#ራሳችንን #የምናይበት #አስገራሚ #ታሪክ
አንዲት ወጣት ሴት ለጉዞ ኤርፖርት ውስጥ ተቀምጣለች አውሮፕላኑ እንደሚዘገይ ባወቀች ጊዜ ኤርፓርት ውስጥ ካሉት ሱቆች ኩኪስና
መጽሐፍ ገዛች።ወደ VIP (የተመረጡ ሰዎች) ብቻ ወደ የሚስተናገዱበት ክፍል ገብታ ለንባብ ምቹ ወደ ሆነው መደገፊያ ወንበር አመራች
ተደላድላ ተቀምጣ ማንበብ ጀመረች አጠገቧ እንድ ሰው መጽሐፍ ያነባል
በሁለት መደገፊያ ወንበሮች መሐል ኩኪስ ተቀምጧል በንባቧ መካከል መተከዢያ ሆኗታል ታዲያ ከኩኪሷ አንድ ስታነሳ ሰውየውም አንድ አነሳ ገረማት ሳያስፈቅዳት መውሰዱ
አስደነቃት ግን ዝም አለች
ቀጥላ እርሷ አንድ ስትወስድ እርሱም ሌላ
ወሰደ አሁን ተበሳጨች። ድፍረቱ አናደዳት።
በዚህ አላበቃም እስከ መጨረሻው ቀጠለ።
ቅጥል አለች! ግን ንቃ ተወችው።
በአካባቢው ያሉ ሰዎችን አትኩሮት መሳብ
አልፈለገችም። ለዚህ ብቻ አይደለም በኩኪስ
ምክንያት ጸብ ረብሻ መፍጠር
አልፈለገችም።እንዲህ እንዲህ እያለ
የመጨረሻ አንድ ኩኪስ ቀረች። " ይሄ
የተረገመሰው ምን ያደርግ ይሆን? " ስትል
አሰበችና በቀስታ ማየት ጀመረች። ከዚያም
ሰውየው ኩኪሷን ሁለት ቦታ ከፈላትና ግማሹን
ወሰደ። ለድፍረቱ ጥግ አጣችለት። ከልክ ያለፈ
ስርዓት የለሽ እንደሆነ ደመደመች።ሰዓቱ
ደርሶ አውሮፕላን ላይ እንደተሳፈረች መነጽር
ለማውጣት ቦርሳዋን ስትከፍት አይኗን
ማመን አልቻለችም። ያልተከፈተው
የታሸገው ኩኪሷ ቦርሳዋ ውስጥ አለ። በጣም
አፈረች ተሸማቀቀች። ለካስ የራስዋን ኩኪስ
ቦርሳዋ ውስጥ ረስታ የሰውየውን ነበር
ስትበላ የቆየችው። ከሁሉም በላይ በጣም
ያጸጸታት ሰውየው እስከ መጨረሻው አንዲት
ኩኪስ እስክትቀር ድረስ ያካፍላት የነበረው
ምንም ሳይቆጣና ሳይመረር በደስታ መሆኑ
ነበር።የራሱን ኩኪስ እየበላች በሰውየው ላይ
ስትበሳጭበት በመቆየቷ እጅግ አፈረች።
አሁን ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳን ጊዜው
አልፏል። እርሱም በሌላ አውሮፕላን ወደ
ሐገሩ አቅንቷል። እርሱን የማግኘት አንድ
ተጨማሪ እድል እንኳን የላትም። ብዙ ተመኘች ማመስገን፣ ይቅርታ መጠየቅ፣ ጉዳዩን ማብራራት፣ .....ግን ሁሉም እሷው ጋር ቀሩ አልፏል።
#አራት #የማይጠገኑ #ነገሮችን #አሰበች
👉 ድንጋይ ከተወረወረ በኋላ
👉 ቃላት ከተናገርናቸው በኋላ
👉ድርጊቶች ካመለጡን በኋላ
👉ጊዜ ካለፈ በኋላዋጋ እንደሌለው እኛም
ምንም ነገር ከመናገራችን ከመፈፀማችን
በፊት መጀመሪያ ራሳችንን እንይ
ዛሬ ልናመሰግናቸው ዋጋ ልንሰጣቸው
ልናከብራቸው የሚገባን ወዳጆቻችን የትዳር
አጋሮቻችንን ጀግኖቻችን ጊዜው ሳያልፍ
እናመስግናቸው።
#መልካም #ቀን
አንዲት ወጣት ሴት ለጉዞ ኤርፖርት ውስጥ ተቀምጣለች አውሮፕላኑ እንደሚዘገይ ባወቀች ጊዜ ኤርፓርት ውስጥ ካሉት ሱቆች ኩኪስና
መጽሐፍ ገዛች።ወደ VIP (የተመረጡ ሰዎች) ብቻ ወደ የሚስተናገዱበት ክፍል ገብታ ለንባብ ምቹ ወደ ሆነው መደገፊያ ወንበር አመራች
ተደላድላ ተቀምጣ ማንበብ ጀመረች አጠገቧ እንድ ሰው መጽሐፍ ያነባል
በሁለት መደገፊያ ወንበሮች መሐል ኩኪስ ተቀምጧል በንባቧ መካከል መተከዢያ ሆኗታል ታዲያ ከኩኪሷ አንድ ስታነሳ ሰውየውም አንድ አነሳ ገረማት ሳያስፈቅዳት መውሰዱ
አስደነቃት ግን ዝም አለች
ቀጥላ እርሷ አንድ ስትወስድ እርሱም ሌላ
ወሰደ አሁን ተበሳጨች። ድፍረቱ አናደዳት።
በዚህ አላበቃም እስከ መጨረሻው ቀጠለ።
ቅጥል አለች! ግን ንቃ ተወችው።
በአካባቢው ያሉ ሰዎችን አትኩሮት መሳብ
አልፈለገችም። ለዚህ ብቻ አይደለም በኩኪስ
ምክንያት ጸብ ረብሻ መፍጠር
አልፈለገችም።እንዲህ እንዲህ እያለ
የመጨረሻ አንድ ኩኪስ ቀረች። " ይሄ
የተረገመሰው ምን ያደርግ ይሆን? " ስትል
አሰበችና በቀስታ ማየት ጀመረች። ከዚያም
ሰውየው ኩኪሷን ሁለት ቦታ ከፈላትና ግማሹን
ወሰደ። ለድፍረቱ ጥግ አጣችለት። ከልክ ያለፈ
ስርዓት የለሽ እንደሆነ ደመደመች።ሰዓቱ
ደርሶ አውሮፕላን ላይ እንደተሳፈረች መነጽር
ለማውጣት ቦርሳዋን ስትከፍት አይኗን
ማመን አልቻለችም። ያልተከፈተው
የታሸገው ኩኪሷ ቦርሳዋ ውስጥ አለ። በጣም
አፈረች ተሸማቀቀች። ለካስ የራስዋን ኩኪስ
ቦርሳዋ ውስጥ ረስታ የሰውየውን ነበር
ስትበላ የቆየችው። ከሁሉም በላይ በጣም
ያጸጸታት ሰውየው እስከ መጨረሻው አንዲት
ኩኪስ እስክትቀር ድረስ ያካፍላት የነበረው
ምንም ሳይቆጣና ሳይመረር በደስታ መሆኑ
ነበር።የራሱን ኩኪስ እየበላች በሰውየው ላይ
ስትበሳጭበት በመቆየቷ እጅግ አፈረች።
አሁን ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳን ጊዜው
አልፏል። እርሱም በሌላ አውሮፕላን ወደ
ሐገሩ አቅንቷል። እርሱን የማግኘት አንድ
ተጨማሪ እድል እንኳን የላትም። ብዙ ተመኘች ማመስገን፣ ይቅርታ መጠየቅ፣ ጉዳዩን ማብራራት፣ .....ግን ሁሉም እሷው ጋር ቀሩ አልፏል።
#አራት #የማይጠገኑ #ነገሮችን #አሰበች
👉 ድንጋይ ከተወረወረ በኋላ
👉 ቃላት ከተናገርናቸው በኋላ
👉ድርጊቶች ካመለጡን በኋላ
👉ጊዜ ካለፈ በኋላዋጋ እንደሌለው እኛም
ምንም ነገር ከመናገራችን ከመፈፀማችን
በፊት መጀመሪያ ራሳችንን እንይ
ዛሬ ልናመሰግናቸው ዋጋ ልንሰጣቸው
ልናከብራቸው የሚገባን ወዳጆቻችን የትዳር
አጋሮቻችንን ጀግኖቻችን ጊዜው ሳያልፍ
እናመስግናቸው።
#መልካም #ቀን
👍3❤1
ጓደኛ ነው:: አብርሃም ነው፡፡
ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡
ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡
“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::
“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡
ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡
ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡
ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…
የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡
#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡
#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡
#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡
#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡
#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡
ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....
💫ይቀጥላል💫
ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡
ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡
“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::
“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡
ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡
ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡
ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…
የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡
#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡
#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡
#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡
#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡
#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡
ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....
💫ይቀጥላል💫
👍2
#ቀስ_ብሎ_ይቆማል
፡
፡
#አራት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
..."እ..ጎረምሳው መቼ ጀመረህ?” አለኝ። (በቃ ምርመራ ተጀመረ ማለት ነው ?) ሰውዬውን ትኩረት
ስመለከተው ለካስ ዓይኑ ልክ አይደለም፤ ትንሽ ሸውረር ያለ ነው። ታዲያ መጽሔት ላይ ከየት አባቱ ያመጣውን ፎቶ ነው የለጠፈው ?..
“መቼ እንደ ጀመረኝ አላወቅኩም ድንገት ከፍቅረኛዬ ጋር…"
"እ … ድንገት ከፍቅረኛህ ጋር ዓለምሆን ልትቀጭ … ሱሪህን አውልቀህ .… ቡታንታህን አውልቀህ በልስትለው…. ባባቴም የለ ብሎ ድፍት፣ ቅዝቅዝ አለብህ … እ? አዋራጅ እኮ ነው!አዋራጅ! ስንቱ በዚህ ዓይነት አጉል ጊዜ በሴት ፊት መዋረዱ አሸማቅቆት ገመዱን ቋጥሮ ራሱን ሲጥ አድርጓል መሰለህ ! እኔ እንኳን ሁለት ምን የመሳሰሉ ልጆች በዚሁ ጠንቅ ታንቀው የሞቱ አውቃለሁ አንዱ እንኳን መርዝ ጠጥቶ ነው … ያው ነው!ቀላል ነገር እንዳይመስላችሁ፡ ሴቶቹ ደሞ ይችን ወሬ ካገኙ እየዞሩ ለሁሉ
ነው የሚያወሩት“ አለ ከአፌ ላይ ነጥቆ። ይሄ ሰውዬ እንዴት ነው የሚቀባጥረው በእግዚአብሔር
በአንድ ጊዜ መንፈሴንም አኮላሸው እኮ።
እና.እንዴት ነው ትንሽም አይላወስ፣ ወይስ ጀማምሮ መሃል ላይ ወገቤን ነው የሚለው ሲል
ጠየቀኝ።
"ምኑ ?” ብዬ ጠየቅኩት።
"ቆ..ህ ነዋ" ብሎ ቃሉን እንደተፈጠረ አፈረጠው! ስድ !
“አይ ምንም የለም” አልኩ እየተሸማቀቅኩ።
"ከዚህ በፊት ሌላ ሴት ጋር እንዴት ነው …አልጀማመርክም ?”
"ሌላ ሴት ጋር ሄጄ አላውቅም
“ተው ተው ! ለኃኪምና ለንስኃ አባት ሚስጥር አይደበቅም … ሃሃሃ እስቲ አንተኛው ወደ ውጭ
ውጣ¨ አለና ሃኒባልን እዘዘው። ሃኒባል ሹክክ ብሎ ወጣ (ይሄ ደግሞ ምን ያሽቆጠቁጠዋል)
ሃኒባል እስኪወጣ ጠበቀና፣
"እ… ጓደኛህ እንዴት ናት ”
“እንዴት ናት ማለት ?” አልኩት ጥያቄው ግራ አጋብቶኝ።
እንደው መልኳ፣ ጸባይዋ ማለቴ ነው። አንዳንዷ ሴት እኮ ትዘጋለች። እውነቴን ነው ዛላዋ አምሮህ፡፡
መልኳ ስብሆ ስትቀርባት አንዳንዷ ሴት እንኳን መተቃቀፍ ምግብ ትዘጋለች
"እ … ፀባይማ እናት ናት መልኳም ቢሆን" አልኩና ዋሌቴን አውጥቼ ፎቶዋን ሰጠሁት። መነፅሩን ፈልጎ ዓይኑ ላይ ሰካና ፎቶውን በትኩረት ወደ ዓይኑ ቀረብ ራቅ እያደረገ ተመልከቶ፣
"ኧረግ… ኧረግ ... ኧረግ ወንድሜን ! እውነትም ተይዘሃል። ይችን የመሰለች ልጅማ ካመለጠችህማ ሰውም አትሆን…” ብሎ አፉን ጠረገ። ዝም ብዩ አየዋለሁ፡፡ የሙናን ፈቶ እስኪበቃው ተመለከተውና
ጉሮሮውን ገርገጭ አድርጎ ምራቁን ከዋጠ በኋላ
እንደው ትንሽም አልሞከራችሁ ?” ሲል ጠየቀኝ።
"ኧረ ምንም የለም" ፎቶዋን እንደገና ተመለከተው።
"ምናምን አዙራብህ እንዳይሆን” አለኝ።
"ምንድነው ምናምን ?”
"የዛሬ ሰው አይታመንም። አንዳንድ ሴቶች ሌላ ሴት ጋር እንዳትሄድባቸው ሌላ ሌላ ነገር እንዳታደርግ ያሰሩብህና፣ ሲቆይ ለነሱም ይተርፋል ጠንቁ። እንደው አቋም ብቻ ሆንክ እንጂ አንተም ብትሆን ሸበላ አንዷ እንዳትቀማት አዙራብህ ቢሆን ማን ያውቃል"
"አረ እሷ" ሰለቸኝ ሰውዬው። እውነቱን ለመናገር ራሱን ቁልል ያደረገ ዘላባጅ ነገር ነው። ለስጋዬ
ፈውስ ብመጣ ጭራሽ ነፍሴንም ያቆስላታል እንዴ ?!
"ቀላል ነው አይዘህ !! የሰው እጅም ሆነ ሌላ መፍትሄው በእጃችን ነው' ሲለኝ ብስጭቴ ብን ብሎ ጠፍቶ ጆርዬ ቆመ።
አውርቶም ተሳድቦም ብቻ ያቁምልኝ፤ ሌላው ትርፍ ነው።
"እውነትዎትን ነው ቀላል ነው ” አልኩት በጉጉት።
"አዎ ! ይች ምንአላት ?” አለ ልክ ወደ ብልቴ አቅጣጫ በእጁ እየጠቆመና ቀማጣጣል ዓይነት ከንፈሩን ወደ ታች ጣል እያደረገ። እንኳን ይችን ስቱን አቁምነዋል!ይሄ ወዲህ ስትመጡ መታጠፊያው ጋ ያለውን ቀልቀሎ ሆቴል ታቀው የለም?”
"አዎ አውቀዋለሁ" አልኩ በጉጉት። ደግሞ አንድ የሆቴል ሕንፃ ከእኔ ጕዳይ ጋር ምን አገኘው ብዬ።
“ይሄውልህ የሱ ሕንፃ ባለቤት እንዲህ እንዳተ ፀሐይ የመሰለች ሚስት አለችው። መቼስ ብር አለን
ብነሆ ጉዳያቸውን ሳይፈትሹ ነው ትዳር ውስጥ የሚዘፈቁት። እቅፎ ቢለው ቢሰራው ወንድነት ከየት
ይምጣ ? ጭራሽ አጅሪት ውጭ ውጭ ታይ ጀመረልሃ ... ይሄን ሲሰማ ሊያብድ ሆነ። በኋላ እኔ ጋ
በሰው በሰው መጣና እንደሚሆን አድርጌ ላኩት። ይሄው ዛሬ እንኳን ለሚስቱ ለውሽሞቹም ተርፏል።
ሚስቱ እንዴት እንደምትንሰፈሰፍለት አገር የሚያውቀው ነው” የተቸገረ ሰው ሞኝ ነው፤ ዝም ብዬ
ሰውዬውን እሰማዋለሁ። አወራሩ ድራማ የሚሰራ ነው የሚመስለው።
“አንተ እሱን ትላለህ ! ይሄ በየቀኑ ቴሌቪዥን ሳይ 'እንትን' ፕሮግራም ላያ የሚቀርበው አውግቸው
” … በቴሌቪዥን ሲናገር ድምጹ ሲያስገመግም አንሰሳ ገዳይ አይመስልም ነበር ? ሃሃሃሃ ማታ ማታ ሚስቱ እያንከላፈተችው ስንት ዓመት አልቅሷል መሰለህ፡፡ እንደውም ይሄ ትልቁ ልጁ የሱ አይደለም እየተባለ ይታማልኮ። አሃ ምን ታርግ ታዲያ ያችን የመሰለች ቆንጆ በአምሮት ትሙት እንዴ ! የሱ እንኳን ሽንፈተ ወሲብ ነው”
“ሸንፈተ ወሲብ ምንድን ነው ?”
አልኩ መጽሔቱ ላይ አይቼው ያልገባኝ ነገር ትዝ ብሎኝ።
“እሱማ እንግዲህ … አገር አማን ብለህ ልትተቃቀፍ ገና ሴቷ ሰላም ብላ እጅህን ስትጨብጥህ አንተ
ጥንቅቅ ብለህ በቁምህ ጨራርሰሃል !! ሲበዛ እስከመሳሳም ብትዘልቅ ነው፡፡ አንዳንዱማ የተሞናደለ ዳሌ፣ ሎሚ የመሰለ ተረከዝ ሲመለከትም በቁሙ ሱሪው ላይ ይለቀዋል። ባንድ ፊቱ እንዲህ እንዳተ መዳፈን ይሻላል እንጂ፣ ሴቶች ሽንፈተ ወሲብ ያለበት ወንድ ላይናቸው ነው የሚቀፋቸው … ላይናቸው ወይ አይተወው ወይ አያደርገው … አጉል ነካክቶ የሰው አምሮት መቀስቀስና ሥም ነው ትርፉ ከፉ ችግር ነው። ያንተ በስንት ጣዕሙ፡ ያንተማ ምናላት ቢሆንልህ እሰየው ባይሆንም ሴት ቀረ አትሞት"
“ላይሳካ ይችላል እንዴ ?” ስል የነበረችኝ ተስፋ ኩስምን ብላ ጠየቅኩ።
“ምሳሌውን ማለቴ ነው እንጂ .. አንተማ ታሰታውቃልህ፤ የአገር ሴት አይመልስህም ቱ ግዛው ምናለ
ቀለኝ። ከዚህ ቤት እግርህ ሳይወጣ ነው እንደ ሚዳቋ ቀንድ ቀጥ ብሎ የሚቆመው። ወዮላት ለዛች ሚስኪን” አለና የሙናን ፎቶ እንደገና ወደ ዓያኑ እስጠግቶ ተመለከተው። ተስፋዬ መለስ አለልኝ።
“እግዲህ ሁለት ዓይነት አሰራር አለ፤ አንዱ .. ይሄ እንኳን ላንተ አይሆንም” አለ መልሶ።
“ለምንድነው ለኔ የማይሆነው ?”
“ውድነዋ ! ውድ ነው ... ዋጋውን ብትሰማ ከወንድነትህ በፊት ትንፋሸህ ነው እዚሁ የሚቆመው
"ወዳጄ"
"ግዴለም ይንገሩኝ ?"
"አይ ይቅርብህ። አሁን ጓጉተህ ነው፣ በኋላ ፍቅሩም አምሮቱም ሲወጣልሀ የከፈልከው ገንዘብ ትዝ ባለህ ቁጥር እንኳን እንትንህ ነፍስህም ጭምር ነው የሚሸማቀቀው። እንደውስ ተመልሰህ መጥተህ ብሬን መለስልኝ ልትል ነው ? ቅቅቅቅ' ሳቁ ይቀፋል። የሆነ ነገር ሲቧጠጥ የሚወጣው ዓይነት ድምጽ ነው።
"እሺ ሁለተኛውስ ?"
"ባይሆን እሷ ትሻላለች አንድ ሐያ ሺ ታስከፍልሃለች እንጂ ፍቱን ናት”
"ሐያ ሺ …?”
"አዎ! ምነው?”
"አልተወደደም ?”
"እኮ ! የመጀመሪያውን ብትሰማ ያልኩህ ለዚህ እኮ ነው ! ቢሆንም ዓይንን ባይን ለማየት ሒያ ሺ ምን
አላት ? እንኳን ለማቆም የቆመበት ልክስክስ ሁሉ እዚህ እኛ አካባቢ ላሉ ሴተኛ አዳሪዎች ሐያ ሺ
ይከፍል የለም እንዴ ?! ያውም ላንድ ሌሊት። መቼስ ሐያ ሺ ብር ሳይኖርህ ይችን የመሰለች ቆንጆ ላይ አትንጠለጠልም፤ እንግዲህ ምርጫው ያንተ ነው።” ብሎ ፎቶውን መለሰልኝ ወደ ቴሌቪዥኑ ዞሮ በሪሞት መቆጣጠሪያው ድምጹን ከፍ አደረገው፡፡
፡
፡
#አራት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
..."እ..ጎረምሳው መቼ ጀመረህ?” አለኝ። (በቃ ምርመራ ተጀመረ ማለት ነው ?) ሰውዬውን ትኩረት
ስመለከተው ለካስ ዓይኑ ልክ አይደለም፤ ትንሽ ሸውረር ያለ ነው። ታዲያ መጽሔት ላይ ከየት አባቱ ያመጣውን ፎቶ ነው የለጠፈው ?..
“መቼ እንደ ጀመረኝ አላወቅኩም ድንገት ከፍቅረኛዬ ጋር…"
"እ … ድንገት ከፍቅረኛህ ጋር ዓለምሆን ልትቀጭ … ሱሪህን አውልቀህ .… ቡታንታህን አውልቀህ በልስትለው…. ባባቴም የለ ብሎ ድፍት፣ ቅዝቅዝ አለብህ … እ? አዋራጅ እኮ ነው!አዋራጅ! ስንቱ በዚህ ዓይነት አጉል ጊዜ በሴት ፊት መዋረዱ አሸማቅቆት ገመዱን ቋጥሮ ራሱን ሲጥ አድርጓል መሰለህ ! እኔ እንኳን ሁለት ምን የመሳሰሉ ልጆች በዚሁ ጠንቅ ታንቀው የሞቱ አውቃለሁ አንዱ እንኳን መርዝ ጠጥቶ ነው … ያው ነው!ቀላል ነገር እንዳይመስላችሁ፡ ሴቶቹ ደሞ ይችን ወሬ ካገኙ እየዞሩ ለሁሉ
ነው የሚያወሩት“ አለ ከአፌ ላይ ነጥቆ። ይሄ ሰውዬ እንዴት ነው የሚቀባጥረው በእግዚአብሔር
በአንድ ጊዜ መንፈሴንም አኮላሸው እኮ።
እና.እንዴት ነው ትንሽም አይላወስ፣ ወይስ ጀማምሮ መሃል ላይ ወገቤን ነው የሚለው ሲል
ጠየቀኝ።
"ምኑ ?” ብዬ ጠየቅኩት።
"ቆ..ህ ነዋ" ብሎ ቃሉን እንደተፈጠረ አፈረጠው! ስድ !
“አይ ምንም የለም” አልኩ እየተሸማቀቅኩ።
"ከዚህ በፊት ሌላ ሴት ጋር እንዴት ነው …አልጀማመርክም ?”
"ሌላ ሴት ጋር ሄጄ አላውቅም
“ተው ተው ! ለኃኪምና ለንስኃ አባት ሚስጥር አይደበቅም … ሃሃሃ እስቲ አንተኛው ወደ ውጭ
ውጣ¨ አለና ሃኒባልን እዘዘው። ሃኒባል ሹክክ ብሎ ወጣ (ይሄ ደግሞ ምን ያሽቆጠቁጠዋል)
ሃኒባል እስኪወጣ ጠበቀና፣
"እ… ጓደኛህ እንዴት ናት ”
“እንዴት ናት ማለት ?” አልኩት ጥያቄው ግራ አጋብቶኝ።
እንደው መልኳ፣ ጸባይዋ ማለቴ ነው። አንዳንዷ ሴት እኮ ትዘጋለች። እውነቴን ነው ዛላዋ አምሮህ፡፡
መልኳ ስብሆ ስትቀርባት አንዳንዷ ሴት እንኳን መተቃቀፍ ምግብ ትዘጋለች
"እ … ፀባይማ እናት ናት መልኳም ቢሆን" አልኩና ዋሌቴን አውጥቼ ፎቶዋን ሰጠሁት። መነፅሩን ፈልጎ ዓይኑ ላይ ሰካና ፎቶውን በትኩረት ወደ ዓይኑ ቀረብ ራቅ እያደረገ ተመልከቶ፣
"ኧረግ… ኧረግ ... ኧረግ ወንድሜን ! እውነትም ተይዘሃል። ይችን የመሰለች ልጅማ ካመለጠችህማ ሰውም አትሆን…” ብሎ አፉን ጠረገ። ዝም ብዩ አየዋለሁ፡፡ የሙናን ፈቶ እስኪበቃው ተመለከተውና
ጉሮሮውን ገርገጭ አድርጎ ምራቁን ከዋጠ በኋላ
እንደው ትንሽም አልሞከራችሁ ?” ሲል ጠየቀኝ።
"ኧረ ምንም የለም" ፎቶዋን እንደገና ተመለከተው።
"ምናምን አዙራብህ እንዳይሆን” አለኝ።
"ምንድነው ምናምን ?”
"የዛሬ ሰው አይታመንም። አንዳንድ ሴቶች ሌላ ሴት ጋር እንዳትሄድባቸው ሌላ ሌላ ነገር እንዳታደርግ ያሰሩብህና፣ ሲቆይ ለነሱም ይተርፋል ጠንቁ። እንደው አቋም ብቻ ሆንክ እንጂ አንተም ብትሆን ሸበላ አንዷ እንዳትቀማት አዙራብህ ቢሆን ማን ያውቃል"
"አረ እሷ" ሰለቸኝ ሰውዬው። እውነቱን ለመናገር ራሱን ቁልል ያደረገ ዘላባጅ ነገር ነው። ለስጋዬ
ፈውስ ብመጣ ጭራሽ ነፍሴንም ያቆስላታል እንዴ ?!
"ቀላል ነው አይዘህ !! የሰው እጅም ሆነ ሌላ መፍትሄው በእጃችን ነው' ሲለኝ ብስጭቴ ብን ብሎ ጠፍቶ ጆርዬ ቆመ።
አውርቶም ተሳድቦም ብቻ ያቁምልኝ፤ ሌላው ትርፍ ነው።
"እውነትዎትን ነው ቀላል ነው ” አልኩት በጉጉት።
"አዎ ! ይች ምንአላት ?” አለ ልክ ወደ ብልቴ አቅጣጫ በእጁ እየጠቆመና ቀማጣጣል ዓይነት ከንፈሩን ወደ ታች ጣል እያደረገ። እንኳን ይችን ስቱን አቁምነዋል!ይሄ ወዲህ ስትመጡ መታጠፊያው ጋ ያለውን ቀልቀሎ ሆቴል ታቀው የለም?”
"አዎ አውቀዋለሁ" አልኩ በጉጉት። ደግሞ አንድ የሆቴል ሕንፃ ከእኔ ጕዳይ ጋር ምን አገኘው ብዬ።
“ይሄውልህ የሱ ሕንፃ ባለቤት እንዲህ እንዳተ ፀሐይ የመሰለች ሚስት አለችው። መቼስ ብር አለን
ብነሆ ጉዳያቸውን ሳይፈትሹ ነው ትዳር ውስጥ የሚዘፈቁት። እቅፎ ቢለው ቢሰራው ወንድነት ከየት
ይምጣ ? ጭራሽ አጅሪት ውጭ ውጭ ታይ ጀመረልሃ ... ይሄን ሲሰማ ሊያብድ ሆነ። በኋላ እኔ ጋ
በሰው በሰው መጣና እንደሚሆን አድርጌ ላኩት። ይሄው ዛሬ እንኳን ለሚስቱ ለውሽሞቹም ተርፏል።
ሚስቱ እንዴት እንደምትንሰፈሰፍለት አገር የሚያውቀው ነው” የተቸገረ ሰው ሞኝ ነው፤ ዝም ብዬ
ሰውዬውን እሰማዋለሁ። አወራሩ ድራማ የሚሰራ ነው የሚመስለው።
“አንተ እሱን ትላለህ ! ይሄ በየቀኑ ቴሌቪዥን ሳይ 'እንትን' ፕሮግራም ላያ የሚቀርበው አውግቸው
” … በቴሌቪዥን ሲናገር ድምጹ ሲያስገመግም አንሰሳ ገዳይ አይመስልም ነበር ? ሃሃሃሃ ማታ ማታ ሚስቱ እያንከላፈተችው ስንት ዓመት አልቅሷል መሰለህ፡፡ እንደውም ይሄ ትልቁ ልጁ የሱ አይደለም እየተባለ ይታማልኮ። አሃ ምን ታርግ ታዲያ ያችን የመሰለች ቆንጆ በአምሮት ትሙት እንዴ ! የሱ እንኳን ሽንፈተ ወሲብ ነው”
“ሸንፈተ ወሲብ ምንድን ነው ?”
አልኩ መጽሔቱ ላይ አይቼው ያልገባኝ ነገር ትዝ ብሎኝ።
“እሱማ እንግዲህ … አገር አማን ብለህ ልትተቃቀፍ ገና ሴቷ ሰላም ብላ እጅህን ስትጨብጥህ አንተ
ጥንቅቅ ብለህ በቁምህ ጨራርሰሃል !! ሲበዛ እስከመሳሳም ብትዘልቅ ነው፡፡ አንዳንዱማ የተሞናደለ ዳሌ፣ ሎሚ የመሰለ ተረከዝ ሲመለከትም በቁሙ ሱሪው ላይ ይለቀዋል። ባንድ ፊቱ እንዲህ እንዳተ መዳፈን ይሻላል እንጂ፣ ሴቶች ሽንፈተ ወሲብ ያለበት ወንድ ላይናቸው ነው የሚቀፋቸው … ላይናቸው ወይ አይተወው ወይ አያደርገው … አጉል ነካክቶ የሰው አምሮት መቀስቀስና ሥም ነው ትርፉ ከፉ ችግር ነው። ያንተ በስንት ጣዕሙ፡ ያንተማ ምናላት ቢሆንልህ እሰየው ባይሆንም ሴት ቀረ አትሞት"
“ላይሳካ ይችላል እንዴ ?” ስል የነበረችኝ ተስፋ ኩስምን ብላ ጠየቅኩ።
“ምሳሌውን ማለቴ ነው እንጂ .. አንተማ ታሰታውቃልህ፤ የአገር ሴት አይመልስህም ቱ ግዛው ምናለ
ቀለኝ። ከዚህ ቤት እግርህ ሳይወጣ ነው እንደ ሚዳቋ ቀንድ ቀጥ ብሎ የሚቆመው። ወዮላት ለዛች ሚስኪን” አለና የሙናን ፎቶ እንደገና ወደ ዓያኑ እስጠግቶ ተመለከተው። ተስፋዬ መለስ አለልኝ።
“እግዲህ ሁለት ዓይነት አሰራር አለ፤ አንዱ .. ይሄ እንኳን ላንተ አይሆንም” አለ መልሶ።
“ለምንድነው ለኔ የማይሆነው ?”
“ውድነዋ ! ውድ ነው ... ዋጋውን ብትሰማ ከወንድነትህ በፊት ትንፋሸህ ነው እዚሁ የሚቆመው
"ወዳጄ"
"ግዴለም ይንገሩኝ ?"
"አይ ይቅርብህ። አሁን ጓጉተህ ነው፣ በኋላ ፍቅሩም አምሮቱም ሲወጣልሀ የከፈልከው ገንዘብ ትዝ ባለህ ቁጥር እንኳን እንትንህ ነፍስህም ጭምር ነው የሚሸማቀቀው። እንደውስ ተመልሰህ መጥተህ ብሬን መለስልኝ ልትል ነው ? ቅቅቅቅ' ሳቁ ይቀፋል። የሆነ ነገር ሲቧጠጥ የሚወጣው ዓይነት ድምጽ ነው።
"እሺ ሁለተኛውስ ?"
"ባይሆን እሷ ትሻላለች አንድ ሐያ ሺ ታስከፍልሃለች እንጂ ፍቱን ናት”
"ሐያ ሺ …?”
"አዎ! ምነው?”
"አልተወደደም ?”
"እኮ ! የመጀመሪያውን ብትሰማ ያልኩህ ለዚህ እኮ ነው ! ቢሆንም ዓይንን ባይን ለማየት ሒያ ሺ ምን
አላት ? እንኳን ለማቆም የቆመበት ልክስክስ ሁሉ እዚህ እኛ አካባቢ ላሉ ሴተኛ አዳሪዎች ሐያ ሺ
ይከፍል የለም እንዴ ?! ያውም ላንድ ሌሊት። መቼስ ሐያ ሺ ብር ሳይኖርህ ይችን የመሰለች ቆንጆ ላይ አትንጠለጠልም፤ እንግዲህ ምርጫው ያንተ ነው።” ብሎ ፎቶውን መለሰልኝ ወደ ቴሌቪዥኑ ዞሮ በሪሞት መቆጣጠሪያው ድምጹን ከፍ አደረገው፡፡
👍27❤2🔥2
#ከሰሀራ_በታች
፡
፡
#አራት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከፋና ጋር ከተሳሳምንባት ቅዳሜ በኋላ ዋና ስራችን የእማማ አመለ እና የፍቅርተ እግር
ሲወጣ መጠበቅ ሆነ..በቃ ወጣ ሲሉ ፋና ወደ ክፍሌ ሮጣ ትመጣና እቅፌ ላይ ናት፣ከንፈሮቻችን እንዳይገናኙ ማድረግ ከሁለታችንም አቅም በላይ ነበር፡፡ በፍቅር ሰከርን፤አንዳንዴ እማማ አመለ ቤት ውስጥ ሆነውም ፋና ተነስታ ወደ ክፍሌ ትገባለች፣“አብርሽ ስራ ይዘሃል እንዴ?” ትላለች፡፡እማማ አመለ ከትምህርት ጋር የተያያዘ ነገር አድርገው ስለሚያስቡት በጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ፋኒ ወደ ክፍሌ ትገባና እንደ እብድ ትስመኛለች!
ከሚፈታተነኝ ስሜት ጋር እየታገልኩ እማማ አመለ እንዳይሰሙ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ፤ ፋኒ ግን መሳሳም ከጀመርን ነፍሷን አታውቅም፤ ማንም ቢመጣ ግድ አይሰጣትም፡፡
ማታ ማታ ቡናችን ላይ ስንቀመጥ ፋኒ ዓይኖቿን ከእኔ ላይ መንቀል አትችልም፤ በቃ ዓይኗ ቡዝዝ ብሎ ታየኛለች፡፡ አስተያየቷ ይጨንቀኛል፡፡ ፍቅርተ ድንገት ብትጠራጠር ብዬ እፈራለሁ፡፡
ደግነቱ ፍቅርተ ሳታቋርጥ ስለምታወራ ሁለታችንንም አትመለከተንም፡: ፋና ትምህርት ማጥናቷ ሁሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ በየምክንያቱ እኔ ክፍል መመላለስ ሆነ ስራዋ፡፡ መቸም እኔና ፋና ከዚህ በፊት እማማ አመለ አዕምሮ ውስጥ የፈጠርነው እምነት ረዳን እንጂ የፋና ባህሪ መቀየር፣ የሁለታችንን የፍቅር ግንኙነታችንን አፍ አውጥቶ የሚናገር ነበር፡፡ አንዳንድ ሰው አለ
መሃል ላይ መቆም የማይችል፣ ወይ ጥቅልል አድርጎ ራሱን ይሰጣል፣ አልያም ገና ከሩቁ ከሰው ይሸሻል ፋና እንደዛ ነበረች፡፡ ሙሉ እሷነቷን ለእኔ ስለሰጠችኝ ለምትሰራው ነገር ሁሉ ሌላ ሰው አልታይ አላት፡፡
የነፋና ኑሮ ሊገልፁት በማይችሉት ድህነት ውስጥ የተዘፈቀ ነበር፡፡ ባጭሩ ቤት ያላቸው የጎዳና
ተዳዳሪዎች ይመስሉኛል፡፡ አንዳንዴ እማማ አመለ የከሰል መግዣ ብር ያጡ ስለነበረ ከቤቷ
ጋር ተያይዛ የተሰራች በላስቲክ የተጋረደች ኩሽና ውስጥ ምናምኑን ጓድፈው ይማግዱና ቡና ያፈላሉ፡፡ ቡናው ታዲያ ጣዕሙ ጭስ ጭስ ይላል፡፡ እኔ ያን ያህል ብር ባይተርፈኝም አንዳንዴ ከቤተሰብ ሲላክልኝ ለፋና አልያም ለፍቅርተ ትንሽ ብር ልሰጣቸው እሞክራለሁ፡፡ ሁለቱም ቢሞቱ ብር ከእኔ አይቀበሉም፡፡ ብዙ ጊዜ ሞክሬ ሲቸከኝ መጠየቁንም ትቼዋለሁ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ፋና ወደ ክፍሌ ገባችና እየፈራች “አብርሽ ሰላሳ ብር አለህ ?” አለችኝ ፊቷ ላይ የነበረው ሀፍረት ያሳዝን ነበር፡፡ ደስ ብሎኝ ለፋና ድፍን ሃምሳ ብር ሰጠኋት፣ ደስ ብሏት እየተጣደፈች ወጣች፡፡
ፋና ወደ ማታ አንድ የተጠቀለለ ነገር ይዛ ወደ ክፍሌ ገባች፡፡ ፊቷ በደስታ ፈገግታ ተጥለቅልቋል፡
፡ ጥቅልሉን ፈታታችና አንድ ጥቁር የሴት ጅንስ ሱሪ አወጣች፣ “ለፍቅርዬ ገዛሁላት” አለችኝ፡፡
ሱሪውን ሳይሆን ፋና ፊት ላይ የነበረውን ፈገግታና ደስታ አይቼ መጥገብ አልቻልኩም፡፡ ፋና
እንደዚህ በደስታ ስትሰክር አይቻት አላውቅም፡፡
ትምህርት ቤታቸው ውስጥ በነበረ የስነተዋልዶ ስልጠና ላይ ተሳትፋ በተሰጣት አበል ከእኔ ሰላሳ
ብር ጨምራ ለፍቅርተ ይህን ሱሪ ገዛች፡፡ ፋና እንዲህ አይነት ልጅ ነበረች፡፡ ቁንጅናዋ የልብሷን
ተራነት ይሸፍነዋል እንጂ ለራሷ አንድም የረባ ልብስ የላትም፡፡ አዲሱን ሱሪ ይዛ ፍራሽ ጫፍ
ላይ ተቀመጠችና በጀርባዋ ተደገፈችኝ፡፡ የሆነ ርካታ ይነበብባት ነበር፡፡
“ፍቅርዬን እወዳታለሁ ከህፃንነታችን ጀምሮ ሁሉም ሰው እንደገፋት ነው የኖረችው፡፡ ሁልጊዜም ስለሷ እያሰብኩ እሰቃያለሁ፡፡“ አብርሽ ፍቅር እኮ እንደ መልኳ አይደለችም ደግ ነች፣ ጥሩ እህት፣ ጥሩ ጓደኛ ናት፡፡ ሁሉም ሰው ግን ይርቃታል” አለችና ማልቀስ ጀመረች፡፡ እንባዎቿን ጠረግኩላት፡፡ እንባዋ በንፁህ ጉንጮቿ ላይ ሲንኳለል መስተዋት ላይ የፈሰሰ ውሃ ይመስል ነበር፤ ጉንጯን ሳምኳት ፤ ወዲያው ግን በየት በኩል እንደተንሸራተትኩ እንጃ ከንፈራችን ተገናኘ፡፡ቅልጥ ያለ መሳሳም ውስጥ ገብተን ይሄን የዘቀጠ ኑሮ የጠቆረ ድህነት ለደቂቃዎች ተሰናበትነው።
ሱሪው ፍቅርተን ቀየራት፡፡ ስትለብሰው ዳሌዋን ሰፋ ኣድርጎ ወገቧን ሸንቀጥ ስላደረገው የፍቅርተ ቁንጅና መቃብሩን ፈንቅሎ ወጣ፡፡ ሱሪውን ስትለብስ አንድ የጥንካሬ መንፈስ የለበሰች ይመስል አስገራሚ በራስ መተማመን ይታይባታል፡፡ ጓደኞቿ ጋር መወጣት፣ አመሻሹ ላይ ከጎረቤት እኩዮቿ ጋር ተያይዛ መዞር ጀመረች፡፡ በዕርግጥም ሱሪው የሰውነቷን ቅርፅ ጎላ አድርጎ አሳምሯት ነበር፡፡ ይህንን አድናቆት ከአንዳንድ ወንዶች ጭምር እንደተቸራትም ፍቅርተ ራሷ በደስታ ለእኔና ለፉና እየነገረችን ስታስቀን ነበር፡፡ ልብስ መንፈስ ነው፡፡ ስጋን ሸፍኖ የስጋን ውበት የሚያጎላ መንፈስ፡፡ ይሄ መንፈስ ሱሪ ተመስሎ ፍቅርተ ላይ አርፎ ነበር ፡፡
የእነፉና ህይወት ከቀን ወደቀን ወደባሰ ድህነት እየተዘፈቀ ነበር የሚሄደው፡፡ እማማ አመለ አልፎ
አልፎ ልብስ ያጥቡላቸው የነበሩ የመንገድ ስራ ሙያተኞች ነበሩ፡፡ ከዛች የሚያገኟት ገቢ እኔ
በየወሩ ከምሰጣቸው የኪራይ ብር ጋር ተዳምራ ኑሯቸውን ስትደጉም ኖራለች፡፡ ታዲያ የመንገድ
ስራ ባለሙያዎቹ መንገዱን ሰርተው ስለጨረሱ የእማማ አመለም ገቢ ተቋረጠና ቤተሰቡ የባሰ ችግር ላይ ወደቀ፡፡ አንዳንድ ቀን የወትሮውን ቡና ማፍሊያ ብር ስለሚያጡ ሁላችንም በጊዜ
እንተኛለን፡፡ ቤቱ እንደ መቃብር ቤት ፀጥ ይላል፡፡ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በሰፈሩ
ለሚያልፈው መንገድ ግንባታ ቤታቸው በቅርቡ እንደሚፈርስ ለእማማ አመለ ተነገራቸው፡፡
እማማ አመለ ይህን መርዶ እንደሰሙ ሙሉ ቀን ታምመው ከአልጋቸው ሳይነሱ ዋሉ፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ፍቅርተ ትምህርቷን አቋርጣ ካፍቴሪያ በእቃ አጣቢነት ለመቀጠር መወሰኗን ለቤተሰቡ አሳወቀች፤ መርዶ ነበረ፡፡ እማማ አመለ እያለቀሱ እግሯ ላይ ወድቀው ለመኗት፡፡ ፋና ፊቷ ገርጥቶ እና አይኖቿ በእንባ ተሞልተው ዝም ብላ ፍቅርተን እና እናቷን ትመለከታለች፡፡በብዙ ልመና ፍቅርተ የዛን ቀን ትምህርት ቤት ሄደች፡፡ ፋና ፊቷ በሐዘን ድባብ ተውጦ ከወትሮ ዝምታዋ ሺ ጊዜ የገዘፈ ዝማታ ውስጥ ሰጥማ ዋለች፡፡ የዛን ጊዜ ፋና የአስራ ሁለተኛ ክፍል ፈተና ወስዳ ውጤት እየተጠባበቀች ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን ወደ ማታ ላይ ፋና ወደ ክፍሌ መጣች፡፡ አልሳመችኝም፣ ትክዝ ብላ ፍራሽ ጫፍ ላይ ተቀመጠችና “አብርሽ አረብ አገር ልላክሽ የሚለኝ የሆነ ጎረቤታችን አለ፣ ብዙ ልጆች ልኳል
እዚሁ እኛ ሰፈር ነው ተፈሪ የሚባለው ታውቀው የለ ?” አለችኝ፡፡
“እና…” አልኳት አሁኑኑ ብርር ብላ ትሄድብኝ ይመስል ስጋት ሁለመናዬን ወርሮት እጆቿን
በእጆቼ እየያዝኩ፡፡ ደንግጬ ነበር፣ መተንፈስ ሁሉ አቅቶኝ ነበር፡፡
“አይ ቢያንስ ፍቅር ትምህርቷን እስክትጨርስ ለሁለት ዓመት ሰርቼ ብመለስ ብዬ አሰብኩ፤
በዛ ላይ ይሄ ቤት ከፈረሰ የት እንወድቃለን ዘመድ የለን መጠጊያ” አለችኝ፡፡ ድንጋጤዬ
አስደንግጧት ሳይሆን አይቀርም ስትናገር ፈርታ ነበር፡፡
“አብደሻል ፋኒ…ምን ሰይጣን ነው ይሄን ያሳሰበሺ..እንዴት እንደዚህ አይነት መጥፎ ነገር ታስቢያለሽ” ጮህኩባት ::
“ኧረ እብርሽ ቀስ እማማ እንዳትሰማ አለችኝ በጭንቀት በአገጯ ወደዛንኛው ክፍል እየጠቆመች።
፡
፡
#አራት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከፋና ጋር ከተሳሳምንባት ቅዳሜ በኋላ ዋና ስራችን የእማማ አመለ እና የፍቅርተ እግር
ሲወጣ መጠበቅ ሆነ..በቃ ወጣ ሲሉ ፋና ወደ ክፍሌ ሮጣ ትመጣና እቅፌ ላይ ናት፣ከንፈሮቻችን እንዳይገናኙ ማድረግ ከሁለታችንም አቅም በላይ ነበር፡፡ በፍቅር ሰከርን፤አንዳንዴ እማማ አመለ ቤት ውስጥ ሆነውም ፋና ተነስታ ወደ ክፍሌ ትገባለች፣“አብርሽ ስራ ይዘሃል እንዴ?” ትላለች፡፡እማማ አመለ ከትምህርት ጋር የተያያዘ ነገር አድርገው ስለሚያስቡት በጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ፋኒ ወደ ክፍሌ ትገባና እንደ እብድ ትስመኛለች!
ከሚፈታተነኝ ስሜት ጋር እየታገልኩ እማማ አመለ እንዳይሰሙ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ፤ ፋኒ ግን መሳሳም ከጀመርን ነፍሷን አታውቅም፤ ማንም ቢመጣ ግድ አይሰጣትም፡፡
ማታ ማታ ቡናችን ላይ ስንቀመጥ ፋኒ ዓይኖቿን ከእኔ ላይ መንቀል አትችልም፤ በቃ ዓይኗ ቡዝዝ ብሎ ታየኛለች፡፡ አስተያየቷ ይጨንቀኛል፡፡ ፍቅርተ ድንገት ብትጠራጠር ብዬ እፈራለሁ፡፡
ደግነቱ ፍቅርተ ሳታቋርጥ ስለምታወራ ሁለታችንንም አትመለከተንም፡: ፋና ትምህርት ማጥናቷ ሁሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ በየምክንያቱ እኔ ክፍል መመላለስ ሆነ ስራዋ፡፡ መቸም እኔና ፋና ከዚህ በፊት እማማ አመለ አዕምሮ ውስጥ የፈጠርነው እምነት ረዳን እንጂ የፋና ባህሪ መቀየር፣ የሁለታችንን የፍቅር ግንኙነታችንን አፍ አውጥቶ የሚናገር ነበር፡፡ አንዳንድ ሰው አለ
መሃል ላይ መቆም የማይችል፣ ወይ ጥቅልል አድርጎ ራሱን ይሰጣል፣ አልያም ገና ከሩቁ ከሰው ይሸሻል ፋና እንደዛ ነበረች፡፡ ሙሉ እሷነቷን ለእኔ ስለሰጠችኝ ለምትሰራው ነገር ሁሉ ሌላ ሰው አልታይ አላት፡፡
የነፋና ኑሮ ሊገልፁት በማይችሉት ድህነት ውስጥ የተዘፈቀ ነበር፡፡ ባጭሩ ቤት ያላቸው የጎዳና
ተዳዳሪዎች ይመስሉኛል፡፡ አንዳንዴ እማማ አመለ የከሰል መግዣ ብር ያጡ ስለነበረ ከቤቷ
ጋር ተያይዛ የተሰራች በላስቲክ የተጋረደች ኩሽና ውስጥ ምናምኑን ጓድፈው ይማግዱና ቡና ያፈላሉ፡፡ ቡናው ታዲያ ጣዕሙ ጭስ ጭስ ይላል፡፡ እኔ ያን ያህል ብር ባይተርፈኝም አንዳንዴ ከቤተሰብ ሲላክልኝ ለፋና አልያም ለፍቅርተ ትንሽ ብር ልሰጣቸው እሞክራለሁ፡፡ ሁለቱም ቢሞቱ ብር ከእኔ አይቀበሉም፡፡ ብዙ ጊዜ ሞክሬ ሲቸከኝ መጠየቁንም ትቼዋለሁ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ፋና ወደ ክፍሌ ገባችና እየፈራች “አብርሽ ሰላሳ ብር አለህ ?” አለችኝ ፊቷ ላይ የነበረው ሀፍረት ያሳዝን ነበር፡፡ ደስ ብሎኝ ለፋና ድፍን ሃምሳ ብር ሰጠኋት፣ ደስ ብሏት እየተጣደፈች ወጣች፡፡
ፋና ወደ ማታ አንድ የተጠቀለለ ነገር ይዛ ወደ ክፍሌ ገባች፡፡ ፊቷ በደስታ ፈገግታ ተጥለቅልቋል፡
፡ ጥቅልሉን ፈታታችና አንድ ጥቁር የሴት ጅንስ ሱሪ አወጣች፣ “ለፍቅርዬ ገዛሁላት” አለችኝ፡፡
ሱሪውን ሳይሆን ፋና ፊት ላይ የነበረውን ፈገግታና ደስታ አይቼ መጥገብ አልቻልኩም፡፡ ፋና
እንደዚህ በደስታ ስትሰክር አይቻት አላውቅም፡፡
ትምህርት ቤታቸው ውስጥ በነበረ የስነተዋልዶ ስልጠና ላይ ተሳትፋ በተሰጣት አበል ከእኔ ሰላሳ
ብር ጨምራ ለፍቅርተ ይህን ሱሪ ገዛች፡፡ ፋና እንዲህ አይነት ልጅ ነበረች፡፡ ቁንጅናዋ የልብሷን
ተራነት ይሸፍነዋል እንጂ ለራሷ አንድም የረባ ልብስ የላትም፡፡ አዲሱን ሱሪ ይዛ ፍራሽ ጫፍ
ላይ ተቀመጠችና በጀርባዋ ተደገፈችኝ፡፡ የሆነ ርካታ ይነበብባት ነበር፡፡
“ፍቅርዬን እወዳታለሁ ከህፃንነታችን ጀምሮ ሁሉም ሰው እንደገፋት ነው የኖረችው፡፡ ሁልጊዜም ስለሷ እያሰብኩ እሰቃያለሁ፡፡“ አብርሽ ፍቅር እኮ እንደ መልኳ አይደለችም ደግ ነች፣ ጥሩ እህት፣ ጥሩ ጓደኛ ናት፡፡ ሁሉም ሰው ግን ይርቃታል” አለችና ማልቀስ ጀመረች፡፡ እንባዎቿን ጠረግኩላት፡፡ እንባዋ በንፁህ ጉንጮቿ ላይ ሲንኳለል መስተዋት ላይ የፈሰሰ ውሃ ይመስል ነበር፤ ጉንጯን ሳምኳት ፤ ወዲያው ግን በየት በኩል እንደተንሸራተትኩ እንጃ ከንፈራችን ተገናኘ፡፡ቅልጥ ያለ መሳሳም ውስጥ ገብተን ይሄን የዘቀጠ ኑሮ የጠቆረ ድህነት ለደቂቃዎች ተሰናበትነው።
ሱሪው ፍቅርተን ቀየራት፡፡ ስትለብሰው ዳሌዋን ሰፋ ኣድርጎ ወገቧን ሸንቀጥ ስላደረገው የፍቅርተ ቁንጅና መቃብሩን ፈንቅሎ ወጣ፡፡ ሱሪውን ስትለብስ አንድ የጥንካሬ መንፈስ የለበሰች ይመስል አስገራሚ በራስ መተማመን ይታይባታል፡፡ ጓደኞቿ ጋር መወጣት፣ አመሻሹ ላይ ከጎረቤት እኩዮቿ ጋር ተያይዛ መዞር ጀመረች፡፡ በዕርግጥም ሱሪው የሰውነቷን ቅርፅ ጎላ አድርጎ አሳምሯት ነበር፡፡ ይህንን አድናቆት ከአንዳንድ ወንዶች ጭምር እንደተቸራትም ፍቅርተ ራሷ በደስታ ለእኔና ለፉና እየነገረችን ስታስቀን ነበር፡፡ ልብስ መንፈስ ነው፡፡ ስጋን ሸፍኖ የስጋን ውበት የሚያጎላ መንፈስ፡፡ ይሄ መንፈስ ሱሪ ተመስሎ ፍቅርተ ላይ አርፎ ነበር ፡፡
የእነፉና ህይወት ከቀን ወደቀን ወደባሰ ድህነት እየተዘፈቀ ነበር የሚሄደው፡፡ እማማ አመለ አልፎ
አልፎ ልብስ ያጥቡላቸው የነበሩ የመንገድ ስራ ሙያተኞች ነበሩ፡፡ ከዛች የሚያገኟት ገቢ እኔ
በየወሩ ከምሰጣቸው የኪራይ ብር ጋር ተዳምራ ኑሯቸውን ስትደጉም ኖራለች፡፡ ታዲያ የመንገድ
ስራ ባለሙያዎቹ መንገዱን ሰርተው ስለጨረሱ የእማማ አመለም ገቢ ተቋረጠና ቤተሰቡ የባሰ ችግር ላይ ወደቀ፡፡ አንዳንድ ቀን የወትሮውን ቡና ማፍሊያ ብር ስለሚያጡ ሁላችንም በጊዜ
እንተኛለን፡፡ ቤቱ እንደ መቃብር ቤት ፀጥ ይላል፡፡ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በሰፈሩ
ለሚያልፈው መንገድ ግንባታ ቤታቸው በቅርቡ እንደሚፈርስ ለእማማ አመለ ተነገራቸው፡፡
እማማ አመለ ይህን መርዶ እንደሰሙ ሙሉ ቀን ታምመው ከአልጋቸው ሳይነሱ ዋሉ፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ፍቅርተ ትምህርቷን አቋርጣ ካፍቴሪያ በእቃ አጣቢነት ለመቀጠር መወሰኗን ለቤተሰቡ አሳወቀች፤ መርዶ ነበረ፡፡ እማማ አመለ እያለቀሱ እግሯ ላይ ወድቀው ለመኗት፡፡ ፋና ፊቷ ገርጥቶ እና አይኖቿ በእንባ ተሞልተው ዝም ብላ ፍቅርተን እና እናቷን ትመለከታለች፡፡በብዙ ልመና ፍቅርተ የዛን ቀን ትምህርት ቤት ሄደች፡፡ ፋና ፊቷ በሐዘን ድባብ ተውጦ ከወትሮ ዝምታዋ ሺ ጊዜ የገዘፈ ዝማታ ውስጥ ሰጥማ ዋለች፡፡ የዛን ጊዜ ፋና የአስራ ሁለተኛ ክፍል ፈተና ወስዳ ውጤት እየተጠባበቀች ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን ወደ ማታ ላይ ፋና ወደ ክፍሌ መጣች፡፡ አልሳመችኝም፣ ትክዝ ብላ ፍራሽ ጫፍ ላይ ተቀመጠችና “አብርሽ አረብ አገር ልላክሽ የሚለኝ የሆነ ጎረቤታችን አለ፣ ብዙ ልጆች ልኳል
እዚሁ እኛ ሰፈር ነው ተፈሪ የሚባለው ታውቀው የለ ?” አለችኝ፡፡
“እና…” አልኳት አሁኑኑ ብርር ብላ ትሄድብኝ ይመስል ስጋት ሁለመናዬን ወርሮት እጆቿን
በእጆቼ እየያዝኩ፡፡ ደንግጬ ነበር፣ መተንፈስ ሁሉ አቅቶኝ ነበር፡፡
“አይ ቢያንስ ፍቅር ትምህርቷን እስክትጨርስ ለሁለት ዓመት ሰርቼ ብመለስ ብዬ አሰብኩ፤
በዛ ላይ ይሄ ቤት ከፈረሰ የት እንወድቃለን ዘመድ የለን መጠጊያ” አለችኝ፡፡ ድንጋጤዬ
አስደንግጧት ሳይሆን አይቀርም ስትናገር ፈርታ ነበር፡፡
“አብደሻል ፋኒ…ምን ሰይጣን ነው ይሄን ያሳሰበሺ..እንዴት እንደዚህ አይነት መጥፎ ነገር ታስቢያለሽ” ጮህኩባት ::
“ኧረ እብርሽ ቀስ እማማ እንዳትሰማ አለችኝ በጭንቀት በአገጯ ወደዛንኛው ክፍል እየጠቆመች።
👍26
#ሚስቴን_አከሸፏት
፡
፡
#አራት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
....የፌቨን እናት ተቀየሙኝ። ሊያስታርቁን መጥተው፣ “ልጅዎትን ከዚህ በኋላ ማየት አልፈልግም ስላልኳቸው ተቀየሙ። ማንም ወላጅ ቢሆን ይሰማዋል። በደካማ አቅማቸው ከየትና የት ድረስ መጥተው ለማስታረቅ ሲሞክሩ እንቢ አይለኝም ብለው ነበር ያሰቡት። የእኔ ፌቨንን መጥላት ...
ርሳቸውን መናቅ መሰላቸው “አንዲት ሴት ፀጉሯን መቆረጧ ትዳር እስከማፍረስ ካደረሰ ከፍቺው ኋላ ፀጉር ብቻ ሳይሆን ሌላ ምክንያት አለ ማለት ነው” ብለው እንዲያስቡ አድርጓቸዋል። እውነት ነው
ከፌቨን ፀጉር ኋላ ሚሊየን ምክንያቶች ነበሩ፤ ሁሉም ምክንያቶች ግን መነሻቸው ፍቅር ነበር።
“ፍቅር ይታገሳል” ይሉኛል ጉዳዩን የሰሙ ሁሉ፣
ሰው በሰላሙ ቀን እግዜሩንም መጽሐፉንም አሽቀንጥሮ አሸሼ ሲል ይከርምና የቁርጥ ቀን ሲመጣ በየሥርቻው የጣለውን የሕይወት መጽሐፍ አቧራውን አራግፎ እያነሳ ሁሉም ሰባኪ፣ ሁሉም ቃል አጣቃሽ ካልሆንኩ ይላል።
“ፍቅር ይታገሳል”ይለኛል መካሪ። እንዲህ ሲሉኝ ተናገር ተናገር ጩህ ጩህ ይለኛል። “እስቲ እንዲህ
ለነፍስህ ያደርክ ከሆንክ ቃሉ እንደሚለው አታመንዝር ! አዎ አንተ ራስህ ይሄን የምትመክረኝ …
እስቲ በየስርቻው ራሳቸውን ነጥቀህ በቀለም የምታዥጎረጉራቸውን የወሲብ እቃዎችህን እንደሰው ቁጠር ! እዚህች አገር እንደ ሴት መጫወቻ የሆነ ፍጥረት አለ ... ? የማንም ወጠጤ መጥቶ የብልግና
ብሩሹን አንከርፍፎ መንገድ ላይ እንደተሰጣ ሸራ ሴቶችህ ላይ ብልግናውን ሲስል የት ነበርክ…” ማለት ያምረኛል።
አዎ ውስጤ በቁጣ ይሞላል፣ “ላንት 'መብታቸው ነው እያልክ በየመጠጥና ጫት ቤቱ እንደ ጥራጊ ማንም ሲረግጣቸው የነበሩ ሴቶችህን ስታልፍ .… ዛሬ ሴተኛ አዳሪነት፣ወሲብን አቃልሎ ማየት፣ በፋሽን ሥም ሴትነትን መንገድ ዳር አቅርቦ መቸብቸብ ሰተት ብሎ ጓዳህ ገባ! ሴቶች በጓዳ አይቅሩ አደባባይ
ይውጡ ከሚለው የሚበዛው ለሴቶች መጨቆን ያዘነ እንዳይመስልህ። በአደባባይ እንደ ፋሲካ በግ ዳሌና ሽንጥ በዓይኑ እየመተረ ለመምረጥ ነው! ምነው የሚመች ጓዳ፣ ክብር ያለው ጎጆ አግኝተው ሴቶች ጓዳቸው ውስጥ አርፈው በተቀመጡ። ግን ባትለውም ኑሮ ራሱ እየመዘዘ አደባባይ ያሰጣቸዋል።
ያውም የኛ ኑሮ…” ብዬ በአደባባይ ድፍን የአበሻ ወንድ ላይ መጮህ መደንፋት ያምረኛል።
“ለመሆኑ የሴቶችን ልብስና ጫማዎች ታዝበሃል ? ለተረት የሚመች አይደለም ሁሉም። ሴት ልጅ ከቤቷ ወጥታ ወደ መኪናዋ ከመኪና ወደ ሥራ ረጋ ያለ ሕይወት እና እንቅስቃሴ እድትኖር ታስበው የተሰሩ ናቸው። እንዳንተ ስኒከር፣ ሸራ ጫማ፣ ከስክስ አይደለም የሴቶች ጫማ ! ሴቶችህ ራሳቸው ለአደባባይ ማንነት “መብት” የሚል ሽፋን ይሰጡታል እንጂ በብዙሃኑ የከተማ ሴት አዕምሮ ውስጥ
ያለው እውነት ጥሩ ሥራ አግኝቶ ወይም አንዱን ኃብታም አግብቶ “
እርፍ” የሚል ሕልም ነው !
(ይሄ አንዳንዶችን ያበሳጫል ግን ምን ይደረግ እውነት ነው። ከተማውን ከሰኞ እስከ አርብ የዘነጠ ሽቅርቅር ትውልድ ሲሞላው ሥራ አጥነት ጣራ እንደነካ አስተውል። የታደሉ ዜጎች የቆሸሸ እጅ፣የሥራ ቱታ የለበሱ ሰውነቶች የታደሉ ናቸው። ከሰኞ እስከ አርብ መዘነጥ ከሰኞ እስከ አርብ አዕምሮም ሰውነትም ሥራ መፍታቱን የሚያሳይ የውድቀት ባንዲራ ነው !” እንዲህ ብዬ የሚሞግተኝን ሁሉ መሞገት ያሻኛል። ምክራቸው መከራ ከመጨመር ውጪ ወንዝ የማያሻግር እንቶፈንቶ ይሆንብኛልና ሁሉም መጽሐፉ እንደሚለው “የሚያደክሙ አፅናኞች” ናቸው።
በሚስቴ ሰርጥ አልፌ ወደ ሰፊው የሴትነት ባሕር ስመለከት ሴቶች ባሕሉ ብቻ ሳይሆን ልብስና
ጫማቸው ሳይቀር ካቴና ሆኖባቸው ይታየኛል።ፋሽን ነፃነታቸውን ነጥቆ፣ ምቾታቸውን ቀምቶ፣ ወንዱ ፊት የእይታ አምሮት እንዲያሳረፍ ይደረድራቸዋል። እነሱም ፍልቅልቅ እያሉ በካቴናቸው ይኮራሉ ..
ፋሽን ነዋ። እንደውም ትክክለኛው ዘመቻ መሆን ያለበት ሴቶች አደባባይ ይውጡ ሳይሆን ወደ ጓዳ ይመለሱ ነው ! ጓዳቸው ምቹ ይሁን ነው !! እግሯ እስኪቀጥን ከተማውን የምታካልል ቆንጆ የሆነ
ቀን እፎይ ዙረት ሰለቸኝ” ስትል ትሰማታለህ ..ዙረት የሴት ልጅ ተፈጥሮ አይደለማ ! በተሰጣቸው
የተፈጥሮ ፀጋ ልጆችን ሊያሳድጉ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ልጅን ለማሳደግ እግርን ሰብስቦ ቤት
ውስጥ መቀመጥ፣ ደስታን አሳልፎ መስጠት ይጠይቃል። ልጅ ጭፈራ ቤት ውስጥ አያድግም። ይሄ የዘመናችን አጉል ዘመናዊነት እንዲህ ተጣምሞ ካደገ፣ ልጆቻቸውን በጋሪ እየገፉ በደረቅ ሌሊት ጭፈራ
ቤት የሚሰየሙ እናቶችን መፍጠሩ አይቀሬ ነው።
ደግሞ እንደ ደንቃራ በመብት ስም ስለእንዝላልነት ልትሞግተኝ ፊቴ የምትደቀን እንስት ብስጭቴን
ጣራ ታስነካዋለች። “አንቺ ራስሽ እስቲ ራስሽን ተመልከች፣ ለምንድነው ፀጉርሽን ቀለም የተቀባሽው ከፊትሽ ከለር ጋር እንደሚሄድ' ባለሞያዎቹ ነግረውሽ …. ወይስ እንዲሁ ሲያደርጉ አይተሽ …. ሞኝ ነገር ነሽ … ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት አጠቃላይ የፀጉር ሞያተኞች ስንት ይሆኑ በሙያው ጥልቅ እውቀት
ያላቸው። ጥቂቶች በጣም ጥቂቶች። ሌላው የተከበረ ፊትና ፀጉርሽን ቤተ ሙከራ የሚያደርግ
የልምድ አዋላጅ' ነው ! እንግዲህ ይሄ መደዴ ፀጉር ተኳሽ ነው የፊትሽ ቅርፅ፣ የቆዳሽ ልስላሴ፣ ይሄን ቀለም ተቀቢ፣ ያንኛውን ሜካፕ ተለቅላቂ እያለ ቅዠቱን የሚመክርሽ !
እየውልሽ የፀጉር ፍሸናው አንቺን አጥፍቶ የሆነች ሌላ ሴት ማስመሰል እንጂ፣ ያለሽን ውበት ማጉላት አለመሆኑ የሚገባሽ የፍሸናውን ስም ስትሰሚ ነው፣
ቢዮንሴ ሹርባ፣
ሪሃና ቁርጥ፣
ዊትኒ ስታይል..
አንቺ ግን ስምሽ አረጋሽ ነው፣ ወላ ነጃት፣ ወላ ነፊሳ፣ ሄለን፣ ሲቲ፣ ቲቲ ሁኝ ብትፈልጊ…። ካናትሽ
ላይ ቆሞ ፀጉርሽን የሚሰራ የሚመስልሽ የፀጉር ባለሞያ በካውያው ፀጉርሽን እየተኮሰ በማያባራ ለፋፊ አንደበቱ ግን አዕምሮሽን ነው በጋለ የውበት እና ፋሽን ካውያው የሚተኩስሽ ! አንቺነትሽን ሊያተን ነው። ከዛ ምንም ከሌሎቹ ሴቶች የተለየ ውበት አይጨምርልሽም። መጨረሻ ላይ እንደሌሎች
ሴቶች ትሆኛለሽ። በቃ ይሄው ነው። ደግሞ ወንዱ ባንቺ ውበት ይደነቃል ብለሽ አትድከሚ። ወንዱ
በሚጎረጉረው ስልኩ መለዓክ የመሰሉ ሴቶች ፎቶ ላይ አፍጥጦ ነው የሚውለው፤ ምንም ብትሆኝ
አይደንቀውም፡፡ ጉዳዩ ከሰውነትሽ ነው። ከስልኩ ወዲያ አምሮት የቀሰቀሰበትን ገላ ሲያጣ አጠገቡ
ያለሽውን አንቺን እንደማስታገሻ ከማይረባ የፍቅር ዲስኩር ጋር ይወስድሻል ! የአንቺን ሥጋ አቅፎ
መንፈሱ በተመለከተው ገላ ላይ ነው የሚቃዠው…” ብቻዬን ተቀምጬ እንዲህ ነው የማስበው።ሴት ወንዱ በሽተኛ የሆነ ይመስለኛል። ለክርክር የሚያሞጠሙጠው አፉ ለምን ራሱን ለመጠየቅ
እንደማይጠቀመው ግራ ይገባኛል።
“እንደ ኳስ መካሪው ወደ ፋሽን …. ፋሽኑ ወደ ወንድ፣ ወንዱ ወደ አልጋ፣ አልጋው ወደ ተዘባረቀ ሕይወት እየተቀባበለ በሴት ልጅ ሕይወት ጨዋታውን ያሞቀ ዘመን እንደዚህ ዘመን ከቶ አልተከሰተም።ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ ነውና ዘመኑ ራሱን 'የሰለጠነ የሚል ስም አከናንቦታል ከክንብንቡ ስር … በስልጣኔ መዳፍ አፋቸውን የታፈኑ 'ስልጡን የፋሽን ባሮች ዓየር አጥሯቸው ይወራጫሉ። ለዚህ መፍትሄው ራስን መሆን ነው። በዚህ ዘመን በትክክል የሚያስፈልገው “ራስሽን ሁኚ” የሚል መካሪ ነው። ልድገመው ራስሽን ሁኚ ! የነፈሰው ንፋስ ጋር ልንፈስ ካልሽ እብድ የበላው በሶ ሆነሽ ትቀሪያለሽ... የኔን ሚስት አታያትም … ይቺን አስቀያሚ ! በክብር ካኖርኩባት ዙፋን ላይ ፀቁልቁል በአናቷ ወርዳ
፡
፡
#አራት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
....የፌቨን እናት ተቀየሙኝ። ሊያስታርቁን መጥተው፣ “ልጅዎትን ከዚህ በኋላ ማየት አልፈልግም ስላልኳቸው ተቀየሙ። ማንም ወላጅ ቢሆን ይሰማዋል። በደካማ አቅማቸው ከየትና የት ድረስ መጥተው ለማስታረቅ ሲሞክሩ እንቢ አይለኝም ብለው ነበር ያሰቡት። የእኔ ፌቨንን መጥላት ...
ርሳቸውን መናቅ መሰላቸው “አንዲት ሴት ፀጉሯን መቆረጧ ትዳር እስከማፍረስ ካደረሰ ከፍቺው ኋላ ፀጉር ብቻ ሳይሆን ሌላ ምክንያት አለ ማለት ነው” ብለው እንዲያስቡ አድርጓቸዋል። እውነት ነው
ከፌቨን ፀጉር ኋላ ሚሊየን ምክንያቶች ነበሩ፤ ሁሉም ምክንያቶች ግን መነሻቸው ፍቅር ነበር።
“ፍቅር ይታገሳል” ይሉኛል ጉዳዩን የሰሙ ሁሉ፣
ሰው በሰላሙ ቀን እግዜሩንም መጽሐፉንም አሽቀንጥሮ አሸሼ ሲል ይከርምና የቁርጥ ቀን ሲመጣ በየሥርቻው የጣለውን የሕይወት መጽሐፍ አቧራውን አራግፎ እያነሳ ሁሉም ሰባኪ፣ ሁሉም ቃል አጣቃሽ ካልሆንኩ ይላል።
“ፍቅር ይታገሳል”ይለኛል መካሪ። እንዲህ ሲሉኝ ተናገር ተናገር ጩህ ጩህ ይለኛል። “እስቲ እንዲህ
ለነፍስህ ያደርክ ከሆንክ ቃሉ እንደሚለው አታመንዝር ! አዎ አንተ ራስህ ይሄን የምትመክረኝ …
እስቲ በየስርቻው ራሳቸውን ነጥቀህ በቀለም የምታዥጎረጉራቸውን የወሲብ እቃዎችህን እንደሰው ቁጠር ! እዚህች አገር እንደ ሴት መጫወቻ የሆነ ፍጥረት አለ ... ? የማንም ወጠጤ መጥቶ የብልግና
ብሩሹን አንከርፍፎ መንገድ ላይ እንደተሰጣ ሸራ ሴቶችህ ላይ ብልግናውን ሲስል የት ነበርክ…” ማለት ያምረኛል።
አዎ ውስጤ በቁጣ ይሞላል፣ “ላንት 'መብታቸው ነው እያልክ በየመጠጥና ጫት ቤቱ እንደ ጥራጊ ማንም ሲረግጣቸው የነበሩ ሴቶችህን ስታልፍ .… ዛሬ ሴተኛ አዳሪነት፣ወሲብን አቃልሎ ማየት፣ በፋሽን ሥም ሴትነትን መንገድ ዳር አቅርቦ መቸብቸብ ሰተት ብሎ ጓዳህ ገባ! ሴቶች በጓዳ አይቅሩ አደባባይ
ይውጡ ከሚለው የሚበዛው ለሴቶች መጨቆን ያዘነ እንዳይመስልህ። በአደባባይ እንደ ፋሲካ በግ ዳሌና ሽንጥ በዓይኑ እየመተረ ለመምረጥ ነው! ምነው የሚመች ጓዳ፣ ክብር ያለው ጎጆ አግኝተው ሴቶች ጓዳቸው ውስጥ አርፈው በተቀመጡ። ግን ባትለውም ኑሮ ራሱ እየመዘዘ አደባባይ ያሰጣቸዋል።
ያውም የኛ ኑሮ…” ብዬ በአደባባይ ድፍን የአበሻ ወንድ ላይ መጮህ መደንፋት ያምረኛል።
“ለመሆኑ የሴቶችን ልብስና ጫማዎች ታዝበሃል ? ለተረት የሚመች አይደለም ሁሉም። ሴት ልጅ ከቤቷ ወጥታ ወደ መኪናዋ ከመኪና ወደ ሥራ ረጋ ያለ ሕይወት እና እንቅስቃሴ እድትኖር ታስበው የተሰሩ ናቸው። እንዳንተ ስኒከር፣ ሸራ ጫማ፣ ከስክስ አይደለም የሴቶች ጫማ ! ሴቶችህ ራሳቸው ለአደባባይ ማንነት “መብት” የሚል ሽፋን ይሰጡታል እንጂ በብዙሃኑ የከተማ ሴት አዕምሮ ውስጥ
ያለው እውነት ጥሩ ሥራ አግኝቶ ወይም አንዱን ኃብታም አግብቶ “
እርፍ” የሚል ሕልም ነው !
(ይሄ አንዳንዶችን ያበሳጫል ግን ምን ይደረግ እውነት ነው። ከተማውን ከሰኞ እስከ አርብ የዘነጠ ሽቅርቅር ትውልድ ሲሞላው ሥራ አጥነት ጣራ እንደነካ አስተውል። የታደሉ ዜጎች የቆሸሸ እጅ፣የሥራ ቱታ የለበሱ ሰውነቶች የታደሉ ናቸው። ከሰኞ እስከ አርብ መዘነጥ ከሰኞ እስከ አርብ አዕምሮም ሰውነትም ሥራ መፍታቱን የሚያሳይ የውድቀት ባንዲራ ነው !” እንዲህ ብዬ የሚሞግተኝን ሁሉ መሞገት ያሻኛል። ምክራቸው መከራ ከመጨመር ውጪ ወንዝ የማያሻግር እንቶፈንቶ ይሆንብኛልና ሁሉም መጽሐፉ እንደሚለው “የሚያደክሙ አፅናኞች” ናቸው።
በሚስቴ ሰርጥ አልፌ ወደ ሰፊው የሴትነት ባሕር ስመለከት ሴቶች ባሕሉ ብቻ ሳይሆን ልብስና
ጫማቸው ሳይቀር ካቴና ሆኖባቸው ይታየኛል።ፋሽን ነፃነታቸውን ነጥቆ፣ ምቾታቸውን ቀምቶ፣ ወንዱ ፊት የእይታ አምሮት እንዲያሳረፍ ይደረድራቸዋል። እነሱም ፍልቅልቅ እያሉ በካቴናቸው ይኮራሉ ..
ፋሽን ነዋ። እንደውም ትክክለኛው ዘመቻ መሆን ያለበት ሴቶች አደባባይ ይውጡ ሳይሆን ወደ ጓዳ ይመለሱ ነው ! ጓዳቸው ምቹ ይሁን ነው !! እግሯ እስኪቀጥን ከተማውን የምታካልል ቆንጆ የሆነ
ቀን እፎይ ዙረት ሰለቸኝ” ስትል ትሰማታለህ ..ዙረት የሴት ልጅ ተፈጥሮ አይደለማ ! በተሰጣቸው
የተፈጥሮ ፀጋ ልጆችን ሊያሳድጉ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ልጅን ለማሳደግ እግርን ሰብስቦ ቤት
ውስጥ መቀመጥ፣ ደስታን አሳልፎ መስጠት ይጠይቃል። ልጅ ጭፈራ ቤት ውስጥ አያድግም። ይሄ የዘመናችን አጉል ዘመናዊነት እንዲህ ተጣምሞ ካደገ፣ ልጆቻቸውን በጋሪ እየገፉ በደረቅ ሌሊት ጭፈራ
ቤት የሚሰየሙ እናቶችን መፍጠሩ አይቀሬ ነው።
ደግሞ እንደ ደንቃራ በመብት ስም ስለእንዝላልነት ልትሞግተኝ ፊቴ የምትደቀን እንስት ብስጭቴን
ጣራ ታስነካዋለች። “አንቺ ራስሽ እስቲ ራስሽን ተመልከች፣ ለምንድነው ፀጉርሽን ቀለም የተቀባሽው ከፊትሽ ከለር ጋር እንደሚሄድ' ባለሞያዎቹ ነግረውሽ …. ወይስ እንዲሁ ሲያደርጉ አይተሽ …. ሞኝ ነገር ነሽ … ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት አጠቃላይ የፀጉር ሞያተኞች ስንት ይሆኑ በሙያው ጥልቅ እውቀት
ያላቸው። ጥቂቶች በጣም ጥቂቶች። ሌላው የተከበረ ፊትና ፀጉርሽን ቤተ ሙከራ የሚያደርግ
የልምድ አዋላጅ' ነው ! እንግዲህ ይሄ መደዴ ፀጉር ተኳሽ ነው የፊትሽ ቅርፅ፣ የቆዳሽ ልስላሴ፣ ይሄን ቀለም ተቀቢ፣ ያንኛውን ሜካፕ ተለቅላቂ እያለ ቅዠቱን የሚመክርሽ !
እየውልሽ የፀጉር ፍሸናው አንቺን አጥፍቶ የሆነች ሌላ ሴት ማስመሰል እንጂ፣ ያለሽን ውበት ማጉላት አለመሆኑ የሚገባሽ የፍሸናውን ስም ስትሰሚ ነው፣
ቢዮንሴ ሹርባ፣
ሪሃና ቁርጥ፣
ዊትኒ ስታይል..
አንቺ ግን ስምሽ አረጋሽ ነው፣ ወላ ነጃት፣ ወላ ነፊሳ፣ ሄለን፣ ሲቲ፣ ቲቲ ሁኝ ብትፈልጊ…። ካናትሽ
ላይ ቆሞ ፀጉርሽን የሚሰራ የሚመስልሽ የፀጉር ባለሞያ በካውያው ፀጉርሽን እየተኮሰ በማያባራ ለፋፊ አንደበቱ ግን አዕምሮሽን ነው በጋለ የውበት እና ፋሽን ካውያው የሚተኩስሽ ! አንቺነትሽን ሊያተን ነው። ከዛ ምንም ከሌሎቹ ሴቶች የተለየ ውበት አይጨምርልሽም። መጨረሻ ላይ እንደሌሎች
ሴቶች ትሆኛለሽ። በቃ ይሄው ነው። ደግሞ ወንዱ ባንቺ ውበት ይደነቃል ብለሽ አትድከሚ። ወንዱ
በሚጎረጉረው ስልኩ መለዓክ የመሰሉ ሴቶች ፎቶ ላይ አፍጥጦ ነው የሚውለው፤ ምንም ብትሆኝ
አይደንቀውም፡፡ ጉዳዩ ከሰውነትሽ ነው። ከስልኩ ወዲያ አምሮት የቀሰቀሰበትን ገላ ሲያጣ አጠገቡ
ያለሽውን አንቺን እንደማስታገሻ ከማይረባ የፍቅር ዲስኩር ጋር ይወስድሻል ! የአንቺን ሥጋ አቅፎ
መንፈሱ በተመለከተው ገላ ላይ ነው የሚቃዠው…” ብቻዬን ተቀምጬ እንዲህ ነው የማስበው።ሴት ወንዱ በሽተኛ የሆነ ይመስለኛል። ለክርክር የሚያሞጠሙጠው አፉ ለምን ራሱን ለመጠየቅ
እንደማይጠቀመው ግራ ይገባኛል።
“እንደ ኳስ መካሪው ወደ ፋሽን …. ፋሽኑ ወደ ወንድ፣ ወንዱ ወደ አልጋ፣ አልጋው ወደ ተዘባረቀ ሕይወት እየተቀባበለ በሴት ልጅ ሕይወት ጨዋታውን ያሞቀ ዘመን እንደዚህ ዘመን ከቶ አልተከሰተም።ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ ነውና ዘመኑ ራሱን 'የሰለጠነ የሚል ስም አከናንቦታል ከክንብንቡ ስር … በስልጣኔ መዳፍ አፋቸውን የታፈኑ 'ስልጡን የፋሽን ባሮች ዓየር አጥሯቸው ይወራጫሉ። ለዚህ መፍትሄው ራስን መሆን ነው። በዚህ ዘመን በትክክል የሚያስፈልገው “ራስሽን ሁኚ” የሚል መካሪ ነው። ልድገመው ራስሽን ሁኚ ! የነፈሰው ንፋስ ጋር ልንፈስ ካልሽ እብድ የበላው በሶ ሆነሽ ትቀሪያለሽ... የኔን ሚስት አታያትም … ይቺን አስቀያሚ ! በክብር ካኖርኩባት ዙፋን ላይ ፀቁልቁል በአናቷ ወርዳ
👍29❤1🔥1😁1
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#አራት
እትዬ ያረፈችባቸው መነኩሲት “የኔ ልጅ አይዞሽ የበላነውን እየበላሽ ልብሽ እስከፈቀደው ጊዜ መቆየት
ችያለሽ የእግዜር ቤት ነው ቤትሽ ነው” አሉና ድርብ የሰሌን ምንጣፍ ብዙ ቦታ ላይ ብዙ ዓይነት ክርና መጣፈያ ከተጠቀመ ብርድ ልብስ ሰጧትና አንዷ ጥግ ላይ ራሳቸው አነጣጠፉላት፡፡
አለም ላይ ጭካኔ ሲፈነጭ ማን አለብኝነት በሀሴት ዋንጫ ልቅለቃውን ሲያስነካው፡ ሰብዓዊነት መቃብር ቤት ውስጥ በፍፁም ፀጥታ ከአትዬ ጋር ተገናኘ፡፡ አትዬ ከደጓ መነኩሴት ጋር በመቃብር ቤት ውስጥ ተቀመጠች፡፡ ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል ቢባልም ቅሉ ኑሮው አልሞቃትም፡፡አጥንቷ ድረስ ዘልቆ የሚያንዘፈዝፍ የፍርሀት ብርድ ሰላም ነሳት፡፡ መሄጃ የለኝም ከሚል ስጋት ለጊዜውም ቢሆን አርፋለች፡፡ ግን መቃብር ቤቱ ውሰጥ የነበራት ቆይታ የስቃይና ዮፍርሀት ነበር፡፡ሰው የተቀበረበት ቤት ውስጥ መተኛቷ ፍርሃት ለቀቀባት፡፡ ከተኛችበት ሰሌን ስር በስብሶ አፅሙ የቀረ ሬሳ ታኝቷል፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሰማችው (አሁንም ድረስ እንደምታምነው ደግሞ ሙታን አካላቸው ቢጋደምም መንፈሳቸው አርፎ አይቀመጥም፡፡ መነኩሲቷ ወጣ ካሉ ተከትላ ደጅ ትቆማለች፡፡ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርጋት አንድ ስጋው ሁሉ ረግፎ ጭራሮ የመሰሉ ጣቶቹ ብቻ የቀሩ አጥንታም እጅ የተኛችበትን መሬት ፈነቃቅሎ አንገቷን ሲያንቃት ይታያትና ኡኡታዋን ታቅልጠዋለች…ቅዠት! መነኩሲቷ አቲዬን ማረጋጋት ለአቲዬ መፀለይ ብቻ ሆነ ስራቸው::
በፍርሀት ሁለት ቀንና ሌሊት እንቅልፍ ስላልወሰዳት በሦስተኛው ቀን ምሽት እንቅልፍ እሰካራትና ሰሌኗ ላይ ኩርምት ብላ ተኛች ዓለም ገፍቶ ገፍቶ የመገነዣ ሰሌኗ ላይ የጣላት ሚስኪን ሴት፧ መነኩሲቷ በሀዘን ግንባሯን እንደ ትንሽ ልጅ እያሻሹና አተነፋፈሷ የተስተካከለ መሆኑን እያዳመጡ እንደ መልካም ወላጅ ቀስ ብለው ድራቡን አልብሰዋት ወደ ፀሎታቸው ተመለሱ::
ብዙ ሳይቆይ ትንሸዋ የመቃብር ቤት በአስደንጋጭ ጩኸት ተሞላች፡፡ እቲዬ ልጄን..ልጄን
እያለች አንደ እብድ ከመኝታዋ በርግጋ በመነሳት ራሷን ይዛ መጮህ ጀመረች፡፡ አቅመ ደካማዋ መነኩሲት አቲዬን ሊያስቆሟት አልቻሉም፡፡ የሷ ባልሆነ ጉልበት ገፈታትራቸው በሚገርም ፍጥነት ሰሌኑን ጠቅልላ የቤቱን ወለል በጥፍሯ ትቧጥጥ ጀመረች፣ "ልጄ.....ልጄን ወሰዱብኝ” እያላች በመረጋጥ ብዛት የደደረውን አፈር ትመነጭር ጀመረ፡፡
እንባዋ በጉንጮቿ ሳይ ለጉድ እየፈሰሰ፣ በላብ ተነክራ እየቃተተች ከትንንሾቹ መቃብር ቤቶች
ጩኸቷን ሰምተው የወጡ መነኮሳት ወደ እማሆይ ቤት መጥተው ተረባርበው እስኪያስቆሟት ድረስ አቲዬ በአስሩም ጥፍሯ መሬቱን እየቧጠጠችና እየቆፈረች ኡኡታዋን ማቅለጥ አላቆመችም
ነበር፡፡
ክፉ ቅዠት የዘወትር ቅዠቷ የሆነው ጭራሮ እጅ ዛሬም ከፈነቀለው መቃብር ውስጥ እጁን
ብቻ ሳይሆን ከትከሻው በላይ ነበር ተመዝዞ የወጣው አፈር እንደለበሰ…!! ከዛም በአስፈሪ
ዓይኖቹ እቲዩ ላይ አፈጠጠባት፤ አየችው ቀለመወርቅ ነበር፡፡ ያውም አፈር ከነሰነሰ ባርኔጣና
ካፖርታው !! "ልጄን አምጪ” ብሎ አጥንታም እጁን ወደ ሆዷ ላከና በቅፅበት አንድ ቀይ የሚያምር ሕፃን ይዞ ተመለሰ፡፡ ሆዷ ባዶ ሲሆን ታያት፤ ቀለላት፡፡ ልጇን በደስታ ትመለከተውና ወደ ውስጥ ወደ መሬት ይዞት ሰረገ፡፡ ልክ ጫጩት ነጥቆ ወደ ጉድጓዱ እንደሚገባ ሸለምጥማጥ'
መሬቱን ከፍቶ ሲገባ፣ መጋረጃ ገልጦ የገባ ነበር የሚመስለው፡፡
በቀጣዩ ቀን አባ እስጢፋኖስ ሁኔታው ሲነገራቸው ድሮም ለአቲዬ ቋሚ መኖሪያ ሲያፈላልጉ ነበርና ፍለጋውን አፋጥነው ከሁለት ቀን በኋላ በፊት ትኖርበት ወደ ነበረው መንደር ወስደው አንዲት ከዋናው የቀበሌ አጥር ጋር ተያይዛ የተሰራች የቆርቆሮ ቤት ውስጥ አስገቧት፡፡ የመንደሩ እድር እቃ ማስቀመጫ ነበረች፡፡ የእቃ ማስቀመጫዋ ቤት ጣራና ግድግዳዋ በድንብ ስላልገጠመ፣ ሌሊት ብርዱ ቀን ፀሐዩ በክፍተቱ ውስጥ እያለፈ ይገባ ነበር፡፡ አባ እስጢፋኖስ ከንሰሀ ልጆቻቸው ለምነውም ተለማምጠውም ያገኟቸውን አሮጌ ፍራሽ፣ ብርድ ልብስና የውሀ መያዣ ጎማ ለእቲዬ እያሳዩ እንደምታውቂው ቤሳ ቤስቲን የሌላኝ የእግዚሃር አገልጋይ ነኝ፡፡ ከዚህ የተሻለ ባይሆን ጎንሽን ማሳረፊያ ካገኘሽ ሌላው ሌላው በፈጣሪ ፈቃድ ቀስ እያለ ይሟላል እኔም እየመጣሁ አይሻለሁ።" ብለዋት ሄዱ።
የእድሩ ድንኳን፡ እንጨቶች፣ ወንበሮችና ስጋጃ ምንጣፎች በአንድ በኩል ተሰድረው ገባ ብሎ ወደ ውስጥ ካለችው ትርፍ ቦታ ላይ ደግሞ የአቲዬ ፍራሽ ተዘርግታለች፡፡ ብዙ ጊዜ ሞት ወይም መርዶ ሰለሚኖር የእድሩ እቃ አይኖርም፡፡ ስለዚህ ሰፋ ትላለች ቤቷ፡፡ አንዳንዴ ደግሞ
እድርተኛው እቃውን ሲመልስ በግዴለሽነት ወንበሩን፣ እንጨቱን ከባባዶቹን ምንጣፎች አቲዩ
መኝታ ላይ ጥለውት ይሄዱ ስለነበር ያንን ሁሉ ጓዝ ጎትቶ ቦታ ማስያዙ ለአንዲቷ ነፍሰ ጡር ሴት ፈተና ነበር።
አትዬ ግን ታደርገዋለች፣ እንዲህ አታድርጉ” አትል ነገር ሆሆ ወደዛ ውጪ ቢሏትስ፡፡
አባ እስጢፋኖስ ብዙ ቤት ሊያስቀጥሯት ደክመው ነበር፡፡ ይሁንና ቀጣሪዎቹ ነፍሰ ጡር
መሆኗን ሲሰሙ ሁሉም አቲዬን ቤታቸው ማስገባት አልፈለጉም፡፡ አባ ቢጨንቃቸው የአቲዬ ነገር
ሰላም ቢነሳቸው አቲዩን ለዚህ ሁሉ መከራ የዳረገቻት ዘርፈ ቤት ሳይቀር ሄዱና፣ እችን ደሀ ይቅር በያት ባክሽ ብለው ታማፀኑ፡፡
አይይይይ አባ ምነው እያወቁት… እንደ ልጆቼ አንከብካቤ በያዘኩ አይደለም እንዴ ጥጋብ ፈንቅሏት ለመንደሩ ሁሉ ስሜን አጥፍታው የሄደች” አለች አቃጣሪዋ፡፡ አባን በአፍ መሸንገል
እግዜርን መሸንገል ይመስል የአቲዬን በደለኝነት ስትዘረዝር ደስ እያላት ነበር፡፡
ልጅ አይደለችም እንደ ወለተማሪያም ደግሞስ አንች ቤት ከመቼ ወዲህ ነው ይቅርታ የነጠፈው ተይ እንጂ” አሉ አባ፡፡
በዛብኛ አባ በዛብኝ ...ምን በደልኩ እናት በሆንኳት…የበላሁትን ባበላሁ የለበስኩትን ባለበስኩ ሰው ሁኝ፣ ሰልጥኝ!' ባልኩ ይሄ ይገባኝ ነበር እንባ እየተናነቃት አባ ፊት በደሏን ዘረዘረች እች አስመሳይ!!
ይሄው የትም ስትንዘላዘል ዲቃላዋን ይዛ አረፈችው” አለች ዘርፌ፡፡ ከእኔ የተጣላ እጣ ፋንታው
ውድቀት ነው" ልትል እየዳዳት…፡፡
አባ እንደሆኑ የአቲዬን ነፍስ መታደግ ይቅደም ብለው እንጂ የቀለመወርቅንና የዘርፌን ሴራ ውስጣቸው ያውቀዋል፡፡ አንዳንዴ የእግዜር አገልጋይ ከመሆን ሽፍታ በሆንኩ፡ ነፍስ ገዳይ በሆንኩ የሚያስብሉ እንደ ዘርፌ ዓይነት ገርፈው የሚጮኹ ጅራፎች ሲያጋጥሙ የንስሀ አባቶች
ልብ ምን ያህል ይሰበር ይሆን? ቢቻል ጥምጣምና መስቀልን ላንዴ አስቀምጦ ምንሽር መታጠቅና እንዲህ አይነቶቹን እድሜ ጠገብ እባቦች ግንባር ግንባራቸውን ማለት ነበር፡፡
ዘርፈ hዚህ ሀሉ ፉከራና ማስመሰል በኋላ እቲዬን ቤቷ እንደማትመልሳትና ከፈለገች ተመላልሳ ላሞቹን የመንከባከብ ልብስ የማጠብ ስራ እንድትሰራ በወር 10 ብር ልትከፍላት ለአባ ቃል ገባች፡፡
“ያው ለነፍሴ ብዬ እንጂ የደረሰች እርጉዝ ምኗ እለቻቸው ሰእባ፡፡
“ግዴለም ወለተማሪያም መቼስ ሰው እንዳረገዘ አይኖር ሁሉ ነገር ሲወለድ ጊዜ አለው፡፡ ደግሜ ይሁን ክፉ ተረግዞ አይቀርም፣ ነገን ነው ማየት” አሉ አባ፡፡ የቄስ ምንሽሩ ቅኔ ነው ተኮሱባት
አባ!
የቅኔ ጥይት ከተኳሹ እስከ ኢላማው ለመድረስ ጊዜ ይወስዳል፡፡ ለዛ ነው ዘርፈ አባ እግር ስር ድፍት ያላለችው ይድፋትና!! አባ እውነት ነበራቸው፣ እንደ ተረገዘ የሚኖር በደል የለም ይወለዳል አንድ ቀን፡፡
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#አራት
እትዬ ያረፈችባቸው መነኩሲት “የኔ ልጅ አይዞሽ የበላነውን እየበላሽ ልብሽ እስከፈቀደው ጊዜ መቆየት
ችያለሽ የእግዜር ቤት ነው ቤትሽ ነው” አሉና ድርብ የሰሌን ምንጣፍ ብዙ ቦታ ላይ ብዙ ዓይነት ክርና መጣፈያ ከተጠቀመ ብርድ ልብስ ሰጧትና አንዷ ጥግ ላይ ራሳቸው አነጣጠፉላት፡፡
አለም ላይ ጭካኔ ሲፈነጭ ማን አለብኝነት በሀሴት ዋንጫ ልቅለቃውን ሲያስነካው፡ ሰብዓዊነት መቃብር ቤት ውስጥ በፍፁም ፀጥታ ከአትዬ ጋር ተገናኘ፡፡ አትዬ ከደጓ መነኩሴት ጋር በመቃብር ቤት ውስጥ ተቀመጠች፡፡ ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል ቢባልም ቅሉ ኑሮው አልሞቃትም፡፡አጥንቷ ድረስ ዘልቆ የሚያንዘፈዝፍ የፍርሀት ብርድ ሰላም ነሳት፡፡ መሄጃ የለኝም ከሚል ስጋት ለጊዜውም ቢሆን አርፋለች፡፡ ግን መቃብር ቤቱ ውሰጥ የነበራት ቆይታ የስቃይና ዮፍርሀት ነበር፡፡ሰው የተቀበረበት ቤት ውስጥ መተኛቷ ፍርሃት ለቀቀባት፡፡ ከተኛችበት ሰሌን ስር በስብሶ አፅሙ የቀረ ሬሳ ታኝቷል፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሰማችው (አሁንም ድረስ እንደምታምነው ደግሞ ሙታን አካላቸው ቢጋደምም መንፈሳቸው አርፎ አይቀመጥም፡፡ መነኩሲቷ ወጣ ካሉ ተከትላ ደጅ ትቆማለች፡፡ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርጋት አንድ ስጋው ሁሉ ረግፎ ጭራሮ የመሰሉ ጣቶቹ ብቻ የቀሩ አጥንታም እጅ የተኛችበትን መሬት ፈነቃቅሎ አንገቷን ሲያንቃት ይታያትና ኡኡታዋን ታቅልጠዋለች…ቅዠት! መነኩሲቷ አቲዬን ማረጋጋት ለአቲዬ መፀለይ ብቻ ሆነ ስራቸው::
በፍርሀት ሁለት ቀንና ሌሊት እንቅልፍ ስላልወሰዳት በሦስተኛው ቀን ምሽት እንቅልፍ እሰካራትና ሰሌኗ ላይ ኩርምት ብላ ተኛች ዓለም ገፍቶ ገፍቶ የመገነዣ ሰሌኗ ላይ የጣላት ሚስኪን ሴት፧ መነኩሲቷ በሀዘን ግንባሯን እንደ ትንሽ ልጅ እያሻሹና አተነፋፈሷ የተስተካከለ መሆኑን እያዳመጡ እንደ መልካም ወላጅ ቀስ ብለው ድራቡን አልብሰዋት ወደ ፀሎታቸው ተመለሱ::
ብዙ ሳይቆይ ትንሸዋ የመቃብር ቤት በአስደንጋጭ ጩኸት ተሞላች፡፡ እቲዬ ልጄን..ልጄን
እያለች አንደ እብድ ከመኝታዋ በርግጋ በመነሳት ራሷን ይዛ መጮህ ጀመረች፡፡ አቅመ ደካማዋ መነኩሲት አቲዬን ሊያስቆሟት አልቻሉም፡፡ የሷ ባልሆነ ጉልበት ገፈታትራቸው በሚገርም ፍጥነት ሰሌኑን ጠቅልላ የቤቱን ወለል በጥፍሯ ትቧጥጥ ጀመረች፣ "ልጄ.....ልጄን ወሰዱብኝ” እያላች በመረጋጥ ብዛት የደደረውን አፈር ትመነጭር ጀመረ፡፡
እንባዋ በጉንጮቿ ሳይ ለጉድ እየፈሰሰ፣ በላብ ተነክራ እየቃተተች ከትንንሾቹ መቃብር ቤቶች
ጩኸቷን ሰምተው የወጡ መነኮሳት ወደ እማሆይ ቤት መጥተው ተረባርበው እስኪያስቆሟት ድረስ አቲዬ በአስሩም ጥፍሯ መሬቱን እየቧጠጠችና እየቆፈረች ኡኡታዋን ማቅለጥ አላቆመችም
ነበር፡፡
ክፉ ቅዠት የዘወትር ቅዠቷ የሆነው ጭራሮ እጅ ዛሬም ከፈነቀለው መቃብር ውስጥ እጁን
ብቻ ሳይሆን ከትከሻው በላይ ነበር ተመዝዞ የወጣው አፈር እንደለበሰ…!! ከዛም በአስፈሪ
ዓይኖቹ እቲዩ ላይ አፈጠጠባት፤ አየችው ቀለመወርቅ ነበር፡፡ ያውም አፈር ከነሰነሰ ባርኔጣና
ካፖርታው !! "ልጄን አምጪ” ብሎ አጥንታም እጁን ወደ ሆዷ ላከና በቅፅበት አንድ ቀይ የሚያምር ሕፃን ይዞ ተመለሰ፡፡ ሆዷ ባዶ ሲሆን ታያት፤ ቀለላት፡፡ ልጇን በደስታ ትመለከተውና ወደ ውስጥ ወደ መሬት ይዞት ሰረገ፡፡ ልክ ጫጩት ነጥቆ ወደ ጉድጓዱ እንደሚገባ ሸለምጥማጥ'
መሬቱን ከፍቶ ሲገባ፣ መጋረጃ ገልጦ የገባ ነበር የሚመስለው፡፡
በቀጣዩ ቀን አባ እስጢፋኖስ ሁኔታው ሲነገራቸው ድሮም ለአቲዬ ቋሚ መኖሪያ ሲያፈላልጉ ነበርና ፍለጋውን አፋጥነው ከሁለት ቀን በኋላ በፊት ትኖርበት ወደ ነበረው መንደር ወስደው አንዲት ከዋናው የቀበሌ አጥር ጋር ተያይዛ የተሰራች የቆርቆሮ ቤት ውስጥ አስገቧት፡፡ የመንደሩ እድር እቃ ማስቀመጫ ነበረች፡፡ የእቃ ማስቀመጫዋ ቤት ጣራና ግድግዳዋ በድንብ ስላልገጠመ፣ ሌሊት ብርዱ ቀን ፀሐዩ በክፍተቱ ውስጥ እያለፈ ይገባ ነበር፡፡ አባ እስጢፋኖስ ከንሰሀ ልጆቻቸው ለምነውም ተለማምጠውም ያገኟቸውን አሮጌ ፍራሽ፣ ብርድ ልብስና የውሀ መያዣ ጎማ ለእቲዬ እያሳዩ እንደምታውቂው ቤሳ ቤስቲን የሌላኝ የእግዚሃር አገልጋይ ነኝ፡፡ ከዚህ የተሻለ ባይሆን ጎንሽን ማሳረፊያ ካገኘሽ ሌላው ሌላው በፈጣሪ ፈቃድ ቀስ እያለ ይሟላል እኔም እየመጣሁ አይሻለሁ።" ብለዋት ሄዱ።
የእድሩ ድንኳን፡ እንጨቶች፣ ወንበሮችና ስጋጃ ምንጣፎች በአንድ በኩል ተሰድረው ገባ ብሎ ወደ ውስጥ ካለችው ትርፍ ቦታ ላይ ደግሞ የአቲዬ ፍራሽ ተዘርግታለች፡፡ ብዙ ጊዜ ሞት ወይም መርዶ ሰለሚኖር የእድሩ እቃ አይኖርም፡፡ ስለዚህ ሰፋ ትላለች ቤቷ፡፡ አንዳንዴ ደግሞ
እድርተኛው እቃውን ሲመልስ በግዴለሽነት ወንበሩን፣ እንጨቱን ከባባዶቹን ምንጣፎች አቲዩ
መኝታ ላይ ጥለውት ይሄዱ ስለነበር ያንን ሁሉ ጓዝ ጎትቶ ቦታ ማስያዙ ለአንዲቷ ነፍሰ ጡር ሴት ፈተና ነበር።
አትዬ ግን ታደርገዋለች፣ እንዲህ አታድርጉ” አትል ነገር ሆሆ ወደዛ ውጪ ቢሏትስ፡፡
አባ እስጢፋኖስ ብዙ ቤት ሊያስቀጥሯት ደክመው ነበር፡፡ ይሁንና ቀጣሪዎቹ ነፍሰ ጡር
መሆኗን ሲሰሙ ሁሉም አቲዬን ቤታቸው ማስገባት አልፈለጉም፡፡ አባ ቢጨንቃቸው የአቲዬ ነገር
ሰላም ቢነሳቸው አቲዩን ለዚህ ሁሉ መከራ የዳረገቻት ዘርፈ ቤት ሳይቀር ሄዱና፣ እችን ደሀ ይቅር በያት ባክሽ ብለው ታማፀኑ፡፡
አይይይይ አባ ምነው እያወቁት… እንደ ልጆቼ አንከብካቤ በያዘኩ አይደለም እንዴ ጥጋብ ፈንቅሏት ለመንደሩ ሁሉ ስሜን አጥፍታው የሄደች” አለች አቃጣሪዋ፡፡ አባን በአፍ መሸንገል
እግዜርን መሸንገል ይመስል የአቲዬን በደለኝነት ስትዘረዝር ደስ እያላት ነበር፡፡
ልጅ አይደለችም እንደ ወለተማሪያም ደግሞስ አንች ቤት ከመቼ ወዲህ ነው ይቅርታ የነጠፈው ተይ እንጂ” አሉ አባ፡፡
በዛብኛ አባ በዛብኝ ...ምን በደልኩ እናት በሆንኳት…የበላሁትን ባበላሁ የለበስኩትን ባለበስኩ ሰው ሁኝ፣ ሰልጥኝ!' ባልኩ ይሄ ይገባኝ ነበር እንባ እየተናነቃት አባ ፊት በደሏን ዘረዘረች እች አስመሳይ!!
ይሄው የትም ስትንዘላዘል ዲቃላዋን ይዛ አረፈችው” አለች ዘርፌ፡፡ ከእኔ የተጣላ እጣ ፋንታው
ውድቀት ነው" ልትል እየዳዳት…፡፡
አባ እንደሆኑ የአቲዬን ነፍስ መታደግ ይቅደም ብለው እንጂ የቀለመወርቅንና የዘርፌን ሴራ ውስጣቸው ያውቀዋል፡፡ አንዳንዴ የእግዜር አገልጋይ ከመሆን ሽፍታ በሆንኩ፡ ነፍስ ገዳይ በሆንኩ የሚያስብሉ እንደ ዘርፌ ዓይነት ገርፈው የሚጮኹ ጅራፎች ሲያጋጥሙ የንስሀ አባቶች
ልብ ምን ያህል ይሰበር ይሆን? ቢቻል ጥምጣምና መስቀልን ላንዴ አስቀምጦ ምንሽር መታጠቅና እንዲህ አይነቶቹን እድሜ ጠገብ እባቦች ግንባር ግንባራቸውን ማለት ነበር፡፡
ዘርፈ hዚህ ሀሉ ፉከራና ማስመሰል በኋላ እቲዬን ቤቷ እንደማትመልሳትና ከፈለገች ተመላልሳ ላሞቹን የመንከባከብ ልብስ የማጠብ ስራ እንድትሰራ በወር 10 ብር ልትከፍላት ለአባ ቃል ገባች፡፡
“ያው ለነፍሴ ብዬ እንጂ የደረሰች እርጉዝ ምኗ እለቻቸው ሰእባ፡፡
“ግዴለም ወለተማሪያም መቼስ ሰው እንዳረገዘ አይኖር ሁሉ ነገር ሲወለድ ጊዜ አለው፡፡ ደግሜ ይሁን ክፉ ተረግዞ አይቀርም፣ ነገን ነው ማየት” አሉ አባ፡፡ የቄስ ምንሽሩ ቅኔ ነው ተኮሱባት
አባ!
የቅኔ ጥይት ከተኳሹ እስከ ኢላማው ለመድረስ ጊዜ ይወስዳል፡፡ ለዛ ነው ዘርፈ አባ እግር ስር ድፍት ያላለችው ይድፋትና!! አባ እውነት ነበራቸው፣ እንደ ተረገዘ የሚኖር በደል የለም ይወለዳል አንድ ቀን፡፡
👍23🥰1