YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ምክር ቤቶቹ ዛሬ የፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱን መልቀቂያ #በመቀበል አዲስ የሪፐብሊኩን #ፕሬዚዳንት ይሾማሉ

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ዛሬ ሁለተኛ ልዩ ስብሰባቸውን ያካሂዳሉ።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ እንደሚጠቁመውም፥ ምክር ቤቶቹ በስብሰባቸው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት #ዶክተር ሙላቱ ተሾመ የሚያቀርቡትን መልቀቂያ በመቀበል አዲስ ፕሬዚዳንት ይሾማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ መስከረም 27 ቀን 2006 ዓመተ ምህረት ነበር አቶ ግርማ ወልደጊዮርጊስን በመተካት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት በመሆን የተሾሙት።

ሶስተኛው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ነገ ለሚተካቸው አራተኛ የኢፌደሪ ፕሬዚዳንት በምክር ቤቶቹ ፊት ስልጣን ያስረክባሉ ተብሎ ይጠበቃል
©FBC
@yenetube @mycase27
#update ​ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ፈረንሳይ #ገቡ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር #ዶክተር አብይ አህመድ በአውሮፓ የሚያደርጉትን ይፋዊ የስራ ጉበኝት በዛሬው እለት ጀምረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን በፈረንሳይ የጀመሩ ሲሆን፥ በዛሬው እለትም ፈረንሳይ ገብተዋል።

በፈረንሳይ በሚኖራቸው ቆይታም ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት #ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በፓሪስ ተገናኝተው እንደሚወያዩ ይጠበቃል።

በቆይታቸውም በአጠቃላይ የሁለትዮሽና የጋራ አጀንዳ በሆኑ አካባቢያዊና አለምዓቀፋዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ምንጭ ፦የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@yenetube @mycase27
#update ጀርመን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በጀርመን የሚያደርጉትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ጀምረዋል።

ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በበርሊን በከተፈተውና አፍሪካ ኢኮኖሚ ድጋፍ በማደረግ ላይ የሚያተኩረው ቡድን ሃያ ሃገራት #ኢኒሼቲቭ ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ ስብሰባ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

በስብሰባው ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር #ዶክተር አብይ በተጨማሪም የጀርመን መራሄተ መንግስት አንጌላ ሜርክልና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ መሃመት ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትና መሪዎች እየተሳተፉ ነው።

ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2017 በጀርመን አነሳሽት የተጀመረ ነው።

ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ መሰረተ ልማትን ጨምሮ የግሉን ዘርፍ ኢንቨስትመንት ለማጠናከርና ለማበረታት የተጀመረ ኢኒሼቲቭ ነው።

የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚና የፋይናንስ መዋቅራቸውን ሳቢ በማድረግ የግሉ ዘርፍ በኢንቨስትመንት በስፋት እንዲሰማራ የሚደግፍ መርሃ ግብር ነው።

በዚህም በሀገራቱ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ዐድሎችን በስፋት ያስተዋውቃል።
በሀገራቱ የሚወሰዱ የማሻሻያ አጀንዳዎችና የፖሊሲ እርምጃዎችንም ይደግፋል።

ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ የቡድን ሃያ አባል ሀገራትን፣ ለለውጥ ዝግጁ ናቸው፣ የለውጥ አሥተሳሰብን ያራምዳሉ የሚባሉ አፍሪካ ሀገራትንና ዓለም ዓቀፍ አጋሮችን ያሰባሰበ ነው።

እስካሁንም #ኢትዮጵያ#ሩዋንዳ#ግብጽ#ጋና#ሴኔጋልና #ሞሮኮን ጨምሮ አሠራ አንድ የአፍሪካ ሀገራት በዚህ ኢንሼቲቭ ተካተዋል።
©FBC
@YENETUBE @MYCASE27
#የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዲሱ መዋቅር መሰረት አምስት #ቋሚ ተጠሪዎችን መሾሙ ተገለፀ።

የቋሚ ተጠሪነት ሹመት #የተሰጣቸው አምባሳደር ወይንሸት ታደሰ፣ አምባሳደር ማህሌት ኃይሉ፣ አምባሳደር ዶክተር ቦጋለ ቶሎሳ፣ አምባሳደር ነገ ፀጋዬ እና አምባሳደር ደዋኖ ከድር ናቸው፡፡
በዚህም መሰረት፦

🔹አምባሳደር ወይንሽት ታደሰ- የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጉዳዮች ቋሚ ተጠሪ

🔹አምባሰዳር ማህሌት ኃይሉ- የአውሮፓ፣ የአሜሪካ፣ የኤዥያ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ቋሚ ተጠሪ

🔹አምባሳደር በጋለ ቶሎሳ- የዳያስፖራ እና ቆንስላ ጎዳዮች ቋሚ ተጠሪ

🔹አምባሳደር ነጋ ፀጋዬ- የኃብት ማኔጅመንትና አገልግሎት ቋሚ ተጠሪ

🔹አምባሳደር ደዋኖ ከድር- የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ቋሚ ተጠሪ ሆነው ተሹመዋል።

አምባሳደር #ወይንሸት በሲዊዲን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛን ሲያገለግሉ የነበሩ ሲሆን፥

አምባሳደር #ማህሌት ኃይሉ ደግሞ በኒውዮርክ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቋሚ መልዕክተኛ ጽህፈት ቤት ምክትል የሚስዮን መሪ በመሆን አገልግለዋል፡፡

አምባሳደር #ዶክተር ቦጋለ ቶሎሳ በኩባ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር እንዲሁም ወደ ዋናው መስሪያ ቤት ተመልሰውም የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው አገልግለዋል፡፡

አምባሳደር #ነጋ ፀጋዬ በፈረንሳይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፥ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጄነራል በመሆንም ሰርተዋል፡፡

አምባሳደር #ደዋኖ ከድር ደግሞ በኩባ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ አምባሳደር ሆነው ቆይተዋል፡፡

ሁለቱም በተለያየ ወቅት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው አገልግለዋል።

ቋሚ ተጠሪዎች የመስሪያ ቤቱን የዕለት ተዕለት ስራ የመከታተልና ውሳኔ የማሳለፍ ሃላፊነት የሚኖራቸው ሲሆን በተለያዩ አገሮች በስፋት ይሰራበታል፡፡

በቀጣይም የዳይሬክተር ጀኔራሎች እና ሌሎች የሃላፊነት እርከኖች ድልድል ይፋ እንደሚያደርግም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ምንጭ ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@yenetube @mycase27
አንጋፋዉ #አርቲስት_ደበበ_እሸቱ «#ኢትዮጵያዊነት አማራጭ የማይገኝለት ነዉ።

ልክ እንደሙዚቃዉ ህብር ያለዉ ነዉ። ሙዚቃን አዳምጠነዉ ቋንቋዉም ባይገባን በሙዚቃዎቹ ምት ስሜታችን ረክቶ ሊደነቅ የሚቻል ጥበብ ነዉ።

በመድረኩ ግጥም ያቀረቡት ባለሞያዎች ልጆችም ቢሆኑ፤ #ኢትዮጵያ እያለች ግጥምን ካቀረበችዉ #ታዳጊ_ልጅ ጀምሮ፤ ኢትዮጵያ ብላ ልታወድስ የቻለችዉ ያ መድረክ በመዘጋጀቱ ነዉ። ሕብረት ያስፈልጋል፤ አንድ መሆን ያስፈልጋል፤ ኢትዮጵያ አደጋ ዉስጥ እንዳትገባ የሁላችንም ተሳትፎ አስፈላጊ ነዉ ብሎአል።

ደራሲና ገጣሚ #ዶክተር_በድሉ_ዋቅጅራ በበኩላቸዉ
«ብዙዎች የዘረፉትን አስመላሽ፣ ገድለው የጣሉትን አፈላላጊ ያፈናቀሉትን ዜጋ አስፋሪ ሆነዋል። ማህበረሰባችን የስነ ምግባር አረም ለማብቀል ተስማሚ ሆኗል። በየትምርት ቤቱ የሥነ- ምግባር ትምህርት የለም። በዝያ ፋንታ ልጆች የሚማሩት ፖለቲካ ነዉ። ሥነ ምግባርን በማስተማር ረገድ ቤተ-ክህነት አቋም ልትይዝ ይገባል። ቤተ ክርስትያን አሁን የተቸገረ ማደርያ አይደለም ፤ ቤተ ክርስትያን የሚጠበቀዉ መስቀል በያዘ ቄስ ሳይሆን፤ ጠመንጃ በያዘ ፌደራል ነዉ። ቤተ-ክህነቶቹ አከራይተዉ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ገቢ ያገኛሉ። በአንፃሩ ገጠር ያሉት ቤተ-ክርስትያናት የሚያስቀድሱበት ጧፍ የላቸዉም። ይሄን ይሄን ስናይ የማኅበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ ተበላሽቶአል፤ ዘቅጦአል።

ስለዚህ ቆጭ ብለን፤ ቤተ-ክርስትያንን እንደተቋም፤ ትምህርትን እንደተቋም የመገናኛ ብዙኃንን እንደተቋም ልናዋቅር በፖሊሲ ልነድፍ ይገባል።» ብለዋል።

ምንጭ:- Dw
@YeneTube @FikerAssefa
የመድኃኒት አምራች ኩባንያ #ጆንሰን እና #ጆንሰን ገዳይ የሆነውን የኮሮኖ ቫይረስ በሽታ ለመከላከል የሚሆን #ክትባት (መድሓኒት) እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ በቅርቡ በተደረገው ቃለ ምልልስ የጆንሰን እና ጆንሰን ዋና ሳይንቲስት #ዶክተር ፖል ስቶልፍልስ በወራት ጊዜ ውስጥ ክትባቱን እንደሚፈጥሩ በሙሉ እምነት ተናግረዋል፡፡ ሆኖም ፣ ለህዝቡ እስኪቀርብ እስከ አንድ ዓመት ድረስ ሊወስድ ይችላል ብለዋል።

Via:- one america news
@YeneTube @Fikerassefa
Forwarded from Teklu Tilahun
#የስኬት_ቀመር
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ

ቀመሩ ሂሳብ አይደለም፤ ኬሚስትሪም አይደለም- ስነልቦናዊ ቀመር እንጂ፡፡ ይህ የስኬት ቀመር መቶ አመታትን አስቆጥሯል።

ቀመሩን አንድ ጊዜ ካወቁትና መተግበር ከጀመሩ… በሕይወትዎ አስደናቂ ለውጥ ማየት ይጀምራሉ፡፡

ከመቶ ሚሊየን ኮፒ በላይ በተሸጠው ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች ላይ የተመሰረተ የናፖሊዮን ሂል ድንቅ ስራ። #የህይወት_መመሪያ በተሰኘው መጽሐፍ የምናውቃት ሀኒም_ኤልያስ ተርጉማዋለች፡፡

ለመሆኑ መቶ አመታትን ያስቆጠረው እና አሁንም ድረስ የሚሰራው ይህ የስኬት ቀመር ምን ይሆን?

ይህ መጽሐፍ ታላላቅ መልእክቶች፣ ታላላቅ መሪዎችና መንፈስ ማነቃቂያ ያሉበት የነፍስ ምግብ ነው፤ ወደ ስኬት የሚወስድ ካርታ ነው፡፡
#ዶክተር_ዴኒስ_ዌይትሊ

በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡

ይቀላቀሉን 👉http://tttttt.me/teklutilahun
Forwarded from Teklu Tilahun
#የስኬት_ቀመር
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ

ቀመሩ ሂሳብ አይደለም፤ ኬሚስትሪም አይደለም- ስነልቦናዊ ቀመር እንጂ፡፡ ይህ የስኬት ቀመር መቶ አመታትን አስቆጥሯል።

ቀመሩን አንድ ጊዜ ካወቁትና መተግበር ከጀመሩ… በሕይወትዎ አስደናቂ ለውጥ ማየት ይጀምራሉ፡፡

ከመቶ ሚሊየን ኮፒ በላይ በተሸጠው ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች ላይ የተመሰረተ የናፖሊዮን ሂል ድንቅ ስራ። #የህይወት_መመሪያ በተሰኘው መጽሐፍ የምናውቃት ሀኒም_ኤልያስ ተርጉማዋለች፡፡

ለመሆኑ መቶ አመታትን ያስቆጠረው እና አሁንም ድረስ የሚሰራው ይህ የስኬት ቀመር ምን ይሆን?

ይህ መጽሐፍ ታላላቅ መልእክቶች፣ ታላላቅ መሪዎችና መንፈስ ማነቃቂያ ያሉበት የነፍስ ምግብ ነው፤ ወደ ስኬት የሚወስድ ካርታ ነው፡፡
#ዶክተር_ዴኒስ_ዌይትሊ

በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡

ይቀላቀሉን 👉http://tttttt.me/teklutilahun
Forwarded from Teklu Tilahun
#የስኬት_ቀመር
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ

ቀመሩ ሂሳብ አይደለም፤ ኬሚስትሪም አይደለም- ስነልቦናዊ ቀመር እንጂ፡፡ ይህ የስኬት ቀመር መቶ አመታትን አስቆጥሯል።

ቀመሩን አንድ ጊዜ ካወቁትና መተግበር ከጀመሩ… በሕይወትዎ አስደናቂ ለውጥ ማየት ይጀምራሉ፡፡

ከመቶ ሚሊየን ኮፒ በላይ በተሸጠው ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች ላይ የተመሰረተ የናፖሊዮን ሂል ድንቅ ስራ። #የህይወት_መመሪያ በተሰኘው መጽሐፍ የምናውቃት ሀኒም_ኤልያስ ተርጉማዋለች፡፡

ለመሆኑ መቶ አመታትን ያስቆጠረው እና አሁንም ድረስ የሚሰራው ይህ የስኬት ቀመር ምን ይሆን?

ይህ መጽሐፍ ታላላቅ መልእክቶች፣ ታላላቅ መሪዎችና መንፈስ ማነቃቂያ ያሉበት የነፍስ ምግብ ነው፤ ወደ ስኬት የሚወስድ ካርታ ነው፡፡
#ዶክተር_ዴኒስ_ዌይትሊ

በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡

ይቀላቀሉን 👉http://tttttt.me/teklutilahun