Audio
👉መንፈሳዊ ውይይት
ርዕስ:- #ቅዱሳን_ሐዋርያትና_ጾማቸው
#በወንድማችን ብሩክ መልሳቸው እና
#በወንድማችን ተርቢኖስ ሰብስቤ የተዘጋጀ
መዝሙር :-በዘማሪት #ሰብለ ስፍር
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ርዕስ:- #ቅዱሳን_ሐዋርያትና_ጾማቸው
#በወንድማችን ብሩክ መልሳቸው እና
#በወንድማችን ተርቢኖስ ሰብስቤ የተዘጋጀ
መዝሙር :-በዘማሪት #ሰብለ ስፍር
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#መላእከ ውቃቢ
.......ካለፈው የለጠቀ.........
ሰኔ 12የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ምክንያት በማድረግ በዚሁ ርዕስ ሥር መላከ ውቃቢ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እና ነገደ መላእክትን ከነ አለቆቻቸው መዳሰስ ጀምረን ነበር ዛሬም ቀጣዮንና የመጨረሻውን ክፍል ሰኔ 19 የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ምክንያት አድርገን ይዘንላችሁ ቀርበናል። ዛሬ
.........................
#ውቃቢ የሚለው ገላጭ ግሥ ለምን በብዛት ከጥንቁልና ጋር ተያይዞ ይነሳል? መላእክትስ እራሳቸው ስለዚህ (ስለ ጥንቁልና) ምን ይላሉ? የሚለውን እንቃኛለን አብራቹን ቆዮ ::
..........................
ውቃቢ የሚለው ቃል አቃቢ ጠባቂ የሚል ትርጉም ያለው በመሆኑ ሰዎች ያድነናል ከክፉሁ ነገር ይጠብቀናል ብለው ስለሚያምኑ የሚያመልኩትን አካል ውቃቢዬ (ጠባቂዬ )ብለው ሲጠሩ ይስተዋላል ጠንቆይ ከሰዎች በግ ፍየል በሬ ገንዘብ ወዘተ ነገሮች የሚጠብቅ(የሚሻ)እንጂ ሰዎችን የሚጠብቅ አይደለም ስለዚህ ውቃቢ የሚለው ስም አይገባውም ከዛይልቅ አውዳሚ የሚለው ስመ ስያሜ ይስማማዋል ::ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠንቋይ የሚለውስ መጠሪያ ስትተረጉመው እራሱ ጠንቋይ ማለት #ጠ_ን_ቀ_ነ_ዋ_ይ (የገንዘብ ጠንቅ ) ማለት ነው ብላ አርቃ ትተረጉማለት:: እውነት ነው የተባረከ ሥራ እንድሰጥህ ውድ ሽቶ አምጣ የተባረከ ትዳር እንድሰጥህ መካደሚያ የሚሆን ቪላ ቤት ሰርተህ ስጠኝ የተባረከ ልጅ እንድሰጥህ ሰንጋ በሬ ጣልልኝ የሚሉ ጠንቀ ነዋዮች (ጠንቋዮች) ብዙ ናቸው:: ለሰዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ጠባቂ አቃቢ መላክ አላቸው አንዱ በቀን ሌላኛው በሌሊት የቀኑ ከጠዋቱ 12ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ይጠብቅና ለሌላኛው መላክ ይሰጠዋል ያም መላክ ይህ ሰው ደገኛ ነውን ይለዋል ደገኛ ከሆነ አዎን እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ጆሮው ከቃለ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም አይተለየኝ ይለዋል ተረኛው መላክም ደስ እያለው ከምሽቱ 12ሰዓት እስከ ንጋቱ 12ሰዓት ይጠብቀዋል ሰውየው ደገኛ ካልሆነ ግን ማለትም እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም ከራቀ ግን ተረካቢው መላክ ያዝናል ምነው አምላኬ ይህን ከምታስጠብቀኝ እንሰሳ ብታስጠብቀኝ ይሻላል ይላል ይጠየፈዋል ::ጠንቋዮች ጠንቀኞች ናቸው :: በማሳያ ጠቀስን እንጂ ጠንቀኝነታቸውም በገንዘብ ብቻ የሚቆም አይደለም የእግሬን እጣቢ ጠጣ የሚሉ ጠንቀ ጤና ፣ ያገባአት ሴት ዕጣ ክፍልህ አይደለችም የሚሉ ጠንቀ ፍቅር ፣ ግደል ግደል የሚሉጨጠንቀ ሠላም ፣ አሁን ምን ቀረህ እራስህን አጥፋ አጥፋ የሚያሰኙ ጠንቀ ተስፋ ፣ አምጣ አምጣ የሚሉ በዝባዦች ጠንቀ ብልጥግና፣ የሚያጠራጥሩ ከእምነት ጎዳና የሚያወጡ ጠንቀ እምነትቶች ጭምር ናቸው:: እግዚአብሔር ግን እነዚህ መሠል ሰዎች ጋር እንዳንገኝ አስጠንቅቆናል “አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ።” ዘዳግም 18፥11 ባንተ ዘንድ አይገኝ ማለት አንተ እራስህ ጠንቁል ጠንቁል የሚል ሰሜት አይሰማህ እንደዚህም የሚያደርጉ ቤተሰቦች ወንድሞች ወይም እህቶች ጓደኞች የሥራ ባልደረቦች አይኑሩህ ማለቱ ጭምር ነው ጠንቋዮች እግዚአብሔር እና የእግዚአብሔር ሰዎችን የሚገዳደሩ ደፋሮችም ናቸው:: ለምሳሌ ላይ የእግዚአብሔር ነቢይ የሆነ ነቢዮ ሙሴን የተገዳደሩትን ሁለቱን ጠንቋዮች መመልከት እንችላለን መገዳደራቸው ግን በተአምራት ሳይሆን በምትዐት በቅድስና ብቃት ሳይሆን በእርኩሰት ብቃት በማድረግ ሳይሆን ያደረጉ በማስመሰል በቅዱሱ በእግዚአብሔር መንፈስ ሳይሆን በእርኩሱ በሰይጣን መንፈስ በመሰራት ነው :: “ሙሴና አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ እግዚአብሔርም እንዳዘዛቸው እንዲሁ አደረጉ፤ አሮንም በትሩን በፈርዖንና በባሮቹ ፊት ጣለ፥ እባብም ሆነች።” ዘጸአት 7፥10 ፈርዖንም ጠቢባንንና መተተኞችን ጠራ፤ የግብፅም ጠንቋዮች በአስማታቸው እንዲሁ ደግሞ አደረጉ እያንዳንዳቸውም በትራቸውን ጣሉ፥ እባቦችም ሆኑ፤ የአሮን በትር ግን በትራቸውን ዋጠች።” ዘጸአት 7፥12 እነዚህ ሙሴና አሮንን የተገዳደሩ ሁለቱ ጠንቋዮች ምንም እንኳን በምተአት በትሮቻቸውን ወደ እባብነት ቢለውጡም ከጠንቋዮች ምትዐት ይልቅ የእግዚአብሔር ሰዎች ተአምራት እንደሚበልጥ ሲያስገነዝበን የጠንቋዮቹ እባቦች በነ ሙሴ እባቦች ተመዋጡ ብሎናል:: ዛሬም ይመላቸው እንጂ የኃላ የኃላ ሥር ማሽ፣ ቅጠል በጣሽ ፣ ሙት ሳቢ፣ ጋኔን ጠሪ፣ ሞራ ገላጭ ውቃቢ አምላኪ ሙአርተኛ እና መተተኛ በገሃነም እሳት መዋጣቸው አይቀርም :: “የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።”1ኛ ቆሮንቶስ 3፥19-20 በመጽሐፍ ዲቢሎስ እባብ ተብሎ ተጠርቷል“የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥” ራእይ 20፥2 ታዲያ የእባቡን የዲያቢሎስን ጥበብ (መርዝ) በጥበቡ ለመሻር ሲል መድኃኒተ ዓለም ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ተገለጠ ለመርዘኛው መድኃኒት መርዙ ነውና ዲያቢሎስ በመድኃኒት የሞተ የተሸነፈ የመጀመሪያ ፍጡር ሆነ “ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ዮሐንስ 3፥9 :: ጥንቆላ ጠንቀኝነት ነውና በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተጠየፈ ነው ኢት አምልክ (ሌሎች አማልክትን አታምልክ የሚል ትዕዛዝም አስቀድሞ መስጠቱ ለዚሁ ነው:: ዘጸ20፥1- ፍቅረ ጣዖት ያደረባቸው እሥራኤል ዘሥጋም ሙሴ በሥጋ በተለያቸው ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ከእሥራኤል ፊት ቅዱሱን የሙሴን ሥጋ ሰውሮባቸው ነበር ::ለምን ያልን እንደሆነ ሙሴን አብዝተው ይወዱት ስለነበረ ሥጋውን ሳይቀብሩ እናምልከው ይሉ ነበርና ነው:: ሰው ለሚወደው ነገር ባሪያ ነው :: ክፋት የክፋት ልጅ ዲያቢሎስ ታዲያ የተሠወረውን የውሴን ሥጋ ካለበት አድርሶ ለእስራኤል ገልጦላቸው ሊያሰመልካቸው ወደደ በዚህ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ ከሰይጣን ጋር ተከራከረ:: ዛሬ ብዙዎች በቅዱሳን አማላጅነትና ተራዳይነት መማጠናችንን እያነሱ ይኮኑኑናል ቅድስ ኦርቶዶክስ ግን ሙሴን ሳይሆን የሙሴ አምላክ ክርስቶስን ታመልካለች ለሙሴ የጸጋ ለክርስቶስ የባህሪ የአምልኮ ስግደት ታቀርባለች ሙሴን አማላጅ ክርስቶስን ደግሞ ፈራጅ ብላ ታከብራቸዋለች:: ሰይጣን ዲያቢሎስ ግን እስራኤል የሙሴን ሥጋ አግኝተው እንዲያመልኩት እንዲጠነቁሉበት ለማድረግ ካልገለጥኩ ሲል ተጋ ቅዱስ ሚካኤል ግን ገሰጸው ሲገስጸውም አልተሳደበም፣ አልተራገመምም :: “የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።” ይሁዳ 1፥9 ዛሬም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በፍርሃትም ይሁን በድፍረት የሚጠነቁሉና የሚያስጠነቁሉ ሰዎችን መሳደብ ሳይሆን መገሰጽ ማንቋሸሽ ሳይሆን ማስተማር እና ከዚህ ሕይወት በቸርነቱ ነጻ ያወጣቸው ዘንድ መለመን እንደሚገባን አስተምሮናል::
..........ይቆየን..........ተፈጸመ...... ዝንቱ ጡሁማር::
ከአቃቢያነ መላክ ከቅዱስ ሚካኤል ወገብርኤል እረድኤትን ይክፈለይ::
አዘጋጅ:- #ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
@YEAWEDIMERITE
ሰኔ 19/2012ዓ.ም
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
.......ካለፈው የለጠቀ.........
ሰኔ 12የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ምክንያት በማድረግ በዚሁ ርዕስ ሥር መላከ ውቃቢ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እና ነገደ መላእክትን ከነ አለቆቻቸው መዳሰስ ጀምረን ነበር ዛሬም ቀጣዮንና የመጨረሻውን ክፍል ሰኔ 19 የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ምክንያት አድርገን ይዘንላችሁ ቀርበናል። ዛሬ
.........................
#ውቃቢ የሚለው ገላጭ ግሥ ለምን በብዛት ከጥንቁልና ጋር ተያይዞ ይነሳል? መላእክትስ እራሳቸው ስለዚህ (ስለ ጥንቁልና) ምን ይላሉ? የሚለውን እንቃኛለን አብራቹን ቆዮ ::
..........................
ውቃቢ የሚለው ቃል አቃቢ ጠባቂ የሚል ትርጉም ያለው በመሆኑ ሰዎች ያድነናል ከክፉሁ ነገር ይጠብቀናል ብለው ስለሚያምኑ የሚያመልኩትን አካል ውቃቢዬ (ጠባቂዬ )ብለው ሲጠሩ ይስተዋላል ጠንቆይ ከሰዎች በግ ፍየል በሬ ገንዘብ ወዘተ ነገሮች የሚጠብቅ(የሚሻ)እንጂ ሰዎችን የሚጠብቅ አይደለም ስለዚህ ውቃቢ የሚለው ስም አይገባውም ከዛይልቅ አውዳሚ የሚለው ስመ ስያሜ ይስማማዋል ::ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠንቋይ የሚለውስ መጠሪያ ስትተረጉመው እራሱ ጠንቋይ ማለት #ጠ_ን_ቀ_ነ_ዋ_ይ (የገንዘብ ጠንቅ ) ማለት ነው ብላ አርቃ ትተረጉማለት:: እውነት ነው የተባረከ ሥራ እንድሰጥህ ውድ ሽቶ አምጣ የተባረከ ትዳር እንድሰጥህ መካደሚያ የሚሆን ቪላ ቤት ሰርተህ ስጠኝ የተባረከ ልጅ እንድሰጥህ ሰንጋ በሬ ጣልልኝ የሚሉ ጠንቀ ነዋዮች (ጠንቋዮች) ብዙ ናቸው:: ለሰዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ጠባቂ አቃቢ መላክ አላቸው አንዱ በቀን ሌላኛው በሌሊት የቀኑ ከጠዋቱ 12ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ይጠብቅና ለሌላኛው መላክ ይሰጠዋል ያም መላክ ይህ ሰው ደገኛ ነውን ይለዋል ደገኛ ከሆነ አዎን እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ጆሮው ከቃለ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም አይተለየኝ ይለዋል ተረኛው መላክም ደስ እያለው ከምሽቱ 12ሰዓት እስከ ንጋቱ 12ሰዓት ይጠብቀዋል ሰውየው ደገኛ ካልሆነ ግን ማለትም እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም ከራቀ ግን ተረካቢው መላክ ያዝናል ምነው አምላኬ ይህን ከምታስጠብቀኝ እንሰሳ ብታስጠብቀኝ ይሻላል ይላል ይጠየፈዋል ::ጠንቋዮች ጠንቀኞች ናቸው :: በማሳያ ጠቀስን እንጂ ጠንቀኝነታቸውም በገንዘብ ብቻ የሚቆም አይደለም የእግሬን እጣቢ ጠጣ የሚሉ ጠንቀ ጤና ፣ ያገባአት ሴት ዕጣ ክፍልህ አይደለችም የሚሉ ጠንቀ ፍቅር ፣ ግደል ግደል የሚሉጨጠንቀ ሠላም ፣ አሁን ምን ቀረህ እራስህን አጥፋ አጥፋ የሚያሰኙ ጠንቀ ተስፋ ፣ አምጣ አምጣ የሚሉ በዝባዦች ጠንቀ ብልጥግና፣ የሚያጠራጥሩ ከእምነት ጎዳና የሚያወጡ ጠንቀ እምነትቶች ጭምር ናቸው:: እግዚአብሔር ግን እነዚህ መሠል ሰዎች ጋር እንዳንገኝ አስጠንቅቆናል “አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ።” ዘዳግም 18፥11 ባንተ ዘንድ አይገኝ ማለት አንተ እራስህ ጠንቁል ጠንቁል የሚል ሰሜት አይሰማህ እንደዚህም የሚያደርጉ ቤተሰቦች ወንድሞች ወይም እህቶች ጓደኞች የሥራ ባልደረቦች አይኑሩህ ማለቱ ጭምር ነው ጠንቋዮች እግዚአብሔር እና የእግዚአብሔር ሰዎችን የሚገዳደሩ ደፋሮችም ናቸው:: ለምሳሌ ላይ የእግዚአብሔር ነቢይ የሆነ ነቢዮ ሙሴን የተገዳደሩትን ሁለቱን ጠንቋዮች መመልከት እንችላለን መገዳደራቸው ግን በተአምራት ሳይሆን በምትዐት በቅድስና ብቃት ሳይሆን በእርኩሰት ብቃት በማድረግ ሳይሆን ያደረጉ በማስመሰል በቅዱሱ በእግዚአብሔር መንፈስ ሳይሆን በእርኩሱ በሰይጣን መንፈስ በመሰራት ነው :: “ሙሴና አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ እግዚአብሔርም እንዳዘዛቸው እንዲሁ አደረጉ፤ አሮንም በትሩን በፈርዖንና በባሮቹ ፊት ጣለ፥ እባብም ሆነች።” ዘጸአት 7፥10 ፈርዖንም ጠቢባንንና መተተኞችን ጠራ፤ የግብፅም ጠንቋዮች በአስማታቸው እንዲሁ ደግሞ አደረጉ እያንዳንዳቸውም በትራቸውን ጣሉ፥ እባቦችም ሆኑ፤ የአሮን በትር ግን በትራቸውን ዋጠች።” ዘጸአት 7፥12 እነዚህ ሙሴና አሮንን የተገዳደሩ ሁለቱ ጠንቋዮች ምንም እንኳን በምተአት በትሮቻቸውን ወደ እባብነት ቢለውጡም ከጠንቋዮች ምትዐት ይልቅ የእግዚአብሔር ሰዎች ተአምራት እንደሚበልጥ ሲያስገነዝበን የጠንቋዮቹ እባቦች በነ ሙሴ እባቦች ተመዋጡ ብሎናል:: ዛሬም ይመላቸው እንጂ የኃላ የኃላ ሥር ማሽ፣ ቅጠል በጣሽ ፣ ሙት ሳቢ፣ ጋኔን ጠሪ፣ ሞራ ገላጭ ውቃቢ አምላኪ ሙአርተኛ እና መተተኛ በገሃነም እሳት መዋጣቸው አይቀርም :: “የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።”1ኛ ቆሮንቶስ 3፥19-20 በመጽሐፍ ዲቢሎስ እባብ ተብሎ ተጠርቷል“የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥” ራእይ 20፥2 ታዲያ የእባቡን የዲያቢሎስን ጥበብ (መርዝ) በጥበቡ ለመሻር ሲል መድኃኒተ ዓለም ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ተገለጠ ለመርዘኛው መድኃኒት መርዙ ነውና ዲያቢሎስ በመድኃኒት የሞተ የተሸነፈ የመጀመሪያ ፍጡር ሆነ “ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ዮሐንስ 3፥9 :: ጥንቆላ ጠንቀኝነት ነውና በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተጠየፈ ነው ኢት አምልክ (ሌሎች አማልክትን አታምልክ የሚል ትዕዛዝም አስቀድሞ መስጠቱ ለዚሁ ነው:: ዘጸ20፥1- ፍቅረ ጣዖት ያደረባቸው እሥራኤል ዘሥጋም ሙሴ በሥጋ በተለያቸው ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ከእሥራኤል ፊት ቅዱሱን የሙሴን ሥጋ ሰውሮባቸው ነበር ::ለምን ያልን እንደሆነ ሙሴን አብዝተው ይወዱት ስለነበረ ሥጋውን ሳይቀብሩ እናምልከው ይሉ ነበርና ነው:: ሰው ለሚወደው ነገር ባሪያ ነው :: ክፋት የክፋት ልጅ ዲያቢሎስ ታዲያ የተሠወረውን የውሴን ሥጋ ካለበት አድርሶ ለእስራኤል ገልጦላቸው ሊያሰመልካቸው ወደደ በዚህ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ ከሰይጣን ጋር ተከራከረ:: ዛሬ ብዙዎች በቅዱሳን አማላጅነትና ተራዳይነት መማጠናችንን እያነሱ ይኮኑኑናል ቅድስ ኦርቶዶክስ ግን ሙሴን ሳይሆን የሙሴ አምላክ ክርስቶስን ታመልካለች ለሙሴ የጸጋ ለክርስቶስ የባህሪ የአምልኮ ስግደት ታቀርባለች ሙሴን አማላጅ ክርስቶስን ደግሞ ፈራጅ ብላ ታከብራቸዋለች:: ሰይጣን ዲያቢሎስ ግን እስራኤል የሙሴን ሥጋ አግኝተው እንዲያመልኩት እንዲጠነቁሉበት ለማድረግ ካልገለጥኩ ሲል ተጋ ቅዱስ ሚካኤል ግን ገሰጸው ሲገስጸውም አልተሳደበም፣ አልተራገመምም :: “የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።” ይሁዳ 1፥9 ዛሬም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በፍርሃትም ይሁን በድፍረት የሚጠነቁሉና የሚያስጠነቁሉ ሰዎችን መሳደብ ሳይሆን መገሰጽ ማንቋሸሽ ሳይሆን ማስተማር እና ከዚህ ሕይወት በቸርነቱ ነጻ ያወጣቸው ዘንድ መለመን እንደሚገባን አስተምሮናል::
..........ይቆየን..........ተፈጸመ...... ዝንቱ ጡሁማር::
ከአቃቢያነ መላክ ከቅዱስ ሚካኤል ወገብርኤል እረድኤትን ይክፈለይ::
አዘጋጅ:- #ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
@YEAWEDIMERITE
ሰኔ 19/2012ዓ.ም
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
" የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም። ሲል ማፍራት ብቻ ሳይሆን ምን ዓይነት ፍሬም ማፍራት እንደሚገባ ዘርዝሮ ነግሮናል ገላ5÷22 አስቀድሞ በኢሳይያስ ነቢይ ላይም አድሮ " እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላላችሁ እንቢ ብትሉ ብታምጹ ግን ሰይፍ ይበላችዋል " ብሎ እሺ ብለን ታዘን የምድርን በረከት እንድንበላ አስቦናል ኢሳ 1÷19 ወላዲ መጥቅ ዮሐንስም በምስክርነቱ “መንሹም በእጁ ነው፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፥ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፥ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል።” ማቴዎስ 3፥12 ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ዋግ እንዳልመታው ውርጭም እንዳላገኘው ንጽሕ ስንዴን ያቀረበ የአቤልን መሰዋይት ያሳረገች እኛንም ንጽሕ ስንዴ አድርጋ ጎተራ በተባለች መንግስተ ሰማያት እንድንገባ የማክሰኞ እርሻ የእመቤታችን በረከት ይደርብን:: አሜን🙏.....ይቆየን......
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ሐምሌ 21 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ሐምሌ 21 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤” 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥6
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ሐምሌ 18 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ሐምሌ 18 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይበልጡኑ ደግሞ ለክርስቲያኖች እንኳን ደስ ያለኘን !
"ስለ ሰማዮ ንፋስ ስለ ወንዞችም ሙላት እንማልዳለን"
እነሆ ከአሁኟ ሰዓት ጀምሮ ያሎትን ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ
#እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ! አሜን🙏
የመልዕክት ሳጥን
@YEAWEDIMERITE
በኩል ይስደዱልን!
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
"ስለ ሰማዮ ንፋስ ስለ ወንዞችም ሙላት እንማልዳለን"
እነሆ ከአሁኟ ሰዓት ጀምሮ ያሎትን ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ
#እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ! አሜን🙏
የመልዕክት ሳጥን
@YEAWEDIMERITE
በኩል ይስደዱልን!
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ሱባዔ
ሱባዔ በሰዋሰው ትርጉሙ ቆየ ሰነበተ ዘገየ ሰባት ማለት ሲሆን ምሥጢራዊ ትርጓሜውም ደግሞ አንድ ሰው ከዚህ ቀን እከዚህ ቀን ድረስ ፈጣሪዬን በጸሎት እገናኛለሁብሎ የሚያቅደው ዕቅድ ነው። ሰባት ቁጥር በእስራኤላዊያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር አረፈ እንዲል በጸሎት የሚተጉ ምዕመናንም በቀን ሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል ። ሱባዔ የተጀመረው ከመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት በኋላ ነው ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዴት እንደሚጸለይ እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ። ለአዳምም የጸሎት ጊዜያትን አስተምረውት አስተምረውት ነበርና ጥፈቱን አምኖ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔርም በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት ።
ሱባዔ ለምንምክንያት እንገባልን ቢሉ የመጀመሪያው የሚሆነው የሰው ልጅ በባህሪው ኃጢአት የሚስማማው ነው በሥጋ ሰውነቱ ፈጣሪን ይበድላል በፈጸመው በደል / ኃጢአት/ ሕሊናው ይወቅሰዋል በዚህም ያዝናል ይጸጸታል በሰራው ኃጢአትም ልቡ ይደነግጣል በዚህ ጊዜ የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት ሲል ሲል ሱባዔ ይገባል ።እግዚአብሔርን ለመማፀን የሚገባ ሱባዔ አለ ። ማንኛውም ሰው ሱባዔ በገባ ቁጥር ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማጽኖ ሊኖረው ይገባል ምንም የምንለምነውና የምንጠይቀው ነገር ሳይኖር ሰባዔውን ብንገባ የምናገኘው ምንም አይነት መልስ አይኖርም
ስለዚህ ተማፅኖ ሊኖረን ይገባል ። ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔው በኋላ ምን እንደተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖራቸው ሱባዔ በመግባታቸው የሚገኙት ነገር አይኖርም ይህን ተገንዝበው ከመግባታቸው በፊት የሚገቡበትን ምክንያት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው ። ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶቻችን ደማቸውን ካፈሰሱበት አጥንታቸውን ከከሰከሱበት ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራት የሰሩበት ቦታ ገዳማቸውና አድባራት ላይ የሚገባ ሱባዔ ከቅዱሳኑ ረድኤት ተካፋይ ይደርጋል ። ሱባዔ የተደበቀን ምሥጢር የሚገለጥበት ቁልፍ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው ቅዱሳን አባቶቻችን ያዩት እራይ ምሥጢሩና ትርጉሙ አልገለጥ ሲላቸው ሱባዔ ይገቡ ነበር እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነ ነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢሩንና ትርጉሙን ይገልጥላቸዋል ። ነቢዬ ዕዝራ የመጽሐፍታት ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ገባ እግዚአብሔር አምላክም ሁሉን ገለጸለት የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍታት ደግሞ ለመጻፍ ችሏል ይህ ምሥጢር የተገለጠለት በሱባዔ ነው ።
ከብሉይ ጀምሮ ያሉ የሱባዔ አባቶቻችን የገቡት ሱባዔ ሱባዔ አዳም ፣ ሱባዔ ሔኖክ ሱባዔ ነብያት
፣ሱባዔ ዳንኤል ሱባዔ ዳዊት በተጨማሪም የግል ሱባዔ የማኀበር ሱባዔ የአዋጅ ሱባዔ በመባል ይታወቃሉ በሐዲስ ኪዳን ከአራት ቀን በኋላ የምገባ ሐዋርያት የገቡት ሱባዔ ነው የፍልሰታ ሱባዔ በዚህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ የተገኘበት ትንሣኤዋ እንዲገለጥላቸው የተገባ ሱባዔ ነው ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን 14 ቀን ያክል በጻም በጸሎት ተማጽነው ትንሣኤዋን ገለጠችላቸው ። እንግዲህ ሱባዔ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ወቅቱ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ስባዔ እንደ መሆኑ መጠን እኛም የሐዋርያቱን ፈለግ በመከተል በንጹሕ ልቦና በትሁት መንፈስ ሆነን የእናታችን ትንሣኤ ይገለጥልን ዘንድ በሱባዔው እንትጋ ። ለሐዋርያቱ በሙሉ የልባቸውን መሻት የፈጸመች የጌታችን እናት ድንግል ማርያም የእኛንም የልባችንን ትፈጽምልናለች። ወቅቱን የጾም፣የጸሎት፣የስግደት፣ የምጽዋት፣ ስለ ሀገራችን ኢትዮጲያ የምናለቅስበት ነው ። ስለዚህ ሁላችን በሱባዔው እንበርታ
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥42
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
.....ይቆየን.......
ምንጭ :-እናት ማህበሬ ምክሐ ደናግል ሰሌዴ መጽሔት ሐምሌ ና ነሀሴ2010ዓ.ም የተለጠፈ
ሱባዔ በሰዋሰው ትርጉሙ ቆየ ሰነበተ ዘገየ ሰባት ማለት ሲሆን ምሥጢራዊ ትርጓሜውም ደግሞ አንድ ሰው ከዚህ ቀን እከዚህ ቀን ድረስ ፈጣሪዬን በጸሎት እገናኛለሁብሎ የሚያቅደው ዕቅድ ነው። ሰባት ቁጥር በእስራኤላዊያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር አረፈ እንዲል በጸሎት የሚተጉ ምዕመናንም በቀን ሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል ። ሱባዔ የተጀመረው ከመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት በኋላ ነው ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዴት እንደሚጸለይ እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ። ለአዳምም የጸሎት ጊዜያትን አስተምረውት አስተምረውት ነበርና ጥፈቱን አምኖ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔርም በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት ።
ሱባዔ ለምንምክንያት እንገባልን ቢሉ የመጀመሪያው የሚሆነው የሰው ልጅ በባህሪው ኃጢአት የሚስማማው ነው በሥጋ ሰውነቱ ፈጣሪን ይበድላል በፈጸመው በደል / ኃጢአት/ ሕሊናው ይወቅሰዋል በዚህም ያዝናል ይጸጸታል በሰራው ኃጢአትም ልቡ ይደነግጣል በዚህ ጊዜ የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት ሲል ሲል ሱባዔ ይገባል ።እግዚአብሔርን ለመማፀን የሚገባ ሱባዔ አለ ። ማንኛውም ሰው ሱባዔ በገባ ቁጥር ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማጽኖ ሊኖረው ይገባል ምንም የምንለምነውና የምንጠይቀው ነገር ሳይኖር ሰባዔውን ብንገባ የምናገኘው ምንም አይነት መልስ አይኖርም
ስለዚህ ተማፅኖ ሊኖረን ይገባል ። ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔው በኋላ ምን እንደተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖራቸው ሱባዔ በመግባታቸው የሚገኙት ነገር አይኖርም ይህን ተገንዝበው ከመግባታቸው በፊት የሚገቡበትን ምክንያት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው ። ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶቻችን ደማቸውን ካፈሰሱበት አጥንታቸውን ከከሰከሱበት ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራት የሰሩበት ቦታ ገዳማቸውና አድባራት ላይ የሚገባ ሱባዔ ከቅዱሳኑ ረድኤት ተካፋይ ይደርጋል ። ሱባዔ የተደበቀን ምሥጢር የሚገለጥበት ቁልፍ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው ቅዱሳን አባቶቻችን ያዩት እራይ ምሥጢሩና ትርጉሙ አልገለጥ ሲላቸው ሱባዔ ይገቡ ነበር እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነ ነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢሩንና ትርጉሙን ይገልጥላቸዋል ። ነቢዬ ዕዝራ የመጽሐፍታት ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ገባ እግዚአብሔር አምላክም ሁሉን ገለጸለት የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍታት ደግሞ ለመጻፍ ችሏል ይህ ምሥጢር የተገለጠለት በሱባዔ ነው ።
ከብሉይ ጀምሮ ያሉ የሱባዔ አባቶቻችን የገቡት ሱባዔ ሱባዔ አዳም ፣ ሱባዔ ሔኖክ ሱባዔ ነብያት
፣ሱባዔ ዳንኤል ሱባዔ ዳዊት በተጨማሪም የግል ሱባዔ የማኀበር ሱባዔ የአዋጅ ሱባዔ በመባል ይታወቃሉ በሐዲስ ኪዳን ከአራት ቀን በኋላ የምገባ ሐዋርያት የገቡት ሱባዔ ነው የፍልሰታ ሱባዔ በዚህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ የተገኘበት ትንሣኤዋ እንዲገለጥላቸው የተገባ ሱባዔ ነው ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን 14 ቀን ያክል በጻም በጸሎት ተማጽነው ትንሣኤዋን ገለጠችላቸው ። እንግዲህ ሱባዔ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ወቅቱ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ስባዔ እንደ መሆኑ መጠን እኛም የሐዋርያቱን ፈለግ በመከተል በንጹሕ ልቦና በትሁት መንፈስ ሆነን የእናታችን ትንሣኤ ይገለጥልን ዘንድ በሱባዔው እንትጋ ። ለሐዋርያቱ በሙሉ የልባቸውን መሻት የፈጸመች የጌታችን እናት ድንግል ማርያም የእኛንም የልባችንን ትፈጽምልናለች። ወቅቱን የጾም፣የጸሎት፣የስግደት፣ የምጽዋት፣ ስለ ሀገራችን ኢትዮጲያ የምናለቅስበት ነው ። ስለዚህ ሁላችን በሱባዔው እንበርታ
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥42
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
.....ይቆየን.......
ምንጭ :-እናት ማህበሬ ምክሐ ደናግል ሰሌዴ መጽሔት ሐምሌ ና ነሀሴ2010ዓ.ም የተለጠፈ
" #ቀርታ_ያስቀረችን_ምርጥ_ዘር "
ጊዜው ክረምት ወቅቱም የዘር የመከር ወቅት በመሆኑ ዘርና ፍሬ ዝናብና ጠል ገበሬና በሬ ያለ መነጣጠል ይነሱበታል ። የክረምት ወቅት ምሳሌያዊ ትርጉም ዘርፈ ብዙ ነው ። አንዱ ና ዋናው ግን የ5500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ዘመን ፣ የመከራ ፣ የስቃይ ፣ የጨለማ ጊዜ ምሳሌ መሆኑ ነው :: ይኸውም ክረምት የ5ሺህ 500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው መባሉ በክረምት ጭጋግ ፣ ጉም ፣ደመና ይበረታሉ ነጎድጓዳት ይሰማሉ መባርቅት በርቀው ያስደነግጣሉ ይልቁኑ ደግሞ ውኃ ይሰለጥናል :: የክረምት ወቅት ሰቆቃ ይበዛዋል ይልቁኑ በስደት በደጅ ላሉ ሰውች ይብስባቸዋል “ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤”
የሚለው የጌታችን ምክርም የዚህን የክረምት ወቅት ጠንካራነት ያሳያል። ማቴ24፥20
የ5500ዘመንም ዘመነ ፍዳ ዘመነ መከራ ዘመነ ጨለማ ነውና በእግረ አጋንንት ተገዝተን በሲዖል እሳት ውስጥ ተግዘን ኖረናል ። በክረምት ውኃ እንዲሰለጥን በብሉይ ኪዳንም ውኃ ሰልጥኖ ፍጥረትን አጥፍቷል ገኃነመ እሳት በርትቷል በክረምት ምድር በውኃ እረክታ ትረሰርሳለች መሬት ትጨቀያለች በብሉይም ሰዎች በኃጢያት ዝናብ በስብሰው በሰዶም ግብር ጨቅይተው ነበር በዚህ ሰበብም ፈጣሪና ፍጡር ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ ተጣልተው ከርመዋል በመሆኑም ዘመነ ብሉይ (5500 ዘመን) ከአሰቃቂው የክረምት ወቅት ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል ። በመካከላቸውም የጠብ ግድግዳ ተገንብቶ ቆይቷል ቤተ ክርስቲያን በዚህ ወቅት ዘሪ ሊዘራ ወጣ እያለች የመንገድ ዳር፣ የጭንጫ ፣የሾህ ልቡና ያላቸውን ምዕመኖቿን ልብ በስብከተ መልካም መሬት አድርጋ በወንጌሏ ታቀናዋለች ቃል ዘርታ ሕይወት ታጭዳለች ።
ዛሬ ዛሬ ዓለማችን ነጭ ጥቁር ሀገራችን ደግሞ ኦሮሞ ትግሬ አማራ ጉራጌ በመባባል ተከፋፈለዋል። ሁሉም ዘሩ ምርጥ ዘር እንደሆነ ያስባል ሌላው ዘር ሁሉ እንክርዳድ የሚመስለው ነቀዝ ብዙ ነው ። ከሰዶምና ከጎሞራ ቅጣት የተረፍንባት ምርጥ ዘራችን ድንግል ማርያም ነች። ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችም መጀመራያ ብሎ እንደጠራት ትምክተ ዘመድነ የምትባል እመቤታችን ነች ። ከእርሷ በቀር ምርጥ ዘር የሚባል የለንም ።
ይህች ንጽሕት ዘር ወርቅ ነች ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከወደቁት ከአዳም እና ከሔዋን ዘሮች የተገች ዳግማዊት ሔዋን ብትሆንም የበደል ጥንት አልነካታም የመተላለፍ እድፍ አላጎደፋትም ስለዚህ በአዳም ገላ ውስጥ ታበራ የነበረች ነጭ እንቁ ነች።
ነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ “የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ዘርን_ባያስቀርልን_ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።” ብሎ የተናገረላት ከኃጢያት መተዳደፍ በመንጻት ከከፋት ሥራ ሁሉ ቀርታ ከጥፈት ያስቀረችን ምርጥ ዘራችን እመቤታችን ነች። ኢሳ 1፥9 ይህችሁም ንጽሕይት ዘር በወርኃ ክረምቱ ማዕከላዊ ጊዜ በሆነው በነሐሴ 7 (ሰባት)በዛሬዋ ቀን ከሐናና ከኢያቄም ተጸንሳልናለች ይህ ቀን የእመቤታችን ብቻ ሳይሆን እያገዳደለን ካለው የዘረኝነት ግዳይ ዓለማችንንና የሀገራችንን ትንሳኤ የምታደርግበት የድኅነታችን ጽንስ መጀመሪያም ቀን ነው።
በክረምት ወቅት የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ይሰጣሉ ታዲያ ይህ ጊዜ ለትጉህ ገበሬ ምቹ ነው በሬውን ይጠምዳል መሬቱን ያርሳል ዘሩን ይዘራል ዝናቡን በጉድጓድ ያጠራቅማል መባርቅቱን ፣ ነፋሳቱን ይታገሳል። በመጨረሻውም የድካሙን ፍሬ አዝመራውን ያጭዳል በመከራ እንዳልዘራ በደስታ ይሰበስባል " በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ ። በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ ። መዝ (125) 126 ÷5 ሰነፍ ገበሬ በአንጻሩ ብርዱን ቸነፈሩን ተሰቆ ቤቱ ይተኛል እገሌ ከኔ ወገን ነው ደግ ነው እገሊት ከወንዝ ማዶ ናት አትመስለንም ባለፈችበት እንዳታልፉ በዞረችበት አትዙሩ የሚል ነው የአጥንት እንጂ የእህል ዘር የማያውቅ :: ዘረኝነት ኃጢያት ነው ኃጢያት ደግሞ ማጣት ማለት ነው ባለ ብዙ ዘሮች ነን የሚሉ ዘረኞች ሃይማኖቱን፣ ምግባሩን ፣ ፖለቲካውን ፣ ሥልጣኑን ፣ ዕውቀቱን፣ ውበቱን ፣ ሙቀቱን ፣ድምቀቱን፣ ዝናውን ፣ተሰሚነቱን የያዙ ይመስላቸው ይሆናል ነገር ግን አንዱም እንኳ የላቸውም አጥተውታል። ሰው ኃጢያትን (ዘረኝነት) ዘርቶ እንዴት አንድነትን ሊያጭድ ይችላል ??? በእኩልነት ሰበብ በኩይ ከከፋፈሉን በኃላ በእንድነት ደግሞ እንምራቹ አሉን በአንድ ገመድ ሁሉንም ከብቶች አስሬ ልምራቸው የሚል እረኛ የለም ቢኖር ግን ይህ ምንደኛ እንጂ እረኛ አይደለም ምክንያቱም ከብቶቹን በአንድ ታስረው ወደ ሚፈልጉት የልማት ጉዳና የሥልጣኔ ማማ መድረስ አይቻላቸውምና። አንዱ ወድቆ ሊላውን የሚጠልፍበት የውድቀት ትርምስ ነው የሚሆንባቸው ። ከዛም አልፎ ከለመለመው መስክ ሳይሰማሩ በረፍትም ውኃ ዘንድ ሳይቀርቡ ከናፈቁት በረታቸውም ሳይገቡ የነጣቂ ተኩላ ሲሳይ የጅብ እራት ሆነው ይቀራሉ ። “ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ ”ምሳሌ 22፥8 " ማሰር መፍትኤ የሚሆነው ጠባቂ ከሌለ ብቻ ነው! " ። እረኛ ካለ ገመድ ለምኔ ?
........ ይቆየን.............
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 7 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጊዜው ክረምት ወቅቱም የዘር የመከር ወቅት በመሆኑ ዘርና ፍሬ ዝናብና ጠል ገበሬና በሬ ያለ መነጣጠል ይነሱበታል ። የክረምት ወቅት ምሳሌያዊ ትርጉም ዘርፈ ብዙ ነው ። አንዱ ና ዋናው ግን የ5500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ዘመን ፣ የመከራ ፣ የስቃይ ፣ የጨለማ ጊዜ ምሳሌ መሆኑ ነው :: ይኸውም ክረምት የ5ሺህ 500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው መባሉ በክረምት ጭጋግ ፣ ጉም ፣ደመና ይበረታሉ ነጎድጓዳት ይሰማሉ መባርቅት በርቀው ያስደነግጣሉ ይልቁኑ ደግሞ ውኃ ይሰለጥናል :: የክረምት ወቅት ሰቆቃ ይበዛዋል ይልቁኑ በስደት በደጅ ላሉ ሰውች ይብስባቸዋል “ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤”
የሚለው የጌታችን ምክርም የዚህን የክረምት ወቅት ጠንካራነት ያሳያል። ማቴ24፥20
የ5500ዘመንም ዘመነ ፍዳ ዘመነ መከራ ዘመነ ጨለማ ነውና በእግረ አጋንንት ተገዝተን በሲዖል እሳት ውስጥ ተግዘን ኖረናል ። በክረምት ውኃ እንዲሰለጥን በብሉይ ኪዳንም ውኃ ሰልጥኖ ፍጥረትን አጥፍቷል ገኃነመ እሳት በርትቷል በክረምት ምድር በውኃ እረክታ ትረሰርሳለች መሬት ትጨቀያለች በብሉይም ሰዎች በኃጢያት ዝናብ በስብሰው በሰዶም ግብር ጨቅይተው ነበር በዚህ ሰበብም ፈጣሪና ፍጡር ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ ተጣልተው ከርመዋል በመሆኑም ዘመነ ብሉይ (5500 ዘመን) ከአሰቃቂው የክረምት ወቅት ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል ። በመካከላቸውም የጠብ ግድግዳ ተገንብቶ ቆይቷል ቤተ ክርስቲያን በዚህ ወቅት ዘሪ ሊዘራ ወጣ እያለች የመንገድ ዳር፣ የጭንጫ ፣የሾህ ልቡና ያላቸውን ምዕመኖቿን ልብ በስብከተ መልካም መሬት አድርጋ በወንጌሏ ታቀናዋለች ቃል ዘርታ ሕይወት ታጭዳለች ።
ዛሬ ዛሬ ዓለማችን ነጭ ጥቁር ሀገራችን ደግሞ ኦሮሞ ትግሬ አማራ ጉራጌ በመባባል ተከፋፈለዋል። ሁሉም ዘሩ ምርጥ ዘር እንደሆነ ያስባል ሌላው ዘር ሁሉ እንክርዳድ የሚመስለው ነቀዝ ብዙ ነው ። ከሰዶምና ከጎሞራ ቅጣት የተረፍንባት ምርጥ ዘራችን ድንግል ማርያም ነች። ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችም መጀመራያ ብሎ እንደጠራት ትምክተ ዘመድነ የምትባል እመቤታችን ነች ። ከእርሷ በቀር ምርጥ ዘር የሚባል የለንም ።
ይህች ንጽሕት ዘር ወርቅ ነች ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከወደቁት ከአዳም እና ከሔዋን ዘሮች የተገች ዳግማዊት ሔዋን ብትሆንም የበደል ጥንት አልነካታም የመተላለፍ እድፍ አላጎደፋትም ስለዚህ በአዳም ገላ ውስጥ ታበራ የነበረች ነጭ እንቁ ነች።
ነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ “የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ዘርን_ባያስቀርልን_ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።” ብሎ የተናገረላት ከኃጢያት መተዳደፍ በመንጻት ከከፋት ሥራ ሁሉ ቀርታ ከጥፈት ያስቀረችን ምርጥ ዘራችን እመቤታችን ነች። ኢሳ 1፥9 ይህችሁም ንጽሕይት ዘር በወርኃ ክረምቱ ማዕከላዊ ጊዜ በሆነው በነሐሴ 7 (ሰባት)በዛሬዋ ቀን ከሐናና ከኢያቄም ተጸንሳልናለች ይህ ቀን የእመቤታችን ብቻ ሳይሆን እያገዳደለን ካለው የዘረኝነት ግዳይ ዓለማችንንና የሀገራችንን ትንሳኤ የምታደርግበት የድኅነታችን ጽንስ መጀመሪያም ቀን ነው።
በክረምት ወቅት የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ይሰጣሉ ታዲያ ይህ ጊዜ ለትጉህ ገበሬ ምቹ ነው በሬውን ይጠምዳል መሬቱን ያርሳል ዘሩን ይዘራል ዝናቡን በጉድጓድ ያጠራቅማል መባርቅቱን ፣ ነፋሳቱን ይታገሳል። በመጨረሻውም የድካሙን ፍሬ አዝመራውን ያጭዳል በመከራ እንዳልዘራ በደስታ ይሰበስባል " በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ ። በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ ። መዝ (125) 126 ÷5 ሰነፍ ገበሬ በአንጻሩ ብርዱን ቸነፈሩን ተሰቆ ቤቱ ይተኛል እገሌ ከኔ ወገን ነው ደግ ነው እገሊት ከወንዝ ማዶ ናት አትመስለንም ባለፈችበት እንዳታልፉ በዞረችበት አትዙሩ የሚል ነው የአጥንት እንጂ የእህል ዘር የማያውቅ :: ዘረኝነት ኃጢያት ነው ኃጢያት ደግሞ ማጣት ማለት ነው ባለ ብዙ ዘሮች ነን የሚሉ ዘረኞች ሃይማኖቱን፣ ምግባሩን ፣ ፖለቲካውን ፣ ሥልጣኑን ፣ ዕውቀቱን፣ ውበቱን ፣ ሙቀቱን ፣ድምቀቱን፣ ዝናውን ፣ተሰሚነቱን የያዙ ይመስላቸው ይሆናል ነገር ግን አንዱም እንኳ የላቸውም አጥተውታል። ሰው ኃጢያትን (ዘረኝነት) ዘርቶ እንዴት አንድነትን ሊያጭድ ይችላል ??? በእኩልነት ሰበብ በኩይ ከከፋፈሉን በኃላ በእንድነት ደግሞ እንምራቹ አሉን በአንድ ገመድ ሁሉንም ከብቶች አስሬ ልምራቸው የሚል እረኛ የለም ቢኖር ግን ይህ ምንደኛ እንጂ እረኛ አይደለም ምክንያቱም ከብቶቹን በአንድ ታስረው ወደ ሚፈልጉት የልማት ጉዳና የሥልጣኔ ማማ መድረስ አይቻላቸውምና። አንዱ ወድቆ ሊላውን የሚጠልፍበት የውድቀት ትርምስ ነው የሚሆንባቸው ። ከዛም አልፎ ከለመለመው መስክ ሳይሰማሩ በረፍትም ውኃ ዘንድ ሳይቀርቡ ከናፈቁት በረታቸውም ሳይገቡ የነጣቂ ተኩላ ሲሳይ የጅብ እራት ሆነው ይቀራሉ ። “ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ ”ምሳሌ 22፥8 " ማሰር መፍትኤ የሚሆነው ጠባቂ ከሌለ ብቻ ነው! " ። እረኛ ካለ ገመድ ለምኔ ?
........ ይቆየን.............
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 7 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ለዳዊት ሦስት ልጆች ነበሩት አቤሴሎም፣አምኖን እና ትዕማር ። የዳዊትም ልጅ አምኖን ትዕማርን ወደዳት። አምኖንም ከእኅቱ ከትዕማር የተነሣ እጅግ ስለ ተከዘ ታመመ፤ ድንግልም ነበረችና አንዳች ያደርጋት ዘንድ በዓይኑ ፊት ጭንቅ ሆኖበት ነበር ።ለአምኖንም የዳዊት ወንድም የሳምዓ ልጅ ኢዮናዳብ የሚባል ወዳጅ ነበረው፤ ኢዮናዳብም እጅግ ብልህ ሰው ነበረ።እርሱም፦ የንጉሥ ልጅ ሆይ፥ ስለ ምን ቀን በቀን እንዲህ ከሳህ? አትነግረኝምን? አለው። አምኖንም፦ የወንድሜን የአቤሴሎምን እኅት ትዕማርን እወድዳታለሁ አለው።
ኢዮናዳብም፦ ታምሜአለሁ ብለህ በአልጋህ ላይ ተኛ፤ አባትህም ሊያይህ በመጣ ጊዜ፦ እኅቴ ትዕማር እንድትመጣና እኔ የምበላውን እንጀራ እንድትሰጠኝ፥ መብሉንም እኔ እያየሁ እንድታዘጋጅልኝ፥ ከእጅዋም እንድበላው እለምንሃለሁ በል አለው። እንዲሁም አምኖን፦ ታምሜአለሁ ብሎ ተኛ፤ ንጉሡም ሊያየው በመጣ ጊዜ አምኖን ንጉሡን፦ እኅቴ ትዕማር እንድትመጣና እኔ እያየሁ ሁለት እንጎቻ እንድታደርግልኝ፥ ከእጅዋም እንድበላ እለምንሃለሁ አለው። ዳዊትም፦ መብልን ታዘጋጂለት ዘንድ ወደ ወንድምሽ ወደ አምኖን ቤት ሂጂ ብሎ መልእክተኞችን ወደ ትዕማር ቤት ላከ።
ትዕማርም ወደ ወንድምዋ ወደ አምኖን ቤት ሄደች፥ ተኝቶም ነበር፤ ዱቄትም ወስዳ ለወሰች፥ እያየም እንጎቻ አደረገች፥ ጋገረችም። ምጣዱንም ወስዳ በፊቱ ገለበጠች እርሱ ግን ይበላ ዘንድ እንቢ አለ። አምኖንም፦ ሰውን ሁሉ ከእኔ ዘንድ አስወጡ አለ፤ ሰውም ሁሉ ከእርሱ ዘንድ ወጣ። አምኖንም ትዕማርን፦ ከእጅሽ እበላ ዘንድ መብሉን ወደ እልፍኙ አግቢው አላት፤ ትዕማርም የሠራችውን እንጎቻ ወስዳ ወንድምዋ አምኖን ወዳለበት እልፍኝ አገባችው። መብሉንም ባቀረበች ጊዜ ያዛትና፦ እኅቴ ሆይ፥ ነዪ ከእኔም ጋር ተኚ አላት። እርስዋ መልሳ፦ ወንድሜ ሆይ፥ አይሆንም፤ እንዲህ ያለ ነገር በእስራኤል ዘንድ አይገባምና አታሳፍረኝ፤ ይህንም ነውረኛ ሥራ አታድርግ።እኔም ነውሬን ወዴት ልሸከም? አንተም በእስራኤል ዘንድ ከምናምንቴዎች እንደ አንዱ ትሆናለህ፤ እንግዲህስ ለንጉሡ ንገረው፥ እኔንም አይነሣህም አለችው። ቃልዋን ግን አልሰማም፤ ከእርስዋም ይልቅ ብርቱ ነበረና በግድ አስነወራት፥ ከእርስዋም ጋር ተኛ ። ከዚያም በኋላ አምኖን ፈጽሞ ጠላት፤ አስቀድሞም ከወደዳት ውድ ይልቅ በኋላ የጠላት ጥል በለጠ። አምኖንም፦ ተነሥተሽ ሂጂ አላት።
እርስዋም፦ አይሆንም ቀድሞ ከሠራኸው ክፋት ይልቅ አኔን በማውጣትህ የበለጠ ክፋት ትሠራለህ አለችው እርሱ ግን አልሰማትም። የሚያገለግለውንም ብላቴና ጠርቶ፦ ይህችን ሴት ከፊቴ አስወጥተህ በሩን ዝጋባት አለው። ብዙ ኅብር ያለውንም ልብስ ለብሳ ነበር፥ እንዲህ ያለውን ልብስ የንጉሡ ልጆች ደናግሉ ይለብሱ ነበርና፤ አገልጋዩም አስወጥቶ በሩን ዘጋባት። ትዕማርም በራስዋ ላይ አመድ ነስንሳ፥ ብዙ ኅብርም ያለውን ልብስዋን ተርትራ፥ እጅዋንም በራስዋ ላይ ጭና እየጮኸች ሄደች።
#ትዕማርን_ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀
👇👇👇👇👇👇👇👇
ሀሳቦን ያጋሯት
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ኢዮናዳብም፦ ታምሜአለሁ ብለህ በአልጋህ ላይ ተኛ፤ አባትህም ሊያይህ በመጣ ጊዜ፦ እኅቴ ትዕማር እንድትመጣና እኔ የምበላውን እንጀራ እንድትሰጠኝ፥ መብሉንም እኔ እያየሁ እንድታዘጋጅልኝ፥ ከእጅዋም እንድበላው እለምንሃለሁ በል አለው። እንዲሁም አምኖን፦ ታምሜአለሁ ብሎ ተኛ፤ ንጉሡም ሊያየው በመጣ ጊዜ አምኖን ንጉሡን፦ እኅቴ ትዕማር እንድትመጣና እኔ እያየሁ ሁለት እንጎቻ እንድታደርግልኝ፥ ከእጅዋም እንድበላ እለምንሃለሁ አለው። ዳዊትም፦ መብልን ታዘጋጂለት ዘንድ ወደ ወንድምሽ ወደ አምኖን ቤት ሂጂ ብሎ መልእክተኞችን ወደ ትዕማር ቤት ላከ።
ትዕማርም ወደ ወንድምዋ ወደ አምኖን ቤት ሄደች፥ ተኝቶም ነበር፤ ዱቄትም ወስዳ ለወሰች፥ እያየም እንጎቻ አደረገች፥ ጋገረችም። ምጣዱንም ወስዳ በፊቱ ገለበጠች እርሱ ግን ይበላ ዘንድ እንቢ አለ። አምኖንም፦ ሰውን ሁሉ ከእኔ ዘንድ አስወጡ አለ፤ ሰውም ሁሉ ከእርሱ ዘንድ ወጣ። አምኖንም ትዕማርን፦ ከእጅሽ እበላ ዘንድ መብሉን ወደ እልፍኙ አግቢው አላት፤ ትዕማርም የሠራችውን እንጎቻ ወስዳ ወንድምዋ አምኖን ወዳለበት እልፍኝ አገባችው። መብሉንም ባቀረበች ጊዜ ያዛትና፦ እኅቴ ሆይ፥ ነዪ ከእኔም ጋር ተኚ አላት። እርስዋ መልሳ፦ ወንድሜ ሆይ፥ አይሆንም፤ እንዲህ ያለ ነገር በእስራኤል ዘንድ አይገባምና አታሳፍረኝ፤ ይህንም ነውረኛ ሥራ አታድርግ።እኔም ነውሬን ወዴት ልሸከም? አንተም በእስራኤል ዘንድ ከምናምንቴዎች እንደ አንዱ ትሆናለህ፤ እንግዲህስ ለንጉሡ ንገረው፥ እኔንም አይነሣህም አለችው። ቃልዋን ግን አልሰማም፤ ከእርስዋም ይልቅ ብርቱ ነበረና በግድ አስነወራት፥ ከእርስዋም ጋር ተኛ ። ከዚያም በኋላ አምኖን ፈጽሞ ጠላት፤ አስቀድሞም ከወደዳት ውድ ይልቅ በኋላ የጠላት ጥል በለጠ። አምኖንም፦ ተነሥተሽ ሂጂ አላት።
እርስዋም፦ አይሆንም ቀድሞ ከሠራኸው ክፋት ይልቅ አኔን በማውጣትህ የበለጠ ክፋት ትሠራለህ አለችው እርሱ ግን አልሰማትም። የሚያገለግለውንም ብላቴና ጠርቶ፦ ይህችን ሴት ከፊቴ አስወጥተህ በሩን ዝጋባት አለው። ብዙ ኅብር ያለውንም ልብስ ለብሳ ነበር፥ እንዲህ ያለውን ልብስ የንጉሡ ልጆች ደናግሉ ይለብሱ ነበርና፤ አገልጋዩም አስወጥቶ በሩን ዘጋባት። ትዕማርም በራስዋ ላይ አመድ ነስንሳ፥ ብዙ ኅብርም ያለውን ልብስዋን ተርትራ፥ እጅዋንም በራስዋ ላይ ጭና እየጮኸች ሄደች።
#ትዕማርን_ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀🤦♀
👇👇👇👇👇👇👇👇
ሀሳቦን ያጋሯት
@YEAWEDIMERITE
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
Audio
#መልካም የደብረ ታቦር በዓል
የማህበረ #ፊሊጶስ መዝሙር
#ቡሄ በሉ ... ሆ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
የማህበረ #ፊሊጶስ መዝሙር
#ቡሄ በሉ ... ሆ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#የዛሬው ባለታሪክ #ግያዝ ይባላል።
የሶርያ ንጉሥ ሠራዊት አለቃ ንዕማንም እግዚአብሔር በእርሱ እጅ ለሶርያ ደኅንነትን ስለ ሰጠ በጌታው ዘንድ ታላቅ ክቡር ሰው ነበረ፤ ደግሞም ጽኑዕ ኃያል ነበረ፥ ነገር ግን ለምጻም ነበረ። ከሶርያውያንም አገር አደጋ ጣዮች ወጥተው ነበር፥ ከእስራኤልም ምድር ታናሽ ብላቴና ሴት ማርከው ነበር፤ የንዕማንንም ሚስት ታገለግል ነበር። እመቤትዋንም፦ ጌታዬ በሰማርያ ካለው ከነቢዩ ፊት ቢደርስ ኖሮ ከለምጹ በፈወሰው ነበር አለቻት። ንዕማንም ገብቶ ለጌታው፦ ከእስራኤል አገር የሆነች አንዲት ብላቴና እንዲህና እንዲህ ብላለች ብሎ ነገረው። የሶርያም ንጉሥ ንዕማንን፦ ሂድ፥ ለእስራኤል ንጉሥ ደብዳቤ እልካለሁ አለው። እርሱም ሄደ፥ አሥርም መክሊት ብር፥ ስድስት ሺህም ወርቅ፥ አሥርም መለውጫ ልብስ በእጁ ወሰደ። ለእስራኤልም ንጉሥ፦ ይህች ደብዳቤ ወደ አንተ ስትደርስ ባሪያዬን ንዕማንን ከለምጹ ትፈውሰው ዘንድ እንደ ሰደድሁልህ እወቅ የሚል ደብዳቤ ወሰደ። የእስራኤልም ንጉሥ ደብዳቤውን ባነበበ ጊዜ ልብሱን ቀድዶ፦ ሰውን ከለምጹ እፈውስ ዘንድ ይህ ሰው ወደ እኔ መስደዱ እኔ በውኑ ለመግደልና ለማዳን የምችል አምላክ ሆኜ ነውን? ተመልከቱ፥ የጠብ ምክንያትም እንደሚፈልግብኝ እዩ አለ። የእግዚአብሔርም ሰው ኤልሳዕ የእስራኤል ንጉሥ ልብሱን እንደ ቀደደ በሰማ ጊዜ፦ ልብስህን ለምን ቀደድህ? ወደ እኔ ይምጣ፥ በእስራኤልም ዘንድ ነቢይ እንዳለ ያውቃል ብሎ ወደ ንጉሡ ላከ። ንዕማንም በፈረሱና በሰረገላው መጣ፥ በኤልሳዕም ቤት ደጃፍ ውጭ ቆመ። ኤልሳዕም፦ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ሰባት ጊዜ ታጠብ ሥጋህም ይፈወሳል፥ አንተም ንጹሕ ትሆናለህ ብሎ ወደ እርሱ መልእክተኛ ላከ። ንዕማን ግን ተቈጥቶ ሄደ፥ እንዲህም አለ፦ እነሆ፥ ወደ እኔ የሚመጣ፥ ቆሞም የአምላኩን የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ፥ የለምጹንም ስፍራ በእጁ ዳስሶ የሚፈውሰኝ መስሎኝ ነበር። የደማስቆ ወንዞች አባናና ፋርፋ ከእስራኤል ውኆች ሁሉ አይሻሉምን? በእነርሱስ ውስጥ መታጠብና መንጻት አይቻለኝም ኖሮአልን? ዘወርም ብሎ ተቈጥቶ ሄደ። ባሪያዎቹም ቀርበው፦ አባት ሆይ፥ ነቢዩ ታላቅ ነገርስ እንኳ ቢነግርህ ኖሮ ባደረግኸው ነበር ይልቁንስ፦ ታጠብና ንጹሕ ሁን ቢልህ እንዴት ነዋ! ብለው ተናገሩት። ወረደም፥ የእግዚአብሔርም ሰው እንደ ተናገረው በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ ሥጋውም እንደ ገና እንደ ትንሽ ብላቴና ሥጋ ሆኖ ተመለሰ፥ ንጹሕም ሆነ። እርሱም ከጭፍራው ሁሉ ጋር ወደ እግዚአብሔር ሰው ተመለሰ፥ ወጥቶም በፊቱ ቆመና፦ እነሆ፥ ከእስራኤል ዘንድ በቀር በምድር ሁሉ አምላክ እንደሌለ አወቅሁ አሁንም ከባሪያህ በረከት ትቀበል ዘንድ እለምንሃለሁ አለ። እርሱም፦ በፊቱ የቆምሁት ሕያው እግዚአብሔርን! አልቀበልም አለ። ይቀበለውም ዘንድ ግድ አለው፤ እርሱ ግን እንቢ አለ። ንዕማንም፦ እኔ ባሪያህ ከእንግዲህ ወዲህ ከእግዚአብሔር በቀር ለሌሎች አማልክት የሚቃጠል መሥዋዕት ወይም ሌላ መሥዋዕት አላቀርብምና ሁለት የበቅሎ ጭነት አፈር እንድወስድ እሺ ትለኝ ዘንድ እለምንሃለሁ።እግዚአብሔርም ለእኔ ለባሪያህ በዚህ ነገር ብቻ ይቅር ይበለኝ፤ ጌታዬ በዚያ ይሰግድ ዘንድ እጄን ተደግፎ ወደ ሬሞን ቤት በገባ ጊዜ፥ እኔም በሬሞን ቤት በሰገድሁ ጊዜ፥ እግዚአብሔር በዚህ ነገር ለእኔ ለባሪያህ ይቅር ይበለኝ አለ። እርሱም፦ በደኅና ሂድ አለው። አንድ አግድመትም ያህል ከእርሱ ራቀ።
የእግዚአብሔርም ሰው ሎሌ ግያዝ፦ ጌታዬ ሶርያዊውን ይህን ንዕማንን ማረው፥ ካመጣለትም ነገር ምንም አልተቀበለም፤ ሕያው እግዚአብሔርን! በስተ ኋለው እሮጣለሁ፥ ከእርሱም አንዳች እወስዳለሁ አለ።ግያዝም ንዕማንን ተከተለው፤ ንዕማንም ወደ እርሱ ሲሮጥ ባየው ጊዜ ሊገናኘው ከሰረገላው ወርዶ፦ ሁሉ ደኅና ነውን? አለው። እርሱም፦ ደኅና ነው። አሁን ከነቢያት ወገን የሆኑት ሁለት ጕልማሶች ከተራራማው ከኤፍሬም አገር ወደ እኔ መጥተዋል፤ አንድ መክሊት ብርና ሁለት መለወጫ ልብስ ትሰጣቸው ዘንድ እለምንሃለሁ ብሎ ጌታዬ ላከኝ አለ። ንዕማንም፦ ሁለት መክሊት ትወስድ ዘንድ ይፈቀድልህ አለ፤ ግድ አለውም፤ ሁለቱንም መክሊት ብር በሁለት ከረጢት ውስጥ አሰረና ከሁለት መለወጫ ልብስ ጋር ለሁለት ሎሌዎቹ አስያዘ፤ እነርሱም ተሸክመው በፊቱ ሄዱ።ወደ ኮረብታውም በመጣ ጊዜ ከእጃቸው ወስዶ በቤቱ ውስጥ አኖራቸው፤ ሰዎቹንም አሰናበተ፥ እነርሱም ሄዱ። እርሱ ግን ገብቶ በጌታው ፊት ቆመ፤ ኤልሳዕም፦ ግያዝ ሆይ፥ ከወዴት መጣህ? አለው። እርሱም፦ እኔ ባሪያህ ወዴትም አልሄድሁም አለ። እርሱም፦ ያ ሰው ከሰረገላው ወርዶ ሊቀበልህ በተመለሰ ጊዜ ልቤ ከአንተ ጋር አልሄደምን? ብሩንና ልብሱን፥ የወይራውንና የወይኑን ቦታ፥ በጎችንና በሬዎችን፥ ወንዶችንና ሴቶችን ባሪያዎች ትቀበል ዘንድ ይህ ጊዜው ነውን?
እንግዲህስ የንዕማን ለምጽ በአንተ ላይ፥ ለዘላለምም በዘርህ ላይ ይጣበቃል አለው። እንደ በረዶም ለምጻም ሆኖ ከእርሱ ዘንድ ወጣ።
#ግያዝን ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
👉በገንዘብ ፍቅር ቢነደፉ?
👉 የዚህ ዓለም ሀብትና ነዋይ ቢያጓጓዎ?
👉 የገንዘቡ ምንጭ ምንም ካልተጎዳ ምን አለበት እኔ ብጠቀምበት የሚል ሀሳብ ቢፈታተኖት? ምን ያደርጋሉ?
👉 #ግያዝስ ስሕተቱን ከሰራ በኃላ ወደፊት ምን ያድርግ?
#ግያዝ ምክሮቻችሁን ዛሬም እየጠበቀ ነው
👇👇👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ_ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
የሶርያ ንጉሥ ሠራዊት አለቃ ንዕማንም እግዚአብሔር በእርሱ እጅ ለሶርያ ደኅንነትን ስለ ሰጠ በጌታው ዘንድ ታላቅ ክቡር ሰው ነበረ፤ ደግሞም ጽኑዕ ኃያል ነበረ፥ ነገር ግን ለምጻም ነበረ። ከሶርያውያንም አገር አደጋ ጣዮች ወጥተው ነበር፥ ከእስራኤልም ምድር ታናሽ ብላቴና ሴት ማርከው ነበር፤ የንዕማንንም ሚስት ታገለግል ነበር። እመቤትዋንም፦ ጌታዬ በሰማርያ ካለው ከነቢዩ ፊት ቢደርስ ኖሮ ከለምጹ በፈወሰው ነበር አለቻት። ንዕማንም ገብቶ ለጌታው፦ ከእስራኤል አገር የሆነች አንዲት ብላቴና እንዲህና እንዲህ ብላለች ብሎ ነገረው። የሶርያም ንጉሥ ንዕማንን፦ ሂድ፥ ለእስራኤል ንጉሥ ደብዳቤ እልካለሁ አለው። እርሱም ሄደ፥ አሥርም መክሊት ብር፥ ስድስት ሺህም ወርቅ፥ አሥርም መለውጫ ልብስ በእጁ ወሰደ። ለእስራኤልም ንጉሥ፦ ይህች ደብዳቤ ወደ አንተ ስትደርስ ባሪያዬን ንዕማንን ከለምጹ ትፈውሰው ዘንድ እንደ ሰደድሁልህ እወቅ የሚል ደብዳቤ ወሰደ። የእስራኤልም ንጉሥ ደብዳቤውን ባነበበ ጊዜ ልብሱን ቀድዶ፦ ሰውን ከለምጹ እፈውስ ዘንድ ይህ ሰው ወደ እኔ መስደዱ እኔ በውኑ ለመግደልና ለማዳን የምችል አምላክ ሆኜ ነውን? ተመልከቱ፥ የጠብ ምክንያትም እንደሚፈልግብኝ እዩ አለ። የእግዚአብሔርም ሰው ኤልሳዕ የእስራኤል ንጉሥ ልብሱን እንደ ቀደደ በሰማ ጊዜ፦ ልብስህን ለምን ቀደድህ? ወደ እኔ ይምጣ፥ በእስራኤልም ዘንድ ነቢይ እንዳለ ያውቃል ብሎ ወደ ንጉሡ ላከ። ንዕማንም በፈረሱና በሰረገላው መጣ፥ በኤልሳዕም ቤት ደጃፍ ውጭ ቆመ። ኤልሳዕም፦ ሂድ፥ በዮርዳኖስም ሰባት ጊዜ ታጠብ ሥጋህም ይፈወሳል፥ አንተም ንጹሕ ትሆናለህ ብሎ ወደ እርሱ መልእክተኛ ላከ። ንዕማን ግን ተቈጥቶ ሄደ፥ እንዲህም አለ፦ እነሆ፥ ወደ እኔ የሚመጣ፥ ቆሞም የአምላኩን የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ፥ የለምጹንም ስፍራ በእጁ ዳስሶ የሚፈውሰኝ መስሎኝ ነበር። የደማስቆ ወንዞች አባናና ፋርፋ ከእስራኤል ውኆች ሁሉ አይሻሉምን? በእነርሱስ ውስጥ መታጠብና መንጻት አይቻለኝም ኖሮአልን? ዘወርም ብሎ ተቈጥቶ ሄደ። ባሪያዎቹም ቀርበው፦ አባት ሆይ፥ ነቢዩ ታላቅ ነገርስ እንኳ ቢነግርህ ኖሮ ባደረግኸው ነበር ይልቁንስ፦ ታጠብና ንጹሕ ሁን ቢልህ እንዴት ነዋ! ብለው ተናገሩት። ወረደም፥ የእግዚአብሔርም ሰው እንደ ተናገረው በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ ሥጋውም እንደ ገና እንደ ትንሽ ብላቴና ሥጋ ሆኖ ተመለሰ፥ ንጹሕም ሆነ። እርሱም ከጭፍራው ሁሉ ጋር ወደ እግዚአብሔር ሰው ተመለሰ፥ ወጥቶም በፊቱ ቆመና፦ እነሆ፥ ከእስራኤል ዘንድ በቀር በምድር ሁሉ አምላክ እንደሌለ አወቅሁ አሁንም ከባሪያህ በረከት ትቀበል ዘንድ እለምንሃለሁ አለ። እርሱም፦ በፊቱ የቆምሁት ሕያው እግዚአብሔርን! አልቀበልም አለ። ይቀበለውም ዘንድ ግድ አለው፤ እርሱ ግን እንቢ አለ። ንዕማንም፦ እኔ ባሪያህ ከእንግዲህ ወዲህ ከእግዚአብሔር በቀር ለሌሎች አማልክት የሚቃጠል መሥዋዕት ወይም ሌላ መሥዋዕት አላቀርብምና ሁለት የበቅሎ ጭነት አፈር እንድወስድ እሺ ትለኝ ዘንድ እለምንሃለሁ።እግዚአብሔርም ለእኔ ለባሪያህ በዚህ ነገር ብቻ ይቅር ይበለኝ፤ ጌታዬ በዚያ ይሰግድ ዘንድ እጄን ተደግፎ ወደ ሬሞን ቤት በገባ ጊዜ፥ እኔም በሬሞን ቤት በሰገድሁ ጊዜ፥ እግዚአብሔር በዚህ ነገር ለእኔ ለባሪያህ ይቅር ይበለኝ አለ። እርሱም፦ በደኅና ሂድ አለው። አንድ አግድመትም ያህል ከእርሱ ራቀ።
የእግዚአብሔርም ሰው ሎሌ ግያዝ፦ ጌታዬ ሶርያዊውን ይህን ንዕማንን ማረው፥ ካመጣለትም ነገር ምንም አልተቀበለም፤ ሕያው እግዚአብሔርን! በስተ ኋለው እሮጣለሁ፥ ከእርሱም አንዳች እወስዳለሁ አለ።ግያዝም ንዕማንን ተከተለው፤ ንዕማንም ወደ እርሱ ሲሮጥ ባየው ጊዜ ሊገናኘው ከሰረገላው ወርዶ፦ ሁሉ ደኅና ነውን? አለው። እርሱም፦ ደኅና ነው። አሁን ከነቢያት ወገን የሆኑት ሁለት ጕልማሶች ከተራራማው ከኤፍሬም አገር ወደ እኔ መጥተዋል፤ አንድ መክሊት ብርና ሁለት መለወጫ ልብስ ትሰጣቸው ዘንድ እለምንሃለሁ ብሎ ጌታዬ ላከኝ አለ። ንዕማንም፦ ሁለት መክሊት ትወስድ ዘንድ ይፈቀድልህ አለ፤ ግድ አለውም፤ ሁለቱንም መክሊት ብር በሁለት ከረጢት ውስጥ አሰረና ከሁለት መለወጫ ልብስ ጋር ለሁለት ሎሌዎቹ አስያዘ፤ እነርሱም ተሸክመው በፊቱ ሄዱ።ወደ ኮረብታውም በመጣ ጊዜ ከእጃቸው ወስዶ በቤቱ ውስጥ አኖራቸው፤ ሰዎቹንም አሰናበተ፥ እነርሱም ሄዱ። እርሱ ግን ገብቶ በጌታው ፊት ቆመ፤ ኤልሳዕም፦ ግያዝ ሆይ፥ ከወዴት መጣህ? አለው። እርሱም፦ እኔ ባሪያህ ወዴትም አልሄድሁም አለ። እርሱም፦ ያ ሰው ከሰረገላው ወርዶ ሊቀበልህ በተመለሰ ጊዜ ልቤ ከአንተ ጋር አልሄደምን? ብሩንና ልብሱን፥ የወይራውንና የወይኑን ቦታ፥ በጎችንና በሬዎችን፥ ወንዶችንና ሴቶችን ባሪያዎች ትቀበል ዘንድ ይህ ጊዜው ነውን?
እንግዲህስ የንዕማን ለምጽ በአንተ ላይ፥ ለዘላለምም በዘርህ ላይ ይጣበቃል አለው። እንደ በረዶም ለምጻም ሆኖ ከእርሱ ዘንድ ወጣ።
#ግያዝን ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ?
👉በገንዘብ ፍቅር ቢነደፉ?
👉 የዚህ ዓለም ሀብትና ነዋይ ቢያጓጓዎ?
👉 የገንዘቡ ምንጭ ምንም ካልተጎዳ ምን አለበት እኔ ብጠቀምበት የሚል ሀሳብ ቢፈታተኖት? ምን ያደርጋሉ?
👉 #ግያዝስ ስሕተቱን ከሰራ በኃላ ወደፊት ምን ያድርግ?
#ግያዝ ምክሮቻችሁን ዛሬም እየጠበቀ ነው
👇👇👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
#ዓውደ_ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
...ጷጒሜን በጥቂቱ...
ጷጒሜ ሥርወ ቃሉ "ኤጳግሚኖስ" ከሚለው የግሪክ ቃል የወጣ ሲሆን "ተጨማሪ" የሚለውን ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን እንደ አዋጅ ጾም ያይደለ እንደ ፈቃድ ጾም አስቀምጣልን በጾም በጸሎት በሱባኤ እናስባታለን ሀገራችን ኢትዮጵያም 13ኛ ወር አድርጋ ትቆጥራታለች ለዚህም ነው የ13 ወር ፀጋ ተብላ የምትሞገሰው። ይህች በዕድሜዎ ከሌሎቹ አስራ ሁለት ወራት ብታንስም እኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የእግዚአብሔር ገንዘቦች ልዮ አድርገን እናስባታለን ልዮ ምስጢር ይዛለችና የእግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በዚህ በአራት ዓመት አንዴ ስድስት በስድስት መቶ ዓመት አንዴ ደግሞ ሰባት በምትሆነው በጷጒሜ ወር የምድር ውሆችን የውሃ አካላትን በሙሉ ይባርካቸዋል ቤተሳይዳ የነበረውን ውሃ መልአኩ እንዳናወጠው (እንደባርከው) ሁሉ ...ይህንም በሙሉ እምነት አምኖ የተጠመቀ ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ይፈወሳል ሕጻናትንም ያሳድጋል ፤ በተለምዶም የእግዚአብሔር መድኃኒት ተብሎ የሚጠራው የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ሲመቱ በሚውልበት በጷጒሜ 3 ዕለት በሚዘንበው ጠበል ሕጻናት " ሩፋኤል አሳድገኝ " እያሉ ይጠመቃሉ አዋቂውም እንደዛው ይጠመቃል ጠበሉንም በማስቀመጫ እቃ እያስቀመጥን ቤታችንን ከጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ ክፉ ሴራ እንጠበቃለን እናቶቻችንም ጠበሉን የእንጀራ ሊጥ ውስጥ እየጨመሩ ምግበ ሥጋ ወነፍስ የሆነ እንጀራ ጋግረው ይመግቡናል። ይህን ጾም እየጾምን ፈዋሽ ጠበሉን እየተጠመቅን ወርዋን ካገባደድን መጪው አዲስ ዓመት የበረከት ፣ የረድኤት ፣ የፍቅር እና የሰላም ይሆንልናል ያድርግልንም! መልካም በዓል!!
አዘጋጅ፦ባሮክ ዘ ደብረ አሚን
ቀን 3/13/2012
አ.አ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጷጒሜ ሥርወ ቃሉ "ኤጳግሚኖስ" ከሚለው የግሪክ ቃል የወጣ ሲሆን "ተጨማሪ" የሚለውን ትርጉም ይሰጠናል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን እንደ አዋጅ ጾም ያይደለ እንደ ፈቃድ ጾም አስቀምጣልን በጾም በጸሎት በሱባኤ እናስባታለን ሀገራችን ኢትዮጵያም 13ኛ ወር አድርጋ ትቆጥራታለች ለዚህም ነው የ13 ወር ፀጋ ተብላ የምትሞገሰው። ይህች በዕድሜዎ ከሌሎቹ አስራ ሁለት ወራት ብታንስም እኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የእግዚአብሔር ገንዘቦች ልዮ አድርገን እናስባታለን ልዮ ምስጢር ይዛለችና የእግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በዚህ በአራት ዓመት አንዴ ስድስት በስድስት መቶ ዓመት አንዴ ደግሞ ሰባት በምትሆነው በጷጒሜ ወር የምድር ውሆችን የውሃ አካላትን በሙሉ ይባርካቸዋል ቤተሳይዳ የነበረውን ውሃ መልአኩ እንዳናወጠው (እንደባርከው) ሁሉ ...ይህንም በሙሉ እምነት አምኖ የተጠመቀ ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ይፈወሳል ሕጻናትንም ያሳድጋል ፤ በተለምዶም የእግዚአብሔር መድኃኒት ተብሎ የሚጠራው የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ሲመቱ በሚውልበት በጷጒሜ 3 ዕለት በሚዘንበው ጠበል ሕጻናት " ሩፋኤል አሳድገኝ " እያሉ ይጠመቃሉ አዋቂውም እንደዛው ይጠመቃል ጠበሉንም በማስቀመጫ እቃ እያስቀመጥን ቤታችንን ከጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ ክፉ ሴራ እንጠበቃለን እናቶቻችንም ጠበሉን የእንጀራ ሊጥ ውስጥ እየጨመሩ ምግበ ሥጋ ወነፍስ የሆነ እንጀራ ጋግረው ይመግቡናል። ይህን ጾም እየጾምን ፈዋሽ ጠበሉን እየተጠመቅን ወርዋን ካገባደድን መጪው አዲስ ዓመት የበረከት ፣ የረድኤት ፣ የፍቅር እና የሰላም ይሆንልናል ያድርግልንም! መልካም በዓል!!
አዘጋጅ፦ባሮክ ዘ ደብረ አሚን
ቀን 3/13/2012
አ.አ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ጷጉሜ የተባለችው ወር ከየት መጣች?
______ (በአለቃ ዕፁብ ማናዬ)____________
ብዙዎቻችን ስለ ዓመት ስንናገርና ለልጆቻችን ስናስተምር አንድ ዓመት 365 ¼ ቀንት፣ 52 ሳምንታት እና 12 ወራት በማለት እንናገራለል፡፡ እውነትም ልክ ነው፤ ነገር ግን 365 ¼ ማለት ምን ማለት ነው? ¼ የሚባል ቀን አለን? 12 ወራት በሠላሳ በሠላሳ ቀናት የተከፋፈሉ ሆነው ድምራቸው 12X30 = 360 ነው፡፡ ታዲያ 5ቀናት እና ¼ የተባለው ከየት መጣ? ጷጉሜስ የተባለችው ወርስ ከየት መጣች? ለሚባሉትን ጥያቄዎች አስተዋዮች ይጠይቃሉ፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን እንደሚከተለው ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ አስቀምጠውልናል፡፡(ይህ መልስ ብዛት ካላቸው የብራና ጽሑፎች ተውጣቶ ቀለል ባለ ዘዴ የቀረበ ነው፡፡) ይህ ትምህርት የሚገኘው አቡሻኽር በተባለው የቤተክርስቲያን ትምህርት ነው ፡፡ ትምህርቱ ሰፊ ነው፡፡ አብዛኛውም የሒሳብ ስሌት ያለበትም ነው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ወደተነሳንበት ስንመለስ ስንት ወቅቶች አሉን ከተባለ አራት ናቸው፡፡ እነሱም
#1 ክረምት(ከሰኔ26 መስከረም25)፣
#2 መፀው/መከር(ከመስከረም26- ታኅሣሥ25)፣ #3 በጋ/ሐጋይ (ከታኅሣሥ26 - መጋቢት25)፣
#4 ጸደይ/በልግ(ከመጋቢት26 - ሰኔ25) ነው፡፡ እያንዳንዱ ወቅት ደግሞ ሦስት ወራትን ይዟል፡፡ 3X30=90 ነው፡፡ 90 ሲባዛ በ4 ደግሞ 360 ነው፡፡ እንግዲህ የስሌቱ ነገር የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ከላይ አንድ ወቅት 90 ቀን ሳይሆን 91 ቀን 7ሰዓት እና 30 ደቂቃ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው የየወሩ ቀን ማጠር እና መርዘምን ተከትሎ በሚመጣ ልዩነት ነው፡፡ #ለምሳሌ
መስከረም ላይ 12 ሰዓት አይመሽም ብርሃን ነው፡፡
ታኅሣሥ ላይ ግን 12 ሰዓት ጭልምልም ይላል፡፡ ሌሊቱም ረዥም ነው፡፡ ለምሳሌ እነዚህ ቀረቡ እንጂ እያንዳንዱ ወር የተለያየ ልዩነት አለው፡፡ ስለዚህ ጠቅላላውን አራቱንም ወቅቶች ስንደምራቸው የምናገኘው ውጤት አንድ ዓመትን ያስገኙልናል፡፡
🚩ክረምት 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩መፀው 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩በጋ/ሐጋይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩ጸደይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
::::::::::::::::::::::::::
ጠቅለል አድርገን ስንደምረው ዘጠና ዘጠናው ቀን ስንደምረው 90 X 4 = 360 ይሆናል፡፡ ይህ የአሥራሁለት ወሩን ያዘ ማለት ነው፡፡ የየወቅቱን አንዳንድ ቀን ስንደምር 1 X 4 = 4 ይሆናል፡፡ ይህም የጷጉሜ አራቱ ቀናት ናቸው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የቀሩትን 7 ሰዓት እና 30 ደቂቃዎች ስንደምራቸው 30ሰዓት ይመጣል፡፡ ወደ ዕለት ሲቀየር 1 ቀን እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከላይ ካገኘነው 4 ጋር ሲደመር 5 ቀናት እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡
#በጠቅላላ አንድ ዓመት 365 ከ6ሰዓት ወይም ¼የሚባለው ለዚህ ነው ይህ ስድስት ሰዓት በአራት ዓመት አንድቀን ሆኖ ጷጉሜ ስድስት እንድትሆን ያደርገዋል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጳጉሜ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ጭማሪ” ማለት ነው ፡፡ በግእዝ “ወሰከ – ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ተውሳክ (ተጨማሪ) ማለት ነው፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የዓመት ተጨማሪ ወር አድርገናታል፡፡ ይህቺ ወር በ600 ዓመት 7 ትሆናለች ነገር ግን ሊቃውንት ይቺን የትርፍ ትርፍ ናትና ከስሌት ውጪ የማይኖርባት በማለት ይገልጧታል፡፡
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጷጉሜ ፫/፳ ፻- ፲፪ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
______ (በአለቃ ዕፁብ ማናዬ)____________
ብዙዎቻችን ስለ ዓመት ስንናገርና ለልጆቻችን ስናስተምር አንድ ዓመት 365 ¼ ቀንት፣ 52 ሳምንታት እና 12 ወራት በማለት እንናገራለል፡፡ እውነትም ልክ ነው፤ ነገር ግን 365 ¼ ማለት ምን ማለት ነው? ¼ የሚባል ቀን አለን? 12 ወራት በሠላሳ በሠላሳ ቀናት የተከፋፈሉ ሆነው ድምራቸው 12X30 = 360 ነው፡፡ ታዲያ 5ቀናት እና ¼ የተባለው ከየት መጣ? ጷጉሜስ የተባለችው ወርስ ከየት መጣች? ለሚባሉትን ጥያቄዎች አስተዋዮች ይጠይቃሉ፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን እንደሚከተለው ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ አስቀምጠውልናል፡፡(ይህ መልስ ብዛት ካላቸው የብራና ጽሑፎች ተውጣቶ ቀለል ባለ ዘዴ የቀረበ ነው፡፡) ይህ ትምህርት የሚገኘው አቡሻኽር በተባለው የቤተክርስቲያን ትምህርት ነው ፡፡ ትምህርቱ ሰፊ ነው፡፡ አብዛኛውም የሒሳብ ስሌት ያለበትም ነው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ወደተነሳንበት ስንመለስ ስንት ወቅቶች አሉን ከተባለ አራት ናቸው፡፡ እነሱም
#1 ክረምት(ከሰኔ26 መስከረም25)፣
#2 መፀው/መከር(ከመስከረም26- ታኅሣሥ25)፣ #3 በጋ/ሐጋይ (ከታኅሣሥ26 - መጋቢት25)፣
#4 ጸደይ/በልግ(ከመጋቢት26 - ሰኔ25) ነው፡፡ እያንዳንዱ ወቅት ደግሞ ሦስት ወራትን ይዟል፡፡ 3X30=90 ነው፡፡ 90 ሲባዛ በ4 ደግሞ 360 ነው፡፡ እንግዲህ የስሌቱ ነገር የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ከላይ አንድ ወቅት 90 ቀን ሳይሆን 91 ቀን 7ሰዓት እና 30 ደቂቃ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው የየወሩ ቀን ማጠር እና መርዘምን ተከትሎ በሚመጣ ልዩነት ነው፡፡ #ለምሳሌ
መስከረም ላይ 12 ሰዓት አይመሽም ብርሃን ነው፡፡
ታኅሣሥ ላይ ግን 12 ሰዓት ጭልምልም ይላል፡፡ ሌሊቱም ረዥም ነው፡፡ ለምሳሌ እነዚህ ቀረቡ እንጂ እያንዳንዱ ወር የተለያየ ልዩነት አለው፡፡ ስለዚህ ጠቅላላውን አራቱንም ወቅቶች ስንደምራቸው የምናገኘው ውጤት አንድ ዓመትን ያስገኙልናል፡፡
🚩ክረምት 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩መፀው 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩በጋ/ሐጋይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩ጸደይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
::::::::::::::::::::::::::
ጠቅለል አድርገን ስንደምረው ዘጠና ዘጠናው ቀን ስንደምረው 90 X 4 = 360 ይሆናል፡፡ ይህ የአሥራሁለት ወሩን ያዘ ማለት ነው፡፡ የየወቅቱን አንዳንድ ቀን ስንደምር 1 X 4 = 4 ይሆናል፡፡ ይህም የጷጉሜ አራቱ ቀናት ናቸው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የቀሩትን 7 ሰዓት እና 30 ደቂቃዎች ስንደምራቸው 30ሰዓት ይመጣል፡፡ ወደ ዕለት ሲቀየር 1 ቀን እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከላይ ካገኘነው 4 ጋር ሲደመር 5 ቀናት እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡
#በጠቅላላ አንድ ዓመት 365 ከ6ሰዓት ወይም ¼የሚባለው ለዚህ ነው ይህ ስድስት ሰዓት በአራት ዓመት አንድቀን ሆኖ ጷጉሜ ስድስት እንድትሆን ያደርገዋል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጳጉሜ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ጭማሪ” ማለት ነው ፡፡ በግእዝ “ወሰከ – ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ተውሳክ (ተጨማሪ) ማለት ነው፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የዓመት ተጨማሪ ወር አድርገናታል፡፡ ይህቺ ወር በ600 ዓመት 7 ትሆናለች ነገር ግን ሊቃውንት ይቺን የትርፍ ትርፍ ናትና ከስሌት ውጪ የማይኖርባት በማለት ይገልጧታል፡፡
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጷጉሜ ፫/፳ ፻- ፲፪ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሰን።
ነገረ ጥምቀት
ወአሜሃ መጽአ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ እም ገሊላ ውስተ ዮርዳኖስ ከመ ይጠመቅ እም ዮሐንስ ... ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
ለጌታ ሠላሳ ሲሞላው ለዮሐንስ መንፈቅ ሲተርፈው (ሠላሳ ዓመት ከስድስት ወር በኃላ) ያን ጊዜ ጌታ በዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
እስቲ እንጠይቅ?
ማን ወደ ማን ነበር መሔድ የነበረበት? ዮሐንስ ወደ ጌታ ወይስ ጌታ ወደ ዮሐንስ? እርግጥ ፈጣሪ ወደ ፍጡሩ መሔዱ የመጣው ለትዕትና እንጂ ለልዕልና አለመሆኑን ሲያጠይቅ ነው። እንዴት ያለ ትዕትና ነው!
አንድም ስርዓትን ሲሰራ ነው። እንዴት ያለ ስርዓት ቢሉ ማንም ተጠማቂ ወደ ካህናት መሔድ እንዳለበት ሲያጠይቅ ወደ ዮሐንስ ሄዶ ተጠመቀ።
ለምን በዮርዳኖስ ተጠመቀ ቢሉ?
1. ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ
• ❝ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።❞ መዝሙር 114: 3
• ❝አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?❞ መዝሙር 114: 5
2. ምሳሌነቱ ይፈጸም ዘንድ
• ዮርዳኖስ ነቁ አንድ ነው በኃላም በደሴቱ ይከፈላል መልሶ ከታች መልሶ ይገናኛል ።
ምሳሌነቱ ፡- ከላይ ነቁ (መነሻው) አንድ መሆኑ የሰው ዘር ሁሉ በአዳም አንድ መሆኑን ሲሆን በኃላም በደሴት መለያየቱ አንድ የነበረው የሰው ልጅ ደሴት በተባለ ኃጥያት መከፋፈሉ አንድም ህዝበ እስራኤል እና አህዛብ ተብሎ መለያየቱ ፣ ወርዶ አንድ መሆኑ በጥምቀተ ክርስቶስ ህዝብ እና አህዛብ አንድ መሆናቸውን ያሳየናል።
ዮሐንስ ግን፦ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።
እናቱ ኤልሳቤጥ ድንግል ወደ እርሷ በመጣች ጊዜ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል ያለው በማዕጸን እያለ ሰምቶ ነበር እና እርሱም አምላኩን ወደ እርሱ መምጣቱ ተመልክቶ ይህ ነገር እንዴት ይሆንልኛል ብሎ የጌታውን አምላክነት መሰከረ !
ኢየሱስም መልሶ፦ አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት። ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
ማቴ 3 ፡ 13-17
ጌታ ለምን ተጠመቀ?
1. በጥምቀቱ ድኅነተ ሰጋ ድኅነተ ነብስን ሊሰጠን
• ማርቆስ 16: 16 ❝ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።❞
2. ዳግም ልደትን ለእኛ ሊሰጠን
• ዮሐንስ 3: 3 ❝ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።❞
• ቲቶ 3፡4 ❞ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም❞
3. ለኃጥያታችን የስርየት መንገድ ሲሰራልን
• ሐዋርያት ስራ 22: 16 ❝አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።❞
በጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድ እንደሆንን እንዲሁ መለያየታችንን ክርስቶስ በፍቅር አንድ ያድርገን ።
መምህር ዲ/ን ኢ/ር እስጢፋኖስ ደሳለኝ
👇👇👇👇
👉@Yotor24
@Yotor24
ጥር 11 2013 ዓ.ም
አ.አ / ኢትዮጲያ
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ነገረ ጥምቀት
ወአሜሃ መጽአ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ እም ገሊላ ውስተ ዮርዳኖስ ከመ ይጠመቅ እም ዮሐንስ ... ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
ለጌታ ሠላሳ ሲሞላው ለዮሐንስ መንፈቅ ሲተርፈው (ሠላሳ ዓመት ከስድስት ወር በኃላ) ያን ጊዜ ጌታ በዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
እስቲ እንጠይቅ?
ማን ወደ ማን ነበር መሔድ የነበረበት? ዮሐንስ ወደ ጌታ ወይስ ጌታ ወደ ዮሐንስ? እርግጥ ፈጣሪ ወደ ፍጡሩ መሔዱ የመጣው ለትዕትና እንጂ ለልዕልና አለመሆኑን ሲያጠይቅ ነው። እንዴት ያለ ትዕትና ነው!
አንድም ስርዓትን ሲሰራ ነው። እንዴት ያለ ስርዓት ቢሉ ማንም ተጠማቂ ወደ ካህናት መሔድ እንዳለበት ሲያጠይቅ ወደ ዮሐንስ ሄዶ ተጠመቀ።
ለምን በዮርዳኖስ ተጠመቀ ቢሉ?
1. ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ
• ❝ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።❞ መዝሙር 114: 3
• ❝አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?❞ መዝሙር 114: 5
2. ምሳሌነቱ ይፈጸም ዘንድ
• ዮርዳኖስ ነቁ አንድ ነው በኃላም በደሴቱ ይከፈላል መልሶ ከታች መልሶ ይገናኛል ።
ምሳሌነቱ ፡- ከላይ ነቁ (መነሻው) አንድ መሆኑ የሰው ዘር ሁሉ በአዳም አንድ መሆኑን ሲሆን በኃላም በደሴት መለያየቱ አንድ የነበረው የሰው ልጅ ደሴት በተባለ ኃጥያት መከፋፈሉ አንድም ህዝበ እስራኤል እና አህዛብ ተብሎ መለያየቱ ፣ ወርዶ አንድ መሆኑ በጥምቀተ ክርስቶስ ህዝብ እና አህዛብ አንድ መሆናቸውን ያሳየናል።
ዮሐንስ ግን፦ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።
እናቱ ኤልሳቤጥ ድንግል ወደ እርሷ በመጣች ጊዜ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል ያለው በማዕጸን እያለ ሰምቶ ነበር እና እርሱም አምላኩን ወደ እርሱ መምጣቱ ተመልክቶ ይህ ነገር እንዴት ይሆንልኛል ብሎ የጌታውን አምላክነት መሰከረ !
ኢየሱስም መልሶ፦ አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት። ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።
ማቴ 3 ፡ 13-17
ጌታ ለምን ተጠመቀ?
1. በጥምቀቱ ድኅነተ ሰጋ ድኅነተ ነብስን ሊሰጠን
• ማርቆስ 16: 16 ❝ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።❞
2. ዳግም ልደትን ለእኛ ሊሰጠን
• ዮሐንስ 3: 3 ❝ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው።❞
• ቲቶ 3፡4 ❞ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም❞
3. ለኃጥያታችን የስርየት መንገድ ሲሰራልን
• ሐዋርያት ስራ 22: 16 ❝አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።❞
በጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድ እንደሆንን እንዲሁ መለያየታችንን ክርስቶስ በፍቅር አንድ ያድርገን ።
መምህር ዲ/ን ኢ/ር እስጢፋኖስ ደሳለኝ
👇👇👇👇
👉@Yotor24
@Yotor24
ጥር 11 2013 ዓ.ም
አ.አ / ኢትዮጲያ
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ሱባዔ
ሱባዔ በሰዋሰው ትርጉሙ ቆየ ሰነበተ ዘገየ ሰባት ማለት ሲሆን ምሥጢራዊ ትርጓሜውም ደግሞ አንድ ሰው ከዚህ ቀን እከዚህ ቀን ድረስ ፈጣሪዬን በጸሎት እገናኛለሁብሎ የሚያቅደው ዕቅድ ነው። ሰባት ቁጥር በእስራኤላዊያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር አረፈ እንዲል በጸሎት የሚተጉ ምዕመናንም በቀን ሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል ። ሱባዔ የተጀመረው ከመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት በኋላ ነው ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዴት እንደሚጸለይ እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ። ለአዳምም የጸሎት ጊዜያትን አስተምረውት አስተምረውት ነበርና ጥፈቱን አምኖ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔርም በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት ።
ሱባዔ ለምንምክንያት እንገባልን ቢሉ የመጀመሪያው የሚሆነው የሰው ልጅ በባህሪው ኃጢአት የሚስማማው ነው በሥጋ ሰውነቱ ፈጣሪን ይበድላል በፈጸመው በደል / ኃጢአት/ ሕሊናው ይወቅሰዋል በዚህም ያዝናል ይጸጸታል በሰራው ኃጢአትም ልቡ ይደነግጣል በዚህ ጊዜ የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት ሲል ሲል ሱባዔ ይገባል ።እግዚአብሔርን ለመማፀን የሚገባ ሱባዔ አለ ። ማንኛውም ሰው ሱባዔ በገባ ቁጥር ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማጽኖ ሊኖረው ይገባል ምንም የምንለምነውና የምንጠይቀው ነገር ሳይኖር ሰባዔውን ብንገባ የምናገኘው ምንም አይነት መልስ አይኖርም
ስለዚህ ተማፅኖ ሊኖረን ይገባል ። ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔው በኋላ ምን እንደተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖራቸው ሱባዔ በመግባታቸው የሚገኙት ነገር አይኖርም ይህን ተገንዝበው ከመግባታቸው በፊት የሚገቡበትን ምክንያት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው ። ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶቻችን ደማቸውን ካፈሰሱበት አጥንታቸውን ከከሰከሱበት ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራት የሰሩበት ቦታ ገዳማቸውና አድባራት ላይ የሚገባ ሱባዔ ከቅዱሳኑ ረድኤት ተካፋይ ይደርጋል ። ሱባዔ የተደበቀን ምሥጢር የሚገለጥበት ቁልፍ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው ቅዱሳን አባቶቻችን ያዩት እራይ ምሥጢሩና ትርጉሙ አልገለጥ ሲላቸው ሱባዔ ይገቡ ነበር እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነ ነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢሩንና ትርጉሙን ይገልጥላቸዋል ። ነቢዬ ዕዝራ የመጽሐፍታት ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ገባ እግዚአብሔር አምላክም ሁሉን ገለጸለት የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍታት ደግሞ ለመጻፍ ችሏል ይህ ምሥጢር የተገለጠለት በሱባዔ ነው ።
ከብሉይ ጀምሮ ያሉ የሱባዔ አባቶቻችን የገቡት ሱባዔ ሱባዔ አዳም ፣ ሱባዔ ሔኖክ ሱባዔ ነብያት
፣ሱባዔ ዳንኤል ሱባዔ ዳዊት በተጨማሪም የግል ሱባዔ የማኀበር ሱባዔ የአዋጅ ሱባዔ በመባል ይታወቃሉ በሐዲስ ኪዳን ከአራት ቀን በኋላ የምገባ ሐዋርያት የገቡት ሱባዔ ነው የፍልሰታ ሱባዔ በዚህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ የተገኘበት ትንሣኤዋ እንዲገለጥላቸው የተገባ ሱባዔ ነው ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን 14 ቀን ያክል በጻም በጸሎት ተማጽነው ትንሣኤዋን ገለጠችላቸው ። እንግዲህ ሱባዔ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ወቅቱ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ስባዔ እንደ መሆኑ መጠን እኛም የሐዋርያቱን ፈለግ በመከተል በንጹሕ ልቦና በትሁት መንፈስ ሆነን የእናታችን ትንሣኤ ይገለጥልን ዘንድ በሱባዔው እንትጋ ። ለሐዋርያቱ በሙሉ የልባቸውን መሻት የፈጸመች የጌታችን እናት ድንግል ማርያም የእኛንም የልባችንን ትፈጽምልናለች። ወቅቱን የጾም፣የጸሎት፣የስግደት፣ የምጽዋት፣ ስለ ሀገራችን ኢትዮጲያ የምናለቅስበት ነው ። ስለዚህ ሁላችን በሱባዔው እንበርታ
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥42
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
.....ይቆየን.......
ምንጭ :-እናት ማህበሬ ምክሐ ደናግል ሰሌዴ መጽሔት ሐምሌ ና ነሀሴ2010ዓ.ም የተለጠፈ
ሱባዔ በሰዋሰው ትርጉሙ ቆየ ሰነበተ ዘገየ ሰባት ማለት ሲሆን ምሥጢራዊ ትርጓሜውም ደግሞ አንድ ሰው ከዚህ ቀን እከዚህ ቀን ድረስ ፈጣሪዬን በጸሎት እገናኛለሁብሎ የሚያቅደው ዕቅድ ነው። ሰባት ቁጥር በእስራኤላዊያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር አረፈ እንዲል በጸሎት የሚተጉ ምዕመናንም በቀን ሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል ። ሱባዔ የተጀመረው ከመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት በኋላ ነው ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዴት እንደሚጸለይ እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ። ለአዳምም የጸሎት ጊዜያትን አስተምረውት አስተምረውት ነበርና ጥፈቱን አምኖ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔርም በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት ።
ሱባዔ ለምንምክንያት እንገባልን ቢሉ የመጀመሪያው የሚሆነው የሰው ልጅ በባህሪው ኃጢአት የሚስማማው ነው በሥጋ ሰውነቱ ፈጣሪን ይበድላል በፈጸመው በደል / ኃጢአት/ ሕሊናው ይወቅሰዋል በዚህም ያዝናል ይጸጸታል በሰራው ኃጢአትም ልቡ ይደነግጣል በዚህ ጊዜ የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት ሲል ሲል ሱባዔ ይገባል ።እግዚአብሔርን ለመማፀን የሚገባ ሱባዔ አለ ። ማንኛውም ሰው ሱባዔ በገባ ቁጥር ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማጽኖ ሊኖረው ይገባል ምንም የምንለምነውና የምንጠይቀው ነገር ሳይኖር ሰባዔውን ብንገባ የምናገኘው ምንም አይነት መልስ አይኖርም
ስለዚህ ተማፅኖ ሊኖረን ይገባል ። ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔው በኋላ ምን እንደተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖራቸው ሱባዔ በመግባታቸው የሚገኙት ነገር አይኖርም ይህን ተገንዝበው ከመግባታቸው በፊት የሚገቡበትን ምክንያት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው ። ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶቻችን ደማቸውን ካፈሰሱበት አጥንታቸውን ከከሰከሱበት ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራት የሰሩበት ቦታ ገዳማቸውና አድባራት ላይ የሚገባ ሱባዔ ከቅዱሳኑ ረድኤት ተካፋይ ይደርጋል ። ሱባዔ የተደበቀን ምሥጢር የሚገለጥበት ቁልፍ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው ቅዱሳን አባቶቻችን ያዩት እራይ ምሥጢሩና ትርጉሙ አልገለጥ ሲላቸው ሱባዔ ይገቡ ነበር እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነ ነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢሩንና ትርጉሙን ይገልጥላቸዋል ። ነቢዬ ዕዝራ የመጽሐፍታት ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ገባ እግዚአብሔር አምላክም ሁሉን ገለጸለት የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍታት ደግሞ ለመጻፍ ችሏል ይህ ምሥጢር የተገለጠለት በሱባዔ ነው ።
ከብሉይ ጀምሮ ያሉ የሱባዔ አባቶቻችን የገቡት ሱባዔ ሱባዔ አዳም ፣ ሱባዔ ሔኖክ ሱባዔ ነብያት
፣ሱባዔ ዳንኤል ሱባዔ ዳዊት በተጨማሪም የግል ሱባዔ የማኀበር ሱባዔ የአዋጅ ሱባዔ በመባል ይታወቃሉ በሐዲስ ኪዳን ከአራት ቀን በኋላ የምገባ ሐዋርያት የገቡት ሱባዔ ነው የፍልሰታ ሱባዔ በዚህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ የተገኘበት ትንሣኤዋ እንዲገለጥላቸው የተገባ ሱባዔ ነው ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን 14 ቀን ያክል በጻም በጸሎት ተማጽነው ትንሣኤዋን ገለጠችላቸው ። እንግዲህ ሱባዔ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ወቅቱ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ስባዔ እንደ መሆኑ መጠን እኛም የሐዋርያቱን ፈለግ በመከተል በንጹሕ ልቦና በትሁት መንፈስ ሆነን የእናታችን ትንሣኤ ይገለጥልን ዘንድ በሱባዔው እንትጋ ። ለሐዋርያቱ በሙሉ የልባቸውን መሻት የፈጸመች የጌታችን እናት ድንግል ማርያም የእኛንም የልባችንን ትፈጽምልናለች። ወቅቱን የጾም፣የጸሎት፣የስግደት፣ የምጽዋት፣ ስለ ሀገራችን ኢትዮጲያ የምናለቅስበት ነው ። ስለዚህ ሁላችን በሱባዔው እንበርታ
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥42
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
.....ይቆየን.......
ምንጭ :-እናት ማህበሬ ምክሐ ደናግል ሰሌዴ መጽሔት ሐምሌ ና ነሀሴ2010ዓ.ም የተለጠፈ
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (ተርቢኖስ ሰብስቤ)
" #ቀርታ_ያስቀረችን_ምርጥ_ዘር "
ጊዜው ክረምት ወቅቱም የዘር የመከር ወቅት በመሆኑ ዘርና ፍሬ ዝናብና ጠል ገበሬና በሬ ያለ መነጣጠል ይነሱበታል ። የክረምት ወቅት ምሳሌያዊ ትርጉም ዘርፈ ብዙ ነው ። አንዱ ና ዋናው ግን የ5500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ዘመን ፣ የመከራ ፣ የስቃይ ፣ የጨለማ ጊዜ ምሳሌ መሆኑ ነው :: ይኸውም ክረምት የ5ሺህ 500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው መባሉ በክረምት ጭጋግ ፣ ጉም ፣ደመና ይበረታሉ ነጎድጓዳት ይሰማሉ መባርቅት በርቀው ያስደነግጣሉ ይልቁኑ ደግሞ ውኃ ይሰለጥናል :: የክረምት ወቅት ሰቆቃ ይበዛዋል ይልቁኑ በስደት በደጅ ላሉ ሰውች ይብስባቸዋል “ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤”
የሚለው የጌታችን ምክርም የዚህን የክረምት ወቅት ጠንካራነት ያሳያል። ማቴ24፥20
የ5500ዘመንም ዘመነ ፍዳ ዘመነ መከራ ዘመነ ጨለማ ነውና በእግረ አጋንንት ተገዝተን በሲዖል እሳት ውስጥ ተግዘን ኖረናል ። በክረምት ውኃ እንዲሰለጥን በብሉይ ኪዳንም ውኃ ሰልጥኖ ፍጥረትን አጥፍቷል ገኃነመ እሳት በርትቷል በክረምት ምድር በውኃ እረክታ ትረሰርሳለች መሬት ትጨቀያለች በብሉይም ሰዎች በኃጢያት ዝናብ በስብሰው በሰዶም ግብር ጨቅይተው ነበር በዚህ ሰበብም ፈጣሪና ፍጡር ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ ተጣልተው ከርመዋል በመሆኑም ዘመነ ብሉይ (5500 ዘመን) ከአሰቃቂው የክረምት ወቅት ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል ። በመካከላቸውም የጠብ ግድግዳ ተገንብቶ ቆይቷል ቤተ ክርስቲያን በዚህ ወቅት ዘሪ ሊዘራ ወጣ እያለች የመንገድ ዳር፣ የጭንጫ ፣የሾህ ልቡና ያላቸውን ምዕመኖቿን ልብ በስብከተ መልካም መሬት አድርጋ በወንጌሏ ታቀናዋለች ቃል ዘርታ ሕይወት ታጭዳለች ።
ዛሬ ዛሬ ዓለማችን ነጭ ጥቁር ሀገራችን ደግሞ ኦሮሞ ትግሬ አማራ ጉራጌ በመባባል ተከፋፈለዋል። ሁሉም ዘሩ ምርጥ ዘር እንደሆነ ያስባል ሌላው ዘር ሁሉ እንክርዳድ የሚመስለው ነቀዝ ብዙ ነው ። ከሰዶምና ከጎሞራ ቅጣት የተረፍንባት ምርጥ ዘራችን ድንግል ማርያም ነች። ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችም መጀመራያ ብሎ እንደጠራት ትምክተ ዘመድነ የምትባል እመቤታችን ነች ። ከእርሷ በቀር ምርጥ ዘር የሚባል የለንም ።
ይህች ንጽሕት ዘር ወርቅ ነች ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከወደቁት ከአዳም እና ከሔዋን ዘሮች የተገች ዳግማዊት ሔዋን ብትሆንም የበደል ጥንት አልነካታም የመተላለፍ እድፍ አላጎደፋትም ስለዚህ በአዳም ገላ ውስጥ ታበራ የነበረች ነጭ እንቁ ነች።
ነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ “የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ዘርን_ባያስቀርልን_ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።” ብሎ የተናገረላት ከኃጢያት መተዳደፍ በመንጻት ከከፋት ሥራ ሁሉ ቀርታ ከጥፈት ያስቀረችን ምርጥ ዘራችን እመቤታችን ነች። ኢሳ 1፥9 ይህችሁም ንጽሕይት ዘር በወርኃ ክረምቱ ማዕከላዊ ጊዜ በሆነው በነሐሴ 7 (ሰባት)በዛሬዋ ቀን ከሐናና ከኢያቄም ተጸንሳልናለች ይህ ቀን የእመቤታችን ብቻ ሳይሆን እያገዳደለን ካለው የዘረኝነት ግዳይ ዓለማችንንና የሀገራችንን ትንሳኤ የምታደርግበት የድኅነታችን ጽንስ መጀመሪያም ቀን ነው።
በክረምት ወቅት የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ይሰጣሉ ታዲያ ይህ ጊዜ ለትጉህ ገበሬ ምቹ ነው በሬውን ይጠምዳል መሬቱን ያርሳል ዘሩን ይዘራል ዝናቡን በጉድጓድ ያጠራቅማል መባርቅቱን ፣ ነፋሳቱን ይታገሳል። በመጨረሻውም የድካሙን ፍሬ አዝመራውን ያጭዳል በመከራ እንዳልዘራ በደስታ ይሰበስባል " በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ ። በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ ። መዝ (125) 126 ÷5 ሰነፍ ገበሬ በአንጻሩ ብርዱን ቸነፈሩን ተሰቆ ቤቱ ይተኛል እገሌ ከኔ ወገን ነው ደግ ነው እገሊት ከወንዝ ማዶ ናት አትመስለንም ባለፈችበት እንዳታልፉ በዞረችበት አትዙሩ የሚል ነው የአጥንት እንጂ የእህል ዘር የማያውቅ :: ዘረኝነት ኃጢያት ነው ኃጢያት ደግሞ ማጣት ማለት ነው ባለ ብዙ ዘሮች ነን የሚሉ ዘረኞች ሃይማኖቱን፣ ምግባሩን ፣ ፖለቲካውን ፣ ሥልጣኑን ፣ ዕውቀቱን፣ ውበቱን ፣ ሙቀቱን ፣ድምቀቱን፣ ዝናውን ፣ተሰሚነቱን የያዙ ይመስላቸው ይሆናል ነገር ግን አንዱም እንኳ የላቸውም አጥተውታል። ሰው ኃጢያትን (ዘረኝነት) ዘርቶ እንዴት አንድነትን ሊያጭድ ይችላል ??? በእኩልነት ሰበብ በኩይ ከከፋፈሉን በኃላ በእንድነት ደግሞ እንምራቹ አሉን በአንድ ገመድ ሁሉንም ከብቶች አስሬ ልምራቸው የሚል እረኛ የለም ቢኖር ግን ይህ ምንደኛ እንጂ እረኛ አይደለም ምክንያቱም ከብቶቹን በአንድ ታስረው ወደ ሚፈልጉት የልማት ጉዳና የሥልጣኔ ማማ መድረስ አይቻላቸውምና። አንዱ ወድቆ ሊላውን የሚጠልፍበት የውድቀት ትርምስ ነው የሚሆንባቸው ። ከዛም አልፎ ከለመለመው መስክ ሳይሰማሩ በረፍትም ውኃ ዘንድ ሳይቀርቡ ከናፈቁት በረታቸውም ሳይገቡ የነጣቂ ተኩላ ሲሳይ የጅብ እራት ሆነው ይቀራሉ ። “ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ ”ምሳሌ 22፥8 " ማሰር መፍትኤ የሚሆነው ጠባቂ ከሌለ ብቻ ነው! " ። እረኛ ካለ ገመድ ለምኔ ?
........ ይቆየን.............
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 7 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጊዜው ክረምት ወቅቱም የዘር የመከር ወቅት በመሆኑ ዘርና ፍሬ ዝናብና ጠል ገበሬና በሬ ያለ መነጣጠል ይነሱበታል ። የክረምት ወቅት ምሳሌያዊ ትርጉም ዘርፈ ብዙ ነው ። አንዱ ና ዋናው ግን የ5500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ዘመን ፣ የመከራ ፣ የስቃይ ፣ የጨለማ ጊዜ ምሳሌ መሆኑ ነው :: ይኸውም ክረምት የ5ሺህ 500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው መባሉ በክረምት ጭጋግ ፣ ጉም ፣ደመና ይበረታሉ ነጎድጓዳት ይሰማሉ መባርቅት በርቀው ያስደነግጣሉ ይልቁኑ ደግሞ ውኃ ይሰለጥናል :: የክረምት ወቅት ሰቆቃ ይበዛዋል ይልቁኑ በስደት በደጅ ላሉ ሰውች ይብስባቸዋል “ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤”
የሚለው የጌታችን ምክርም የዚህን የክረምት ወቅት ጠንካራነት ያሳያል። ማቴ24፥20
የ5500ዘመንም ዘመነ ፍዳ ዘመነ መከራ ዘመነ ጨለማ ነውና በእግረ አጋንንት ተገዝተን በሲዖል እሳት ውስጥ ተግዘን ኖረናል ። በክረምት ውኃ እንዲሰለጥን በብሉይ ኪዳንም ውኃ ሰልጥኖ ፍጥረትን አጥፍቷል ገኃነመ እሳት በርትቷል በክረምት ምድር በውኃ እረክታ ትረሰርሳለች መሬት ትጨቀያለች በብሉይም ሰዎች በኃጢያት ዝናብ በስብሰው በሰዶም ግብር ጨቅይተው ነበር በዚህ ሰበብም ፈጣሪና ፍጡር ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ ተጣልተው ከርመዋል በመሆኑም ዘመነ ብሉይ (5500 ዘመን) ከአሰቃቂው የክረምት ወቅት ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል ። በመካከላቸውም የጠብ ግድግዳ ተገንብቶ ቆይቷል ቤተ ክርስቲያን በዚህ ወቅት ዘሪ ሊዘራ ወጣ እያለች የመንገድ ዳር፣ የጭንጫ ፣የሾህ ልቡና ያላቸውን ምዕመኖቿን ልብ በስብከተ መልካም መሬት አድርጋ በወንጌሏ ታቀናዋለች ቃል ዘርታ ሕይወት ታጭዳለች ።
ዛሬ ዛሬ ዓለማችን ነጭ ጥቁር ሀገራችን ደግሞ ኦሮሞ ትግሬ አማራ ጉራጌ በመባባል ተከፋፈለዋል። ሁሉም ዘሩ ምርጥ ዘር እንደሆነ ያስባል ሌላው ዘር ሁሉ እንክርዳድ የሚመስለው ነቀዝ ብዙ ነው ። ከሰዶምና ከጎሞራ ቅጣት የተረፍንባት ምርጥ ዘራችን ድንግል ማርያም ነች። ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችም መጀመራያ ብሎ እንደጠራት ትምክተ ዘመድነ የምትባል እመቤታችን ነች ። ከእርሷ በቀር ምርጥ ዘር የሚባል የለንም ።
ይህች ንጽሕት ዘር ወርቅ ነች ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከወደቁት ከአዳም እና ከሔዋን ዘሮች የተገች ዳግማዊት ሔዋን ብትሆንም የበደል ጥንት አልነካታም የመተላለፍ እድፍ አላጎደፋትም ስለዚህ በአዳም ገላ ውስጥ ታበራ የነበረች ነጭ እንቁ ነች።
ነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ “የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ዘርን_ባያስቀርልን_ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።” ብሎ የተናገረላት ከኃጢያት መተዳደፍ በመንጻት ከከፋት ሥራ ሁሉ ቀርታ ከጥፈት ያስቀረችን ምርጥ ዘራችን እመቤታችን ነች። ኢሳ 1፥9 ይህችሁም ንጽሕይት ዘር በወርኃ ክረምቱ ማዕከላዊ ጊዜ በሆነው በነሐሴ 7 (ሰባት)በዛሬዋ ቀን ከሐናና ከኢያቄም ተጸንሳልናለች ይህ ቀን የእመቤታችን ብቻ ሳይሆን እያገዳደለን ካለው የዘረኝነት ግዳይ ዓለማችንንና የሀገራችንን ትንሳኤ የምታደርግበት የድኅነታችን ጽንስ መጀመሪያም ቀን ነው።
በክረምት ወቅት የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ይሰጣሉ ታዲያ ይህ ጊዜ ለትጉህ ገበሬ ምቹ ነው በሬውን ይጠምዳል መሬቱን ያርሳል ዘሩን ይዘራል ዝናቡን በጉድጓድ ያጠራቅማል መባርቅቱን ፣ ነፋሳቱን ይታገሳል። በመጨረሻውም የድካሙን ፍሬ አዝመራውን ያጭዳል በመከራ እንዳልዘራ በደስታ ይሰበስባል " በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ ። በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ ። መዝ (125) 126 ÷5 ሰነፍ ገበሬ በአንጻሩ ብርዱን ቸነፈሩን ተሰቆ ቤቱ ይተኛል እገሌ ከኔ ወገን ነው ደግ ነው እገሊት ከወንዝ ማዶ ናት አትመስለንም ባለፈችበት እንዳታልፉ በዞረችበት አትዙሩ የሚል ነው የአጥንት እንጂ የእህል ዘር የማያውቅ :: ዘረኝነት ኃጢያት ነው ኃጢያት ደግሞ ማጣት ማለት ነው ባለ ብዙ ዘሮች ነን የሚሉ ዘረኞች ሃይማኖቱን፣ ምግባሩን ፣ ፖለቲካውን ፣ ሥልጣኑን ፣ ዕውቀቱን፣ ውበቱን ፣ ሙቀቱን ፣ድምቀቱን፣ ዝናውን ፣ተሰሚነቱን የያዙ ይመስላቸው ይሆናል ነገር ግን አንዱም እንኳ የላቸውም አጥተውታል። ሰው ኃጢያትን (ዘረኝነት) ዘርቶ እንዴት አንድነትን ሊያጭድ ይችላል ??? በእኩልነት ሰበብ በኩይ ከከፋፈሉን በኃላ በእንድነት ደግሞ እንምራቹ አሉን በአንድ ገመድ ሁሉንም ከብቶች አስሬ ልምራቸው የሚል እረኛ የለም ቢኖር ግን ይህ ምንደኛ እንጂ እረኛ አይደለም ምክንያቱም ከብቶቹን በአንድ ታስረው ወደ ሚፈልጉት የልማት ጉዳና የሥልጣኔ ማማ መድረስ አይቻላቸውምና። አንዱ ወድቆ ሊላውን የሚጠልፍበት የውድቀት ትርምስ ነው የሚሆንባቸው ። ከዛም አልፎ ከለመለመው መስክ ሳይሰማሩ በረፍትም ውኃ ዘንድ ሳይቀርቡ ከናፈቁት በረታቸውም ሳይገቡ የነጣቂ ተኩላ ሲሳይ የጅብ እራት ሆነው ይቀራሉ ። “ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ ”ምሳሌ 22፥8 " ማሰር መፍትኤ የሚሆነው ጠባቂ ከሌለ ብቻ ነው! " ። እረኛ ካለ ገመድ ለምኔ ?
........ ይቆየን.............
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 7 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ከአክራሪ እስልምና ወደ አፍቃሪ ክርስትና
የጥንቷ የከፋ መናገሻ የአሁና ጂማ ክርስትና ከተስፋፋባቸው የመካከለኛው ዘመን የስብከተ ወንጌል ዋና መዳረሻዎች ውስጥ አንዷ ናት ከጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ደቀመዛሙርት መካከል አባ ዮሴፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የወንጌልን ብርሃን ካበሩ አባቶቻችን አንደኛው ናቸው።
ጅማ የቀድሞዋ እናርያ ያለችው ቅድስት ቤተክርስቲያን በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራት አሁንም ያላት የኢትዮጵያ ግዛት ናት ዛሬ ዛሬ እነ ዋቢያ እነ ሰለፊያ እነ ሱኒዎች ወዘተ ባልኖሩበት ዘመን ቅድስት ቤተክርስቲያን በዚያ አካባቢ ያለውን ምዕመን ፈሪኃ እግዚአብሔር እንዲኖረው ለሺ ዓመታት ደክማበታለች እበሚያሳርፉባት መከራ በተለያየ ጊዜ ቅድስት ቤተክርስቲያን በጂማ አገረ ስብከት መከራ አሳልፋለች የዛሬው ታሪክም በጂማ ከተማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በተደጋጋሚ የቃጠሎ የማፍረስ እና ምዕመኗን የማንገላታት ሂደትም ውስጥ ከተሳተፉት አንዱ ቃሲም አባ ሁሴን ይገኝበታል (ስሙ የተቀየረ) ከቃሲም ጋር የተገናኘነው አዲስ አበባ ሲሆን ስለቅድስት ቤተክርስቲያን አንዳንድ ጉዳዮችን ከበቆጂ የተዋሕዶ ልጆች ጋር በማወራበት ስዓት ነበር ይሄን በሌላ ጊዜ አጫውታችዋለሁ ድንገት ቃሲም አንድ ቃል ወረወረ ጅማ ቤተክርስቲያን ሲቃጠል ግምባር ቀደም ሆኜ ሳቃጥል ነበር በማለት ወዲያው ትኩረቴን ሳበው የ2002 ረብሻው ሲነሳ በስራ አጋጣሚ እዛ ስለነበርኩ ጆሮዪን ሳበውና በደምብ ላወራው ፈለኩ ተቀጣጥረን ድምፁንም እንደምቀዳው ነገርኩት በዚህም ተስማምተን ተለያየን በቀጠሯችንም በሳምንቱ ተገናኘን።
ከመጀመርያ ጀምሮ ያለውን ታሪክና እንዲህ በማለት አጫወተኝ እኔ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ።
2000 ላይ ሁለት ጊዜ በረብሻው ተካፍያለሁ ቁራን የምንቀራበት የጅማው አኗር መስኪድ ኢመማ በማይክራፎን ሙስሊም አደጋ ላይነው አደጋውንም የሚያደርሱት ኦርቶዶክሶች ናቸው በማለት ቅስቀሳ አደረገ እኛም ተሰብስበን በመሄድ ቤተክርስቲያኗ ላይ ጥቃት አደረስን ትርምስ ሆነ በዚህ መልኩ በዚሁ ዓመት ሁለቴ ተሳትፊያለሆ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፍኩት 2002 ሲሆን እንደቀድሞው ተቀሰቀስን ለሊት ስድስት ሰዓት ላይ ቤተክርስቲያኗን ማቃጠል አለብን ብለን ተነስተን ሄድን እንደ ሌላው ጊዜ ግን አልሆነም ከአዕምሮ በላይ የሆነ ለዓይን የሚከብድ ብርሃን ሆነ እኔ ብቻ አይደለም ያየሁት ቤተክርስቲያኗን ለማጥቃት የሄድነው ሁላችንም አንድላይ ነው ያየነው አላዋክበር ሌላም ሌላም በማለት ተበታተንን ይሄ ቂያማ ነው እያልን ወደቤት የሚሄደው ወደ ቤት የተቀረው ወደ መስኪድ ተበተነ በነገራችን ላያ ቂያማ በእስልምናው የመጨረሻው ቀን እንደማለት ነው። ቃሲም ይቀጥላል ብቻዬን ቀረው በውስጤ ሁለቴ አልሞትም ከሞትኩ አንዴነው በማለት እዛው የሚሆነውን አየው የታየው ብርሃን ጠፋ ብርሃን የወረደበት ቦታው ላይም ጠበል ፈለቀ በሌላ ቀን በጠዋት ሲነጋጋ ሰብሰብ ብለን ለማጣራት ሄድን ቄሶቹ የፈለቀውን ጠበል ምዕመኑን እያጠመቁ ከምዕመናኑም መካከል ሲፈውሱ አየሁ እስላሙም እየተጠመቀ እየተፈወሰ ሲሄድ በአይኔ ተመለከትኩ ብርሃኑን ባየሁበት ቅጽበት ውስጤ በጥያቄና በመልስ ተሞልቶ ስለነበር እንዴት ሃይማኖት መግደል ይሰብካል፤ ኢሳ አልሞተም መሐመድ ሞቷል እንዴት የኢሳን ልደት አላከበርንም እንዴት ስለማርያም አያስተምሩንም የሚሉ ጥያቄዎች በአዕምሮዬ ተመላለሱ ወዲያው ነበር መስኪድ ቁራን ለሚያስቀራን ኢማም አስር ሆነን ጠየቅን ኢማሙም እናንተ ገና ናቹ በማለት ሳይመልስልን ቀረ እኛም ድጋሚ እንደዚህ አይነት ግጭት ውስጥ ከወንድሞቻችን ጋር አንገባም በማለት እራሳችንን አገለልን በወቅቱ ከፌደራል ታዞነው ተብሎ ክርስቲያኑ መስኪድ ኢስላሙ ደግሞ ቤተክርስቲያን እንድንሰራ ሆነ አስር የምንሆን ወጣቶች ከዛ ቡድን ተለየን እንደዚህ አይነት ብርሃን አይቼ አላውቅም ፈጣሪ ነው ይህን ተአምር የገለጠው በማለት ከአጥፊዎቹ መሃል ተለየ ፈጣሪ ክፉ ነገርን አያዝምና ።
ከጂማ እስከ አዲስ አበባ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቃሲም ይቀጥላል.........
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- መ/ር ማርቆስ አለማየሁ
ነሐሴ ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
የጥንቷ የከፋ መናገሻ የአሁና ጂማ ክርስትና ከተስፋፋባቸው የመካከለኛው ዘመን የስብከተ ወንጌል ዋና መዳረሻዎች ውስጥ አንዷ ናት ከጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ደቀመዛሙርት መካከል አባ ዮሴፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የወንጌልን ብርሃን ካበሩ አባቶቻችን አንደኛው ናቸው።
ጅማ የቀድሞዋ እናርያ ያለችው ቅድስት ቤተክርስቲያን በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራት አሁንም ያላት የኢትዮጵያ ግዛት ናት ዛሬ ዛሬ እነ ዋቢያ እነ ሰለፊያ እነ ሱኒዎች ወዘተ ባልኖሩበት ዘመን ቅድስት ቤተክርስቲያን በዚያ አካባቢ ያለውን ምዕመን ፈሪኃ እግዚአብሔር እንዲኖረው ለሺ ዓመታት ደክማበታለች እበሚያሳርፉባት መከራ በተለያየ ጊዜ ቅድስት ቤተክርስቲያን በጂማ አገረ ስብከት መከራ አሳልፋለች የዛሬው ታሪክም በጂማ ከተማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በተደጋጋሚ የቃጠሎ የማፍረስ እና ምዕመኗን የማንገላታት ሂደትም ውስጥ ከተሳተፉት አንዱ ቃሲም አባ ሁሴን ይገኝበታል (ስሙ የተቀየረ) ከቃሲም ጋር የተገናኘነው አዲስ አበባ ሲሆን ስለቅድስት ቤተክርስቲያን አንዳንድ ጉዳዮችን ከበቆጂ የተዋሕዶ ልጆች ጋር በማወራበት ስዓት ነበር ይሄን በሌላ ጊዜ አጫውታችዋለሁ ድንገት ቃሲም አንድ ቃል ወረወረ ጅማ ቤተክርስቲያን ሲቃጠል ግምባር ቀደም ሆኜ ሳቃጥል ነበር በማለት ወዲያው ትኩረቴን ሳበው የ2002 ረብሻው ሲነሳ በስራ አጋጣሚ እዛ ስለነበርኩ ጆሮዪን ሳበውና በደምብ ላወራው ፈለኩ ተቀጣጥረን ድምፁንም እንደምቀዳው ነገርኩት በዚህም ተስማምተን ተለያየን በቀጠሯችንም በሳምንቱ ተገናኘን።
ከመጀመርያ ጀምሮ ያለውን ታሪክና እንዲህ በማለት አጫወተኝ እኔ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ።
2000 ላይ ሁለት ጊዜ በረብሻው ተካፍያለሁ ቁራን የምንቀራበት የጅማው አኗር መስኪድ ኢመማ በማይክራፎን ሙስሊም አደጋ ላይነው አደጋውንም የሚያደርሱት ኦርቶዶክሶች ናቸው በማለት ቅስቀሳ አደረገ እኛም ተሰብስበን በመሄድ ቤተክርስቲያኗ ላይ ጥቃት አደረስን ትርምስ ሆነ በዚህ መልኩ በዚሁ ዓመት ሁለቴ ተሳትፊያለሆ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፍኩት 2002 ሲሆን እንደቀድሞው ተቀሰቀስን ለሊት ስድስት ሰዓት ላይ ቤተክርስቲያኗን ማቃጠል አለብን ብለን ተነስተን ሄድን እንደ ሌላው ጊዜ ግን አልሆነም ከአዕምሮ በላይ የሆነ ለዓይን የሚከብድ ብርሃን ሆነ እኔ ብቻ አይደለም ያየሁት ቤተክርስቲያኗን ለማጥቃት የሄድነው ሁላችንም አንድላይ ነው ያየነው አላዋክበር ሌላም ሌላም በማለት ተበታተንን ይሄ ቂያማ ነው እያልን ወደቤት የሚሄደው ወደ ቤት የተቀረው ወደ መስኪድ ተበተነ በነገራችን ላያ ቂያማ በእስልምናው የመጨረሻው ቀን እንደማለት ነው። ቃሲም ይቀጥላል ብቻዬን ቀረው በውስጤ ሁለቴ አልሞትም ከሞትኩ አንዴነው በማለት እዛው የሚሆነውን አየው የታየው ብርሃን ጠፋ ብርሃን የወረደበት ቦታው ላይም ጠበል ፈለቀ በሌላ ቀን በጠዋት ሲነጋጋ ሰብሰብ ብለን ለማጣራት ሄድን ቄሶቹ የፈለቀውን ጠበል ምዕመኑን እያጠመቁ ከምዕመናኑም መካከል ሲፈውሱ አየሁ እስላሙም እየተጠመቀ እየተፈወሰ ሲሄድ በአይኔ ተመለከትኩ ብርሃኑን ባየሁበት ቅጽበት ውስጤ በጥያቄና በመልስ ተሞልቶ ስለነበር እንዴት ሃይማኖት መግደል ይሰብካል፤ ኢሳ አልሞተም መሐመድ ሞቷል እንዴት የኢሳን ልደት አላከበርንም እንዴት ስለማርያም አያስተምሩንም የሚሉ ጥያቄዎች በአዕምሮዬ ተመላለሱ ወዲያው ነበር መስኪድ ቁራን ለሚያስቀራን ኢማም አስር ሆነን ጠየቅን ኢማሙም እናንተ ገና ናቹ በማለት ሳይመልስልን ቀረ እኛም ድጋሚ እንደዚህ አይነት ግጭት ውስጥ ከወንድሞቻችን ጋር አንገባም በማለት እራሳችንን አገለልን በወቅቱ ከፌደራል ታዞነው ተብሎ ክርስቲያኑ መስኪድ ኢስላሙ ደግሞ ቤተክርስቲያን እንድንሰራ ሆነ አስር የምንሆን ወጣቶች ከዛ ቡድን ተለየን እንደዚህ አይነት ብርሃን አይቼ አላውቅም ፈጣሪ ነው ይህን ተአምር የገለጠው በማለት ከአጥፊዎቹ መሃል ተለየ ፈጣሪ ክፉ ነገርን አያዝምና ።
ከጂማ እስከ አዲስ አበባ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቃሲም ይቀጥላል.........
@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- መ/ር ማርቆስ አለማየሁ
ነሐሴ ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ሱባዔ
ሱባዔ በሰዋሰው ትርጉሙ ቆየ ሰነበተ ዘገየ ሰባት ማለት ሲሆን ምሥጢራዊ ትርጓሜውም ደግሞ አንድ ሰው ከዚህ ቀን እከዚህ ቀን ድረስ ፈጣሪዬን በጸሎት እገናኛለሁብሎ የሚያቅደው ዕቅድ ነው። ሰባት ቁጥር በእስራኤላዊያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር አረፈ እንዲል በጸሎት የሚተጉ ምዕመናንም በቀን ሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል ። ሱባዔ የተጀመረው ከመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት በኋላ ነው ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዴት እንደሚጸለይ እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ። ለአዳምም የጸሎት ጊዜያትን አስተምረውት አስተምረውት ነበርና ጥፈቱን አምኖ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔርም በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት ።
ሱባዔ ለምንምክንያት እንገባልን ቢሉ የመጀመሪያው የሚሆነው የሰው ልጅ በባህሪው ኃጢአት የሚስማማው ነው በሥጋ ሰውነቱ ፈጣሪን ይበድላል በፈጸመው በደል / ኃጢአት/ ሕሊናው ይወቅሰዋል በዚህም ያዝናል ይጸጸታል በሰራው ኃጢአትም ልቡ ይደነግጣል በዚህ ጊዜ የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት ሲል ሲል ሱባዔ ይገባል ።እግዚአብሔርን ለመማፀን የሚገባ ሱባዔ አለ ። ማንኛውም ሰው ሱባዔ በገባ ቁጥር ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማጽኖ ሊኖረው ይገባል ምንም የምንለምነውና የምንጠይቀው ነገር ሳይኖር ሰባዔውን ብንገባ የምናገኘው ምንም አይነት መልስ አይኖርም
ስለዚህ ተማፅኖ ሊኖረን ይገባል ። ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔው በኋላ ምን እንደተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖራቸው ሱባዔ በመግባታቸው የሚገኙት ነገር አይኖርም ይህን ተገንዝበው ከመግባታቸው በፊት የሚገቡበትን ምክንያት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው ። ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶቻችን ደማቸውን ካፈሰሱበት አጥንታቸውን ከከሰከሱበት ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራት የሰሩበት ቦታ ገዳማቸውና አድባራት ላይ የሚገባ ሱባዔ ከቅዱሳኑ ረድኤት ተካፋይ ይደርጋል ። ሱባዔ የተደበቀን ምሥጢር የሚገለጥበት ቁልፍ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው ቅዱሳን አባቶቻችን ያዩት እራይ ምሥጢሩና ትርጉሙ አልገለጥ ሲላቸው ሱባዔ ይገቡ ነበር እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነ ነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢሩንና ትርጉሙን ይገልጥላቸዋል ። ነቢዬ ዕዝራ የመጽሐፍታት ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ገባ እግዚአብሔር አምላክም ሁሉን ገለጸለት የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍታት ደግሞ ለመጻፍ ችሏል ይህ ምሥጢር የተገለጠለት በሱባዔ ነው ።
ከብሉይ ጀምሮ ያሉ የሱባዔ አባቶቻችን የገቡት ሱባዔ ሱባዔ አዳም ፣ ሱባዔ ሔኖክ ሱባዔ ነብያት
፣ሱባዔ ዳንኤል ሱባዔ ዳዊት በተጨማሪም የግል ሱባዔ የማኀበር ሱባዔ የአዋጅ ሱባዔ በመባል ይታወቃሉ በሐዲስ ኪዳን ከአራት ቀን በኋላ የምገባ ሐዋርያት የገቡት ሱባዔ ነው የፍልሰታ ሱባዔ በዚህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ የተገኘበት ትንሣኤዋ እንዲገለጥላቸው የተገባ ሱባዔ ነው ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን 14 ቀን ያክል በጻም በጸሎት ተማጽነው ትንሣኤዋን ገለጠችላቸው ። እንግዲህ ሱባዔ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ወቅቱ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ስባዔ እንደ መሆኑ መጠን እኛም የሐዋርያቱን ፈለግ በመከተል በንጹሕ ልቦና በትሁት መንፈስ ሆነን የእናታችን ትንሣኤ ይገለጥልን ዘንድ በሱባዔው እንትጋ ። ለሐዋርያቱ በሙሉ የልባቸውን መሻት የፈጸመች የጌታችን እናት ድንግል ማርያም የእኛንም የልባችንን ትፈጽምልናለች። ወቅቱን የጾም፣የጸሎት፣የስግደት፣ የምጽዋት፣ ስለ ሀገራችን ኢትዮጲያ የምናለቅስበት ነው ። ስለዚህ ሁላችን በሱባዔው እንበርታ
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥42
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
.....ይቆየን.......
ምንጭ :-እናት ማህበሬ ምክሐ ደናግል ሰሌዴ መጽሔት ሐምሌ ና ነሀሴ2010ዓ.ም የተለጠፈ
ሱባዔ በሰዋሰው ትርጉሙ ቆየ ሰነበተ ዘገየ ሰባት ማለት ሲሆን ምሥጢራዊ ትርጓሜውም ደግሞ አንድ ሰው ከዚህ ቀን እከዚህ ቀን ድረስ ፈጣሪዬን በጸሎት እገናኛለሁብሎ የሚያቅደው ዕቅድ ነው። ሰባት ቁጥር በእስራኤላዊያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር አረፈ እንዲል በጸሎት የሚተጉ ምዕመናንም በቀን ሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል ። ሱባዔ የተጀመረው ከመጀመሪያው ሰው አዳም ውድቀት በኋላ ነው ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዴት እንደሚጸለይ እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ። ለአዳምም የጸሎት ጊዜያትን አስተምረውት አስተምረውት ነበርና ጥፈቱን አምኖ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔርም በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት ።
ሱባዔ ለምንምክንያት እንገባልን ቢሉ የመጀመሪያው የሚሆነው የሰው ልጅ በባህሪው ኃጢአት የሚስማማው ነው በሥጋ ሰውነቱ ፈጣሪን ይበድላል በፈጸመው በደል / ኃጢአት/ ሕሊናው ይወቅሰዋል በዚህም ያዝናል ይጸጸታል በሰራው ኃጢአትም ልቡ ይደነግጣል በዚህ ጊዜ የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት ሲል ሲል ሱባዔ ይገባል ።እግዚአብሔርን ለመማፀን የሚገባ ሱባዔ አለ ። ማንኛውም ሰው ሱባዔ በገባ ቁጥር ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማጽኖ ሊኖረው ይገባል ምንም የምንለምነውና የምንጠይቀው ነገር ሳይኖር ሰባዔውን ብንገባ የምናገኘው ምንም አይነት መልስ አይኖርም
ስለዚህ ተማፅኖ ሊኖረን ይገባል ። ያለ ምንም ቅድመ ሆኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔው በኋላ ምን እንደተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖራቸው ሱባዔ በመግባታቸው የሚገኙት ነገር አይኖርም ይህን ተገንዝበው ከመግባታቸው በፊት የሚገቡበትን ምክንያት ራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው ። ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶቻችን ደማቸውን ካፈሰሱበት አጥንታቸውን ከከሰከሱበት ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተአምራት የሰሩበት ቦታ ገዳማቸውና አድባራት ላይ የሚገባ ሱባዔ ከቅዱሳኑ ረድኤት ተካፋይ ይደርጋል ። ሱባዔ የተደበቀን ምሥጢር የሚገለጥበት ቁልፍ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው ቅዱሳን አባቶቻችን ያዩት እራይ ምሥጢሩና ትርጉሙ አልገለጥ ሲላቸው ሱባዔ ይገቡ ነበር እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነ ነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢሩንና ትርጉሙን ይገልጥላቸዋል ። ነቢዬ ዕዝራ የመጽሐፍታት ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ገባ እግዚአብሔር አምላክም ሁሉን ገለጸለት የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍታት ደግሞ ለመጻፍ ችሏል ይህ ምሥጢር የተገለጠለት በሱባዔ ነው ።
ከብሉይ ጀምሮ ያሉ የሱባዔ አባቶቻችን የገቡት ሱባዔ ሱባዔ አዳም ፣ ሱባዔ ሔኖክ ሱባዔ ነብያት
፣ሱባዔ ዳንኤል ሱባዔ ዳዊት በተጨማሪም የግል ሱባዔ የማኀበር ሱባዔ የአዋጅ ሱባዔ በመባል ይታወቃሉ በሐዲስ ኪዳን ከአራት ቀን በኋላ የምገባ ሐዋርያት የገቡት ሱባዔ ነው የፍልሰታ ሱባዔ በዚህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ሥጋ የተገኘበት ትንሣኤዋ እንዲገለጥላቸው የተገባ ሱባዔ ነው ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን 14 ቀን ያክል በጻም በጸሎት ተማጽነው ትንሣኤዋን ገለጠችላቸው ። እንግዲህ ሱባዔ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል ወቅቱ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የፍልሰታ ስባዔ እንደ መሆኑ መጠን እኛም የሐዋርያቱን ፈለግ በመከተል በንጹሕ ልቦና በትሁት መንፈስ ሆነን የእናታችን ትንሣኤ ይገለጥልን ዘንድ በሱባዔው እንትጋ ። ለሐዋርያቱ በሙሉ የልባቸውን መሻት የፈጸመች የጌታችን እናት ድንግል ማርያም የእኛንም የልባችንን ትፈጽምልናለች። ወቅቱን የጾም፣የጸሎት፣የስግደት፣ የምጽዋት፣ ስለ ሀገራችን ኢትዮጲያ የምናለቅስበት ነው ። ስለዚህ ሁላችን በሱባዔው እንበርታ
“በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥42
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
.....ይቆየን.......
ምንጭ :-እናት ማህበሬ ምክሐ ደናግል ሰሌዴ መጽሔት ሐምሌ ና ነሀሴ2010ዓ.ም የተለጠፈ
እሾህ #የሌለባት_ጽጌ_ሬዳ
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ጊዜው የአበባና የፍሬ ጊዜ ነው ቤተክርስቲያንም ዘመነ ጽጌ ወርሃ ጽጌ ብላ ስለ ጽጌያት ታስተምራለች:: #ከመስከረም 26 እስከ #ህዳር 6 ቀን ያሉት ተከታታይ 40 ቀናት ናቸው ስለ ጽጌ ወይም ስለ አበባ የምታስተምረው ትምህርት ይህ እኛ የምናውቀውን በአፈር፣ በውኃና በፀሐይ ብርሃን አማካኝነት የሚያድገውን የእጽዋት አይነት ብቻ የሚመለከት አይደለም። ከዛ ይልቅ አማናዊት አበባ ስለምትባል ስለ ድንግል ማርያም በዚህ ወቅት በምልዐት ታስተምራለች ትሰብካለች:: እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እውነተኛ አበባ ነች።
እንደ ሳይንሱ ገለጻ አንድ እጽዋት እጽዋት ለመሰኘት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ሊያሞላ ይገባል ይላል። እነርሱም እውነተኛ ሥር እውነተኛ ግንድ እውነተኛ ቅርንጫፍ ናቸው ። እነዚህ እጽዋት በሥሮቻቸው አማካኝነት ከአፈር ውስጥ ውኃና ሚኒራልን በመውሰድ ከቅርንጫፍቻቸው ካሉ ቅጠሎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን በማምጣት በግንዶቻቸው አጓጓዠነት በመጠቀም ፖቶሰቴንስስ በተባለ ሂደት ምግቦቻቸውን ማዘጋጀት ይችላሉ ።እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የሌላቸውን አረንጓዴ ተክሎች ግን አልጋይ እና ፈንጋይ እየተባሉ ይጠራሉ እውነተኛ ሥር ግንድና ቅርንጫፍ የላቸውምና ምግባቸውን ማዘጋጀት አይችሉም ስለዚህ እጽዋት ተብለው አይጠሩም ::
#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ታዲያ ከእውነተኛም እውነተኛ የሆነች ( እጸ ሕይወት) እውነተኛ የሕይወት አበባ ነች መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች እውነተኛ የወይን ግንድ አብቃይ ቅርንጫፎቿም በሰማያተ የሚገኑ አረገ ወይን ነች:: (ሥር) መዝ 86÷1 (ግንድ)ኢሳ11÷1 (ቅርንጫፍ)ዮሐ 15÷5 ።
የሕይወት መብል መጠጥ የሆነ ክርስቶስን የወለደችልን ድንግል ማርያም እውነተኛ ሥር ግንድና ቅጠል ያላት እውነተኛ አበባ መሆኖን አሰረግጦ መናገር የተገባ ነው። ለምን ቢሉ
አንዳንድ ዲያቢሎስ ያደረባቸው ደፋር ሴቶች በዘመኑ ብኖር እኔም ክርስቶስን እወልደው ነበር ብለው የድንግልን ክብር ከእራሳቸው ክብር ጋር በትቢት ባልተገባ የሚያስተካክሉ ልካቸውን ማሳወቅ ስለሚገባ ነው በእስራኤል ያሉ ሴቶች ደግሞ ዛሬ ድረስ ክርስቶስ አልተወለደም ወደፊት ከአንዳችን ይወለዳል ብለው በድፍረት በከንቱ ይጠባበቃሉ በእውነት ግን እነዚህ ሴቶች እንኳን የሕይወት መብልና መጠጥ የሆነውን ክርስቶስን ሊወልዱ ቀርቶ ሊወልዱት የሚችሉትል ተራ ሰው እንኳ በአግባቡ ስለመመገባቸው እርግጠኞች አይደሉም ስለዚህም ምግባቸውን እንኳን ማዘጋጀት እንደ ማይችሉ አልጋይና ፋንጋይ ናቸው ማለት ይቻላል። እውነተኞች አይደሉምና ።
#እርሷ_እመቤታችን እንኳን ስለራሷ በትንቢት የተጻፈውን ባነበበች ጊዜ ከዚህች ቅድስት ሴት ከዘመኗ ደርሼ ውኃ ቀድቼ እንጨት ፈልጬ ገረዷ ሆኜ ባገለገልኳት ብላ በትህትና ገረድነትን ተመኘች እንጂ እኔ በሆኩ አላለችም ጊዜው ደርሶም መላእኩ ገብርኤል መጥቶ አምላክን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል ብሎ የመውለዷን ዜና ሲያበሥራት እንኳ ይህ እንዴት ይሆንልኛል እኔ #የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ አለችሁ እንጂ ከወነማ ከመጣህማ ብላ በኩራት ሆና አልተናገረችሁም .....ይህ እንዴት ያለህ ትህትና ነው? የአምላክ እናቱ ነሽ እየተባሉ እራስን ገረድ ማለት! ሊቁም ይህ ትህትና ቢገርመው ልዕልናዋን ከትህትናዋ አስማምቶ " #በትህትና_የተናገርሽ ተራራ ሆይ " ብሎ ጠራት::
እውነተኛይቱ አበባ ግን አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር በተዘክሮተ ፈጣሪ ዋላም ዓለም ከተፈጠረ በኃላ በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በደቂቀ አዳም ልብ የነበረች፣ ያለችና ፣የምትኖር የማደርቅና የማጠወልግ እንቡጥ አበባ ነች።
#አበባ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የአፍንጫ መዐዛ ነው እመቤታችንም አስቀድማ ለእናት ለአባትዋ በኃላም ለደቂቀ አዳም ሁሉ የዓይን ማረፊያ የልብ ተስፋ የነፍስ መዐዛ ነች " #ከዕሴይ_ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ " እንዳለ ሊቁ #ውዳሴ_ማርያም ዘእሁድ ኢሳ11÷1
#አበባ መድኃኒትን ያስገኛል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም መዳኒ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች እስለዚህ " እሙ ለመዳኒት" የመዳኒት እናት ትባላለችና አባባ ነች ሉቃ 2÷10-11
አበባ ንብቦችን ይስባል ማርን ያሰራል እውነተኛይቱ አበባ እመቤታችንም ወልድ ክርስቶስን ስባለች ማር የሆነች የወንጌል ሕግን አሰርታለች። ማር ጥዑም ነው ክርስቶስና ወንጌልም ጥዑማን ናቸው አንድም ማር መድኃኒት ነው ክርስቶስ እና ወንጌልም መድኃኒት ናቸው::"ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል" መዝ 86(87)÷2
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና" መዝ 44(45)÷10-11
አበባ ምግበ ሥጋን ያስገኛል (ለምሳሌ አበባ ጎመን የመሰሉ ተክሎች ወዘተ...) እውነተኛይቱ አባ እመቤታችንም ምግበ ሥጋወነፍስ የሆነ ክርቶስን አስገኝታለች ዮሐ 6÷56 ማቴ 26÷26
"በመኑ ወበ አምሳለ መኑ ናስተማስለኪ " እንዳሉ ሊቃውንት ድንግል ሆይ በምንና በማን እንመስልሻለን ክብርሽን የሚገልጥ ነገር አጣን ብለን በተደሞ ዝም እንበል እንጂ እመቤታችንንስ አበባ ብቻ የሚገልጣት ሆኖ አይደለም።
እንዴት? ቢሉ አበባ ከምድር ተገኝቶ በምድር ይቀራል አበባይቱ እመቤታች ግን ከምድር ብትገኝም ቅሉ የማትደርቅ የማትጠወልግ ምድራዊት ወ ሰማያዊት የሆነች ለምለም አበባ ነች።
አበባ ይልቁኑ ጽጌ ሬዳ በእህሾ የተከበበ ነው ። አበባይቱ እመቤታችን ግን የጥንተ አብሶ እሾህ ያልከበባት ንፁህ ጽጌ ሬዳ ናት። ወርቅ ከመሬት ከጭቃ ይገኛል ነገር ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም ከምድር የተገኘች ሆና ሳለ ግን ምድራዊ በደል ያላቆሸሻት እሾህ አልባ የወርቅ አበባ ነች ለይቶ ቀድሷታልና “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።” መዝ45(46)፥4
አበባ መድኃኒት ቢያስገኝ ከጊዜያዊ ሕመም የሚያድን ጊዜያዊ መድኃኒት ነው የሚያስገኘው አበባይቱ እመቤታችን ግን አንዴ ከተበላ አንዴ ከተጠጣ ዳግመኛ የማያስፈልገውን ዘላለማዊ ፍቱን መድኃኒትን ያስገኘች ሕያው አበባ ነች።
አንድ ንጥል አበባ ዘሩን የሚተካው ወንዴና ሴቴ የተባሉ ክፍሎቹን በመጠቀም ነው የወንዴው ብናኝ ጊዜውን ጠብቆ እራሱን ሲያበን ማጣበቅ የሚችለው የሴቴ ክፍል ብናኙን ይቀበልና ሌሎች አበቦችን ማፍራት ይጀምራል ። ይህ ሂደት ኢ ተሻጋሪ(እዛው በዛው) የማፍራት ሂደት ይባላል ። በሌላ በኩል ደግሞ የአንዱ ንጥል አበባ የወንዴ ብናኝ በንቦች ፣በወፎች፣ እንዲሁም በሰዎች ንኪኪ ወይም በንፋስ ሽውታ አማካኝነት በኖ ከራሱ የሴቴ ብናኝ ተቀባይ ውጪ ተሻግሮ በሌላ አበባ የሴቴ ክፍል ላይ በመጣበቅ የሚያፈራበትም መንገድ አለ ይህም ተሻጋሪ የአረባብ ዘዴ በመባል ይታወቃል ።
አበባ እንዲ ባለ መልክ ሲያብብ አማናዊቷ አበባ እመቤታችን ግን ያለ ዘርዐ ብዕሲ ያለ ወንድ ዘር ) በ ግብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ ጸንሳ መውለድ ችላለች ስለዚህ በእጅጉ ከአበባዎች ሁሉ ትበልጣለች አልን።
"ሳይተክሏትና ውኃ ሳያጠጧት የለመለመች የአሮን በትር ነበረች #አንቺ_እንደ_እርሷ_ነሽ #ውዳሴ_ማርያም_ዘእሁድ
.......ይቆየን ............
ምልጃ ቃልኪዳኗ ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያኖች ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር ...አሜን!
ኃ/ ማርያም
ጥቅምት 1/2013 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጲያ
👇👇👇👇👇👇👇
#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit