YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#update ጀርመን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በጀርመን የሚያደርጉትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ጀምረዋል።

ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በበርሊን በከተፈተውና አፍሪካ ኢኮኖሚ ድጋፍ በማደረግ ላይ የሚያተኩረው ቡድን ሃያ ሃገራት #ኢኒሼቲቭ ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ ስብሰባ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

በስብሰባው ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር #ዶክተር አብይ በተጨማሪም የጀርመን መራሄተ መንግስት አንጌላ ሜርክልና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ መሃመት ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትና መሪዎች እየተሳተፉ ነው።

ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2017 በጀርመን አነሳሽት የተጀመረ ነው።

ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ መሰረተ ልማትን ጨምሮ የግሉን ዘርፍ ኢንቨስትመንት ለማጠናከርና ለማበረታት የተጀመረ ኢኒሼቲቭ ነው።

የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚና የፋይናንስ መዋቅራቸውን ሳቢ በማድረግ የግሉ ዘርፍ በኢንቨስትመንት በስፋት እንዲሰማራ የሚደግፍ መርሃ ግብር ነው።

በዚህም በሀገራቱ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ዐድሎችን በስፋት ያስተዋውቃል።
በሀገራቱ የሚወሰዱ የማሻሻያ አጀንዳዎችና የፖሊሲ እርምጃዎችንም ይደግፋል።

ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ የቡድን ሃያ አባል ሀገራትን፣ ለለውጥ ዝግጁ ናቸው፣ የለውጥ አሥተሳሰብን ያራምዳሉ የሚባሉ አፍሪካ ሀገራትንና ዓለም ዓቀፍ አጋሮችን ያሰባሰበ ነው።

እስካሁንም #ኢትዮጵያ#ሩዋንዳ#ግብጽ#ጋና#ሴኔጋልና #ሞሮኮን ጨምሮ አሠራ አንድ የአፍሪካ ሀገራት በዚህ ኢንሼቲቭ ተካተዋል።
©FBC
@YENETUBE @MYCASE27
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ወታደራዊ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ጉብኝት በ #ሩዋንዳ እያደረጉ ነው

#ኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በሩዋንዳ ከሚያዚያ 5 ቀን ጀምሮ የአራት ቀን የስራ ጉብኝት እያደረጉ እንደሚገኙ ተዘገበ።

ጉብኝቱ ሁለቱ ሀገራት ወታደራዊ ትብብርን ለማጠናከር እያደረጉ ያሉትን ጥረት ተከትሎ የተካሄደ ነው።  የሩዋንዳ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ መበጋቢት ወር  በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት በተለያዩ ወታደራዊ መስኮች በጋራ መስራት የሚያስችል ስምምነት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ተፈራርመዋል።

እንደ ዘኒው ታይምስ ዘገባ፤ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ሰኞ ዕለት፤ ኪሚሁሩራ በሚገኘው የሩዋንዳ መከላከያ ሠራዊት  ዋና መስሪያ ቤት ከጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ ጋር ውይይት አድርገዋል።

ይህንንም ተከትሎ የሩዋንዳ መከላከያ ሠራዊት በሰጠው መግለጫ፣ ጉብኝቱ "የረጅም ጊዜ የሁለትዮሽ ትብብርን” ለማስፋት "ቁልፍ ዕድል" መሆኑን በመግለጽ ውይይቶቹ "በመከላከያና በሌሎች ተዛማጅ ዘርፎች  አዲስ የትብብር መስኮች" ላይ ያተኮሩ ናቸው ብሏል።

ፌልድ ማርሻል ብርሃኑ  የኪጋሊ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሙዚየምን እንደሚጎበኙ ዘኒው ታይምስ ዘግቧል። የሩዋንዳ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ሙባረክ ሙጋጋ በመጋቢት ወር ወደ ኢትዮጵያ በተጓዙበት ወቅት ልዑካቸው በ #ቢሾፍቱ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን መጎብኘታቸው ይታወሳል።

በተጨማሪም በወቅቱም ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር በወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና፣ በተሞክሮ ልውውጥ፣ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እና በሌሎችም ተያያዥነት ባላቸው ወታደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ስምምነት ተፈራርመዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
😁40👍196👎2🔥2