ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
🔽▶️ *⃣ #ሮሜ 8፥34 እና #የመናፍቃኑ እርስ በእርስ አለመግባባት፦ ‹‹ #የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ #በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው›› (ሮሜ 8፡34)፡፡ #በልማድ ለያዙት #የተሳሳተ ትምህርት አልመች ያለውና #በምንፍቅና #ጎዳና ላይ ሆነው #የአዳኛችንን #የኢየሱስ ክርስቶስ #የማዳን ግብር የሆነው #የምልጃ ሥራውን ሽምጥጥ አድርገው…
🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽

#ቀደም ሲል ከቀረበው "ምንባቡ #ይማልዳል ሳይሆን #ይፈርዳል ነው ማለት የነበረበት" በሚል ከተቀመጠው "ከመጋቤ ዐዲስ ሮዳስ ታደሰ" #ሐሳብ የተለየ #ሐሳብ ያላቸው "መምህር ደምሰው ዘውዴ" ደግሞ #ይማልዳል የሚለውን ይቀበሉና እንዲህ ይላሉ..

〽️ 2፦ ‹‹[መናፍቃን] ለማታለል ሲሉ #በግእዝ #ይማልዳል ብለው ጽፈውታል፤ ቃሉ #ግእዝ ነው #ግእዝና #ፍቺውን የማያውቅ #ሊታለል ይችላል፡፡ እነርሱ ግን ግእዝን ይቃወማሉ፤ #ለማወናበጃ ግን #ሊጠቀሙበት ይሞክራሉ፡፡ #ቅዱስ ዳዊት ግን የቃልህ ፍቺ ያበራል… እንዳለ #ፍቺው ይመሰክርባቸዋል፡፡ ምክንያቱም
/ #ይማልዳል/ የሚለው #የግእዝ #ቃል ሲሆን #ፍቺው / #ይፈርዳል/ ነው፡፡ አማላጅ ቢሆን ኖሮ ቅዱስ ጳውሎስ በግልጽ ዐማርኛ ‹ #ያማልዳል› ብሎ በጻፈ ነበር፡፡… እስኪ ፍረዱኝ››
📖/፤ (ደምሰው ዘውዴ (መምህር)፣ " ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ" (2001) ገጽ 30)፡፡

▶️ ጸሀፊው መጽሐፍ ቅዱስ በዐማርኛ የተጻፈ መስሏቸው ይሆን? ወይስ ምናልባት #አብርሃም ኢትዮጵያዊ ነው፣ #መልከ #ጼዴቅ ኢትዮጵያዊ ነው፣ #ማርያም ኢትዮጵያዊት ናት፣… እንደሚባለው #ሐዋርያው ቅዱስ #ጳውሎስም ኢትዮጵያዊ ነው እያለ ይሆን? እነርሱ እንደ መሰላቸው መጽሐፍ ቅዱስ #በዐማርኛ #ቋንቋ የተጻፈ አይደለም፡፡ ይህን ማንም የሚያውቀው እውነት ነው። #ብሉይ ኪዳን #በዕብራይስጥ #ዐዲስ ኪዳን ደግሞ #በግሪክ ቋንቋ የተጻፉ ሲሆን መላው #ዓለም (ኢትዮጵያን ጨምሮ) ከእነዚህ #ቋንቋዎች ነው ወደ #የሀገራቸው #ቋንቋ የተረጐሙት፡፡ #የእኛ ሀገር ሰዎች (በተለይ ቤተ ክርስቲያናችን) ግን መጽሐፉን ወደ #ዐማርኛ ሲተረጉሙት #የግሪኩ የማይለውን #በማስፈር #እንግዳ ትምህርት ለማስተማር #ምክንያት ሆኑ እንጂ፡፡ ግሪኩስ የሚለው "ኢየሱስ ይማልዳል" ነው። ይህን ለማረጋገጥ ከፈለጉ #በ2000 ዓ.ም #የታተመውን 80 አሀዱ #በሮሜ 8፥34 የግርጌ ማስታወሻ ላይ "ግሪኩ <የሚማልደው> ይላል" የሚለውን ፎቶው ላይ ይመልከቱ።

ሌላው የኚህ ጸሀፊ አስጋራሚ ነገር ከላይ ከቀበረው የተለየ ሐሳብ ካላቸው "ከመጋቤ ዐዲስ ሮዳስ ታደሰ" ጋር #አለመስማማታቸው ነው፡፡ ቀደም ሲል ያየነው " #የሚማልደው ሳይሆን #የሚፈርደው ነው መሆን ያለበት #የሚማልደው የሚለው የተቀየረ ነው። #መናፍቃን የጨመሩት ነው ሲል" ከዚህ የተለየ ሀሳብ ያላቸው "መምህር ደምሰው ዘውዴ" ደግሞ " #የሚማልደው ነው መሆን ያለበት ምክንያቱም #የግእዝ ቃል ነውና፡፡ በግእዙ #የሚማልደው ማለት #የሚፈርደው ማለት ነው" በማለት ሀሳባቸውን ያስቀምጣሉ፡፡

▶️ በክፍል 2(የኢየሱስ አማላጅነት) ላይ #የምልጃ ትርጉም መቅረቡ ይታወሳል። በዛ #ትርጉም መሰረት #ይማልዳል የሚለው ቃል #ይፈርዳል ተብሎ ሊተረጎም የሚችልበት ምንም ዓይነት አግባብ እንደ ሌለ መመልከት ይቻላል። በመሆኑም ጸሀፊው የሌለ #ትርጉም በመስጠት ሰውን #ለማሳሳት እየሞከሩ ነው ከማለት ያለፈ ሊባል የሚችል ምንም ነገር የለም።

ይቀጥላል...(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
መጽሀፈ ሰአታት

💠 "ሰዓሊ ለነ ሰንበት ክርስቲያን ቅድስት፣ ለውለደ ሰብእ መድኃኒት፣ ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት"
💠 " ለሰው ልጆች መድኃኒት የሆንሽ እስከ ዘላለም ገዢ የሆንሽ የክርስቲያን ሰንበት ሆይ ለምኝልን (አማልጅን)
/ሰዓሊ ለነ ከሚባል ክፍል -- ገጽ 30/

▶️ የመጽሀፉ ደራሲ #ሰንበተ #ክርስቲያን የሚለው #ዕለተ #እሁድን እንደሆነ ከተለመደው አባባል ማወቅ ይቻላል። #እሑድን በተመለከተ በግእዙ ሐዲስ ኪዳን <<ወበእሑድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት>> የሚባል ንባብ ይገኛል(ዩሐ 20፥1)። በአማርኛው ግን <<ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን ማርያም መግደላዊት ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች>> ይላል። ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን የሚለው በግሪኩ <<μιᾷτῶν σαββάτων/ሚያ ቶን ሳባቶን/>> የሚለው ቃል ሲሆን ትርጉሙም ያው <ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን> የሚል ነው። በግእዙ <<ወበእሑድ ሰንበት>> የሚለው ንባብ ግን በግሪኩ ስለሌለ #የትርጉም #ስህተት መሆኑ ግልጽ ነው። እንዲሁም በሌላ ቦታ <<ወበዕለተ እሑድ እንዘ ጉቡኣን ንሕነ ከመ ንባርክ ማዕደ>>/ሐዋ 20፥7/ ይላል፤ ይህም በአማርኛው << #ከሳምንቱ #በመጀመሪያው ቀን እንጀራ ለመቁረስ ተሰብስበን ሳለን..>> ተብሎ #የተተረጎመ ሲሆን በዚህኛውም ሆነ በፊተኛው ምንባብ ያለው #የግሪኩ ቃል እሁድ ሰንበት እንደሆነች የማያሳይ በመሆኑ "እለተ እሑድ" <<ሰንበት>> እንደሆነች የማያሳይ በመሆኑ "እለተ እሁድ" <<ሰንበት>> እንደሆነች የሚናገረው የግእዝ ንባብ #የትርጉም #ስህተት የወለደው መሆኑን እንገነዘባለን። ለብሉይ ኪዳን #ህዝብ #እግዚአብሔር #ዕረፍተ #ስጋ እንድትሆናቸው #ዕለተ #ሰንበትን ሰጥቷቸው ነበር፤ ይሁንና #ሰንበት #በጥላነት #ክርስቶስን ታመለክት ነበር፤ ይህንንም መጽሀፍ ቅዱስ ሲያስረዳ <<እንግዲህ #በመብል ወይም #በመጠጥ ወይም ስለ #በዓል ወይም ስለ #ወር መባቻ ወይም ስለ #ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ፤ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች #ጥላ ናቸውና #አካሉ ግን #የክርስቶስ ነው>> ይላል/ቆላ 2፤ 16-17/። ስለሆነም <በአዲስ ኪዳን> #ሰንበተ #ክርስቲያን #ኢየሱስ #ክርስቶስ ነው እንጂ #ዕለተ #እሑድ አይደለችም።
ከዚህም ጋር ደግሞ << ንዑ ኅቤየ ኲልክሙ ስሩሐን ወጽዑራን ወአነ አአርፈክሙ ማለትም እናንተ ደካሞች #ሸክማችሁ #የከበደ ሁሉ ወደኔ ኑ እኔም #አሳርፋችኋለሁ>>/ማቴ 11፥29/ የሚለውን ማስተዋል ያስፈልጋል፤ ይህንን በመረዳት አንዲት #የማትሰማና #ሕያዊት ያልሆነች #የጊዜ #ክፍልፋይ ዕለተ #እሁድን #ሰንበት ብሎ ማክበርን ትቶ <አማናዊውን ሰንበት> #ክርስቶስን ማክበርና #በእርሱም #ማረፍ ይገባል።
እጅግ #የሚያሳዝነው ደግሞ ዕለቷ <<ለውሉደ ሰብእ መድኃኒት ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት>> <<ለሰው ልጆች #መድኃኒት ለዘላለዓም #ገዥ የሆንሽ>> መባሏ ነው። #የኑፋቄውን ክፋት ለመረዳት ለዚህች #ዕለት የተሰጡትንና #መድኃኒት#ገዥ የሚሉትን #ቃላት እንመርምር።