#ተሰደደ
-ከገነት የተሰደደ አዳምን ይመልሰው ዘንድ ዳግማይ አዳም ተሰደደ
-የነቢያት፣ የሐዋርያት ፣የቅዱሳኑን ሁሉ ስደት ይባርክ ዘንድ ተሰደደ
-የግብጽን ጣዖታት ያሳፍራቸው ዘንድ ተሰደደ
-ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ ተሰደደ
“ስለ ግብጽ የተነገረ ሸክም። እነሆ፥ #እግዚአብሔር_በፈጣን_ደመና እይበረረ ወደ ግብጽ ይመጣል፤ የግብጽም ጣዖታት በፊቱ ይርዳሉ፥ የግብጽም ልብ በውስጥዋ ይቀልጣል።” ኢሳ 19፥1
-ከገነት የተሰደደ አዳምን ይመልሰው ዘንድ ዳግማይ አዳም ተሰደደ
-የነቢያት፣ የሐዋርያት ፣የቅዱሳኑን ሁሉ ስደት ይባርክ ዘንድ ተሰደደ
-የግብጽን ጣዖታት ያሳፍራቸው ዘንድ ተሰደደ
-ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ ተሰደደ
“ስለ ግብጽ የተነገረ ሸክም። እነሆ፥ #እግዚአብሔር_በፈጣን_ደመና እይበረረ ወደ ግብጽ ይመጣል፤ የግብጽም ጣዖታት በፊቱ ይርዳሉ፥ የግብጽም ልብ በውስጥዋ ይቀልጣል።” ኢሳ 19፥1
❤ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው❤
ክፍል 1 በመምህር ኢዮብ ክንፈ
ሦስቱ የጥበብ ሰዎች የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?እያሉ ወደ ምድረ እስራኤል ከመጡ ወዲህ ሄሮድስ ተሸብሯል።ምክንያቱም ንጉሥ ንጉሥን ሳይገድል አይነግሥም ከሚል ሥጋት ነው።ጠቢባኑን ሰብስቦ ይወለድ ዘንድ ስላለው ስለ መሲሑ ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ይገድለው ዘንድ ለንጉሡ ሰግደው እሱም ይሰግድለት ዘንድ መጥተው እንዲነግሩት በተንኮል ነገራቸው።ለሄሮድስ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ሥልጣንን ቀምቶ የሚነግሥ ሳይሆን በሚወዱትና በሚያምኑት ላይ ነግሦ የሚኖር መሆኑን ማን በነገረው።ሰማይና ምድር በመላ የገዛ ግዛቱ መሆናቸውን ማን ባስረዳው።ለእርሱ ለራሱ ንግሥናን የሰጠው የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ መሆኑን ቢረዳ ወደ ሕፃኑ በሄደ ከጥበብ ሰዎችም ጋር እጅ መንሻ ባቀረበ ነበር።
ሦስቱ የጥበብ ሰዎች ለጥበብ ክርስቶስ እጅ መንሻ ካቀረቡ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር እንዳመለከታቸው በሌላ መንገድ ሄዱ።ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደተሳለቁበት ባወቀ ጊዜ እብደቱ አይሏል።ሄሮድስ ሆይ ሰብአ ሰገል ጥበብን ካገኙ በኋላ በድንቁርና ፤ ፍቅርን ካገኙ በኋላ በጥል ፤ ሕይወትን ካገኙ በኋላ በሞት መንገድ እንዲሄዱ ስለምን ፈለግህ?እነሱስ መንገዳቸው ክርስቶስን አግኝተዋል ስለዚህ በአንተ መንገድ መሄድ አያሻቸውም።
ሰይጣን ላይ መሳለቅ እንዲህ ነው።ሕፃኑን አግኝቶ በሌላ አዲስ መንገድ መሄድ።
ሄሮድስ ሕፃኑን ፍለጋ ከሰብአ ሰገል እንደተረዳው ዘመን ሁለት ዓመትና ከዚያ በታች የሆናቸውን ሕፃናት በእርዳታ ስም ሰብስቦ ፈጃቸው።ዛሬም ምእመናንን በእርዳታ ስም እየሸነገሉ ሃይማኖታቸውን እያስካዱና ማዕተባቸውን እያስበጠሱ በነፍስ የሚፈጇቸው ሄሮድሳውያን ሞልተዋል።ጥበብ ሲጎድል እንዲህ ነው ብስጭት ፣ አለመረጋጋት ፣ ፍጅት ይከተላሉ።በጌታ መከራ የተሳተፉ አእላፍ ሕፃናት የታደሉ ናቸው።ሰማዕታተ ክርስቶስ ሆነዋልና
ሄሮድስ ክርስቶስን አሳደደው።ድንግልም ልጇን ይዛ ተሰደደች።እውነት በሐሰት ፣ ፍቅር በጥል ፣ ብርሃን በጨለማ ፣ ሕይወት በሞት ፣ እጅግ ኃያሉ በእጅጉ ደካማው ፣ ፈጣሪ በፍጡር ዛሬ በምድር ተሰደደ።ይህ እንዴት ያለ ትሕትና ነው? ከምድር ሰውነታችን የዓለምና የምኞቱ ፍቅር ሕፃኑን ከእናቱ ጋር አላሳደደውምን?እንግዲያውስ የቀደመ እኩይ ግብራችንን ትተን እንደ ሰብአ ሰገል በሌላ መንገድ እንሂድ።
የሔዋን ተስፋ ድንግል የአዳም ተስፋ ልጇ ክርስቶስን ይዛ በረሃ ለበረሃ ተንከራተተች።ቀኑን ለሠራዊት ሌሊቱን ለአራዊት የሰጠ አምላክ ከእናቱ ጋር ቀንና ሌሊት ተንከራተተ።ድንግል ሆይ መናን ይዘሽ መራብሽ ፣ ውኃን አዝለሽ መጠማትሽ እንዴት ያለ ነገር ነው?ፍጥረታትን በቸርነቱ የሚመግበውን ይዤ እንዴት እራበለሁ?የአፍላጋትን ጌታ ታቅፌ እንዴት እጠማለሁ?አላለችም።ቅዱስ ሉቃስ እንደነገረን ይህን ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር እንጂ።
ፀሐይን የተጎናፀፈች፣ከእግሮቿ በታች ጨረቃን የተጫማችና የዐሥራ ሁለት ከዋክብት የሆኑላት እመቤት በእነዚህ ብርሃናት መፈራረቅ ተንገላታች።በልጇ አምላክነት ግን አንዳች ጥርጣሬ አልገባትም።"ያመነች ብፅዕት ናትና"።
ሃይማኖተኛ ቢያንስ አንዴ ሊጠራጠር ይችላል።ሃይማኖት ግን ምን ብላ ትጠራጠራለች።እመቤታችን ራሷ ሃይማኖት ናት።"የቀናች የቅዱሳን አባቶቻችን ሃይማኖታቸው ነሽ"እንዲል።(ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ)።እመቤታችን በዚህ
ምድር ስትመላለስ ምድር በሷ አበባነት በልጇ ውበት ፈካች።ድንግል ሆይ እንፈካ ዘንድ ከልጅሽ ጋር በልባችን ተመላለሺበት።
ከቀደመ አባታችን አዳም ልቡና በምክረ ሰይጣን ሃይማኖት
፣ ተስፋ ፣ ፍቅር ተሰደው ነበር።ሃይማኖት እግዚአብሔርን አምኖ በእርሱም ታምኖ መኖር ነው ፤ ተስፋ መንግሥቱን ያወርሰኛል ማለት ነው ፤ ፍቅር ትእዛዙን መጠበቅ ነው። "ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ"እንዳለን።አዳምን ለመካስ ሃይማኖት ፣ ተስፋ ፣ ፍቅር ጌታ ተሰደደለት።አስቀድሞ በገነት ዛፎች መካከል የሰው ኮቴ እያሰማ አዳምን የፈለገ እግዚአብሔር አሁን ደግሞ ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ እያለቀሰ ፈለገው።ፍቅር ፍለጋ ነውና።
አምላካችን ሆይ ሃይማኖታችን አንተን ከሚያርቅብን ክህደት ፣ተስፋችን አንተን ከሚያስጥለን ቀቢጸ ተስፋ ፣ፍቅራችን አንተን ከሚነጥቀን ጥላቻ ሄሮድስ እንድትሠውረን አንድ ልጇ አንተን ይዛ በተንገላታች ድንግል እናትህ እንለምንሃለን።"ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ" ማለት እዚህ ጋር ነው።
ማርያም ወረደች አሸዋ ለአሸዋ
ማንን ይዛ?አንድ አምላክን ይዛ!!!
የሚሉ እናቶቻችን አንድ አምላክን ይዞ የመሰደድ ነገር እንዴት የገባቸው ናቸው።
መስከረም 27 2012 ዓ.ም
ክፍል 1 በመምህር ኢዮብ ክንፈ
ሦስቱ የጥበብ ሰዎች የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?እያሉ ወደ ምድረ እስራኤል ከመጡ ወዲህ ሄሮድስ ተሸብሯል።ምክንያቱም ንጉሥ ንጉሥን ሳይገድል አይነግሥም ከሚል ሥጋት ነው።ጠቢባኑን ሰብስቦ ይወለድ ዘንድ ስላለው ስለ መሲሑ ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ይገድለው ዘንድ ለንጉሡ ሰግደው እሱም ይሰግድለት ዘንድ መጥተው እንዲነግሩት በተንኮል ነገራቸው።ለሄሮድስ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ሥልጣንን ቀምቶ የሚነግሥ ሳይሆን በሚወዱትና በሚያምኑት ላይ ነግሦ የሚኖር መሆኑን ማን በነገረው።ሰማይና ምድር በመላ የገዛ ግዛቱ መሆናቸውን ማን ባስረዳው።ለእርሱ ለራሱ ንግሥናን የሰጠው የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ መሆኑን ቢረዳ ወደ ሕፃኑ በሄደ ከጥበብ ሰዎችም ጋር እጅ መንሻ ባቀረበ ነበር።
ሦስቱ የጥበብ ሰዎች ለጥበብ ክርስቶስ እጅ መንሻ ካቀረቡ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር እንዳመለከታቸው በሌላ መንገድ ሄዱ።ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደተሳለቁበት ባወቀ ጊዜ እብደቱ አይሏል።ሄሮድስ ሆይ ሰብአ ሰገል ጥበብን ካገኙ በኋላ በድንቁርና ፤ ፍቅርን ካገኙ በኋላ በጥል ፤ ሕይወትን ካገኙ በኋላ በሞት መንገድ እንዲሄዱ ስለምን ፈለግህ?እነሱስ መንገዳቸው ክርስቶስን አግኝተዋል ስለዚህ በአንተ መንገድ መሄድ አያሻቸውም።
ሰይጣን ላይ መሳለቅ እንዲህ ነው።ሕፃኑን አግኝቶ በሌላ አዲስ መንገድ መሄድ።
ሄሮድስ ሕፃኑን ፍለጋ ከሰብአ ሰገል እንደተረዳው ዘመን ሁለት ዓመትና ከዚያ በታች የሆናቸውን ሕፃናት በእርዳታ ስም ሰብስቦ ፈጃቸው።ዛሬም ምእመናንን በእርዳታ ስም እየሸነገሉ ሃይማኖታቸውን እያስካዱና ማዕተባቸውን እያስበጠሱ በነፍስ የሚፈጇቸው ሄሮድሳውያን ሞልተዋል።ጥበብ ሲጎድል እንዲህ ነው ብስጭት ፣ አለመረጋጋት ፣ ፍጅት ይከተላሉ።በጌታ መከራ የተሳተፉ አእላፍ ሕፃናት የታደሉ ናቸው።ሰማዕታተ ክርስቶስ ሆነዋልና
ሄሮድስ ክርስቶስን አሳደደው።ድንግልም ልጇን ይዛ ተሰደደች።እውነት በሐሰት ፣ ፍቅር በጥል ፣ ብርሃን በጨለማ ፣ ሕይወት በሞት ፣ እጅግ ኃያሉ በእጅጉ ደካማው ፣ ፈጣሪ በፍጡር ዛሬ በምድር ተሰደደ።ይህ እንዴት ያለ ትሕትና ነው? ከምድር ሰውነታችን የዓለምና የምኞቱ ፍቅር ሕፃኑን ከእናቱ ጋር አላሳደደውምን?እንግዲያውስ የቀደመ እኩይ ግብራችንን ትተን እንደ ሰብአ ሰገል በሌላ መንገድ እንሂድ።
የሔዋን ተስፋ ድንግል የአዳም ተስፋ ልጇ ክርስቶስን ይዛ በረሃ ለበረሃ ተንከራተተች።ቀኑን ለሠራዊት ሌሊቱን ለአራዊት የሰጠ አምላክ ከእናቱ ጋር ቀንና ሌሊት ተንከራተተ።ድንግል ሆይ መናን ይዘሽ መራብሽ ፣ ውኃን አዝለሽ መጠማትሽ እንዴት ያለ ነገር ነው?ፍጥረታትን በቸርነቱ የሚመግበውን ይዤ እንዴት እራበለሁ?የአፍላጋትን ጌታ ታቅፌ እንዴት እጠማለሁ?አላለችም።ቅዱስ ሉቃስ እንደነገረን ይህን ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር እንጂ።
ፀሐይን የተጎናፀፈች፣ከእግሮቿ በታች ጨረቃን የተጫማችና የዐሥራ ሁለት ከዋክብት የሆኑላት እመቤት በእነዚህ ብርሃናት መፈራረቅ ተንገላታች።በልጇ አምላክነት ግን አንዳች ጥርጣሬ አልገባትም።"ያመነች ብፅዕት ናትና"።
ሃይማኖተኛ ቢያንስ አንዴ ሊጠራጠር ይችላል።ሃይማኖት ግን ምን ብላ ትጠራጠራለች።እመቤታችን ራሷ ሃይማኖት ናት።"የቀናች የቅዱሳን አባቶቻችን ሃይማኖታቸው ነሽ"እንዲል።(ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ)።እመቤታችን በዚህ
ምድር ስትመላለስ ምድር በሷ አበባነት በልጇ ውበት ፈካች።ድንግል ሆይ እንፈካ ዘንድ ከልጅሽ ጋር በልባችን ተመላለሺበት።
ከቀደመ አባታችን አዳም ልቡና በምክረ ሰይጣን ሃይማኖት
፣ ተስፋ ፣ ፍቅር ተሰደው ነበር።ሃይማኖት እግዚአብሔርን አምኖ በእርሱም ታምኖ መኖር ነው ፤ ተስፋ መንግሥቱን ያወርሰኛል ማለት ነው ፤ ፍቅር ትእዛዙን መጠበቅ ነው። "ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ"እንዳለን።አዳምን ለመካስ ሃይማኖት ፣ ተስፋ ፣ ፍቅር ጌታ ተሰደደለት።አስቀድሞ በገነት ዛፎች መካከል የሰው ኮቴ እያሰማ አዳምን የፈለገ እግዚአብሔር አሁን ደግሞ ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ እያለቀሰ ፈለገው።ፍቅር ፍለጋ ነውና።
አምላካችን ሆይ ሃይማኖታችን አንተን ከሚያርቅብን ክህደት ፣ተስፋችን አንተን ከሚያስጥለን ቀቢጸ ተስፋ ፣ፍቅራችን አንተን ከሚነጥቀን ጥላቻ ሄሮድስ እንድትሠውረን አንድ ልጇ አንተን ይዛ በተንገላታች ድንግል እናትህ እንለምንሃለን።"ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ" ማለት እዚህ ጋር ነው።
ማርያም ወረደች አሸዋ ለአሸዋ
ማንን ይዛ?አንድ አምላክን ይዛ!!!
የሚሉ እናቶቻችን አንድ አምላክን ይዞ የመሰደድ ነገር እንዴት የገባቸው ናቸው።
መስከረም 27 2012 ዓ.ም
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ከሞተ ሰው አፍ ውስጥ ጽጌ ሬዳ አበባ በቅሎ ተገኘ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ከኢየሩሳሌም በቅርብ እርቀት ላይ በምትገኘው በኢያሪኮ ደሰት የሚኖር እመቤታችንን እጅግ አብዝቶ የሚወድ ስመ " አስቴራስ " የሚባል አንድ ዲያቆን ነበር ከሴቶች ሁለ ተለይተሽ #የተባረክሽ_ድንግል_ማርያም_ሆይ_አምላክን_በድንግና_ጸንሰሽ_በድንግልና_ትወልጃለሽና_ደስ_ይበልሽ እያለ #ቅዱስ_ገብርኤል_ያበሰራትንና ያቀረበላትን ሠላምታ ሳያቆርጥ ዘወትር ይጸልይ ነበር :: ሉቃ 1÷26 -29
ከዕለትም በአንዲቱ ቀን ለሥራው ወደ እሩቅ ሀገር ሲሄድ እርህራኄ የሌላቸው ሰዎች በመንገድ አገኙትና ገድለው ሳይቀብሩት ሄዱ። ነገር ግን ሊሎች ሰዎች በመንገደድ ሲያልፉሁ አስክሬኑን አይተው ከመንገዱ ጥግ መቃብር ቆፍረው ቀብረውት ሄዱ።
ከተቀበረም ከሦስት ቀይ በኃላም ክፉ ሰዎች ባሉባት በዚያች ሀገር ባለች ቤተ ክርስቲያን ቅንነት ለሚያገለግል አንድ ዲያቆን እመቤታችን በእራይ ተገልጻ ወዳጄ ሆይ ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለገለና ጸሎቱ በእኔና በልጄ ዘንድ እጅግ የተወደደችለት አንድ ዲያቆንን ስለገደሉት ሰዎች አዝኛለሁ ጓደኞችህ ዲያቆናትን ይዘህ በመንገድ ጥግ ወደ ተቀበረው ዲያቆን ሂዱና መቃብሩን ቆፍራችሁ አስክሬኑን አውንታችሁ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ቅበሩት አለችው ። ዲያቆኑም እመቤታችን እንደ ነገረችው አጓደኞቹ ጋር ሄዶ መቃብሩን ቆፍረው አስክሬኑን ባወጡ ጊዜ " #ርሔ " እንደሚባል ሽቶ መዐዛው እጅግ ደስ የሚያሰኝ ከአፉሁ የበቀለ አንድ የጽጌ ሬዳን አበባ አገኙ " #መንክር_እግዚአብሔር በላይለ ቅዱሳኒሁ " # እግዚአብሔር_በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው " ተብሎ በነቢይ የተነገረውንም አስበው ፈጽመው አደነቁ መዝ 67÷ 65 ክዎች ሰዎች ከገደሉት ከዲያቆን "አስቴራስ " አስክሬን አፍ የጽጌ ጌዳ አበባ በቅሎ መገኘቱን ያዮና የሰሙ ሰዎችም ሁሉ ይህስ ከዚህ በፊት በዐይናችን ያላየነውና በታሪክም ያልሰማነው አዲስና አስደናቂ ነገር ነው እያሉ በማድነቅ ለዲያቆን እንደሚገባ አድርገው እንደ ሥርዓቱ አክብረው በቤተክርስቲያን ቅጥር ቀበሩት ::
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ልመና ክብሯ አማላጅነቷም እስከ ዘላለሙ ድረስ ከና አይራቅብን አሜን!
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ምንጭ:-
በምሥራቅ ጎጃም ሞጣ ደብረ ገነተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያለ የብራና ተአምረ ማርያም ገጽ 223 ጠቅሶ የጻፈው ማህሌተ ጽጌ የተሰኘው ትንሽዬ መጻሕፍ ነው
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ከኢየሩሳሌም በቅርብ እርቀት ላይ በምትገኘው በኢያሪኮ ደሰት የሚኖር እመቤታችንን እጅግ አብዝቶ የሚወድ ስመ " አስቴራስ " የሚባል አንድ ዲያቆን ነበር ከሴቶች ሁለ ተለይተሽ #የተባረክሽ_ድንግል_ማርያም_ሆይ_አምላክን_በድንግና_ጸንሰሽ_በድንግልና_ትወልጃለሽና_ደስ_ይበልሽ እያለ #ቅዱስ_ገብርኤል_ያበሰራትንና ያቀረበላትን ሠላምታ ሳያቆርጥ ዘወትር ይጸልይ ነበር :: ሉቃ 1÷26 -29
ከዕለትም በአንዲቱ ቀን ለሥራው ወደ እሩቅ ሀገር ሲሄድ እርህራኄ የሌላቸው ሰዎች በመንገድ አገኙትና ገድለው ሳይቀብሩት ሄዱ። ነገር ግን ሊሎች ሰዎች በመንገደድ ሲያልፉሁ አስክሬኑን አይተው ከመንገዱ ጥግ መቃብር ቆፍረው ቀብረውት ሄዱ።
ከተቀበረም ከሦስት ቀይ በኃላም ክፉ ሰዎች ባሉባት በዚያች ሀገር ባለች ቤተ ክርስቲያን ቅንነት ለሚያገለግል አንድ ዲያቆን እመቤታችን በእራይ ተገልጻ ወዳጄ ሆይ ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለገለና ጸሎቱ በእኔና በልጄ ዘንድ እጅግ የተወደደችለት አንድ ዲያቆንን ስለገደሉት ሰዎች አዝኛለሁ ጓደኞችህ ዲያቆናትን ይዘህ በመንገድ ጥግ ወደ ተቀበረው ዲያቆን ሂዱና መቃብሩን ቆፍራችሁ አስክሬኑን አውንታችሁ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ቅበሩት አለችው ። ዲያቆኑም እመቤታችን እንደ ነገረችው አጓደኞቹ ጋር ሄዶ መቃብሩን ቆፍረው አስክሬኑን ባወጡ ጊዜ " #ርሔ " እንደሚባል ሽቶ መዐዛው እጅግ ደስ የሚያሰኝ ከአፉሁ የበቀለ አንድ የጽጌ ሬዳን አበባ አገኙ " #መንክር_እግዚአብሔር በላይለ ቅዱሳኒሁ " # እግዚአብሔር_በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው " ተብሎ በነቢይ የተነገረውንም አስበው ፈጽመው አደነቁ መዝ 67÷ 65 ክዎች ሰዎች ከገደሉት ከዲያቆን "አስቴራስ " አስክሬን አፍ የጽጌ ጌዳ አበባ በቅሎ መገኘቱን ያዮና የሰሙ ሰዎችም ሁሉ ይህስ ከዚህ በፊት በዐይናችን ያላየነውና በታሪክም ያልሰማነው አዲስና አስደናቂ ነገር ነው እያሉ በማድነቅ ለዲያቆን እንደሚገባ አድርገው እንደ ሥርዓቱ አክብረው በቤተክርስቲያን ቅጥር ቀበሩት ::
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ልመና ክብሯ አማላጅነቷም እስከ ዘላለሙ ድረስ ከና አይራቅብን አሜን!
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ምንጭ:-
በምሥራቅ ጎጃም ሞጣ ደብረ ገነተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያለ የብራና ተአምረ ማርያም ገጽ 223 ጠቅሶ የጻፈው ማህሌተ ጽጌ የተሰኘው ትንሽዬ መጻሕፍ ነው
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ከጸሎተኛው_አፍ_በሚወጣ_አበባ ያመኑ ሽፍቶች
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ከሮም ነገሥታት ወገን የሆነ ስሙ ዘካሪያስ የሚባል ጎልማሳ ሰው ነበር ከዕለታት አንድ ቀን #ቤተ_ክርስቲያን ገብቶ #ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ሲጸልይ ከሥዕሏ ማማር የተነሳ እጅግ ደስ አለውና ለዚህች ሥዕል ምን ዐይነት እጅ መንሻ ላቅርብላት እያለ ሲያወጣና ሲያወርድ ወራቱ የጽጌ ጌዳ ወራት ነበርና ፶ (50) የጽጌ ጌዳ አበባ ወስዶ ዘውድ አስመስሎና አክሊል ሰርቶ ከሥዕሏ እራስ ላይ ወስዶ በክብር አቀዳጃት ይህ ሰው እንዲ እያደሰገ ሲጸልይ ከቆየ በኃላ የጽጌ ወራት ባለፈ ጊዜ ግን ለሥዕሏ ክብር የሚያቀርብላት የጽጌ ሬዳ አበባ በማጣቱ እጅግ አዝኖ ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሄደና #እመቤቴ ሆይ የጽጌ ሬዳ፣ የአበባ ወራት እንዳለፈ አንቺ ታውቂያለሽ በ፶ (50)ው የጽጌ ሬዳ አበባ ፈንታ (ምትክ) ፶ (50)ጊዜ #በሠላመ_ቅዱስ_ገብርኤልን የሚለውን ጸሎትሽን ወይም ሠላምታሽን እጸልያለው በማለት እንዲ አለ " #እመቤቴ_ማርያም_ሆይ_በመላእኩ_በቅዱስ_ገብርኤል_ሠላምታ_ሠላም_እልሻለሁ_እግዚአብሔር_ካንቺ_ጋር_ነውና_ደስ_ይበልሽ " እያለ በየቀኑ ፶ (50) ጊዜ ሲጸልይ ኖረ ።
ከዕለታት አንድ ቀን ግን እረስቶ ይህችን ጸሎት ሳያደርስ መንገድ ጀመረ በመንገድም እያለ ይህችን ጸሎት አለማድረሱ ታወሰውና ጉዞውን ገታ አድርጎ ከመንገድም ወጣ ብሎ እንደ ቀድሞው እየሰገደ ሠላምታዋን ፶ (50) ጊዜ በጸሎት ማድረስ ቀጠለ ሲጸልይም ከአፉሁ በእያንዳንዱ ሠላምታ አንድ አንድ ጽጌ ሬዳ አበባ ይወጣ ነበር። #እመቤታችንም አበባው ፶ (50) እስኪሞላ ድረስ ከአፉሁ እየተቀበለች በክንዷ ሰብስባ ትታቀፈው ነበር :: በአካባቢው የነበረ የሽፍቶች አለቃ የሆነ አንድ ሰው ይህንን አይቶ ዘካሪያስ ጸሎቱን እስኪ ጨርስ ድረስ ከአፉሁ የሚወጡትን የጽጌ ሬዳ አበቦች ይቆጥር ጀመር። ዘካሪያስም ጸሎቱን ሲጨርስና አበባዎቹም ፶ ሲሞሉ #እመቤታችን ባርካው አበባዎቹን ይዛ ወደላይ ስታርግ ይህ የሽፍቶች አለቃ አይቶ እጅግ አደነቀና ጓደኛቱይ ጠርቶ " የጌታን ተአምራት ታዮ ዘንድ ኑ " ተብሎ እንደ ተጻፈ "የእመቤታችንን ተአምራት ያዮ ዘንድ ኑ " ብሎ ወደ ዘካሪያስ ወሰዳቸው መዝ 45÷8 ሽፍቶቹም ዘካሪያስን ይህ ድንቅ ተአምራት ምንድ ነው? ብለው ጠየቁት እርሱም እኔ ኃጢያተኛ ከመሆኔ በቀር ሌላ በጎ ሥራ የለኝም ነገር ግን የሠማይና የምድር ንግሥት የሆነች አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች የእመቤታችንን በሠላመ #ቅዱስ_ገብርኤል_መላእክ ሠላም እልሻለሁ እያልኩ #በቅዱስ_ገብርኤል ሙሉ ሰላምታ በየ ቀኑ ፶ ( 50)ጊዜ ሠላም እላታለሁኝ አላቸው በዚህ ጊዜ ደስ ብሏቸው ዘካሪያስን ሸኙት እነርሱም ከዛች ቀን ጀምሮ ከክፉሁ ሥራቸው ተመልሰው ወደ ገዳም ሄደው በምንኩስና ሕይወት ተወስነው መኖር ጀመሩ::
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ምንጭ:-
በምሥራቅ ጎጃም ሞጣ ደብረ ገነተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያለ የብራና ተአምረ ማርያም ገጽ 223 ጠቅሶ የጻፈው ማህሌተ ጽጌ የተሰኘው ትንሽዬ መጻሕፍ ነው
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ከሮም ነገሥታት ወገን የሆነ ስሙ ዘካሪያስ የሚባል ጎልማሳ ሰው ነበር ከዕለታት አንድ ቀን #ቤተ_ክርስቲያን ገብቶ #ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ሲጸልይ ከሥዕሏ ማማር የተነሳ እጅግ ደስ አለውና ለዚህች ሥዕል ምን ዐይነት እጅ መንሻ ላቅርብላት እያለ ሲያወጣና ሲያወርድ ወራቱ የጽጌ ጌዳ ወራት ነበርና ፶ (50) የጽጌ ጌዳ አበባ ወስዶ ዘውድ አስመስሎና አክሊል ሰርቶ ከሥዕሏ እራስ ላይ ወስዶ በክብር አቀዳጃት ይህ ሰው እንዲ እያደሰገ ሲጸልይ ከቆየ በኃላ የጽጌ ወራት ባለፈ ጊዜ ግን ለሥዕሏ ክብር የሚያቀርብላት የጽጌ ሬዳ አበባ በማጣቱ እጅግ አዝኖ ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሄደና #እመቤቴ ሆይ የጽጌ ሬዳ፣ የአበባ ወራት እንዳለፈ አንቺ ታውቂያለሽ በ፶ (50)ው የጽጌ ሬዳ አበባ ፈንታ (ምትክ) ፶ (50)ጊዜ #በሠላመ_ቅዱስ_ገብርኤልን የሚለውን ጸሎትሽን ወይም ሠላምታሽን እጸልያለው በማለት እንዲ አለ " #እመቤቴ_ማርያም_ሆይ_በመላእኩ_በቅዱስ_ገብርኤል_ሠላምታ_ሠላም_እልሻለሁ_እግዚአብሔር_ካንቺ_ጋር_ነውና_ደስ_ይበልሽ " እያለ በየቀኑ ፶ (50) ጊዜ ሲጸልይ ኖረ ።
ከዕለታት አንድ ቀን ግን እረስቶ ይህችን ጸሎት ሳያደርስ መንገድ ጀመረ በመንገድም እያለ ይህችን ጸሎት አለማድረሱ ታወሰውና ጉዞውን ገታ አድርጎ ከመንገድም ወጣ ብሎ እንደ ቀድሞው እየሰገደ ሠላምታዋን ፶ (50) ጊዜ በጸሎት ማድረስ ቀጠለ ሲጸልይም ከአፉሁ በእያንዳንዱ ሠላምታ አንድ አንድ ጽጌ ሬዳ አበባ ይወጣ ነበር። #እመቤታችንም አበባው ፶ (50) እስኪሞላ ድረስ ከአፉሁ እየተቀበለች በክንዷ ሰብስባ ትታቀፈው ነበር :: በአካባቢው የነበረ የሽፍቶች አለቃ የሆነ አንድ ሰው ይህንን አይቶ ዘካሪያስ ጸሎቱን እስኪ ጨርስ ድረስ ከአፉሁ የሚወጡትን የጽጌ ሬዳ አበቦች ይቆጥር ጀመር። ዘካሪያስም ጸሎቱን ሲጨርስና አበባዎቹም ፶ ሲሞሉ #እመቤታችን ባርካው አበባዎቹን ይዛ ወደላይ ስታርግ ይህ የሽፍቶች አለቃ አይቶ እጅግ አደነቀና ጓደኛቱይ ጠርቶ " የጌታን ተአምራት ታዮ ዘንድ ኑ " ተብሎ እንደ ተጻፈ "የእመቤታችንን ተአምራት ያዮ ዘንድ ኑ " ብሎ ወደ ዘካሪያስ ወሰዳቸው መዝ 45÷8 ሽፍቶቹም ዘካሪያስን ይህ ድንቅ ተአምራት ምንድ ነው? ብለው ጠየቁት እርሱም እኔ ኃጢያተኛ ከመሆኔ በቀር ሌላ በጎ ሥራ የለኝም ነገር ግን የሠማይና የምድር ንግሥት የሆነች አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች የእመቤታችንን በሠላመ #ቅዱስ_ገብርኤል_መላእክ ሠላም እልሻለሁ እያልኩ #በቅዱስ_ገብርኤል ሙሉ ሰላምታ በየ ቀኑ ፶ ( 50)ጊዜ ሠላም እላታለሁኝ አላቸው በዚህ ጊዜ ደስ ብሏቸው ዘካሪያስን ሸኙት እነርሱም ከዛች ቀን ጀምሮ ከክፉሁ ሥራቸው ተመልሰው ወደ ገዳም ሄደው በምንኩስና ሕይወት ተወስነው መኖር ጀመሩ::
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ምንጭ:-
በምሥራቅ ጎጃም ሞጣ ደብረ ገነተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያለ የብራና ተአምረ ማርያም ገጽ 223 ጠቅሶ የጻፈው ማህሌተ ጽጌ የተሰኘው ትንሽዬ መጻሕፍ ነው
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
Audio
#መዝሙር #ከካራን_ውጡ
#በአርቲስት #ነብዩ_ኤርሚያስ
#ክራር #ሀብታሙ_ሽፈራው
ከካራን ውጡ
ከካራን ውጡ ከነዓን ግቡ
ወደ ጽድቅ ሕይወት ዛሬ ቅረቡ
ካራን ጣኦት ነው የሚመለከው
የአህዛብ ሀገር የሞት መንደር ነው /2/
እንደ አባታችን እንደ አብርሃም
ወገኖች ውጡ ከካራን ዓለም
የግፍ እንጀራ ይብቃችሁና
ከካራን ውጡ በአምላክ ጎዳና
የጣኦት ምስል ከሚሸጥበት
ዓለም በዝሙት ከሚነድበት
ከሰዶም መንደር ከካራን ውጡ
የሃጢያትን ስር ዛሬ ቁረጡ
የሃጢያት ዓለም ዛሬ ይብቃና
የፍቅርን ሕይወት እንልበስና
ከካራን መንደር በፍጥነት ወጥተን
ከነዓን ገብተን ማደር አለብን
ማርና ወተት ከሚፈልቅበት
ሰዎች በፍቅር ከሚኖሩበት
ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም
ዛሬ ብንገባ እናገኛለን የአምላክን ሠላም
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#በአርቲስት #ነብዩ_ኤርሚያስ
#ክራር #ሀብታሙ_ሽፈራው
ከካራን ውጡ
ከካራን ውጡ ከነዓን ግቡ
ወደ ጽድቅ ሕይወት ዛሬ ቅረቡ
ካራን ጣኦት ነው የሚመለከው
የአህዛብ ሀገር የሞት መንደር ነው /2/
እንደ አባታችን እንደ አብርሃም
ወገኖች ውጡ ከካራን ዓለም
የግፍ እንጀራ ይብቃችሁና
ከካራን ውጡ በአምላክ ጎዳና
የጣኦት ምስል ከሚሸጥበት
ዓለም በዝሙት ከሚነድበት
ከሰዶም መንደር ከካራን ውጡ
የሃጢያትን ስር ዛሬ ቁረጡ
የሃጢያት ዓለም ዛሬ ይብቃና
የፍቅርን ሕይወት እንልበስና
ከካራን መንደር በፍጥነት ወጥተን
ከነዓን ገብተን ማደር አለብን
ማርና ወተት ከሚፈልቅበት
ሰዎች በፍቅር ከሚኖሩበት
ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም
ዛሬ ብንገባ እናገኛለን የአምላክን ሠላም
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#መዝሙር #ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ
#በአርቲስት #ነብዩ_ኤርሚያስ እና #ዳዊት_ክብሩ
#ክራር #ሀብታሙ_ሽፈራው
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘይሰርር በአክናፍ
ኀበ ዓምደ ወርቅ(2) ስሙ ጽሑፍ
እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ።
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#በአርቲስት #ነብዩ_ኤርሚያስ እና #ዳዊት_ክብሩ
#ክራር #ሀብታሙ_ሽፈራው
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘይሰርር በአክናፍ
ኀበ ዓምደ ወርቅ(2) ስሙ ጽሑፍ
እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ።
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ስለ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ የሚባሉ ተአማኚነት ያላቸው ይትባህሎች
፩. #አስታራቂነት ፡-ነብርና አንበሳ አይስማሙም፤ በአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሥዕል ሥር ግን ነብርና አንበሳ ተስማምተው ይታያሉ፡፡ በዚህ የተነሣ ለመታረቅ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለማስታረቅ የሚሄዱ ሽማግሌዎች ‹አቦን ሆነን መጥተናል› ይላሉ፡፡
፪. #የአቦ_ጠበል ፡- አንድ ሰው እየተመገበ ቢያንቀው ‹የአቦ ጠበል› እያልክ ውኃን ሦስት ጊዜ ጠጣው ይባላል፡፡
፫. #የአቦ_ብቅል ፡- አንድ ሰው ከማያውቀው ቦታ ስሙ ቢጠራና በአካባቢው የሚያውቀውን ሰው ቢያጣ የጠራው ሰይጣን ሊሆን ስለሚችል ‹‹የአቦን ብቅል እፈጫለሁ› በል ይባላል፡፡
፬. #የአቦ_መገበሪያ ፡- አንድ ሰው አንድን ነገር አጥፍቶ ተሠውሮ እንደማይቀመጥ ለመግለጥ ‹‹የአቦን መገበሪያ የበላ ሲለፈልፍ ይውላል›› ይባላል፡፡
፭. #አቦ_ሰጥ ፡- አንድ ሰው የማያውቀውን ነገር በግምት ሲናገር ‹አቦ ሰጥ› ይባላል፡፡
፮. #በአቦ_ይዤሃለሁ ፡- አራዊት የቤት እንስሳትን እንዳይበሉባቸው ገበሬዎች ‹በአቦ ይዤሃለሁ› ብለው ይገዝቷቸዋል፡፡
፯. #የአቦ_መንገድ ፡- በሰሜን ሸዋ መራኛ አካባቢ ባሉ ሕዝቦች ዘንድ ‹የአቦ መንገድ› የሚባል ብሂል አለ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሚዳ ከሚገኘው የአቡነ መልከ ጼዴቅ ገዳም ጥቂት ጊዜ ቆይተዋል ይባላል፡፡ በኋላ ከዚያ ገዳም ሲወጡ አቡነ መልከ ጼዴቅ ‹‹የት ሊሄዱ ነው›› ብለው ቢጠይቋቸው ‹እርሱ ወደ መራኝ›› ብለው መለሱላቸው፡፡
ከተማው ‹‹መራኛ›. የተባለው በዚህ ምክንያት ነው ይባላል፡፡ ታድያ በዚህ ምክንያት አንድ ሰው መድረሻውን በውል ሳያውቀው መንገድ ሲጀምር መንገዱ ‹የአቦ መንገድ› ይባላል፡፡
፰. #የአቦ_ቁራ ፡- ሰይጣን በቁራ ተመስሎ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ዓይናቸውን ሊያወጣ ስለመጣ በጎ ነገር የያዘ መስሎ የሚመጣ ክፉ ሰው ‹የአቦ ቁራ› ይባላል፡፡
፱. #በአቦ_በሥላሴ ፡- በሕዝቡ ብሂል ውስጥ ከሥላሴ ጋር ተያይዘው ብዙ ጊዜ የሚጠሩት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ‹በአቦ በሥላሴ› ሲባል አጥብቆ መለመን ነው፡፡ በሕዝባዊ መዝሙሮችም ውስጥ ‹በአምስት አቦ ናቸው በሰባት ሥላሴ› የሚል ሐረግ በተደጋጋሚ ይሰማል፡፡
#እረድኤት በረከታቸው ከኛ ከ ኢትዮጵያዊያ እስከ ዘላለሙ ድረስ አይለየን 🙏
#ምንጭ :- ከሙሃዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ጽሁፍ የተቀነጨበ
፩. #አስታራቂነት ፡-ነብርና አንበሳ አይስማሙም፤ በአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሥዕል ሥር ግን ነብርና አንበሳ ተስማምተው ይታያሉ፡፡ በዚህ የተነሣ ለመታረቅ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለማስታረቅ የሚሄዱ ሽማግሌዎች ‹አቦን ሆነን መጥተናል› ይላሉ፡፡
፪. #የአቦ_ጠበል ፡- አንድ ሰው እየተመገበ ቢያንቀው ‹የአቦ ጠበል› እያልክ ውኃን ሦስት ጊዜ ጠጣው ይባላል፡፡
፫. #የአቦ_ብቅል ፡- አንድ ሰው ከማያውቀው ቦታ ስሙ ቢጠራና በአካባቢው የሚያውቀውን ሰው ቢያጣ የጠራው ሰይጣን ሊሆን ስለሚችል ‹‹የአቦን ብቅል እፈጫለሁ› በል ይባላል፡፡
፬. #የአቦ_መገበሪያ ፡- አንድ ሰው አንድን ነገር አጥፍቶ ተሠውሮ እንደማይቀመጥ ለመግለጥ ‹‹የአቦን መገበሪያ የበላ ሲለፈልፍ ይውላል›› ይባላል፡፡
፭. #አቦ_ሰጥ ፡- አንድ ሰው የማያውቀውን ነገር በግምት ሲናገር ‹አቦ ሰጥ› ይባላል፡፡
፮. #በአቦ_ይዤሃለሁ ፡- አራዊት የቤት እንስሳትን እንዳይበሉባቸው ገበሬዎች ‹በአቦ ይዤሃለሁ› ብለው ይገዝቷቸዋል፡፡
፯. #የአቦ_መንገድ ፡- በሰሜን ሸዋ መራኛ አካባቢ ባሉ ሕዝቦች ዘንድ ‹የአቦ መንገድ› የሚባል ብሂል አለ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሚዳ ከሚገኘው የአቡነ መልከ ጼዴቅ ገዳም ጥቂት ጊዜ ቆይተዋል ይባላል፡፡ በኋላ ከዚያ ገዳም ሲወጡ አቡነ መልከ ጼዴቅ ‹‹የት ሊሄዱ ነው›› ብለው ቢጠይቋቸው ‹እርሱ ወደ መራኝ›› ብለው መለሱላቸው፡፡
ከተማው ‹‹መራኛ›. የተባለው በዚህ ምክንያት ነው ይባላል፡፡ ታድያ በዚህ ምክንያት አንድ ሰው መድረሻውን በውል ሳያውቀው መንገድ ሲጀምር መንገዱ ‹የአቦ መንገድ› ይባላል፡፡
፰. #የአቦ_ቁራ ፡- ሰይጣን በቁራ ተመስሎ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ዓይናቸውን ሊያወጣ ስለመጣ በጎ ነገር የያዘ መስሎ የሚመጣ ክፉ ሰው ‹የአቦ ቁራ› ይባላል፡፡
፱. #በአቦ_በሥላሴ ፡- በሕዝቡ ብሂል ውስጥ ከሥላሴ ጋር ተያይዘው ብዙ ጊዜ የሚጠሩት ገብረ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ‹በአቦ በሥላሴ› ሲባል አጥብቆ መለመን ነው፡፡ በሕዝባዊ መዝሙሮችም ውስጥ ‹በአምስት አቦ ናቸው በሰባት ሥላሴ› የሚል ሐረግ በተደጋጋሚ ይሰማል፡፡
#እረድኤት በረከታቸው ከኛ ከ ኢትዮጵያዊያ እስከ ዘላለሙ ድረስ አይለየን 🙏
#ምንጭ :- ከሙሃዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ጽሁፍ የተቀነጨበ
🔥ገብረ አብ💥:
ሰላም ለእርስዎ ይሁን!🙏
ጥያቄ ነበረኝ።
ከማኅፀን የሚመረጡ ቅዱሳን አሉ?
ከማኅፀን የሚመረጡ ኃጥኣንስ?
ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ሳለ ለጌታ ለምን ዘለለ?...በምንስ አውቆ?
የሰው ነጻ ፈቃድ እና የእግዚአብሔር ወሳኝነት እንዴት ይታያል?
እጣፈንታ የሚባል ነገርስ አለ?
❤በመጀመሪያ ስለ ጥያቄዎ እናመሰግናለን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን
በጽሁፍ አመቺ ስላሎነ ወደ ፊት ይህን መሰሉ ጥያቄ በድምጽ የምመልው ይሆናል ..... ለዛሬ ግን
1 ) ከማኅፀን የሚመረጡ ቅዱሳን አሉ?
አዎን በደንብ አሉ #ለምሳሌ እንደነ ማን ቢሉ
በብሉይ ኪዳን
#መስፍኑ_ሶምሶም
“እነሆ ...ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናል ” መሳፍንት13፥5
#ነቢዮ_ኤርምያስ
“በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ”ት.ኤር 1፥5
*በአዲስ ኪዳን
#መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ
- “በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤” ሉቃስ 1፥15
-ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት ገ/ ተ/ሃይማኖት ወዘተ
2) ከማኅፀን የሚመረጡ ኃጥኣንስ?
ከጅምሩ መመረጥ የሚለው ቃል ለበጎ የሚቀጸል ነው ለክፉሁ ነገር መመረጥ አይባልም መመረጥ የሚባለው ለመልካም ነገር ነው ይህ ዐይነቱ ስህተት አገሌ የተባለው ተጫዋች የእግር መሰበር አደጋ አስተናገደ እንደሚሉ ጋዜጠኖች አይነት ስህተት ነው አስተናገደ ለደጎ ነገር ይናገሩለታል እንጂ ለክፉሁ አይነገርም ተቀብለው የሚያስተናግዱት መልካሙን ጥሩሁን ነር ነውና ። ክፉሁንማ ማን ተቀብሎ ሊያስተናግደው ይፋልጋል??? ማንም ዛሬ ቅልጥሜን ከጥቅም ውጪ ላርገው ብሎ ወደ ሚዳ የሚገባ ተጫዋች የለም ስለዚህ አደጋ ገጠመው ፣ አደጋ ደረሰበት ተብሎ ይነገራል እንጂ አስተናገደ ተብሎ አይነገርም ማስለናገድ የአስተናጋጁን መልካም ፍቃድ የሚጠይቅ ነገር ነው ። በዚህ አንጻር ተመረጠ ወይም ተመረጡ ሲባል ለመልካም ነገር ብቻ ተቀጽሎ ይነገራል እንጂ ለክፉሁ ነገር ተመረጠ፣ ተመረጡ አይባልም ፍጹም ጸያፍ ነው ! ከማኃጸን የተመረጡ ኃጥኃን አሉ ? ለሚለው ጥያቄ የሉም የሚል አጭር መልስ እንሰጣለን ። ዲያቢሎስ ሰልጥኖበት በነበረበት በብሉይ ጊዜ (5500ዘመን ) ላይ ዲያቢሎስ ሊወለዱ የተጸነሱ ጽንሶችን ገና በእናታቸው ማህፀን ሳሉ ይቆራኛቸዋል ሲወለዱም ይጠናወታቸውና ክፉሁ ሥራ ሲያሰራቸው ቆይቶ በኃላ ሲሞቱ ነፍሳቸውን በሲኦል ሥጋቸውንም በመቃብር ይቀራመታቸው ነበር ሌላው ቀርቶ ከማህጸን ጀምሮ የተመረጡ የእግዚአብሔር ሰዎች እንኳ ሲሞቱ ይገቡ የነበሩት ሲኦል ውስጥ ነበር ይህ የሆነበትም ምክንያት በአዳም በደል ምክንያት 5500ዘመን ሙሉ ገነት ተዘግታለ ሲኦል ተከፍታ ሰው ከአምላክ ነፍሥ ከሥጋ ሰማይ ከምድር ተጣልተው የነበረ በመሆኑ ነው። “...ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥ ...።” ኢሳ64፥6
#አሁን ግን ያ የመከራ ጊዜ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መሰዋትነት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተወግዷል ። ከእንግዲህ ከዲያቢሎስ ቁራኝነት ነጻ ወጥተናል ማንም በማኃፀን ሳለ ያለ ወላጆቹ ክፉሁ ፍቃድና ክፉሁ ምርጫ ካልሆነ በቀር በዲያቢሎስ ቁራኚነት ተይዞ አይወለድም “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤” ቆላስይስ 2፥14
#በነጻነት_ልንኖር_ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።” ገላ5፥1
“በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርስዋ ተጠላልፈው የተሸነፉ ቢሆኑ፥ ከፊተኛው ኑሮአቸው ይልቅ የኋለኛው የባሰ ሆኖባቸዋል።” 2ኛ ጴጥሮስ 2፥20
❤ ከእርኩሳት መናፍስት ጋር ከአጋንንት ጋር በመተባበር ፍቃዳቸውን ለዲያቢሎስ ሰጥተው የዲያቢሎስ የግብር ልጅ የሚሆኑ ሰዎች የሚወልዱ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ :: ቢሆንም ግን የተወለዱት ልጆች ነፍስ ካወቁበት ጊዜ ጀምረው ትክክለኛውን መንገድ መከተልና በክርስቶስ ክርስቲያን የመባል መብትም ፍቃድም ሆነ ችሎታ ሙሉ በሙሉ አላቸው ስለዚህ እኔኮ እንዲ ስለሆንኩ ነው ብሎ በቤተሰቡ የተሳሳተ መንገድ መቀጠል የበለጠ ትልቁ ስሕተት ነው አንድ ጊዜ ከተሰራልን የድኀነት ሥራ በየ ጊዜው የሚነሱ ሰዎች ሁሉ የመሳተፍ የመካፈል ዕድል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ለሁሉ የተሰጠ ነው ።“ወዳጆች ሆይ፥ #ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።” ይሁዳ 1፥3
3) ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ሳለ ለጌታ ለምን ዘለለ?...በምንስ አውቆ?
#ዘለለ የሚለውን አገላለጽ በመጀመሪያ በወጉ ማወቅ ይገባል ። በዚህ አገባባዊ ፍቺ መሠረት ዘለለ የሚለው የድርጊት ገላጭ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰገደ ብላ ትተረጉመዋለች ። ትርጓሜ ሁለት ዐይነት ነው የመጀመሪያው ዘይቤያዊ ትርጓሜ ይባላል ይህም ቃሉ በተነገረበት ሀገር ፣ቋንቋ ፣ባህል ፣ልማድና ትውፊት እንዳሁም የንግግር ዘዬ ተከትሎ ለቃሉ ቀጥተኛ ፍቺ መስጠት ማለት ነው ።
🌷 #ለምሳሌ ፦ዘለለ - ሽቅብ ሽቅብ አለ ፣ ፏነነ፣ ቦረቀ ፣ፈነደቀ፣ተደሰተ የሚል ቀጥተኛ ትርጓሜን ይሰጣል ።#ሁለተኛው የትርጓሜ መንገድ ደግሞ ምሥጢራዊ ትርጓሜ የሚባል ሲሆን ከቃሉ ቀጥተኛ ትርጉም ባሻገር የቃሉን ምሥጢራዊ (የተሸሸገ፣የተሰወረ ፣ያልታወቀ፣ግልጥ ያልሆነ) ፍቺ የሚገልጥ ከዘይቤያዊው ትርጉም ጋር አንድ ላይ ሊሆድ የሚችልና ፈጽሞም ከዘይቤያዊ ትርጉም ጋር ሊገናኝ በማይችል መልኩ ሊተረጉም የሚችል የአተረጓጓም ዐይነት ነው።
🌷 #ለምሳሌ ፦ዘለለ- በምሥጢራዊው ትርጉሙ ሰገደ፣ አመሰገነ፣ አከበረ ማለት ነው
❤ለምን መጻሕፍ የዮሐንስን ስግደት ዘለለ ብሎ ገለጠው? ቢሉ
1) መጻሕፍት ምሥጢርን እንጂ ዘይቤን ሰለ ማይጠነቅቁ ነው። ማለትም በምሥጢር ለሚሰጡት መልክትና ትርጉም ይጨነቃሉ እንጂ የቋንቋን የአገላለጽ ዘይቤን በመጠበቅ እረገድ ብዙ አይጨነቁም ለማለት ነው። ይህ የቅዱሳት መጻሕፍት የታወቀ ልማድ ነው።
2) የሕጻናት የደስተኝነት ሁኔታ(ስሜት) ዘለለ ፣ፈነደቀ፣ ቦረቀ፣ በሚሉ የዘይቤ አነጋገር ስለሚገለጹ ሰዎች በሚገባቸው ዐይነት አገላለጽ ለመግለጽ ስለፈለገ ሕጻኑ በደስታ የሰገደውን ስግደት ዘለለ ብሎ ገለጠው ::
3) በማህጸን ያለ ጽንስ ከፍተኛ እንቅስቃሴውን ለመግለጽ ስንፈልግ ጽንሱ ዘለለ እንላለን ። ማህጸን ለጽንሱ መተኛና እግር ለመዘርጊያ ከሚሆን ቦታ የበለጠ ለመዝለያነት የሚሆን ሰፊ ቦታ ኖሮት አይደለም መጠነኛ የሆነ የጽንስ እንቅስቃሴ በራሱ ለእናቲቱ በመዝለል መጠን የሚሰማ ስሜት እንዲሰማት ያደርጋል ። ጌታውንና የጌታውን እናት የተረዳ ዮሐንስእንዴት አብልጦ በደስታ አይዘል ? ኤልሳቤጥም ይህ የልጇ የደስታ ስሜት ተሰማትና "የጌታዬ እናት ወደእኔ ትመጣ ዘንድ ይህ እንዴት ይሆንልኛል የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በደረሰ ጊዜ ጽንሱ በማህጸኔ በደስታ ዘሏል " አለች። ሉቃ 1፥43-44 ስለዚህ ቅዱስ ሉቃስም በእናቲቱ አገላለጽ ጽንሱ በማህጸኟ በደስ ዘለለ ብሎ ሰጊዱን ጻፈልን ሉቃ1÷41
🚩*ለጌታ ለምን ዘለለ ? ( በሌላ አገላለጽ ይህ ጥያቄ ለጌታው ለምን ሰ
ሰላም ለእርስዎ ይሁን!🙏
ጥያቄ ነበረኝ።
ከማኅፀን የሚመረጡ ቅዱሳን አሉ?
ከማኅፀን የሚመረጡ ኃጥኣንስ?
ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ሳለ ለጌታ ለምን ዘለለ?...በምንስ አውቆ?
የሰው ነጻ ፈቃድ እና የእግዚአብሔር ወሳኝነት እንዴት ይታያል?
እጣፈንታ የሚባል ነገርስ አለ?
❤በመጀመሪያ ስለ ጥያቄዎ እናመሰግናለን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን
በጽሁፍ አመቺ ስላሎነ ወደ ፊት ይህን መሰሉ ጥያቄ በድምጽ የምመልው ይሆናል ..... ለዛሬ ግን
1 ) ከማኅፀን የሚመረጡ ቅዱሳን አሉ?
አዎን በደንብ አሉ #ለምሳሌ እንደነ ማን ቢሉ
በብሉይ ኪዳን
#መስፍኑ_ሶምሶም
“እነሆ ...ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ ይሆናል ” መሳፍንት13፥5
#ነቢዮ_ኤርምያስ
“በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ”ት.ኤር 1፥5
*በአዲስ ኪዳን
#መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ
- “በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤” ሉቃስ 1፥15
-ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት ገ/ ተ/ሃይማኖት ወዘተ
2) ከማኅፀን የሚመረጡ ኃጥኣንስ?
ከጅምሩ መመረጥ የሚለው ቃል ለበጎ የሚቀጸል ነው ለክፉሁ ነገር መመረጥ አይባልም መመረጥ የሚባለው ለመልካም ነገር ነው ይህ ዐይነቱ ስህተት አገሌ የተባለው ተጫዋች የእግር መሰበር አደጋ አስተናገደ እንደሚሉ ጋዜጠኖች አይነት ስህተት ነው አስተናገደ ለደጎ ነገር ይናገሩለታል እንጂ ለክፉሁ አይነገርም ተቀብለው የሚያስተናግዱት መልካሙን ጥሩሁን ነር ነውና ። ክፉሁንማ ማን ተቀብሎ ሊያስተናግደው ይፋልጋል??? ማንም ዛሬ ቅልጥሜን ከጥቅም ውጪ ላርገው ብሎ ወደ ሚዳ የሚገባ ተጫዋች የለም ስለዚህ አደጋ ገጠመው ፣ አደጋ ደረሰበት ተብሎ ይነገራል እንጂ አስተናገደ ተብሎ አይነገርም ማስለናገድ የአስተናጋጁን መልካም ፍቃድ የሚጠይቅ ነገር ነው ። በዚህ አንጻር ተመረጠ ወይም ተመረጡ ሲባል ለመልካም ነገር ብቻ ተቀጽሎ ይነገራል እንጂ ለክፉሁ ነገር ተመረጠ፣ ተመረጡ አይባልም ፍጹም ጸያፍ ነው ! ከማኃጸን የተመረጡ ኃጥኃን አሉ ? ለሚለው ጥያቄ የሉም የሚል አጭር መልስ እንሰጣለን ። ዲያቢሎስ ሰልጥኖበት በነበረበት በብሉይ ጊዜ (5500ዘመን ) ላይ ዲያቢሎስ ሊወለዱ የተጸነሱ ጽንሶችን ገና በእናታቸው ማህፀን ሳሉ ይቆራኛቸዋል ሲወለዱም ይጠናወታቸውና ክፉሁ ሥራ ሲያሰራቸው ቆይቶ በኃላ ሲሞቱ ነፍሳቸውን በሲኦል ሥጋቸውንም በመቃብር ይቀራመታቸው ነበር ሌላው ቀርቶ ከማህጸን ጀምሮ የተመረጡ የእግዚአብሔር ሰዎች እንኳ ሲሞቱ ይገቡ የነበሩት ሲኦል ውስጥ ነበር ይህ የሆነበትም ምክንያት በአዳም በደል ምክንያት 5500ዘመን ሙሉ ገነት ተዘግታለ ሲኦል ተከፍታ ሰው ከአምላክ ነፍሥ ከሥጋ ሰማይ ከምድር ተጣልተው የነበረ በመሆኑ ነው። “...ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥ ...።” ኢሳ64፥6
#አሁን ግን ያ የመከራ ጊዜ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መሰዋትነት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተወግዷል ። ከእንግዲህ ከዲያቢሎስ ቁራኝነት ነጻ ወጥተናል ማንም በማኃፀን ሳለ ያለ ወላጆቹ ክፉሁ ፍቃድና ክፉሁ ምርጫ ካልሆነ በቀር በዲያቢሎስ ቁራኚነት ተይዞ አይወለድም “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤” ቆላስይስ 2፥14
#በነጻነት_ልንኖር_ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።” ገላ5፥1
“በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርስዋ ተጠላልፈው የተሸነፉ ቢሆኑ፥ ከፊተኛው ኑሮአቸው ይልቅ የኋለኛው የባሰ ሆኖባቸዋል።” 2ኛ ጴጥሮስ 2፥20
❤ ከእርኩሳት መናፍስት ጋር ከአጋንንት ጋር በመተባበር ፍቃዳቸውን ለዲያቢሎስ ሰጥተው የዲያቢሎስ የግብር ልጅ የሚሆኑ ሰዎች የሚወልዱ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ :: ቢሆንም ግን የተወለዱት ልጆች ነፍስ ካወቁበት ጊዜ ጀምረው ትክክለኛውን መንገድ መከተልና በክርስቶስ ክርስቲያን የመባል መብትም ፍቃድም ሆነ ችሎታ ሙሉ በሙሉ አላቸው ስለዚህ እኔኮ እንዲ ስለሆንኩ ነው ብሎ በቤተሰቡ የተሳሳተ መንገድ መቀጠል የበለጠ ትልቁ ስሕተት ነው አንድ ጊዜ ከተሰራልን የድኀነት ሥራ በየ ጊዜው የሚነሱ ሰዎች ሁሉ የመሳተፍ የመካፈል ዕድል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ለሁሉ የተሰጠ ነው ።“ወዳጆች ሆይ፥ #ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።” ይሁዳ 1፥3
3) ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ሳለ ለጌታ ለምን ዘለለ?...በምንስ አውቆ?
#ዘለለ የሚለውን አገላለጽ በመጀመሪያ በወጉ ማወቅ ይገባል ። በዚህ አገባባዊ ፍቺ መሠረት ዘለለ የሚለው የድርጊት ገላጭ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰገደ ብላ ትተረጉመዋለች ። ትርጓሜ ሁለት ዐይነት ነው የመጀመሪያው ዘይቤያዊ ትርጓሜ ይባላል ይህም ቃሉ በተነገረበት ሀገር ፣ቋንቋ ፣ባህል ፣ልማድና ትውፊት እንዳሁም የንግግር ዘዬ ተከትሎ ለቃሉ ቀጥተኛ ፍቺ መስጠት ማለት ነው ።
🌷 #ለምሳሌ ፦ዘለለ - ሽቅብ ሽቅብ አለ ፣ ፏነነ፣ ቦረቀ ፣ፈነደቀ፣ተደሰተ የሚል ቀጥተኛ ትርጓሜን ይሰጣል ።#ሁለተኛው የትርጓሜ መንገድ ደግሞ ምሥጢራዊ ትርጓሜ የሚባል ሲሆን ከቃሉ ቀጥተኛ ትርጉም ባሻገር የቃሉን ምሥጢራዊ (የተሸሸገ፣የተሰወረ ፣ያልታወቀ፣ግልጥ ያልሆነ) ፍቺ የሚገልጥ ከዘይቤያዊው ትርጉም ጋር አንድ ላይ ሊሆድ የሚችልና ፈጽሞም ከዘይቤያዊ ትርጉም ጋር ሊገናኝ በማይችል መልኩ ሊተረጉም የሚችል የአተረጓጓም ዐይነት ነው።
🌷 #ለምሳሌ ፦ዘለለ- በምሥጢራዊው ትርጉሙ ሰገደ፣ አመሰገነ፣ አከበረ ማለት ነው
❤ለምን መጻሕፍ የዮሐንስን ስግደት ዘለለ ብሎ ገለጠው? ቢሉ
1) መጻሕፍት ምሥጢርን እንጂ ዘይቤን ሰለ ማይጠነቅቁ ነው። ማለትም በምሥጢር ለሚሰጡት መልክትና ትርጉም ይጨነቃሉ እንጂ የቋንቋን የአገላለጽ ዘይቤን በመጠበቅ እረገድ ብዙ አይጨነቁም ለማለት ነው። ይህ የቅዱሳት መጻሕፍት የታወቀ ልማድ ነው።
2) የሕጻናት የደስተኝነት ሁኔታ(ስሜት) ዘለለ ፣ፈነደቀ፣ ቦረቀ፣ በሚሉ የዘይቤ አነጋገር ስለሚገለጹ ሰዎች በሚገባቸው ዐይነት አገላለጽ ለመግለጽ ስለፈለገ ሕጻኑ በደስታ የሰገደውን ስግደት ዘለለ ብሎ ገለጠው ::
3) በማህጸን ያለ ጽንስ ከፍተኛ እንቅስቃሴውን ለመግለጽ ስንፈልግ ጽንሱ ዘለለ እንላለን ። ማህጸን ለጽንሱ መተኛና እግር ለመዘርጊያ ከሚሆን ቦታ የበለጠ ለመዝለያነት የሚሆን ሰፊ ቦታ ኖሮት አይደለም መጠነኛ የሆነ የጽንስ እንቅስቃሴ በራሱ ለእናቲቱ በመዝለል መጠን የሚሰማ ስሜት እንዲሰማት ያደርጋል ። ጌታውንና የጌታውን እናት የተረዳ ዮሐንስእንዴት አብልጦ በደስታ አይዘል ? ኤልሳቤጥም ይህ የልጇ የደስታ ስሜት ተሰማትና "የጌታዬ እናት ወደእኔ ትመጣ ዘንድ ይህ እንዴት ይሆንልኛል የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በደረሰ ጊዜ ጽንሱ በማህጸኔ በደስታ ዘሏል " አለች። ሉቃ 1፥43-44 ስለዚህ ቅዱስ ሉቃስም በእናቲቱ አገላለጽ ጽንሱ በማህጸኟ በደስ ዘለለ ብሎ ሰጊዱን ጻፈልን ሉቃ1÷41
🚩*ለጌታ ለምን ዘለለ ? ( በሌላ አገላለጽ ይህ ጥያቄ ለጌታው ለምን ሰ
ገደ? የሚል ጥያቄ ሆኖ እናገኘዋለን) መልሱ ጥያቄው ውስጥ ያለ ነው ጌታው ስለሆነ ለጌታ ደግሞ ስግደት ስለሚገባ ሰገደለት ። “ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና አለው።” ማቴ4፥10 ዘጸ 20÷4-5 ይህ አይነቱ ስግደት ለእግዚአብሔር ብቻ የሚገባ ስግደት ነው በስያሜ ደረጃም የአምልኮ ወይም የባህሪ ስግደት በመባል ይታወቃል ። ፈጥረህ የምትገዛ አልፋና ኦሜጋ አንተ ብቻ ነህ ስንል አምላክነት የባሕርይ ገንዘቡ ለሆነ ለእግዚአብሔር ብቻ የምንሰግደው የአምልኮ የስግደት ዐይነት ነው ሁለተኛው ደግሞ ለቅዱሳኑ ሁሉ ይበልጡኑ ለእመቤታች የምንሰግደው የስግደት ዐይነት ሲሆን የጸጋ ወይም የአክብሮት ስግደት በመባል ይጠራል :: በኤልሳቤጥ ሆድ ውስጥ የነበረው የ6ወሩ ጽንስ ቅዱስ ዮሐንስም ይህ ጠንቅቆ የገባው በመሆኑ በእናቱ በኤልሳቤጥ ፊት ለፊት ለቆመችው ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የፀጋ (የአክብሮት)በሆዷ ለጸነሰችው የዕለት ጽንስ ደግሞ እንደ ፈጣሪነቱ የባሕርይ (የአምልኮ)ስግደት አስተባብሮ ሰግዷል ::
🚩*በምንስ አውቆ ? ለሚለው በኤልሳቤጥ የመላባት መንፈስ ቅዱስ ለሆዷ ጽንስ ተርፎላት የ6ወሩ ጽንስ ጌታውና እመቤቱን በሚገባ አውቀ የሚገባውንም ስግደት ሰገደላቸው “በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥” #ሉቃስ 1፥41
የቅዱስ ጴጥሮስ እና የቅዱስ ጳውሎስ የአካል ቅድስናቸው ለልብሶቻቸውና ለጥላቸው ተርፎ ተአምራትን እንዳደረጉ ሁሉ የእናቱ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ለልጆ ተረፈና አዋቂ አደረገው “ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና።” #ሉቃስ 1፥37 “የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
4) የሰው ነጻ ፈቃድ እና የእግዚአብሔር ወሳኝነት እንዴት ይታያል?
ሰው ነጻ ፍቃድ አለው እግዚአብሔር ደግሞ የባህሪ አዋቂነት አለው:: እግዚአብሔር አዋቂ ነው እንጂ ለሰዎች በሰጣቸው ነጻ ፍቃድ ላይ ወሳኝ አይደለም ወሳኙ ሰው ነው ከወሰነማ የሰጠው ነጻ ፍቃድ ነጻ ፍቃድ አይሰኝም ስለዚህ የጥያቄውን መንፈስ ማስተካከል ይገባል ሰው ነጻ ፍቃድ አለው እግዚአብሔር ደግሞ የባሕሪው የሆነ ፍጽም ዕውቀት አለው :: የእግዚአብሔር አዋቂነት በሰው ነጻ ፍቃድ ላይ ተጽኖ ያደርጋል ወይ? ካሉ ግን መልሱ በፍጹም አያደርግም የሚል ይሆናል ። #ለምሳሌ ብዙ ጊዜ ከዚህ ርዕስ ጋር ተያይዞ የሚነሳውን የአስቆሮቱ ይሁዳን ብናነሳ ለይሁዳ እንደዛ መሆን የተነገረበት ትንቢት አስገድዶት እንደሆነ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ ትክክል ግን አይደለም ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ፍቅር በተናገረበት አንቀጹ ፍቅር ከሁሉ እንደሚበልጥ ሲጠቅስ ትንቢት እራሱ ቢሆን ይሻራል የማይሻረው ፍቅር ነው ብሎ የፍቅርን ኃያልነት ሲናገር እናነባለን 1ቆሮ 13 ÷ 2(8) ምን ማለት ነው ትንቢትም ቢሆን እንኳ ስለ ፍቅር ፈንታ ይሻራል ማለቱ ነው ስለዚህ የትንቢት አስገዳጅነት የሚባል ነገር የለም ማለት ነው ይሁዳ ከገንዘብ ፍቅር ይልቅ የክርስቶስ ፍቅር አቃጥሎት ቢሆን ኖሮ ትንቢቱ እራሱ ሊሻርለት ይችል ነበር ነገር ግን ከንዘብ ወዳድ ነበርና ከሚጠፉሁ ገንብ ጋር አብሮ ጠፉ የትንቢቱም መፈጸሚያ ሆነ ። ስለዚህ በአጭሩ የእግዚአብሔር የወደፊቱን የማወቅ ባሕሪው አስገዳጅነት አለው አይባልም::
5 ) እጣፈንታ የሚባል ነገርስ አለ?
አዎን አለ ነገር ግን የዕጣ ፈንታው የምርጫ ካርድ ያለው ሰው ጋር ነው #ለምሳሌ “ልብህ በእግዚአብሔር ፊት የቀና አይደለምና ከዚህ ነገር ዕድል ወይም ፈንታ የለህም።” ሐዋ8፥21 ይህ ንግግር ወይም ገጸ ንባብ የሚያስረዳን ዕድል ፈንታና ጽዋ ተርታ የሚባል ነገር እንዳለ ነው የክርስቶስን ፍጽም አምላክነት የመቤታችንን አማላጅነት የቅዱሳኑን ተራዳይነትና ክብር ለሚያምንና ለሚቀበል ሁሉ ጽዋ ተርታው ዕድል ፈንታው ከክርስቶ ጋር ይሆናል ማለት ነው ለዛ ነው የተጠመቅን መሥጋወደሙ የከበርን በቅዱሳኑ ምልጃና ቃል ኪዳን የምንተማመን ሁሉ በክርስቶስ ክርስቲያኖች የተሰኘነው:: ክርስቲያኖች አካል ናቸው ክርስቶስ ደግሞ እራሳቸው ነው::
ዮሐንስ 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።
ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው።
ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው።
ጴጥሮስም፦ የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም፦ካላጠብሁህ፥ከእኔ ጋር #ዕድል_ፈንታ_ጽዋ_ተርታ የለህም ብሎ መለሰለት።
ስምዖን ጴጥሮስም፦ ደንግጡ ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም፦ የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥
የመታጠብና ያለ መታጠብ ምርጫ የቅዱስ ጴጥሮስ ነበር በመታጠቡ ሊያገኘው የሚችለውን ነገር መስጠት እና ባለመታጠቡ ሊያጣው የሚችለው መንፈግ የፈጣሪ ድርሻ ነበር :: ዛሬም በጥምቀት የሚገኝ ጸጋ የማግኘት የምርጫ ካርድ በእጃችን ነው ዕጣ ፈንታችንን በክርስቶስ ወይም ከሌላ ወገም የማድረግ መብቱ የኛ ነው እንደ ምርጫችን መስጠት የርሱ ነው ስለዚህ ዕጣ ፍንታ ለሁሉ የተሰጠና የተፈቀደ ሲሆን የፈለጉ ብቻ የሚመርጡት የዕራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው ማለት ነው።
#ነገር_ግን_ሁላችሁ_አይደላችሁም አለው። (ይህ ማለቱ ይሁዳን የመሰሉ ከአድያንን ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ የተሰጣቸውን በጥምቀት የተገኘ ልጅነታቸውም በገንዘብ የሚያረክሱ እንዳሉ ሲያመለክት ነው ይህም እግዘብሔርን ፍጽም አዋቂ ነው ያልነውን ያጠነክርልናል ይህ ንግግሩ ለይሁዳ በአሉታዊ መንገድ ተጽኖ አላደረገችም ይልቁኑ ከክፋት ሀሳቡ ተመልሶ በቀና ወደ ማገልገል ልትመልሰው የምትችል የማንቂያ ንግግር ነበረች ይሁዳ ግን አላስተዋለም በገንዘብ ፍቅር ዐይነ ልቡናው ታውሯልና የጌታችን ይህ ዐይነት ምክርና ማንቂያ በዚህ ብቻ የቆመ አልነበረም ምክንያቱም ይሁዳ የትንቢት መፈጸሚያ እንዲሁን ከቶ አይፈቅድም ነበርና በእራት ተቀምጠውም ሳሉ “የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር " በማለትም የሀሳብ ክእደቱን ወደ ተግባር እንዳያሳድገው እያስተማረው እያስጠነቀቀውም ጭምር ነበር በገንዘብ ፍቅር ተነድፏልና ግና ሊመለስ አልቻለም ሰይጣን ለወዳጁ ድርብ ነው እንዲሉ ይባስ በልቡ ሰይጣን አደረበት። ማር14፥21
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን የሚሆነውን የድርሻውን ሁሉ ተወጥቷል ከአጥያት መንጫ ጥምቀትን መስርቶ ሥጋውንም ቆርሶ ደሙንም አፍስሶ ሰጥቶናል ከዚህ መዳን ቀርቦ በክርስቶስ ክርስቲያን የመሆንን ዕጣ ፈንታ ጽዋ ተርታን የማግኛ የምርጫ ካርዱ ግን በእጃችን ነው እርሷም ነጻ ፍቃዳችን ናት::
“ማርያምስ ማንም ሊቀማት የማይችለውን መልካሙን ዕድል መረጠች” ሉቃስ 10፥42
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 08/2013ዓ,ም
አ.አ ኢትዮጵያ
@YEAWEDIMERITE
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
🚩*በምንስ አውቆ ? ለሚለው በኤልሳቤጥ የመላባት መንፈስ ቅዱስ ለሆዷ ጽንስ ተርፎላት የ6ወሩ ጽንስ ጌታውና እመቤቱን በሚገባ አውቀ የሚገባውንም ስግደት ሰገደላቸው “በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥” #ሉቃስ 1፥41
የቅዱስ ጴጥሮስ እና የቅዱስ ጳውሎስ የአካል ቅድስናቸው ለልብሶቻቸውና ለጥላቸው ተርፎ ተአምራትን እንዳደረጉ ሁሉ የእናቱ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ለልጆ ተረፈና አዋቂ አደረገው “ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና።” #ሉቃስ 1፥37 “የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
4) የሰው ነጻ ፈቃድ እና የእግዚአብሔር ወሳኝነት እንዴት ይታያል?
ሰው ነጻ ፍቃድ አለው እግዚአብሔር ደግሞ የባህሪ አዋቂነት አለው:: እግዚአብሔር አዋቂ ነው እንጂ ለሰዎች በሰጣቸው ነጻ ፍቃድ ላይ ወሳኝ አይደለም ወሳኙ ሰው ነው ከወሰነማ የሰጠው ነጻ ፍቃድ ነጻ ፍቃድ አይሰኝም ስለዚህ የጥያቄውን መንፈስ ማስተካከል ይገባል ሰው ነጻ ፍቃድ አለው እግዚአብሔር ደግሞ የባሕሪው የሆነ ፍጽም ዕውቀት አለው :: የእግዚአብሔር አዋቂነት በሰው ነጻ ፍቃድ ላይ ተጽኖ ያደርጋል ወይ? ካሉ ግን መልሱ በፍጹም አያደርግም የሚል ይሆናል ። #ለምሳሌ ብዙ ጊዜ ከዚህ ርዕስ ጋር ተያይዞ የሚነሳውን የአስቆሮቱ ይሁዳን ብናነሳ ለይሁዳ እንደዛ መሆን የተነገረበት ትንቢት አስገድዶት እንደሆነ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ ትክክል ግን አይደለም ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ፍቅር በተናገረበት አንቀጹ ፍቅር ከሁሉ እንደሚበልጥ ሲጠቅስ ትንቢት እራሱ ቢሆን ይሻራል የማይሻረው ፍቅር ነው ብሎ የፍቅርን ኃያልነት ሲናገር እናነባለን 1ቆሮ 13 ÷ 2(8) ምን ማለት ነው ትንቢትም ቢሆን እንኳ ስለ ፍቅር ፈንታ ይሻራል ማለቱ ነው ስለዚህ የትንቢት አስገዳጅነት የሚባል ነገር የለም ማለት ነው ይሁዳ ከገንዘብ ፍቅር ይልቅ የክርስቶስ ፍቅር አቃጥሎት ቢሆን ኖሮ ትንቢቱ እራሱ ሊሻርለት ይችል ነበር ነገር ግን ከንዘብ ወዳድ ነበርና ከሚጠፉሁ ገንብ ጋር አብሮ ጠፉ የትንቢቱም መፈጸሚያ ሆነ ። ስለዚህ በአጭሩ የእግዚአብሔር የወደፊቱን የማወቅ ባሕሪው አስገዳጅነት አለው አይባልም::
5 ) እጣፈንታ የሚባል ነገርስ አለ?
አዎን አለ ነገር ግን የዕጣ ፈንታው የምርጫ ካርድ ያለው ሰው ጋር ነው #ለምሳሌ “ልብህ በእግዚአብሔር ፊት የቀና አይደለምና ከዚህ ነገር ዕድል ወይም ፈንታ የለህም።” ሐዋ8፥21 ይህ ንግግር ወይም ገጸ ንባብ የሚያስረዳን ዕድል ፈንታና ጽዋ ተርታ የሚባል ነገር እንዳለ ነው የክርስቶስን ፍጽም አምላክነት የመቤታችንን አማላጅነት የቅዱሳኑን ተራዳይነትና ክብር ለሚያምንና ለሚቀበል ሁሉ ጽዋ ተርታው ዕድል ፈንታው ከክርስቶ ጋር ይሆናል ማለት ነው ለዛ ነው የተጠመቅን መሥጋወደሙ የከበርን በቅዱሳኑ ምልጃና ቃል ኪዳን የምንተማመን ሁሉ በክርስቶስ ክርስቲያኖች የተሰኘነው:: ክርስቲያኖች አካል ናቸው ክርስቶስ ደግሞ እራሳቸው ነው::
ዮሐንስ 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።
ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው።
ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው።
ጴጥሮስም፦ የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም፦ካላጠብሁህ፥ከእኔ ጋር #ዕድል_ፈንታ_ጽዋ_ተርታ የለህም ብሎ መለሰለት።
ስምዖን ጴጥሮስም፦ ደንግጡ ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም፦ የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥
የመታጠብና ያለ መታጠብ ምርጫ የቅዱስ ጴጥሮስ ነበር በመታጠቡ ሊያገኘው የሚችለውን ነገር መስጠት እና ባለመታጠቡ ሊያጣው የሚችለው መንፈግ የፈጣሪ ድርሻ ነበር :: ዛሬም በጥምቀት የሚገኝ ጸጋ የማግኘት የምርጫ ካርድ በእጃችን ነው ዕጣ ፈንታችንን በክርስቶስ ወይም ከሌላ ወገም የማድረግ መብቱ የኛ ነው እንደ ምርጫችን መስጠት የርሱ ነው ስለዚህ ዕጣ ፍንታ ለሁሉ የተሰጠና የተፈቀደ ሲሆን የፈለጉ ብቻ የሚመርጡት የዕራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው ማለት ነው።
#ነገር_ግን_ሁላችሁ_አይደላችሁም አለው። (ይህ ማለቱ ይሁዳን የመሰሉ ከአድያንን ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ የተሰጣቸውን በጥምቀት የተገኘ ልጅነታቸውም በገንዘብ የሚያረክሱ እንዳሉ ሲያመለክት ነው ይህም እግዘብሔርን ፍጽም አዋቂ ነው ያልነውን ያጠነክርልናል ይህ ንግግሩ ለይሁዳ በአሉታዊ መንገድ ተጽኖ አላደረገችም ይልቁኑ ከክፋት ሀሳቡ ተመልሶ በቀና ወደ ማገልገል ልትመልሰው የምትችል የማንቂያ ንግግር ነበረች ይሁዳ ግን አላስተዋለም በገንዘብ ፍቅር ዐይነ ልቡናው ታውሯልና የጌታችን ይህ ዐይነት ምክርና ማንቂያ በዚህ ብቻ የቆመ አልነበረም ምክንያቱም ይሁዳ የትንቢት መፈጸሚያ እንዲሁን ከቶ አይፈቅድም ነበርና በእራት ተቀምጠውም ሳሉ “የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር " በማለትም የሀሳብ ክእደቱን ወደ ተግባር እንዳያሳድገው እያስተማረው እያስጠነቀቀውም ጭምር ነበር በገንዘብ ፍቅር ተነድፏልና ግና ሊመለስ አልቻለም ሰይጣን ለወዳጁ ድርብ ነው እንዲሉ ይባስ በልቡ ሰይጣን አደረበት። ማር14፥21
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዳን የሚሆነውን የድርሻውን ሁሉ ተወጥቷል ከአጥያት መንጫ ጥምቀትን መስርቶ ሥጋውንም ቆርሶ ደሙንም አፍስሶ ሰጥቶናል ከዚህ መዳን ቀርቦ በክርስቶስ ክርስቲያን የመሆንን ዕጣ ፈንታ ጽዋ ተርታን የማግኛ የምርጫ ካርዱ ግን በእጃችን ነው እርሷም ነጻ ፍቃዳችን ናት::
“ማርያምስ ማንም ሊቀማት የማይችለውን መልካሙን ዕድል መረጠች” ሉቃስ 10፥42
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 08/2013ዓ,ም
አ.አ ኢትዮጵያ
@YEAWEDIMERITE
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit