ጓደኛ ነው:: አብርሃም ነው፡፡
ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡
ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡
“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::
“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡
ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡
ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡
ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…
የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡
#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡
#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡
#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡
#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡
#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡
ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....
💫ይቀጥላል💫
ናትናኤል ትክ ብሎ አለቃውን ተመለከታቸው፡፡ አይናቸውን ሰበሩ።
በጎንና በጎን ያንጠለጠሏቸው ክንዶቻቸው የእርሳቸው የራሳቸው እንዳልሆነ
ሁሉ ረዘሙበት፤ ተንዘላዘሉዐት:: እንደገና ቀና ብለው ሲያዩት ኣይኖቻቸው
ውስጥ የሚጋልበውን ያልተገራ ሌጣ ፍርሃት ተመለከተ። አዘነላቸው፡፡
ተፀየፋቸው፡፡
ግድ የለም፡፡ ብቻውን ወደ ጨለማው ይወጣል፡፡ ያለረዳት ብቻውን አድኖ ይይዛቸዋል፡፡ ቀድሞውንም አለቃውን ተማመኖ አልተነሳም፡፡ ቃል ገብቷል ለአብርሃም አልተዋቸውም ብሎታል፡፡ ሞት? ግድ የለውም::አብርሃም እንኳን ልጁን ትቶ ሄዷል፡፡ እሱ አንድ ነው። ብቻውን ነው፡፡ ቢቀርም ቢሄድም ማንንም አይጎዳም፡፡ርብቃ? አዎ፡፡ ግን ቢጤዋን አታጣም፡፡ ቃል ገብቷል፡፡ ከአሁን ወዲያ አይመለስም፡፡ ህግ ፊት እስኪያቀርባቸው፣ በገመድ ተንጠልጥለው ዥው ዥው ሲሉ እስኪያይ አያርፍም፡፡
“የአመት ፈቃዴን አሁን መውሰድ እችላለሁ?” አላቸው አለቃውን አልትናገሩም ጭንቅላታቸውን በ'አዎንታ ነቀነቁለት፡፡ የዘረጉለትን እጃቸውን ሳይጨብጥ ፊቱን መለሰ፡፡ የቢሮአቸውን መዝጊያ ከፍቶ ከመውጣቱ በፊት የበሩን እጀታ እንደጨበጠ ዞር ብሎ አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታቸው::
“ዓርብ እለት አንድ መላምት ላይ እንድደርስ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ የጠየቁኝ መላምት ላይ ደርሻለሁ…አዲስ ኣበባ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቷል፡፡” አላቸው፡፡
ለአንድ አፍታ አገጫቸው የተንጠለጠለ መሰለው፡፡ የቢሮቸውን በር ዘግቶ ወደ ቢሮው አመራ፡፡
ወደ ቢሮው ተመልሶ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ወረቀት ሁሉ እየሰበሰበ በመሳቢያው ወስጥ ያጭቅ ጀመር፡፡ ብዕሮች፣ ወረቀቶች፣ መስፊያዎች፣ የፋይል ትሪዎች አንድ በአንድ እየተነሱ ከታችኛው መሳቢያ ወስጥ ታጎሩ፡፡ ጠረጴዛው እራቁቱን ሲቀር ከወንበሩ ላይ ተቀመጠና ሁለት መዳፎቹን በባዶው ጠረጴዛ ላይ ጫናቸው፡፡ ካልቨርትን አግኝ… ካልቨርትን የአብርሃም ድምፅ ደጋግሞ ተሰማው፡፡
ሙሉ ሃሣቡን አሰባስቦ አንድ ቦታ ማዋል አለበት… ባለው ኃይሉ ፈጥኖ ማስብ አለበት፡፡ ብቻውን ነው::፡ ጠላቶቹ የዋዛ አይደሉም፡፡ አብርሃም እንዳለው እንደ እሳት እራት ወደፍሙ እየተሽቀዳደመ ነው… መቃጠል የለበትም መንደድ የለበትም…መጋየት የለበትም….ሁልጊዜ . መቅደም አለበት ሁሉጊዜ ከፊት መገኘት አለበት… መበለጥ አይችልም… ሁልጊዜ
መብለጥ አለበት፡፡ አለ እንደ አብርሃም ያበቃል አለዛ ያቆማል…ሁሉም ነገር ያከትማል፡፡ ማክተሙን አያፈራም፡፡ ግን እሳቱን ማጥፋት አለበት፡፡ የንፁሃንን ነፍስ እየቀጠፈ በመሃላቸው የሚመላለሰውን አውሬ አጥምዶ መያዝ አለበት፡፡ ከየት ነው መጀመር ያለበት? ለፖሊስ ማስታወቅ? አዎ ፖሊስ ጋ ሂዶ ጉዳቸውን ማፍረጥረጥ! የስውር ክትትል ዘርግቶ አንድ በአንድ ማስለቀም፡፡ ግን…
የአብርሃም አደራ ታወሰው “ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን…” ናትናኤል መሳቢያውን ስቦ ነጭ ወረቀት አወጣ፡፡ ከደረት ኪሱ ውስጥ ብዕር፡፡ ነጩ ወረቀት ላይ ሃሣቡን ያሰፍር ጀመር፡፡
#አንድ፡ በአፍሪካ ኤምባሲዎች የሚሰሩ ወታደራዊ አታሼዎች ወደየአገሮቻ
ቸው እየተጠሩ ሄዱ ማለት የየአገሮቻቸው መንግስታት ሊገልፁላቸው፣ ሊያሳውቋቸው፣ ሊያስጠነቅቋቸው የሚገባ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡
#ሁለት፡ አንዳንድ አታሼዎች ሲመለሱ የተቀሩት በሌሎች ተተኩ ማለት…
ገሚሶቹ ለተመደቡበት ሃላፊነት ብቁ ሆነው በመገኘታቸው ሲመለሱ፣
የተቀሩት ለሃላፊነቱ ተስማሚ በሚሆኑ በሌሎች ተተኩ፡፡
#ሶስት፡ ለሥራው ብቁ ተብለው ከተመለሱ አታሼዎች መካከል በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት ተገድለው ሲገኙ አንድ የገባበት ጠፋ ማለት...
የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለታቸው አለበለዚያም ብቃት
ስለጎደላቸው በአውሬው ተበሉ…. ሁለት ተወገዱ ፤አንድ ተሰወረ፡፡
#አራት፡ ሁኔታውን መከታተሉና ማጣራቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግሥት አካላትም ሆኑ ሌሎች የኣፍሪካ መንግሥታት ነገሩን መሽፋፈን መረጠ ማለት… የአፍሪካ መንግሥታት እንዳይወጣ የሚሉት ምሥጢር ተፈጠረ አለዚያም በዙሪያቸው የተተበተበው የአውሬው መረብ መነቃነቅ ከለከላቸው፡፡
#አምስት: አንዳንዶቹ የጠፋውን የላይቤርያ አታሼ ለማግኘት በግል ያደረ
ጉት ጥረት ኣደጋ ላይ ጣላቸው ማለት... የላይቤርያው አታሼ አድራሻ እንዳይገኝ የሚሉ ወገኖች ምሥጢሩ እንዳይጋለጥ ሲሉ ነፍስ እስከማጥፋት ይደፍራሉ፡፡
ናትናኤል ድንገት አንድ ጥያቄ ተደነቅረበት፡፡ አብርሃም ብቻ አልነበረም የላይቤርያውን አታሽ አድራሻ ያነፈነፈ። እንዳውም በተቃራኒው ነገር ቆስቋሹ እርሱ ራሱ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አብርሃምን ገደሉት… እሱንስ ለምን ተውት....
💫ይቀጥላል💫
👍2
#ቀስ_ብሎ_ይቆማል
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ትከክክክክክ ብላ ስታየኝ እንዲህ እላታለሁ፣
“ከጋብቻ በኋላ”
በዚህ የጭንቅ ሰዓት ላይ እያለሁ ሙናን የምትሰራበት ባንክ ወደ መቀሌ ቅርንጫፍ ቀየራት። ይሄማ
የእግዜር እጅ አለበት። ደስ አለኝ። ስሸኛት አለቀሰች። ለአዲስ አበባ ሳይሆን ከእኔ በመለየቷ፤ እና ደግሞ ከብረት የጠነከረ መሻትን ድል ሰመታ ከእሳት ለተፈተነ ትዕግስቴ” (እሷ እንደዛ ነው የሚመስላት) ለእኔ ግን ጉዳዩን ለራሴ እንኳን ማመን ባልፈልግም ገብቶኛል። ስንፈተ ወሲብ !! ያውም እንደ መርዶ ለራሴም ድንገት ዱብ ብሎ የተገለጠ። ለሙና ምን ብዬ ልንገራት ? ልጅቱ ከቀን ወደ ቀን ጉዳዩን
እንድንፈፅመው አፍ አውጥታ በፅኑ መሻት ትጠይቀኛለች። እንደውም ከሌላ ሴት ጋር አንዳች ጉዳይ የጀመርኩና የገፉኋት እየመሰላት መጠራጠር ጀምራ ነበር ምነው ባደረገው..
መቀሌ እየሰራች ቢያንስ በየወሩ እርሷ ወይም እኔ እየመጣችና እየሄድኩኝ አስደሳች ጊዜ እናሳልፍ
ነበር። ግን ምን ያደርጋል ይሄ የእኔ ነገር ጥላውን አጠላብን።
“ከዚህ በላይ መታገስ አይችልም፡፡ችግር ካለብኝንገረኝ፤ ወይም ካስጠላሁህ በቃ አሳውቀኝ
ፕ…ሊስ አለችኝ አንድ ቀን የአይጥና ድመት ድብብቆሻችን አሰልችቷት። እናም ማስጠንቀቂያ ጨመረችበት፣ “ለሚቀጥለው ስመጣ ካላደረግን የእኔና ያንተ ጉዳይ አበቃ !' ሙና ታደርገዋለች። ጭካኔዋ በፍቅሯ ልክ ነው፤ ቀልድ አታውቅም። ተንቀዥቅዤ አነሳስቼ በምን ላስቁማት ? ቆይ ሰው ንብረቱ እንደሚሠራ እና እንደማይሠራ ሳያረጋግጥ እንዲህ ዓይነት እዳ ውስጥ ይዘፈቃል ?! ቢጨንቀኝ ነው እንጂ እሱማ
እንዴት ይረጋገጣል ?እንደ ደም ግፊት አይለካ ነገር።
ሳወጣና ሳወርድ አድሬ ለሃኒባል ሳማክረው ወሰንኩ። ሃኒባል አብሮ አደግ ጓደኛዬ ነው፧ የልብ ጓደኛዬ። ከሙናም ጋር በደንብ ይተዋወቃሉ። እናም ላሳውቀው ወሰንኩ። ሃኒባል ቢያንስ ለምንም
ነገር አይጨነቅም። መፍትሄም አያጣም። ከድሮውም ልጅ ሆነን እኮ ነው … በቃ ችግር በሃኒባል ፊት የቱንም ያህል ቢገዝፍ እንደ ዝንብ ነው በመፍትሄ ጭራ የሚያባርረው። ደወልኩለትና፣ና እሬሳህን ውሰድ ልለው አስቤ ተውኩት፤ እፈልግሃለሁ” ብቻ አልኩት።
ምን ጉድ ተፈጥሮ ነው እንዲህ እያግለበለብክ ያስመጣኸኝ ጃል ?" አለ ሃኒባል ያዘዘውን ቡና
አማሰለ።
"ባክህ ችግር ገጥሞኛል”
"ችግር የሚባል ነገር የለም ባክህ፤ የመፍትሄ እጥረት በለው” አለ (አላልኳችሁም ?)
"እ..እንዴት መሰለሀ ከሙናጋ የሆነ ትንሽ ችግር ... ኧረ ምን ትንሽ …. ትልቅ ችግር ውስጥ ገብተናል”
አልኩት።"
ቡና ማማሰሉን አቆመና ኮስተር ብሎ፣ “የምን ችግር…” አለኝ።
"እኔ ለካ … እንትን …. ማድረግ አልችልም አሁን ነው ያወቅኩት”
"ምን ማድረግ ?”
ኤጭ ሥሙን ቄስ ይጥራውና እንዴት እንደቀፈፈኝ፣
“ግንኙነት ማድረግ አልችልም"
“የምን ግንኙነት ?"
“የምን ግንኙነት ትለኛለህ እንዴ … ወሲብ ነዋ!" ስል አፈረጥኩት።
"እ...ንዴ ! እና እስከዛሬ ከሙና ጋር ስታድሩ ምን እየሰራችሁ ነበር የምታድሩት ?"
“በቃ ትኝት ነዋ አርፈን … ማለቴ አርፌ"
“ትኝት ትኝት .… ለሽሽ ?”
“አዎ !"
"አንተስ እሺ … ሙና እንዴት አስቻላት ?"
“ያው ላያስችል አይሰጥም”
“ኧረ ሰውዬ ተረቱን አቁምና ወደ መፍትሄው!”
"እኮ! መፍትሄው እኮ ነው የጠፋብኝ፤ ሙና ደግሞ ደበራት”
"እንዴት ነው የማይደብራት፣ ትቀልዳለህ እንዴ ?” ብሎ ተነስቶ ወጣ። አካሄዱ አስደንግጦኝ ዝም ብዬ እንደተቀመጥኩ ትንሽ ቆይቶ አንድ መፅሄት ይዞ ተመለሰ። ከነወንበሩ ጠጋ ብሎኝ የመጽሄቱ የኋላ ሽፋን ላይ በውስጥ በኩል የታተመ ማስታወቂያ ጠቆመኝ።
“ደብተራ ግዛው ደበሌ የባሕል ሕክምና አዋቂ” ይላል። ጥምጣማቸው የሚያምር አፍንጫቸው ደፍጠጥ ያለ ደብተራ ሳይሆን ቦክሰኛ የሚመስሉ ሰውዬ ባለቀለም ፎቶ ሩብ ገፁን ተቆጣጥሮ በኩራት ተገጥግጧል። የሰውየውን ኩራት ለተመለከተው መቼስ እንኳን ከበሽታ ከሞት የሚያድኑ ሳይመስለው አይቀርም። ከሥር “መፍትሔ የተገኘላቸው ሕመሞች” ዝርዝር ሰፍሯል...
ለዓይነ ጥላ
ለቡዳ
ትምህርት ለማይገባው (ከድድብና የባሰ በሽታ የለም ብለው ይሆን)
ለሽንፈተ ወሲብ
ለስንፈተ ወሲብ ….
ቢንጎ !! ግን ስንፈተና ሽንፈተ ወሲብ ልዩነታቸው ምንድን ነው ?
አድራሻ ጦር ኃይሎች! እፎይይይ ሙና ተመልሳ ልትመጣ ሰላሳ አራት ቀናት ብቻ ይቀራሉ።
“በዚህ ሰላሳ አራት ቀናት ደብተራ ግዛው ተዓምር ፈጥረው የወደቀውን እንደሚያነሱት፣ የተኛውንም እንደሚያቀኑት ተስፋ እናደርጋለን አይዞህ ወዳጄ” ሃኒባል አፅናናኝ።
እናም ታሪካዊው ጉዞ ወደ ጦር ኃይሎች። የጠፋውን ወንድነት ፍለጋ። ወንድነትን ለመፈለግ፣
መኮላሸትን እምቢ ልንል
እንኳን ጦር ኃይሎች ጦር ሜዳ እንዘምታለን።
ኧ…ረ
ጎራው…
አልዋጋም ብሎ የተኛውን አውሬ.
ቆስቁሰው ቆስቁሰው አደረጉት አውሬ ... አለ ያገሬ አሽቀራሪ - መጣንልሽ ሙና !!
“በመጪዎቹ ሰላሳ አራት ቀናት የወንድነት ሕዳሴን ለማረጋገጥ ከደብተራ ግዛው ደበሌ ጋር ወ ደ ፊ ት !!”
ይሄ ሃኒባል የሚባል ልጅ እኮ የማይቀልድበት ችግር፣ በንቀት የማይመለከተው መከራ የለም፤ እንዲህ ጨንቆኝ እንኳ በግድ ፈገግ ያስብለኛል።
ጦር ኃይሎች እስከምንደርስ ሃኒባል ቀልድ እያወራ ብሶቴን ሊያስረሳኝ ቢሞክርም በፍፁም መርሳት አልቻልኩም። “አቡቹ ጣጣ የለውም ሰውዬው አደገኛ ናቸው፤ እንደ መኪና ተረክ አድርገው ነው የሚያስነሱት” ይለኛል። አይ ተረክ ... በስንት ጉድ ግፊ፣ እንደ ነዳጅ በትኩሳት የምትነድ ልጅ አየተማፀነችው ለሽሽ ያለ 'እንትን' እንዴት ነው ተረክ ብሎ የሚነሳው ? መርሳት ብቻ ሳይሆን የሆነውን
ሁሉ ማመን አልቻልኩም። ብቻ ቶሎ ይሄ ሰውዬ የሚያደርጉትን ባደረጉና
ጦር ኃይሎች የተባለው ሰፈር ደረስን፤ ዓየር ጤና አካባቢ ነው
አሉን፤ ዓየር ጤና ሄድን - ዘነበ ወርቅ፣ ከዛ ወይራ ሰፈር ... አንዲት ጭርንቁስ በቅጠላቅጠል የታጠረች አጥር ውስጥ ያዘመመች የጭቃ ቤት። “ይሄ
ነው ቤቱ” አሉን። አሁን ማን ይሙት ይሄን ቤታቸውን በስርዓት ያላቆሙ ሰውዬ ሌላ ነገር ያቆማሉ ?
እንደዚህ እያሰብኩ አሮጌውን የቆርቆሮ በር ገፍተን ገባን።
አንድ የቆሸሸ ቱታ የለበሰ ጎልማሳ ሰው አገኘን።
“ደብተራ ግዛውማ ቦሌ ምን የመሰለ ቢላ ቤት ገዝቶ ሄደ እናትዬ፤ ዛሬ ጆሮውን ቢቆርጡት የማይሰማ ኃብታም ሁኗል። ሰው ሁሉ በባዶ እግሩ ከገጠር እየመጣ እንዲህ ባለፀጋ ይሆናል፤ እኛ ነን የአርባ ቀን እድላችን ከአፈር አትነሱ ብሎን.." እያለ ብሶቱን ይዘረግፈው ገባ።
ተመለስን።
“እንዳንከራተትሽኝ አላህ ያንከራትሽ አለ አሉ ሰውየው፤ ጨረቃን መግቢያዋን አያለሁ ብሎ ሲከተል ከርም አልሆን ቢለው እኮ ነው። ስንመለስ ሃኒባል እንዲህ አለኝ፣ “አቡቹ አየህ የዚህን አገር ነገር፡ አንተ በቀን ስምንት ሰዓት ቆመህ በየወሩ የቤት ኪራይ መክፈል የማትችል ደመወዝ ትከፈላለሁ አጅሬው እንትን ከቁሞ ቪላ ይገዛል ያውም ቦሌ”
“ተናግረህ ሞተሃል፤ እንትን ከማቆም በላይ ለአንዲት አገር ምን ትልቅ ሥራ አለ” ብዬ ገላመጥኩት:
“አብርሽ እንዲህማ አትነጫነጭ፣ ይቆማል አይዞህ”
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ትከክክክክክ ብላ ስታየኝ እንዲህ እላታለሁ፣
“ከጋብቻ በኋላ”
በዚህ የጭንቅ ሰዓት ላይ እያለሁ ሙናን የምትሰራበት ባንክ ወደ መቀሌ ቅርንጫፍ ቀየራት። ይሄማ
የእግዜር እጅ አለበት። ደስ አለኝ። ስሸኛት አለቀሰች። ለአዲስ አበባ ሳይሆን ከእኔ በመለየቷ፤ እና ደግሞ ከብረት የጠነከረ መሻትን ድል ሰመታ ከእሳት ለተፈተነ ትዕግስቴ” (እሷ እንደዛ ነው የሚመስላት) ለእኔ ግን ጉዳዩን ለራሴ እንኳን ማመን ባልፈልግም ገብቶኛል። ስንፈተ ወሲብ !! ያውም እንደ መርዶ ለራሴም ድንገት ዱብ ብሎ የተገለጠ። ለሙና ምን ብዬ ልንገራት ? ልጅቱ ከቀን ወደ ቀን ጉዳዩን
እንድንፈፅመው አፍ አውጥታ በፅኑ መሻት ትጠይቀኛለች። እንደውም ከሌላ ሴት ጋር አንዳች ጉዳይ የጀመርኩና የገፉኋት እየመሰላት መጠራጠር ጀምራ ነበር ምነው ባደረገው..
መቀሌ እየሰራች ቢያንስ በየወሩ እርሷ ወይም እኔ እየመጣችና እየሄድኩኝ አስደሳች ጊዜ እናሳልፍ
ነበር። ግን ምን ያደርጋል ይሄ የእኔ ነገር ጥላውን አጠላብን።
“ከዚህ በላይ መታገስ አይችልም፡፡ችግር ካለብኝንገረኝ፤ ወይም ካስጠላሁህ በቃ አሳውቀኝ
ፕ…ሊስ አለችኝ አንድ ቀን የአይጥና ድመት ድብብቆሻችን አሰልችቷት። እናም ማስጠንቀቂያ ጨመረችበት፣ “ለሚቀጥለው ስመጣ ካላደረግን የእኔና ያንተ ጉዳይ አበቃ !' ሙና ታደርገዋለች። ጭካኔዋ በፍቅሯ ልክ ነው፤ ቀልድ አታውቅም። ተንቀዥቅዤ አነሳስቼ በምን ላስቁማት ? ቆይ ሰው ንብረቱ እንደሚሠራ እና እንደማይሠራ ሳያረጋግጥ እንዲህ ዓይነት እዳ ውስጥ ይዘፈቃል ?! ቢጨንቀኝ ነው እንጂ እሱማ
እንዴት ይረጋገጣል ?እንደ ደም ግፊት አይለካ ነገር።
ሳወጣና ሳወርድ አድሬ ለሃኒባል ሳማክረው ወሰንኩ። ሃኒባል አብሮ አደግ ጓደኛዬ ነው፧ የልብ ጓደኛዬ። ከሙናም ጋር በደንብ ይተዋወቃሉ። እናም ላሳውቀው ወሰንኩ። ሃኒባል ቢያንስ ለምንም
ነገር አይጨነቅም። መፍትሄም አያጣም። ከድሮውም ልጅ ሆነን እኮ ነው … በቃ ችግር በሃኒባል ፊት የቱንም ያህል ቢገዝፍ እንደ ዝንብ ነው በመፍትሄ ጭራ የሚያባርረው። ደወልኩለትና፣ና እሬሳህን ውሰድ ልለው አስቤ ተውኩት፤ እፈልግሃለሁ” ብቻ አልኩት።
ምን ጉድ ተፈጥሮ ነው እንዲህ እያግለበለብክ ያስመጣኸኝ ጃል ?" አለ ሃኒባል ያዘዘውን ቡና
አማሰለ።
"ባክህ ችግር ገጥሞኛል”
"ችግር የሚባል ነገር የለም ባክህ፤ የመፍትሄ እጥረት በለው” አለ (አላልኳችሁም ?)
"እ..እንዴት መሰለሀ ከሙናጋ የሆነ ትንሽ ችግር ... ኧረ ምን ትንሽ …. ትልቅ ችግር ውስጥ ገብተናል”
አልኩት።"
ቡና ማማሰሉን አቆመና ኮስተር ብሎ፣ “የምን ችግር…” አለኝ።
"እኔ ለካ … እንትን …. ማድረግ አልችልም አሁን ነው ያወቅኩት”
"ምን ማድረግ ?”
ኤጭ ሥሙን ቄስ ይጥራውና እንዴት እንደቀፈፈኝ፣
“ግንኙነት ማድረግ አልችልም"
“የምን ግንኙነት ?"
“የምን ግንኙነት ትለኛለህ እንዴ … ወሲብ ነዋ!" ስል አፈረጥኩት።
"እ...ንዴ ! እና እስከዛሬ ከሙና ጋር ስታድሩ ምን እየሰራችሁ ነበር የምታድሩት ?"
“በቃ ትኝት ነዋ አርፈን … ማለቴ አርፌ"
“ትኝት ትኝት .… ለሽሽ ?”
“አዎ !"
"አንተስ እሺ … ሙና እንዴት አስቻላት ?"
“ያው ላያስችል አይሰጥም”
“ኧረ ሰውዬ ተረቱን አቁምና ወደ መፍትሄው!”
"እኮ! መፍትሄው እኮ ነው የጠፋብኝ፤ ሙና ደግሞ ደበራት”
"እንዴት ነው የማይደብራት፣ ትቀልዳለህ እንዴ ?” ብሎ ተነስቶ ወጣ። አካሄዱ አስደንግጦኝ ዝም ብዬ እንደተቀመጥኩ ትንሽ ቆይቶ አንድ መፅሄት ይዞ ተመለሰ። ከነወንበሩ ጠጋ ብሎኝ የመጽሄቱ የኋላ ሽፋን ላይ በውስጥ በኩል የታተመ ማስታወቂያ ጠቆመኝ።
“ደብተራ ግዛው ደበሌ የባሕል ሕክምና አዋቂ” ይላል። ጥምጣማቸው የሚያምር አፍንጫቸው ደፍጠጥ ያለ ደብተራ ሳይሆን ቦክሰኛ የሚመስሉ ሰውዬ ባለቀለም ፎቶ ሩብ ገፁን ተቆጣጥሮ በኩራት ተገጥግጧል። የሰውየውን ኩራት ለተመለከተው መቼስ እንኳን ከበሽታ ከሞት የሚያድኑ ሳይመስለው አይቀርም። ከሥር “መፍትሔ የተገኘላቸው ሕመሞች” ዝርዝር ሰፍሯል...
ለዓይነ ጥላ
ለቡዳ
ትምህርት ለማይገባው (ከድድብና የባሰ በሽታ የለም ብለው ይሆን)
ለሽንፈተ ወሲብ
ለስንፈተ ወሲብ ….
ቢንጎ !! ግን ስንፈተና ሽንፈተ ወሲብ ልዩነታቸው ምንድን ነው ?
አድራሻ ጦር ኃይሎች! እፎይይይ ሙና ተመልሳ ልትመጣ ሰላሳ አራት ቀናት ብቻ ይቀራሉ።
“በዚህ ሰላሳ አራት ቀናት ደብተራ ግዛው ተዓምር ፈጥረው የወደቀውን እንደሚያነሱት፣ የተኛውንም እንደሚያቀኑት ተስፋ እናደርጋለን አይዞህ ወዳጄ” ሃኒባል አፅናናኝ።
እናም ታሪካዊው ጉዞ ወደ ጦር ኃይሎች። የጠፋውን ወንድነት ፍለጋ። ወንድነትን ለመፈለግ፣
መኮላሸትን እምቢ ልንል
እንኳን ጦር ኃይሎች ጦር ሜዳ እንዘምታለን።
ኧ…ረ
ጎራው…
አልዋጋም ብሎ የተኛውን አውሬ.
ቆስቁሰው ቆስቁሰው አደረጉት አውሬ ... አለ ያገሬ አሽቀራሪ - መጣንልሽ ሙና !!
“በመጪዎቹ ሰላሳ አራት ቀናት የወንድነት ሕዳሴን ለማረጋገጥ ከደብተራ ግዛው ደበሌ ጋር ወ ደ ፊ ት !!”
ይሄ ሃኒባል የሚባል ልጅ እኮ የማይቀልድበት ችግር፣ በንቀት የማይመለከተው መከራ የለም፤ እንዲህ ጨንቆኝ እንኳ በግድ ፈገግ ያስብለኛል።
ጦር ኃይሎች እስከምንደርስ ሃኒባል ቀልድ እያወራ ብሶቴን ሊያስረሳኝ ቢሞክርም በፍፁም መርሳት አልቻልኩም። “አቡቹ ጣጣ የለውም ሰውዬው አደገኛ ናቸው፤ እንደ መኪና ተረክ አድርገው ነው የሚያስነሱት” ይለኛል። አይ ተረክ ... በስንት ጉድ ግፊ፣ እንደ ነዳጅ በትኩሳት የምትነድ ልጅ አየተማፀነችው ለሽሽ ያለ 'እንትን' እንዴት ነው ተረክ ብሎ የሚነሳው ? መርሳት ብቻ ሳይሆን የሆነውን
ሁሉ ማመን አልቻልኩም። ብቻ ቶሎ ይሄ ሰውዬ የሚያደርጉትን ባደረጉና
ጦር ኃይሎች የተባለው ሰፈር ደረስን፤ ዓየር ጤና አካባቢ ነው
አሉን፤ ዓየር ጤና ሄድን - ዘነበ ወርቅ፣ ከዛ ወይራ ሰፈር ... አንዲት ጭርንቁስ በቅጠላቅጠል የታጠረች አጥር ውስጥ ያዘመመች የጭቃ ቤት። “ይሄ
ነው ቤቱ” አሉን። አሁን ማን ይሙት ይሄን ቤታቸውን በስርዓት ያላቆሙ ሰውዬ ሌላ ነገር ያቆማሉ ?
እንደዚህ እያሰብኩ አሮጌውን የቆርቆሮ በር ገፍተን ገባን።
አንድ የቆሸሸ ቱታ የለበሰ ጎልማሳ ሰው አገኘን።
“ደብተራ ግዛውማ ቦሌ ምን የመሰለ ቢላ ቤት ገዝቶ ሄደ እናትዬ፤ ዛሬ ጆሮውን ቢቆርጡት የማይሰማ ኃብታም ሁኗል። ሰው ሁሉ በባዶ እግሩ ከገጠር እየመጣ እንዲህ ባለፀጋ ይሆናል፤ እኛ ነን የአርባ ቀን እድላችን ከአፈር አትነሱ ብሎን.." እያለ ብሶቱን ይዘረግፈው ገባ።
ተመለስን።
“እንዳንከራተትሽኝ አላህ ያንከራትሽ አለ አሉ ሰውየው፤ ጨረቃን መግቢያዋን አያለሁ ብሎ ሲከተል ከርም አልሆን ቢለው እኮ ነው። ስንመለስ ሃኒባል እንዲህ አለኝ፣ “አቡቹ አየህ የዚህን አገር ነገር፡ አንተ በቀን ስምንት ሰዓት ቆመህ በየወሩ የቤት ኪራይ መክፈል የማትችል ደመወዝ ትከፈላለሁ አጅሬው እንትን ከቁሞ ቪላ ይገዛል ያውም ቦሌ”
“ተናግረህ ሞተሃል፤ እንትን ከማቆም በላይ ለአንዲት አገር ምን ትልቅ ሥራ አለ” ብዬ ገላመጥኩት:
“አብርሽ እንዲህማ አትነጫነጭ፣ ይቆማል አይዞህ”
👍28❤2🔥1
#አንዲት_መርፌ_ስንቱን_ቀዳዳ_ትስፋው
፡
፡
#ሶስት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እኔ ይሄን ስድብ በፀጋ ተቀብዬ እግር ማየቴን መቼም አላቆምም። የሴት ልጅ እግር የውበት ጥጌ
ነው። ለሰርጌ ቀን አይበለውና እግሯ የሚያምር ግን አንገቷ የተቆረጠ ሴት ጎኔ አምጥተው ሚስትህ ናት ቢሉኝ፣ “በደስታ ይሁን በሐዘን…” ብዬ ከመፈረም አልመለስም። እንዲህ የምንሰፈሰፍለት፣የምማልልለት፣ የምልከሰከስለት፣ ልክስክስክስ የምልለት የሴት ልጅ እግር እንደኔ እንደኔ በሁለት ትላልቅ ክፍል ይከፈላል፣
1ኛ የዓለም ሴቶች እግር ሁሉ በአጠቃላይ ማለት ነው።
2ኛ. የዙቤይዳ እግር ! በቃ እኔን የሚያልከሰክሰኝ፣ በምኞት አፌን የሚያስከፍተኝ፣ ሳመው ሳመው
የሚለኝ ይሄ ሁለተኛው እግር ነው። እናም ድንገት ከቀሚሷ ወጣ ብሎ ፍም የመሰለ ተረከዟ፣የሕፃን
ልጅ ጣት የመሳሰሉ ጣቶቿ፣ ውሃ የመሰሉ (መስተዋትም ይመስሉኛል) ጥፍሮቿ፣ ምንም ቀለም ሳይቀቡ ደግሞ የቁርጭምጭሚት አጥንቶቿ ብይ ብይ መስለው ጠቆር ያለው አረቢያን መጅሊስ ላይ
እንደ እሳት ሲንቀለቀሉ ሳይ ቀልቤን ሳትኩ። ዜድዬ እኮ ለእኔ ሰርክ አዲስ ነች። አይቼ አልጠግባትም ።ተንደርድሬ ሄጄ እግሮቿን ብስማቸው ደስታዬ፤ የሆነ ነገር ሂድ ሂድ እያለ ይገፋኛል።
እ.? ”አሉኝ የዜድ አባት
“እ?…” አልኳቸው እኔም፣ የተናገሩትን ባለመስማቴ አፍሬም ደንግጬም ነበር፤(ታዲያ ምን ላድርግ እኔ የብቸኝነት፣ የክህደት፣ የውሸት፣ የማስመሰል፣ የጥቅም ማሳደድ እና የዝሙት ቆፈን በሚያቆራምደው ከተማ፣ የፍቅር እሳታቸውን ወልደው እሳት ውስጥ ቆሜ እንዴት ያሉትን ልስማ…? )
“እናቴዋ…ቀልቡን ወሰድ ያደርገዋል አንዳንዴ እንደ አብዱ” አሉ የዜድ እናት (ጎበዝ ኧረ ይሄ አብዱ ማነው…?) ዙቤይዳ ቡፍ ብላ ሳቀች። እናቷም ሰውነታቸው እስኪረግፍ ሳቁ። አባቷግን ኮስተር እንዳሉ ፂማቸውን በመዳፋቸው እየዳሰሱ ዝም ብለው ቆዩ። በዝምታው ውስጥ ድምፃቸው የሚያማምር ሕፃናት ከሩቅ በስርቅርቅ ድምፃቸው ቁርዓን ሲቀሩ ይሰማል። ለምን እንደሆነ ባላውቅም የሕፃናቱ ድምፅ፣ የአባቷ ዝምታ፣ የዙቤይዳ አቀርቅራ በክሪሟ መጫወት ተዳምሮ ዜድን ላጣት ከዜድ ጋር
ልንለያይ ሴኮንዶች የቀሩ መሰለኝ። ምፅአት መሰለኝ። ድንገት ነው በቃ እንደዚህ የተሰማኝ። እንባዬ
ሁሉ ይታገለኝ ጀመረ እልህ ውስጤ ተንተከተከ።
የዜድዬ እናት ድንገት ዝምታውን ሰብረው፣ “ዘምዘም…” ብለው ተጣሩ ።
“አቤትእማማ ! ብላ የዙቤይዳ እህት ከውስጠኛው ክፍል የግቢ በር የሚያክለውን በጌጥ የተሽቆጠቆጠ ባለሁለት ተከፋች የጣውላ በር ከፍታ ገባች። ዘምዘም ቁመቷ የትየለሌ ነው። በዛ ቁመት ላይ ሙልት ያለ ሰውነቷ ተጨምሮበት ክብድ የሚል ነገር አላት። ሳሎኑ ውስጥ መጥታ ስትቆም የሆነ ረዥም ማማ
ነገር የቆመ ነበር የሚመስለው፣ አንጋጥጬ ሽቅብ ተመለከትኳት። ኮስተር አለችብኝ። አሁን የመረረው
ባላጋራ መጣ አልኩ በሆዴ። በተቻለኝ መጠን ዘምዘምን ላለማየት ወደ ዙቤይዳ ዞርኩ፤ ፈገግ አለችልኝ ወደ ዘምዘም በድፍረት ዞርኩ ቡትሌ አክላ ታየችኝ፡፡አስማተኛው የዜድ ፈገግታ እንኳን አንዲት ሴት ኪሊማንጃሮን በፊቴ ጠጠር ያሳክለዋል። ከፍቅር የሚገዝፍ ነገር የለማ !
“ምሳ አልደረሰም እንዴ? እንግዳ ጠርታችሁ በራብ ልትገሉት ነው እንዴ” አሉ እማማ። ዘምዘም
ክፉ ደግ ሳትናገር ወደ ውስጥ ተመልሳ ገባች። እኛም በዝምታችን እንደፀናን በሩ ተበረገደና የምግብ መፈክር ያነገቱ ሰላማዊ ሰልፈኞች ወደ ሳሎኑ ተግተልትለው ገቡ አራት እህትና አንዲት ሠራተኛ።
ዘሐራም ከሰልፈኞቹ አንዷ ነበረች። የያዘችውን ሰሐን በትኩረት ተመለከትኩት። “እሷ ከያዘችው ሰሐን አልበላም” አልኩ ለራሴ። ሠራተኛዋ ምንጣፉ መሐል ላይ አንድ ሰፊ ክብ ላስቲክ አነጠፈች። ከዛ የምግብ ዓይነት በሚያማምር ሰፋፊ የሸክላ ሰሀኖች ተደረደሩ። ላስቲኩ ላይ ዙሪያውን የተደረደሩትን
ነጫጭ ሰሀኖች በክብ ተደርድረው ስመለከት በፀሐይ ዙሪያ ምህዋራቸውን ተከትለው የሚሽከረከሩ ፕላኔቶች ሥዕል ትዝ አለኝ።
ሰልፈኞቹ ወጡና ሌላ ሰሐን ይዘው ተመለሱ(ምንድን ነው ይሄ ሁሉ ጉድ)። ብስኩቱ፣ ጣፋጩ፣ ስሙን
የማላውቀው ነገር ሁሉ በዓይነት ተደረደረ። አንድ ነገር ውስጤን በሐዘን ሞላው። ዙቤይዳ ሱቅ ፀሐይ ልንሞቅ ስንቀመጥ የምጋብዛትን ቦንቦሊኖ ለመብላት ቁርስ ሳትበላ ትመጣ እንደነበር አስታወስኩ።እውነቴን ነው ይሄን ማዕድ ስለ ፍቅር ረግጣ፣ “አብርሽ ኧረ ርቦኛል ቦንቦሊኖ ግዛልኝ…” ትላለች።ፀሐያችንን እየሞቅን ፊት ለፊታችን ካለች ሻይ ቤት ቦንቦሊኖ አዝዘን እየተጎራረስን በሻይ እንበላለን።እንደውም አንድ ጊዜ አረፋ በዓል ሆኖ የነዙቤይዳ ሱቅ ዝግ ነበር፤ እኔ ተቀጥሬ የምሠራበት ሱቅ ደግሞ
አልተዘጋም፤ ዙቤይዳ ከቤቷ ሹልክ ብላ መጥታ በበዓሉ ቀን እዛች ሻይ ቤት ሄድንና ቦንቦሊኖ በሻይ በላን። ለረመዳን ሙሉ ቀን ዙቤይዳ ስለማትበላ እኔም ሳልበላ የምውልባቸው ቀናት ይበዙ ነበር።
የዙቤይዳ እናት “በልና ወዲህ፣ ዙቤይዳ ነቅነቅ በይ እንጂ መታጠቢያ ቤቱን አሳይው” አሉ። ዙቤይዳ እየመራች በሚያምረው በር አልፋ ወደ መታጠቢያው ወሰደችኝ። አንዳንድ ነገሮች አሉ በአክብሮት ሲደረጉ ስድብ የሚሆኑ። የነዙቤይዳ መታጠቢያ ቤት ስፋት የአባቴን መኝታ ቤት ያክላል። የመታጠቢያ
ሸክላዎቹ ንጣት፣ የቤቱ አስደሳች ጠረን አፍ አውጥቶ የሰደበኝ መሰለኝ፣ “አንተ አመዳም ደሀ ልካችንን እየው…" የሚለኝ መሰለኝ። ዙቤይዳ ፈዝዤ መቆሜን ስታይ “ታጠብ…” አለችኝና ዞር ብላ ወደ ኋላዋ
ተመልክታ ማንም አለመኖሩን ካረጋገጠች በኋላ ጉንጬን ሳመችኝ። ከንፈሯ ይሞቃል። የሆነ ርጥበቱ ጉንጩ ላይ የቀረ መሰለኝ። ስትስመኝ ድንጋጤው ይሁን ንዝረቱ አስበረገገኝ። “ብቻችንን ከሆንን አያስችለኝም ቶሎ ውጣ” አለችኝ እየሳቀች። እና ራሷ እጇን መታጠብ ጀመረች። በመስተዋቱ ውስጥ ዓይኖቿ አፍጥጠውብኝ ነበር። የመታጠቢያ ቤቱ ውበት ውበቷን አጉልቶት ነው መሰል፤ ዙቤይዳ
በጣም አማረችብኝ። ለዚህች ልጅማ አንድ ሰውና አንድ ጥይት እስኪቀር ታጥበን ወጣን።
ወደ ሳሎን ስንመለስ የዙቤይዳ እናት ኖር.. አሉኝ፣ አባቷ ግን አሁንም ፂማቸውን እያሻሹ ዝም
ብለው ተቀምጠዋል። እንደውም ከቅድሙ በላይ ፊታቸው ተቀያይሮ ቁጣ ነበር ከግንባራቸው
የሚስፈነጠረው። ወደ መታጠቢያ ቤቱ እንደገባን የዜድ እናት ጋር የሆነ ነገር እንደተነጋገሩ ገመትኩ።
እንዴት ይጨንቃሉ። ዘሐራ ጭልፉ ይዛ ስትገባ፣ እኛ ታጥበን ስንወጣ አንድ ሆነ። እንደው ይህች ልጅ
ደንቃራ ነገር ናት ልበል። በግርምት እግሬን ተመለከተችኝ። ዓይኗን ተከትዬ ወደ እግሬ ስመለከት ወደ
መታጠቢያ ቤት ስገባ ያደረግኩት የዙቤይዳን ሰንደል ጫማ ነበር። ያውም ብዙ ጊዜ ኡዱ ስታደርግ
የምትጫማውን። እሾህ ! ዓይኗ የማያየው ነገር የለም። እኔ ራሴ ጫማ ላድርግ፣ በእግሬ ልሁን ትዝ
ያለኝ አሁን ነው።
አንዲት ትንሽ ትራስ ነገር ከተሰደረው ምግብ ፊት ዙቤይዳ አመቻቸችልኝና ተቀመጥኩ። አባቷ
ከምግቡ ክምር ወዲያ፣ እኔ ወዲህ። ምግብን ድንበር አድርገን የተፋጠጥን ጠላቶች። (አንቱ ወዲያ ማዶ፣ እኔ ወዲህ ማዶ፣ አንገናኝም ወይ ተራራው ተንዶ..) መብላት አልቻልኩም። አባቷ ዓይኔን ላለማየት ሲሸሹ ምግቡ ዘጋኝ። በቤታቸው ምግብ አቅርበው ፊታቸውን ሲያጠቁሩብኝ ለልመና የመጣሁ እስኪመስለኝ አፈርኩ ተሳቀቅኩ። ዙቤይዳ ገብቷታል። ምንም ነገር ሳትፈራ ሰሀኔ ላይ እንጀራና ንጣቱ
፡
፡
#ሶስት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እኔ ይሄን ስድብ በፀጋ ተቀብዬ እግር ማየቴን መቼም አላቆምም። የሴት ልጅ እግር የውበት ጥጌ
ነው። ለሰርጌ ቀን አይበለውና እግሯ የሚያምር ግን አንገቷ የተቆረጠ ሴት ጎኔ አምጥተው ሚስትህ ናት ቢሉኝ፣ “በደስታ ይሁን በሐዘን…” ብዬ ከመፈረም አልመለስም። እንዲህ የምንሰፈሰፍለት፣የምማልልለት፣ የምልከሰከስለት፣ ልክስክስክስ የምልለት የሴት ልጅ እግር እንደኔ እንደኔ በሁለት ትላልቅ ክፍል ይከፈላል፣
1ኛ የዓለም ሴቶች እግር ሁሉ በአጠቃላይ ማለት ነው።
2ኛ. የዙቤይዳ እግር ! በቃ እኔን የሚያልከሰክሰኝ፣ በምኞት አፌን የሚያስከፍተኝ፣ ሳመው ሳመው
የሚለኝ ይሄ ሁለተኛው እግር ነው። እናም ድንገት ከቀሚሷ ወጣ ብሎ ፍም የመሰለ ተረከዟ፣የሕፃን
ልጅ ጣት የመሳሰሉ ጣቶቿ፣ ውሃ የመሰሉ (መስተዋትም ይመስሉኛል) ጥፍሮቿ፣ ምንም ቀለም ሳይቀቡ ደግሞ የቁርጭምጭሚት አጥንቶቿ ብይ ብይ መስለው ጠቆር ያለው አረቢያን መጅሊስ ላይ
እንደ እሳት ሲንቀለቀሉ ሳይ ቀልቤን ሳትኩ። ዜድዬ እኮ ለእኔ ሰርክ አዲስ ነች። አይቼ አልጠግባትም ።ተንደርድሬ ሄጄ እግሮቿን ብስማቸው ደስታዬ፤ የሆነ ነገር ሂድ ሂድ እያለ ይገፋኛል።
እ.? ”አሉኝ የዜድ አባት
“እ?…” አልኳቸው እኔም፣ የተናገሩትን ባለመስማቴ አፍሬም ደንግጬም ነበር፤(ታዲያ ምን ላድርግ እኔ የብቸኝነት፣ የክህደት፣ የውሸት፣ የማስመሰል፣ የጥቅም ማሳደድ እና የዝሙት ቆፈን በሚያቆራምደው ከተማ፣ የፍቅር እሳታቸውን ወልደው እሳት ውስጥ ቆሜ እንዴት ያሉትን ልስማ…? )
“እናቴዋ…ቀልቡን ወሰድ ያደርገዋል አንዳንዴ እንደ አብዱ” አሉ የዜድ እናት (ጎበዝ ኧረ ይሄ አብዱ ማነው…?) ዙቤይዳ ቡፍ ብላ ሳቀች። እናቷም ሰውነታቸው እስኪረግፍ ሳቁ። አባቷግን ኮስተር እንዳሉ ፂማቸውን በመዳፋቸው እየዳሰሱ ዝም ብለው ቆዩ። በዝምታው ውስጥ ድምፃቸው የሚያማምር ሕፃናት ከሩቅ በስርቅርቅ ድምፃቸው ቁርዓን ሲቀሩ ይሰማል። ለምን እንደሆነ ባላውቅም የሕፃናቱ ድምፅ፣ የአባቷ ዝምታ፣ የዙቤይዳ አቀርቅራ በክሪሟ መጫወት ተዳምሮ ዜድን ላጣት ከዜድ ጋር
ልንለያይ ሴኮንዶች የቀሩ መሰለኝ። ምፅአት መሰለኝ። ድንገት ነው በቃ እንደዚህ የተሰማኝ። እንባዬ
ሁሉ ይታገለኝ ጀመረ እልህ ውስጤ ተንተከተከ።
የዜድዬ እናት ድንገት ዝምታውን ሰብረው፣ “ዘምዘም…” ብለው ተጣሩ ።
“አቤትእማማ ! ብላ የዙቤይዳ እህት ከውስጠኛው ክፍል የግቢ በር የሚያክለውን በጌጥ የተሽቆጠቆጠ ባለሁለት ተከፋች የጣውላ በር ከፍታ ገባች። ዘምዘም ቁመቷ የትየለሌ ነው። በዛ ቁመት ላይ ሙልት ያለ ሰውነቷ ተጨምሮበት ክብድ የሚል ነገር አላት። ሳሎኑ ውስጥ መጥታ ስትቆም የሆነ ረዥም ማማ
ነገር የቆመ ነበር የሚመስለው፣ አንጋጥጬ ሽቅብ ተመለከትኳት። ኮስተር አለችብኝ። አሁን የመረረው
ባላጋራ መጣ አልኩ በሆዴ። በተቻለኝ መጠን ዘምዘምን ላለማየት ወደ ዙቤይዳ ዞርኩ፤ ፈገግ አለችልኝ ወደ ዘምዘም በድፍረት ዞርኩ ቡትሌ አክላ ታየችኝ፡፡አስማተኛው የዜድ ፈገግታ እንኳን አንዲት ሴት ኪሊማንጃሮን በፊቴ ጠጠር ያሳክለዋል። ከፍቅር የሚገዝፍ ነገር የለማ !
“ምሳ አልደረሰም እንዴ? እንግዳ ጠርታችሁ በራብ ልትገሉት ነው እንዴ” አሉ እማማ። ዘምዘም
ክፉ ደግ ሳትናገር ወደ ውስጥ ተመልሳ ገባች። እኛም በዝምታችን እንደፀናን በሩ ተበረገደና የምግብ መፈክር ያነገቱ ሰላማዊ ሰልፈኞች ወደ ሳሎኑ ተግተልትለው ገቡ አራት እህትና አንዲት ሠራተኛ።
ዘሐራም ከሰልፈኞቹ አንዷ ነበረች። የያዘችውን ሰሐን በትኩረት ተመለከትኩት። “እሷ ከያዘችው ሰሐን አልበላም” አልኩ ለራሴ። ሠራተኛዋ ምንጣፉ መሐል ላይ አንድ ሰፊ ክብ ላስቲክ አነጠፈች። ከዛ የምግብ ዓይነት በሚያማምር ሰፋፊ የሸክላ ሰሀኖች ተደረደሩ። ላስቲኩ ላይ ዙሪያውን የተደረደሩትን
ነጫጭ ሰሀኖች በክብ ተደርድረው ስመለከት በፀሐይ ዙሪያ ምህዋራቸውን ተከትለው የሚሽከረከሩ ፕላኔቶች ሥዕል ትዝ አለኝ።
ሰልፈኞቹ ወጡና ሌላ ሰሐን ይዘው ተመለሱ(ምንድን ነው ይሄ ሁሉ ጉድ)። ብስኩቱ፣ ጣፋጩ፣ ስሙን
የማላውቀው ነገር ሁሉ በዓይነት ተደረደረ። አንድ ነገር ውስጤን በሐዘን ሞላው። ዙቤይዳ ሱቅ ፀሐይ ልንሞቅ ስንቀመጥ የምጋብዛትን ቦንቦሊኖ ለመብላት ቁርስ ሳትበላ ትመጣ እንደነበር አስታወስኩ።እውነቴን ነው ይሄን ማዕድ ስለ ፍቅር ረግጣ፣ “አብርሽ ኧረ ርቦኛል ቦንቦሊኖ ግዛልኝ…” ትላለች።ፀሐያችንን እየሞቅን ፊት ለፊታችን ካለች ሻይ ቤት ቦንቦሊኖ አዝዘን እየተጎራረስን በሻይ እንበላለን።እንደውም አንድ ጊዜ አረፋ በዓል ሆኖ የነዙቤይዳ ሱቅ ዝግ ነበር፤ እኔ ተቀጥሬ የምሠራበት ሱቅ ደግሞ
አልተዘጋም፤ ዙቤይዳ ከቤቷ ሹልክ ብላ መጥታ በበዓሉ ቀን እዛች ሻይ ቤት ሄድንና ቦንቦሊኖ በሻይ በላን። ለረመዳን ሙሉ ቀን ዙቤይዳ ስለማትበላ እኔም ሳልበላ የምውልባቸው ቀናት ይበዙ ነበር።
የዙቤይዳ እናት “በልና ወዲህ፣ ዙቤይዳ ነቅነቅ በይ እንጂ መታጠቢያ ቤቱን አሳይው” አሉ። ዙቤይዳ እየመራች በሚያምረው በር አልፋ ወደ መታጠቢያው ወሰደችኝ። አንዳንድ ነገሮች አሉ በአክብሮት ሲደረጉ ስድብ የሚሆኑ። የነዙቤይዳ መታጠቢያ ቤት ስፋት የአባቴን መኝታ ቤት ያክላል። የመታጠቢያ
ሸክላዎቹ ንጣት፣ የቤቱ አስደሳች ጠረን አፍ አውጥቶ የሰደበኝ መሰለኝ፣ “አንተ አመዳም ደሀ ልካችንን እየው…" የሚለኝ መሰለኝ። ዙቤይዳ ፈዝዤ መቆሜን ስታይ “ታጠብ…” አለችኝና ዞር ብላ ወደ ኋላዋ
ተመልክታ ማንም አለመኖሩን ካረጋገጠች በኋላ ጉንጬን ሳመችኝ። ከንፈሯ ይሞቃል። የሆነ ርጥበቱ ጉንጩ ላይ የቀረ መሰለኝ። ስትስመኝ ድንጋጤው ይሁን ንዝረቱ አስበረገገኝ። “ብቻችንን ከሆንን አያስችለኝም ቶሎ ውጣ” አለችኝ እየሳቀች። እና ራሷ እጇን መታጠብ ጀመረች። በመስተዋቱ ውስጥ ዓይኖቿ አፍጥጠውብኝ ነበር። የመታጠቢያ ቤቱ ውበት ውበቷን አጉልቶት ነው መሰል፤ ዙቤይዳ
በጣም አማረችብኝ። ለዚህች ልጅማ አንድ ሰውና አንድ ጥይት እስኪቀር ታጥበን ወጣን።
ወደ ሳሎን ስንመለስ የዙቤይዳ እናት ኖር.. አሉኝ፣ አባቷ ግን አሁንም ፂማቸውን እያሻሹ ዝም
ብለው ተቀምጠዋል። እንደውም ከቅድሙ በላይ ፊታቸው ተቀያይሮ ቁጣ ነበር ከግንባራቸው
የሚስፈነጠረው። ወደ መታጠቢያ ቤቱ እንደገባን የዜድ እናት ጋር የሆነ ነገር እንደተነጋገሩ ገመትኩ።
እንዴት ይጨንቃሉ። ዘሐራ ጭልፉ ይዛ ስትገባ፣ እኛ ታጥበን ስንወጣ አንድ ሆነ። እንደው ይህች ልጅ
ደንቃራ ነገር ናት ልበል። በግርምት እግሬን ተመለከተችኝ። ዓይኗን ተከትዬ ወደ እግሬ ስመለከት ወደ
መታጠቢያ ቤት ስገባ ያደረግኩት የዙቤይዳን ሰንደል ጫማ ነበር። ያውም ብዙ ጊዜ ኡዱ ስታደርግ
የምትጫማውን። እሾህ ! ዓይኗ የማያየው ነገር የለም። እኔ ራሴ ጫማ ላድርግ፣ በእግሬ ልሁን ትዝ
ያለኝ አሁን ነው።
አንዲት ትንሽ ትራስ ነገር ከተሰደረው ምግብ ፊት ዙቤይዳ አመቻቸችልኝና ተቀመጥኩ። አባቷ
ከምግቡ ክምር ወዲያ፣ እኔ ወዲህ። ምግብን ድንበር አድርገን የተፋጠጥን ጠላቶች። (አንቱ ወዲያ ማዶ፣ እኔ ወዲህ ማዶ፣ አንገናኝም ወይ ተራራው ተንዶ..) መብላት አልቻልኩም። አባቷ ዓይኔን ላለማየት ሲሸሹ ምግቡ ዘጋኝ። በቤታቸው ምግብ አቅርበው ፊታቸውን ሲያጠቁሩብኝ ለልመና የመጣሁ እስኪመስለኝ አፈርኩ ተሳቀቅኩ። ዙቤይዳ ገብቷታል። ምንም ነገር ሳትፈራ ሰሀኔ ላይ እንጀራና ንጣቱ
👍19👏2
#ከሰሀራ_በታች
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
....ፋና ጋር መቀራረብ በጣም ከባድ ነበረ፡፡ አንዳንዴ ባህሪዋ ያበሳጨኛል፡፡ “ምናይነት የደነዘዘች ልጅ ናት” እልና ለራሴ ቁጣ ቁጣ ይለኛል፡፡ ለምን እንደ ፍቅርተ አታናግረኝም ? ሌላው ቢቀር አንድ ዓመት ሙሉ እዚህ ቤት ስኖር ቤቴን እንኳን ተሳስታ ረግጣው አታውቅም፡፡ ፍቅርተ እኮ
እናት ማለት ናት፡፡ ረፍዶብኝ ፍራሼን ሳላነጣጥፍ ከወጣሁ ፍራሼን አነጣጥፋ፣ ያዝረከረኩትን
ወረቀት አስተካክላ የሚጠጣ ውሃ ቀድታ አስቀምጣልኝ ነው የማገኘው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
ደግሞ ምግቤንም የምትሰራልኝ ፍቅርተ ናት፡፡ እች ፋና የሚሏት ዝግ ግን…ዝምታዋ ሰልችቶኝ
ነበር፡፡
የሆነ ጊዜ ታዲያ ድንገት ታመምኩ፡፡ ለሳምንት ትምህርት ቤት አልሄድኩም፤ ፍቅርተና እማማ
አመለ ተጨንቀው ሲሯሯጡ ሰነበቱ፡፡ ፋና ዝርም ብላ አታውቅም፡፡ ከዛን ጊዜ በኋላ የፉና ነገር በቃኝ፡፡ “እግዜር ይግደልህ !” ማንን ገደለ? አንድ ቀን ሳትጠይቀኝ በቃ ድኜ ተነሳሁ፡፡
ፋና የምትባል ልጅ በቃ በቃችኝ፡፡ ሳልፍ ሳገድም እወረውርላት የነበረውን ሰላምታዬን እኔም
አቆምኩ፡፡ ስገባ ብቻዋን ተቀምጣ ባገኛት እንኳን ሰላም አልላትም፡፡ እንደውም ከብስጭቴ
ብዛት ቤት ለመቀየር አሰብኩ፡፡ ግን ለእማማ አመለ ምን ሰበብ እንደማቀርብ ጨነቀኝ፡፡ ከእኔ
ከሚያገኟት የኪራይ ብር በላይ ለእኔ ያላቸው ቤተሰባዊ ፍቅር ቦታ አለው፤ ለእርሳቸው::ደግሞም ብቸኛ መተዳደሪያቸው ከእኔ የሚያገኟት የኪራይ ብር ነበረች፡፡ ምን ሆንኩ ብዬ ቤት ልውጣአ ? እች ጉልት ስወጣ ስገባ እንደ ግኡዝ ነገር ተጎልታ ማየቴ ያበሳጨኛል፡፡ ማታ ማታ ቡና ሲጠሩኝ በህመሜ አሳብቤ ልቀር ብሞክርም አልተሳካም፡፡
“ቡና ባትጠጣ እንኳን ና እና ተጫወት፤ በሽታውም ለብቻ ሲሆኑ ነው የሚጠናው” አሉኝ
እማማ አመለ፡፡ ጨዋታው እንደወትሮው አልጥምህ አለኝ፤ እጣኑ ከነከነኝ፤ ከእጣኑ ወዲያ
አቀርቅራ የምትቀመጠው ፋና ሰለቸችኝ፡፡ እወዳታለሁ፤ ግን ግኡዝ ናት በቃ ! ወይስ ከራሷ
ውበት ጋር በፍቅር ወድቃ ዓለምን ረስታለች ? ምናይነት ድንዛዜ ነው ይሄ ?
!
ፍቅርተ ጋር ቅርርባችን ተጠናክሮ ነበር፡፡ ማታ ማታ ቡናው እስከሚፈላ ደብተሯን ይዛ
ወደ ክፍሌ ትመጣለች፡፡ ግን አታጠናም፤ ቤታቸው ውስጥ ቴፕ ስለሌለ ሁልጊዜ የደብተሯ
ቦርሳ ውስጥ የምታኖረውን የአስቴርን ካሴት ይዛ ትመጣና በእኔ ቴፕ ታዳምጣለች፡፡ ግጥሙን
ሸምድዳዋለች፤ ጀምሮ እስኪጨርስ በቃሏ ትወጣዋለች፡፡ ሙዚቃውን እንደ ሙዚቃ ሳይሆን
እንደ መርዶ ነበር ፊቷን አጨፍግጋ የምታዳምጠው፡፡ አንድ ቀን ሙዚቃውን እያዳመጠች
እንባዋ በጉንጫ ላይ ኮለል ብሎ ወረደ፤
“ምን ሆንሽ ፍቅርተ” አልኳት ደንግጬ፤
“ምንም” ብላ ተነስታ ከክፍሌ ወጣች፡፡ከዛን ቀን ጀምሮ ፍቅርተ የወትሮዋ አልነበረችም፤ የሌላትን
አመል መነጫነጭ ጀመረች፡፡ ከመሬት ተነስታ ታለቅሳለች፤ በትንሽ ነገር ይከፋታል፡፡ ከወራት
ልመና በኋላ ጭንቋን ተነፈሰችው፤ ፍቅርተ ፍቅር ይዟት ነበር፡፡ ፍቅር እንደያዛት ስትነግረኝ
“እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፣ የነገስታት ንጉስ፣ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ ኃያል! እባክህ ይህች ልጅ
ፍቅር የያዛት ከእኔ እንዳይሆን እርዳኝ” ብዬ ፀለይኩ፡፡
“ከስምንተኛ ክፍል ጀምሮ አብረን አንድ ክፍል ነው የተማርነው፤ ቶማስ ይባላል” ስትለኝ ሃሌሉያ!”
ብዬ ልጮኽ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ ኡፍፍፍፍፍፍ ! አሁን እዳው ገብስ ነው ! ተረጋግቼ አዳምጣት
ጀመር፡፡ የከፍሎቿ ልጆች ተሰባስበው የተነሱትን አንድ ፎቶ እየሰጠችኝ ልጁን ጠቆመችኝ፤
ሲበዛ ቆንጆ ልጅ ነበር፡፡ ከግራና ቀኙ ሁለት ቆነጃጅት እንደ መዥገር ተጣብቀውበታል፡፡
“አንቺ የታለሽ ታዲያ!” አልኳት፤
“እኔ ፎቶ መነሳት አልወድም” አለችኝ ትክዝ ብላ፡፡ ለምን ብዬ አልጠየቅኳትም፡፡
“ከወደድሽው ስንት ጊዜ ሆነሽ?” አልኳት ፎቶውን እያየሁ፤
“እኔንጃ ግን ቆይቷል ፤ ሶስት አመት”
“እና ሦሰት ዓመት ሙሉ ስታፈቅሪው እርሱ ምን አለ ?”
“አያውቅም፡፡”
“ተነጋግራችሁ አታውቁም”
“አንድ ቀን አናግሮኛል…”
“እና ምን አለሽ?” አልኳት በጉጉት፡፡
“እርሳስ አጥቼ ስጠይቅ ሰጠኝ…ስመልስለት 'ውሰጂው! አለኝ” አለችና እዛኛው ክፍል ሄዳ አንድ
ቢጫ እርሳስ ይዛ ተመለሰች፡፡ እንደ ትልቅ ቅርስ በፍቅር እርሳሱን እየተመለከተች…፣ “አየኸው
የእሱ ነው” አለችኝ፡፡ ፊቷ ላይ የነበረው ደስታ… ናፍቆት…ፍቅር ያሳዝን ነበር፡፡ ትቀጥላለች
ብዬ ጠበቅኳት፡፡ የተነጋገሩት ግን እችኑ ነበር፡፡ አንድ ቃል “ውሰጅው” አላት፤ በቃ፡፡ ይሄ ቃል ለፍቅርተ “ንግግር” ነበር፡፡
“ለምን አታናግሪውም ታዲያ ? በቀጥታ መናገር እንኳን ባትችይ በሆነ መንገድ እንደወደድሽው
አሳውቂው፡፡ እሱም ሊወድሽ ይችላል” አልኳት እንደው ለማፅናናት እንጂ ያልኩትን ለራሴም አላመንኩበትም፡፡ ይሄ ልጅ ፍቅርተን ቢወዳት በሺ ዓመት አንድ ጊዜ የሚከሰት አጋጣሚ
አድርጌ ላየው ሁሉ እችላለሁ፡፡
በድንጋጤ አፍጥጣ እያየችኝ፣ “ትቀልዳለህ ?” አለችኝና አፏን በሁለት እጆቿ አፍና እንደዘገነነው
ሰው ሰውነቷ ተንዘረዘረ፤
“በጣም የሃብታም ልጅ ነው፤ በዛ ላይ ክላሳችን ውስጥ ካሉ ሰላሳ ሴቶች ግማሹ በሱ ፍቅር ያበዱ
ናቸው፡፡ በእረፍት ሰዓት ጎታቹ ብዙ ነው፤ በዚያ ላይ ጎበዝ ተማሪ፤ ኤጭ” ብላ በምሬት ፊቷ
አጨፈገገች፡፡ ዝም ብዬ አየኋት፤ ፍቅርተ ይበልጥ በቀረቧት ቁጥር ይበልጥ መልከጥፉ የምትሆን
ሚስኪን ነበረች፡፡ በቦዙ አይኖቿ ባዶውን እየተመለከተች ምሬቷን አምበለበለችው፡፡ የሆነ ነገር
ያስፈልግሃል፡ ለመፈቀር አንድ የሆነ ነገር ያስፈልግሃል፣ መልክ ወይም ሃብት…ብቻ የሆነ ነገር
እኔ ደግሞ ምንም የለኝም፤ መልክ የለኝ፣ ሃብት የለኝ፣ በትምህርት እንኳን እንዳላካክሰው እንደ ትምህርት የሚያስጠላኝ ነገር የለም እማማ እንዳይከፋት ነው የምማረው ቸኮኛል ከቤት
ባልወጣ ደስታዬ ነው፡ ማንንም ባላይ፡ ማንም ሳያየኝ ደስታዬ ነው አለችና እንባዋ ይፈስ ጀመር
“ፍቅርተ ለፍቅር ሃብት ፣ መልከ ምናምን ሲያስፈልግ ኖሮ እኮ አታፈቅሪም ነበር” አልኳት፡፡
ከአፌ ነጥቃ በቁጣ መናገር ጀመረች፡፡ንግግሯ በምሬት የተሞላ ነበር፡፡ “እንኳን ለፍቅር ለተራ
ሰላምታም ሀብት ያስፈልጋል ፡፡መልክ ያስፈልጋል ፡፡ አንተ አስቀያሚ ወጣት ሆነህ ታውቃለህ ? አስቀያሚ ሴት ሆነህስ ታውቃለህ ? ህመሙ አይገባህም፡፡አብርሽ መገፋቱ ስሜት አይሰጥህም….እየውልህ እንኳን አሁን ሕፃን ሆነን እኔና ፋና መንገድ ላይ ስንሄድ ያገኘን ሁሉ ፋናን አገላብጦ ጉንጯን ይስምና እኔን…” መጨረስ አልቻለችም እንባዋ ቀደማት፡፡
“አስራ ስምንት ዓመት አልፎኛል፡፡ እስካሁን አንድ ወንድ እንኳን ጠይቆኝ አያውቅም፡፡አንዳንዴ እንዴት እንደተፋቀሩ ይቅርና ያፈቀሩት ጋር እንዴት እንደተጣሉ ሴቶች ሲያወሩ እቀናለሁ..ከፍቅረኛ ጋር መጣላት በራሱ ያስቀናል፤ ይናፍቅሃል፤ ሰው ሆነህ በፍቅር መጋጨትህ ለራሱ ከሰው እኩል ያደርግሃል፡፡ የሚጣላህም የሚወድህም በሌለበት ዓለም መኖር ካለመኖር እኩል ነው” ፍቅርተ ባንዴ ተቀየረችብኝ፤ አስፈሪ ሆነችብኝ፡፡ ንፍጧ በአፍንጫዋ ተዝረከረከ፤
እንባዋ ፊቷን አጨቀየው፤ አስቀያሚነቷ ሙሉ ሆነ፡፡ ስታሳዝን!
“አስራ ስምንት ዓመት እኮ ትንሽ እድሜ ነው…ገና ነሽ ወደፊት የሚያፈቅርሽ የራስሽ ሰው
ይመጣል” አልኳት ልክ የሚያፈቅራትን ሰው የቀጠርኩት ይመስል በእርግጠኝነት፡፡ ግን ውስጤ መቼም ቢሆን ፍቅርተን የሚያፈቅር ሰው በምድር ላይ የሚፈጠር አይመስለውም፤ እናገራለሁ፤ግን የምለውን እኔም አላምንበትም፡፡
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
....ፋና ጋር መቀራረብ በጣም ከባድ ነበረ፡፡ አንዳንዴ ባህሪዋ ያበሳጨኛል፡፡ “ምናይነት የደነዘዘች ልጅ ናት” እልና ለራሴ ቁጣ ቁጣ ይለኛል፡፡ ለምን እንደ ፍቅርተ አታናግረኝም ? ሌላው ቢቀር አንድ ዓመት ሙሉ እዚህ ቤት ስኖር ቤቴን እንኳን ተሳስታ ረግጣው አታውቅም፡፡ ፍቅርተ እኮ
እናት ማለት ናት፡፡ ረፍዶብኝ ፍራሼን ሳላነጣጥፍ ከወጣሁ ፍራሼን አነጣጥፋ፣ ያዝረከረኩትን
ወረቀት አስተካክላ የሚጠጣ ውሃ ቀድታ አስቀምጣልኝ ነው የማገኘው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
ደግሞ ምግቤንም የምትሰራልኝ ፍቅርተ ናት፡፡ እች ፋና የሚሏት ዝግ ግን…ዝምታዋ ሰልችቶኝ
ነበር፡፡
የሆነ ጊዜ ታዲያ ድንገት ታመምኩ፡፡ ለሳምንት ትምህርት ቤት አልሄድኩም፤ ፍቅርተና እማማ
አመለ ተጨንቀው ሲሯሯጡ ሰነበቱ፡፡ ፋና ዝርም ብላ አታውቅም፡፡ ከዛን ጊዜ በኋላ የፉና ነገር በቃኝ፡፡ “እግዜር ይግደልህ !” ማንን ገደለ? አንድ ቀን ሳትጠይቀኝ በቃ ድኜ ተነሳሁ፡፡
ፋና የምትባል ልጅ በቃ በቃችኝ፡፡ ሳልፍ ሳገድም እወረውርላት የነበረውን ሰላምታዬን እኔም
አቆምኩ፡፡ ስገባ ብቻዋን ተቀምጣ ባገኛት እንኳን ሰላም አልላትም፡፡ እንደውም ከብስጭቴ
ብዛት ቤት ለመቀየር አሰብኩ፡፡ ግን ለእማማ አመለ ምን ሰበብ እንደማቀርብ ጨነቀኝ፡፡ ከእኔ
ከሚያገኟት የኪራይ ብር በላይ ለእኔ ያላቸው ቤተሰባዊ ፍቅር ቦታ አለው፤ ለእርሳቸው::ደግሞም ብቸኛ መተዳደሪያቸው ከእኔ የሚያገኟት የኪራይ ብር ነበረች፡፡ ምን ሆንኩ ብዬ ቤት ልውጣአ ? እች ጉልት ስወጣ ስገባ እንደ ግኡዝ ነገር ተጎልታ ማየቴ ያበሳጨኛል፡፡ ማታ ማታ ቡና ሲጠሩኝ በህመሜ አሳብቤ ልቀር ብሞክርም አልተሳካም፡፡
“ቡና ባትጠጣ እንኳን ና እና ተጫወት፤ በሽታውም ለብቻ ሲሆኑ ነው የሚጠናው” አሉኝ
እማማ አመለ፡፡ ጨዋታው እንደወትሮው አልጥምህ አለኝ፤ እጣኑ ከነከነኝ፤ ከእጣኑ ወዲያ
አቀርቅራ የምትቀመጠው ፋና ሰለቸችኝ፡፡ እወዳታለሁ፤ ግን ግኡዝ ናት በቃ ! ወይስ ከራሷ
ውበት ጋር በፍቅር ወድቃ ዓለምን ረስታለች ? ምናይነት ድንዛዜ ነው ይሄ ?
!
ፍቅርተ ጋር ቅርርባችን ተጠናክሮ ነበር፡፡ ማታ ማታ ቡናው እስከሚፈላ ደብተሯን ይዛ
ወደ ክፍሌ ትመጣለች፡፡ ግን አታጠናም፤ ቤታቸው ውስጥ ቴፕ ስለሌለ ሁልጊዜ የደብተሯ
ቦርሳ ውስጥ የምታኖረውን የአስቴርን ካሴት ይዛ ትመጣና በእኔ ቴፕ ታዳምጣለች፡፡ ግጥሙን
ሸምድዳዋለች፤ ጀምሮ እስኪጨርስ በቃሏ ትወጣዋለች፡፡ ሙዚቃውን እንደ ሙዚቃ ሳይሆን
እንደ መርዶ ነበር ፊቷን አጨፍግጋ የምታዳምጠው፡፡ አንድ ቀን ሙዚቃውን እያዳመጠች
እንባዋ በጉንጫ ላይ ኮለል ብሎ ወረደ፤
“ምን ሆንሽ ፍቅርተ” አልኳት ደንግጬ፤
“ምንም” ብላ ተነስታ ከክፍሌ ወጣች፡፡ከዛን ቀን ጀምሮ ፍቅርተ የወትሮዋ አልነበረችም፤ የሌላትን
አመል መነጫነጭ ጀመረች፡፡ ከመሬት ተነስታ ታለቅሳለች፤ በትንሽ ነገር ይከፋታል፡፡ ከወራት
ልመና በኋላ ጭንቋን ተነፈሰችው፤ ፍቅርተ ፍቅር ይዟት ነበር፡፡ ፍቅር እንደያዛት ስትነግረኝ
“እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፣ የነገስታት ንጉስ፣ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ ኃያል! እባክህ ይህች ልጅ
ፍቅር የያዛት ከእኔ እንዳይሆን እርዳኝ” ብዬ ፀለይኩ፡፡
“ከስምንተኛ ክፍል ጀምሮ አብረን አንድ ክፍል ነው የተማርነው፤ ቶማስ ይባላል” ስትለኝ ሃሌሉያ!”
ብዬ ልጮኽ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ ኡፍፍፍፍፍፍ ! አሁን እዳው ገብስ ነው ! ተረጋግቼ አዳምጣት
ጀመር፡፡ የከፍሎቿ ልጆች ተሰባስበው የተነሱትን አንድ ፎቶ እየሰጠችኝ ልጁን ጠቆመችኝ፤
ሲበዛ ቆንጆ ልጅ ነበር፡፡ ከግራና ቀኙ ሁለት ቆነጃጅት እንደ መዥገር ተጣብቀውበታል፡፡
“አንቺ የታለሽ ታዲያ!” አልኳት፤
“እኔ ፎቶ መነሳት አልወድም” አለችኝ ትክዝ ብላ፡፡ ለምን ብዬ አልጠየቅኳትም፡፡
“ከወደድሽው ስንት ጊዜ ሆነሽ?” አልኳት ፎቶውን እያየሁ፤
“እኔንጃ ግን ቆይቷል ፤ ሶስት አመት”
“እና ሦሰት ዓመት ሙሉ ስታፈቅሪው እርሱ ምን አለ ?”
“አያውቅም፡፡”
“ተነጋግራችሁ አታውቁም”
“አንድ ቀን አናግሮኛል…”
“እና ምን አለሽ?” አልኳት በጉጉት፡፡
“እርሳስ አጥቼ ስጠይቅ ሰጠኝ…ስመልስለት 'ውሰጂው! አለኝ” አለችና እዛኛው ክፍል ሄዳ አንድ
ቢጫ እርሳስ ይዛ ተመለሰች፡፡ እንደ ትልቅ ቅርስ በፍቅር እርሳሱን እየተመለከተች…፣ “አየኸው
የእሱ ነው” አለችኝ፡፡ ፊቷ ላይ የነበረው ደስታ… ናፍቆት…ፍቅር ያሳዝን ነበር፡፡ ትቀጥላለች
ብዬ ጠበቅኳት፡፡ የተነጋገሩት ግን እችኑ ነበር፡፡ አንድ ቃል “ውሰጅው” አላት፤ በቃ፡፡ ይሄ ቃል ለፍቅርተ “ንግግር” ነበር፡፡
“ለምን አታናግሪውም ታዲያ ? በቀጥታ መናገር እንኳን ባትችይ በሆነ መንገድ እንደወደድሽው
አሳውቂው፡፡ እሱም ሊወድሽ ይችላል” አልኳት እንደው ለማፅናናት እንጂ ያልኩትን ለራሴም አላመንኩበትም፡፡ ይሄ ልጅ ፍቅርተን ቢወዳት በሺ ዓመት አንድ ጊዜ የሚከሰት አጋጣሚ
አድርጌ ላየው ሁሉ እችላለሁ፡፡
በድንጋጤ አፍጥጣ እያየችኝ፣ “ትቀልዳለህ ?” አለችኝና አፏን በሁለት እጆቿ አፍና እንደዘገነነው
ሰው ሰውነቷ ተንዘረዘረ፤
“በጣም የሃብታም ልጅ ነው፤ በዛ ላይ ክላሳችን ውስጥ ካሉ ሰላሳ ሴቶች ግማሹ በሱ ፍቅር ያበዱ
ናቸው፡፡ በእረፍት ሰዓት ጎታቹ ብዙ ነው፤ በዚያ ላይ ጎበዝ ተማሪ፤ ኤጭ” ብላ በምሬት ፊቷ
አጨፈገገች፡፡ ዝም ብዬ አየኋት፤ ፍቅርተ ይበልጥ በቀረቧት ቁጥር ይበልጥ መልከጥፉ የምትሆን
ሚስኪን ነበረች፡፡ በቦዙ አይኖቿ ባዶውን እየተመለከተች ምሬቷን አምበለበለችው፡፡ የሆነ ነገር
ያስፈልግሃል፡ ለመፈቀር አንድ የሆነ ነገር ያስፈልግሃል፣ መልክ ወይም ሃብት…ብቻ የሆነ ነገር
እኔ ደግሞ ምንም የለኝም፤ መልክ የለኝ፣ ሃብት የለኝ፣ በትምህርት እንኳን እንዳላካክሰው እንደ ትምህርት የሚያስጠላኝ ነገር የለም እማማ እንዳይከፋት ነው የምማረው ቸኮኛል ከቤት
ባልወጣ ደስታዬ ነው፡ ማንንም ባላይ፡ ማንም ሳያየኝ ደስታዬ ነው አለችና እንባዋ ይፈስ ጀመር
“ፍቅርተ ለፍቅር ሃብት ፣ መልከ ምናምን ሲያስፈልግ ኖሮ እኮ አታፈቅሪም ነበር” አልኳት፡፡
ከአፌ ነጥቃ በቁጣ መናገር ጀመረች፡፡ንግግሯ በምሬት የተሞላ ነበር፡፡ “እንኳን ለፍቅር ለተራ
ሰላምታም ሀብት ያስፈልጋል ፡፡መልክ ያስፈልጋል ፡፡ አንተ አስቀያሚ ወጣት ሆነህ ታውቃለህ ? አስቀያሚ ሴት ሆነህስ ታውቃለህ ? ህመሙ አይገባህም፡፡አብርሽ መገፋቱ ስሜት አይሰጥህም….እየውልህ እንኳን አሁን ሕፃን ሆነን እኔና ፋና መንገድ ላይ ስንሄድ ያገኘን ሁሉ ፋናን አገላብጦ ጉንጯን ይስምና እኔን…” መጨረስ አልቻለችም እንባዋ ቀደማት፡፡
“አስራ ስምንት ዓመት አልፎኛል፡፡ እስካሁን አንድ ወንድ እንኳን ጠይቆኝ አያውቅም፡፡አንዳንዴ እንዴት እንደተፋቀሩ ይቅርና ያፈቀሩት ጋር እንዴት እንደተጣሉ ሴቶች ሲያወሩ እቀናለሁ..ከፍቅረኛ ጋር መጣላት በራሱ ያስቀናል፤ ይናፍቅሃል፤ ሰው ሆነህ በፍቅር መጋጨትህ ለራሱ ከሰው እኩል ያደርግሃል፡፡ የሚጣላህም የሚወድህም በሌለበት ዓለም መኖር ካለመኖር እኩል ነው” ፍቅርተ ባንዴ ተቀየረችብኝ፤ አስፈሪ ሆነችብኝ፡፡ ንፍጧ በአፍንጫዋ ተዝረከረከ፤
እንባዋ ፊቷን አጨቀየው፤ አስቀያሚነቷ ሙሉ ሆነ፡፡ ስታሳዝን!
“አስራ ስምንት ዓመት እኮ ትንሽ እድሜ ነው…ገና ነሽ ወደፊት የሚያፈቅርሽ የራስሽ ሰው
ይመጣል” አልኳት ልክ የሚያፈቅራትን ሰው የቀጠርኩት ይመስል በእርግጠኝነት፡፡ ግን ውስጤ መቼም ቢሆን ፍቅርተን የሚያፈቅር ሰው በምድር ላይ የሚፈጠር አይመስለውም፤ እናገራለሁ፤ግን የምለውን እኔም አላምንበትም፡፡
👍28
#ሚስቴን_አከሸፏት
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከዚህ ሁሉ የሚከፋው ግን ወሬዋ ..! ወይኔ ወሬዋ ! ሰው እንዴት በቅሌቱ አንቱ ለመባል ይጥራል በእግዚአብሔር። እኔ ጥሎብኝ ዋው! እሷ እኮ ተጫዋች ምናምን.. ለመባል ብሎ የሚቀባጥር ሰው ያስመርረኛል።
“ዋው እንትናዬ ! እንዴት አባቱ የሚጥም ተጨዋች መሰለሽ ...! ሙድ ያለው ጨዋታው ብትይ፣
የሚወስደኝ ቦታ ብትይ፣ በዛ ላይ አልጋ ላይ ሂሂሂሂሂሂሂሂሂ” አፏን እስከመጨረሻው ከፍታ
ታሽካካለት…። ይህቺን ሴትዮ ሳስባት ከእናትና ከአባት ሳይሆን እንደሙጃ ሕይወት ይሉት ዝናብ
ዘንቦባት ድንገት ሜዳ ላይ ቱግ ብላ የበቀለች አረም ነው የምትመስለኝ የሰው አራሙቻ !
ከፌቨን ጋር የተዋወቁት በአንድ የግል ድርጅት ሲሠሩ ነበር።
“ኦ ማሜ ማለትኮ እናት ማለት
ትላታለች ሚስቴ ይህቺን ሴት ስታደንቃት .. !ይታያችሁ እናት !ለነገሩ እናት” ናት።
"ፌቪዬ የኔ ማር…! ይሄን ሽንኩርት የሚባል ነገር እየከተፍሽ ቆንጅዬ እጅሽን ልታበላሽው ነው…።”
ትላታለች። ፌቨን ልታስተናግዳት ጉድ ጉድ ስትል እኮ ነው፤ ምክሯ ሁሉ ግራ ነው የሚያጋባው።
አንዳንዴ ደግሞ እኔና ፌቨንን እየተመለከተች፣ “እንዴ እናንተ ሁለታችሁ ብቻ ናችሁ፤ የምን እንጀራ መጠፍጠፍ ነው .. የቀን ሠራተኛ ቅጠሪና ወጥ ምናምን ሠርታ ፍሪጅ ውስጥ ማስቀመጥ፣ እንጀራ ከሱቅ ገዛ አድርገሽ መጠቀም፤ እንደው አበሻ ጓዳ ገብቶ ፍዳውን ካልበላ ካላቦካ፣ ካልተጨማለቀ እሳት ላይ ካልተጠበሰ የበላ አይመስለውም፤ ... አይደል እንዴ አብርሽ? ሂሂሂሂሂሂ …ይህቺን የመሰለች ማር የሆነች ልጅማ ሽንኩርት አታስከትፋት…።”
ፌቨን ምሳ ሠርታ ይህቺ መካሪ በደንብ እያጣጣመች ከበላች በኋላ መልሳ እንዲህ ትላለች፣
“ላለለት ሰውማ ማን እንደ ቤት ምግብ እናቴ ትሙት (እናቴ ትሙት ብሎ መሐላ አይቀፍም?) ... ውይ
እንዴት ርቦኝ ነበር። ጥሞኝ በላሁ። ፌቪዬ ከአልጫዋ ትንሽ ጨምሪልኝ ትላለች። እውነቱን ለመናገር
እንደዚህ ስትል ታሳዝነኛለች። ሴት ራበኝ ስትል አልወድም። በዛላይ አንዲት ሴት ያውም ኢትዮጵያዊት
ሴት የፈለገ የሞራል ውድቀት ውስጥ ብትገባ የዚህ ዓይነት አኗኗር የምትመርጥ አይመስለኝም። አንድ
ከሕይወቷ መጽሐፍ የተገነጠለ የኑሮ ገጽ ይኖራል፣ ወይም አንዱ ደደብ የሕያውነት አንቀጿን በክፋት
ሰርዞታል። ወዶ አይደለም ወሬዋ የሚምታታው..
በጣም ቆንጆ ናት። ያውም ውብ የሚባል ዓይነት። ላግባ ብትል እግሯ ላይ ወድቆ የሚያገባት ሺ
ከሚሊየን ነው (በዚህ ዕድሜዋ እንኳን ላግባ ብትል የሚሻማባት ጎረምሳ ብዙ ይመስለኛል…) ግን
ከርታታ ናት። በቃ እዛ ስታድር፣ እዚህ ስትውል፣ ሽሽቷን ልታዘምነው አንዴ ትልልቅ ሆቴሎች፣ ሌላ ጊዜ ሌላ የመዝናኛ ቦታዎች ብትንከራተትም ዓይኗ ላይ እንደሩቅ አገር እሳት ቢል ቢል ሲል የሚታየው አምሮት … እፎይ ማያ ጎጆ መናፈቋ ነው!!
እናም ፌቨንን ፊቴ እንዲህ አለቻት፣ ፌቪ ማር…!ይሄ እንቁላል ቅርፅ ያለው ፊትሽ በዚህ ፀጉርሽ
ባይሸፈን ኖሮ መልክሽ የሚያሳብድ ይሆን ነበር። ብዙ ሳይሆን ትንሽ አጠር …፤ ምን አሁን እኮ ፀጉር ጀርባ ላይ ለቅቆ አንበሳ መምሰል ትንሽ ጊዜው አልፎበታል። ዳሩ አንቺ ወጣ ብለሽ አታይ፤ እዚህ ባልሽ ጋር ታፍነሽ እየዋልሽ ሂሂሂሂሂሂ። ቀልድ አልብሳ መርዟን ረጨችው።
ማታ እንደተኛን ፌቨን ድንገት ከጎኔ ቀጥ ብላ ደረቴ ላይ አገጯን አስደገፈች። ጥቁር ፀጉሯ ፊቴ ላይ
ተነሰነሰ።ዓይኖቼን ጨፍኜ የፀጉሯን ዝናብ ተጠመቅኩት በደስታ … እንደ ሩፋኤል ፀበል።
“አብርሽዬ…”
“እ!”
“ዓይንህን ግለጣ” አለች፤ ገለጥኩ። ከጥቁር ደመና ውስጥ ብቅ ያለች ጠይም ፀሐይ ከበላዬ።
“ማሜ ያለችው ነገር ግን አልገረመህም፤ እንዴት እስከዛሬ አላሰብኩትም…?”
“ምኑን?” አሁን እኔም ነቃ አልኩ።
“ፀጉሬን ባሳጥረው እንደሚያምርብኝ ፀጉር የምትሠራኝ ልጅም ደጋግማ ነግራኛለች” ፊቷ ላይ ያለው
ስሜት የመጠየቅ ሳይሆን ፀጉሯን የምትቆርጥበት መቀስ እንዳቀብላት የመጠየቅ ዓይነት ያበቃለት መርዶ ነበር። ሁሉም ነገር ቅድሚያ የሚቆረጠውም የሚቀጠለውም ልብ ላይ ነው።
“ፀጉርሽን እንድትቆረጭ አልፈልግም። እንኳን መቆረጥ ፀጉርሽን ስታበጥሪ ማበጠሪያው ላይየሚቀሩት የፀጉር ዘለላዎችሽ ያሳዝኑኛል። እና ለእኔ የምታምሪኝ እንደዚህ ስትሆኝ ነው። ፀጉርሽን ከዓይኖችሽ፣ ከአፍንጫሽ እና ከእነዚህ ውብ እጅና እግሮችሽ እኩል እወደዋለሁ፤ እንደ አንድ የሰውነትሽ ክፍል ነው
የማየው” አልኳት ጣቶቼን ፀጉሯ ውስጥ እያርመሰመስኩ።
“እንደዚህ አንበሳ ስመስል ነው የምትወደኝ?” ብላ በማሾፍ ከተናገረች በኋላ ፀጉሯን በጣቷ
መነጨረችውና ከንፈሬን ስማኝ ደረቴ ላይ ልጥፍ ብላ ተኛች። (ይሄ መሳም ቃሌን መስማት ይሁን
ወይስ ስሞ መሸጥ ዓይነት ይሁዳዊ መሳም አልገባኝም)። አተኛኘቷን ሳየው የልብ ምቴን የምታደምጥ ነበር የምትመስለው እንቅልፍ ወሰዳት።ስንተኛ ፀጉሯን ስለማታስይዘው እንዲሁ ነው የምትተኛው።በእንቅልፍ ልቧ በተንቀሳቀሰች ቁጥር የፀጉር መዓበል ትራሱ ላይ ሲነሳ ከትራሱ ላይ እየተንሸራተተ ፍራሹ ላይ ሲርመሰመስ ነፍሴ ሐሴት ታደርጋለች።
ፀጉር እኮ መንፈስ ነው። በተለይ የሴት ልጅ ፀጉር። የቅዱሳን ሥዕልላይ ከራሳቸው በላይ እንደሚታየው የብርሃን አምድ …. የሴት ልጅ ፀጉርም ባፈቀራት ወንድ ብቻ የመንፈስ ዓይን የሚታይ የውበት አምድ
ነው ! የሴት ልጅ ሰውነት በማይታይ የክብር ብርሃን የተከበበ ሕያው ቅድስና ነው። ትልቁ ችግር የብዙ ሴቶች ፍላጎት ለብዙኃኑ ቆንጆ ሆኖ የመታየት መሆኑ ነው። ብዙኃኑ አድናቂ ነው። ብዙኃኑ ጤዛ የሆነ አብሮነቱ ከዓይን ሲርቁ አብሮ ይከስማል። ብዙኃኑን የኔ ከምንለው ሰው ጋር በአንድ ሚዛን ልናስቀምጠው አይገባም። ለብዙኃኑ ብዙ ሆኖ መገኘት በመፈለጋቸው አንዱንም ሳይዙት ምንም ሆነው እንዲቀሩ ያደረጋቸው ብዙ ናቸው።
ፌቨን ተኛች። ስትተኛ የተመጠነ አተነፋፈስና ሰላም ያለው እረፍት ፊቷ ላይ ይረብባታል። የፌቨን
እንቅልፍ ሰላም ባለው ሰፊ ባሕር ላይ ያለ ምንም እንቅስቃሴ በጀልባ እንደመንሳፈፍ ይመስለኛል።ተኝታ ሳያት ታሳሳኛለች። እና ቀስቅሳት ቀስቅሳት ይለኛል። ለብቻዬ ትታኝ ወደሆነ ሰላም ወዳለው ዓለም የሄደች ይመስለኛል፤ እኔ ግን በሐሳብ ነጎድኩ። ወደኋላ … ፌቨንን ዓይቻት ፍቅር የጀማመረኝ
ሰሞን ከሩቅ ስመለከታት የሚገርመኝ ፀጉሯ ነበር። ድብን ያለ ጥቁርና ጠንካራ ፀጉር። ከርዝመቱ ብዛቱ። ከተዋወቅንና ከተቀራረብን በኋላ ደግሞ ፀጉሯ መሐል ጣቶቼ ጠፉ ማለት ዘበት ነው። አንገቷን ወደግራ ዘንበል ስታደርግ ፀጉሯ ወደ ግራ ይናድና በግራ ትከሻዋ አልፎ እየተርመሰመሰ የግራ ጡቷን
ይሸፍነዋል።
ፀጉር ቤት ቆይታ ስትመለስ የሆነ የተቃጠለ ፀጉር ሽታ አፍንጫዬን ያውደዋል። ያንን ሽታ እወደዋለሁ።
እንደውም በሴቶች ፀጉር ቤት ሳልፍ ይሄ የተቃጠለ የፀጉር ሽታ ሲሸተኝ ፀጉር ቤቱ ውስጥ ፌቨን ያለች ይመስለኛል። ፀጉር መተኮስ ማለት እኮ ለውበት አምላክ የሚቃጠል የፀጉር መስዋዕት እንደማቅረብ ነው። (የመረረ የፋሽን ጥላቻ ኖሮብኝ ሳይሆን ውበት ዋጋ እንደሚያስከፍል ለመግለፅ)
ጠዋት ከእንቅልፌ የቀሰቀሰችኝ ፌቨን ናት ቁርስ ሰርታ ሁልጊዜም እንዲሁ ነች። ቁርስ እየበላን
ድንገት ፍርፍሩ ውስጥ አልያም እንቁላል ጥብሱ ውስጥ የፀጉር ዘለላ ማግኘቴ አይቀርም። ዛሬም
ይሄው አንድ ቢመዘዝ የማያልቅ የፌቪን ፀጉር አገኘሁ።
ተሳሳቅን።
የግራ እጄን ጣቶች ወደ ዓይኗ አስጠግታ እየተመለከተች እንዲህ አለች፣ “ይሄ ሽንኩርት እጄን
"አሻከረው”።
ዝም አልኩ።
ዝም ተባባልን።
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከዚህ ሁሉ የሚከፋው ግን ወሬዋ ..! ወይኔ ወሬዋ ! ሰው እንዴት በቅሌቱ አንቱ ለመባል ይጥራል በእግዚአብሔር። እኔ ጥሎብኝ ዋው! እሷ እኮ ተጫዋች ምናምን.. ለመባል ብሎ የሚቀባጥር ሰው ያስመርረኛል።
“ዋው እንትናዬ ! እንዴት አባቱ የሚጥም ተጨዋች መሰለሽ ...! ሙድ ያለው ጨዋታው ብትይ፣
የሚወስደኝ ቦታ ብትይ፣ በዛ ላይ አልጋ ላይ ሂሂሂሂሂሂሂሂሂ” አፏን እስከመጨረሻው ከፍታ
ታሽካካለት…። ይህቺን ሴትዮ ሳስባት ከእናትና ከአባት ሳይሆን እንደሙጃ ሕይወት ይሉት ዝናብ
ዘንቦባት ድንገት ሜዳ ላይ ቱግ ብላ የበቀለች አረም ነው የምትመስለኝ የሰው አራሙቻ !
ከፌቨን ጋር የተዋወቁት በአንድ የግል ድርጅት ሲሠሩ ነበር።
“ኦ ማሜ ማለትኮ እናት ማለት
ትላታለች ሚስቴ ይህቺን ሴት ስታደንቃት .. !ይታያችሁ እናት !ለነገሩ እናት” ናት።
"ፌቪዬ የኔ ማር…! ይሄን ሽንኩርት የሚባል ነገር እየከተፍሽ ቆንጅዬ እጅሽን ልታበላሽው ነው…።”
ትላታለች። ፌቨን ልታስተናግዳት ጉድ ጉድ ስትል እኮ ነው፤ ምክሯ ሁሉ ግራ ነው የሚያጋባው።
አንዳንዴ ደግሞ እኔና ፌቨንን እየተመለከተች፣ “እንዴ እናንተ ሁለታችሁ ብቻ ናችሁ፤ የምን እንጀራ መጠፍጠፍ ነው .. የቀን ሠራተኛ ቅጠሪና ወጥ ምናምን ሠርታ ፍሪጅ ውስጥ ማስቀመጥ፣ እንጀራ ከሱቅ ገዛ አድርገሽ መጠቀም፤ እንደው አበሻ ጓዳ ገብቶ ፍዳውን ካልበላ ካላቦካ፣ ካልተጨማለቀ እሳት ላይ ካልተጠበሰ የበላ አይመስለውም፤ ... አይደል እንዴ አብርሽ? ሂሂሂሂሂሂ …ይህቺን የመሰለች ማር የሆነች ልጅማ ሽንኩርት አታስከትፋት…።”
ፌቨን ምሳ ሠርታ ይህቺ መካሪ በደንብ እያጣጣመች ከበላች በኋላ መልሳ እንዲህ ትላለች፣
“ላለለት ሰውማ ማን እንደ ቤት ምግብ እናቴ ትሙት (እናቴ ትሙት ብሎ መሐላ አይቀፍም?) ... ውይ
እንዴት ርቦኝ ነበር። ጥሞኝ በላሁ። ፌቪዬ ከአልጫዋ ትንሽ ጨምሪልኝ ትላለች። እውነቱን ለመናገር
እንደዚህ ስትል ታሳዝነኛለች። ሴት ራበኝ ስትል አልወድም። በዛላይ አንዲት ሴት ያውም ኢትዮጵያዊት
ሴት የፈለገ የሞራል ውድቀት ውስጥ ብትገባ የዚህ ዓይነት አኗኗር የምትመርጥ አይመስለኝም። አንድ
ከሕይወቷ መጽሐፍ የተገነጠለ የኑሮ ገጽ ይኖራል፣ ወይም አንዱ ደደብ የሕያውነት አንቀጿን በክፋት
ሰርዞታል። ወዶ አይደለም ወሬዋ የሚምታታው..
በጣም ቆንጆ ናት። ያውም ውብ የሚባል ዓይነት። ላግባ ብትል እግሯ ላይ ወድቆ የሚያገባት ሺ
ከሚሊየን ነው (በዚህ ዕድሜዋ እንኳን ላግባ ብትል የሚሻማባት ጎረምሳ ብዙ ይመስለኛል…) ግን
ከርታታ ናት። በቃ እዛ ስታድር፣ እዚህ ስትውል፣ ሽሽቷን ልታዘምነው አንዴ ትልልቅ ሆቴሎች፣ ሌላ ጊዜ ሌላ የመዝናኛ ቦታዎች ብትንከራተትም ዓይኗ ላይ እንደሩቅ አገር እሳት ቢል ቢል ሲል የሚታየው አምሮት … እፎይ ማያ ጎጆ መናፈቋ ነው!!
እናም ፌቨንን ፊቴ እንዲህ አለቻት፣ ፌቪ ማር…!ይሄ እንቁላል ቅርፅ ያለው ፊትሽ በዚህ ፀጉርሽ
ባይሸፈን ኖሮ መልክሽ የሚያሳብድ ይሆን ነበር። ብዙ ሳይሆን ትንሽ አጠር …፤ ምን አሁን እኮ ፀጉር ጀርባ ላይ ለቅቆ አንበሳ መምሰል ትንሽ ጊዜው አልፎበታል። ዳሩ አንቺ ወጣ ብለሽ አታይ፤ እዚህ ባልሽ ጋር ታፍነሽ እየዋልሽ ሂሂሂሂሂሂ። ቀልድ አልብሳ መርዟን ረጨችው።
ማታ እንደተኛን ፌቨን ድንገት ከጎኔ ቀጥ ብላ ደረቴ ላይ አገጯን አስደገፈች። ጥቁር ፀጉሯ ፊቴ ላይ
ተነሰነሰ።ዓይኖቼን ጨፍኜ የፀጉሯን ዝናብ ተጠመቅኩት በደስታ … እንደ ሩፋኤል ፀበል።
“አብርሽዬ…”
“እ!”
“ዓይንህን ግለጣ” አለች፤ ገለጥኩ። ከጥቁር ደመና ውስጥ ብቅ ያለች ጠይም ፀሐይ ከበላዬ።
“ማሜ ያለችው ነገር ግን አልገረመህም፤ እንዴት እስከዛሬ አላሰብኩትም…?”
“ምኑን?” አሁን እኔም ነቃ አልኩ።
“ፀጉሬን ባሳጥረው እንደሚያምርብኝ ፀጉር የምትሠራኝ ልጅም ደጋግማ ነግራኛለች” ፊቷ ላይ ያለው
ስሜት የመጠየቅ ሳይሆን ፀጉሯን የምትቆርጥበት መቀስ እንዳቀብላት የመጠየቅ ዓይነት ያበቃለት መርዶ ነበር። ሁሉም ነገር ቅድሚያ የሚቆረጠውም የሚቀጠለውም ልብ ላይ ነው።
“ፀጉርሽን እንድትቆረጭ አልፈልግም። እንኳን መቆረጥ ፀጉርሽን ስታበጥሪ ማበጠሪያው ላይየሚቀሩት የፀጉር ዘለላዎችሽ ያሳዝኑኛል። እና ለእኔ የምታምሪኝ እንደዚህ ስትሆኝ ነው። ፀጉርሽን ከዓይኖችሽ፣ ከአፍንጫሽ እና ከእነዚህ ውብ እጅና እግሮችሽ እኩል እወደዋለሁ፤ እንደ አንድ የሰውነትሽ ክፍል ነው
የማየው” አልኳት ጣቶቼን ፀጉሯ ውስጥ እያርመሰመስኩ።
“እንደዚህ አንበሳ ስመስል ነው የምትወደኝ?” ብላ በማሾፍ ከተናገረች በኋላ ፀጉሯን በጣቷ
መነጨረችውና ከንፈሬን ስማኝ ደረቴ ላይ ልጥፍ ብላ ተኛች። (ይሄ መሳም ቃሌን መስማት ይሁን
ወይስ ስሞ መሸጥ ዓይነት ይሁዳዊ መሳም አልገባኝም)። አተኛኘቷን ሳየው የልብ ምቴን የምታደምጥ ነበር የምትመስለው እንቅልፍ ወሰዳት።ስንተኛ ፀጉሯን ስለማታስይዘው እንዲሁ ነው የምትተኛው።በእንቅልፍ ልቧ በተንቀሳቀሰች ቁጥር የፀጉር መዓበል ትራሱ ላይ ሲነሳ ከትራሱ ላይ እየተንሸራተተ ፍራሹ ላይ ሲርመሰመስ ነፍሴ ሐሴት ታደርጋለች።
ፀጉር እኮ መንፈስ ነው። በተለይ የሴት ልጅ ፀጉር። የቅዱሳን ሥዕልላይ ከራሳቸው በላይ እንደሚታየው የብርሃን አምድ …. የሴት ልጅ ፀጉርም ባፈቀራት ወንድ ብቻ የመንፈስ ዓይን የሚታይ የውበት አምድ
ነው ! የሴት ልጅ ሰውነት በማይታይ የክብር ብርሃን የተከበበ ሕያው ቅድስና ነው። ትልቁ ችግር የብዙ ሴቶች ፍላጎት ለብዙኃኑ ቆንጆ ሆኖ የመታየት መሆኑ ነው። ብዙኃኑ አድናቂ ነው። ብዙኃኑ ጤዛ የሆነ አብሮነቱ ከዓይን ሲርቁ አብሮ ይከስማል። ብዙኃኑን የኔ ከምንለው ሰው ጋር በአንድ ሚዛን ልናስቀምጠው አይገባም። ለብዙኃኑ ብዙ ሆኖ መገኘት በመፈለጋቸው አንዱንም ሳይዙት ምንም ሆነው እንዲቀሩ ያደረጋቸው ብዙ ናቸው።
ፌቨን ተኛች። ስትተኛ የተመጠነ አተነፋፈስና ሰላም ያለው እረፍት ፊቷ ላይ ይረብባታል። የፌቨን
እንቅልፍ ሰላም ባለው ሰፊ ባሕር ላይ ያለ ምንም እንቅስቃሴ በጀልባ እንደመንሳፈፍ ይመስለኛል።ተኝታ ሳያት ታሳሳኛለች። እና ቀስቅሳት ቀስቅሳት ይለኛል። ለብቻዬ ትታኝ ወደሆነ ሰላም ወዳለው ዓለም የሄደች ይመስለኛል፤ እኔ ግን በሐሳብ ነጎድኩ። ወደኋላ … ፌቨንን ዓይቻት ፍቅር የጀማመረኝ
ሰሞን ከሩቅ ስመለከታት የሚገርመኝ ፀጉሯ ነበር። ድብን ያለ ጥቁርና ጠንካራ ፀጉር። ከርዝመቱ ብዛቱ። ከተዋወቅንና ከተቀራረብን በኋላ ደግሞ ፀጉሯ መሐል ጣቶቼ ጠፉ ማለት ዘበት ነው። አንገቷን ወደግራ ዘንበል ስታደርግ ፀጉሯ ወደ ግራ ይናድና በግራ ትከሻዋ አልፎ እየተርመሰመሰ የግራ ጡቷን
ይሸፍነዋል።
ፀጉር ቤት ቆይታ ስትመለስ የሆነ የተቃጠለ ፀጉር ሽታ አፍንጫዬን ያውደዋል። ያንን ሽታ እወደዋለሁ።
እንደውም በሴቶች ፀጉር ቤት ሳልፍ ይሄ የተቃጠለ የፀጉር ሽታ ሲሸተኝ ፀጉር ቤቱ ውስጥ ፌቨን ያለች ይመስለኛል። ፀጉር መተኮስ ማለት እኮ ለውበት አምላክ የሚቃጠል የፀጉር መስዋዕት እንደማቅረብ ነው። (የመረረ የፋሽን ጥላቻ ኖሮብኝ ሳይሆን ውበት ዋጋ እንደሚያስከፍል ለመግለፅ)
ጠዋት ከእንቅልፌ የቀሰቀሰችኝ ፌቨን ናት ቁርስ ሰርታ ሁልጊዜም እንዲሁ ነች። ቁርስ እየበላን
ድንገት ፍርፍሩ ውስጥ አልያም እንቁላል ጥብሱ ውስጥ የፀጉር ዘለላ ማግኘቴ አይቀርም። ዛሬም
ይሄው አንድ ቢመዘዝ የማያልቅ የፌቪን ፀጉር አገኘሁ።
ተሳሳቅን።
የግራ እጄን ጣቶች ወደ ዓይኗ አስጠግታ እየተመለከተች እንዲህ አለች፣ “ይሄ ሽንኩርት እጄን
"አሻከረው”።
ዝም አልኩ።
ዝም ተባባልን።
👍37
#ዶክተር_አሸብር
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...አቲዩ ለስድስት ወር ከሰውነት ተራ እስከትወጣ ለባለኪዮስኳ ስትሰራ ከከረመች በኋላ ክረምት ገባ፡፡ ባላኪዮስካ አቲዬን በንስር ዓይን ስትከታተላት ነበር፡፡ ከእያንዳንዱ ቀን ጋር
እየተሽቀጓደመች ነበር፡፡ አንድ ማለዳ የአቲዬን ድሪቶ ልብሶች በፌስታል ቋጥራ ከድፍን ሃምሳ
ብር ጋር ሰጠቻትና፣ “በይ እግዜር ይከትልሽ!” ብላ ከቤቷ አስወጥታ ወረረቻት፡፡ የአቲዬ ሆድ ገፍቶ ነበር፡፡ የቀለመወርቅ ፅንስ ከውስጥ፣ የመንደሩ ሰው ከውጭ እየገፋ ሰው በሞላው አገር
እናቴን ምድረ በዳ ላይ አቆሟት፡፡
አቲዪ ስትፈጭ እና ስታነፍስ የዋለችው የምስር ክክ ብናኝ ፊቷና ፀጉሯ ላይ ተነስንሶ ነበር፡፡ ከስድስት ወር በፊት የነበረችው ልጅ እግር ቆንጆ ልጃገረድ ናት ቢባል ቀለሙ ራሱ አያምንም፡፡ መንገድ ዳር ቆመች፡፡ የክረምት ዝናብ ያካፋል፡፡ አንድ የመኪና ዕቃ መለዋወጫ ሱቅ በር ላይ ፍዝዝ ብላ ቆመች::ምንም እያየች ምንም ሰው፣ ምንም መኪና ምንም ቤት፡፡ ህይወት ዝም የምትልበት፣ አዕምሮ ዝም
የሚልበት፣ የሰው ልጅ ለሆነች ቅፅበት በቁሙ የሚሞትበት ቅፅበት አለ አይደል፡፡ አቲዬ በቁሟ ሞተች፡፡
አላዛርን ከሞት ያስነሳ ራሱም ከሞት የተነሳ ክርስቶስ አቲዬ! ብሎ ልክ እኔ እንደምጠራት
ጠራት፡፡ ዞር አለች ወደ ኋላዋ፡፡ ክርስቶስ ሳይሆን እንዲት ምቾት መድረሻ ያሳጣት ቆንጆ
ወጣት ነበረች … “ወደ ውስጥ ግቢ! ዝናብ መታሽ እኮ” አለቻት አቲዬን፡፡ ገና ሲያጉረመርም
እግሬ አውጭኝ ብሎ ሰው የሚሸሸው ዝናብ እንኳን፣ እንዳሻው ሰው ሳይ ይጨፍር ዘንድ ሰው በቁሙ የሚጠፋበት ቀን አለ፡፡ አቲዬ ጠፍታ ነበር፡፡
ወጣቷ ከፍ ያለ ወንበር ላይ ተቀምጣ እንፋሎቱ ወደ ላይ የሚመዘዝ ትኩስ ሻይ እየጠጣች ነበር፡፡
እቲዬ ወደ ውስተ ገባችና ኩርምት ብላ አንዱ ጥግ ቆመች፡፡ እንደ ቆመች ዝናቡ አባራ፡፡ ሰዉ
በያቅጣጫው ሩጫውን ጀመረ፡፡ አቲዪ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ የእርሷ ዝናብ አላባራም፣
መጠጊያ ላጣ ሰው የሕይወት ዶፍ አባርቶ አያውቅም፡፡ ሰው የፍቅር ዣንጥላ፣ የዝምድና ዣንጥላ፤
የጓደኝነት ዣንጥላ፣ የትዳር ዣንጥላ፣ የእውቀት ዣንጥላ፣ የስራ ዣንተላ፣ የተስፋ ዣንጥላ፣
የእምነት ዣንጥላ ይዞ ስለሚኖር እንጂ ከሕይወት ሰማይ ላይ ነፍስን የሚያበሰብስ መንፈስን
እንደ ወረቀት የሚያላሽቅ የብቸኝነት እና የተስፋ መቁረጥ ዝናብ አባርቶ አያውቅም፡፡
የአቲዬ ዝናብ አላባራም፡፡ ይሄን ሁኑ የነፍስ ዣንጥላ ጨካኝ ንፋስ ከእጇ ነጥቋታል፡፡ ንፋሱ
ቀሚሷን በግድ ገልቦ ውስጧ ቅዝቃዜ አስቀምጧል፡፡ ንፋሱ የሕይወት አቧራ አንስቶ ፊቷና
ፀጉሯን አልብሷል።ንፋሱ የተስፋ ጎጆዋን አፈራርሶ እዚህ አቁሟታል፡፡ አቲዬ የእኔ እናት
መሄጃ የላትም።
ቁልፎች ታንኳኩ፡፡ ቆንጆዋ ልጅ ጃኬቷን ደረበች፡፡ ውጭ የተደረደሩ እቃዎችን አስገባች፤ እናም ቁልፏን በሚያማምሩ ጣቶቿ እንዳንጠለጠሰች አቲዩን ግራ በመጋባት አየቻት፣ “
ውጪ!' ማለት ብልግና ነው፡፡ ቀድሞ ወጥቶ፣ ውጪ ጋር መቆም ግን ያው ውጪ ማለት ነው፡፡
አትዬ ዝናብ እስከያባራ ከተጠለለችበት ሱቅ በቀስታ እርምጃ ወጣችና በረንዳው ላይ ቆመች፤ባለሱቋ ቆንጆ ሴት ሱቋን ቆላለፈች፡፡ የአቲዩ ነገር ሳያሳዝናት አልቀረም፣ እ..ምን ሆነሽ ነው
እናትዬ?አለቻት፡፡ እቲዬ ዝም፡፡ ዓይኗ እንባ አቅርሮ ዝም…ወደ ሞቀ ቤቷ አልያም ወደ ቀጠራት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ያኮበኮበች ወጣት የአቲዬን የአርባ ቀን ዕጣ ከየት ጀምሮ ቢነገራት ይገባታል? አቲዪ ዝም አለች፡፡ አልለመደባትም እንዲህ ሆንኩ ብሎ ማውራት፣ አልለመደባትም ምሬት መዘብዘብ ልማዷ አይደለም።
ወጣቷ ጥቂት ብሮች ከቦርሳዋ አውጥታ ለአቲዬ ዘረጋችላትና “አይዞሽ! ይሄን ያዥ በቃ” አለቻት።
አተዬ ግን አማትባ ከተዘረጋው የወጣቷ እጅ በድንጋጤ አፈገፈገች፡፡ ልክ ጩቢ እንደተሳነዘረበት ሰው ነበር የበረገገችው፡፡ ለማኝ ልሆን?” ብላ በውስጧ አሰበች፡፡ እንባዋን እያዘራች ሽቅብ እግሯን ተከትላ ትጓዝ ጀመር፡፡
የትም የማያደርሱ የሚመስሉ እርምጃዎች አንዳንዴ አዕምሮ አስቦ ከሚደርስበት የተሻለ መፍትሄ ላይ ይደርሳሉ። ሰዎች የፈጣሪ መንገድ ይሏቸዋል፡፡ አቲዬ ዝም ብላ ብዙ ርቀት ተጓዘች። መታጠፊያ ስታገኝ እየታጠፈች፣ መንገድ ስታገኝ እየተሻገረች ዝም ብላ ወደፊት፡፡ ከዕጣ ፋንታዋ ትሸሽ ይመስል መንገዱ ባያልቅ ብላ ተመኘች፡፡ በቃ እስካዓለም ጥግ ዝም ብሎ ቀሪ እድሜዋን መጓዝ ::
ቀጥ ብላ ተመለከተች። ፀጥ ያለ ቤተከርስቲያን ከነታላቅ ጉልላቱ ፊት ፊቷ መንገዱን ተሻግሮ
ይታያል፡፡ የልብስ ፌስታሏን አንጠልጥላ አሮጌ ሃምሳ ብሯን በእጇ እንደጨበጠች፣ ዓለምን
መዳፉ የጨበጠ እግዚአብሔር ጋር የተፋጠጠች መሰላት፡፡
በዚህ ሁሉ በደል የዚህ ሁሉ ግፍና ስቃይ ጠንሳሽ እግዚኣብሔርን ፊትለፊት ያገኘችው መሰላት፡፡
እግዚአብሔር አይቷት ሳያፈገፍግ፣ የበደላት ሁሉ አሳፍሮት ሳይሸሽ በፊት ልትደርስበት መንገዱን
አቋርጣ ወደ ቤተክርስቲያኑ ገሰገሰች፡፡
እግዜር ፈርቷት እግሬ አውጭኝ የሚል መሰላት አቲዬ፡፡ መኪናዎች አምባረቁ፣ ሹፌሮች መኪናቸው መስኮት ብቅ ብለው ፀያፍ ስድብ ወረወሩባት። አንበሳ ጋር ልትፋለም ታላቁን ፈጣሪ 'በላ ልበልሃ' ልትለው በድፍረት የምትገሰግስ ጀግና በውሻዎች ጩኸት የምትበረግግ መስሏቸው።
አቲዬ ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ደረሰች፡፡ እግዜር ያኔ ለያት፡፡ ከሰማየ ሰማያት ዙፋኑ ላይ
እንደተቀመጠ ድምፅ ከወደ ምድር ሰማ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ” እያሉ በታላቅ ድምፅ የሚሰግዱና
የሚያሸበሽቡ እልፍ አእላፍ መላክትን “ዝም በሉ አንድ ለየት ያለ ድምፅ ከምድር ሰምቻለሁ” አለ፡፡
“ጌታ ሆይ ሞልቃቆች በስሱ እያማተቡ መኪናቸው ውስጥ ሆነው ሽው የሚሉት አይነት ድምፅ ይሆናል" አሉት መላዕክቱ፡፡
“አይደለም” አለ እግዚአብሔር፡፡
"የኮተታሞች የኮተት ጥያቄ ይሆናል" አሉት በምድራዊ ትርኪምርኪ የስጋ ጥያቄ የተማረሩት መላዕክት፡፡
"አይደለም አልኩ እኮ” አለ እግዚአብሔር በታላቅ ድምፅ፡፡
“ጌታ ሆይ! ምናልባት የሀብታሞች ከስኳር፣ ከደም ግፊት ከፈወስከኝ መጋረጃ ዣንጥላ የሚሉት
አይነት የተለመደው ስእለት ይሆን” ጠየቁ መላዕክቱ፡፡
ዝም አለ እግዚአብሐር !! ዝምታው አንዳች አስፈሪ ነገር አለው፡፡ በዝምታው ውስጥ ፅንፍ
የለሽ ሀዘንና ፍቅር ነበር።
ከልጅ ስጠኝ ንዝንዝ፣ ከስራ ስጠኝ ንትርክም የተለየ ድምፅ ነበር፡፡ ድምፄ ካማረልኝ ብላ
የምትዘምር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታላቅ ግርማ ሞገስ በእሳት ሰረገላ ደርሰህ ጠላቴን አፈር
ድሜ የምታስበላ የነገስታት ንጉስ፡፡ ከፀሐይ አስራ ዘጠኝ እጅ የምታበራ እያለች በተጠና
መንፈሳዊ ፉከራ መንፈሳዊ ዘራፍ የምታደነቁር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታሰበረ ልቧ በወጣ ማቃተት ዙፋኑን የነቃነቀችው እዚህ ግቢ የማትባል ሴት ናት፡፡ አንዲት ሴት በሩ ላይ ስትቆም፣
“ማነው የልብሴን ጫፍ በዕምነት የነካው” ብሏል እግዚአብሔር!
አቲዩ የእኔ ጀግና ማንንም ደጅ አልጠናቸም፡፡ በልብሷ መቆሸሽ ይናቋት እንጂ የእኔ እናት
ከአዲስ አበባ የሕዝብ ጎርፍ ቁራሽ አልለመነችም፡፡ ለማን ስሞታ እንደምትናገር አውቃለች፡፡
አጥሩን በድንጋይ ቢያጥር፣ ባማረ መኪና ቢንፈላሰሰ፣ ሴቱ በወርቅ ሽቆጠቆጥ..የአዲስ አበባ
ሰውና አቲዬ ልብ ለልብ ተነቃቅተዋል፡፡
አይታዋለች ሕዝቡን የህሊናውን ዓይን ጨፍና ጎዳና የፈሰሱትን የራሱን ጉዶች እንቁልልጭ እያለ
በየስጋ ቤቱ በረንዳ ላይ ጥሬ ስጋውን ሲያጋብስ፣ ቢራና ውስኪውን ሲገለብጥ አይታዋለች፡፡
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...አቲዩ ለስድስት ወር ከሰውነት ተራ እስከትወጣ ለባለኪዮስኳ ስትሰራ ከከረመች በኋላ ክረምት ገባ፡፡ ባላኪዮስካ አቲዬን በንስር ዓይን ስትከታተላት ነበር፡፡ ከእያንዳንዱ ቀን ጋር
እየተሽቀጓደመች ነበር፡፡ አንድ ማለዳ የአቲዬን ድሪቶ ልብሶች በፌስታል ቋጥራ ከድፍን ሃምሳ
ብር ጋር ሰጠቻትና፣ “በይ እግዜር ይከትልሽ!” ብላ ከቤቷ አስወጥታ ወረረቻት፡፡ የአቲዬ ሆድ ገፍቶ ነበር፡፡ የቀለመወርቅ ፅንስ ከውስጥ፣ የመንደሩ ሰው ከውጭ እየገፋ ሰው በሞላው አገር
እናቴን ምድረ በዳ ላይ አቆሟት፡፡
አቲዪ ስትፈጭ እና ስታነፍስ የዋለችው የምስር ክክ ብናኝ ፊቷና ፀጉሯ ላይ ተነስንሶ ነበር፡፡ ከስድስት ወር በፊት የነበረችው ልጅ እግር ቆንጆ ልጃገረድ ናት ቢባል ቀለሙ ራሱ አያምንም፡፡ መንገድ ዳር ቆመች፡፡ የክረምት ዝናብ ያካፋል፡፡ አንድ የመኪና ዕቃ መለዋወጫ ሱቅ በር ላይ ፍዝዝ ብላ ቆመች::ምንም እያየች ምንም ሰው፣ ምንም መኪና ምንም ቤት፡፡ ህይወት ዝም የምትልበት፣ አዕምሮ ዝም
የሚልበት፣ የሰው ልጅ ለሆነች ቅፅበት በቁሙ የሚሞትበት ቅፅበት አለ አይደል፡፡ አቲዬ በቁሟ ሞተች፡፡
አላዛርን ከሞት ያስነሳ ራሱም ከሞት የተነሳ ክርስቶስ አቲዬ! ብሎ ልክ እኔ እንደምጠራት
ጠራት፡፡ ዞር አለች ወደ ኋላዋ፡፡ ክርስቶስ ሳይሆን እንዲት ምቾት መድረሻ ያሳጣት ቆንጆ
ወጣት ነበረች … “ወደ ውስጥ ግቢ! ዝናብ መታሽ እኮ” አለቻት አቲዬን፡፡ ገና ሲያጉረመርም
እግሬ አውጭኝ ብሎ ሰው የሚሸሸው ዝናብ እንኳን፣ እንዳሻው ሰው ሳይ ይጨፍር ዘንድ ሰው በቁሙ የሚጠፋበት ቀን አለ፡፡ አቲዬ ጠፍታ ነበር፡፡
ወጣቷ ከፍ ያለ ወንበር ላይ ተቀምጣ እንፋሎቱ ወደ ላይ የሚመዘዝ ትኩስ ሻይ እየጠጣች ነበር፡፡
እቲዬ ወደ ውስተ ገባችና ኩርምት ብላ አንዱ ጥግ ቆመች፡፡ እንደ ቆመች ዝናቡ አባራ፡፡ ሰዉ
በያቅጣጫው ሩጫውን ጀመረ፡፡ አቲዪ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ የእርሷ ዝናብ አላባራም፣
መጠጊያ ላጣ ሰው የሕይወት ዶፍ አባርቶ አያውቅም፡፡ ሰው የፍቅር ዣንጥላ፣ የዝምድና ዣንጥላ፤
የጓደኝነት ዣንጥላ፣ የትዳር ዣንጥላ፣ የእውቀት ዣንጥላ፣ የስራ ዣንተላ፣ የተስፋ ዣንጥላ፣
የእምነት ዣንጥላ ይዞ ስለሚኖር እንጂ ከሕይወት ሰማይ ላይ ነፍስን የሚያበሰብስ መንፈስን
እንደ ወረቀት የሚያላሽቅ የብቸኝነት እና የተስፋ መቁረጥ ዝናብ አባርቶ አያውቅም፡፡
የአቲዬ ዝናብ አላባራም፡፡ ይሄን ሁኑ የነፍስ ዣንጥላ ጨካኝ ንፋስ ከእጇ ነጥቋታል፡፡ ንፋሱ
ቀሚሷን በግድ ገልቦ ውስጧ ቅዝቃዜ አስቀምጧል፡፡ ንፋሱ የሕይወት አቧራ አንስቶ ፊቷና
ፀጉሯን አልብሷል።ንፋሱ የተስፋ ጎጆዋን አፈራርሶ እዚህ አቁሟታል፡፡ አቲዬ የእኔ እናት
መሄጃ የላትም።
ቁልፎች ታንኳኩ፡፡ ቆንጆዋ ልጅ ጃኬቷን ደረበች፡፡ ውጭ የተደረደሩ እቃዎችን አስገባች፤ እናም ቁልፏን በሚያማምሩ ጣቶቿ እንዳንጠለጠሰች አቲዩን ግራ በመጋባት አየቻት፣ “
ውጪ!' ማለት ብልግና ነው፡፡ ቀድሞ ወጥቶ፣ ውጪ ጋር መቆም ግን ያው ውጪ ማለት ነው፡፡
አትዬ ዝናብ እስከያባራ ከተጠለለችበት ሱቅ በቀስታ እርምጃ ወጣችና በረንዳው ላይ ቆመች፤ባለሱቋ ቆንጆ ሴት ሱቋን ቆላለፈች፡፡ የአቲዩ ነገር ሳያሳዝናት አልቀረም፣ እ..ምን ሆነሽ ነው
እናትዬ?አለቻት፡፡ እቲዬ ዝም፡፡ ዓይኗ እንባ አቅርሮ ዝም…ወደ ሞቀ ቤቷ አልያም ወደ ቀጠራት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ያኮበኮበች ወጣት የአቲዬን የአርባ ቀን ዕጣ ከየት ጀምሮ ቢነገራት ይገባታል? አቲዪ ዝም አለች፡፡ አልለመደባትም እንዲህ ሆንኩ ብሎ ማውራት፣ አልለመደባትም ምሬት መዘብዘብ ልማዷ አይደለም።
ወጣቷ ጥቂት ብሮች ከቦርሳዋ አውጥታ ለአቲዬ ዘረጋችላትና “አይዞሽ! ይሄን ያዥ በቃ” አለቻት።
አተዬ ግን አማትባ ከተዘረጋው የወጣቷ እጅ በድንጋጤ አፈገፈገች፡፡ ልክ ጩቢ እንደተሳነዘረበት ሰው ነበር የበረገገችው፡፡ ለማኝ ልሆን?” ብላ በውስጧ አሰበች፡፡ እንባዋን እያዘራች ሽቅብ እግሯን ተከትላ ትጓዝ ጀመር፡፡
የትም የማያደርሱ የሚመስሉ እርምጃዎች አንዳንዴ አዕምሮ አስቦ ከሚደርስበት የተሻለ መፍትሄ ላይ ይደርሳሉ። ሰዎች የፈጣሪ መንገድ ይሏቸዋል፡፡ አቲዬ ዝም ብላ ብዙ ርቀት ተጓዘች። መታጠፊያ ስታገኝ እየታጠፈች፣ መንገድ ስታገኝ እየተሻገረች ዝም ብላ ወደፊት፡፡ ከዕጣ ፋንታዋ ትሸሽ ይመስል መንገዱ ባያልቅ ብላ ተመኘች፡፡ በቃ እስካዓለም ጥግ ዝም ብሎ ቀሪ እድሜዋን መጓዝ ::
ቀጥ ብላ ተመለከተች። ፀጥ ያለ ቤተከርስቲያን ከነታላቅ ጉልላቱ ፊት ፊቷ መንገዱን ተሻግሮ
ይታያል፡፡ የልብስ ፌስታሏን አንጠልጥላ አሮጌ ሃምሳ ብሯን በእጇ እንደጨበጠች፣ ዓለምን
መዳፉ የጨበጠ እግዚአብሔር ጋር የተፋጠጠች መሰላት፡፡
በዚህ ሁሉ በደል የዚህ ሁሉ ግፍና ስቃይ ጠንሳሽ እግዚኣብሔርን ፊትለፊት ያገኘችው መሰላት፡፡
እግዚአብሔር አይቷት ሳያፈገፍግ፣ የበደላት ሁሉ አሳፍሮት ሳይሸሽ በፊት ልትደርስበት መንገዱን
አቋርጣ ወደ ቤተክርስቲያኑ ገሰገሰች፡፡
እግዜር ፈርቷት እግሬ አውጭኝ የሚል መሰላት አቲዬ፡፡ መኪናዎች አምባረቁ፣ ሹፌሮች መኪናቸው መስኮት ብቅ ብለው ፀያፍ ስድብ ወረወሩባት። አንበሳ ጋር ልትፋለም ታላቁን ፈጣሪ 'በላ ልበልሃ' ልትለው በድፍረት የምትገሰግስ ጀግና በውሻዎች ጩኸት የምትበረግግ መስሏቸው።
አቲዬ ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ደረሰች፡፡ እግዜር ያኔ ለያት፡፡ ከሰማየ ሰማያት ዙፋኑ ላይ
እንደተቀመጠ ድምፅ ከወደ ምድር ሰማ፡፡ ቅዱስ ቅዱስ” እያሉ በታላቅ ድምፅ የሚሰግዱና
የሚያሸበሽቡ እልፍ አእላፍ መላክትን “ዝም በሉ አንድ ለየት ያለ ድምፅ ከምድር ሰምቻለሁ” አለ፡፡
“ጌታ ሆይ ሞልቃቆች በስሱ እያማተቡ መኪናቸው ውስጥ ሆነው ሽው የሚሉት አይነት ድምፅ ይሆናል" አሉት መላዕክቱ፡፡
“አይደለም” አለ እግዚአብሔር፡፡
"የኮተታሞች የኮተት ጥያቄ ይሆናል" አሉት በምድራዊ ትርኪምርኪ የስጋ ጥያቄ የተማረሩት መላዕክት፡፡
"አይደለም አልኩ እኮ” አለ እግዚአብሔር በታላቅ ድምፅ፡፡
“ጌታ ሆይ! ምናልባት የሀብታሞች ከስኳር፣ ከደም ግፊት ከፈወስከኝ መጋረጃ ዣንጥላ የሚሉት
አይነት የተለመደው ስእለት ይሆን” ጠየቁ መላዕክቱ፡፡
ዝም አለ እግዚአብሐር !! ዝምታው አንዳች አስፈሪ ነገር አለው፡፡ በዝምታው ውስጥ ፅንፍ
የለሽ ሀዘንና ፍቅር ነበር።
ከልጅ ስጠኝ ንዝንዝ፣ ከስራ ስጠኝ ንትርክም የተለየ ድምፅ ነበር፡፡ ድምፄ ካማረልኝ ብላ
የምትዘምር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታላቅ ግርማ ሞገስ በእሳት ሰረገላ ደርሰህ ጠላቴን አፈር
ድሜ የምታስበላ የነገስታት ንጉስ፡፡ ከፀሐይ አስራ ዘጠኝ እጅ የምታበራ እያለች በተጠና
መንፈሳዊ ፉከራ መንፈሳዊ ዘራፍ የምታደነቁር ሴትም አልነበረችም፡፡ ከታሰበረ ልቧ በወጣ ማቃተት ዙፋኑን የነቃነቀችው እዚህ ግቢ የማትባል ሴት ናት፡፡ አንዲት ሴት በሩ ላይ ስትቆም፣
“ማነው የልብሴን ጫፍ በዕምነት የነካው” ብሏል እግዚአብሔር!
አቲዩ የእኔ ጀግና ማንንም ደጅ አልጠናቸም፡፡ በልብሷ መቆሸሽ ይናቋት እንጂ የእኔ እናት
ከአዲስ አበባ የሕዝብ ጎርፍ ቁራሽ አልለመነችም፡፡ ለማን ስሞታ እንደምትናገር አውቃለች፡፡
አጥሩን በድንጋይ ቢያጥር፣ ባማረ መኪና ቢንፈላሰሰ፣ ሴቱ በወርቅ ሽቆጠቆጥ..የአዲስ አበባ
ሰውና አቲዬ ልብ ለልብ ተነቃቅተዋል፡፡
አይታዋለች ሕዝቡን የህሊናውን ዓይን ጨፍና ጎዳና የፈሰሱትን የራሱን ጉዶች እንቁልልጭ እያለ
በየስጋ ቤቱ በረንዳ ላይ ጥሬ ስጋውን ሲያጋብስ፣ ቢራና ውስኪውን ሲገለብጥ አይታዋለች፡፡
👍27❤1👏1