#ከሰሀራ_በታች
፡
፡
#አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
የፍቅርተ ጂንስ ሱሪ ታጥቦ ከተሰጣበት የልብስ ማስጫ ገመድ ላይ ጠፋ፡፡ “የትኛው ሱሪ?”
የሚል ይኖራል፤ ፍቅርተ የነበራት አንድ ሱሪ ነበር፡፡ የጠፋውም ይሄው አንድ ለናቱ የሆነ ሱሪ ነው፡፡ የመንደሩ ሱሰኛ ጎረምሶች ለዕለት ሱሳቸው ማስታገሻ ወስደው ሸጠውት ይሁን አልያም ሞገደኛ ነፋስ እያግለበለበ ወስዶ አንዱ ቂርቂራ ሸጉጦት እግዜር ይወቅ፡፡ ግራም ነፈሰ ቀኝ ከተገዛ ገና ስድስት ወር ብቻ የሆነው፣ ግርጌው ቀበኛ ከብት አኝኮ እንደተወው ጨርቅ
የተተፈተፈው የፍቅርተ ጥቁር ጅንስ ሱሪ ታጥቦ ከተሰጣበት ገመድ ላይ ጠፋ፡፡ ትልቅ የአገር
ቅርስ የጠፋ ያህል ነበር አንጀቴ ቁርጥ ያለው፡፡ ደምና አጥንት የተከፈለለት የአገር ድንበር
የተቆረሰ ያህል ነበር ውስጤ በቁጭት የተንገበገበው፡፡
በእርግጥ ይሄ ሱሪ መታጠብ ብዛት የልጅነት ጥቁር ቀለሙ ተገፍፎ ግራጫ መሆን ጀምሮ
ነበር፡፡ ኧረ እንደውም እንደ ሰው ፀጉር በስተርጅና ነጫጭ ጭረት ጣል ጣል ያደረገበት ሱሪ
ነበር፡፡ ቢሆንም እርጅናው ከሱሪው ህያው ዋጋ ላይ ሽራፊ ሳንቲም ሊቀንስ አይቻለውም፡፡
እርጅና የማያደበዝዘው እውነት፣ የዘመን ብዛት የማያጠፋው ሃቅ አለና፤ የዛ እውነት ማህደር
ነው የተወሰደው፡፡
የፍቅርተ ሱሪ ጠፋ ማለት የመንደራችን ባንዲራ ጠፋ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ሱሪ ተራ ሱሪ ብቻ አልነበረም፤ የማንነት መቋጠሪያ ጨርቅ፣ የተገፉ ድሆች እንባ ማበሻ መሃረም፣ የፍቅር
መክተቻ ከረጢት ነበር፡፡ ምን ያደርጋል ! ታጥቦ ከተሰጣበት ገመድ ላይ ጠፋ ፡፡
አንዳንዱ የደላው መንደርተኛ የፍቅርተ ሱሪ መጥፋቱን ሲሰማ “ይሄ ሁሉ ላይ ታች ማለት ለአንድ
አሮጌ ሱሪ ነው ?” እያለ ወደየ ጉዳዩ ይጣደፋል፡፡ “በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት” ቢባልም
ቅሉ እንዴት ሰው በራሱ ቁስል እንጨት ይሰድዳል? ስለፍቅርተ ሱሪ የማይመለከተው ማነው?
እኔ በበኩሌ የፍቅርተ ሱሪ ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ ባይ ነኝ፡፡ ስንለው ስንጮኸው የኖርነው ቃል ነበር የፍቅርተ ሱሪ! አብሮን የኖረ ቃል ጨርቅ ለብሶ የተከሰተው በፍቅርተ ሱሪ ነበር፡፡ ድንገት የቀኝ እጄን ስመለከተው ሁለት ጣቶቼን ከቦታቸው ላይ ባጣቸው እንኳን የዚህን ያህል የምደነግጥ አይመስለኝም፡፡ እዚህ መዲናችን ውስጥ ያለው የአፍሪካ ህብረት ሕንፃ ድንገት ከስሩ ተነቅሎ የደረሰበት ጠፋ ሲባል የፍቅርተን ሱሪ ያህል አያስደነግጠኝም፤ ኧረ ፍቅርተ ራሷ ብትጠፋ የሱሪዋን ያህል
አታስደነግጠኝም፡፡ ስለዚህ ሱሪ የተዳፈነ ተስፋ፣ የተኮላሸ ፍቅር አለና ሱሪው ሱሪ ብቻ አልነበረም፡፡
ሱሪው የጠፋ ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ስምንት ሰዓት አካባቢ ከምማርበት ኮሌጅ ስመለስ እማማ አመለወርቅ በራቸው ስር ሁልጊዜ የሚቀመጡባት ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው አገኘኋቸው ዓይናቸው ቡዝዝ ብሎ በሀሳብ በመመሰጣቸው እስካናግራቸው ድረስ አጠገባቸው መድረሴንም
አላዩም ነበር፡፡ ለወትሮው እዚህች ድንጋይ መቀመጫ ላይ የሚቀመጡት እጃቸው አጠር ብላ
ለዕለት ቡና ብር ቢጤ ሲቸግራቸው ነበር፡፡ የድንጋይ ወንበሯ የመተከዣ መድረካቸው ናት::
“ማዘር ምነው ሰላም አይደሉም እንዴ?” አልኳቸው፤
ቀጥ ብለው እንባ ባኳተሩ ዐይኖቻቸው ተመለከቱኝና ሳግ ተናነቀው አሳዛኝ ድምፅ ፣ “የፍቅርን ሱሪ ወሰዱባት አብርሽ!” አሉኝ፤ ሊያናግሩኝ ቀና ሲሉ እያለቀሱ እንደቆዩ ፊታቸው ላይ ዳናውን የተወ እንባቸው ይናገራል፡፡
“እነማን ናቸው የወሰዱት?” አልኳቸው የሰማሁትን ባለማመን፤ ቅስም ከሚሰብር ዜና ኋላ
የተከሰተ የጅል የሚመስል ጥያቄ፡፡
“ምናውቄ ብለህ አብርሽ ! ከዚህ ከተሰጣበት ገመድ ላይ አንስተው ወሰዱት” አሉና እንባቸውን
ዘረገፉት፡፡ ድህነት እንደ ሸንኮራ መጥጦ ካደረቀው ሰውነት ይሄን ያህል እንባ ይወጣል ብዬ
አላሰብኩም ነበር፡፡ ሕይወት ምንጊዜም አዲስ እንባ አላት፡፡ከእንባቸው የበለጠ ፊታቸው ላይ
ያረበበው ሐዘንና ምሬት ያሳዝን ነበር፡፡አንጋጥጬ የልብስ ማስጫ ገመዱን ተመለከትኩት፡፡
ወዲህ የኤሌክትሪክ ምሰሶ ላይ ወዲያ ደግሞ የአንዲት ጎረቤት የቤት ጣራ ማገር ላይ የተወጠረው ገመድ የተወረረ ከተማ መስሏል፡፡ ባንዲራውን እንዳወረዱበት የሰንደቅ ምሰሶ ትከሻው ቀሏል፡፡ ባዶ !! ለፍቅርተ፣ ለእኔ፣ ለእማማ ዓመለ፣ ለመንደሩና ለአገሩ ባዶነትን ትቶልን የሄደው ማነው?
ይሄ ገመድ ባዶውን ውሎ አያውቅም ነበር፡፡ ቢጠፋ ቢጠፋ የጉግሳ አውራ ጣቱ የተሸነቆረ
ካልሲ ወይም አሁን የጠፋው የፍቅርተ ሱሪ ተሰጥቶበት ነበር የሚውለው፡፡ የፍቅርተ ሱሪና
የጉግሳ ካልሲ ሁልጊዜም ገመዱ ላይ ጎን ለጎን ተሰጥተው ስለማያቸው የልብ ወዳጆች ይመስሉኝ ነበር ፡፡የፍቅርተ ሱሪ ከፍ ያሉት ንቀውት ዝቅ ብሎ የካልሲ ጓደኛ የሆነ፡፡ ካልሲውም ቢጤዎቹ ንቀውት ቀን ከገፋው ሱሪ ጋር የዋለ ዓይነት፡፡
አንጋጥጬ ስመለከት ከገመዱ በላይ ጥርት ያለው ሰማይ ተዘርግቷል፡፡ የፍቅርተን ሱሪ የወሰዱት ሌቦች ለወትሮው ሰማዩ ላይ የማይጠፋውን ደመና የወሰዱት ይመስል ነበር፡፡ ሰማዩ ባዶ! የልብስ ማስጫው ገመድ ባዶ!! አይ አይ ሰማዩ እንኳን ባዶ አልነበረም፡፡ ነግቶ የረፈደባት የምትመስል ግማሽ ጨረቃ ትታያለች፡፡ የሱሪ ሌባው ግማሿን ጨረቃ ሸርፎ የወሰዳት ይመስል፡፡
ቆይ ግን ሱሪውን የወሰደው ሌባ ከሆነ ሌባውን ምን ነካው? እንዴት የፍቅርተን ሱሪ ይወስዳል? እሺ
ነፋስም ከሆነ ንፋሱን ምን ነካው ? አቧራ ያስነሳ፣ የቤት ጣራ ይገነጣጥል ቢፈልግ ! ያንን ከሰፈራችን ወደታች ያለውን የአድባር ዛፍ ከስሩ ገርስሶ ይጣለው ! ግን እንዴት የፍቅርተን አንድ ለእናቱ የሆነ ሱሪ ይወስዳል ? ምን ቁርጥ አድርጎት የመንደራችንን ባንዲራ ይደፍራል ? በሌባው ተቆጣሁ
በነፋሱ ተቆጣሁ ፡፡ በፈጣሪም ተቆጣሁ :: መምሬ ልሳኑ ታዲያ (የእማማ አመለ ንስሃ አባት)
የሱሪውን መጥፋት ሲሰሙ፣ እማማ አመለን ለማፅናናት ብለው ይሁን አልያም አምነውበት እንጃ
ብቻ ጥቅስ አጣቀሱ፤ “ላለው ይጨመርለታል፣ ከሌለው ግን ያለውም ይወሰድበታል ወለተ ኪዳን አይዞሽ” በዚህ ማፅናኛቸው በጣም ተበሳጨሁ፤ እንደውም በፈጣሪ ላይ የተሰማኝ ቅሬታ ተባባሰ፡፡
ፈጣሪ የሌባው እጅ ወደ ፍቅርተ ሱሪ ሲዘረጋ እንደ ደረቅ እንጨት ድርቅ አድርጎ ማስቀረት ይችል ነበር፡፡ ነፋስና ማዕበልን የሚገስጽ ፈጣሪ እንዴት ዝም አለ ? እሳት ከሰማይ የሚያወርድ አምላክ ከዚህ በላይ በደል፣ ከዚህ በላይ ግፍ ምን አለና ታገሰ ? የፍቅርተን ሱሪ የወሰደው ንፋስ ከሆነም መገሰጽ ይችል ነበር፣ ስለምን ዝም አለ ? እንኳን አጋጣሚውን አገኘሁ እንጂ ፈጣሪ ጋርማ በፍቅርተ ጉዳይ ብዙ ጥያቄ አለኝ! ብዙ ! ሲጀመር ፍቅርተን ስለምን እንዲህ አድርጎ ፈጠራት…እኮ ለምን !? ለእሱስ ለስሙ ጥሩ ነው ??
“የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ነው” ይሉት ብሂል ስጋ ለብሶ የተገለጠው እማማ አመለ ቤት ነበር፡፡እማማ አመለ በመልክ ይሁን በባህሪ የማይገናኙ፣ ከፆታቸው በቀር አንድ የሚያደርጋቸው አንድ
ነገር እንኳን ፈልጎ ማግኘት የሚከብድ ሁለት ሴት ልጆች ያሏቸው፣ እድሜያቸው የገፋ ደግ ሴት ነበሩ ፡፡ ከሁለት ክፍል ቤታቸው አንዷን ተከራይቼ ለአራት ዓመታት ቤታቸው ውስጥ ኖሬያለሁ፡፡
፡
፡
#አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
የፍቅርተ ጂንስ ሱሪ ታጥቦ ከተሰጣበት የልብስ ማስጫ ገመድ ላይ ጠፋ፡፡ “የትኛው ሱሪ?”
የሚል ይኖራል፤ ፍቅርተ የነበራት አንድ ሱሪ ነበር፡፡ የጠፋውም ይሄው አንድ ለናቱ የሆነ ሱሪ ነው፡፡ የመንደሩ ሱሰኛ ጎረምሶች ለዕለት ሱሳቸው ማስታገሻ ወስደው ሸጠውት ይሁን አልያም ሞገደኛ ነፋስ እያግለበለበ ወስዶ አንዱ ቂርቂራ ሸጉጦት እግዜር ይወቅ፡፡ ግራም ነፈሰ ቀኝ ከተገዛ ገና ስድስት ወር ብቻ የሆነው፣ ግርጌው ቀበኛ ከብት አኝኮ እንደተወው ጨርቅ
የተተፈተፈው የፍቅርተ ጥቁር ጅንስ ሱሪ ታጥቦ ከተሰጣበት ገመድ ላይ ጠፋ፡፡ ትልቅ የአገር
ቅርስ የጠፋ ያህል ነበር አንጀቴ ቁርጥ ያለው፡፡ ደምና አጥንት የተከፈለለት የአገር ድንበር
የተቆረሰ ያህል ነበር ውስጤ በቁጭት የተንገበገበው፡፡
በእርግጥ ይሄ ሱሪ መታጠብ ብዛት የልጅነት ጥቁር ቀለሙ ተገፍፎ ግራጫ መሆን ጀምሮ
ነበር፡፡ ኧረ እንደውም እንደ ሰው ፀጉር በስተርጅና ነጫጭ ጭረት ጣል ጣል ያደረገበት ሱሪ
ነበር፡፡ ቢሆንም እርጅናው ከሱሪው ህያው ዋጋ ላይ ሽራፊ ሳንቲም ሊቀንስ አይቻለውም፡፡
እርጅና የማያደበዝዘው እውነት፣ የዘመን ብዛት የማያጠፋው ሃቅ አለና፤ የዛ እውነት ማህደር
ነው የተወሰደው፡፡
የፍቅርተ ሱሪ ጠፋ ማለት የመንደራችን ባንዲራ ጠፋ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ሱሪ ተራ ሱሪ ብቻ አልነበረም፤ የማንነት መቋጠሪያ ጨርቅ፣ የተገፉ ድሆች እንባ ማበሻ መሃረም፣ የፍቅር
መክተቻ ከረጢት ነበር፡፡ ምን ያደርጋል ! ታጥቦ ከተሰጣበት ገመድ ላይ ጠፋ ፡፡
አንዳንዱ የደላው መንደርተኛ የፍቅርተ ሱሪ መጥፋቱን ሲሰማ “ይሄ ሁሉ ላይ ታች ማለት ለአንድ
አሮጌ ሱሪ ነው ?” እያለ ወደየ ጉዳዩ ይጣደፋል፡፡ “በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት” ቢባልም
ቅሉ እንዴት ሰው በራሱ ቁስል እንጨት ይሰድዳል? ስለፍቅርተ ሱሪ የማይመለከተው ማነው?
እኔ በበኩሌ የፍቅርተ ሱሪ ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ ባይ ነኝ፡፡ ስንለው ስንጮኸው የኖርነው ቃል ነበር የፍቅርተ ሱሪ! አብሮን የኖረ ቃል ጨርቅ ለብሶ የተከሰተው በፍቅርተ ሱሪ ነበር፡፡ ድንገት የቀኝ እጄን ስመለከተው ሁለት ጣቶቼን ከቦታቸው ላይ ባጣቸው እንኳን የዚህን ያህል የምደነግጥ አይመስለኝም፡፡ እዚህ መዲናችን ውስጥ ያለው የአፍሪካ ህብረት ሕንፃ ድንገት ከስሩ ተነቅሎ የደረሰበት ጠፋ ሲባል የፍቅርተን ሱሪ ያህል አያስደነግጠኝም፤ ኧረ ፍቅርተ ራሷ ብትጠፋ የሱሪዋን ያህል
አታስደነግጠኝም፡፡ ስለዚህ ሱሪ የተዳፈነ ተስፋ፣ የተኮላሸ ፍቅር አለና ሱሪው ሱሪ ብቻ አልነበረም፡፡
ሱሪው የጠፋ ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ስምንት ሰዓት አካባቢ ከምማርበት ኮሌጅ ስመለስ እማማ አመለወርቅ በራቸው ስር ሁልጊዜ የሚቀመጡባት ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው አገኘኋቸው ዓይናቸው ቡዝዝ ብሎ በሀሳብ በመመሰጣቸው እስካናግራቸው ድረስ አጠገባቸው መድረሴንም
አላዩም ነበር፡፡ ለወትሮው እዚህች ድንጋይ መቀመጫ ላይ የሚቀመጡት እጃቸው አጠር ብላ
ለዕለት ቡና ብር ቢጤ ሲቸግራቸው ነበር፡፡ የድንጋይ ወንበሯ የመተከዣ መድረካቸው ናት::
“ማዘር ምነው ሰላም አይደሉም እንዴ?” አልኳቸው፤
ቀጥ ብለው እንባ ባኳተሩ ዐይኖቻቸው ተመለከቱኝና ሳግ ተናነቀው አሳዛኝ ድምፅ ፣ “የፍቅርን ሱሪ ወሰዱባት አብርሽ!” አሉኝ፤ ሊያናግሩኝ ቀና ሲሉ እያለቀሱ እንደቆዩ ፊታቸው ላይ ዳናውን የተወ እንባቸው ይናገራል፡፡
“እነማን ናቸው የወሰዱት?” አልኳቸው የሰማሁትን ባለማመን፤ ቅስም ከሚሰብር ዜና ኋላ
የተከሰተ የጅል የሚመስል ጥያቄ፡፡
“ምናውቄ ብለህ አብርሽ ! ከዚህ ከተሰጣበት ገመድ ላይ አንስተው ወሰዱት” አሉና እንባቸውን
ዘረገፉት፡፡ ድህነት እንደ ሸንኮራ መጥጦ ካደረቀው ሰውነት ይሄን ያህል እንባ ይወጣል ብዬ
አላሰብኩም ነበር፡፡ ሕይወት ምንጊዜም አዲስ እንባ አላት፡፡ከእንባቸው የበለጠ ፊታቸው ላይ
ያረበበው ሐዘንና ምሬት ያሳዝን ነበር፡፡አንጋጥጬ የልብስ ማስጫ ገመዱን ተመለከትኩት፡፡
ወዲህ የኤሌክትሪክ ምሰሶ ላይ ወዲያ ደግሞ የአንዲት ጎረቤት የቤት ጣራ ማገር ላይ የተወጠረው ገመድ የተወረረ ከተማ መስሏል፡፡ ባንዲራውን እንዳወረዱበት የሰንደቅ ምሰሶ ትከሻው ቀሏል፡፡ ባዶ !! ለፍቅርተ፣ ለእኔ፣ ለእማማ ዓመለ፣ ለመንደሩና ለአገሩ ባዶነትን ትቶልን የሄደው ማነው?
ይሄ ገመድ ባዶውን ውሎ አያውቅም ነበር፡፡ ቢጠፋ ቢጠፋ የጉግሳ አውራ ጣቱ የተሸነቆረ
ካልሲ ወይም አሁን የጠፋው የፍቅርተ ሱሪ ተሰጥቶበት ነበር የሚውለው፡፡ የፍቅርተ ሱሪና
የጉግሳ ካልሲ ሁልጊዜም ገመዱ ላይ ጎን ለጎን ተሰጥተው ስለማያቸው የልብ ወዳጆች ይመስሉኝ ነበር ፡፡የፍቅርተ ሱሪ ከፍ ያሉት ንቀውት ዝቅ ብሎ የካልሲ ጓደኛ የሆነ፡፡ ካልሲውም ቢጤዎቹ ንቀውት ቀን ከገፋው ሱሪ ጋር የዋለ ዓይነት፡፡
አንጋጥጬ ስመለከት ከገመዱ በላይ ጥርት ያለው ሰማይ ተዘርግቷል፡፡ የፍቅርተን ሱሪ የወሰዱት ሌቦች ለወትሮው ሰማዩ ላይ የማይጠፋውን ደመና የወሰዱት ይመስል ነበር፡፡ ሰማዩ ባዶ! የልብስ ማስጫው ገመድ ባዶ!! አይ አይ ሰማዩ እንኳን ባዶ አልነበረም፡፡ ነግቶ የረፈደባት የምትመስል ግማሽ ጨረቃ ትታያለች፡፡ የሱሪ ሌባው ግማሿን ጨረቃ ሸርፎ የወሰዳት ይመስል፡፡
ቆይ ግን ሱሪውን የወሰደው ሌባ ከሆነ ሌባውን ምን ነካው? እንዴት የፍቅርተን ሱሪ ይወስዳል? እሺ
ነፋስም ከሆነ ንፋሱን ምን ነካው ? አቧራ ያስነሳ፣ የቤት ጣራ ይገነጣጥል ቢፈልግ ! ያንን ከሰፈራችን ወደታች ያለውን የአድባር ዛፍ ከስሩ ገርስሶ ይጣለው ! ግን እንዴት የፍቅርተን አንድ ለእናቱ የሆነ ሱሪ ይወስዳል ? ምን ቁርጥ አድርጎት የመንደራችንን ባንዲራ ይደፍራል ? በሌባው ተቆጣሁ
በነፋሱ ተቆጣሁ ፡፡ በፈጣሪም ተቆጣሁ :: መምሬ ልሳኑ ታዲያ (የእማማ አመለ ንስሃ አባት)
የሱሪውን መጥፋት ሲሰሙ፣ እማማ አመለን ለማፅናናት ብለው ይሁን አልያም አምነውበት እንጃ
ብቻ ጥቅስ አጣቀሱ፤ “ላለው ይጨመርለታል፣ ከሌለው ግን ያለውም ይወሰድበታል ወለተ ኪዳን አይዞሽ” በዚህ ማፅናኛቸው በጣም ተበሳጨሁ፤ እንደውም በፈጣሪ ላይ የተሰማኝ ቅሬታ ተባባሰ፡፡
ፈጣሪ የሌባው እጅ ወደ ፍቅርተ ሱሪ ሲዘረጋ እንደ ደረቅ እንጨት ድርቅ አድርጎ ማስቀረት ይችል ነበር፡፡ ነፋስና ማዕበልን የሚገስጽ ፈጣሪ እንዴት ዝም አለ ? እሳት ከሰማይ የሚያወርድ አምላክ ከዚህ በላይ በደል፣ ከዚህ በላይ ግፍ ምን አለና ታገሰ ? የፍቅርተን ሱሪ የወሰደው ንፋስ ከሆነም መገሰጽ ይችል ነበር፣ ስለምን ዝም አለ ? እንኳን አጋጣሚውን አገኘሁ እንጂ ፈጣሪ ጋርማ በፍቅርተ ጉዳይ ብዙ ጥያቄ አለኝ! ብዙ ! ሲጀመር ፍቅርተን ስለምን እንዲህ አድርጎ ፈጠራት…እኮ ለምን !? ለእሱስ ለስሙ ጥሩ ነው ??
“የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ነው” ይሉት ብሂል ስጋ ለብሶ የተገለጠው እማማ አመለ ቤት ነበር፡፡እማማ አመለ በመልክ ይሁን በባህሪ የማይገናኙ፣ ከፆታቸው በቀር አንድ የሚያደርጋቸው አንድ
ነገር እንኳን ፈልጎ ማግኘት የሚከብድ ሁለት ሴት ልጆች ያሏቸው፣ እድሜያቸው የገፋ ደግ ሴት ነበሩ ፡፡ ከሁለት ክፍል ቤታቸው አንዷን ተከራይቼ ለአራት ዓመታት ቤታቸው ውስጥ ኖሬያለሁ፡፡
👍26❤2🥰2🔥1
#ከሰሀራ_በታች
፡
፡
#ሁለት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ማንም ችኩል ቢለኝ ግድ አይሰጠኝም፡፡ ፋናን ገና ስመለከታት ልቤ ውስጥ የማይናወጥ የፍቅር ሐውልት ቆሟል፡፡ ማንም ብትሆን ግድ አይሰጠኝም፤ ቤት ውስጥ ምንሽር የታጠቀ፣ ጓንዴ ትራሱ ስር
ያስተኛ ባሏ ቢቀመጥ፣ ሰባት ልጆቿ “እማ እማ!” እያሉ የሚንጫጩ ሴት ብትሆንም ግድ የለኝም፡፡ፋናን አየኋት፣ ወደድኳት በቃ!! ይሄ ሁሉ ነገር የሆነው አንድ ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ እና ይሄን ሁሉ ሴኮንድ፣ ዘላለም የሚያህል ደቂቃ ፋናን አይቼ ባፈቅራት “ቸኮልክ” የሚለኝ ማነው?!.
ቤተሰቦቼ በየወሩ የሚልኩልኝ ብር ከዚህ የተሻለ ቤት እንድከራይ የሚያስችለኝ ቢሆንም ፋና
የምትባል የእግር ብረት ተጠናውታኝ በየት በኩል ! ቤቱ ለአንድ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ምኑም
የሚመች አልነበረም፡፡ ከእኔ ክፍል ኋላ የታወቀ ጠላ ቤት ነበር፤ ጫጫታው፣ ሁካታው፣ ዘፈኑ፡
ፀቡ ሁሉ ይረብሸኛል ፡፡ በሳምንት ሦስት ቀን !!
የጠላ ቤቱ ጩኸት ጋብ ሲል ኳስ የሚጫወቱ ልጆች ይተካሉ፡፡ ግድግዳየን በኳስ ሲነርቱት
የቤቴ ምርጊት አፈሩ በለጠፍኩት የግድግዳ መሸፈኛ ወረቀት ስር እየተንኮሻኮሻ ሲፈርስ
ይሰማኛል፡፡ ይህን ሁሉ ስችለው ደግሞ የጠላ ቤቱ አሻሮ ሲታመስ ፣ የጠላ ቂጣው ሲጋራ አአአሻሮ አሻሮ የሚሸትት እንኩሮ እንኩሮ የሚተነፍግ ጭስ ጠባብ ክፍሌን ይሞላታል፡፡
ይህ ሁሉ ችግር ግን ቤቱን እንድጠላው አላደረገኝም፡፡ ፋናን ስመለከት ጫጫታው የፍቅር
ሙዚቃ፣ ጭሱ ፍቅርን የሚያጥን
የገነት ከርቤ እስኪመስለኝ ይስማማኛል፡፡
እዚህ ቤት ውስጥ ለስድስት ወራት ስኖር ከፍቅርተ ጋር ተግባባን፤ እማማ አመለ ጋር የእናትና የልጅ ያህል ተቀራረብን፤ ከፋና ጋር ግን ከሰላምታ ውጭ አንዲት ቃል ተለዋውጠን አናውቅም። ፋና እዛው ተቀምጣ አንድ ቤት እየኖርን ትናፍቀኛለች ፤ አትናገር አትጋገር ! ዝም፡፡ ፋና
ቤት ውስጥ አለች ማለት ማንም ቤት ውስጥ የለም እንደማለት ነው፤ ዝምታ ይነግሳል፡፡ የፋናን
ድምፅ አንዳንዴ ለአራት ለአምስት ቀናት አልሰማውም፤ እዛው እያለች፡፡ አይገርምም ? እኔም
በቤተሰቦቼ “እሱ አይናገር አይጋገር ዝም ነው!” እየተባልኩ እሞካሽ ነበር፡፡ ጉዳቸውን ባዩ !
እዚህ ሞት የሚያስንቅ ዝምታ የሰፈረባት ጋግርታም ጋር በፍቅር ወድቄ አንድ ቃል ሲናፍቀኝ፡፡
የፋና ዝምተኝነት የጤና አልመስል ብሎኝ ነበር፡፡ እንጀራ እየበሉ ወጥ ሲያልቅባት እንኳን ወጥ
ጨምሩልኝ አትልም፡፡ ደግነቱ እናቷ እማማ አመለ ዓይናቸው ከፋና ላይ ስለማይነቀል ገና ወጡ
ሲያልቅባት በላይ በላዩ ይጨምሩላታል፡፡ ፋና በቀን ውስጥ የምትናገራቸው ቃላት ሲደመሩ
እህቷ ፍቅርተ በግማሽ ደቂቃ ከምታዘንበው ንግግር እሚበልጡ አይመስለኝም፡፡ ፍቅርተ ሙሉ
ቀን ስታወራ፣ ስትስቅ፣ ስትጫወት ነው የምትውለው፡፡ አንዳንዴ ፈገግታ የሚያጭርብኝ ነገር
ፋናና ፍቅርተ ሲያወሩ መስማት ነበር፡፡ ፍቅርተ ብቻዋን የምታወራ ነው የምትመስለው።ፋና አንድ ቃል አትመልስም፤ ፍቅርተም ብትሆን የእህቷን አመል ያወቀች ይመስል መልስ አትጠብቅም፤ ዝም ብላ ታወራለች ::
የፍቅርተን ወሬ መስማት አይሰለችም፡፡ እንደው ፍቅርተን መልኳን ሳይመለከት ድምጿን ብቻ
ያደመጠ ሰው በዓለም አንደኛዋ ቆንጆ ሴት እየተናገረች ሊመስለው ይችላል፡፡ በተለይ ሳቋ ! የፍቅርተ ውበት ግን ድምጿ ብቻ ነው:: “ስምን መልአክ ያወጣዋል” የሚባለው ብሂል እውነት
ከሆነ የፍቅርተን ስም ያወጣው መልዓክ ድምጿን ብቻ በሆነ መንገድ አድምጦ “ፍቅርተ” ብሎ
ሳይሰይማት አልቀረም፡፡
እማማ አመለወርቅ ብርቱ እናት ነበሩ፡፡ ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን ያሳደጉት ካለ አባት ነው፡፡
ዛፍ ቆራጭ የነበሩ ባለቤታቸው አንድ ቀን ዛፍ ሲቆርጡ የዛፉ ቅርንጫፍ የተላጠ ኤሌክትሪክ
መስመር ጋር የተነካካ ሆኖ በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወታቸው አለፈ፡፡ ያኔ ፋና የሶስት፣ ፍቅርተ
የሁለት ዓመት ሕፃናት ነበሩ፡፡ እነዚህን ሁለት ልጆች ለማሳደግ ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም፡፡
ያለፉበትን አሰቃቂ የድህነት መንገድ ተመልሰው ሲያስቡት ያንገሸግሻቸዋል፡፡ ታዲያ ከተቀራረብንና እኔም ከቤተሰቡ አባል እንደ አንድ ተቆጥሬ ገመናቸውን ተካፋይ ስሆን ማታ ማታ ቡና ተፈልቶ ታሪካቸውን ያወሩልኝ ነበር፡፡ እማማ አመለ ወሬ ይችላሉ፤ አሁን በሐዘን ዐይናችንን በእንባ ሞልተውት ድንገት ጣል በሚያደርጉት ቀልድ ለሐዘን የኳተረ እንባችን በሳቅ ይፈሳል፡፡
የማታ ቡና አብሬያቸው መጠጣት የጀመርኩበት ቀን ትዝ ይለኛል፡፡ በፊት ቡና ሲያፈሉ ፍቅርተ
መጋረጃዬን ገለጥ አድርጋ አንድ ስኒ ታቀብለኝና እጠጣለሁ፤ እጣኑም ቢሆን እየተጥመለመለ
መጋረጃዬን አልፎ ክፍሌ ይደርሳል ፡
“አብዬ” ይሉኛል እማማ አመለ ሲጠሩኝ እንዲህ ነው፤
“አቤት ማዘር !”
"ሁለተኛ ትጠጣለህ?”
“አይ ይበቃኛል ማዘር” እላለሁ፡፡ እየፈራሁ እንጂ ብጠጣ ደስ ይለኝ ነበር፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ቡናው ተፈልቶ፣ እጣኑ ቤቱን ሞልቶት፣ እኔም ነቃ ብዬ ፍቅርተ መጋረጃዬን
ገለጥ አድርጋ ቡናዬን እስክታቀብለኝ ስጠብቅ እማማ አመለ ጠሩኝ፡፡
“አብዬ !”
“አቤት ማዘር”
“እንደው ከሰውም አልተፈጠርክ ? ምናለ ወዲህ ወጣ ብለህ ብትጫወት፣…ጀበናውንም እያየህ ቡና ብትጠጣ፣ እኔም እናትህ ነኝ፣ እነፍቅርዬም እህቶችህ ናቸው” አሉኝ፡፡ ይሄ የመለአክት ጥሪ ነው !
ልብሴን ቀየርኩ፤ (ምርጥ የምላትን ልብስ ነው የለበስኩት፣ ከዚህች እዚች የመጋረጃ ድንበር ለማለፍ
ሽክ!!)፡፡ እናም መጋረጃዬን ገለጥ አድርጌ ብቅ አልኩ፤ ሁሉም በአክብሮት ተቀበሉኝ፡፡ የተዘጋጀችልኝ ኩርሲ ላይ ተቀመጥኩ ፡፡ እዩት እንግዲህ እግዜር ጨዋታውን ሲያሳምረው! ፋና ፊት ለፊቴ ነው የተቀመጠችው፡፡ ከዚህ በፊት ፊት ለፊቴ ተቀምጦ የሚያውቅ ውብ ነገር ምን ነበር?…ምንም !!
በእኔና በፋና መሃል የሲኒ ረከቦት፣ ሲኒዎቹ ስድስት ጨረቃ መስለው፣ ከረከቦቱ ጎን ማጨሻው
እንደ ደመና በቀስታ ሽቅብ ወደ ጠቆረው ጣራ፣ ከሚሳብ የእጣን ጭሱ ጋር፡፡ ከስሱ የእጣን
መጋረጃ ባሻገር ፋና አንገቷን ደፍታ መሬት መሬት እየተመለከተች ተቀምጣለች፡፡ አዲስ ሰው
ስለተቀላቀልኩ ጨንቋታል፡፡ አቤት እንዲህ ፊቷ ተቀምጠው በእጣኑ ጭስ ውስጥ ሲመለከቷት
“ምነው ባልነቃሁ” በሚባልበት እንቅልፍ ውስጥ የተከሰተች ጣፋጭ ህልም ነው የምትመስለው ፋና የኔ ውብ፡፡
ድህነትን አፈር ድሜ ያስጋጠ ውበት በዚህ ጭርንቁስ ቤት ውስጥ ፊት ለፊቴ በእጣን ደመና
ተከብቦ ተቀምጧል፤ እኔም ከእግር ጥፍር እስከራስ ፀጉር በሚነዝር በሚያስረቀርቅ ደስታ
ውስጥ ህያውና ዘላለማዊ ሥዕል ላደርጋት እያጠናኋት ነው ፡፡ነፍሱ በፍቅር ፍላፃ እንደተወጋች
አይደለም የሚያሳምረው፤ የተፈቃሪውን ነፍስ ይመለከታል፤ ነገን ይመለከታል፤ በዝምታ ውስጥ ያለ ሰላምን የሚቃኙ ዐይኖች ይታደላል፡፡ ከተከዘ ፊት ፈገግታን ያወጣል፡፡ እውነትን በዓይነ ህሊናው ይቃኛል! አፍቃሪ ሠዓሊ ነው!
ከዛን ቀን ጀምሮ ፋና ጋር በእጣን ጭስ መሃል መተያየት የዘወትር ተግባራችን ነበር፡፡ የእማማ
አመለ ጣፋጭ ወግ፣ የፍቅርተ የማያባራ ሳቅና ጨዋታ፣ የፋና የማይገሰስ ዝምታና የዝምታዋ
ውበት፣ የውበቷ ግዝፈት እንደ መንፊስ በቤቱ ውስጥ ያረብብ ነበር፡፡ ያችን የድህነት ጎጆ ሙሉ
ያደረገ መልካም ቤተሰባዊ ፍቅራችን ለአራት አመታት አብሮን ኑሯል፡፡
፡
፡
#ሁለት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
ማንም ችኩል ቢለኝ ግድ አይሰጠኝም፡፡ ፋናን ገና ስመለከታት ልቤ ውስጥ የማይናወጥ የፍቅር ሐውልት ቆሟል፡፡ ማንም ብትሆን ግድ አይሰጠኝም፤ ቤት ውስጥ ምንሽር የታጠቀ፣ ጓንዴ ትራሱ ስር
ያስተኛ ባሏ ቢቀመጥ፣ ሰባት ልጆቿ “እማ እማ!” እያሉ የሚንጫጩ ሴት ብትሆንም ግድ የለኝም፡፡ፋናን አየኋት፣ ወደድኳት በቃ!! ይሄ ሁሉ ነገር የሆነው አንድ ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ እና ይሄን ሁሉ ሴኮንድ፣ ዘላለም የሚያህል ደቂቃ ፋናን አይቼ ባፈቅራት “ቸኮልክ” የሚለኝ ማነው?!.
ቤተሰቦቼ በየወሩ የሚልኩልኝ ብር ከዚህ የተሻለ ቤት እንድከራይ የሚያስችለኝ ቢሆንም ፋና
የምትባል የእግር ብረት ተጠናውታኝ በየት በኩል ! ቤቱ ለአንድ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ምኑም
የሚመች አልነበረም፡፡ ከእኔ ክፍል ኋላ የታወቀ ጠላ ቤት ነበር፤ ጫጫታው፣ ሁካታው፣ ዘፈኑ፡
ፀቡ ሁሉ ይረብሸኛል ፡፡ በሳምንት ሦስት ቀን !!
የጠላ ቤቱ ጩኸት ጋብ ሲል ኳስ የሚጫወቱ ልጆች ይተካሉ፡፡ ግድግዳየን በኳስ ሲነርቱት
የቤቴ ምርጊት አፈሩ በለጠፍኩት የግድግዳ መሸፈኛ ወረቀት ስር እየተንኮሻኮሻ ሲፈርስ
ይሰማኛል፡፡ ይህን ሁሉ ስችለው ደግሞ የጠላ ቤቱ አሻሮ ሲታመስ ፣ የጠላ ቂጣው ሲጋራ አአአሻሮ አሻሮ የሚሸትት እንኩሮ እንኩሮ የሚተነፍግ ጭስ ጠባብ ክፍሌን ይሞላታል፡፡
ይህ ሁሉ ችግር ግን ቤቱን እንድጠላው አላደረገኝም፡፡ ፋናን ስመለከት ጫጫታው የፍቅር
ሙዚቃ፣ ጭሱ ፍቅርን የሚያጥን
የገነት ከርቤ እስኪመስለኝ ይስማማኛል፡፡
እዚህ ቤት ውስጥ ለስድስት ወራት ስኖር ከፍቅርተ ጋር ተግባባን፤ እማማ አመለ ጋር የእናትና የልጅ ያህል ተቀራረብን፤ ከፋና ጋር ግን ከሰላምታ ውጭ አንዲት ቃል ተለዋውጠን አናውቅም። ፋና እዛው ተቀምጣ አንድ ቤት እየኖርን ትናፍቀኛለች ፤ አትናገር አትጋገር ! ዝም፡፡ ፋና
ቤት ውስጥ አለች ማለት ማንም ቤት ውስጥ የለም እንደማለት ነው፤ ዝምታ ይነግሳል፡፡ የፋናን
ድምፅ አንዳንዴ ለአራት ለአምስት ቀናት አልሰማውም፤ እዛው እያለች፡፡ አይገርምም ? እኔም
በቤተሰቦቼ “እሱ አይናገር አይጋገር ዝም ነው!” እየተባልኩ እሞካሽ ነበር፡፡ ጉዳቸውን ባዩ !
እዚህ ሞት የሚያስንቅ ዝምታ የሰፈረባት ጋግርታም ጋር በፍቅር ወድቄ አንድ ቃል ሲናፍቀኝ፡፡
የፋና ዝምተኝነት የጤና አልመስል ብሎኝ ነበር፡፡ እንጀራ እየበሉ ወጥ ሲያልቅባት እንኳን ወጥ
ጨምሩልኝ አትልም፡፡ ደግነቱ እናቷ እማማ አመለ ዓይናቸው ከፋና ላይ ስለማይነቀል ገና ወጡ
ሲያልቅባት በላይ በላዩ ይጨምሩላታል፡፡ ፋና በቀን ውስጥ የምትናገራቸው ቃላት ሲደመሩ
እህቷ ፍቅርተ በግማሽ ደቂቃ ከምታዘንበው ንግግር እሚበልጡ አይመስለኝም፡፡ ፍቅርተ ሙሉ
ቀን ስታወራ፣ ስትስቅ፣ ስትጫወት ነው የምትውለው፡፡ አንዳንዴ ፈገግታ የሚያጭርብኝ ነገር
ፋናና ፍቅርተ ሲያወሩ መስማት ነበር፡፡ ፍቅርተ ብቻዋን የምታወራ ነው የምትመስለው።ፋና አንድ ቃል አትመልስም፤ ፍቅርተም ብትሆን የእህቷን አመል ያወቀች ይመስል መልስ አትጠብቅም፤ ዝም ብላ ታወራለች ::
የፍቅርተን ወሬ መስማት አይሰለችም፡፡ እንደው ፍቅርተን መልኳን ሳይመለከት ድምጿን ብቻ
ያደመጠ ሰው በዓለም አንደኛዋ ቆንጆ ሴት እየተናገረች ሊመስለው ይችላል፡፡ በተለይ ሳቋ ! የፍቅርተ ውበት ግን ድምጿ ብቻ ነው:: “ስምን መልአክ ያወጣዋል” የሚባለው ብሂል እውነት
ከሆነ የፍቅርተን ስም ያወጣው መልዓክ ድምጿን ብቻ በሆነ መንገድ አድምጦ “ፍቅርተ” ብሎ
ሳይሰይማት አልቀረም፡፡
እማማ አመለወርቅ ብርቱ እናት ነበሩ፡፡ ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን ያሳደጉት ካለ አባት ነው፡፡
ዛፍ ቆራጭ የነበሩ ባለቤታቸው አንድ ቀን ዛፍ ሲቆርጡ የዛፉ ቅርንጫፍ የተላጠ ኤሌክትሪክ
መስመር ጋር የተነካካ ሆኖ በአሰቃቂ ሁኔታ ሕይወታቸው አለፈ፡፡ ያኔ ፋና የሶስት፣ ፍቅርተ
የሁለት ዓመት ሕፃናት ነበሩ፡፡ እነዚህን ሁለት ልጆች ለማሳደግ ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም፡፡
ያለፉበትን አሰቃቂ የድህነት መንገድ ተመልሰው ሲያስቡት ያንገሸግሻቸዋል፡፡ ታዲያ ከተቀራረብንና እኔም ከቤተሰቡ አባል እንደ አንድ ተቆጥሬ ገመናቸውን ተካፋይ ስሆን ማታ ማታ ቡና ተፈልቶ ታሪካቸውን ያወሩልኝ ነበር፡፡ እማማ አመለ ወሬ ይችላሉ፤ አሁን በሐዘን ዐይናችንን በእንባ ሞልተውት ድንገት ጣል በሚያደርጉት ቀልድ ለሐዘን የኳተረ እንባችን በሳቅ ይፈሳል፡፡
የማታ ቡና አብሬያቸው መጠጣት የጀመርኩበት ቀን ትዝ ይለኛል፡፡ በፊት ቡና ሲያፈሉ ፍቅርተ
መጋረጃዬን ገለጥ አድርጋ አንድ ስኒ ታቀብለኝና እጠጣለሁ፤ እጣኑም ቢሆን እየተጥመለመለ
መጋረጃዬን አልፎ ክፍሌ ይደርሳል ፡
“አብዬ” ይሉኛል እማማ አመለ ሲጠሩኝ እንዲህ ነው፤
“አቤት ማዘር !”
"ሁለተኛ ትጠጣለህ?”
“አይ ይበቃኛል ማዘር” እላለሁ፡፡ እየፈራሁ እንጂ ብጠጣ ደስ ይለኝ ነበር፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ቡናው ተፈልቶ፣ እጣኑ ቤቱን ሞልቶት፣ እኔም ነቃ ብዬ ፍቅርተ መጋረጃዬን
ገለጥ አድርጋ ቡናዬን እስክታቀብለኝ ስጠብቅ እማማ አመለ ጠሩኝ፡፡
“አብዬ !”
“አቤት ማዘር”
“እንደው ከሰውም አልተፈጠርክ ? ምናለ ወዲህ ወጣ ብለህ ብትጫወት፣…ጀበናውንም እያየህ ቡና ብትጠጣ፣ እኔም እናትህ ነኝ፣ እነፍቅርዬም እህቶችህ ናቸው” አሉኝ፡፡ ይሄ የመለአክት ጥሪ ነው !
ልብሴን ቀየርኩ፤ (ምርጥ የምላትን ልብስ ነው የለበስኩት፣ ከዚህች እዚች የመጋረጃ ድንበር ለማለፍ
ሽክ!!)፡፡ እናም መጋረጃዬን ገለጥ አድርጌ ብቅ አልኩ፤ ሁሉም በአክብሮት ተቀበሉኝ፡፡ የተዘጋጀችልኝ ኩርሲ ላይ ተቀመጥኩ ፡፡ እዩት እንግዲህ እግዜር ጨዋታውን ሲያሳምረው! ፋና ፊት ለፊቴ ነው የተቀመጠችው፡፡ ከዚህ በፊት ፊት ለፊቴ ተቀምጦ የሚያውቅ ውብ ነገር ምን ነበር?…ምንም !!
በእኔና በፋና መሃል የሲኒ ረከቦት፣ ሲኒዎቹ ስድስት ጨረቃ መስለው፣ ከረከቦቱ ጎን ማጨሻው
እንደ ደመና በቀስታ ሽቅብ ወደ ጠቆረው ጣራ፣ ከሚሳብ የእጣን ጭሱ ጋር፡፡ ከስሱ የእጣን
መጋረጃ ባሻገር ፋና አንገቷን ደፍታ መሬት መሬት እየተመለከተች ተቀምጣለች፡፡ አዲስ ሰው
ስለተቀላቀልኩ ጨንቋታል፡፡ አቤት እንዲህ ፊቷ ተቀምጠው በእጣኑ ጭስ ውስጥ ሲመለከቷት
“ምነው ባልነቃሁ” በሚባልበት እንቅልፍ ውስጥ የተከሰተች ጣፋጭ ህልም ነው የምትመስለው ፋና የኔ ውብ፡፡
ድህነትን አፈር ድሜ ያስጋጠ ውበት በዚህ ጭርንቁስ ቤት ውስጥ ፊት ለፊቴ በእጣን ደመና
ተከብቦ ተቀምጧል፤ እኔም ከእግር ጥፍር እስከራስ ፀጉር በሚነዝር በሚያስረቀርቅ ደስታ
ውስጥ ህያውና ዘላለማዊ ሥዕል ላደርጋት እያጠናኋት ነው ፡፡ነፍሱ በፍቅር ፍላፃ እንደተወጋች
አይደለም የሚያሳምረው፤ የተፈቃሪውን ነፍስ ይመለከታል፤ ነገን ይመለከታል፤ በዝምታ ውስጥ ያለ ሰላምን የሚቃኙ ዐይኖች ይታደላል፡፡ ከተከዘ ፊት ፈገግታን ያወጣል፡፡ እውነትን በዓይነ ህሊናው ይቃኛል! አፍቃሪ ሠዓሊ ነው!
ከዛን ቀን ጀምሮ ፋና ጋር በእጣን ጭስ መሃል መተያየት የዘወትር ተግባራችን ነበር፡፡ የእማማ
አመለ ጣፋጭ ወግ፣ የፍቅርተ የማያባራ ሳቅና ጨዋታ፣ የፋና የማይገሰስ ዝምታና የዝምታዋ
ውበት፣ የውበቷ ግዝፈት እንደ መንፊስ በቤቱ ውስጥ ያረብብ ነበር፡፡ ያችን የድህነት ጎጆ ሙሉ
ያደረገ መልካም ቤተሰባዊ ፍቅራችን ለአራት አመታት አብሮን ኑሯል፡፡
👍27❤4🥰4👎1
#ከሰሀራ_በታች
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
....ፋና ጋር መቀራረብ በጣም ከባድ ነበረ፡፡ አንዳንዴ ባህሪዋ ያበሳጨኛል፡፡ “ምናይነት የደነዘዘች ልጅ ናት” እልና ለራሴ ቁጣ ቁጣ ይለኛል፡፡ ለምን እንደ ፍቅርተ አታናግረኝም ? ሌላው ቢቀር አንድ ዓመት ሙሉ እዚህ ቤት ስኖር ቤቴን እንኳን ተሳስታ ረግጣው አታውቅም፡፡ ፍቅርተ እኮ
እናት ማለት ናት፡፡ ረፍዶብኝ ፍራሼን ሳላነጣጥፍ ከወጣሁ ፍራሼን አነጣጥፋ፣ ያዝረከረኩትን
ወረቀት አስተካክላ የሚጠጣ ውሃ ቀድታ አስቀምጣልኝ ነው የማገኘው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
ደግሞ ምግቤንም የምትሰራልኝ ፍቅርተ ናት፡፡ እች ፋና የሚሏት ዝግ ግን…ዝምታዋ ሰልችቶኝ
ነበር፡፡
የሆነ ጊዜ ታዲያ ድንገት ታመምኩ፡፡ ለሳምንት ትምህርት ቤት አልሄድኩም፤ ፍቅርተና እማማ
አመለ ተጨንቀው ሲሯሯጡ ሰነበቱ፡፡ ፋና ዝርም ብላ አታውቅም፡፡ ከዛን ጊዜ በኋላ የፉና ነገር በቃኝ፡፡ “እግዜር ይግደልህ !” ማንን ገደለ? አንድ ቀን ሳትጠይቀኝ በቃ ድኜ ተነሳሁ፡፡
ፋና የምትባል ልጅ በቃ በቃችኝ፡፡ ሳልፍ ሳገድም እወረውርላት የነበረውን ሰላምታዬን እኔም
አቆምኩ፡፡ ስገባ ብቻዋን ተቀምጣ ባገኛት እንኳን ሰላም አልላትም፡፡ እንደውም ከብስጭቴ
ብዛት ቤት ለመቀየር አሰብኩ፡፡ ግን ለእማማ አመለ ምን ሰበብ እንደማቀርብ ጨነቀኝ፡፡ ከእኔ
ከሚያገኟት የኪራይ ብር በላይ ለእኔ ያላቸው ቤተሰባዊ ፍቅር ቦታ አለው፤ ለእርሳቸው::ደግሞም ብቸኛ መተዳደሪያቸው ከእኔ የሚያገኟት የኪራይ ብር ነበረች፡፡ ምን ሆንኩ ብዬ ቤት ልውጣአ ? እች ጉልት ስወጣ ስገባ እንደ ግኡዝ ነገር ተጎልታ ማየቴ ያበሳጨኛል፡፡ ማታ ማታ ቡና ሲጠሩኝ በህመሜ አሳብቤ ልቀር ብሞክርም አልተሳካም፡፡
“ቡና ባትጠጣ እንኳን ና እና ተጫወት፤ በሽታውም ለብቻ ሲሆኑ ነው የሚጠናው” አሉኝ
እማማ አመለ፡፡ ጨዋታው እንደወትሮው አልጥምህ አለኝ፤ እጣኑ ከነከነኝ፤ ከእጣኑ ወዲያ
አቀርቅራ የምትቀመጠው ፋና ሰለቸችኝ፡፡ እወዳታለሁ፤ ግን ግኡዝ ናት በቃ ! ወይስ ከራሷ
ውበት ጋር በፍቅር ወድቃ ዓለምን ረስታለች ? ምናይነት ድንዛዜ ነው ይሄ ?
!
ፍቅርተ ጋር ቅርርባችን ተጠናክሮ ነበር፡፡ ማታ ማታ ቡናው እስከሚፈላ ደብተሯን ይዛ
ወደ ክፍሌ ትመጣለች፡፡ ግን አታጠናም፤ ቤታቸው ውስጥ ቴፕ ስለሌለ ሁልጊዜ የደብተሯ
ቦርሳ ውስጥ የምታኖረውን የአስቴርን ካሴት ይዛ ትመጣና በእኔ ቴፕ ታዳምጣለች፡፡ ግጥሙን
ሸምድዳዋለች፤ ጀምሮ እስኪጨርስ በቃሏ ትወጣዋለች፡፡ ሙዚቃውን እንደ ሙዚቃ ሳይሆን
እንደ መርዶ ነበር ፊቷን አጨፍግጋ የምታዳምጠው፡፡ አንድ ቀን ሙዚቃውን እያዳመጠች
እንባዋ በጉንጫ ላይ ኮለል ብሎ ወረደ፤
“ምን ሆንሽ ፍቅርተ” አልኳት ደንግጬ፤
“ምንም” ብላ ተነስታ ከክፍሌ ወጣች፡፡ከዛን ቀን ጀምሮ ፍቅርተ የወትሮዋ አልነበረችም፤ የሌላትን
አመል መነጫነጭ ጀመረች፡፡ ከመሬት ተነስታ ታለቅሳለች፤ በትንሽ ነገር ይከፋታል፡፡ ከወራት
ልመና በኋላ ጭንቋን ተነፈሰችው፤ ፍቅርተ ፍቅር ይዟት ነበር፡፡ ፍቅር እንደያዛት ስትነግረኝ
“እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፣ የነገስታት ንጉስ፣ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ ኃያል! እባክህ ይህች ልጅ
ፍቅር የያዛት ከእኔ እንዳይሆን እርዳኝ” ብዬ ፀለይኩ፡፡
“ከስምንተኛ ክፍል ጀምሮ አብረን አንድ ክፍል ነው የተማርነው፤ ቶማስ ይባላል” ስትለኝ ሃሌሉያ!”
ብዬ ልጮኽ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ ኡፍፍፍፍፍፍ ! አሁን እዳው ገብስ ነው ! ተረጋግቼ አዳምጣት
ጀመር፡፡ የከፍሎቿ ልጆች ተሰባስበው የተነሱትን አንድ ፎቶ እየሰጠችኝ ልጁን ጠቆመችኝ፤
ሲበዛ ቆንጆ ልጅ ነበር፡፡ ከግራና ቀኙ ሁለት ቆነጃጅት እንደ መዥገር ተጣብቀውበታል፡፡
“አንቺ የታለሽ ታዲያ!” አልኳት፤
“እኔ ፎቶ መነሳት አልወድም” አለችኝ ትክዝ ብላ፡፡ ለምን ብዬ አልጠየቅኳትም፡፡
“ከወደድሽው ስንት ጊዜ ሆነሽ?” አልኳት ፎቶውን እያየሁ፤
“እኔንጃ ግን ቆይቷል ፤ ሶስት አመት”
“እና ሦሰት ዓመት ሙሉ ስታፈቅሪው እርሱ ምን አለ ?”
“አያውቅም፡፡”
“ተነጋግራችሁ አታውቁም”
“አንድ ቀን አናግሮኛል…”
“እና ምን አለሽ?” አልኳት በጉጉት፡፡
“እርሳስ አጥቼ ስጠይቅ ሰጠኝ…ስመልስለት 'ውሰጂው! አለኝ” አለችና እዛኛው ክፍል ሄዳ አንድ
ቢጫ እርሳስ ይዛ ተመለሰች፡፡ እንደ ትልቅ ቅርስ በፍቅር እርሳሱን እየተመለከተች…፣ “አየኸው
የእሱ ነው” አለችኝ፡፡ ፊቷ ላይ የነበረው ደስታ… ናፍቆት…ፍቅር ያሳዝን ነበር፡፡ ትቀጥላለች
ብዬ ጠበቅኳት፡፡ የተነጋገሩት ግን እችኑ ነበር፡፡ አንድ ቃል “ውሰጅው” አላት፤ በቃ፡፡ ይሄ ቃል ለፍቅርተ “ንግግር” ነበር፡፡
“ለምን አታናግሪውም ታዲያ ? በቀጥታ መናገር እንኳን ባትችይ በሆነ መንገድ እንደወደድሽው
አሳውቂው፡፡ እሱም ሊወድሽ ይችላል” አልኳት እንደው ለማፅናናት እንጂ ያልኩትን ለራሴም አላመንኩበትም፡፡ ይሄ ልጅ ፍቅርተን ቢወዳት በሺ ዓመት አንድ ጊዜ የሚከሰት አጋጣሚ
አድርጌ ላየው ሁሉ እችላለሁ፡፡
በድንጋጤ አፍጥጣ እያየችኝ፣ “ትቀልዳለህ ?” አለችኝና አፏን በሁለት እጆቿ አፍና እንደዘገነነው
ሰው ሰውነቷ ተንዘረዘረ፤
“በጣም የሃብታም ልጅ ነው፤ በዛ ላይ ክላሳችን ውስጥ ካሉ ሰላሳ ሴቶች ግማሹ በሱ ፍቅር ያበዱ
ናቸው፡፡ በእረፍት ሰዓት ጎታቹ ብዙ ነው፤ በዚያ ላይ ጎበዝ ተማሪ፤ ኤጭ” ብላ በምሬት ፊቷ
አጨፈገገች፡፡ ዝም ብዬ አየኋት፤ ፍቅርተ ይበልጥ በቀረቧት ቁጥር ይበልጥ መልከጥፉ የምትሆን
ሚስኪን ነበረች፡፡ በቦዙ አይኖቿ ባዶውን እየተመለከተች ምሬቷን አምበለበለችው፡፡ የሆነ ነገር
ያስፈልግሃል፡ ለመፈቀር አንድ የሆነ ነገር ያስፈልግሃል፣ መልክ ወይም ሃብት…ብቻ የሆነ ነገር
እኔ ደግሞ ምንም የለኝም፤ መልክ የለኝ፣ ሃብት የለኝ፣ በትምህርት እንኳን እንዳላካክሰው እንደ ትምህርት የሚያስጠላኝ ነገር የለም እማማ እንዳይከፋት ነው የምማረው ቸኮኛል ከቤት
ባልወጣ ደስታዬ ነው፡ ማንንም ባላይ፡ ማንም ሳያየኝ ደስታዬ ነው አለችና እንባዋ ይፈስ ጀመር
“ፍቅርተ ለፍቅር ሃብት ፣ መልከ ምናምን ሲያስፈልግ ኖሮ እኮ አታፈቅሪም ነበር” አልኳት፡፡
ከአፌ ነጥቃ በቁጣ መናገር ጀመረች፡፡ንግግሯ በምሬት የተሞላ ነበር፡፡ “እንኳን ለፍቅር ለተራ
ሰላምታም ሀብት ያስፈልጋል ፡፡መልክ ያስፈልጋል ፡፡ አንተ አስቀያሚ ወጣት ሆነህ ታውቃለህ ? አስቀያሚ ሴት ሆነህስ ታውቃለህ ? ህመሙ አይገባህም፡፡አብርሽ መገፋቱ ስሜት አይሰጥህም….እየውልህ እንኳን አሁን ሕፃን ሆነን እኔና ፋና መንገድ ላይ ስንሄድ ያገኘን ሁሉ ፋናን አገላብጦ ጉንጯን ይስምና እኔን…” መጨረስ አልቻለችም እንባዋ ቀደማት፡፡
“አስራ ስምንት ዓመት አልፎኛል፡፡ እስካሁን አንድ ወንድ እንኳን ጠይቆኝ አያውቅም፡፡አንዳንዴ እንዴት እንደተፋቀሩ ይቅርና ያፈቀሩት ጋር እንዴት እንደተጣሉ ሴቶች ሲያወሩ እቀናለሁ..ከፍቅረኛ ጋር መጣላት በራሱ ያስቀናል፤ ይናፍቅሃል፤ ሰው ሆነህ በፍቅር መጋጨትህ ለራሱ ከሰው እኩል ያደርግሃል፡፡ የሚጣላህም የሚወድህም በሌለበት ዓለም መኖር ካለመኖር እኩል ነው” ፍቅርተ ባንዴ ተቀየረችብኝ፤ አስፈሪ ሆነችብኝ፡፡ ንፍጧ በአፍንጫዋ ተዝረከረከ፤
እንባዋ ፊቷን አጨቀየው፤ አስቀያሚነቷ ሙሉ ሆነ፡፡ ስታሳዝን!
“አስራ ስምንት ዓመት እኮ ትንሽ እድሜ ነው…ገና ነሽ ወደፊት የሚያፈቅርሽ የራስሽ ሰው
ይመጣል” አልኳት ልክ የሚያፈቅራትን ሰው የቀጠርኩት ይመስል በእርግጠኝነት፡፡ ግን ውስጤ መቼም ቢሆን ፍቅርተን የሚያፈቅር ሰው በምድር ላይ የሚፈጠር አይመስለውም፤ እናገራለሁ፤ግን የምለውን እኔም አላምንበትም፡፡
፡
፡
#ሶስት
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
....ፋና ጋር መቀራረብ በጣም ከባድ ነበረ፡፡ አንዳንዴ ባህሪዋ ያበሳጨኛል፡፡ “ምናይነት የደነዘዘች ልጅ ናት” እልና ለራሴ ቁጣ ቁጣ ይለኛል፡፡ ለምን እንደ ፍቅርተ አታናግረኝም ? ሌላው ቢቀር አንድ ዓመት ሙሉ እዚህ ቤት ስኖር ቤቴን እንኳን ተሳስታ ረግጣው አታውቅም፡፡ ፍቅርተ እኮ
እናት ማለት ናት፡፡ ረፍዶብኝ ፍራሼን ሳላነጣጥፍ ከወጣሁ ፍራሼን አነጣጥፋ፣ ያዝረከረኩትን
ወረቀት አስተካክላ የሚጠጣ ውሃ ቀድታ አስቀምጣልኝ ነው የማገኘው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ
ደግሞ ምግቤንም የምትሰራልኝ ፍቅርተ ናት፡፡ እች ፋና የሚሏት ዝግ ግን…ዝምታዋ ሰልችቶኝ
ነበር፡፡
የሆነ ጊዜ ታዲያ ድንገት ታመምኩ፡፡ ለሳምንት ትምህርት ቤት አልሄድኩም፤ ፍቅርተና እማማ
አመለ ተጨንቀው ሲሯሯጡ ሰነበቱ፡፡ ፋና ዝርም ብላ አታውቅም፡፡ ከዛን ጊዜ በኋላ የፉና ነገር በቃኝ፡፡ “እግዜር ይግደልህ !” ማንን ገደለ? አንድ ቀን ሳትጠይቀኝ በቃ ድኜ ተነሳሁ፡፡
ፋና የምትባል ልጅ በቃ በቃችኝ፡፡ ሳልፍ ሳገድም እወረውርላት የነበረውን ሰላምታዬን እኔም
አቆምኩ፡፡ ስገባ ብቻዋን ተቀምጣ ባገኛት እንኳን ሰላም አልላትም፡፡ እንደውም ከብስጭቴ
ብዛት ቤት ለመቀየር አሰብኩ፡፡ ግን ለእማማ አመለ ምን ሰበብ እንደማቀርብ ጨነቀኝ፡፡ ከእኔ
ከሚያገኟት የኪራይ ብር በላይ ለእኔ ያላቸው ቤተሰባዊ ፍቅር ቦታ አለው፤ ለእርሳቸው::ደግሞም ብቸኛ መተዳደሪያቸው ከእኔ የሚያገኟት የኪራይ ብር ነበረች፡፡ ምን ሆንኩ ብዬ ቤት ልውጣአ ? እች ጉልት ስወጣ ስገባ እንደ ግኡዝ ነገር ተጎልታ ማየቴ ያበሳጨኛል፡፡ ማታ ማታ ቡና ሲጠሩኝ በህመሜ አሳብቤ ልቀር ብሞክርም አልተሳካም፡፡
“ቡና ባትጠጣ እንኳን ና እና ተጫወት፤ በሽታውም ለብቻ ሲሆኑ ነው የሚጠናው” አሉኝ
እማማ አመለ፡፡ ጨዋታው እንደወትሮው አልጥምህ አለኝ፤ እጣኑ ከነከነኝ፤ ከእጣኑ ወዲያ
አቀርቅራ የምትቀመጠው ፋና ሰለቸችኝ፡፡ እወዳታለሁ፤ ግን ግኡዝ ናት በቃ ! ወይስ ከራሷ
ውበት ጋር በፍቅር ወድቃ ዓለምን ረስታለች ? ምናይነት ድንዛዜ ነው ይሄ ?
!
ፍቅርተ ጋር ቅርርባችን ተጠናክሮ ነበር፡፡ ማታ ማታ ቡናው እስከሚፈላ ደብተሯን ይዛ
ወደ ክፍሌ ትመጣለች፡፡ ግን አታጠናም፤ ቤታቸው ውስጥ ቴፕ ስለሌለ ሁልጊዜ የደብተሯ
ቦርሳ ውስጥ የምታኖረውን የአስቴርን ካሴት ይዛ ትመጣና በእኔ ቴፕ ታዳምጣለች፡፡ ግጥሙን
ሸምድዳዋለች፤ ጀምሮ እስኪጨርስ በቃሏ ትወጣዋለች፡፡ ሙዚቃውን እንደ ሙዚቃ ሳይሆን
እንደ መርዶ ነበር ፊቷን አጨፍግጋ የምታዳምጠው፡፡ አንድ ቀን ሙዚቃውን እያዳመጠች
እንባዋ በጉንጫ ላይ ኮለል ብሎ ወረደ፤
“ምን ሆንሽ ፍቅርተ” አልኳት ደንግጬ፤
“ምንም” ብላ ተነስታ ከክፍሌ ወጣች፡፡ከዛን ቀን ጀምሮ ፍቅርተ የወትሮዋ አልነበረችም፤ የሌላትን
አመል መነጫነጭ ጀመረች፡፡ ከመሬት ተነስታ ታለቅሳለች፤ በትንሽ ነገር ይከፋታል፡፡ ከወራት
ልመና በኋላ ጭንቋን ተነፈሰችው፤ ፍቅርተ ፍቅር ይዟት ነበር፡፡ ፍቅር እንደያዛት ስትነግረኝ
“እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፣ የነገስታት ንጉስ፣ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ ኃያል! እባክህ ይህች ልጅ
ፍቅር የያዛት ከእኔ እንዳይሆን እርዳኝ” ብዬ ፀለይኩ፡፡
“ከስምንተኛ ክፍል ጀምሮ አብረን አንድ ክፍል ነው የተማርነው፤ ቶማስ ይባላል” ስትለኝ ሃሌሉያ!”
ብዬ ልጮኽ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ ኡፍፍፍፍፍፍ ! አሁን እዳው ገብስ ነው ! ተረጋግቼ አዳምጣት
ጀመር፡፡ የከፍሎቿ ልጆች ተሰባስበው የተነሱትን አንድ ፎቶ እየሰጠችኝ ልጁን ጠቆመችኝ፤
ሲበዛ ቆንጆ ልጅ ነበር፡፡ ከግራና ቀኙ ሁለት ቆነጃጅት እንደ መዥገር ተጣብቀውበታል፡፡
“አንቺ የታለሽ ታዲያ!” አልኳት፤
“እኔ ፎቶ መነሳት አልወድም” አለችኝ ትክዝ ብላ፡፡ ለምን ብዬ አልጠየቅኳትም፡፡
“ከወደድሽው ስንት ጊዜ ሆነሽ?” አልኳት ፎቶውን እያየሁ፤
“እኔንጃ ግን ቆይቷል ፤ ሶስት አመት”
“እና ሦሰት ዓመት ሙሉ ስታፈቅሪው እርሱ ምን አለ ?”
“አያውቅም፡፡”
“ተነጋግራችሁ አታውቁም”
“አንድ ቀን አናግሮኛል…”
“እና ምን አለሽ?” አልኳት በጉጉት፡፡
“እርሳስ አጥቼ ስጠይቅ ሰጠኝ…ስመልስለት 'ውሰጂው! አለኝ” አለችና እዛኛው ክፍል ሄዳ አንድ
ቢጫ እርሳስ ይዛ ተመለሰች፡፡ እንደ ትልቅ ቅርስ በፍቅር እርሳሱን እየተመለከተች…፣ “አየኸው
የእሱ ነው” አለችኝ፡፡ ፊቷ ላይ የነበረው ደስታ… ናፍቆት…ፍቅር ያሳዝን ነበር፡፡ ትቀጥላለች
ብዬ ጠበቅኳት፡፡ የተነጋገሩት ግን እችኑ ነበር፡፡ አንድ ቃል “ውሰጅው” አላት፤ በቃ፡፡ ይሄ ቃል ለፍቅርተ “ንግግር” ነበር፡፡
“ለምን አታናግሪውም ታዲያ ? በቀጥታ መናገር እንኳን ባትችይ በሆነ መንገድ እንደወደድሽው
አሳውቂው፡፡ እሱም ሊወድሽ ይችላል” አልኳት እንደው ለማፅናናት እንጂ ያልኩትን ለራሴም አላመንኩበትም፡፡ ይሄ ልጅ ፍቅርተን ቢወዳት በሺ ዓመት አንድ ጊዜ የሚከሰት አጋጣሚ
አድርጌ ላየው ሁሉ እችላለሁ፡፡
በድንጋጤ አፍጥጣ እያየችኝ፣ “ትቀልዳለህ ?” አለችኝና አፏን በሁለት እጆቿ አፍና እንደዘገነነው
ሰው ሰውነቷ ተንዘረዘረ፤
“በጣም የሃብታም ልጅ ነው፤ በዛ ላይ ክላሳችን ውስጥ ካሉ ሰላሳ ሴቶች ግማሹ በሱ ፍቅር ያበዱ
ናቸው፡፡ በእረፍት ሰዓት ጎታቹ ብዙ ነው፤ በዚያ ላይ ጎበዝ ተማሪ፤ ኤጭ” ብላ በምሬት ፊቷ
አጨፈገገች፡፡ ዝም ብዬ አየኋት፤ ፍቅርተ ይበልጥ በቀረቧት ቁጥር ይበልጥ መልከጥፉ የምትሆን
ሚስኪን ነበረች፡፡ በቦዙ አይኖቿ ባዶውን እየተመለከተች ምሬቷን አምበለበለችው፡፡ የሆነ ነገር
ያስፈልግሃል፡ ለመፈቀር አንድ የሆነ ነገር ያስፈልግሃል፣ መልክ ወይም ሃብት…ብቻ የሆነ ነገር
እኔ ደግሞ ምንም የለኝም፤ መልክ የለኝ፣ ሃብት የለኝ፣ በትምህርት እንኳን እንዳላካክሰው እንደ ትምህርት የሚያስጠላኝ ነገር የለም እማማ እንዳይከፋት ነው የምማረው ቸኮኛል ከቤት
ባልወጣ ደስታዬ ነው፡ ማንንም ባላይ፡ ማንም ሳያየኝ ደስታዬ ነው አለችና እንባዋ ይፈስ ጀመር
“ፍቅርተ ለፍቅር ሃብት ፣ መልከ ምናምን ሲያስፈልግ ኖሮ እኮ አታፈቅሪም ነበር” አልኳት፡፡
ከአፌ ነጥቃ በቁጣ መናገር ጀመረች፡፡ንግግሯ በምሬት የተሞላ ነበር፡፡ “እንኳን ለፍቅር ለተራ
ሰላምታም ሀብት ያስፈልጋል ፡፡መልክ ያስፈልጋል ፡፡ አንተ አስቀያሚ ወጣት ሆነህ ታውቃለህ ? አስቀያሚ ሴት ሆነህስ ታውቃለህ ? ህመሙ አይገባህም፡፡አብርሽ መገፋቱ ስሜት አይሰጥህም….እየውልህ እንኳን አሁን ሕፃን ሆነን እኔና ፋና መንገድ ላይ ስንሄድ ያገኘን ሁሉ ፋናን አገላብጦ ጉንጯን ይስምና እኔን…” መጨረስ አልቻለችም እንባዋ ቀደማት፡፡
“አስራ ስምንት ዓመት አልፎኛል፡፡ እስካሁን አንድ ወንድ እንኳን ጠይቆኝ አያውቅም፡፡አንዳንዴ እንዴት እንደተፋቀሩ ይቅርና ያፈቀሩት ጋር እንዴት እንደተጣሉ ሴቶች ሲያወሩ እቀናለሁ..ከፍቅረኛ ጋር መጣላት በራሱ ያስቀናል፤ ይናፍቅሃል፤ ሰው ሆነህ በፍቅር መጋጨትህ ለራሱ ከሰው እኩል ያደርግሃል፡፡ የሚጣላህም የሚወድህም በሌለበት ዓለም መኖር ካለመኖር እኩል ነው” ፍቅርተ ባንዴ ተቀየረችብኝ፤ አስፈሪ ሆነችብኝ፡፡ ንፍጧ በአፍንጫዋ ተዝረከረከ፤
እንባዋ ፊቷን አጨቀየው፤ አስቀያሚነቷ ሙሉ ሆነ፡፡ ስታሳዝን!
“አስራ ስምንት ዓመት እኮ ትንሽ እድሜ ነው…ገና ነሽ ወደፊት የሚያፈቅርሽ የራስሽ ሰው
ይመጣል” አልኳት ልክ የሚያፈቅራትን ሰው የቀጠርኩት ይመስል በእርግጠኝነት፡፡ ግን ውስጤ መቼም ቢሆን ፍቅርተን የሚያፈቅር ሰው በምድር ላይ የሚፈጠር አይመስለውም፤ እናገራለሁ፤ግን የምለውን እኔም አላምንበትም፡፡
👍28
#ከሰሀራ_በታች
፡
፡
#አራት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከፋና ጋር ከተሳሳምንባት ቅዳሜ በኋላ ዋና ስራችን የእማማ አመለ እና የፍቅርተ እግር
ሲወጣ መጠበቅ ሆነ..በቃ ወጣ ሲሉ ፋና ወደ ክፍሌ ሮጣ ትመጣና እቅፌ ላይ ናት፣ከንፈሮቻችን እንዳይገናኙ ማድረግ ከሁለታችንም አቅም በላይ ነበር፡፡ በፍቅር ሰከርን፤አንዳንዴ እማማ አመለ ቤት ውስጥ ሆነውም ፋና ተነስታ ወደ ክፍሌ ትገባለች፣“አብርሽ ስራ ይዘሃል እንዴ?” ትላለች፡፡እማማ አመለ ከትምህርት ጋር የተያያዘ ነገር አድርገው ስለሚያስቡት በጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ፋኒ ወደ ክፍሌ ትገባና እንደ እብድ ትስመኛለች!
ከሚፈታተነኝ ስሜት ጋር እየታገልኩ እማማ አመለ እንዳይሰሙ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ፤ ፋኒ ግን መሳሳም ከጀመርን ነፍሷን አታውቅም፤ ማንም ቢመጣ ግድ አይሰጣትም፡፡
ማታ ማታ ቡናችን ላይ ስንቀመጥ ፋኒ ዓይኖቿን ከእኔ ላይ መንቀል አትችልም፤ በቃ ዓይኗ ቡዝዝ ብሎ ታየኛለች፡፡ አስተያየቷ ይጨንቀኛል፡፡ ፍቅርተ ድንገት ብትጠራጠር ብዬ እፈራለሁ፡፡
ደግነቱ ፍቅርተ ሳታቋርጥ ስለምታወራ ሁለታችንንም አትመለከተንም፡: ፋና ትምህርት ማጥናቷ ሁሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ በየምክንያቱ እኔ ክፍል መመላለስ ሆነ ስራዋ፡፡ መቸም እኔና ፋና ከዚህ በፊት እማማ አመለ አዕምሮ ውስጥ የፈጠርነው እምነት ረዳን እንጂ የፋና ባህሪ መቀየር፣ የሁለታችንን የፍቅር ግንኙነታችንን አፍ አውጥቶ የሚናገር ነበር፡፡ አንዳንድ ሰው አለ
መሃል ላይ መቆም የማይችል፣ ወይ ጥቅልል አድርጎ ራሱን ይሰጣል፣ አልያም ገና ከሩቁ ከሰው ይሸሻል ፋና እንደዛ ነበረች፡፡ ሙሉ እሷነቷን ለእኔ ስለሰጠችኝ ለምትሰራው ነገር ሁሉ ሌላ ሰው አልታይ አላት፡፡
የነፋና ኑሮ ሊገልፁት በማይችሉት ድህነት ውስጥ የተዘፈቀ ነበር፡፡ ባጭሩ ቤት ያላቸው የጎዳና
ተዳዳሪዎች ይመስሉኛል፡፡ አንዳንዴ እማማ አመለ የከሰል መግዣ ብር ያጡ ስለነበረ ከቤቷ
ጋር ተያይዛ የተሰራች በላስቲክ የተጋረደች ኩሽና ውስጥ ምናምኑን ጓድፈው ይማግዱና ቡና ያፈላሉ፡፡ ቡናው ታዲያ ጣዕሙ ጭስ ጭስ ይላል፡፡ እኔ ያን ያህል ብር ባይተርፈኝም አንዳንዴ ከቤተሰብ ሲላክልኝ ለፋና አልያም ለፍቅርተ ትንሽ ብር ልሰጣቸው እሞክራለሁ፡፡ ሁለቱም ቢሞቱ ብር ከእኔ አይቀበሉም፡፡ ብዙ ጊዜ ሞክሬ ሲቸከኝ መጠየቁንም ትቼዋለሁ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ፋና ወደ ክፍሌ ገባችና እየፈራች “አብርሽ ሰላሳ ብር አለህ ?” አለችኝ ፊቷ ላይ የነበረው ሀፍረት ያሳዝን ነበር፡፡ ደስ ብሎኝ ለፋና ድፍን ሃምሳ ብር ሰጠኋት፣ ደስ ብሏት እየተጣደፈች ወጣች፡፡
ፋና ወደ ማታ አንድ የተጠቀለለ ነገር ይዛ ወደ ክፍሌ ገባች፡፡ ፊቷ በደስታ ፈገግታ ተጥለቅልቋል፡
፡ ጥቅልሉን ፈታታችና አንድ ጥቁር የሴት ጅንስ ሱሪ አወጣች፣ “ለፍቅርዬ ገዛሁላት” አለችኝ፡፡
ሱሪውን ሳይሆን ፋና ፊት ላይ የነበረውን ፈገግታና ደስታ አይቼ መጥገብ አልቻልኩም፡፡ ፋና
እንደዚህ በደስታ ስትሰክር አይቻት አላውቅም፡፡
ትምህርት ቤታቸው ውስጥ በነበረ የስነተዋልዶ ስልጠና ላይ ተሳትፋ በተሰጣት አበል ከእኔ ሰላሳ
ብር ጨምራ ለፍቅርተ ይህን ሱሪ ገዛች፡፡ ፋና እንዲህ አይነት ልጅ ነበረች፡፡ ቁንጅናዋ የልብሷን
ተራነት ይሸፍነዋል እንጂ ለራሷ አንድም የረባ ልብስ የላትም፡፡ አዲሱን ሱሪ ይዛ ፍራሽ ጫፍ
ላይ ተቀመጠችና በጀርባዋ ተደገፈችኝ፡፡ የሆነ ርካታ ይነበብባት ነበር፡፡
“ፍቅርዬን እወዳታለሁ ከህፃንነታችን ጀምሮ ሁሉም ሰው እንደገፋት ነው የኖረችው፡፡ ሁልጊዜም ስለሷ እያሰብኩ እሰቃያለሁ፡፡“ አብርሽ ፍቅር እኮ እንደ መልኳ አይደለችም ደግ ነች፣ ጥሩ እህት፣ ጥሩ ጓደኛ ናት፡፡ ሁሉም ሰው ግን ይርቃታል” አለችና ማልቀስ ጀመረች፡፡ እንባዎቿን ጠረግኩላት፡፡ እንባዋ በንፁህ ጉንጮቿ ላይ ሲንኳለል መስተዋት ላይ የፈሰሰ ውሃ ይመስል ነበር፤ ጉንጯን ሳምኳት ፤ ወዲያው ግን በየት በኩል እንደተንሸራተትኩ እንጃ ከንፈራችን ተገናኘ፡፡ቅልጥ ያለ መሳሳም ውስጥ ገብተን ይሄን የዘቀጠ ኑሮ የጠቆረ ድህነት ለደቂቃዎች ተሰናበትነው።
ሱሪው ፍቅርተን ቀየራት፡፡ ስትለብሰው ዳሌዋን ሰፋ ኣድርጎ ወገቧን ሸንቀጥ ስላደረገው የፍቅርተ ቁንጅና መቃብሩን ፈንቅሎ ወጣ፡፡ ሱሪውን ስትለብስ አንድ የጥንካሬ መንፈስ የለበሰች ይመስል አስገራሚ በራስ መተማመን ይታይባታል፡፡ ጓደኞቿ ጋር መወጣት፣ አመሻሹ ላይ ከጎረቤት እኩዮቿ ጋር ተያይዛ መዞር ጀመረች፡፡ በዕርግጥም ሱሪው የሰውነቷን ቅርፅ ጎላ አድርጎ አሳምሯት ነበር፡፡ ይህንን አድናቆት ከአንዳንድ ወንዶች ጭምር እንደተቸራትም ፍቅርተ ራሷ በደስታ ለእኔና ለፉና እየነገረችን ስታስቀን ነበር፡፡ ልብስ መንፈስ ነው፡፡ ስጋን ሸፍኖ የስጋን ውበት የሚያጎላ መንፈስ፡፡ ይሄ መንፈስ ሱሪ ተመስሎ ፍቅርተ ላይ አርፎ ነበር ፡፡
የእነፉና ህይወት ከቀን ወደቀን ወደባሰ ድህነት እየተዘፈቀ ነበር የሚሄደው፡፡ እማማ አመለ አልፎ
አልፎ ልብስ ያጥቡላቸው የነበሩ የመንገድ ስራ ሙያተኞች ነበሩ፡፡ ከዛች የሚያገኟት ገቢ እኔ
በየወሩ ከምሰጣቸው የኪራይ ብር ጋር ተዳምራ ኑሯቸውን ስትደጉም ኖራለች፡፡ ታዲያ የመንገድ
ስራ ባለሙያዎቹ መንገዱን ሰርተው ስለጨረሱ የእማማ አመለም ገቢ ተቋረጠና ቤተሰቡ የባሰ ችግር ላይ ወደቀ፡፡ አንዳንድ ቀን የወትሮውን ቡና ማፍሊያ ብር ስለሚያጡ ሁላችንም በጊዜ
እንተኛለን፡፡ ቤቱ እንደ መቃብር ቤት ፀጥ ይላል፡፡ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በሰፈሩ
ለሚያልፈው መንገድ ግንባታ ቤታቸው በቅርቡ እንደሚፈርስ ለእማማ አመለ ተነገራቸው፡፡
እማማ አመለ ይህን መርዶ እንደሰሙ ሙሉ ቀን ታምመው ከአልጋቸው ሳይነሱ ዋሉ፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ፍቅርተ ትምህርቷን አቋርጣ ካፍቴሪያ በእቃ አጣቢነት ለመቀጠር መወሰኗን ለቤተሰቡ አሳወቀች፤ መርዶ ነበረ፡፡ እማማ አመለ እያለቀሱ እግሯ ላይ ወድቀው ለመኗት፡፡ ፋና ፊቷ ገርጥቶ እና አይኖቿ በእንባ ተሞልተው ዝም ብላ ፍቅርተን እና እናቷን ትመለከታለች፡፡በብዙ ልመና ፍቅርተ የዛን ቀን ትምህርት ቤት ሄደች፡፡ ፋና ፊቷ በሐዘን ድባብ ተውጦ ከወትሮ ዝምታዋ ሺ ጊዜ የገዘፈ ዝማታ ውስጥ ሰጥማ ዋለች፡፡ የዛን ጊዜ ፋና የአስራ ሁለተኛ ክፍል ፈተና ወስዳ ውጤት እየተጠባበቀች ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን ወደ ማታ ላይ ፋና ወደ ክፍሌ መጣች፡፡ አልሳመችኝም፣ ትክዝ ብላ ፍራሽ ጫፍ ላይ ተቀመጠችና “አብርሽ አረብ አገር ልላክሽ የሚለኝ የሆነ ጎረቤታችን አለ፣ ብዙ ልጆች ልኳል
እዚሁ እኛ ሰፈር ነው ተፈሪ የሚባለው ታውቀው የለ ?” አለችኝ፡፡
“እና…” አልኳት አሁኑኑ ብርር ብላ ትሄድብኝ ይመስል ስጋት ሁለመናዬን ወርሮት እጆቿን
በእጆቼ እየያዝኩ፡፡ ደንግጬ ነበር፣ መተንፈስ ሁሉ አቅቶኝ ነበር፡፡
“አይ ቢያንስ ፍቅር ትምህርቷን እስክትጨርስ ለሁለት ዓመት ሰርቼ ብመለስ ብዬ አሰብኩ፤
በዛ ላይ ይሄ ቤት ከፈረሰ የት እንወድቃለን ዘመድ የለን መጠጊያ” አለችኝ፡፡ ድንጋጤዬ
አስደንግጧት ሳይሆን አይቀርም ስትናገር ፈርታ ነበር፡፡
“አብደሻል ፋኒ…ምን ሰይጣን ነው ይሄን ያሳሰበሺ..እንዴት እንደዚህ አይነት መጥፎ ነገር ታስቢያለሽ” ጮህኩባት ::
“ኧረ እብርሽ ቀስ እማማ እንዳትሰማ አለችኝ በጭንቀት በአገጯ ወደዛንኛው ክፍል እየጠቆመች።
፡
፡
#አራት(መጨረሻ)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...ከፋና ጋር ከተሳሳምንባት ቅዳሜ በኋላ ዋና ስራችን የእማማ አመለ እና የፍቅርተ እግር
ሲወጣ መጠበቅ ሆነ..በቃ ወጣ ሲሉ ፋና ወደ ክፍሌ ሮጣ ትመጣና እቅፌ ላይ ናት፣ከንፈሮቻችን እንዳይገናኙ ማድረግ ከሁለታችንም አቅም በላይ ነበር፡፡ በፍቅር ሰከርን፤አንዳንዴ እማማ አመለ ቤት ውስጥ ሆነውም ፋና ተነስታ ወደ ክፍሌ ትገባለች፣“አብርሽ ስራ ይዘሃል እንዴ?” ትላለች፡፡እማማ አመለ ከትምህርት ጋር የተያያዘ ነገር አድርገው ስለሚያስቡት በጭራሽ አይጠራጠሩም፡፡ፋኒ ወደ ክፍሌ ትገባና እንደ እብድ ትስመኛለች!
ከሚፈታተነኝ ስሜት ጋር እየታገልኩ እማማ አመለ እንዳይሰሙ የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ፤ ፋኒ ግን መሳሳም ከጀመርን ነፍሷን አታውቅም፤ ማንም ቢመጣ ግድ አይሰጣትም፡፡
ማታ ማታ ቡናችን ላይ ስንቀመጥ ፋኒ ዓይኖቿን ከእኔ ላይ መንቀል አትችልም፤ በቃ ዓይኗ ቡዝዝ ብሎ ታየኛለች፡፡ አስተያየቷ ይጨንቀኛል፡፡ ፍቅርተ ድንገት ብትጠራጠር ብዬ እፈራለሁ፡፡
ደግነቱ ፍቅርተ ሳታቋርጥ ስለምታወራ ሁለታችንንም አትመለከተንም፡: ፋና ትምህርት ማጥናቷ ሁሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ በየምክንያቱ እኔ ክፍል መመላለስ ሆነ ስራዋ፡፡ መቸም እኔና ፋና ከዚህ በፊት እማማ አመለ አዕምሮ ውስጥ የፈጠርነው እምነት ረዳን እንጂ የፋና ባህሪ መቀየር፣ የሁለታችንን የፍቅር ግንኙነታችንን አፍ አውጥቶ የሚናገር ነበር፡፡ አንዳንድ ሰው አለ
መሃል ላይ መቆም የማይችል፣ ወይ ጥቅልል አድርጎ ራሱን ይሰጣል፣ አልያም ገና ከሩቁ ከሰው ይሸሻል ፋና እንደዛ ነበረች፡፡ ሙሉ እሷነቷን ለእኔ ስለሰጠችኝ ለምትሰራው ነገር ሁሉ ሌላ ሰው አልታይ አላት፡፡
የነፋና ኑሮ ሊገልፁት በማይችሉት ድህነት ውስጥ የተዘፈቀ ነበር፡፡ ባጭሩ ቤት ያላቸው የጎዳና
ተዳዳሪዎች ይመስሉኛል፡፡ አንዳንዴ እማማ አመለ የከሰል መግዣ ብር ያጡ ስለነበረ ከቤቷ
ጋር ተያይዛ የተሰራች በላስቲክ የተጋረደች ኩሽና ውስጥ ምናምኑን ጓድፈው ይማግዱና ቡና ያፈላሉ፡፡ ቡናው ታዲያ ጣዕሙ ጭስ ጭስ ይላል፡፡ እኔ ያን ያህል ብር ባይተርፈኝም አንዳንዴ ከቤተሰብ ሲላክልኝ ለፋና አልያም ለፍቅርተ ትንሽ ብር ልሰጣቸው እሞክራለሁ፡፡ ሁለቱም ቢሞቱ ብር ከእኔ አይቀበሉም፡፡ ብዙ ጊዜ ሞክሬ ሲቸከኝ መጠየቁንም ትቼዋለሁ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ፋና ወደ ክፍሌ ገባችና እየፈራች “አብርሽ ሰላሳ ብር አለህ ?” አለችኝ ፊቷ ላይ የነበረው ሀፍረት ያሳዝን ነበር፡፡ ደስ ብሎኝ ለፋና ድፍን ሃምሳ ብር ሰጠኋት፣ ደስ ብሏት እየተጣደፈች ወጣች፡፡
ፋና ወደ ማታ አንድ የተጠቀለለ ነገር ይዛ ወደ ክፍሌ ገባች፡፡ ፊቷ በደስታ ፈገግታ ተጥለቅልቋል፡
፡ ጥቅልሉን ፈታታችና አንድ ጥቁር የሴት ጅንስ ሱሪ አወጣች፣ “ለፍቅርዬ ገዛሁላት” አለችኝ፡፡
ሱሪውን ሳይሆን ፋና ፊት ላይ የነበረውን ፈገግታና ደስታ አይቼ መጥገብ አልቻልኩም፡፡ ፋና
እንደዚህ በደስታ ስትሰክር አይቻት አላውቅም፡፡
ትምህርት ቤታቸው ውስጥ በነበረ የስነተዋልዶ ስልጠና ላይ ተሳትፋ በተሰጣት አበል ከእኔ ሰላሳ
ብር ጨምራ ለፍቅርተ ይህን ሱሪ ገዛች፡፡ ፋና እንዲህ አይነት ልጅ ነበረች፡፡ ቁንጅናዋ የልብሷን
ተራነት ይሸፍነዋል እንጂ ለራሷ አንድም የረባ ልብስ የላትም፡፡ አዲሱን ሱሪ ይዛ ፍራሽ ጫፍ
ላይ ተቀመጠችና በጀርባዋ ተደገፈችኝ፡፡ የሆነ ርካታ ይነበብባት ነበር፡፡
“ፍቅርዬን እወዳታለሁ ከህፃንነታችን ጀምሮ ሁሉም ሰው እንደገፋት ነው የኖረችው፡፡ ሁልጊዜም ስለሷ እያሰብኩ እሰቃያለሁ፡፡“ አብርሽ ፍቅር እኮ እንደ መልኳ አይደለችም ደግ ነች፣ ጥሩ እህት፣ ጥሩ ጓደኛ ናት፡፡ ሁሉም ሰው ግን ይርቃታል” አለችና ማልቀስ ጀመረች፡፡ እንባዎቿን ጠረግኩላት፡፡ እንባዋ በንፁህ ጉንጮቿ ላይ ሲንኳለል መስተዋት ላይ የፈሰሰ ውሃ ይመስል ነበር፤ ጉንጯን ሳምኳት ፤ ወዲያው ግን በየት በኩል እንደተንሸራተትኩ እንጃ ከንፈራችን ተገናኘ፡፡ቅልጥ ያለ መሳሳም ውስጥ ገብተን ይሄን የዘቀጠ ኑሮ የጠቆረ ድህነት ለደቂቃዎች ተሰናበትነው።
ሱሪው ፍቅርተን ቀየራት፡፡ ስትለብሰው ዳሌዋን ሰፋ ኣድርጎ ወገቧን ሸንቀጥ ስላደረገው የፍቅርተ ቁንጅና መቃብሩን ፈንቅሎ ወጣ፡፡ ሱሪውን ስትለብስ አንድ የጥንካሬ መንፈስ የለበሰች ይመስል አስገራሚ በራስ መተማመን ይታይባታል፡፡ ጓደኞቿ ጋር መወጣት፣ አመሻሹ ላይ ከጎረቤት እኩዮቿ ጋር ተያይዛ መዞር ጀመረች፡፡ በዕርግጥም ሱሪው የሰውነቷን ቅርፅ ጎላ አድርጎ አሳምሯት ነበር፡፡ ይህንን አድናቆት ከአንዳንድ ወንዶች ጭምር እንደተቸራትም ፍቅርተ ራሷ በደስታ ለእኔና ለፉና እየነገረችን ስታስቀን ነበር፡፡ ልብስ መንፈስ ነው፡፡ ስጋን ሸፍኖ የስጋን ውበት የሚያጎላ መንፈስ፡፡ ይሄ መንፈስ ሱሪ ተመስሎ ፍቅርተ ላይ አርፎ ነበር ፡፡
የእነፉና ህይወት ከቀን ወደቀን ወደባሰ ድህነት እየተዘፈቀ ነበር የሚሄደው፡፡ እማማ አመለ አልፎ
አልፎ ልብስ ያጥቡላቸው የነበሩ የመንገድ ስራ ሙያተኞች ነበሩ፡፡ ከዛች የሚያገኟት ገቢ እኔ
በየወሩ ከምሰጣቸው የኪራይ ብር ጋር ተዳምራ ኑሯቸውን ስትደጉም ኖራለች፡፡ ታዲያ የመንገድ
ስራ ባለሙያዎቹ መንገዱን ሰርተው ስለጨረሱ የእማማ አመለም ገቢ ተቋረጠና ቤተሰቡ የባሰ ችግር ላይ ወደቀ፡፡ አንዳንድ ቀን የወትሮውን ቡና ማፍሊያ ብር ስለሚያጡ ሁላችንም በጊዜ
እንተኛለን፡፡ ቤቱ እንደ መቃብር ቤት ፀጥ ይላል፡፡ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በሰፈሩ
ለሚያልፈው መንገድ ግንባታ ቤታቸው በቅርቡ እንደሚፈርስ ለእማማ አመለ ተነገራቸው፡፡
እማማ አመለ ይህን መርዶ እንደሰሙ ሙሉ ቀን ታምመው ከአልጋቸው ሳይነሱ ዋሉ፡፡
አንድ ቀን ታዲያ ፍቅርተ ትምህርቷን አቋርጣ ካፍቴሪያ በእቃ አጣቢነት ለመቀጠር መወሰኗን ለቤተሰቡ አሳወቀች፤ መርዶ ነበረ፡፡ እማማ አመለ እያለቀሱ እግሯ ላይ ወድቀው ለመኗት፡፡ ፋና ፊቷ ገርጥቶ እና አይኖቿ በእንባ ተሞልተው ዝም ብላ ፍቅርተን እና እናቷን ትመለከታለች፡፡በብዙ ልመና ፍቅርተ የዛን ቀን ትምህርት ቤት ሄደች፡፡ ፋና ፊቷ በሐዘን ድባብ ተውጦ ከወትሮ ዝምታዋ ሺ ጊዜ የገዘፈ ዝማታ ውስጥ ሰጥማ ዋለች፡፡ የዛን ጊዜ ፋና የአስራ ሁለተኛ ክፍል ፈተና ወስዳ ውጤት እየተጠባበቀች ነበር፡፡
በቀጣዩ ቀን ወደ ማታ ላይ ፋና ወደ ክፍሌ መጣች፡፡ አልሳመችኝም፣ ትክዝ ብላ ፍራሽ ጫፍ ላይ ተቀመጠችና “አብርሽ አረብ አገር ልላክሽ የሚለኝ የሆነ ጎረቤታችን አለ፣ ብዙ ልጆች ልኳል
እዚሁ እኛ ሰፈር ነው ተፈሪ የሚባለው ታውቀው የለ ?” አለችኝ፡፡
“እና…” አልኳት አሁኑኑ ብርር ብላ ትሄድብኝ ይመስል ስጋት ሁለመናዬን ወርሮት እጆቿን
በእጆቼ እየያዝኩ፡፡ ደንግጬ ነበር፣ መተንፈስ ሁሉ አቅቶኝ ነበር፡፡
“አይ ቢያንስ ፍቅር ትምህርቷን እስክትጨርስ ለሁለት ዓመት ሰርቼ ብመለስ ብዬ አሰብኩ፤
በዛ ላይ ይሄ ቤት ከፈረሰ የት እንወድቃለን ዘመድ የለን መጠጊያ” አለችኝ፡፡ ድንጋጤዬ
አስደንግጧት ሳይሆን አይቀርም ስትናገር ፈርታ ነበር፡፡
“አብደሻል ፋኒ…ምን ሰይጣን ነው ይሄን ያሳሰበሺ..እንዴት እንደዚህ አይነት መጥፎ ነገር ታስቢያለሽ” ጮህኩባት ::
“ኧረ እብርሽ ቀስ እማማ እንዳትሰማ አለችኝ በጭንቀት በአገጯ ወደዛንኛው ክፍል እየጠቆመች።
👍26