ጓደኛ ነው:: አብርሃም ነው፡፡
ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡
ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡
“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::
“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡
ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡
ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡
ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…
የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡
#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡
#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡
#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡
#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡
#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡
ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....
💫ይቀጥላል💫
ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡
ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡
“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::
“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡
ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡
ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡
ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…
የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡
#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡
#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡
#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡
#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡
#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡
ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....
💫ይቀጥላል💫
👍2
#ቀስ_ብሎ_ይቆማል
፡
፡
#አምስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከሃኒባል ጋር ሆነን ያልረገጥነው የባሕል ሕክምና አዋቂ ቤት የለም፤ ደከመን። ሃኒባል ለእኔ ሲል
ያለችውን የዓመት እረፍት ጨርሶ ካለ ክፍያ አንድ ሳምንት ከሥራው ቀረ። ግን ምን ያደርጋል፣ ሁሉም
ነገር ከንቱ ልፋት ብቻ ሆነ። የሄድንባቸው ሁሉ ለእኔ ችግር መፍትሔ ማምጣት ይቅርና፣ ማፅናናት እንኳን ያልፈጠረባቸው አጋሰስ ነጋዴዎች ነበሩ። ቢጨንቀን አንድ ሁለት የልብ ጓደኞቻችንን ጨምረን
ጉዳዩን ነገርናቸው።ኣንዱ ጓደኛችን ለትምሕርት ውጭ ቆይቶ ገና መመለሱ ነበረ፤ ማይክሮባይሎጅ
ነው።
ጉዳዩን በጥሞና አዳመጠና፣ “…እስቲ እንዲት ውጭ ኣብረን የተማርን የስነልቦና ባለሞያ አውቃለሁ”አለ። ደስ የምትል የተረጋጋች ልጅ ጋር ወሰደኝ። ቢሮዋ ይገርማል፤ ሁሉም ነገር ነጭ ከእስከርብቶና ወረቀቱ ውጭ። ተነስታ ተቀበለችን። ከአንድ ሰዓት በላይ ያወራሁ ሳይመስለኝ ብዙ አስወራችኝ
“እኔ የምልህ አብርሃምም
እ ?"
ፍቅረኛህ ምናልባት ከቤተሰብህ አንድኛቸውጋ በመልከ ወይ በባሕሪ ትመሳሰል ይሆን?ፀ
"ኧረ በጭራሽ !እህቴ አፍንጫ የሚባል ነገር አልፈጠረባትም፣ ሙና'ኮ ሰልካካ ናት። እህቴ ከማጠር ብዛት ከራሷ ቦርሳ ቻፕስቲክ ለማውጣት እንኳን ወንበር ላይ ቆማ ነው፤ ሙና'ኮ መለሎ ፈገግ አለች
የሥነልቦና ባለሞያዋ። ጥርሶቿ ያማምራሉ (ልብ አይሞት አሁንም ሴት አደንቃለሁ)
እናቴም ብትሆን ቁመቷ እህቴ ነው የወጣችው። በዛ ላይ እናቴ ጠይም ሙና እኮ ዝም አልኩ!
ምናልባት የወሲብ ፊልሞችን ትመለከት ነበር እንዴ ?
“ኧረ አይቼ አላውቅም" እውነቴን ነበር።
“ቤተሰባችሁ ውስጥ የሚበዙት ሴቶች ናቸው ወንዶች ?
“ልጆቹ እኔና እህቴ ነን.… በቃ ! የሥነልቦና ባለሞያዋ የሆነ ነገር ቀይ ወረቀት ላይ በቀይ እስክርቢቶ
ስትጽፍ ቆየችና፣ (እንዴት እንደሚታያት እኔጃ
«ኃይማኖት ላይ እንዴት ነህ ?» «ታጠብቃለህ ?”
«ኧረ የለሁበትም።"
ቤተከርስቲያን የሄድኩት ራሱ ኢህአዴግ አዲስ ኣበባን ሲቆጣጠር የበቅሎ ቤቱ
ፍንዳታ ጊዜ፡ እናቴ ሚካኤል ልትደበቅ ስትሄድ እጄን ይዛኝ ነው ከዛ በኋላ ሄጄ አላውቅም
ፍቅረኛህ ሌላ ወንድ ጋር ግንኙነት አላት ብለህ ታስባለህ ?”
ማን ሙና … ኧረረረረረረረረረረ"
ከዚህ በፊት ከሌላ ሴት ጋር ወሲብ ያልፈጸምከው ለምንድን ነው ”
"እኔጃ"
"ሴን ትፈራለህ እንዴ ?
"መፍራት ሳይሆን እንዲሁ መቅረብ ብዙም አልፈልግም።” ወንበሯ ላይ ተመቻችታ ወደኔ ዘንበል አለችና (ጡቶቿ አፈጠጡብኝ)
“ለምን ?” ስትል ጠየቀችኝ፤ ቁልፉን ያገኘችው ሳይመስላት አልቀረም።
ረዥም ሰዓት በስልክ እንዳያወሩኝና ሸኘኝ እንዳይሉኝ … ! ስል መለስኩላት። እንደው ይህ ምላሽ መታበይ ይመስል ይሆናል እንጂ ማንንም እንደመሸኘትና እና በስልክ እንደማውራት የምጠላው ነገር
የለም። እኔም ሲሸኙኝ አልወድም፤ ሰውም መሸኘት ያንገሸግሽኛል። ምንድን ነው መጓተት፣ ምንድነው
ስልክ ላይ ተለጥፎ ማላዘን ? እንዴት እንደሚያስጠላኝ ! ስልከ አልወድም።
እሺ አብርሽ ጨርሰናል፣ ስልክህን ስጠኝና እደውልልሃለሁ” እርፍ!!
የሥነልቦና ባለሞያዋ እየደወለች ልትረዳኝ ብትሞከርም ነገሩ ዋጋ አልነበረውም። የበለጠ ስለጉዳዩ
ባሰብኩ ቁጥር በእግሮቼ መሃል ሳይሆን በፍርሃት መሃል ቁም ነገሩ ጠፋ። ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም !! ወዶ ነው አበሻ፣ “ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ" የሚለው። ትውልድን የሚሻገር ሕያው ድምጽ
መፈጠሪያው የት እንደሆነ ሲገባው እንጂ ! ኤዲያ!ወንድነት ደገፍ ብሎ የሚኮፈስበት ከዘራ ሸንበቆ ሲሆን አለ ከልብ የሚሰነጠር ወኔ ከተራ ብልግና የገዘፈ ሃቅ፤ ቃጭሉም ዝም ! ቤቴ ውስጥ ካሉት እቃዎች ምን አስጠላሀ ብባል አልጋዬ። የተሸነፍኩበት፣ የተማረክኩበት፣ የቆሰልኩበትና የተሰዋሁበት
ጦር ማዴ መስሎ ታየኝ። “ወኔዬን ያፈሰስኩበት አልጋ እኮ ነው ብዬ የልጅ ልጆቼ ላይ እኮፈስበት
ይሆናል። ያኔ ወኔው ያፈሰሰ ትውልድ ነፍ ነው የሚሆነው ! ወኔ ቢስነትም ክብር!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙና ልትመጣ አስራ አንድ ቀናት ቀሩ ። አስራ አንድ የሽብር ቀናት ! “አብርሽ ፈራህ እንዴ ?ሂሂሂሂሂ
እንደ ቀልድ ትጠይቃለች። ለምን ጀግና ለመምሰል እንደምጣጣር ለራሴም አይገባኝ፤ ፈርቻለው
አይደል እንዴ ? አዎ ፈርቻለሁ ብላት ምን ነበር ? እኔ ግን ኮስተር ብዬ እንዲህ አልኳት፣ “ለምኑ ነው
የምፈራው?
“ለብር አምባሩ ነዋ አለችና ትንፋሽ እስኪያጥራት በሳቅ ፈረሰች። ሳቋ ውስጥ ሺ ጊዜ ፍራ እንጂ
አሁንማ ቁርጥ ነው የሚል ንዝረት አለ። እኔ'ኮ የሚገርመኝ “ብር አምባር” ከእንትን” ጋር ምን
አገናኘው? እውነቴን እኮ ነው … ብዙ ወንዶች ከአንዲት ሴት ጋር ወሲብ ሊፈፅሙ “ፈረሱም ሜዳውም ያውላችሁ” ሲባሉ በስሜት ስለሚሳከሩ እንኳን ቃል ሊሰነጥቁና ሊመረምሩ አልጋ ላይ ይሁኑ ዓየር ላይ የሚያውቁት ከተረጋጉ በኋላ ነው። ከዛ በፊትማ ብር ይልሰር አምባር ይሰበር ብርጭቆ ይሰበር ቅስም
ይሰበር ምን ግዳቸው "ሰማዩን ሰበረው ጀግናው” ቢባልም አይሰሙም፤ እኔ ግን የያዘ ይዞኝ ቀልቤን አሰላሳይ አድርጓታልና “ብር አምባር” ከድንግልና ጋር ምን አገናኘው ብዬ አስባለሁ -- (ሰው ወዶ ፈላስፋ አይሆንም መቼስ ይሄ ሁሉ ሚዜ እና ታዳሚ ላንቃው እስኪደርቅ በየሰርግ ቤቱ“ብር አምባር ሰበረልዎ ጀግናው ልጅዎ እያለ ይዝፈነው እንጂ “ድንግልናን ከብር አምባር ምን አገናኘው ለሚለው ጥያቄ መልስ ያለው አይመስለኝም።
እኔ ግን ዝም ብዬ ሳስሰው፣ “ብር አምባር መስበር አስገድዶ ከመድፈር ጋር “ጥብቅ ቁርኝት ያለው ጉዳይ ይመስለኛል። ልጅቱ የብር አምባር እጇ ላይ አጥልቃለች፤ ያው ሴት የብር አምባር ማድረጓ ከጥንት የተለመደ ነገር ነው) እና ባሏ ወላ ወዳጇ እጇን ይይዛታል .… (ያዝ እጆን) እንዲል ዘፈኑ ከዛ ለማምለጥ ወይም ራሷን ለማዳን እንዳቅሟ መታገሏ አይቀርም፤ መቼስ ዝም ብሎ ያውልህ አይባልም።
በሩን ይዘጋል (ዝጋ ደጇን) እንዲል ቀጣዩ የዘፈኑ ስንኝ፤ ትግሉ ከበረታ እጇን ጠምዝዞ ጉንጯን (ሳም ጉንጯን ) የሚለው ልክ መጣ። ለከንፈሯ ያሞጠሞጠው ከንፈር በልጅቱ መወራጨት ስቶ
ጉንጯ ላይ አርፎም ሊሆን ይችላል፣ ወይም አየር ላይ እንደ ርችት የከሸፈ መሳም ብትን ! ሲታገላታ እጇ ላይ ያለው አምባር ስብር ! ከሽ ! “ይሰበር የታባቱ ቅዳሜ ገበያ ስወጣ ሌላ እገዛልሻለሁ ያውም ወርቅ የመስለ” እያለ ወደ ጉዳዩ !
እንዲህ የሚያስለፈሰፈኝ ወድጄ አይደለም፤ አምባሩ እኔ እጅ ላይ ያለ እስኪመስለኝ መዘዜ ሊመዘዝ
አስራ አንድ ቀን ቢቀረኝ እንጂ። ሙና ይቅርታ አታውቅም ! በአሁኑ ጉብኝቷ ጉንጯን ስሜ ብልካት
እርሷም እንደ ይሁዳ ስማ ነው ለብቸኝነት ስቅላቴ የምትሸጠኝ። ሙናን እኮ አፈቅራታለሁ። እንደ
ቀልድ ሳጣት ነው በቃ ? እሺ አሁን የእኔ ጥፋት ምንድን ነው? የሙና ጥፋትስ ? እግዚኣብሔር ግን
ምን አደረግኩት ? እስኪ አሁን ማን ይሙት ሊቃጣኝ ፈልጎ ከሆነ ሌላ ልምጭ አጥቶ ነው !? ለምሳሌ ሰፈራችንን በጎርፍ አጥለቅልቆ እኔን ብቻ በመግደል ዜና ማድረግ አይችልም ? መንገድ ላይ ሱክ ሱክ ስል መብረቅ አውርዶ ድምጥማጤን ማጥፋት ያቅተዋል ? ምን አድርጌው ከማን የተለየ ጥፋትና በደል ሰርቼ በውርደት የምወዳትን ልጅ ዓይኔ እያየ ያስነጥቀኛል ? አባታችን አብርሃም እንኳን በዘጠና ስንት
አሙቱ ተሳክቶለት ልጅ ሲወልድ እኔን ሚስኪኑ በሃያ ሰባት አመቴ እንዲህ ጉድ ስሆን እግዜር እንዴት
ሆዱ ቻለ ?
'አብርሽ” እለኝ ሃኒባል፣
"እ"
“ግን ችግሩ ከሙና ቢሆንስ ?"
“እንዴዴዴዴዴ ምን አገናኘው ከሙና ጋር”
፡
፡
#አምስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከሃኒባል ጋር ሆነን ያልረገጥነው የባሕል ሕክምና አዋቂ ቤት የለም፤ ደከመን። ሃኒባል ለእኔ ሲል
ያለችውን የዓመት እረፍት ጨርሶ ካለ ክፍያ አንድ ሳምንት ከሥራው ቀረ። ግን ምን ያደርጋል፣ ሁሉም
ነገር ከንቱ ልፋት ብቻ ሆነ። የሄድንባቸው ሁሉ ለእኔ ችግር መፍትሔ ማምጣት ይቅርና፣ ማፅናናት እንኳን ያልፈጠረባቸው አጋሰስ ነጋዴዎች ነበሩ። ቢጨንቀን አንድ ሁለት የልብ ጓደኞቻችንን ጨምረን
ጉዳዩን ነገርናቸው።ኣንዱ ጓደኛችን ለትምሕርት ውጭ ቆይቶ ገና መመለሱ ነበረ፤ ማይክሮባይሎጅ
ነው።
ጉዳዩን በጥሞና አዳመጠና፣ “…እስቲ እንዲት ውጭ ኣብረን የተማርን የስነልቦና ባለሞያ አውቃለሁ”አለ። ደስ የምትል የተረጋጋች ልጅ ጋር ወሰደኝ። ቢሮዋ ይገርማል፤ ሁሉም ነገር ነጭ ከእስከርብቶና ወረቀቱ ውጭ። ተነስታ ተቀበለችን። ከአንድ ሰዓት በላይ ያወራሁ ሳይመስለኝ ብዙ አስወራችኝ
“እኔ የምልህ አብርሃምም
እ ?"
ፍቅረኛህ ምናልባት ከቤተሰብህ አንድኛቸውጋ በመልከ ወይ በባሕሪ ትመሳሰል ይሆን?ፀ
"ኧረ በጭራሽ !እህቴ አፍንጫ የሚባል ነገር አልፈጠረባትም፣ ሙና'ኮ ሰልካካ ናት። እህቴ ከማጠር ብዛት ከራሷ ቦርሳ ቻፕስቲክ ለማውጣት እንኳን ወንበር ላይ ቆማ ነው፤ ሙና'ኮ መለሎ ፈገግ አለች
የሥነልቦና ባለሞያዋ። ጥርሶቿ ያማምራሉ (ልብ አይሞት አሁንም ሴት አደንቃለሁ)
እናቴም ብትሆን ቁመቷ እህቴ ነው የወጣችው። በዛ ላይ እናቴ ጠይም ሙና እኮ ዝም አልኩ!
ምናልባት የወሲብ ፊልሞችን ትመለከት ነበር እንዴ ?
“ኧረ አይቼ አላውቅም" እውነቴን ነበር።
“ቤተሰባችሁ ውስጥ የሚበዙት ሴቶች ናቸው ወንዶች ?
“ልጆቹ እኔና እህቴ ነን.… በቃ ! የሥነልቦና ባለሞያዋ የሆነ ነገር ቀይ ወረቀት ላይ በቀይ እስክርቢቶ
ስትጽፍ ቆየችና፣ (እንዴት እንደሚታያት እኔጃ
«ኃይማኖት ላይ እንዴት ነህ ?» «ታጠብቃለህ ?”
«ኧረ የለሁበትም።"
ቤተከርስቲያን የሄድኩት ራሱ ኢህአዴግ አዲስ ኣበባን ሲቆጣጠር የበቅሎ ቤቱ
ፍንዳታ ጊዜ፡ እናቴ ሚካኤል ልትደበቅ ስትሄድ እጄን ይዛኝ ነው ከዛ በኋላ ሄጄ አላውቅም
ፍቅረኛህ ሌላ ወንድ ጋር ግንኙነት አላት ብለህ ታስባለህ ?”
ማን ሙና … ኧረረረረረረረረረረ"
ከዚህ በፊት ከሌላ ሴት ጋር ወሲብ ያልፈጸምከው ለምንድን ነው ”
"እኔጃ"
"ሴን ትፈራለህ እንዴ ?
"መፍራት ሳይሆን እንዲሁ መቅረብ ብዙም አልፈልግም።” ወንበሯ ላይ ተመቻችታ ወደኔ ዘንበል አለችና (ጡቶቿ አፈጠጡብኝ)
“ለምን ?” ስትል ጠየቀችኝ፤ ቁልፉን ያገኘችው ሳይመስላት አልቀረም።
ረዥም ሰዓት በስልክ እንዳያወሩኝና ሸኘኝ እንዳይሉኝ … ! ስል መለስኩላት። እንደው ይህ ምላሽ መታበይ ይመስል ይሆናል እንጂ ማንንም እንደመሸኘትና እና በስልክ እንደማውራት የምጠላው ነገር
የለም። እኔም ሲሸኙኝ አልወድም፤ ሰውም መሸኘት ያንገሸግሽኛል። ምንድን ነው መጓተት፣ ምንድነው
ስልክ ላይ ተለጥፎ ማላዘን ? እንዴት እንደሚያስጠላኝ ! ስልከ አልወድም።
እሺ አብርሽ ጨርሰናል፣ ስልክህን ስጠኝና እደውልልሃለሁ” እርፍ!!
የሥነልቦና ባለሞያዋ እየደወለች ልትረዳኝ ብትሞከርም ነገሩ ዋጋ አልነበረውም። የበለጠ ስለጉዳዩ
ባሰብኩ ቁጥር በእግሮቼ መሃል ሳይሆን በፍርሃት መሃል ቁም ነገሩ ጠፋ። ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም !! ወዶ ነው አበሻ፣ “ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ" የሚለው። ትውልድን የሚሻገር ሕያው ድምጽ
መፈጠሪያው የት እንደሆነ ሲገባው እንጂ ! ኤዲያ!ወንድነት ደገፍ ብሎ የሚኮፈስበት ከዘራ ሸንበቆ ሲሆን አለ ከልብ የሚሰነጠር ወኔ ከተራ ብልግና የገዘፈ ሃቅ፤ ቃጭሉም ዝም ! ቤቴ ውስጥ ካሉት እቃዎች ምን አስጠላሀ ብባል አልጋዬ። የተሸነፍኩበት፣ የተማረክኩበት፣ የቆሰልኩበትና የተሰዋሁበት
ጦር ማዴ መስሎ ታየኝ። “ወኔዬን ያፈሰስኩበት አልጋ እኮ ነው ብዬ የልጅ ልጆቼ ላይ እኮፈስበት
ይሆናል። ያኔ ወኔው ያፈሰሰ ትውልድ ነፍ ነው የሚሆነው ! ወኔ ቢስነትም ክብር!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙና ልትመጣ አስራ አንድ ቀናት ቀሩ ። አስራ አንድ የሽብር ቀናት ! “አብርሽ ፈራህ እንዴ ?ሂሂሂሂሂ
እንደ ቀልድ ትጠይቃለች። ለምን ጀግና ለመምሰል እንደምጣጣር ለራሴም አይገባኝ፤ ፈርቻለው
አይደል እንዴ ? አዎ ፈርቻለሁ ብላት ምን ነበር ? እኔ ግን ኮስተር ብዬ እንዲህ አልኳት፣ “ለምኑ ነው
የምፈራው?
“ለብር አምባሩ ነዋ አለችና ትንፋሽ እስኪያጥራት በሳቅ ፈረሰች። ሳቋ ውስጥ ሺ ጊዜ ፍራ እንጂ
አሁንማ ቁርጥ ነው የሚል ንዝረት አለ። እኔ'ኮ የሚገርመኝ “ብር አምባር” ከእንትን” ጋር ምን
አገናኘው? እውነቴን እኮ ነው … ብዙ ወንዶች ከአንዲት ሴት ጋር ወሲብ ሊፈፅሙ “ፈረሱም ሜዳውም ያውላችሁ” ሲባሉ በስሜት ስለሚሳከሩ እንኳን ቃል ሊሰነጥቁና ሊመረምሩ አልጋ ላይ ይሁኑ ዓየር ላይ የሚያውቁት ከተረጋጉ በኋላ ነው። ከዛ በፊትማ ብር ይልሰር አምባር ይሰበር ብርጭቆ ይሰበር ቅስም
ይሰበር ምን ግዳቸው "ሰማዩን ሰበረው ጀግናው” ቢባልም አይሰሙም፤ እኔ ግን የያዘ ይዞኝ ቀልቤን አሰላሳይ አድርጓታልና “ብር አምባር” ከድንግልና ጋር ምን አገናኘው ብዬ አስባለሁ -- (ሰው ወዶ ፈላስፋ አይሆንም መቼስ ይሄ ሁሉ ሚዜ እና ታዳሚ ላንቃው እስኪደርቅ በየሰርግ ቤቱ“ብር አምባር ሰበረልዎ ጀግናው ልጅዎ እያለ ይዝፈነው እንጂ “ድንግልናን ከብር አምባር ምን አገናኘው ለሚለው ጥያቄ መልስ ያለው አይመስለኝም።
እኔ ግን ዝም ብዬ ሳስሰው፣ “ብር አምባር መስበር አስገድዶ ከመድፈር ጋር “ጥብቅ ቁርኝት ያለው ጉዳይ ይመስለኛል። ልጅቱ የብር አምባር እጇ ላይ አጥልቃለች፤ ያው ሴት የብር አምባር ማድረጓ ከጥንት የተለመደ ነገር ነው) እና ባሏ ወላ ወዳጇ እጇን ይይዛታል .… (ያዝ እጆን) እንዲል ዘፈኑ ከዛ ለማምለጥ ወይም ራሷን ለማዳን እንዳቅሟ መታገሏ አይቀርም፤ መቼስ ዝም ብሎ ያውልህ አይባልም።
በሩን ይዘጋል (ዝጋ ደጇን) እንዲል ቀጣዩ የዘፈኑ ስንኝ፤ ትግሉ ከበረታ እጇን ጠምዝዞ ጉንጯን (ሳም ጉንጯን ) የሚለው ልክ መጣ። ለከንፈሯ ያሞጠሞጠው ከንፈር በልጅቱ መወራጨት ስቶ
ጉንጯ ላይ አርፎም ሊሆን ይችላል፣ ወይም አየር ላይ እንደ ርችት የከሸፈ መሳም ብትን ! ሲታገላታ እጇ ላይ ያለው አምባር ስብር ! ከሽ ! “ይሰበር የታባቱ ቅዳሜ ገበያ ስወጣ ሌላ እገዛልሻለሁ ያውም ወርቅ የመስለ” እያለ ወደ ጉዳዩ !
እንዲህ የሚያስለፈሰፈኝ ወድጄ አይደለም፤ አምባሩ እኔ እጅ ላይ ያለ እስኪመስለኝ መዘዜ ሊመዘዝ
አስራ አንድ ቀን ቢቀረኝ እንጂ። ሙና ይቅርታ አታውቅም ! በአሁኑ ጉብኝቷ ጉንጯን ስሜ ብልካት
እርሷም እንደ ይሁዳ ስማ ነው ለብቸኝነት ስቅላቴ የምትሸጠኝ። ሙናን እኮ አፈቅራታለሁ። እንደ
ቀልድ ሳጣት ነው በቃ ? እሺ አሁን የእኔ ጥፋት ምንድን ነው? የሙና ጥፋትስ ? እግዚኣብሔር ግን
ምን አደረግኩት ? እስኪ አሁን ማን ይሙት ሊቃጣኝ ፈልጎ ከሆነ ሌላ ልምጭ አጥቶ ነው !? ለምሳሌ ሰፈራችንን በጎርፍ አጥለቅልቆ እኔን ብቻ በመግደል ዜና ማድረግ አይችልም ? መንገድ ላይ ሱክ ሱክ ስል መብረቅ አውርዶ ድምጥማጤን ማጥፋት ያቅተዋል ? ምን አድርጌው ከማን የተለየ ጥፋትና በደል ሰርቼ በውርደት የምወዳትን ልጅ ዓይኔ እያየ ያስነጥቀኛል ? አባታችን አብርሃም እንኳን በዘጠና ስንት
አሙቱ ተሳክቶለት ልጅ ሲወልድ እኔን ሚስኪኑ በሃያ ሰባት አመቴ እንዲህ ጉድ ስሆን እግዜር እንዴት
ሆዱ ቻለ ?
'አብርሽ” እለኝ ሃኒባል፣
"እ"
“ግን ችግሩ ከሙና ቢሆንስ ?"
“እንዴዴዴዴዴ ምን አገናኘው ከሙና ጋር”
👍23
#ሚስቴን_አከሸፏት
፡
፡
#አምስት (መጨረሻው)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ፌቨን ከዛ ቀን በኋለ የፀጉሩ ነገር እንዳበቃለት ሲገባት ያማልለኛል ያለችውን ነገር ሁሉ እያሳየች የተንኮታኮተ ፍቅሬን ልትመልሰው ተፍገመገመች። አንዴ አጭር ቀሚስ ለብሳ እግሯን እስከታፋዋ ታሳየኛለች፤ (እግርሽ ያምራል እላት ነበር ድሮ እንደዛሬው እያንቀዠቀዠ አልባሌ ቦታ ሳይወስዳት በፊት) የእጇን ጣቶች ብታወናጭፍ፣ ዓይኗን ብታፈጥ፣ከንፈሯን ብታሞጠሙጥ... ውሉን ቆርጣ ጥላ ትርፍራፊ ውበቷን ብታግተለትል ወይ ፍንክች። እንደውም የባሰ አስጠላችኝ። አይናገረውም እንጂ ሁሉም አፍቃሪ ለዘላለሙ የሚያመልከው የሚያፈቅረው ሰው ላይ በየቀኑ ዓይኑ የሚፈልገው የውበት አማካይ ቦታ አለው። ሌላው ሁሉ ካለዚህ ነጥብ ባዶ ነው። ለእኔ የፌቨን አማካይ የውበት ቦታ ፀጉሯ ነበር። ፌቨንን እንደከተማ ብመለከታት መሐል አደባባይዋ ፈርሷል። አንጋፋ ፍቅር አዲስ ከተማ ላይ መኖር ያንገሸግሸዋል።
የዘመናዊው ፋሽን ትልቅ ችግር የሴቶችን ፀጉር የሚያደንቅ ተፈጥሯችንን በግድ ጠምዝዞ ሴቶች ዳሌ ላይ ለማሳረፍ መጣሩ ነው። ሴቶች እግር ላይ ሴቶች ጡት ላይ ዓይናችንን በግድ ማስተከል። እንቢ ማየት
አንፈልግም ስንል ውበት የማይገባን ገገማዎች መሆናችንን በማሳመን ስልጡን አይደላችሁም ይለናል ሞላ ያለች ሴት እይታችንን ትስበው ይሆናል። ፋሽን ተብዬው ግን የትከሻዋ አጥንት ካልተሰረጎደ
ሴት ምኑን ሴት ሆነች ብሎ ሊያሳምነን ይጥራል። ፋሽን ጉልበተኛ ነው። በተለይ ሴቶች ላይ ክንዱ ይበረታል። ዛሬ ፋሽን ለመከተል ፀጉሯን የቆረጠች ሴት ነገ የላይኛውን የፊት ጥርስ አስነቅሎ በባዶ ድድ መገልፈጥ ያምርብሻል ብትባል ጥርሷን ከማራገፍ አትመለስም፡፡ የተጋነነ ይመስላል እንጂ ባለፉት
አስር ዓመታት በአገራችን አይሆኑም ያልናቸው ጉዳዮች ዛሬ ላይ ለትውልዱ ተራ ጉዳዮች ሆነዋል።ደግሞ ፍጥነታችን
የፌቨንን ፀጉር መቆረጥ ከሴት ልጅ ግርዛት ለይቼ አላየውም። ልዩነቱ የሴት ልጅ ግርዛት በሴቷ ስሚት ላይ መቀለድ ሲሆን ይሄንኛው በእኔ ፍላጎትና ስሜት ላይ መጫወት መሆኑ ነው። እናም ፌቨንን እፈታታለሁ !! እሷን ብሎ ሚስት። የፍርድ ቤት ቀጠሮዬ ነገ ነው። ፌቨን እናቷ ጋር ከሄደች ሃያ ቀናቶች አልፈዋል፡፡ አልናፈቀችኝም። እንደውም የተሰማኝ ሰላም ልክ አልነበረውም። ትንሽ የተሰማኝ ፌቨንንም ሆነ እናቷን በገንዘብ የምረዳቸው እኔ ነበርኩ በዚህኛው ወር ግን ምንም አልሰጠኋቸውም። ከፌሽን
ጋር ስለተጣላሁ ሳይሆን ብሩን ብልክላቸው ፌቨንን የመፈለግ ስሜት ያደረብኝ እንዳይመስላቸው
በማሰብ ብቻ ነው….
ከፌቨን ጋር ከተለያየን በኋላ ብዙዎች እንዳሰቡት ስትናፍቀኝ “ማሪኝ” ብዬ ቤቷም አልሄድኩ።
ስልክም አልደወልኩም። እንደውም አንዳንዶች፣ “ሚስቴ ቤቱን ጥላልኝ ስትሄድ ቤቱ ሊበላኝ ደረሰ፣ ጭር አለ ኦና ሆነ” ምናምን የሚሉት ነገር ለምን እንደሚባል ገረመኝ። በጣም ነው ቤቱ የተስማማኝ ገነት ነው የሆነብኝ ! ምግብ ራሴ አበስላለሁ፣ ቤቴን በደንብ አፀዳለሁ፣ አነባለሁ፣ ፊልም አያለሁ
(እንደውም ከዚያ ፌቨን ከምትከፍተው አሰልቺ የቴሌቪዥን ድራማ ተገላገልኩ) እና ደግሞ ሰላም ሆንኩ!! እንደውም ባልና ሚስት የፈለገ ቢፋቀሩ፣ ትንሽ መለያየት፣ ራሳቸውን የሚያደምጡባት
“ሱባዔ” መሰል ብቸኝነት ታስፈልጋቸዋለች ብዬ አሰብኩ።
ፌቨንን ለራሴ እንኳን ስሟን በውስጤ መጥራት ይቀፈኛል። በቃ በተፈጥሮዬ ወግ አጥባቂ ነገር ነኝ ማለት ነው ብዬ አሰብኩ። እና እንዴት ይሄን ሁሉ ዓመት አብራኝ የኖረች ሴት ያውም በፍቅር ተነስታ ስትሄድ ምንም ሳይመስለኝ ቀረ። ለደቂቃ መኝታ ቤታችን ውስጥ ስትበር የነበረች ትንኝ
እንኳ በሆነ ሽንቁር ስትወጣ የሚናፍቅ ነገር አላት። አይ ጤነኛ አይደለሁም ማለት ነው። ወይስ የሆነ ውስጣችን ሳያውቀው የሚሰለቸው አብሮነት አለ ... ምክንያት ፈልጎ የሚፈነዳ ... ፌቨንን ሳላስበው ውስጤ ሰልችቷት ይሆን ? ዓይቷት የማይቋምጥ ወንድ የለም … ቁንጅናዋ እንግዳ ነገር ነው ..
መኝታ ቤት ገብታ ወደ ሳሎን ስትመለስ እንኳ አዲስ ቆንጆ ሴት እንዳየ ጎረምሳ ልቤ ይደነግጥላት
ነበር ... እና እንዴት ነው ነገሩ ... እንዲህ ልክ የሌለው ግዴለሽነት የሞላኝ ወይስ እየቆየ እንደተዳፈነ
እሳት ሊያንገበግበኝ ይሆን ...
ለነገሩ ቆንጆ ሴቶች ቶሎ ነው የሚሰለቹት ይባላል። በጥናት ባይረጋገጥም የሆነ እውነት እንዳለው በብዙ ቆንጆ ፍቅረኛ ባላቸው ጓደኞቼ ታዝቤያለሁ። በተለይ ከተጋቡ በኋላ ቆንጆ ሚስቶች ለውጭ ተመልካች እንጂ ለባሎቻቸው ያን ያህል አስገራሚም አስደሳችም ነገር የላቸውም እየተባለ ከፉኛ
ይታማል ሚስቶቹም ራሳቸው ይሄ ነገር ግራ ይገባቸዋል አንድ ጓደኛዬ እንዳለኝ ከሆነ እንደውም
ቃል በቃል፣ ለዛ ቢስ ናቸው !!” ነበር ያለው እንግዲህ ከሰፊ የብሶት ምክሩ የተወሰነውን ሳስታውስ (ያኔ እንኳ ችላ ብዬው ነበር) ቁንጅናቸው ይስብሃል፣ ቁንጅናቸውን ትፈልጋለህ፣ ታገኘዋለህ፣ ቁንጅናቸው መጋረጃ ሆኖ ስለሚጋርድህ ከማግኘት ቀጥሎ ያለውን ሕይወት አታስበውም። መጋረጃውን ስታልፍ ግን ጭው ያለ በረሃ ይጠብቀሃል.. ሰሐራ ! ምንም አይኖርም ወላ ሃንቲ !! ሁሉም ነገራቸው ወዲያው ነው
የሚሰለችህ... እንደውም እነሱን ለማግኘት የደከምከው ድካም ከንቱ ሆኖ ስለሚታይህ ነጭናጫ
ትሆናለህ ድሮ ይቺን ሚስትህን አፍቅረህ ስትንከራተት ፊት የነሳሃት በፍቅር ዓይን ስትስለመለምልህ
የነበረች ጎራዳ ሽቦ ፀጉር ልጅ ሁሉ ትናፍቅሃለች ! ለዛ ነው ብዙውን ጊዜ “ልዕልት የመሰለች ሚስት
አስቀምጦ ሰራተኛው ጋር…” ምናምን ሲባል የምትሰማው እንጅማ ሚስትህ ልዕልት ባትመስልም ሌላ ሴት ጋር ሂድ የሚል ፍርድ የለም መቼስ።” የጓደኛዬ ምክር ይከሰትልኝ ይጀምራል። የበላኝን
እንደሚያክልኝ ሁሉ ንግግሩን የራሱ ልምድና አመለካከት አድርጌ ከማድመጥ በላይ ዓለምአቀፍ
የሴቶች ባህሪ አድርጌ ልቀበለው ይዳዳኛል። ማንም ሰው በጋራ ብሶት ውስጥ ሲኖር በአዕምሮው ልክ ሳይሆን በብሶቱ ልክ ያስባልና።
“ሴትን ልጅ ለማየት ይሄ ደካማ ሥጋዊ ዓይን በቂ አይደለም ድፍን የስሜት ሕዋሳቶችህ፣ በአካባቢህ ያለው እውነታ፣ ታሪክ፣ ፍልስፍና፣ ኃይማኖት፣ አስተዳደግህ፣ የትምሕርት ደረጃህ ሁሉ “ተቀናጅቶ” መሥራት ይኖርበታል። በደመ ነፍስ ዘለህ ከገባህ በደም ግፊት ዘለህ መቃብር ጉድጓድህ ውስጥ ነው
የምትገባው ያውም በጭንቅላትህ። ፍቅር ላይ ያለህ ነገር ከተበላሸ በምድር ላይ ያለህ ማንኛውም ነገር እንደተበላሸ ቁጠረው። ሌላው ቢቀር እየቆየ የሚያገረሽ የተበላሸ ትዝታ ይኖርሃል። ልብህን ለፍቅር
ስትሰጥ ወሲብ ያዞረው ናላህን አሽቀንጥረህ መጣል አለብህ። እሱ ነው እንደጋሪ ፈረስ ሸብቦ አንድ ነገር ብቻ እንድታይ የሚነዳህ። ለምን እቅጩን አልነግርህም ያኔ አንድ ቤት የሁለትዮሽ ስብሰባ ላይ ስትገናኝ
ተረከዝ አይመስጥህ፣ ዳሌ አያማልልህ፣ ከንፈር አያስጎመዥህ፣ ስርቅርቅ ድምፅ ቀልብ አያሳጣህ፣ ጉችም ይበል
ዝርግፍም ይበል ጡት ከመጤፍ አይቆጠር ሃቂቃዋ የፍቅር ዘርልብህ ውስጥ ከሌለች
አለቀልህ !”
፡
፡
#አምስት (መጨረሻው)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ፌቨን ከዛ ቀን በኋለ የፀጉሩ ነገር እንዳበቃለት ሲገባት ያማልለኛል ያለችውን ነገር ሁሉ እያሳየች የተንኮታኮተ ፍቅሬን ልትመልሰው ተፍገመገመች። አንዴ አጭር ቀሚስ ለብሳ እግሯን እስከታፋዋ ታሳየኛለች፤ (እግርሽ ያምራል እላት ነበር ድሮ እንደዛሬው እያንቀዠቀዠ አልባሌ ቦታ ሳይወስዳት በፊት) የእጇን ጣቶች ብታወናጭፍ፣ ዓይኗን ብታፈጥ፣ከንፈሯን ብታሞጠሙጥ... ውሉን ቆርጣ ጥላ ትርፍራፊ ውበቷን ብታግተለትል ወይ ፍንክች። እንደውም የባሰ አስጠላችኝ። አይናገረውም እንጂ ሁሉም አፍቃሪ ለዘላለሙ የሚያመልከው የሚያፈቅረው ሰው ላይ በየቀኑ ዓይኑ የሚፈልገው የውበት አማካይ ቦታ አለው። ሌላው ሁሉ ካለዚህ ነጥብ ባዶ ነው። ለእኔ የፌቨን አማካይ የውበት ቦታ ፀጉሯ ነበር። ፌቨንን እንደከተማ ብመለከታት መሐል አደባባይዋ ፈርሷል። አንጋፋ ፍቅር አዲስ ከተማ ላይ መኖር ያንገሸግሸዋል።
የዘመናዊው ፋሽን ትልቅ ችግር የሴቶችን ፀጉር የሚያደንቅ ተፈጥሯችንን በግድ ጠምዝዞ ሴቶች ዳሌ ላይ ለማሳረፍ መጣሩ ነው። ሴቶች እግር ላይ ሴቶች ጡት ላይ ዓይናችንን በግድ ማስተከል። እንቢ ማየት
አንፈልግም ስንል ውበት የማይገባን ገገማዎች መሆናችንን በማሳመን ስልጡን አይደላችሁም ይለናል ሞላ ያለች ሴት እይታችንን ትስበው ይሆናል። ፋሽን ተብዬው ግን የትከሻዋ አጥንት ካልተሰረጎደ
ሴት ምኑን ሴት ሆነች ብሎ ሊያሳምነን ይጥራል። ፋሽን ጉልበተኛ ነው። በተለይ ሴቶች ላይ ክንዱ ይበረታል። ዛሬ ፋሽን ለመከተል ፀጉሯን የቆረጠች ሴት ነገ የላይኛውን የፊት ጥርስ አስነቅሎ በባዶ ድድ መገልፈጥ ያምርብሻል ብትባል ጥርሷን ከማራገፍ አትመለስም፡፡ የተጋነነ ይመስላል እንጂ ባለፉት
አስር ዓመታት በአገራችን አይሆኑም ያልናቸው ጉዳዮች ዛሬ ላይ ለትውልዱ ተራ ጉዳዮች ሆነዋል።ደግሞ ፍጥነታችን
የፌቨንን ፀጉር መቆረጥ ከሴት ልጅ ግርዛት ለይቼ አላየውም። ልዩነቱ የሴት ልጅ ግርዛት በሴቷ ስሚት ላይ መቀለድ ሲሆን ይሄንኛው በእኔ ፍላጎትና ስሜት ላይ መጫወት መሆኑ ነው። እናም ፌቨንን እፈታታለሁ !! እሷን ብሎ ሚስት። የፍርድ ቤት ቀጠሮዬ ነገ ነው። ፌቨን እናቷ ጋር ከሄደች ሃያ ቀናቶች አልፈዋል፡፡ አልናፈቀችኝም። እንደውም የተሰማኝ ሰላም ልክ አልነበረውም። ትንሽ የተሰማኝ ፌቨንንም ሆነ እናቷን በገንዘብ የምረዳቸው እኔ ነበርኩ በዚህኛው ወር ግን ምንም አልሰጠኋቸውም። ከፌሽን
ጋር ስለተጣላሁ ሳይሆን ብሩን ብልክላቸው ፌቨንን የመፈለግ ስሜት ያደረብኝ እንዳይመስላቸው
በማሰብ ብቻ ነው….
ከፌቨን ጋር ከተለያየን በኋላ ብዙዎች እንዳሰቡት ስትናፍቀኝ “ማሪኝ” ብዬ ቤቷም አልሄድኩ።
ስልክም አልደወልኩም። እንደውም አንዳንዶች፣ “ሚስቴ ቤቱን ጥላልኝ ስትሄድ ቤቱ ሊበላኝ ደረሰ፣ ጭር አለ ኦና ሆነ” ምናምን የሚሉት ነገር ለምን እንደሚባል ገረመኝ። በጣም ነው ቤቱ የተስማማኝ ገነት ነው የሆነብኝ ! ምግብ ራሴ አበስላለሁ፣ ቤቴን በደንብ አፀዳለሁ፣ አነባለሁ፣ ፊልም አያለሁ
(እንደውም ከዚያ ፌቨን ከምትከፍተው አሰልቺ የቴሌቪዥን ድራማ ተገላገልኩ) እና ደግሞ ሰላም ሆንኩ!! እንደውም ባልና ሚስት የፈለገ ቢፋቀሩ፣ ትንሽ መለያየት፣ ራሳቸውን የሚያደምጡባት
“ሱባዔ” መሰል ብቸኝነት ታስፈልጋቸዋለች ብዬ አሰብኩ።
ፌቨንን ለራሴ እንኳን ስሟን በውስጤ መጥራት ይቀፈኛል። በቃ በተፈጥሮዬ ወግ አጥባቂ ነገር ነኝ ማለት ነው ብዬ አሰብኩ። እና እንዴት ይሄን ሁሉ ዓመት አብራኝ የኖረች ሴት ያውም በፍቅር ተነስታ ስትሄድ ምንም ሳይመስለኝ ቀረ። ለደቂቃ መኝታ ቤታችን ውስጥ ስትበር የነበረች ትንኝ
እንኳ በሆነ ሽንቁር ስትወጣ የሚናፍቅ ነገር አላት። አይ ጤነኛ አይደለሁም ማለት ነው። ወይስ የሆነ ውስጣችን ሳያውቀው የሚሰለቸው አብሮነት አለ ... ምክንያት ፈልጎ የሚፈነዳ ... ፌቨንን ሳላስበው ውስጤ ሰልችቷት ይሆን ? ዓይቷት የማይቋምጥ ወንድ የለም … ቁንጅናዋ እንግዳ ነገር ነው ..
መኝታ ቤት ገብታ ወደ ሳሎን ስትመለስ እንኳ አዲስ ቆንጆ ሴት እንዳየ ጎረምሳ ልቤ ይደነግጥላት
ነበር ... እና እንዴት ነው ነገሩ ... እንዲህ ልክ የሌለው ግዴለሽነት የሞላኝ ወይስ እየቆየ እንደተዳፈነ
እሳት ሊያንገበግበኝ ይሆን ...
ለነገሩ ቆንጆ ሴቶች ቶሎ ነው የሚሰለቹት ይባላል። በጥናት ባይረጋገጥም የሆነ እውነት እንዳለው በብዙ ቆንጆ ፍቅረኛ ባላቸው ጓደኞቼ ታዝቤያለሁ። በተለይ ከተጋቡ በኋላ ቆንጆ ሚስቶች ለውጭ ተመልካች እንጂ ለባሎቻቸው ያን ያህል አስገራሚም አስደሳችም ነገር የላቸውም እየተባለ ከፉኛ
ይታማል ሚስቶቹም ራሳቸው ይሄ ነገር ግራ ይገባቸዋል አንድ ጓደኛዬ እንዳለኝ ከሆነ እንደውም
ቃል በቃል፣ ለዛ ቢስ ናቸው !!” ነበር ያለው እንግዲህ ከሰፊ የብሶት ምክሩ የተወሰነውን ሳስታውስ (ያኔ እንኳ ችላ ብዬው ነበር) ቁንጅናቸው ይስብሃል፣ ቁንጅናቸውን ትፈልጋለህ፣ ታገኘዋለህ፣ ቁንጅናቸው መጋረጃ ሆኖ ስለሚጋርድህ ከማግኘት ቀጥሎ ያለውን ሕይወት አታስበውም። መጋረጃውን ስታልፍ ግን ጭው ያለ በረሃ ይጠብቀሃል.. ሰሐራ ! ምንም አይኖርም ወላ ሃንቲ !! ሁሉም ነገራቸው ወዲያው ነው
የሚሰለችህ... እንደውም እነሱን ለማግኘት የደከምከው ድካም ከንቱ ሆኖ ስለሚታይህ ነጭናጫ
ትሆናለህ ድሮ ይቺን ሚስትህን አፍቅረህ ስትንከራተት ፊት የነሳሃት በፍቅር ዓይን ስትስለመለምልህ
የነበረች ጎራዳ ሽቦ ፀጉር ልጅ ሁሉ ትናፍቅሃለች ! ለዛ ነው ብዙውን ጊዜ “ልዕልት የመሰለች ሚስት
አስቀምጦ ሰራተኛው ጋር…” ምናምን ሲባል የምትሰማው እንጅማ ሚስትህ ልዕልት ባትመስልም ሌላ ሴት ጋር ሂድ የሚል ፍርድ የለም መቼስ።” የጓደኛዬ ምክር ይከሰትልኝ ይጀምራል። የበላኝን
እንደሚያክልኝ ሁሉ ንግግሩን የራሱ ልምድና አመለካከት አድርጌ ከማድመጥ በላይ ዓለምአቀፍ
የሴቶች ባህሪ አድርጌ ልቀበለው ይዳዳኛል። ማንም ሰው በጋራ ብሶት ውስጥ ሲኖር በአዕምሮው ልክ ሳይሆን በብሶቱ ልክ ያስባልና።
“ሴትን ልጅ ለማየት ይሄ ደካማ ሥጋዊ ዓይን በቂ አይደለም ድፍን የስሜት ሕዋሳቶችህ፣ በአካባቢህ ያለው እውነታ፣ ታሪክ፣ ፍልስፍና፣ ኃይማኖት፣ አስተዳደግህ፣ የትምሕርት ደረጃህ ሁሉ “ተቀናጅቶ” መሥራት ይኖርበታል። በደመ ነፍስ ዘለህ ከገባህ በደም ግፊት ዘለህ መቃብር ጉድጓድህ ውስጥ ነው
የምትገባው ያውም በጭንቅላትህ። ፍቅር ላይ ያለህ ነገር ከተበላሸ በምድር ላይ ያለህ ማንኛውም ነገር እንደተበላሸ ቁጠረው። ሌላው ቢቀር እየቆየ የሚያገረሽ የተበላሸ ትዝታ ይኖርሃል። ልብህን ለፍቅር
ስትሰጥ ወሲብ ያዞረው ናላህን አሽቀንጥረህ መጣል አለብህ። እሱ ነው እንደጋሪ ፈረስ ሸብቦ አንድ ነገር ብቻ እንድታይ የሚነዳህ። ለምን እቅጩን አልነግርህም ያኔ አንድ ቤት የሁለትዮሽ ስብሰባ ላይ ስትገናኝ
ተረከዝ አይመስጥህ፣ ዳሌ አያማልልህ፣ ከንፈር አያስጎመዥህ፣ ስርቅርቅ ድምፅ ቀልብ አያሳጣህ፣ ጉችም ይበል
ዝርግፍም ይበል ጡት ከመጤፍ አይቆጠር ሃቂቃዋ የፍቅር ዘርልብህ ውስጥ ከሌለች
አለቀልህ !”
👍45❤3👏3👎1
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#አምስት
...እኔ የተወለድኩ ቀን ጠዋት አቲዬ አቃጣሪዋ ዘርፌ ቤት ወተት ስታልብ ነበር፡፡ ረፋዱ ላይ
የአንዲት ጎረቤት በርበሬ ስትቀነጥስ ዋለች፡፡ ውጋት ሲጀምራትና ምጡ ሲጫናት ከበርበሬ ቅንጠሳው በኋላ ልብስ ወደምታጥብበት ቤት ለመሄድ እየተዘጋጀች ነበር፡፡ ህመሙ ሲጀምራት ግን መንገዷን ቀይራ ወደ መንደር አዋላጅ አልማዝ ቤት ሄዳ እየፈራች፣ “እትዬ አልማዝ
እያመመኝ ነው፡: ምጥ ነው መሰለኝ…" አለቻት፡፡
“ውይ በሞትኩት መጣሁ ሂጂና ቤትሽ አረፍ በይ…" አለቻት፡፡
አቲዬ እንደታዘዘችው አደረገች፡፡ እዛች እሮጌ ፍራሽ ላይ ተኝታ ምጥ እየናጣት በር በሩን ማየት
ጀመረች፡፡ አልማዝ ግን ወደ አቲዬ አልሄደችላትም፡፡ ምክንያቱም እቲቲዬ ምጥ የተያዘች ቀን፣
ዘርፌ የምትባለዋ አቃጣሪ ባልቴት የአሜሪካ ላሟ ያልታወቀ ነገር በልታ ሆዷ ተቆዝሮና አረፋ
ደፍቃ እየጓጎረች ስለነበር፣ መንደርተኛው ሁሉ ወደዚያው ሄዶ ነበር፡፡ አዋላጇ ኣልማዝም
ቅድሚያ ለወርፌ ላም ሰጥታ ነበር፡፡
አንድ ግብርና የሚሰራ የእንስሳት ህክምና ባለሙያ ተጠርቶ እስከሪብቶ በሚመስል ነገር የላሟን ሆድ ወግቶ ካስተነፈሳት በኋላ ላሟ ነፍሷ መለስ በማለቱ የመንደሩ ሰው ደስታውን በእልልታ
ገለፀ፡፡
በዚህ መሐል እዋላጇ አልማዝ፣ “በሞትኩት ያች ሚስኪን ምን ደርሳ ይሆን?” ብላ ወደ ቤታችን
ተጣድፋ ብትደርስ አቲዩ እኔን አቅፋ አገኘቻት፡፡ የወርቅ ፍልቃቂ የመሰልኩ እኔ፣ በእሳት የተፈትንኩና የጥላቻ እሳት የምትፋ እኔ፣ አላፊ አግዳሚውን የምራገም እኔ በእናቴ እቅፍ ላይ ታሪክ ይወቀኝም አይወቀኝም፣ እናት የተባለች ታላቅ ሀገር ከስግብግብ፣ ከአስመሳይ፣ ከራስ
ወዳድ፣ ከአሽቃባጭ፣ ደሀ ከማይወድ፣ እምነት ከሌለው፣ ሆድ አምላኩ ከሆነ አመንዝራ እና
ጨካኝ ጎረቤት ቅኝ ግዛት የወጣሁ ጀግና እኔ ተወለድኩ !! አገሬ እናቴ አፀደ ናት ! ባንዲራዬም
የእናቴ ቀለም አልባ አሮጌ ቀሚስ !! ድምጿ መዝሙሬ ነው፣ ትዕዛዟ ሕገ መንግስቴ !! እናቴ
አፀደ ወይንም ሞት!! አቲዬ ትቅደም !! አቲዬ ለዘላለም ትኑር!
መዝመሬ፣
ተንቀሽ የኖርሽው ድሮ ከዚህ ቀደም፧
እናቴ አፀደ የደፈረሽ ይውደም !!
በሰሜን ስግብግብ የደሀ ደም መጣጭ ጎረቤቶች፣ በደቡብ ራስ ወዳድ በድሀ እምባ የሚዋኙ
እጋሰሶች፣ በምስራቅ የእናቴን ፀሐይ እንዳትወጣ የሚጋርዱ አስመሳይና ሆዳሞች፤ በምዕራብ
ሚስኪን ሴት ደፋሪዎች እና ትውልድ የሚነዱ ካፖርታሞች…፡፡ ከታች በባዶ እግሯ የምትረግጠው
ምድር፣ ከላይ እግዚአብሔር (የባህር በሯን የሚያዋስናት ሀገር አፀደ ትባላለች - የእኔ አገር እሷ
ናት !!
አፀደ ከሰማይ ዱብ እንዳለ ጉድ ዘመድ የላትም፡፡ እናት፣ አባት፣ አክስት፣ አጎት የላትም፡፡
አልተማረችም ገንዘብም የላትም፡፡ ግን ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ ለሆነ ባለፅጋ አግዚያብሔር እንብና ድፍን የኢትዮጲያ ሃምሳ ብር ያበደረች ልበ ሙሉ ሴት ናት፡፡ እግዚያብሔርም የማንም
ብድር በእጁ ይቆይ ዘንድ አይወድምና ብድሩን ይከፍል ዘንድ እኔን መንገድ አደረገ፡፡ በድፍን ሀያ አምስት ዓመታትም አነፀኝ ደለደለኝ።
እግዚኣብሔር ፈጠነም ዘገየም ወደ እያንዳንዱ ሰው ሕይወት ውስጥ ይመጣል፡፡ ሲመጣ የእግዜርን እርምጃ የእግሩንም ዳና የሚቋቋም መንገድ የሚሰራው መከራ በሚባል ኮንክሪት ነው :: ዙሪያህን የከበበህን ችግርና እልህ አስጨራሽ የሕይወት ፈተና ስታልፍ፣ የእግዜር የመጀመሪያ
እርምጃ ትጀምራለች፡፡ ያኔ ታዲያ ርሀብን ብቻ ሳይሆን ጥጋብንም የምትችል አድርጎ እንዳነፀህ ይገበሀል።
አሰራሩ እንደዛ ነው፤ ሳይሆንም እኔ እንደዛ ነው እላለሁ፡፡ አንተን ከድህነት ማውጣት ብቻ ሳይሆን መጭውን የጥጋብ ዘመንም የሚሸከም ትከሻ እንዲኖርህ አድርጎ ይሰራሀል ካለመንክ
እንደ የዕምነትህ መጽሀፍህን ግለጥ፣ አዱኒያን እንደ ምናምንቴ ንቀው ፈጣሪን ያመኑ፣ የተከተሉ
ሁሉ ሰፈርህ ሕንፃ አቁሞ እንደሚሸልለው እብሪተኛ ሃብታም ባንዴ ሰማይ ጥግ አልደረሱም፡፡
ፈጣሪ ሲሰራህ ቀስ ብሎ ነው፣ ግን መቼም እንዳትፈርስ አድርጎ፡፡ ያኔ ደስ ይልሃል ወደህ ነው ጎንበስ ብለህ ታመሰግናለህ በግድህ አንተ ላለማመስገን ብትጥር እንኳን ስጋህ ያማረ ፍራሸ ላይ ለሽ ሲል፣ በርሀብ የተንሰፈሰፈ አንጀትሀ ውስጥ የጣመ ምግብ ሲጎዘጎዝ፣ በላዩ ላይ ጥሩ ቡና ስትጨምርበት፣ ከምንም በላይ ደግሞ ራስህን ስትገዛና ልብህ በሰላም ሲሞላ፣ እግሲያብሔር ይመስገን ይልሀል አፍህ ከአንተ ትዕዛዝ ውጭ!!
አቲዬ እኔን ከወለደች በኋላ ትንሽ ተስፋ ልቧ ውስጥ አደረ፡፡ አባቱ በልጁ አይጨክንም መቼም
ብላ፡፡ ግን አባት በልጁ ጨከነ፡፡ ቀለመ ወርቅ አባት የመሆን ሞራሉም ብቃቱም የሌለው
ሴሰኛ ሽማግሌ መሆኑን የአቲዬ ልብ ያወቀው ብዙ ቆይቶ ነበር፡፡ ወንዶች ለአገር ዳር ድንበር
እየፎከሩና እየሸለሉ የመዝመታቸውን ያህል አባትነትን ለመቀበል፣ ትዳርንም አሜን! ብሎ
ለመኖር፣ ከነፍሳቸው ጋር የሚገጥሙት ጦርነት ቀላል አይደለም፡፡ ለመውለድ ወንድ መሆን በቂ ነው፡አባት መሆን ግን ታላቅ ጀግንነትን ይጠይቃል፡፡ ቀለመወርቅ ደግሞ ጀግና አልነበረም፡፡ስለዚህ እኔን ልጁን ዶሮ ሳይጮህ ሦስቴ ካደኝ፡፡
አቲዬ የእኔ ብርቱ ግን በሰባት ቀኗ ከአራስ ቤቷ ተነስታ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ስራዋን
ጀመረች፡፡ “ኧረ ወገብሽ ይጥና” ያላት አልነበረም፡፡ የበሰበሰ ድሪቷቸውን ከምረው ጠበቋት
እንጂ ! 'የምትገርሚ ጠንካራ ልጅ እያሉ ፡፡ እርሳ ቐን ሙሉ አርባ ቀን ሙሉ ተዘፍዝፈው ሊጣቸውን ሲያሻምዱ ኑረው ሲወጡ እንኳን አራስነት ምን ያህል ከባድ መሆኑን እንደማያውቁ ሁሉ፥ አቲዩን በሥራ
ሲያጣድፏት ምንም አልከበዳቸው፡፡
ልጅ ይዛ ሥራ መሥራት ከባድ ነበር ለአቲዬ:: በየቤቱ በረንዳ ላይ እያስተኛች ሳለቅስባት እያጠባችኝ(ምናባቴ እንደሚያስለቅሰኝ እንጃ !)፡፡ አቲዬ እናቴ ብርቱ ሰው ከህይወት ጋር ትግሏን ቀጠለች.…አንድ.. ሁለት..ሦስት...አራት ወር ለአቃጣሪዋ ዘርፌ አቲዬ እየፈራች እንዲህ አለቻት፡
“አትዬ እኔ እንግዲህ እስካሁን ለልጁ አንድ ነገር ያደርጋሉ ብዩ ጠበቅኳቸው እሳቸው ግን
“ማናቸው ልጄ አለች ዘርፈ አካሄዱ አላምር ብሏት ፊቷን አጨፍግጋ፡፡
“ጋሽ ቀለመወርቅ" አለች አቲዬ፡፡
"እህ…ደም እሱ ምን ቤት ነው ባንች ልጅ”
"እትዬ ፈርቼ አልነገርኮትም እንጂ፣ እኔ ሌላም ወንድ ነክቶኝ አያውቅ ተሳቸው ነው :"
“ወዲያ ዝም በይ…ምን ትላለች
እቺ..የተከበረ ሰው አናት ዘሎ ፊጥ ማለት ምን ይሉት ብልግና
ነው?! ሁላተኛ እንዲህ ያለ ነውር ስትተነፍሽ ብሰማ ውርድ ከራሴ፡፡ ሂጂ አሁን ወዲያ ያው
ደሞዝሽ!"
ብላ አስር ብር ወረወረችላት፡፡ ስራዋ አስደንግጧት እንጂ ሳምንት ነው ገና ደሞዝ ለእቲ ከከፈለቻት፡፡
ቀለመወርቅ ይህችን ጭምጭምታ ሲሰማ ተንኮሉን ጀመረው:: አቲዬን ከመንደሩ ሊነቅል እንቅልፍ አጣ፡፡ አቲዬ ለአባ እስጢፋኖስ ሽምግልና ላከችበት፡፡
“ቀለመወርቅ መቼስ ዘር አይጣላም፡፡ ነገ የት እንደሚደርስ አንድ ፈጣሪ ነው የሚያውቀው፡፡
ሌላው ቢቀር የወተት መግዣ እንኳን ስጣት መቼስ እሷ ጋር እንዲህ ሠራህ፣ እንዲህ አደረግክ
ለማለት ባልደፍርም ልጁ ቆርጠው የጣሉት አንትን ነው…”
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
፡
፡
#አምስት
...እኔ የተወለድኩ ቀን ጠዋት አቲዬ አቃጣሪዋ ዘርፌ ቤት ወተት ስታልብ ነበር፡፡ ረፋዱ ላይ
የአንዲት ጎረቤት በርበሬ ስትቀነጥስ ዋለች፡፡ ውጋት ሲጀምራትና ምጡ ሲጫናት ከበርበሬ ቅንጠሳው በኋላ ልብስ ወደምታጥብበት ቤት ለመሄድ እየተዘጋጀች ነበር፡፡ ህመሙ ሲጀምራት ግን መንገዷን ቀይራ ወደ መንደር አዋላጅ አልማዝ ቤት ሄዳ እየፈራች፣ “እትዬ አልማዝ
እያመመኝ ነው፡: ምጥ ነው መሰለኝ…" አለቻት፡፡
“ውይ በሞትኩት መጣሁ ሂጂና ቤትሽ አረፍ በይ…" አለቻት፡፡
አቲዬ እንደታዘዘችው አደረገች፡፡ እዛች እሮጌ ፍራሽ ላይ ተኝታ ምጥ እየናጣት በር በሩን ማየት
ጀመረች፡፡ አልማዝ ግን ወደ አቲዬ አልሄደችላትም፡፡ ምክንያቱም እቲቲዬ ምጥ የተያዘች ቀን፣
ዘርፌ የምትባለዋ አቃጣሪ ባልቴት የአሜሪካ ላሟ ያልታወቀ ነገር በልታ ሆዷ ተቆዝሮና አረፋ
ደፍቃ እየጓጎረች ስለነበር፣ መንደርተኛው ሁሉ ወደዚያው ሄዶ ነበር፡፡ አዋላጇ ኣልማዝም
ቅድሚያ ለወርፌ ላም ሰጥታ ነበር፡፡
አንድ ግብርና የሚሰራ የእንስሳት ህክምና ባለሙያ ተጠርቶ እስከሪብቶ በሚመስል ነገር የላሟን ሆድ ወግቶ ካስተነፈሳት በኋላ ላሟ ነፍሷ መለስ በማለቱ የመንደሩ ሰው ደስታውን በእልልታ
ገለፀ፡፡
በዚህ መሐል እዋላጇ አልማዝ፣ “በሞትኩት ያች ሚስኪን ምን ደርሳ ይሆን?” ብላ ወደ ቤታችን
ተጣድፋ ብትደርስ አቲዩ እኔን አቅፋ አገኘቻት፡፡ የወርቅ ፍልቃቂ የመሰልኩ እኔ፣ በእሳት የተፈትንኩና የጥላቻ እሳት የምትፋ እኔ፣ አላፊ አግዳሚውን የምራገም እኔ በእናቴ እቅፍ ላይ ታሪክ ይወቀኝም አይወቀኝም፣ እናት የተባለች ታላቅ ሀገር ከስግብግብ፣ ከአስመሳይ፣ ከራስ
ወዳድ፣ ከአሽቃባጭ፣ ደሀ ከማይወድ፣ እምነት ከሌለው፣ ሆድ አምላኩ ከሆነ አመንዝራ እና
ጨካኝ ጎረቤት ቅኝ ግዛት የወጣሁ ጀግና እኔ ተወለድኩ !! አገሬ እናቴ አፀደ ናት ! ባንዲራዬም
የእናቴ ቀለም አልባ አሮጌ ቀሚስ !! ድምጿ መዝሙሬ ነው፣ ትዕዛዟ ሕገ መንግስቴ !! እናቴ
አፀደ ወይንም ሞት!! አቲዬ ትቅደም !! አቲዬ ለዘላለም ትኑር!
መዝመሬ፣
ተንቀሽ የኖርሽው ድሮ ከዚህ ቀደም፧
እናቴ አፀደ የደፈረሽ ይውደም !!
በሰሜን ስግብግብ የደሀ ደም መጣጭ ጎረቤቶች፣ በደቡብ ራስ ወዳድ በድሀ እምባ የሚዋኙ
እጋሰሶች፣ በምስራቅ የእናቴን ፀሐይ እንዳትወጣ የሚጋርዱ አስመሳይና ሆዳሞች፤ በምዕራብ
ሚስኪን ሴት ደፋሪዎች እና ትውልድ የሚነዱ ካፖርታሞች…፡፡ ከታች በባዶ እግሯ የምትረግጠው
ምድር፣ ከላይ እግዚአብሔር (የባህር በሯን የሚያዋስናት ሀገር አፀደ ትባላለች - የእኔ አገር እሷ
ናት !!
አፀደ ከሰማይ ዱብ እንዳለ ጉድ ዘመድ የላትም፡፡ እናት፣ አባት፣ አክስት፣ አጎት የላትም፡፡
አልተማረችም ገንዘብም የላትም፡፡ ግን ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ ለሆነ ባለፅጋ አግዚያብሔር እንብና ድፍን የኢትዮጲያ ሃምሳ ብር ያበደረች ልበ ሙሉ ሴት ናት፡፡ እግዚያብሔርም የማንም
ብድር በእጁ ይቆይ ዘንድ አይወድምና ብድሩን ይከፍል ዘንድ እኔን መንገድ አደረገ፡፡ በድፍን ሀያ አምስት ዓመታትም አነፀኝ ደለደለኝ።
እግዚኣብሔር ፈጠነም ዘገየም ወደ እያንዳንዱ ሰው ሕይወት ውስጥ ይመጣል፡፡ ሲመጣ የእግዜርን እርምጃ የእግሩንም ዳና የሚቋቋም መንገድ የሚሰራው መከራ በሚባል ኮንክሪት ነው :: ዙሪያህን የከበበህን ችግርና እልህ አስጨራሽ የሕይወት ፈተና ስታልፍ፣ የእግዜር የመጀመሪያ
እርምጃ ትጀምራለች፡፡ ያኔ ታዲያ ርሀብን ብቻ ሳይሆን ጥጋብንም የምትችል አድርጎ እንዳነፀህ ይገበሀል።
አሰራሩ እንደዛ ነው፤ ሳይሆንም እኔ እንደዛ ነው እላለሁ፡፡ አንተን ከድህነት ማውጣት ብቻ ሳይሆን መጭውን የጥጋብ ዘመንም የሚሸከም ትከሻ እንዲኖርህ አድርጎ ይሰራሀል ካለመንክ
እንደ የዕምነትህ መጽሀፍህን ግለጥ፣ አዱኒያን እንደ ምናምንቴ ንቀው ፈጣሪን ያመኑ፣ የተከተሉ
ሁሉ ሰፈርህ ሕንፃ አቁሞ እንደሚሸልለው እብሪተኛ ሃብታም ባንዴ ሰማይ ጥግ አልደረሱም፡፡
ፈጣሪ ሲሰራህ ቀስ ብሎ ነው፣ ግን መቼም እንዳትፈርስ አድርጎ፡፡ ያኔ ደስ ይልሃል ወደህ ነው ጎንበስ ብለህ ታመሰግናለህ በግድህ አንተ ላለማመስገን ብትጥር እንኳን ስጋህ ያማረ ፍራሸ ላይ ለሽ ሲል፣ በርሀብ የተንሰፈሰፈ አንጀትሀ ውስጥ የጣመ ምግብ ሲጎዘጎዝ፣ በላዩ ላይ ጥሩ ቡና ስትጨምርበት፣ ከምንም በላይ ደግሞ ራስህን ስትገዛና ልብህ በሰላም ሲሞላ፣ እግሲያብሔር ይመስገን ይልሀል አፍህ ከአንተ ትዕዛዝ ውጭ!!
አቲዬ እኔን ከወለደች በኋላ ትንሽ ተስፋ ልቧ ውስጥ አደረ፡፡ አባቱ በልጁ አይጨክንም መቼም
ብላ፡፡ ግን አባት በልጁ ጨከነ፡፡ ቀለመ ወርቅ አባት የመሆን ሞራሉም ብቃቱም የሌለው
ሴሰኛ ሽማግሌ መሆኑን የአቲዬ ልብ ያወቀው ብዙ ቆይቶ ነበር፡፡ ወንዶች ለአገር ዳር ድንበር
እየፎከሩና እየሸለሉ የመዝመታቸውን ያህል አባትነትን ለመቀበል፣ ትዳርንም አሜን! ብሎ
ለመኖር፣ ከነፍሳቸው ጋር የሚገጥሙት ጦርነት ቀላል አይደለም፡፡ ለመውለድ ወንድ መሆን በቂ ነው፡አባት መሆን ግን ታላቅ ጀግንነትን ይጠይቃል፡፡ ቀለመወርቅ ደግሞ ጀግና አልነበረም፡፡ስለዚህ እኔን ልጁን ዶሮ ሳይጮህ ሦስቴ ካደኝ፡፡
አቲዬ የእኔ ብርቱ ግን በሰባት ቀኗ ከአራስ ቤቷ ተነስታ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ስራዋን
ጀመረች፡፡ “ኧረ ወገብሽ ይጥና” ያላት አልነበረም፡፡ የበሰበሰ ድሪቷቸውን ከምረው ጠበቋት
እንጂ ! 'የምትገርሚ ጠንካራ ልጅ እያሉ ፡፡ እርሳ ቐን ሙሉ አርባ ቀን ሙሉ ተዘፍዝፈው ሊጣቸውን ሲያሻምዱ ኑረው ሲወጡ እንኳን አራስነት ምን ያህል ከባድ መሆኑን እንደማያውቁ ሁሉ፥ አቲዩን በሥራ
ሲያጣድፏት ምንም አልከበዳቸው፡፡
ልጅ ይዛ ሥራ መሥራት ከባድ ነበር ለአቲዬ:: በየቤቱ በረንዳ ላይ እያስተኛች ሳለቅስባት እያጠባችኝ(ምናባቴ እንደሚያስለቅሰኝ እንጃ !)፡፡ አቲዬ እናቴ ብርቱ ሰው ከህይወት ጋር ትግሏን ቀጠለች.…አንድ.. ሁለት..ሦስት...አራት ወር ለአቃጣሪዋ ዘርፌ አቲዬ እየፈራች እንዲህ አለቻት፡
“አትዬ እኔ እንግዲህ እስካሁን ለልጁ አንድ ነገር ያደርጋሉ ብዩ ጠበቅኳቸው እሳቸው ግን
“ማናቸው ልጄ አለች ዘርፈ አካሄዱ አላምር ብሏት ፊቷን አጨፍግጋ፡፡
“ጋሽ ቀለመወርቅ" አለች አቲዬ፡፡
"እህ…ደም እሱ ምን ቤት ነው ባንች ልጅ”
"እትዬ ፈርቼ አልነገርኮትም እንጂ፣ እኔ ሌላም ወንድ ነክቶኝ አያውቅ ተሳቸው ነው :"
“ወዲያ ዝም በይ…ምን ትላለች
እቺ..የተከበረ ሰው አናት ዘሎ ፊጥ ማለት ምን ይሉት ብልግና
ነው?! ሁላተኛ እንዲህ ያለ ነውር ስትተነፍሽ ብሰማ ውርድ ከራሴ፡፡ ሂጂ አሁን ወዲያ ያው
ደሞዝሽ!"
ብላ አስር ብር ወረወረችላት፡፡ ስራዋ አስደንግጧት እንጂ ሳምንት ነው ገና ደሞዝ ለእቲ ከከፈለቻት፡፡
ቀለመወርቅ ይህችን ጭምጭምታ ሲሰማ ተንኮሉን ጀመረው:: አቲዬን ከመንደሩ ሊነቅል እንቅልፍ አጣ፡፡ አቲዬ ለአባ እስጢፋኖስ ሽምግልና ላከችበት፡፡
“ቀለመወርቅ መቼስ ዘር አይጣላም፡፡ ነገ የት እንደሚደርስ አንድ ፈጣሪ ነው የሚያውቀው፡፡
ሌላው ቢቀር የወተት መግዣ እንኳን ስጣት መቼስ እሷ ጋር እንዲህ ሠራህ፣ እንዲህ አደረግክ
ለማለት ባልደፍርም ልጁ ቆርጠው የጣሉት አንትን ነው…”
👍31❤1