር ፍቅር የጀመርነው ከሁለት አመት በፊት አስረኛ ክፍል እያለሁ ነው ። አንድ ክፍል ነበርን ቀድሜ የወደድኳት እኔ ነበርኩ እንደወደድኳት ግን ነግሪያት አላውቅም እንኳን ለሷ ልነግራት እኔ እራሴ የያዘኝ ፍቅር መሆኑን መች ቶሎ ገባኝና ብቻ እኔ የማውቀው
ስተኛ ትዝ እንደምትለኝ ።
ስበላ እንደማስታውሳት።
ሴት ልጅ ከሩቁ ባየሁ ቁጥር እሷ እንደምትመስለኝ።
ሳትጠራኝ የጠራችኝ እየመሰለኝ ብንን እንደምል።
ጥዋት ገብቼ ለመማር ሳይሆን እሷን ለማየት ከክፍሉ ተማሪ በሙሉ ቀድሜ እንደምገኝ።
ሌሎች ወንዶች ሲያናግራት የሆነ የሚያቃጥል ነገር እንደሚሰማኝ በለው በለው ንከሰው ቦጭቀው እንደሚለኝ።
አጠገቤ ስትቀመጥ ላብ እንደሚያሰምጠኝ ።
ስታወራኝ ምላሴ ወደውስጥ ገብቶ እማወራው ነገር እንደሚጠፋብኝ ።
ቅዳሜና እሁድ የሚባል ነገር እንደሚያስጠላኝ ።
ሰኞ እንደምፅአት ቀን እንደምትርቅብኝ ብቻ ነበር።
ለእንደኔ አይነቱ ጭምት እንኳን ፍቅር ሊጀምር የፍቅር ፊልም እንዲያይ አባቱ የማይፈቅድለት
ከደብተሩና ከቤተሰቦቹ ውጪ ከሌላው አለም ጋር ሳይተዋወቅ ያደገ ልጅ ከላይ የታዩበት ምልክቶች የፍቅር ምልክት መሆናቸውን መለየት ከባድ ነበር አይ ፍቅር ዶክተር አልባ ህመም ።
እናማ በአንድ አጋጣሚ የቤተሰብ ፕሮግራም ላይ ለአንድ የአክስቴ ልጅ የፍቅር ህመም ምልክቶቼን አውራሁለት
በቃ ሳያት ደስ ይለኛል ተለይቻት ፊቷ ከፊቴ ላይ አይጠፋም ለምን እንደሆነ እኔ እንጃ ከሌላ ወንድ ጋር ስታወራ እናደዳለሁ ስለው
ረጅም ሳቅ ሳቀብኝ በትግስት ጠበኩት የትግስቴን ፍሬ ነገረኝ ። "ፍቅር ይዞሀል ሶልዬ " አለኝ። ብትችል ትምህርትህን እስክትጨርስ እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ባትገባ ይሻል ነበር
አሁን ግን ከነገርከኝ አንፃር ላትመለስ ተዘፍቀህበታል እና ንገራት" የሚለውን አስከትሎ ተለየኝ ። ንገራት! ንገራት! ንገራት! የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኞ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ ። ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በጥላሁን
የኔም የጓደኛዬም ፍቅረኞች ሁለቱም ሀብታም የሚለው ምን አይነት ሀብታም? የሚለን ጥያቄ የማያብራራ ጥቅል መጠሪያ ከማይገልፃቸው ከበቃቸው ሀብታም ቤተሰቦች የተወለዱ ናቸው።
የኔና የጋደኛዬ ቤተሰቦች ለመኖር የማይቸገሩ መካከለኛ የኑሮ ደረጃ በመባል የሚጠራውን አይነት ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ። የኔ ፍቅር ሊሊ ስትባል የጋደኛዬ ፍቅረኛ ኪሪያ ትባላለች ትርጉሙስ ካላችሁ እኔን ሳይሆን እራሷን ጠይቋት ።
ገና በአዳማ ዩኒቨርስቲ የአንደኛ አመት የአካውንቲንግ ተማሪ ነኝ ፍቅር የጀመርኩት አስረኛ ክፍል ሆኜ ነው ታድያ ለፍቅር ምን አጣደፈህ አትበሉኝ የደረሰበት እንኳን እንደማይለኝ አውቃለሁ ያልደረሰባችሁ ካላችሁ
" አርፎ ትምህርቱን አይማርም ለፍቅሩ ይደርስበታል!" ምናምን እያለችሁ ብትሞልጩኝም እችለዋለሁ።
መጀመሪያ በጥፊ ተመቶ ቀጥሎ በኮብል የተፈነከተ ሰው የመጀመሪያውን ጥፊ ወድያው ረሳው ቢሉት ባይረሳው ገረመውን ይገርመው ነበር አለ ገረመው
የራሴ አባባል ነች ስለዚህ አሁን በተቆለለብኝ ዱብዳ የተነሳ ጭንቅላቴ ስድብም ብጨቃም ዝልዘላም አይሰማውም አቅማችሁ የቻለውን ያህል ተሳደቡ አጋጣሚውን ተጠቀሙበት።
እናላችሁ ••• ከዚቹ ከኔ ፍቅር ከሊሊ ጋር ፍቅር የጀመርነው ከሁለት አመት በፊት አስረኛ ክፍል እያለሁ ነው ። አንድ ክፍል ነበርን ቀድሜ የወደድኳት እኔ ነበርኩ እንደወደድኳት ግን ነግሪያት አላውቅም እንኳን ለሷ ልነግራት እኔ እራሴ የያዘኝ ፍቅር መሆኑን መች ቶሎ ገባኝና ብቻ እኔ የማውቀው
ስተኛ ትዝ እንደምትለኝ ።
ስበላ እንደማስታውሳት።
ሴት ልጅ ከሩቁ ባየሁ ቁጥር እሷ እንደምትመስለኝ።
ሳትጠራኝ የጠራችኝ እየመሰለኝ ብንን እንደምል።
ጥዋት ገብቼ ለመማር ሳይሆን እሷን ለማየት ከክፍሉ ተማሪ በሙሉ ቀድሜ እንደምገኝ።
ሌሎች ወንዶች ሲያናግራት የሆነ የሚያቃጥል ነገር እንደሚሰማኝ በለው በለው ንከሰው ቦጭቀው እንደሚለኝ።
አጠገቤ ስትቀመጥ ላብ እንደሚያሰምጠኝ ።
ስታወራኝ ምላሴ ወደውስጥ ገብቶ እማወራው ነገር እንደሚጠፋብኝ ።
ቅዳሜና እሁድ የሚባል ነገር እንደሚያስጠላኝ ።
ሰኞ እንደምፅአት ቀን እንደምትርቅብኝ ብቻ ነበር።
ለእንደኔ አይነቱ ጭምት እንኳን ፍቅር ሊጀምር የፍቅር ፊልም እንዲያይ አባቱ የማይፈቅድለት
ከደብተሩና ከቤተሰቦቹ ውጪ ከሌላው አለም ጋር ሳይተዋወቅ ያደገ ልጅ ከላይ የታዩበት ምልክቶች የፍቅር ምልክት መሆናቸውን መለየት ከባድ ነበር አይ ፍቅር ዶክተር አልባ ህመም ።
እናማ በአንድ አጋጣሚ የቤተሰብ ፕሮግራም ላይ ለአንድ የአክስቴ ልጅ የፍቅር ህመም ምልክቶቼን አውራሁለት
በቃ ሳያት ደስ ይለኛል ተለይቻት ፊቷ ከፊቴ ላይ አይጠፋም ለምን እንደሆነ እኔ እንጃ ከሌላ ወንድ ጋር ስታወራ እናደዳለሁ ስለው
ረጅም ሳቅ ሳቀብኝ በትግስት ጠበኩት የትግስቴን ፍሬ ነገረኝ ። "ፍቅር ይዞሀል ሶልዬ " አለኝ። ብትችል ትምህርትህን እስክትጨርስ እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ባትገባ ይሻል ነበር
አሁን ግን ከነገርከኝ አንፃር ላትመለስ ተዘፍቀህበታል እና ንገራት" የሚለውን አስከትሎ ተለየኝ ። ንገራት! ንገራት! ንገራት! የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኞ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ ። ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1
#የሚሰሙ_ህልሞች
እረፍ ልል ተኛሁ
በአልጋ ጎዳና ፥ እንቅልፌ ወሰደኝ
ከማይዳሰሱ
ከማይታዩ ህልሞች ፥ አድርሶ አላመደኝ።
ጨለማ አይደለም
ብርሃንም አይደለም ፥ ድምፆች ይሰማሉ
እንደ ነፋስ አይነት ፥ የወንድም ያልሆኑ የሴትም ያይደሉ
ሚታይ አካል የለም
የሚሰሙ ህልሞች ፥ ኬ'ትም ይመጣሉ፡፡
ይመስለኛል በህልሜ
የሚታዩን ህልሞች
ዓለም እያለመ ፥ ሊያስፈታ ሲባትል
ከጫጫታ መሃል
አንድ ህልም ሰማሁ ፥ ተፈተሃል ምትል።
እላት ይመስለኛል ፥ “ከምን ነው ምፈታው?”
“መልስህ ታስሯል” የሚል
ሌላ ድምፅ ይመጣል ፥ ወጥቶ ከጫጫታው።
“ምን ነበረ መልሱ?”
የምል ይመሥለኛል ፥ ታፍኜ በሲቃ
ከጫጫታው መሃል
ሌላ ድምፅ ይለኛል ፥ “መልስ የለም ሳትነቃ።”
🔘በዕውቀቱ ስዪም🔘
እረፍ ልል ተኛሁ
በአልጋ ጎዳና ፥ እንቅልፌ ወሰደኝ
ከማይዳሰሱ
ከማይታዩ ህልሞች ፥ አድርሶ አላመደኝ።
ጨለማ አይደለም
ብርሃንም አይደለም ፥ ድምፆች ይሰማሉ
እንደ ነፋስ አይነት ፥ የወንድም ያልሆኑ የሴትም ያይደሉ
ሚታይ አካል የለም
የሚሰሙ ህልሞች ፥ ኬ'ትም ይመጣሉ፡፡
ይመስለኛል በህልሜ
የሚታዩን ህልሞች
ዓለም እያለመ ፥ ሊያስፈታ ሲባትል
ከጫጫታ መሃል
አንድ ህልም ሰማሁ ፥ ተፈተሃል ምትል።
እላት ይመስለኛል ፥ “ከምን ነው ምፈታው?”
“መልስህ ታስሯል” የሚል
ሌላ ድምፅ ይመጣል ፥ ወጥቶ ከጫጫታው።
“ምን ነበረ መልሱ?”
የምል ይመሥለኛል ፥ ታፍኜ በሲቃ
ከጫጫታው መሃል
ሌላ ድምፅ ይለኛል ፥ “መልስ የለም ሳትነቃ።”
🔘በዕውቀቱ ስዪም🔘
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በጥላሁን
ንገራት ንገራት ንገራት የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ. አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኛ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ
ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
ምን ብዬ እንደምጀምር ምን ብዬ እንደምቀጥል እና ምን ብዬ እንደምደመድም የትኛው ሀሳብ መቅደም የትኛው መከተል እንዳለበት መግቢያ ማጠናከሪያ መደምደሚያ ብዬ ከፋፍዬ ላስቀምጥ ብሞክርም ውስጤ ያለውን የፍቅር ንዳድ በደንብ ሊገልፁላት የሚችሉ ቃላቶች ማግኘት ፈተና ሆነብኝ።
መግቢያ:- ሊሊዬ ለብቻሽ ላናግርሽ የፈለኩት አንድ ጉዳይ ነበረኝ ለዛ ነው ለብቻሽን ላናግርሽ የፈለኩት....
ወይ ጣጣ እሄ ደሞ የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ብድር የሚጠይቅ ሰው የሚጠቀምበት የመግቢያ ንግግር ይመስላ አቦ አልኩና እላዩ ላይ ትልቅ የኤክስ ምልክት አጋድሜ ግድግዳውን ተደግፌ ከክፍሉ ሴት ተማሪዎች በሙሉ እንኳን የትምህርትቤቱን ይንፎርም የተቀዳደደ ጆንያ ለብሳ ብትመጣ ውበቷ የማይጎድልብኝን የለበሰችው የሳቀችው የተናገረችው ሁሉ ልዩ እና ውብ መስሎ የሚታየኝን እኔ ከተቀመጥኩበት በስተግራ እክፍሉ መሀል ላይ ከሁለት ሴት ጓደኛቿ መሀል ላይ ያለችውን ሊሊዬን ከጀርባ እያየሁ የምላትን ማሰብ ጀመርኩ።
የመጣልኝን ሁለተኛውን ሀሳብ መፃፍ ጀመርኩ•••
ፅሁፉ እየመራኝ ይሁን እኔ እየመራሁት ባይገባኝም ፊደሎቹ እየተፈላለጉ መመሳሰል ጀመሩ ። ሳላስበው እንደመግጠምም አደረገኝ•••
ምን መሰለሽ ? እሄውልሽ ሊሊዬ
እኔ ባንቺ ፍቅር ሁሉን ነገር ጥዬ
ሳይሽ ደስ ይለኛል
ካጠገብሽ ስርቅ ጭንቀት ይወረኛል
ሲለው ፍርሀት ፍርሀት ብርድ ብርድ ይለኛል
በቤተሰብ መሀል እቤቴ ቁጭ ብዬ
ብቻዬን የሆንኩኝ ያህል ይሰማኛል
ሳቅሽ ይርበኛል
አንቺ ሳትኖሪ ድምፅሽ ይጠራኛል
በውድቅት ለሊት ሰው ሁሉ ተኝቶ
እኔ አስብሻለሁ
አንቺ ሳትመጪ ኮቴሽ ይሰማኛል
የቱንስ ልንገርሽ የቱኛውን ትቼ
በፍቅርሽ ሳስቼ እራሴን ረስቼ
ምግብ መብላት ትቼ
መኖር እንደጀመርኩ እኔን ላንቺ ትቼ
ስትስቂ ካየሁ ባንቺ ደስታ ስስቅ
የከፋሽ ሲመስለኝ ሲልብኝ ድብልቅልቅ
በጣም የሚገርመው ይህ ሁሉ በኔ ላይ ሲሆን የነበረው በፍቅርሽ መያዜን ከቶም ሳልረዳው ጭራሽ ሳይገባኝ ነው
እናም የኔ ፍቅር
ፍቃድሽ ከሆነ ወድሻለሁና
ያንቺ ልሁንና ላንቺው ፍቅር ልኑር።
አሁን ይሄን ባነብላት ከዚህ በፊት ሁለት ስንኝ ያላት ግጥም ስፅፍ አይታኝ አታውቅ ላንቺ የውስጤን ይገልፅልኛል ብዬ የፃፍኩት ግጥም ነው ብላት ያንን ደስ የሚል ሳቋን ስቃ። አይ ሶልዬ በዳዲ ሞት ሙድ መያዝህን ተውና ግጥሙን ወድጄዋለሁ ይልቅ ኬትኛው መፅሀፍ ላይ ነው ያገኘከው ብትለኝ ምን ይውጠኛል ከዛ ቡሀላ ቁምነገር ነው ብላትም አላግጣብኝ ነው እምትሄደው ይቅርብኝ።
ባይሆን እሄን ግጥም ምናልባት ከሊሊ በላይ ማፍቀሬን ባልነግረውም የሚረዳኝ እና ውስጤን የሚያውቀው የፍቅር አምላክ አሳክቶልኝ እሺ ብላኝ አብራኝ ከሆነች ቡሀላ ባነብላት ይሻላል ።
ይሄም ተሰረዘ ። ግጥሙን የፃፍኩባትን ወረቀት በጥንቃቄ አጣጥፌ ኪሴ ውስጥ ከተትኩና ሌላ ባዶ ወረቀት ፊቴ አስቀመጥኩ።
ይልቅ እንድታምነኝ ንግግሬን በሀይለ ቃል አጅቤ ማዥጎድጎድ እንዳለብኝ ውስጤ ሹክ አለኝ።
በቃ በፍቅርሽ ጨርቄን ጥዬ ማበዴ ነው አልቻልኩም እኔስ አፍቅሬሽ ልበድ ላንቺ ማበዴ አይበዛብሽም ግን ደግሞ የኔ ማበድ ለቤቴሰቦቼ ከባድ ነው የማይቋቋሙት ትልቅ ሀዘን ውስጥ እንደሚገቡ አውቃለሁ ያንን ሳስበው ደሞ እንደዛ የሚንሰፈሰፉልኝ ቤተሰቦቼ በኔ ምክንያት ተጎድተው ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ ። እውነቴን ነው ሊሊዬ እኔ አብጄ ሁሌ እያዩኝ የስቃይ ሂወት ከሚገፉ ዛሬውኑ ብሞት ይሻለኛል።
እሄን የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ከፊሉ ዛቻ ከፊሉ ኑዛዜ የመሰለ ፅሁፍ ወረቀት ላይ አስፍሬ የራሴ ሀሳብ ሳይሆን ሰው ፅፎ የሰጠኝ ይመስል መልሼ ሳነበው ተናደድኩ። ወረቀቱን በጫጭቄ ጣልኩት።
ሁለተኛው የትምህርት ክፍለ ግዜ ተጠናቆ ሶስተኛው ተጋመሰ።ሲደወል እረፍት ነው። ሊሊን አዋራታለሁ። እስካሁን ግን ምን እንደምላት አልወሰንኩም ።
ደቂቃዎቹ እያለቁ በሄዱ ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ። የእረፍት ሰአት ሲደወል ።መፃፉን አቃረጥኩና ብእሩን ዴክሱ ላይ አስቀምጬ እጄን አጣጥፌ ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ•••
ቆይ ግን ፍቅር እኔን የያዘኝ አለማምዶ ነው እንዴ? ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነና እንዴት እንደሚያደርግ እንደማላውቅ እያወቀ አደል እንዴ ዘሎ የተከመረብኝ ታድያ ምን እንደምል እንዴት እንደማስረዳት እንዴት እንደማሳምናት እያሰብኩ ምን አጨናነቀኝ።
ልክ ሳገኛት ለስንት ወራት ውስጤ ተቀምጦ የነበረው ፍቅር እራሱን ይግለጥላት።
ሰው ምን ብዬ ባስረዳት ታምነኛለች እያለ መጨነቅ ያለበት ፍቅሩ የውሸት ከሆነ ብቻ ነው። እኔ እሷን ማፍቀሬ ግን እውነት ነው። እውነት ደሞ እራሱን የሚገልጥበት መንገድ አያጣም። የቃላት ቀመር የንግግር ልምምድ አያስፈልገውም። ምክንያቱም ምን ልበል ብዬ አላስብም የምለው ነገር በሙሉ የሆንኩትን ነው።
የሆነውን ነገር መናገር ቢያቅተኝ እንኳን እሷ ፊት ቆሜ የልቤን ህመም መግለጥ አለመቻሌ በራሱ ፍቅር ነው አልኩና።
ያሰብኩትን ደግሜ ሳስበው ይገርማል ፍቅር ፈላስፋም፣ ዘፋኝም፣ ገጣሚም፣ እብድም፣ ፀሀፊም፣ አልቃሽ ደስተኛም ተካዥም፣ ብቸኛም ያረጋል ሲባል አይገባኝም ነበር ዛሬ ግን ያሰብኩት ምን ማለት እንደሆነ ለራሴም ግራ እስኪገባኝ ፈላስፋ አድርጎኝ አረፈው።
ግን ይሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትምሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር
ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ
እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
💫የቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በጥላሁን
ንገራት ንገራት ንገራት የሚለው ቃሉ ጭንቃላቴ ላይ ሲያቃጭልብኝ አምሽቶ. አነጋ ። እነግራታለሁ ወሰንኩ ሰኛ ለሊት አስራ አንድ ሰአት ተነስቼ ገላዬን ታጠብኩ
ጥዋት ሶስት ፔሬድ ሙሉ የተማርኩትም የፃፍኩትም ትዝ አይለኝም ።
ምን እንደምላት ስፅፍ ስለማመድ ቆየሁ•••
ምን ብዬ እንደምጀምር ምን ብዬ እንደምቀጥል እና ምን ብዬ እንደምደመድም የትኛው ሀሳብ መቅደም የትኛው መከተል እንዳለበት መግቢያ ማጠናከሪያ መደምደሚያ ብዬ ከፋፍዬ ላስቀምጥ ብሞክርም ውስጤ ያለውን የፍቅር ንዳድ በደንብ ሊገልፁላት የሚችሉ ቃላቶች ማግኘት ፈተና ሆነብኝ።
መግቢያ:- ሊሊዬ ለብቻሽ ላናግርሽ የፈለኩት አንድ ጉዳይ ነበረኝ ለዛ ነው ለብቻሽን ላናግርሽ የፈለኩት....
ወይ ጣጣ እሄ ደሞ የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ብድር የሚጠይቅ ሰው የሚጠቀምበት የመግቢያ ንግግር ይመስላ አቦ አልኩና እላዩ ላይ ትልቅ የኤክስ ምልክት አጋድሜ ግድግዳውን ተደግፌ ከክፍሉ ሴት ተማሪዎች በሙሉ እንኳን የትምህርትቤቱን ይንፎርም የተቀዳደደ ጆንያ ለብሳ ብትመጣ ውበቷ የማይጎድልብኝን የለበሰችው የሳቀችው የተናገረችው ሁሉ ልዩ እና ውብ መስሎ የሚታየኝን እኔ ከተቀመጥኩበት በስተግራ እክፍሉ መሀል ላይ ከሁለት ሴት ጓደኛቿ መሀል ላይ ያለችውን ሊሊዬን ከጀርባ እያየሁ የምላትን ማሰብ ጀመርኩ።
የመጣልኝን ሁለተኛውን ሀሳብ መፃፍ ጀመርኩ•••
ፅሁፉ እየመራኝ ይሁን እኔ እየመራሁት ባይገባኝም ፊደሎቹ እየተፈላለጉ መመሳሰል ጀመሩ ። ሳላስበው እንደመግጠምም አደረገኝ•••
ምን መሰለሽ ? እሄውልሽ ሊሊዬ
እኔ ባንቺ ፍቅር ሁሉን ነገር ጥዬ
ሳይሽ ደስ ይለኛል
ካጠገብሽ ስርቅ ጭንቀት ይወረኛል
ሲለው ፍርሀት ፍርሀት ብርድ ብርድ ይለኛል
በቤተሰብ መሀል እቤቴ ቁጭ ብዬ
ብቻዬን የሆንኩኝ ያህል ይሰማኛል
ሳቅሽ ይርበኛል
አንቺ ሳትኖሪ ድምፅሽ ይጠራኛል
በውድቅት ለሊት ሰው ሁሉ ተኝቶ
እኔ አስብሻለሁ
አንቺ ሳትመጪ ኮቴሽ ይሰማኛል
የቱንስ ልንገርሽ የቱኛውን ትቼ
በፍቅርሽ ሳስቼ እራሴን ረስቼ
ምግብ መብላት ትቼ
መኖር እንደጀመርኩ እኔን ላንቺ ትቼ
ስትስቂ ካየሁ ባንቺ ደስታ ስስቅ
የከፋሽ ሲመስለኝ ሲልብኝ ድብልቅልቅ
በጣም የሚገርመው ይህ ሁሉ በኔ ላይ ሲሆን የነበረው በፍቅርሽ መያዜን ከቶም ሳልረዳው ጭራሽ ሳይገባኝ ነው
እናም የኔ ፍቅር
ፍቃድሽ ከሆነ ወድሻለሁና
ያንቺ ልሁንና ላንቺው ፍቅር ልኑር።
አሁን ይሄን ባነብላት ከዚህ በፊት ሁለት ስንኝ ያላት ግጥም ስፅፍ አይታኝ አታውቅ ላንቺ የውስጤን ይገልፅልኛል ብዬ የፃፍኩት ግጥም ነው ብላት ያንን ደስ የሚል ሳቋን ስቃ። አይ ሶልዬ በዳዲ ሞት ሙድ መያዝህን ተውና ግጥሙን ወድጄዋለሁ ይልቅ ኬትኛው መፅሀፍ ላይ ነው ያገኘከው ብትለኝ ምን ይውጠኛል ከዛ ቡሀላ ቁምነገር ነው ብላትም አላግጣብኝ ነው እምትሄደው ይቅርብኝ።
ባይሆን እሄን ግጥም ምናልባት ከሊሊ በላይ ማፍቀሬን ባልነግረውም የሚረዳኝ እና ውስጤን የሚያውቀው የፍቅር አምላክ አሳክቶልኝ እሺ ብላኝ አብራኝ ከሆነች ቡሀላ ባነብላት ይሻላል ።
ይሄም ተሰረዘ ። ግጥሙን የፃፍኩባትን ወረቀት በጥንቃቄ አጣጥፌ ኪሴ ውስጥ ከተትኩና ሌላ ባዶ ወረቀት ፊቴ አስቀመጥኩ።
ይልቅ እንድታምነኝ ንግግሬን በሀይለ ቃል አጅቤ ማዥጎድጎድ እንዳለብኝ ውስጤ ሹክ አለኝ።
በቃ በፍቅርሽ ጨርቄን ጥዬ ማበዴ ነው አልቻልኩም እኔስ አፍቅሬሽ ልበድ ላንቺ ማበዴ አይበዛብሽም ግን ደግሞ የኔ ማበድ ለቤቴሰቦቼ ከባድ ነው የማይቋቋሙት ትልቅ ሀዘን ውስጥ እንደሚገቡ አውቃለሁ ያንን ሳስበው ደሞ እንደዛ የሚንሰፈሰፉልኝ ቤተሰቦቼ በኔ ምክንያት ተጎድተው ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ ። እውነቴን ነው ሊሊዬ እኔ አብጄ ሁሌ እያዩኝ የስቃይ ሂወት ከሚገፉ ዛሬውኑ ብሞት ይሻለኛል።
እሄን የፍቅር ጥያቄ ሳይሆን ከፊሉ ዛቻ ከፊሉ ኑዛዜ የመሰለ ፅሁፍ ወረቀት ላይ አስፍሬ የራሴ ሀሳብ ሳይሆን ሰው ፅፎ የሰጠኝ ይመስል መልሼ ሳነበው ተናደድኩ። ወረቀቱን በጫጭቄ ጣልኩት።
ሁለተኛው የትምህርት ክፍለ ግዜ ተጠናቆ ሶስተኛው ተጋመሰ።ሲደወል እረፍት ነው። ሊሊን አዋራታለሁ። እስካሁን ግን ምን እንደምላት አልወሰንኩም ።
ደቂቃዎቹ እያለቁ በሄዱ ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ። የእረፍት ሰአት ሲደወል ።መፃፉን አቃረጥኩና ብእሩን ዴክሱ ላይ አስቀምጬ እጄን አጣጥፌ ከራሴ ጋር ማውራት ጀመርኩ•••
ቆይ ግን ፍቅር እኔን የያዘኝ አለማምዶ ነው እንዴ? ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነና እንዴት እንደሚያደርግ እንደማላውቅ እያወቀ አደል እንዴ ዘሎ የተከመረብኝ ታድያ ምን እንደምል እንዴት እንደማስረዳት እንዴት እንደማሳምናት እያሰብኩ ምን አጨናነቀኝ።
ልክ ሳገኛት ለስንት ወራት ውስጤ ተቀምጦ የነበረው ፍቅር እራሱን ይግለጥላት።
ሰው ምን ብዬ ባስረዳት ታምነኛለች እያለ መጨነቅ ያለበት ፍቅሩ የውሸት ከሆነ ብቻ ነው። እኔ እሷን ማፍቀሬ ግን እውነት ነው። እውነት ደሞ እራሱን የሚገልጥበት መንገድ አያጣም። የቃላት ቀመር የንግግር ልምምድ አያስፈልገውም። ምክንያቱም ምን ልበል ብዬ አላስብም የምለው ነገር በሙሉ የሆንኩትን ነው።
የሆነውን ነገር መናገር ቢያቅተኝ እንኳን እሷ ፊት ቆሜ የልቤን ህመም መግለጥ አለመቻሌ በራሱ ፍቅር ነው አልኩና።
ያሰብኩትን ደግሜ ሳስበው ይገርማል ፍቅር ፈላስፋም፣ ዘፋኝም፣ ገጣሚም፣ እብድም፣ ፀሀፊም፣ አልቃሽ ደስተኛም ተካዥም፣ ብቸኛም ያረጋል ሲባል አይገባኝም ነበር ዛሬ ግን ያሰብኩት ምን ማለት እንደሆነ ለራሴም ግራ እስኪገባኝ ፈላስፋ አድርጎኝ አረፈው።
ግን ይሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትምሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር
ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ
እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
💫የቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1🔥1
#ወደ_ምንም_የሚያደርሰው_መንገድ
ቸኳይ የሚመስለው
ፈጣን የሚመስለው .
በውልውል መኪና
በፋሽን መጫሚያ
ወይም በባዶ እግሩ
ሽው እልም የሚለው
ይኼ ሁሉ ምሁር፣ ይኼ ሁሉ ማይም
መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም
ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
ቸኳይ የሚመስለው
ፈጣን የሚመስለው .
በውልውል መኪና
በፋሽን መጫሚያ
ወይም በባዶ እግሩ
ሽው እልም የሚለው
ይኼ ሁሉ ምሁር፣ ይኼ ሁሉ ማይም
መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም
ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
👍1
#በኔ_የደረሰ•
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በጥላሁን
...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በጥላሁን
...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ፍቅር_ሲሸሽ
አንድም ፍጡር ላይኖር ከስ'ተት የጸዳ
ሆድሽ እጅግ ጠቦ ልብሽ እጅግ ከብዳ
ጠርጥረሽ ላትበይው
አኝከሽ ላትውጪው
በማላመጥ ብዛት ኮስሶ አኮሰስሽው
ጓዴ የሆነውን ዘርዝሬ ብነግርሽ
በጉዳቱ አዝነሽ
እጅግ ተቆጭተሽ
እምዬ ማሪያምን አብረሽው በቆረብሽ
የጨረቃ ወጋገን ፈክቶ በሰማይ ላይ
አንቀላፍታ ሳለች ምድሪቷ በአንድ ላይ
ፍቅርን ሲለግስሽ ስትሰጪው ፍቅርን
ድንገት አውሬ አይቶ በቁም ሲባንን
ነግረሽው ነበረ ውሻ መሆኑን
ነገር ግን . . . ነገር ግን . . .
ሽሽትን መረጠ ከነፈ ከቤቱ
አንድያ ነውና ለናትና አባቱ
አንቺ ግን . . . አንቺ ግን .
ደብቀሽ ሳትይዥ ይሄ ሚስጥሩን
ሃገር እንዲያውቅ አርገሽ ትንሹ ልቡን
“ ጥንቸሊቱ ” አስባልሽው መጠሪያ ስሙን
ውቢት . . .ውቢት .
ሊሳሳት ይችላል ማንም በቀን ውሎ
ቢሮጥ ምን ነበረ እኔን አስከትሎ
ብለሽ ተቀይመሽ ልብሽን አትዝጊው
ለበጎ ነው ብለሽ ሁሉንም አስቢው
ደ'ሞም ዱብ እዳ ነው አስጨናቂ ብርቱ
አውሬ ሲያጋጥመው ሳያስብ ከፊቱ
ሊሆን ደ'ሞ ይችላል የደፈጣ ስልቱ
ይህን አውሬ ፍጡር ሊያቆስለው በብርቱ
ብለሽ አስቢና አፍቅሪው ካ'ንጀትሽ
ታድያ ምኑ ላይ ነው ሩሩ ሴትነትሽ
ውቢት........
ምን አልባት . . .ምን አልባት . . .
የወሬ ነጋሪ ጭራሽ እንዳይጠፋ
ይሆናል መሮጡ ሳይነግር ከፊትሽ
ሲያወራው ለመኖር ዝነኛውን ፍቅርሽ፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
አንድም ፍጡር ላይኖር ከስ'ተት የጸዳ
ሆድሽ እጅግ ጠቦ ልብሽ እጅግ ከብዳ
ጠርጥረሽ ላትበይው
አኝከሽ ላትውጪው
በማላመጥ ብዛት ኮስሶ አኮሰስሽው
ጓዴ የሆነውን ዘርዝሬ ብነግርሽ
በጉዳቱ አዝነሽ
እጅግ ተቆጭተሽ
እምዬ ማሪያምን አብረሽው በቆረብሽ
የጨረቃ ወጋገን ፈክቶ በሰማይ ላይ
አንቀላፍታ ሳለች ምድሪቷ በአንድ ላይ
ፍቅርን ሲለግስሽ ስትሰጪው ፍቅርን
ድንገት አውሬ አይቶ በቁም ሲባንን
ነግረሽው ነበረ ውሻ መሆኑን
ነገር ግን . . . ነገር ግን . . .
ሽሽትን መረጠ ከነፈ ከቤቱ
አንድያ ነውና ለናትና አባቱ
አንቺ ግን . . . አንቺ ግን .
ደብቀሽ ሳትይዥ ይሄ ሚስጥሩን
ሃገር እንዲያውቅ አርገሽ ትንሹ ልቡን
“ ጥንቸሊቱ ” አስባልሽው መጠሪያ ስሙን
ውቢት . . .ውቢት .
ሊሳሳት ይችላል ማንም በቀን ውሎ
ቢሮጥ ምን ነበረ እኔን አስከትሎ
ብለሽ ተቀይመሽ ልብሽን አትዝጊው
ለበጎ ነው ብለሽ ሁሉንም አስቢው
ደ'ሞም ዱብ እዳ ነው አስጨናቂ ብርቱ
አውሬ ሲያጋጥመው ሳያስብ ከፊቱ
ሊሆን ደ'ሞ ይችላል የደፈጣ ስልቱ
ይህን አውሬ ፍጡር ሊያቆስለው በብርቱ
ብለሽ አስቢና አፍቅሪው ካ'ንጀትሽ
ታድያ ምኑ ላይ ነው ሩሩ ሴትነትሽ
ውቢት........
ምን አልባት . . .ምን አልባት . . .
የወሬ ነጋሪ ጭራሽ እንዳይጠፋ
ይሆናል መሮጡ ሳይነግር ከፊትሽ
ሲያወራው ለመኖር ዝነኛውን ፍቅርሽ፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘