ሰበር ዜና‼️
ጉዞ ዓድዋ 6 ተጀመረ!! ታሪካዊቷ የሐረር ከተማ የዘንድሮ ጉዞ መነሻ ተደርጋ ተመርጣለች።
"ፍቅር ለኢትዮጵያ" የሚል መርሕ የያዘው የዘንድሮ የእግር ጉዞ መነሻውን ከሀረር ከተማ በማድረግ ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ የሚነሱ ተጓዦችን በመቀላቀል የካቲት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ ይጠናቀቃል።
በትናትናው ምሽት በድሬዳዋ ከተማ በተካሔደው የመሸኛ ስነሥርዓት ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ኡስማን ባደረጉት ንግግር "ዓድዋ የመላው ኢትዮጵያዊያን ህብረት ያታየበት ሁላችንም የምንኮራበት ድላችን መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ድል ለመዘከር በየአመቱ የሚዘጋጀውን የጉዞ ዓድዋ እንቅስቃሴ የከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚያግዝ አረጋግጠው የዘንድሮው 123ኛ የዓድዋ ድል በዓል አከባበር መጀመሩን በይፋ አብስረው፤ ለተጓዦች መልካም መንገድ ተመኝተዋል።
በታላቁ የዓድዋ ጦርነት ወቅት የምስራቅ ኢትዮጵያን ጦር የመሩት የቀዳሚው ጦር አዝማች ልዑል ራስ መኮንን ከተነሱበት የሐረር ከተማ በ5 ተጓዦች የተጀመረው የዘንድሮው ጉዞ ዓድዋ በተለያዩ ደማቅ ሥነስርዓቶች ለመካሔድ በዛሬው እለት ታህሳስ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለጉዞ ዓድዋ አዘጋጆች በስልክ እንዳረጋገጡት የከተማ አስተዳደሩ ከሀረር የተነሱ ተጓዦችን ተቀብሎ በመሸኘት እና ከአዲስ አበባ የሚነሱ ተጓዦችን አሰፈላጊውን ስንቅ አሟልቶ በመሸኘት የከተማ አስተዳደሩ አጋርነቱን ያሳያል።
፨፨፨
የፍቅር ዘመቻው ሠላምን እና አብሮነትን ሰንቆ በዓድዋ ተራሮች አናት ላይ የካቲት 23 ቀን በድል ይጠናቀቃል።
የጉዞ ዓድዋ አስተባባሪዎች
መሐመድ ካሳ
ያሬድ ሹመቴ
#ፍቅር_ለኢትዮጵያ
#ኢትዮጵያዊነት_ይለምልም !!
#ጉዞ_ዓድዋ_6
#ከሐረር_አዲስ_አበባ_ዓድዋ
#1540ኪ .ሜ
ምንጭ፦ ያሬድ ሹመቴ
@YeneTube @Fikerassefa
ጉዞ ዓድዋ 6 ተጀመረ!! ታሪካዊቷ የሐረር ከተማ የዘንድሮ ጉዞ መነሻ ተደርጋ ተመርጣለች።
"ፍቅር ለኢትዮጵያ" የሚል መርሕ የያዘው የዘንድሮ የእግር ጉዞ መነሻውን ከሀረር ከተማ በማድረግ ጥር 7 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ የሚነሱ ተጓዦችን በመቀላቀል የካቲት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ ይጠናቀቃል።
በትናትናው ምሽት በድሬዳዋ ከተማ በተካሔደው የመሸኛ ስነሥርዓት ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ኡስማን ባደረጉት ንግግር "ዓድዋ የመላው ኢትዮጵያዊያን ህብረት ያታየበት ሁላችንም የምንኮራበት ድላችን መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን ድል ለመዘከር በየአመቱ የሚዘጋጀውን የጉዞ ዓድዋ እንቅስቃሴ የከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚያግዝ አረጋግጠው የዘንድሮው 123ኛ የዓድዋ ድል በዓል አከባበር መጀመሩን በይፋ አብስረው፤ ለተጓዦች መልካም መንገድ ተመኝተዋል።
በታላቁ የዓድዋ ጦርነት ወቅት የምስራቅ ኢትዮጵያን ጦር የመሩት የቀዳሚው ጦር አዝማች ልዑል ራስ መኮንን ከተነሱበት የሐረር ከተማ በ5 ተጓዦች የተጀመረው የዘንድሮው ጉዞ ዓድዋ በተለያዩ ደማቅ ሥነስርዓቶች ለመካሔድ በዛሬው እለት ታህሳስ 21 ቀን 2011 ዓ.ም. ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለጉዞ ዓድዋ አዘጋጆች በስልክ እንዳረጋገጡት የከተማ አስተዳደሩ ከሀረር የተነሱ ተጓዦችን ተቀብሎ በመሸኘት እና ከአዲስ አበባ የሚነሱ ተጓዦችን አሰፈላጊውን ስንቅ አሟልቶ በመሸኘት የከተማ አስተዳደሩ አጋርነቱን ያሳያል።
፨፨፨
የፍቅር ዘመቻው ሠላምን እና አብሮነትን ሰንቆ በዓድዋ ተራሮች አናት ላይ የካቲት 23 ቀን በድል ይጠናቀቃል።
የጉዞ ዓድዋ አስተባባሪዎች
መሐመድ ካሳ
ያሬድ ሹመቴ
#ፍቅር_ለኢትዮጵያ
#ኢትዮጵያዊነት_ይለምልም !!
#ጉዞ_ዓድዋ_6
#ከሐረር_አዲስ_አበባ_ዓድዋ
#1540ኪ .ሜ
ምንጭ፦ ያሬድ ሹመቴ
@YeneTube @Fikerassefa
አንጋፋዉ #አርቲስት_ደበበ_እሸቱ «#ኢትዮጵያዊነት አማራጭ የማይገኝለት ነዉ።
ልክ እንደሙዚቃዉ ህብር ያለዉ ነዉ። ሙዚቃን አዳምጠነዉ ቋንቋዉም ባይገባን በሙዚቃዎቹ ምት ስሜታችን ረክቶ ሊደነቅ የሚቻል ጥበብ ነዉ።
በመድረኩ ግጥም ያቀረቡት ባለሞያዎች ልጆችም ቢሆኑ፤ #ኢትዮጵያ እያለች ግጥምን ካቀረበችዉ #ታዳጊ_ልጅ ጀምሮ፤ ኢትዮጵያ ብላ ልታወድስ የቻለችዉ ያ መድረክ በመዘጋጀቱ ነዉ። ሕብረት ያስፈልጋል፤ አንድ መሆን ያስፈልጋል፤ ኢትዮጵያ አደጋ ዉስጥ እንዳትገባ የሁላችንም ተሳትፎ አስፈላጊ ነዉ ብሎአል።
ደራሲና ገጣሚ #ዶክተር_በድሉ_ዋቅጅራ በበኩላቸዉ
«ብዙዎች የዘረፉትን አስመላሽ፣ ገድለው የጣሉትን አፈላላጊ ያፈናቀሉትን ዜጋ አስፋሪ ሆነዋል። ማህበረሰባችን የስነ ምግባር አረም ለማብቀል ተስማሚ ሆኗል። በየትምርት ቤቱ የሥነ- ምግባር ትምህርት የለም። በዝያ ፋንታ ልጆች የሚማሩት ፖለቲካ ነዉ። ሥነ ምግባርን በማስተማር ረገድ ቤተ-ክህነት አቋም ልትይዝ ይገባል። ቤተ ክርስትያን አሁን የተቸገረ ማደርያ አይደለም ፤ ቤተ ክርስትያን የሚጠበቀዉ መስቀል በያዘ ቄስ ሳይሆን፤ ጠመንጃ በያዘ ፌደራል ነዉ። ቤተ-ክህነቶቹ አከራይተዉ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ገቢ ያገኛሉ። በአንፃሩ ገጠር ያሉት ቤተ-ክርስትያናት የሚያስቀድሱበት ጧፍ የላቸዉም። ይሄን ይሄን ስናይ የማኅበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ ተበላሽቶአል፤ ዘቅጦአል።
ስለዚህ ቆጭ ብለን፤ ቤተ-ክርስትያንን እንደተቋም፤ ትምህርትን እንደተቋም የመገናኛ ብዙኃንን እንደተቋም ልናዋቅር በፖሊሲ ልነድፍ ይገባል።» ብለዋል።
ምንጭ:- Dw
@YeneTube @FikerAssefa
ልክ እንደሙዚቃዉ ህብር ያለዉ ነዉ። ሙዚቃን አዳምጠነዉ ቋንቋዉም ባይገባን በሙዚቃዎቹ ምት ስሜታችን ረክቶ ሊደነቅ የሚቻል ጥበብ ነዉ።
በመድረኩ ግጥም ያቀረቡት ባለሞያዎች ልጆችም ቢሆኑ፤ #ኢትዮጵያ እያለች ግጥምን ካቀረበችዉ #ታዳጊ_ልጅ ጀምሮ፤ ኢትዮጵያ ብላ ልታወድስ የቻለችዉ ያ መድረክ በመዘጋጀቱ ነዉ። ሕብረት ያስፈልጋል፤ አንድ መሆን ያስፈልጋል፤ ኢትዮጵያ አደጋ ዉስጥ እንዳትገባ የሁላችንም ተሳትፎ አስፈላጊ ነዉ ብሎአል።
ደራሲና ገጣሚ #ዶክተር_በድሉ_ዋቅጅራ በበኩላቸዉ
«ብዙዎች የዘረፉትን አስመላሽ፣ ገድለው የጣሉትን አፈላላጊ ያፈናቀሉትን ዜጋ አስፋሪ ሆነዋል። ማህበረሰባችን የስነ ምግባር አረም ለማብቀል ተስማሚ ሆኗል። በየትምርት ቤቱ የሥነ- ምግባር ትምህርት የለም። በዝያ ፋንታ ልጆች የሚማሩት ፖለቲካ ነዉ። ሥነ ምግባርን በማስተማር ረገድ ቤተ-ክህነት አቋም ልትይዝ ይገባል። ቤተ ክርስትያን አሁን የተቸገረ ማደርያ አይደለም ፤ ቤተ ክርስትያን የሚጠበቀዉ መስቀል በያዘ ቄስ ሳይሆን፤ ጠመንጃ በያዘ ፌደራል ነዉ። ቤተ-ክህነቶቹ አከራይተዉ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ገቢ ያገኛሉ። በአንፃሩ ገጠር ያሉት ቤተ-ክርስትያናት የሚያስቀድሱበት ጧፍ የላቸዉም። ይሄን ይሄን ስናይ የማኅበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ ተበላሽቶአል፤ ዘቅጦአል።
ስለዚህ ቆጭ ብለን፤ ቤተ-ክርስትያንን እንደተቋም፤ ትምህርትን እንደተቋም የመገናኛ ብዙኃንን እንደተቋም ልናዋቅር በፖሊሲ ልነድፍ ይገባል።» ብለዋል።
ምንጭ:- Dw
@YeneTube @FikerAssefa