ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
@gedlatnadersanat


ለዚህም ነው ቤተ ክርስቲያኗ ራሷ በግርጌ ማስታወሻ " #በግሪኩ #የሚማልደው #ነው #የሚለው" ብላ የጻፈችው። ይህ ከሆነ ደግሞ #የአዲስ ኪዳን በኩረ ጽሁፍ(እናት ቋንቋ) #ግእዙ ሳይሆን #ግሪኩ መሆኑ ግልጽ ነው። #ግእዙን ጨምሮ ሁሉም #የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት #የትርጉም ሥራቸው የተሰራው #ከግሪኩ በመሆኑ የትኛውም የትርጉም ስራ ሲሰራ #ግሪኩ የሚለውን በማለት ግሪኩ የተወውን በመተው መስራቱ #ለእግዚአብሄር ቃል ያለንን ታማኝነት የምናሳይበት ትልቁ መንገድ ነው። #ግሪኩ እንዲህ #አይልም እያሉ ሌላ ነገር መጻፍ #ታማኝ መሆንን አያሳይም።

▶️ ይህ እንዳለ ሆኖ #ጸሀፊው #ከጠቀሱት #መጻሕፍት በፊት " #በዐጼ ሚኒልክ" ጊዜ የታተመው #የ1887 ዕትም #መጽሀፍ ቅዱስ ይህን ጥቅስ እንዴት #አስፍሮት እንዳለ #መመልከቱ መልካም ነው።
" #ማን ነው የሚኮንን? ክርስቶስ የሱስ የሞተ ነውን? ከሙታን እንኳ የተነሣ በእግዚአብሄር ቀኝ የተቀመጠ እርሱም #ያስምረናል"

አንባቢው ልብ እንዲል የሚገባው ነገር #ሰዎቹ እያሉ ያሉት " #ከጊዜ ቡሀላ #የታተሙት ናቸው እንጂ #ቀደምት ዕትሞች " #ክርስቶስ ያማልዳል" አይሉም የሚል ሲሆን እነርሱ #የቀደሙ ናቸው ከሚሏቸው #ቀድሞ #ለንባብ የበቃው #መጽሀፍ ግን እነርሱ እንዲልላቸው የሚፈልጉትን ሳይሆን #እውነታውን #አስፍሮት ይገኛል።
#ወንድሞቻችን መፈናፈኛ ሲያጡ " #እናንተ የቀየራቹትን ሳይሆን #አባቶቻችን ቀደም ሲል #በግእዝ ጽፈው ያስቀመጡልንን ነው የምንቀበለው" ማለት ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ለዚሁ ደግሞ #በግእዝና #በአማርኛ ተዘጋጅቶ #በትንሣኤ #ማተሚያ ቤት የታተመውን #መጽሀፍ በዋናነት የሚጠቅሱ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ #ግእዙን መሠረት አድርጎ ነው #የታተመው #የሚባለውንና #በ2000 ዓ.ም ለንባብ የበቃውን 80 አሀዱ #መጽሀፍ ቅዱስ ያነሳሉ።
#በግእዝና በአማርኛ የተዘጋጀው መጽሀፍ ምንም እንኳን በአማርኛው
" #የሚፈርድ ማን ነው? የሞተው፥ ይልቁንም #ከሙታን ተለይቶ የተነሳው፥ በእግዚአብሄር ቀኝ የተቀመጠው፥ ደግሞም " #ስለእኛ #የሚፈርደው" በማለት ቢያስቀምጡትም ግእዙ ራሱ ግን
" #ወመኑ፡ ውእቱ፡ እንከ፡ ዘይትዋቀሦሙ ለኅሩያነ እግዚአብሔር ለእመ ለሊሁ ያጸድቅ፤ መኑ ዘይኴንን ክርስቶስ ኢየሱስ ዘሞተ፡ ወተንሥአ እምውታን ወሀሎ ይነብር በየማነ እግዚአብሔር #ወይትዋቀሥ #በእንቲአነ" በሚል ነው የሰፈረው።(ሮሜ 8፤ 33-34)
📖/፤ ትንሳኤ ማሳተሚያ ድርጅት ዐዲስ ኪዳን በግእዝና በዓማርኛ (ዐዲስ አበባ፤ 1994) ገጽ 644።

ሰዎቹ " #ይፈርዳል" እንዲልላቸው የሚጠብቁት ቃል " #ወይትዋቀሥ" የሚለውን ነው።
ሊቁ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
🔽 " #ተዋቀሠ" የሚለውን ቃል ትርጉም " #ተሟገተ#ተከራከረ" እንደሆነ በግልጽ አስቀምጠውታል።
ይህ እንዲህ ሳለ ግን #ሰዎቹ ከመሰረተ ሀሳቡ #ውጭ በሆነ ሁኔታ #ለመተርጎም የተነሳሱበት ምክንያት #ከእግዚአብሄር ቃል ይልቅ #ለፈቃዳቸው ቅድሚያ የሚሰጡ #ሰዎች በመሆናቸው መሆኑ ግልጽ ነው።
📖/፤ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ(አለቃ)፣ መጽሀፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ዐዲስ፣(1948) ገጽ 401።

" #ይከራከል" የሚለው እንዲያውም " #ይማልዳል" ከሚለው በላይ #ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ የሚቆም #መካከለኛ መሆኑን #አጠንክሮ ይገልጣል እንጂ #ይፈርዳል ማለትን አያመለክትም፤ #ግእዙን እንኳን የተጠቀምነው #በአገራችን የተለመደ #ጥንታዊ ትርጓሜ ነው በማለት እንጂ #የአዲስ ኪዳን #መጻህፍት ሁሉ በመጀመሪያ በተጻፉበትና ለሁሉም #ትርጓሜዎች መሰረት በሆነው #የግሪክ ቋንቋ በግልጽ #የሚማልደው ተብሎ ተቀምጧል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው #በግሪክ ቋንቋ እንደሆነ የታወቀ ቢሆንም። ይህንን ስለ እኛ #የሚማልደው የሚለውን ቃል « #የሚፈርደው» ብለው የቀየሩ ሰዎች ራሱ በግሪኩ #የሚያማልደው እንደሚል ራሳቸው ይስማማሉ።(ፎቶው ላይ የግርጌ ማስታወሻውን ይመልከቱ)

@gedlatnadersanat
መጽሀፈ ሰአታት

💠 "ሰዓሊ ለነ ሰንበት ክርስቲያን ቅድስት፣ ለውለደ ሰብእ መድኃኒት፣ ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት"
💠 " ለሰው ልጆች መድኃኒት የሆንሽ እስከ ዘላለም ገዢ የሆንሽ የክርስቲያን ሰንበት ሆይ ለምኝልን (አማልጅን)
/ሰዓሊ ለነ ከሚባል ክፍል -- ገጽ 30/

▶️ የመጽሀፉ ደራሲ #ሰንበተ #ክርስቲያን የሚለው #ዕለተ #እሁድን እንደሆነ ከተለመደው አባባል ማወቅ ይቻላል። #እሑድን በተመለከተ በግእዙ ሐዲስ ኪዳን <<ወበእሑድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት>> የሚባል ንባብ ይገኛል(ዩሐ 20፥1)። በአማርኛው ግን <<ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን ማርያም መግደላዊት ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች>> ይላል። ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን የሚለው በግሪኩ <<μιᾷτῶν σαββάτων/ሚያ ቶን ሳባቶን/>> የሚለው ቃል ሲሆን ትርጉሙም ያው <ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን> የሚል ነው። በግእዙ <<ወበእሑድ ሰንበት>> የሚለው ንባብ ግን በግሪኩ ስለሌለ #የትርጉም #ስህተት መሆኑ ግልጽ ነው። እንዲሁም በሌላ ቦታ <<ወበዕለተ እሑድ እንዘ ጉቡኣን ንሕነ ከመ ንባርክ ማዕደ>>/ሐዋ 20፥7/ ይላል፤ ይህም በአማርኛው << #ከሳምንቱ #በመጀመሪያው ቀን እንጀራ ለመቁረስ ተሰብስበን ሳለን..>> ተብሎ #የተተረጎመ ሲሆን በዚህኛውም ሆነ በፊተኛው ምንባብ ያለው #የግሪኩ ቃል እሁድ ሰንበት እንደሆነች የማያሳይ በመሆኑ "እለተ እሑድ" <<ሰንበት>> እንደሆነች የማያሳይ በመሆኑ "እለተ እሁድ" <<ሰንበት>> እንደሆነች የሚናገረው የግእዝ ንባብ #የትርጉም #ስህተት የወለደው መሆኑን እንገነዘባለን። ለብሉይ ኪዳን #ህዝብ #እግዚአብሔር #ዕረፍተ #ስጋ እንድትሆናቸው #ዕለተ #ሰንበትን ሰጥቷቸው ነበር፤ ይሁንና #ሰንበት #በጥላነት #ክርስቶስን ታመለክት ነበር፤ ይህንንም መጽሀፍ ቅዱስ ሲያስረዳ <<እንግዲህ #በመብል ወይም #በመጠጥ ወይም ስለ #በዓል ወይም ስለ #ወር መባቻ ወይም ስለ #ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ፤ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች #ጥላ ናቸውና #አካሉ ግን #የክርስቶስ ነው>> ይላል/ቆላ 2፤ 16-17/። ስለሆነም <በአዲስ ኪዳን> #ሰንበተ #ክርስቲያን #ኢየሱስ #ክርስቶስ ነው እንጂ #ዕለተ #እሑድ አይደለችም።
ከዚህም ጋር ደግሞ << ንዑ ኅቤየ ኲልክሙ ስሩሐን ወጽዑራን ወአነ አአርፈክሙ ማለትም እናንተ ደካሞች #ሸክማችሁ #የከበደ ሁሉ ወደኔ ኑ እኔም #አሳርፋችኋለሁ>>/ማቴ 11፥29/ የሚለውን ማስተዋል ያስፈልጋል፤ ይህንን በመረዳት አንዲት #የማትሰማና #ሕያዊት ያልሆነች #የጊዜ #ክፍልፋይ ዕለተ #እሁድን #ሰንበት ብሎ ማክበርን ትቶ <አማናዊውን ሰንበት> #ክርስቶስን ማክበርና #በእርሱም #ማረፍ ይገባል።
እጅግ #የሚያሳዝነው ደግሞ ዕለቷ <<ለውሉደ ሰብእ መድኃኒት ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት>> <<ለሰው ልጆች #መድኃኒት ለዘላለዓም #ገዥ የሆንሽ>> መባሏ ነው። #የኑፋቄውን ክፋት ለመረዳት ለዚህች #ዕለት የተሰጡትንና #መድኃኒት#ገዥ የሚሉትን #ቃላት እንመርምር።